headline
stringlengths
2
1.42k
category
stringclasses
6 values
date
stringlengths
9
35
views
stringlengths
1
7
article
stringlengths
63
36.2k
link
stringlengths
28
740
word_len
int64
16
6.74k
label
class label
6 classes
የኦሊምፒክ ማጣሪያ ተሳታፊዎች የሚለዩበት ቻምፒዮና እየተካሄደ ይገኛል
ስፖርት
January 14, 2021
2
ብርሃን ፈይሳየኢትዮጵያ ቦክስ ፌዴሬሽን በየዓመቱ የሚያዘጋጀው የክለቦች ቻምፒዮና በአዲስ አበባ ከተማ በመካሄድ ላይ ይገኛል። የተሻለ ብቃት ያሳዩ ቦክሰኞች ለቶኪዮ ኦሊምፒክ ማጣሪያ ተሳታፊ እንደሚሆኑም ታውቋል።በቦክስ ስፖርት ከሚካሄዱት ዓመታዊ ቻምፒዮናዎች መካከል አንዱ በክለቦች መካከል የሚካሄደው ነው፤ የዚህ ውድድር የመጀመሪያው ዙር በአዲስ አበባ ከተማ ተጀምሯል። የኢትዮጵያ ቦክስ ፌዴሬሽን ከአዲስ አበባ ቦክስ ፌዴሬሽን ጋር በመተባበር በተዘጋጀው በዚህ ቻምፒዮና፤ ከኮቪድ 19 ወረርሽኝ መከሰት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ የተካሄደ ውድድርም ነው። በውድድሩም ላይ አምስት ክለቦች ከአዲስ አበባ (ፌዴራልፖሊስ፣ ፌዴራል ማረሚያ ቤቶች፣ አዲስ አበባ ፖሊስ፣ የኢትዮጵያ ወጣቶች ስፖርት አካዳሚ እና ኦሞቲክ ቦክስ)፣ ሁለት ክለቦች ከአማራ ክልል (ጎንደር ከነማ እና ደሴ ከነማ) እንዲሁም ድሬዳዋ ከነማ በድምሩ ስምንት ክለቦች ተሳታፊ መሆናቸውን የኢትዮጵያ ቦክስ ፌዴሬሽን መረጃ ያሳያል። በአጠቃላይ ክለቦቻቸውን ወክለውም 12 ሴትና 76 ወንድ ቦክሰኞች በጥቅሉ 88 ተወዳዳሪዎች ተሳታፊ ይሆናሉ። ውድድሩ የሚካሄደው በራስ ኃይሉ ስፖርት ትምህርትና ስልጠና ማዕከል ሲሆን፤ በ10 ክብደቶች በ49፣ 52፣ 57፣ 60፣ 63፣ 69፣ 70፣ 81፣ 89 እና 91 ኪሎ ግራሞች እየተካሄደም ይገኛል። የቦክስ ስፖርት ከንክኪ ስፖርቶች መካከል አንዱ እንደመሆኑ ጨዋታው በሚካሄድበት ወቅት ቦክሰኞቹ አካላዊ ቅርርብ ሊያደርጉ እና ሊነካኩ ይችላሉ። በመሆኑም በዚህ ረገድ ውድድሩ ሙሉ ለሙሉ የኮቪድ 19 ጥንቃቄን በተላበሰ መልኩ እየተካሄደ መሆኑን ነው ፌዴሬሽኑ ያረጋገጠው። ይኸውም ተወዳዳሪዎችና አሰልጣኞች የኮቪድ ምርመራ እንዲያደርጉና ከሌሎች ሰዎች ጋር እንዳይገናኙ በካምፕ እንዲቆዩ በማድረግ ነው። ከዚህ ባሻገር ውድድር የሚደረግበት ሪንግ ቶሎ ቶሎ በኬሚካል እንዲጸዱ እንዲሁም ተመልካቾች ውድድሩ ላይ እንዳይገኙም ተደርጓል። ኮቪድ 19 ዓለም አቀፍ ወረርሽኝ እንደመሆኑ በመላው ዓለም ስፖርታዊ ውድድሮች ተቋርጠው መቆየታቸው የሚታወስ ነው። ከእነዚህ ውድድሮች መካከል ለቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ የቦክስ ስፖርት ማጣሪያ የሚካሄደው ውድድር ይጠቀሳል። ውድድሮች ወደ እንቅስቃሴ መግባታቸውን ተከትሎም ማጣሪያው የሚቀጥል ይሆናል። ኢትዮጵያም በዚህ ቻምፒዮና (በመጀመሪያው ዙር) የተሻለ ብቃት ያሳዩ ቦክሰኞችን በማጣሪያው የምታሳትፍ መሆኑ ታውቋል። ቻምፒዮናው አራት ዙሮች ያሉት ሲሆን፤ ሁለተኛው ዙር ከአማራ ክልል ቦክስ ፌዴሬሽን ጋር በመሆን ጎንደር ላይ፣ ሶስተኛውን ከደቡብ ክልል ቦክስ ፌዴሬሽን ጋር በመሆን ወላይታ እንዲሁም የመጨረሻውና የማጠቃለያው ውድድር አዲስ አበባ ላይ የሚካሄድም ይሆናል። ቻምፒዮናው ጥር 4/2013 ዓም የተጀመረ ሲሆን እስከ ጥር 7/2013 ዓም ድረስም ይቆያል።
https://www.press.et/Ama/?p=39481
298
2ስፖርት
አዲስ ዘመን ድሮ
መዝናኛ
December 28, 2020
4
 የአዲስ ዘመን ጋዜጣ ቀደምት ዘገባዎች በእጅጉ ተነባቢ ዛሬም ላገኛቸው በእጅጉ ተነባቢ ናቸው።እኛም ከእነዚህ ዘገባዎች ጋዜጣው በ1950ቹ ያስነበባቸውን ወጣ ያሉ ዘገባዎች ለዛሬ ይዘንላችሁ ቀርበናል። በዛሬው የአዲስ ዘመን ዱሮ አምዳችን አዲስ ዘመን ጋዜጣ በ1950ዎቹ ይዟቸው ከወጣ ዘገባዎች በአዘጋገባቸውና በይዘታቸው ተነባቢ ናቸው ያልናቸውን እና ሌሎች አስደናቂ ዘገባዎችን ይዘን ቀርበናል። ማገጃ ምልክት ይሰጠውማንኛውም የሥራ ድርጅት በብዙ ድካም ከተቋቋመ በኋላ አስፈላጊው ጥንቃቄ ካልተደረገለት የተሠራው እንዳልተሠራ የነበረው እንዳልነበር መሆኑ የማይጠረጠር ነው።በሲዳሞ ጠ/ግዛት ዋና ከተማ ይርጋዓለም የቴሌኮሙኒኬሽን ቦርድ ያቋቋመው ከፍተኛ መሥሪያ ቤት ይገኛል። የተቋቋመውም በትልቁ መኪና መንገድ አጠገብ ስለሆነ ፤ተሽከርካሪዎች የሚመላለሱበት ቦታ ነው።አንዳንድ ጊዜም ከባድ ጭነት የያዙ መኪናዎች ለምሳሌ አውቶቡስን የመሳሰሉት በሁለተኛው መንገድ እንዲያልፉ የሚታዘዙበት ቀን ስለሚያጋጥም በተጠቀሰው መሥሪያ ቤት አደባባይ የሚገኙትን ሽቦዎች ሳይመለከቱ ለማለፍ ሲሞክሩ በብዙ መጯጯህ ስልኩ ሽቦ ከመጣስ የዳነበትና መኪናውንም ለመመለስ የቻለበትን ጊዜ ለማታወስ የማይችል የለም፤ ታናናሽ መኪናዎችን ለማሳለፍ የቦታው ስፋት ይፈቅዳል።ስለ ታላላቅ መኪናዎች ግን የክፍሉ ባለሥልጣን የማገጃ ምልክት ቢያደርግበት የሚሻል መሆኑን አስታውሳለሁ። አቧራ አዋዜ አይደለም። በዚሁ ከተማ ትልቁን መንገድ በመከተል አልፎ አልፎ በሚገኙት ሰፈሮች ብዙዎች የልኳንዳ ሥጋ የተሰቀለባቸውና   ፉርኖ ይህንንም የመሳሰሉት ምግቦች የተደረደረባቸው ቤቶች ይገኛሉ። ሥጋው የሚገኝበት ብዙ ቦታ በረንዳ ስለሆነ ማናቸውም ተንቀሳቃሽና ይልቁንም በማይቋረጠው የመኪና ኃይል ከመንገዱ ላይ የሚነሳው አቧራ በሥጋውና በማናቸውም ምግብ ላይ ሲሰፍርበት ይታያል።ለማስረጃ ያህል በመንገዱ ዳር የሚገኘውን የቡና የሌላውንም ቅጠል የተመለከትን እንደሆነ በአንዱ ቅጠል ላይ ብቻ አንድ ጥርኝ የሚሞላ አቧራ ስለምናገኝ በየቀኑ በያንዳንዱ ብልት ሥጋ ላይ ተደባልቆ ወደ ሆድ የገባውን አቧራ ለመገመት እንችላለን። ስለዚህ ሥጋና ፉርኖ ይህንንም የመሳሰለ ምግብ የሚያሰናዱ ነጋዴዎች ለዚሁ አገልግሎት በዘመናዊ ዕቅድ በተሰናዳው መስታወት ውስጥ ማኖር ይገባቸዋል።ይህም ባይቻል አቧራ ወደሌለበት ሁለተኛው መንገድ እንዲዛወሩ ማድረግ ስለሚገባ ፤ሥራው የሚመለከተው ባለሥልጣን ያስብበት ዘንድ ሳስታውስ በትሕትና ነው። መመሳሰል ይገባዋልበዚሁ ከተማ የሚገኘው የጠቅላይ ግዛቱ በጅሮንድ ጽ/ቤት በሦስት ቦታ ተከፋፍሎ የሚገኝ ከመሆኑም በላይ ቤቱም በጠላት ጊዜ የተሠራ አሁን መፍረስ የጀመረ ነው።ስለ የውስጥ ዕቃውም አጠባበቅ ከቤቱ ይልቅ ዘበኞቹንና ካዝናውን ማመን ግድ ሳይሆን አይቀርም። ይኸውም ሆኖ ለሥራው የተመጠነ ስፋት ያለው አይደለም። በአካባቢው የሚገኙት ቢሮዎች በአማረና በጥሩ ሕንፃ የተሠሩ ሲሆኑ፤ የተጠቀሰው መሥሪያ ቤት እርጅና የእነሱን ውበት ግርማ አሳንሶታል።ስለዚህ ጓደኞቹን እንዲመስል የክፍሉ ባለሥልጣን ይተጋበት ዘንድ ማሳሰብ የጋዜጣው ፋንታ ነው። የሲዳሞ ጠ/ግዛት አዣንስ ኃይለ መስቀል ወልደየስ (የካቲት 20 ቀን 1951 የወጣው አዲስ ዘመን) ሁለት ወንዶች ልጆችእናት በአስር ቀን ልዩነት ሁለት ወንዶች ልጆች ወለደች። በወቅቱ ዜናው ጋዜጣችን ላይ ሲወጣ ርዕሰ ዜናው ከላይ እንደተጠቀሰው ሁለት ወንዶች ልጆች ብቻ ነበር የሚለው በሚከተለው መልኩ ተዘግቦ ስለነበር እንድታነቡት እንጋብዛለን። በደብረ ታቦር ከተማ ዙሪያ ቃናት ማርያም ከተባለው አገር የአቶ መኰንን ካሳ ባለቤት ያልጋነሽ አድማሱ የተባለችው ፤ጥር 22 ቀን 51ዓ.ም ከሌሌቱ 8 ሰዐት ሲሆን አንድ ወንድ ልጅ ከወለደች በኋላ 10 ቀን ቆይታ የካቲት 2 ቀን 1951 ዓ.ም ከጥዋቱ 1 ሰዐት ሲሆን አንድ ወንድ ልጅ ደግማ መውለዷንና ሁለቱም ልጆች እስካሁን በሕይወታቸው መኖራቸውን የነዚሁ ልጆች አባት አቶ መኰንን ካሳ አስታውቀውናል። የደብረ ታቦር ከተማው ዙሪያ ምክትል ገዥ ባላምባራስ ኃይሌ ታምራት በቁጥር100/1951የካቲት 10 ቀን በተጻፈ ደብዳቤ አረጋግጠውልናል።እኒህ የምክትል ወረዳ ገዥ እንደዚህ ያለው ሁኔታ በጋዜጣ እንዲገለጥ በቶሎ ለአውራጃው ግዛት አዣንስ ጽ/ቤት በማስተላለፋቸው እናመሰግናለን። ሌላዎችም ምክትል ገዥዎች የርሳቸውን አርአያ ተከትለው ይህን የመሰለ ጉዳይ ሲያጋጥማቸው በፍጥነት የሚያስታውቁን ቢሆን ከፍ ያለ ምስጋና የሚያገኙበት መሆኑን እንገልጻለን።የደብረ ታቦር አውራጃ አዣንስ አሰፋ ረታ (የካቲት 17 ቀን 1951 የወጣው አዲስ ዘመን)
https://www.press.et/Ama/?p=38334
475
1መዝናኛ
የአረንጓዴ ጎርፍ በጎ አድራጎት አምባሳደሮች ተሰየሙ
ስፖርት
January 6, 2021
6
ቦጋለ አበበየአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስፖርት ኮሚሽን ከኢትዮጵያ አረንጓዴ ጎርፍ የአትሌቲክስ የበጎ አድራጎት ድርጅት ጋር በመተባበር‹‹የገና በዓልን ከአንጋፋ አትሌቶች ጋር እናሳልፍ›› በሚል ትናንት በኢትዮጵያ ሆቴል በተዘጋጀው የእውቅናና የሽልማት መድረክ የበጎ አድራጎት ድርጅቱ ሁለት አምባሳደሮች ተሰይመዋል፡፡ በዚህም ከሴት ፈር ቀዳጇ የአንድ ሺ አምስት መቶ ሜትር የቀድሞ ኮከብ አትሌት ኮማንደር ቁጥሬ ዱለቻ የተሰየመች ሲሆን በወንድ ፋና ወጊው የኦሊምፒክ የሦስት ሺ ሜትር መሰናክል የነሐሴ ሜዳሊያ ባለቤትና የርቀቱ አሰልጣኝ ሻምበል እሸቱ ቱራ የዕውቅና አምባሳደርነት የምስክር ወረቀት ተበርክቶላቸዋል።አምባሳደሮቹ በተሰየሙበት መርሃግብር በህይወት ዘመናቸው ለኢትዮጵያ ስፖርት የላቀ አስተዋፅኦ ላበረከቱ ግለሰቦች የዕውቅናና የምስጋና ካባ እንዲሁም የምስክር ወረቀት ተበርክቶላቸዋል፡፡ አንጋፋው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ሐኪም ዶክተር አያሌው ጥላሁን እንዲሁም አንጋፋው የስፖርት ጋዜጠኛ ሰለሞን ገብረእግዚያብሔር የዕውቅናና የምስክር ወረቀት ከተቀበሉ በኋላ በሞሀ ለስላሳ መጠጦች እንዱስትሪ አክሲዮን ማህበር ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ጌታቸው ቢርቦ የክብር ካባ ተጠልቆላቸዋል፡፡ የኢትዮጵያ አረንጓዴ ጎርፍ አትሌቲክስ የበጎ አድራጎት ድርጅት መስራችና ዋና ስራ አስኪያጅ አትሌት መልካም ተገኝ፣ ‹‹መረዳዳት በህይወት›› በሚል ሀሳብ ለአገራቸው የሰሩ፣ የለፉ ፣ የደከሙና ለአገር ክብር የተጉ አትሌቶችንና ቀጣይ ተተኪዎችን በማንኛውም ማህበራዊ ህይወታቸው ለመታደግ በጎ አድራጎት ድርጅቱ መመስረቱን ጠቅሰው ለዚህ የተቀደሰ አላማ ሁሉም አካላት ትብብር እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል።የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስፖርት ኮሚሽነር በላይ ደጀን በበኩላቸው ‹‹መረዳዳት በህይወት›› የሚለው መሪ ቃል በጎ አድራጎት ድርጅቱን እንደሚወክል በመግለፅ፣ ለአገራቸው ክብር ፣ ህዝብና ባንዲራ የለፉ አንጋፋ አትሌቶችና ጋዜጠኞች እንዲሁም ሌሎች ባለሙያዎች በዚህ ደረጃ ዕውቅና ማግኘታቸው ተገቢ እንደሆነ አስረድተዋል፡፡ በቀጣይ በጎ አድራጎት ድርጅቱ የበለጠ ውጤታማ እንዲሆን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደርና የአዲስ አበባ ስፖርት ኮሚሽን በጋራ እንደሚሰሩም ቃል ገብተዋል፡፡ በክብር እንግድነት የተገኙት የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ዱቤ ጅሎ በበኩላቸው ይህን በጎ አላማ እውን ላደረጉና መርሃግብሩን ላዘጋጁና ለዚህ ያበቁ የአዲስ አበባ ስፖርት ኮሚሽን አመራሮችን አመስግነዋል። በርካታ አንጋፋ አትሌቶች በመርሃግብሩ ታድመውም የእውቅናና የምስክር ወረቀት ተቀብለዋል፡፡አዲስ ዘመን ታህሳስ 28/2013
https://www.press.et/Ama/?p=39010
265
2ስፖርት
የሊጉ በቢዝነስ ሞዴል መመራት አበረታች ጅምር መሆኑ ተገለጸ
ስፖርት
January 6, 2021
5
ብርሃን ፈይሳአዲስ አበባ፡- የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ በሼር ካምፓኒ እንዲተዳደር መደረጉና የቴሌቪዥን ሽፋን ማግኘቱ ለሌሎች ስፖርቶችም አበረታች ጅምር መሆኑ ተገለጸ። በብሄራዊ ስፖርት ምክር ቤት የ2013ዓም የስፖርት ዘርፍ አፈጻጸም ሰነድ ላይ እንደተመለከተው፤የሃገሪቷ ስፖርት በቢዝነስ ሞዴል እንዲመራ በማድረግ ረገድ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሪሚየር ሊጉን (ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ) በሼር ካምፓኒ እንዲመራ ማድረጉ መልካም ጅማሬ ነው። በአጭር ጊዜ ውስጥ የተደራጀው ካምፓኒው ውድድሩን የቴሌቪዥን መብት እንዲያገኝ እና የውድድር ስያሜውንም መሸጥ መቻሉ በስፖርት ላይ ትልቅ ተስፋን እና መነቃቃት ፈጥሯል። የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽነር ኤሊያስ ሽኩር፤ ሃገር አቀፍ የስፖርት ማህበራት ስፖርቱን በቢዝነስ ሞዴል ከመምራት አንጻር ሰፊ ስራ መሰራቱን ጠቅሰው፣ ለእዚህም በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የሊግ ካምፓኒው መቋቋም ተጠቃሽ መሆኑን አመላክተዋል። የውድድሩ መሸጥ በተለይ ክለቦች በገቢ ራሳቸውን እንዲችሉ የሚያደርግ፣ ለተጫዋቾችም መልካም ዕድል የፈጠረና የሃገርን ገጽታ ለመገንባት ትልቅ አስተዋጽኦ ያደረገ ነው ነው ያሉት ኮሚሽነሩ፣በተመሳሳይ የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብም ወደ አክሲዮን የተለወጠበት ሁኔታ ሌሎች ክለቦች ልምድ የሚወስዱበት ነው ብለዋል። ይህም በቢዝነስ ሞዴል ከመመራት አንጻር የተጀመሩ ስራዎች እንዳሉ ማሳያ መሆኑንም ጠቅሰዋል።የኢፌዴሪ ባህልና ቱሪዝም ሚኒስትር ዶክተር ሂሩት ካሳው በበኩላቸው፤ በዓመቱ (2012ዓም) የሊግ ኮሚቴ በመፍጠር እግር ኳስ የስፖርታዊ ጨዋነትና የስፖርት መርህን የሚያከብር ዘርፍ እንዲሆን መደረጉ መልካም መሆኑን ጠቁመዋል። የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብ ራሱን መቻልም ለሌሎች እንዴት ራስን በገቢ መቻል ይቻላል የሚለውን ያሳየ መሆኑን ተናግረው፣ ጥሩ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ጠቋሚ ነው ብለዋል። ይህንንም አጠናክሮና ተባብሮ ማስኬድ ከተቻለ በስፖርቱ የሚነሱ ጥያቄዎችና ችግሮች ይቀረፋሉ ሲሉም ተስፋቸውን አንጸባርቀዋል። ብሔራዊው የስፖርት ሪፎርም ክለቦችና የስፖርት ማህበራት በገቢ ራሳቸውን ችለው ከመንግስት ድጎማ እንዲላቀቁ እንዲሁም ሃብት እንዲያፈሩ ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን ያመላክታል። እንደ ኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን የአፈጻጸም ሪፖርት፤ መንግስት እስካሁን ከክልል እስከ ፌዴራል ባለው ደረጃ 163 ሚሊዮን 177ሺ 165 ብር ድጋፍ አድርጓል። ይህንን ለመቅረፍም ሃገር አቀፍ የስፖርት ማህበራት ያሉበት ሁኔታና ቁመና ለማወቅ ቅኝት በማድረግ ያሉበትን ደረጃ ለመለየት ጥረት ተደርጓል። የስፖርት ማህበራት ስፖርቱን በቢዝነስ ሞዴል በመምራት ከድጎማ የሚላቀቁበትና የራሳቸውን አቅም በማጎልበት የ10 ዓመቱን የስፖርት ልማት እቅድ ግቦች የሚያሳኩበትን ቁመና መፍጠርም በተያዘው ዓመት የኮሚሽኑ እቅድ መሆኑም ተጠቁሟል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 28/2013
https://www.press.et/Ama/?p=39011
296
2ስፖርት
የኦሊምፒክ ሥራ አስፈፃሚው እስከ ቶኪዮ ኦሊምፒክ ማግስት ይቀጥላል
ስፖርት
January 6, 2021
12
ቦጋለ አበበ የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ አርባ አምስተኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔ ባለፈው እሁድ በሐዋሳ ከተማ ሲያካሂድ የተለያዩ ውሳኔዎች ተላልፈዋል፡፡ ባለፉት አራት ዓመታት ሲያገለግል ቆይቶ ዘንድሮ ይጠናቀቅ የነበረው የኮሚቴው የስራ አስፈፃሚና የፕሬዚዳንት የስልጣን ዘመን በመጪው ክረምት እስከሚካሄደው የቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ ማግስት ድረስ እንዲቀጥል ጉባዔው ወስኗል፡፡ የቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ ባለፈው ዓመት ሊካሄድ የነበረ ቢሆንም በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ምክንያት ለአስራ ስድስት ወራት ተራዝሞ በመጪው ክረምት ሊካሄድ ቀን ተቆርጦለታል፡፡ ኮሚቴውን ሲመራ የነበረው ሥራ አስፈፃሚ በኦሊምፒኩ የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ የተለያዩ ዝግጅቶችን ሲያደርግ የቆየ ሲሆን ዘንድሮ የስራ ዘመኑን አጠናቆ በጠቅላላ ጉባዔ ምርጫ ይካሄድ ነበር፡፡ ይሁን እንጂ ኦሊምፒኩ በመራዘሙ ሲዘጋጅ የቆየው ስራ አስፈፃሚ የልፋቱን ውጤት እንዲመለከት እስከ ኦሊምፒኩ ማግስት እንዲቀጥል ጠቅላላ ጉባዔው ውሳኔ አስተላልፏል፡፡ ጉባዔውን በንግግር የከፈቱት የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ፕሬዚዳንት ዶክተር አሸብር ወልደጊዮርጊስ፣ ኢትዮጵያ የአኖካን ጉባኤ ባስተናገደችበት ማግስት አስረኛ ክልል ሆኖ እንደ አዲስ በተዋቀረው የሲዳማ ክልል ጉባዔው መካሄዱ ልዩ እንደሚያደርገው ገልፀዋል፡፡ ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ግዜ የአፍሪካ ወጣቶች ኦሊምፒክን በ2022 ለማስተናገድ እድል ባገኘችበት ማግስት በሲዳማ ክልል ዘንድሮ የኢትዮጵያ ወጣቶች ኦሊምፒክ ጨዋታ እንደሚካሄድም ጠቁመዋል፡፡ ኮሚቴው በቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ የአበበ ቢቂላን የ1964 የቶኪዮ ኦሊምፒክ ገድል ለመድገም በምትዘጋጅበት ወቅት ጉባዔውን ማካሄዱና በኮቪድ-19 ስጋት ውስጥ ሆኖ መከናወኑ ጉባዔውን የተለየ እንደሚያደርገውም ተናግረዋል፡፡ የባህልና ቱሪዝም ሚኒስትር ዶክተር ሂሩት ካሳው፣ ስፖርት የማህበራዊና ተፈጥሯዊ ሳይንስ ዘውግ መሆኑን ጠቅሰው ማህበራዊ ትስስርን በእጅጉ የሚፈጥር በመሆኑ ህብረተሰቡ ስፖርትን ባህሉ እንዲያደርግ የተጀመሩ እንቅስቃሴዎች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው መልዕክት አስተላልፈዋል። እስካሁን ድረስ በስፖርት ዘርፍ የተፈጠረው ተወዳዳሪነት ዝቅተኛ መሆኑን በመጥቀስም በአትሌትክስ ስፖርት ኢትዮጵያ ያስመዘገበችው ውጤት በሌሎችም እንዲደገም መሠራት እንዳለበት አብራርተዋል። ሚኒስትሯ የህብረተሰብ ስፖርትንም ለማስፋፋት በትምህርት ቤትና በስራ ቦታ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ላይ ትኩረት ተሰጥቶ መሠራት እንዳለበት ገልፀዋል። የኢፌዲሪ ስፖርት ኮሚሽን ኮሚሸነር ኤሊያስ ሽኩር በበኩላቸው፣ 45ኛው የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ የተካሄደው በስፖርት ህብረተሰቡ ዘንድ መነቃቃት በተፈጠረበት ወቅትና በብሔራዊ የስፖርት ምክር ቤት መደበኛ አንደኛ ስብሰባ ትላልቅ ውሳኔዎች በተላለፈበት ወቅት መሆኑን አስታውሰዋል፡፡ የአኖካ ጉባኤ በተሳካ ሁኔታ የተካሄደ መሆኑን ጠቅሰውም ሠላማዊና አስተማማኝ ሁኔታ በኢትዮጵያ መኖሩን አኖካ በማረጋገጡ ቀጣይ ስብሰባዎችን በራሱ ሙሉ ወጪ በኢትዮጵያ ለማካሄድ መነሳሳት እንዳሳየ አብራርተዋል። ለቶኪዮ 2020 የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ ዝግጅት ማድረግ በተጀመረበት ወቅት ላይ ጉባዔው በስፖርት ምክር ቤት በተቀመጡ ወሳኔዎችና አቅጣጫዎች መሠረት በጥልቀት መምከር እንዳለበት አስረድተዋል፡፡ ስፖርት ለሠላም፣ ለወዳጅነት፣ ለአንድነት፣ለወንድማማችነትና ለብልፅግና መሆኑን በመገንዘብ ጠቃሚ ውይይት እንዲደረግ አሳስበዋል፡፡ የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ፕሬዚዳንት አቶ ደስታ ሌዳሞ ጉባኤውን በንግግር የከፈቱ ሲሆን፣በዕለቱ በስፖርት ላይ በመስራት እውቅና ለተሰጣቸው ፈርጦች ምስጋና አቅርበዋል። በጉባኤው በስፖርት አመራርነት በፌደራልና በክልል ደረጃ አገልግሎት ሲሰጡ ቆይተው በአሁኑ ጊዜ በተለያዩ አመራር ቦታዎች ላይ ለሚገኙ አካላት የእውቅና ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።ከነዚህም መካከል የቀድሞ የወጣቶችና ስፖርት ሚኒስትር የነበሩትና በአሁኑ ወቅት የደቡብ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ ርስቱ ይርዳው፣ የቀድሞ ወጣቶችና ስፖርት ሚኒስትር ዴዔታ ወይዘሮ ሃቢባ ሲራጅ፣ የቀድሞ ወጣቶችና ስፖርት ሚኒስትር ዴዔታ የነበሩትና አሁን የደቡብ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ምክትል ፕሬዚዳንት በመሆን እያገለገሉ የሚገኙት አቶ ተስፋየ ይገዙ፣ የቀድሞ የኢፌዴሪ ምክትል ስፖርት ኮሚሽነርና አሁን የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት የኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ የሆኑት አቶ ጌታቸው ባልቻ የእውቅና ሽልማት ከተበረከተላቸው መካከል ዋነኞቹ ናቸው። ጠቅላላ ጉባዔው የ44ኛው መደበኛ ጉባኤ ቃለ ጉባኤ ፣ የ2012 ዓ.ም ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርትና የውጪ ኦዲተር ሪፖርት መርምሮ ያፀደቀ ሲሆን የ2013 ዓ.ም ዕቅድና የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ቀጣይ 46ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔን በተመለከተ መክሮ ውሳኔ አስተላልፏል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 28/2013
https://www.press.et/Ama/?p=39012
476
2ስፖርት
‹‹ሃገራዊ ችግሮችን ለማረምና አብሮነትን ለማጠናከር ስፖርት ወሳኝ ነው››- አቶ ደመቀ መኮንን የብሄራዊ ስፖርት ምክር ቤት ሰብሳቢ
ስፖርት
December 30, 2020
10
 ብርሃን ፈይሳ አዲስ አበባ፡- እንደ ሃገር እየታዩ ያሉትን ስብራቶችና ችግሮች ለማረምና የአብሮነትን ጉዞ ለማጠናከር ስፖርት ወሳኝ ሚና አለው ሲሉ የብሄራዊ ስፖርት ምክር ቤት ሰብሳቢ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን አስታወቁ። ለስፖርቱ ዘርፍ ተገቢው ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ ተጠቆመ። የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር የውጪ ጉዳይ ሚኒስትርና የብሄራዊ ስፖርት ምክር ቤት ሰብሳቢ ደመቀ መኮንን ትናንት የብሄራዊ ስፖርት ምክር ቤት የመጀመሪያ መደበኛ ጉባኤ በተካሄደበት ወቅት እንዳስታወቁት፤ ስፖርት የሰላምና የአብሮነት መሰረት፤ ሰላም ደግሞ ለስፖርት ሁነኛ ነባራዊ ሁኔታ ነው። በመሆኑም እንደ ሃገር ያሉትን ስብራቶችና በተለያየ መልክ የሚታዩ ችግሮችን ለማረምና የአብሮነት ጉዞን ለማጠናከር ስፖርት ወሳኝ ነው። አሁን ባለው ሃገራዊ ሁኔታ በጣም ብዙ ስብራቶች መኖራቸውን የምክር ቤቱ ሰብሳቢ ጠቅሰው፣ እነዚህን ከመጠገንና አብሮነትን ከማጠናከር አኳያ ስፖርት ሁነኛ መስተጋብር መሆኑን አመልክተዋል። የስፖርቱ መርሆዎች በአንድም ሆነ በሌላ መልክ በአስር ዓመት ሃገራዊ ዕቅድ መሪ ሃሳብ ውስጥ የተንጸባረቁ መሆናቸውን ተናግረው፣ ከየትኛውም ተቋም በላይ ሃገሪቷ በመጪዎቹ ዓመታት በሚሰራው ስራ አፍሪካዊ የብልጽግና ተምሳሌት ትሆናለች የሚል መሪ ሃሳብ ተይዟል ብለዋል። በዚህ ጭብጥ ውስጥም ዋና ዋና የስፖርት መርሆዎች ይገኛሉ ያሉት የምክር ቤት ሰብሳቢው፣ ‹‹የስፖርት መርሆዎች ከብልጽግና እንዲሁም የስፖርት መርሆዎች ከአብሮነት አኳያ፣ የስፖርት መርሆዎች በወንድማማችነት፣ በወዳጅነት፣ ጤናማ ማህበረሰብን በመፍጠር አብሮነትን የሚያስተሳስሩ እሴቶችን የተላበሱ ናቸው። በመሆኑም ለእዚህ ኢንዱስትሪ ትኩረት መስጠትና ማጠናከር ለራሳችንና ለሃገራችን ስንል ትውልዱ የሚታወቅባቸውን ስፖርቶች ለማስቀጠል ኃላፊነትና አደራም አለብን። የበለጠ ሆኖ ለመገኘት ስንልም በጣም መሰረታዊውንና ስፖርትን ከዚህ አኳያ ትርጉሙን ከፍ አድርጎ መመልከት ያሻል›› ሲሉም  አብራርተዋል። ስፖርት ተገቢው ትኩረት ሊሰጠው ይገባል የሚለው በምክር ቤቱ የተለመደ አባባል መሆኑን ጠቅሰው፣ ወደ ተግባር ተሟልቶ እስካልተገባ ድረስ አጉልቶ መያዝ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። ‹‹ታላላቅና የኩራታችን ምንጭ የሆኑ ስፖርተኞች በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅና እያስገኙ በመጡበት ሂደት አሁን ላይ ሆነን ሌጋሲውን እንዴት ማስቀጠል እንችላለን፤ ስፖርትስ እንዴት በሃገሪቷ ብልጽግና ጉዞ ውስጥ ሁነኛ ቦታ ይዞ ይሄዳል በሚለው ላይ ኃላፊነት አለብን›› ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ፣ ስፖርት በተወሰኑ አካላት ብቻ የሚታጠር መሆን እንደሌለበትም አስገንዝበዋል። ከታዳጊ ህጻናት እስከ ብሄራዊ እንዲሁም ዓለም አቀፍ ድረስ ተሳትፎ ማድረግ እንደሚገባም ሰብሳቢው አመላክተዋል።በብዙ ትውልዶችና በጀግኖች ጥረት ስፖርቱ ዓለም አቀፋዊ ሆኗል፤ እነዚህ ጀግኖችም ሃገራቸውንም አስተዋውቀዋል፤ አሁንም በብዙ መልኩ ስፖርቱ ዓለም አቀፋዊ መሆን ይኖርበታል፤ ለዚህ ደግሞ ምቹ ሁኔታ ያስፈልጋል፤ በተለይ በታዳጊ ህጻናት ላይ ከተሰራ መጪው ዘመን በስፖርት ያለውን አቅም ወደ ውጤት መመንዘር ያስችላል ብለዋል።አዲስ ዘመን ታኅሳስ 21/2013
https://www.press.et/Ama/?p=38512
336
2ስፖርት
በውድድር ወቅት በወረርሽኙ መከላከያ መመሪያዎች አተገባበር ላይ ስጋት እንዳለው ሚኒስቴሩ ጠቆመ
ስፖርት
December 30, 2020
3
ብርሃን ፈይሳ አዲስ አበባ፡- ስፖርታዊ እንቅስቃሴና ውድድሮች በሚከናወኑበት ወቅት የኮቪድ 19 ወረርሽኝን ለመከላከል የተቀመጡ መመሪያዎች አተገባበር ላይ ስጋት እንዳለው የኢፌዴሪ ጤና ሚኒስቴር አስታወቀ። የኢፌዴሪ ጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ ትናንት በተካሄደው በብሄራዊ የስፖርት ምክር ቤት ጠቅላላ ጉባኤ ላይ የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን በጤና ሚኒስትር እንዲሁም በባህልና ቱሪዝም ሚኒስትር የወጡ የኮቪድ 19 መከላከያ መመሪያዎችን ታሳቢ አድርጎ ውድድሮችንና እንቅስቃሴዎችን ለማከናወን ጥረት እየተደረገ መሆኑ መገለጹን አስታውቀው፣ የጤና ሚኒስቴር ግን በአተገባበሩ ላይ ስጋት እንዳለው ጠቁመዋል። በዚህ ወቅት የቫይረሱ ስርጭት ያለበት ምጣኔ ከ9-10 በመቶ ነው ያሉት ሚኒስትሯ፣ ከዚህ አኳያ ኢትዮጵያ የዓለም ጤና ድርጅት ከፍተኛ ስጋት አለባቸው በሚል ካስቀመጣቸው ሃገሮች ውስጥ ትመደባለች ብለዋል። መመሪያዎቹም ይህንን ተከትለው የወጡ መሆናቸውን ጠቅሰው፣ አተገባበራቸው ላይ ትኩረት ሊሰጥ እንደሚገባ አሳስበዋል። እንደ ዶክተር ሊያ ገለጻ፤ የኮቪድ 19 ወረርሽኝ ከተከሰተ ጀምሮ በስፖርት ዘርፍ ወረርሽኙን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የተወሰዱ እርምጃዎች በርካታና የሚያስመሰግኑ ናቸው። በማህበረሰቡ ዘንድ የሚታየው በሽታውን የማቃለል ሁኔታ የሚስተዋል ሲሆን፣ ይህም በሁሉም ዘርፍ እየታየ ይገኛል፤ ይህን ችግር ለመፍታት አመራሮች ትኩረት ሊሰጡ ይገባል። መመሪያውን መከተልና ውድድሮችን ያለተመልካች ማካሄድ ያስፈልጋል ሲሉም አስገንዝበዋል። ሚኒስቴሩ በዚህ በኩል ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን ጠቅሰው፣ ለእዚህም ከታላቁ ሩጫ አዘጋጆች ጋር እየተሰራ ያለውን በአብነት ጠቅሰዋል። ታላቁ ሩጫን ለማካሄድ በሚደረገው ዝግጅት ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከአዘጋጆቹ ጋር እየሰራ መሆኑንም ጠቅሰው፣ በውድድሩ የታቀደው ብዙ ቁጥር ያላቸው ተሳታፊዎችን ለማካተት መሆኑን አመልክተዋል። ይህን አሀዝ ለመቀነስ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል። ውድድሩን ከዚህ ቀደም ከነበረው ለየት ባለ ሁኔታ ለማድረግም ፈቃደኝነት እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። በአዲስ አበባ ያለው የወረርሽኝ መጠን በጣም ከፍተኛ የሚባል መሆኑን አመልክተው፣ መመሪያዎቹን ብቻ ማዘጋጀት ሳይሆን ለተግባራዊነቱም መስራት እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል።አዲስ ዘመን ታኅሳስ 21/2013
https://www.press.et/Ama/?p=38515
233
2ስፖርት
ስፖርትን ከፖለቲካ የመለየት ፈተናዎች
ስፖርት
December 31, 2020
11
ቦጋለ አበበ‹‹ስፖርትና ፖለቲካ አንድ ናቸው ወይም ጠንካራ ግንኙነት አላቸው›› ብለው የሚያምኑ በርካቶች የመሆናቸውን ያህል ‹‹ስፖርት ከፖለቲካ ነፃና ገለልተኛ ነው ወይም መሆን አለበት›› ብለው በምክንያት የሚሞግቱ ጥቂት አይደሉም።ከዚህ በተለየ መልኩ በዘመናዊው ዓለም ስፖርት የፖለቲካ መጠቀሚያ ዋነኛ መሳሪያ እየሆነ በመምጣቱ ነፃ ሊወጣ እንደሚገባ የሚሞግቱ አልጠፉም።እነዚህ ሞጋቾች ግን ስፖርትን ከፖለቲካ ሙሉ በሙሉ ነፃ ለማውጣት ወይም የመሰንጠቅ ፈተናዎች እንዳሉባቸው በርካታ ማሳያዎችን በመደርደር የሚከራከሩ የየዘርፎቹ ተንታኞች በዓለም ዙሪያ ድምፃቸውን ሲያሰሙ መገንዘብ ይቻላል።ባለፈው ዓመት በሞንቴ ካርሎ በተካሄደው ዓለም አቀፍ የሰላምና የስፖርት ኮንፍረንስ ላይ ስፖርትን ከፖለቲካ የመነጠል ጉዳይ ብዙ ክርክር አስነስቷል። ‹ስፖርትና ሰላም› በሚል እኤአ 2007 ላይ በፈረንሳዊው የቀድሞ አትሌትና የዓለም ኦሊምፒያኖች ማህበር ፕሬዝዳንት ጆኤል ቦዞ የተመሰረተው ተቋም በሞንቴ ካርሎ የተካሄደው የስፖርትና ሰላም ኮንፍረንስ አዘጋጅ ነበር።ይህ ተቋም ‹‹ቻምፒዮኖች ለሰላም›› በሚል መርህ የስፖርቱ ዓለም ከዋክብቶችን በአምባሳደርነት በመያዝ ተፅዕኖው ከዓመት ዓመት እየጨመረ ይገኛል። ኮትዲቯራዊው የእግር ኳስ ኮከብ ዲዲየር ድሮግባ፣ ሰርቢያዊው የሜዳ ቴኒስ ኮከብ ኖቫክ ጆኮቪችና እንግሊዛዊቷ ስመ ጥር አትሌት ፓውላ ራድክሊፍ ከዚህ ተቋም አምባሳደሮች መካከል ይገኙበታል።ተቋሙ በሚያዘጋጃቸው ኮንፍረንሶች የሰብዓዊ መብት ጉዳዮች፣ የፆታ እኩልነት፣ ስፖርትና ቴክኖሎጂ እንዲሁም ስደተኞችና የበጎ አድራጎት ስራዎች አጀንዳ ሆነው ይነሳሉ።ከዓለም ዙሪያ በርካታ ባለሙያዎች፣ የዓለም አቀፍ ስፖርት ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንቶችና ተወካዮቻቸው እንዲሁም መንግስታዊ ያልሆኑ ዓለም አቀፍ ተቋማት ኮንፍረንሱ ላይ ተገኝተውም በአጀንዳዎቹ ላይ ይወያያሉ።ስፖርትን ከየትኛውም አይነት የፖለቲካ ተፅዕኖ ነፃ ማድረግ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ በሚደረጉ ሰፊ ውይይቶች ቀልብ ከመሳባቸው ባሻገር መደምደሚያ ያልተበጀላቸው አጀንዳዎች ስፍር ቁጥር የላቸውም።የስፖርትና ሰላም ተቋም መስራቹ ቦዞ ስፖርትን ከፖለቲካ ተፅዕኖ መነጠል በሚቻልበት አከራካሪ ሁኔታ ላይ በሰጠው አስተያየት ‹‹ሁል ጊዜም ቢሆን የስፖርትን ገለልተኝነት እናከብራለን፣ ስፖርት ከሰላም ጋር እንዲቆራኝም ምክኒያታዊ ሆነን እንሰራለን›› በማለት ይናገራል።ቦዞ ስፖርት ከተለመደው ፖለቲካ ነፃ እንደሆነ በማመን ተቋሙ ስፖርትን ከፖለቲካ ጋር በማይገናኝበት በማንኛውም ሁኔታ ከተለያዩ አካላት ጋር ለመስራት ጥረት እንደሚያደርግም ያስረዳል።ይህም በየትኛውም የዓለም ክፍል ከሚገኝ አገር ጋር በመስራት የስፖርትን ዓለም አቀፋዊነት እስከ ማረጋገጥ እንደሚደርስ እምነቱ ነው።የዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ስራ አስፈፃሚዎች በቅርቡ በሉዛን ባደረጉት ስብሰባ አትሌቶች የኦሊምፒክ መድረክ ላይ በፍፁም የፖለቲካ ተቃውሞ፣ የሐይማኖትና የዘረኝነት መልዕክት ማስተላለፍ እንደሌለባቸው ውሳኔ ላይ መድረሳቸው ይታወሳል። የኮሚቴው ፕሬዝዳንት ቶማስ ባኽ በቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ አትሌቶች የትኛውንም አይነት የፖለቲካ፣ የሐይማኖት፣ የዘርና መሰል ተቃውሞና መልዕክት እንዳያስተላልፉ ማሳሰቢያ መስጠታቸውን ተከትሎም ስፖርት ከፖለቲካ ነፃ መሆን አለበት የለበትም? የሚሉ ሙግቶች ፍጥጫ ፈጥረዋል። በኦሊምፒኩ ወቅት በየትኛውም ስፍራ አትሌቶች ለተፎካካሪዎቻቸው ክብር ማሳየት እንዳለባቸውም ፕሬዝዳንቱ ደጋግመው ሲናገሩ ይደመጣል። ቶማስ ባኽ ስፖርትን የፖለቲካ መጠቀሚያ የማድረግ አዝማሚያ እየሰፋ በመጣበት በዚህ ወቅት በኦሊምፒክ መድረክ አላስፈላጊ መልዕክቶችን ማስተላለፍ ምንም ጥቅም እንደሌለውና የዓለምን ሕዝቦች ከመነጣጠል የዘለለ ፋይዳ እንደማይኖረው ያምናሉ። ‹‹የኦሊምፒክ መድረክ ዓለም አቀፋዊ ይዘት ያለው አትሌቶች ስፖርታዊ ብቃታቸውን የሚያሳዩበት እንጂ የፖለቲካ ወይም ሌላ ፕሮፓጋንዳ የሚያስተላልፉበት አይደለም›› የሚሉት ቶማስ ባኽ፣ ስፖርትን የፖለቲካ መጠቀሚያ ለማድረግ የሚደረገውን ጥረት ለመታገል በመድረኩ እንደዚህ አይነት ማሳሰቢያዎችን ቀድሞ ማሳወቅ እንደሚገባ ይናገራሉ።የዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ የአትሌቶች ኮሚሽን ሊቀመንበር ኪርስቴይ ኮቬንትሪ ከዓመት በፊት በርካታ አትሌቶች ኦሊምፒክ መድረክ ላይ የፖለቲካ ተቃውሞ ለማድረግ ተገቢው ቦታ መሆኑን እንደሚያምኑ በመናገር የአትሌቶቹን ሃሳብ መደገፋቸው በዓለም አቀፉ ኮሚቴ ውስጥ የተከፋፈለ ሃሳብ እንዳለ አሳይተዋል። ይህንንም ተከትሎ አትሌቶች በኦሊምፒክ መድረክ የፖለቲካ ተቃውሞ ማድረግ፣ የሐይማኖትና የዘረኝነት መልዕክት ማስተላለፍ አለባቸው የለባቸውም የሚለው ሃሳብ አከራካሪ ሆኖ ቆይቷል፡፡የዓለም መንግስታት ስፖርትን ለፖለቲካ መጠቀሚያ የሚያደርጉበት አጋጣሚ እንዳለ ሁሉ ከፖለቲካው ትርፍ ጎን ለጎን በማወቅም ይሁን ባለማወቅ ከሰላም ጋር ተያይዞ ለአገርና ለሕዝብ የሚጠቅሙ ክስተቶች ሲፈጠሩ ይታያል።ለአብነት ያህል የቦስኒያና ሄርዝጎቪኒያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ከዓመት በፊት በሳራጄቮና ምስራቅ ሳራጄቮ ከተሞች የአውሮፓን ወጣቶች ኦሊምፒክ በጥምረት በማዘጋጀት ተሸላሚ ሆነዋል። ይህም እኤአ ከ1992 እስከ 1995 በቦስኒያ ተካሂዶ ከነበረው ደም አፋሳሽ ጦርነት ወዲህ ሁለቱ የተከፋፈሉ አገራት የዲፕሎማሲ ግንኙነት እንዲሻሻል አድርጓል።በሌላ መልኩ የወርልድ ቴኳንዶና ኢንተርናሽናል ቴኳንዶ ፌዴሬሽኖች በግልፅ የሚታወቅ የተቀናቃኝነት ታሪክ ቢኖራቸውም ጥቂት ልዩነቶቻቸውን ወደ ጎን ትተው ውድድሮችን አንድ ላይ ያካሄዱበት አጋጣሚ ከስፖርትም የዘለለ ትርጉም ነበረው።ወርልድ ቴኳንዶ መሰረቱን በደቡብ ኮሪያ ሲዎል ከተማ ያደረገ ሲሆን ኢንተርናሽናል ቴኳንዶ መሰረቱ የሰሜን ኮሪያ ነው። ሁለቱ አካላት መቀመጫቸው በአውስትራሊያ ቬና ቢሆንም ሰሜን ኮሪያና ደቡብ ኮሪያን የመሰንጠቅ አቅም እንደነበራቸው ይታወቃል። በተመሳሳይ እንደ ጠላት የሚተያዩት ሰሜን ኮሪያና ደቡብ ኮሪያ ጉዳይ እስካሁን መቋጫ ያላገኘ ቢሆንም በ2018 የፒዮንግያንግ የበጋ ኦሊምፒክ የሁለቱ አገራት የሴቶች የሆኪ ስፖርት ቡድኖች አንድ ሆነው በመድረኩ መሳተፋቸው በሁለቱ አገራት መካከል የነበረውን የፖለቲካ ውጥረት ወደ ተሻለ የዲፕሎማሲ ደረጃ ያሸጋገረ ነበር። ከዚህ ኩነት አኳያ ፖለቲካና ስፖርትን ሙሉ በሙሉ እንዴት መነጠል እንደሚቻል ግልፅ እንዳልሆነ ብዙዎች ይስማማሉ።ስፖርትን ለሰላም መጠቀም ማንም የሚቃወመው ጉዳይ እንዳልሆነ ሁሉ በስፖርት ሽፋን የማይሆን የፖለቲካ ትርፍ ማጋበሻ የማዋል አዝማሚያም በተለያዩ አገራት ይስተዋላል።ዓለም አቀፋዊ ውድድሮችን ማዘጋጀት የሁሉም አገራት መንግስታት ፍላጎት የሚሆነው በዋናነት የአገርን ገፅታ ለመገንባት በማሰብ ነው። አምባገነን መንግስታት ይህን በመጠቀም የአገራቸውን የፖለቲካ ገፅታ ለመቀየር ሲሞክሩ ግን ይታያል።ለዚህ በርካታ ምሳሌዎችን መጥቀስም ይቻላል።በቅርቡ እንግሊዛዊው ቦክሰኛ አንቶኒ ጆሹአ ከሜክሲኳዊው ቦክሰኛ አንዲ ሩይዝ ጋር በሳውዲ አረቢያ ያደረገው የክፍለ ዘመኑ ምርጥ የተባለለት ግጥሚያ መነጋገሪያ ነበር።ሳውዲ አረቢያ በሰብዓዊ መብት አያያዝ ተወቃሽ አገር ከመሆኗ ባሻገር ከዓመት በፊት ቱርክ ኢስታንቡል በሚገኘው ኤምባሲዋ የተገደለው ጋዜጠኛ ጀማል ካሾጊ ጉዳይ አሁንም ድረስ መነጋገሪያ ነው።ያም ሆኖ ቦክሰኛው ጆሹአ በሳውዲ አረቢያው የቡጢ ፍልሚያ ወቅት የጀማል ካሾጊን ግድያ አዘዋል በሚል ሲ አይ ኤ ከፈረጃቸው የሳውዲው ልዑል ሞሐመድ ቢን ሳልማን ጋር ፎቶ በመነሳት በማህበራዊ መገናኛዎች መልቀቁ ውድድሩ በሳውዲ ከመካሄዱ በበለጠ ብዙ ቁጣን የቀሰቀሰ ነበር።ከዓመት በፊት ሁለተኛው የአውሮፓ ጨዋታዎች በቤላሩስ መዲና ሚኒስክ መካሄዱ ይታወሳል።ከአራት ዓመት በፊትም ይህ ውድድር በአዘርባጃን መዲና ባኩ ተካሂዶ ነበር።በሩሲያ የ2018 የዓለም ዋንጫን ጨምሮ በርካታ ዓለም አቀፍ ውድድሮች ተካሂደዋል።በነዚህ አገራት የተጋነነ ባይሆንም ከሰብዓዊ መብት አያያዝ ጋር በተገናኘ ጥያቄዎች የሚነሱ በመሆናቸው አገራቱ ስፖርትን ለፖለቲካ ገፅታ መገንቢያነት ተጠቅመውታል የሚል ወቀሳ ይነሳል።ወደፊትም ቤጂንግ 2022 የበጋ ኦሊምፒክን የምታዘጋጅ ከተማ እንደመሆኗ በቻይና ሰሜን ምዕራብ ክፍል በዢንጃንግ የሚኖሩ የሙስሊም ማህበረሰቦች ላይ ከሚደርሰው የሰብዓዊ መብት ረገጣ ጋር ተያይዞ አወዛጋቢ ነገሮች መፈጠራቸው እንደማይቀር ተንታኞች ከወዲሁ ስጋታቸውን ይገልፃሉ። በተመሳሳይ ዓመት ከዚሁ ከሰብዓዊ መብት አያያዝ ጋር የምትታማው ኳታር የዓለም ዋንጫን ታስተናግዳለች። ሚድል ኢስተርን ኒውስ የተባለ ተቋም ያወጣው ሪፖርት እንደሚያመለክተው 1400 ስደተኞች ኳታር በምታስገነባቸው ስቴድየሞች ስራ ላይ እያሉ በችልተኝነት ሕይወታቸው አልፏል። ኳታር ምናልባት የተሳካ የዓለም ዋንጫ ካስተናገደች ግን ይህ ሁሉ ሊረሳ ይችላል።ኳታር ከሰብዓዊ መብት አያያዝ ጋር በተገናኘ በዓለም አቀፉ ማሕበረሰብ ዘንድ የጎደፈ ስሟንና ገፅታዋን ለመገንባት ታላላቅ ስፖርታዊ ውድድሮች በስፋት እያዘጋጀች የምትገኝ ሲሆን፣ የአገሪቱ ባለሃብቶችና መንግስት በአውሮፓ ታላላቅ ሊጎች ክለቦችን ከፍተኛ ገንዘብ በማውጣት ሲገዙ ማየት እየተለመደ መጥቷል።አገሪቱ እኤአ የ2027 መላው ኤሽያ ጨዋታዎችን ለማዘጋጀት ከሌሎች የአካባቢው አገራት ጋር ጨረታ ውስጥ የገባች ሲሆን ይህንኑ ውድድር ከሦስት ዓመታት በኋላ በ2030 ለማዘጋጀት ፅኑ ፍላጎት እንዳላት መግለጿ ይታወቃል።ይህንንም የዲፕሎማሲ ቀውስ ውስጥ ከገባችው ጎረቤቷ ሳውዲ አረቢያ ጋር ጡንቻ ለመለካካት ያደረገችው እንደሆነ ተቺዎቿ ደጋግመው ያነሱታል፡፡ሳውዲ አረቢያና ኳታር የ2030 የመላው ኤሽያ ጨዋታዎችን ለማዘጋጀት ጨረታ ውስጥ ከገቡ በኋላ የዓለም አቀፉ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ለኤሽያ ኦሊምፒክ ምክር ቤት አገራቱ በሰብዓዊ መብት ላይ ያላቸውን መጥፎ ስም በተግባር አሻሽለው እስካልተገኙ ክልከላ እንዲያደርግ መጠየቁ ይታወቃል፡፡ከወር በፊት ኳታር ይህን ውድድር ማስተናገድ የአገሪቱ ቀዳሚ ትኩረት መሆኑን የገለፀች ሲሆን ዋነኛ ተቀናቃኟ የሆነው የሪያድ መንግስትም ለጉዳዩ ትኩረት ሰጥቶ እየተንቀሳቀሰ መሆኑን ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን ትኩረት ሰጥተው ሲዘግቡ ቆይተዋል። በነዳጅ ሃብት የበለፀጉት ሁለቱ የመካከለኛው ምስራቅ አገራት የዲፕሎማሲ ቀውስ ውስጥ መግባታቸውን ተከትሎ ድንበሮቻቸውን የዘጉ ቢሆንም ከአስር ዓመታት በኋላ የሚካሄድ የስፖርት ውድድርን ጡንቻ መለካኪያ ማድረጋቸው ትዝብት ላይ ጥሏቸዋል፡፡የኤሽያ ኦሊምፒክ ምክር ቤት ከሳምንት በፊት በሙስካት ባደረገው ጠቅላላ ጉባዔ የሁለቱን አገራት ውድድር የማዘጋጀት ፉክክር ምላሽ ለመስጠት መፍትሄ ያለውን ውሳኔ ማሳለፉ ይታወሳል። በዚህም ዶሃ የ2030ን መላ ኤሽያ ጨዋታ እንድታዘጋጅ የወሰነ ሲሆን ከአራት ዓመት በኋላ በ2034 የሚካሄደውን ተመሳሳይ ውድድር ሪያድ እንድታዘጋጅ መርጧል። እዚህ ውሳኔ ላይ ለመድረስ የኤሽያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ፕሬዘዳንት ሼክ አሕመድ አል ፋሃድ አል ሳባህ፣ ሁለቱንም አገራት ሊያስማማ ይችላል ብለው ባሰቡት መንገድ መሰረት በጠቅላላ ጉባዔው ብዙ ድምፅ ያገኘ አገር ቀድሞ ውድድሩን እንዲያዘጋጅ ማድረጋቸው ታውቋል። ውሳኔው ሁለቱን አገራት ያስማማል ተብሎ ቢታመንበትም በምርጫ ወቅት በተፈጠረ የቴክኒክ እክል ድራማ ሳይሰራ እንዳልቀረ መረጃዎች መጠቆማቸው ይታወቃል፡፡ዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ የዓለም መንግስታት በስፖርት ውስጥ እጃቸውን እንዳያስገቡ ፍላጎቱን ከመግለፁ ባሻገር አገራት በበጎም ይሁን በመጥፎ ጎኑ ስፖርትን እንዴት የፖለቲካ መጠቀሚያ ከማድረግ እንደሚቆጠቡ ያስቀመጠው ግልፅ አቅጣጫ የለም። ወይም መንግስታት ለፖለቲካ ፍጆታ እጃቸውን ከስፖርት በምን መልኩ መሰብሰብ እንዳለባቸው የመቆጣጠሪያ ቁልፉን ያገኘ አይመስልም። በዓለም አቀፍ መድረኮች በሚሊየን የሚቆጠሩ አትሌቶችም ቢሆኑ እንደየአመለካከታቸው የፖለቲካ፣ የሐይማኖትና የዘረኝነት መልዕክትን ከማስተላለፍ የሚቆጠቡበትን መንገድ ለመቆጣጠር እንደሚከብደው የበርካቶች እምነት ነው።
https://www.press.et/Ama/?p=38578
1,179
2ስፖርት
የዓለም አትሌቲክስና 2020 የውድድር ዓመት
ስፖርት
January 1, 2021
10
ቦጋለ አበበ በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ምክንያት የዓለም ማህበራዊ፣ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ገፅታ ዝብርቅርቁ በወጣበት የፈረንጆች 2020 ዓመት የዓለም ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎችም ቀላል የማይባል አሉታዊ ተፅዕኖ አርፎባቸዋል። ኦሊምፒክን ጨምሮ ታላላቅ ዓለም አቀፋዊና የአገር ውስጥ ስፖርታዊ ውድድሮች በተሰረዙበትና በተራዘሙበት የውድድር ዓመት የአትሌቲክስ ስፖርት በርካታ ፈተናዎችን ማሳለፉ ይታወቃል። በዓለም ሕዝብ ዘንድ ጥሩ ትውስታን ጥሎ ያላለፈው 2020 ተሸኝቶ ዛሬ በ2021 የውድድር ዓመት አንድ ብሎ የሚጀምርበት ቀን ነው። በአብዛኛው መጥፎ ትዝታውን ጥሎ ባለፈው ዓመት የአትሌቲክሱ ዓለም በርካታ አሉታዊ ተጽእኖዎች አርፈውበታል፤ በርካታ አዎንታዊ ክስተቶችንም አስተናግዷል። ከእነዚህ መካከልም አበይት ክስተት የሆኑት እንደሚከተለው ተዳሰዋል። ጥር የ2020 የውድድር ዓመት በጀመረበት ታህሳስ መጨረሻና ጥር ወር ላይ የአትሌቲክሱ ዓለም በርካታ የዓለም ክብረወሰኖችን አስተናግዷል። ኬንያዊው አትሌት ሮኔክስ ኪፕሩቶ የአስር ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ የዓለም ክብረወሰንን ቫሌንሲያ ላይ 26፡24 በሆነ ሰዓት ያስመዘገበው በዚህ ወር ሲሆን፣ ሌላኛዋ ኬንያዊት ሼላ ቺፕኪሩይ በተመሳሳይ ውድድር የሴቶቹን የዓለም ከገጽ 46 የዞረክብረወሰን 29፡46 በሆነ ሰዓት በማሻሻል የውድድር ዓመቱን በስኬት ጀምራለች። በዚሁ ወር የማራቶን ቁጥር አንድና ቁጥር ሁለት የሆኑት ኢትዮጵያዊና ኬንያዊ አትሌቶች ቀነኒሳ በቀለና ኢሉድ ኪፕቾጌ በለንደን ማራቶን እንደሚፋለሙ ይፋ መደረጉም የውድድር ዓመቱ ትልቅ ክስተት ነበር። ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በየዓመቱ የሚደምቁበት የዱባይ ማራቶን በውድድሩ ለመጀመሪያ ጊዜ የተሳተፈው ኦሊካ አዱኛ አሸናፊ ሲሆን፣ በሴቶች ወርቅነሽ ደገፋ የኢትዮጵያውያንን የተለመደ ድል ማስቀጠል ችላለች። በቻይና ናጂንግ ባለፈው መጋቢት ወር ሊካሄድ ቀጠሮ የተያዘለት የዓለም አትሌቲክስ የቤት ውስጥ ቻምፒዮና መራዘሙ የተሰማው በዚሁ ወር ነበር፤ ይህ ወድድር በኮቪድ-19 ስጋት የተራዘመ የመጀመሪያው ዓለም አቀፍ ውድድርም ሆኗል። የካቲት ያለፈው የካቲት ወርም በዓለም አትሌቲከስ የተለያዩ የዓለም ክብረወሰኖች የተሻሻሉበት ሆኖ ይታወሳል። በተለይም ስዊድናዊው ምርኩዝ ዘላይ ሞንዶ ዱፕሌንቲስ 2014 ላይ በፈረንሳዊው ሪናውድ ላቪሌኒ ተይዞ የቆየውን የዓለም ክብረሰወን 6 ነጥብ 17 ሜትር በመዝለል በአንድ ሴንቲሜትር ያሻሻለበት አጋጣሚ ትልቁ ክስተት ነበር። ላቪሌኒ በተመሳሳይ ወር ግላስጎ ላይ 6 ነጥብ 18 ሜትር በመዝለልም ተጨማሪ የዓለም ክብረወሰን በአንድ ወር ውስጥ ያሻሻለበት አጋጣሚ የሚዘነጋ አይደለም። የውድድር ዓመቱን በበርካታ የዓለም ክብረወሰኖች ታጅቦ ያጠናቀቀው ዩጋንዳዊው አትሌት ጆሽዋ ቺፕቴጌ የዓመቱን የስኬት ጉዞ ሞናኮ ላይ የአምስት ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ የዓለም ክብረወሰንን 12፡51 በሆነ ሰዓት በማሻሻል የጀመረው በዚሁ የካቲት ወር ነበር። ኢትዮጵያዊቷ አትሌት አባብል የሻነህ የግማሽ ማራቶን የዓለም ክብረወሰንን በተባበሩት አረብ ኢሚሬቶች ራስ አል ካይማህ 64፡31 በሆነ ሰዓት ያሻሻለችበትም አጋጣሚ በጉልህ የሚጠቀስ ነው። ቬንዙዌላዊቷ ስሉስ ዘላይ ዩሊማር ሮጃስ በማድሪድ በተካሄደው የቤት ውስጥ ውድድር ለአስራ ስድስት ዓመታት በታትያና ሌቢዴቫ ተይዞ የቆየውን የዓለም ክብረወሰን 15 ነጥብ 43 ሜትር በመዝለል ያሻሻለችበት አጋጣሚም ይታወሳል። መጋቢት የውድድር ዓመቱ ሦስተኛ ወር በሆነው መጋቢት ሕዝብ ባልተሳተፈበት የቶኪዮ ማራቶን ብርሃኑ ለገሰ ባለድል የሆነበት አጋጣሚ ሳይጠቀስ አይታለፍም። ቀነኒሳ በቀለም በለንደን ግማሽ ማራቶን አስደናቂ ብቃት አሳይቶያሸነፈበት ውድድርም አይዘነጋም። በዚህ ወር የኮቪድ-19 ስርጭት እየተስፋፋ መሄዱን ተከትሎ የዓለም ግማሽ ማራቶን ቻምፒዮናም የመራዘም ዕድል ገጥሞታል። በተመሳሳይ ታላላቅ የሚባሉት የለንደንና የቦስተን ማራቶን ውድድሮችም በዚሁ የካቲት ወር እንደተራዘሙ ታውቋል። እንዲካሄድ በርካታ ጥረቶች ሲደረጉ ከቆዩ በኋላ የውድድር ዓመቱ ታላቅ የስፖርት መድረክ ቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ የተራዘመውም በዚሁ ወር ነበር። ሚያዝያ-ግንቦትበአሜሪካ ኦሪገን በሰኔ ወር ሊካሄድ የነበረው የዓለም የቤት ውስጥ አትሌቲክስ ቻምፒዮና በ2022 እንዲካሄድ ውሳኔ ላይ የተደረሰው በሚያዝያ ወር ነበር። የሚያዝያ ወር ምናልባትም በአትሌቲክሱ ዓለም ውድድሮችና ክብረወሰኖች የተመዘገቡበት ሳይሆን በርካታ ተጠባቂ ውድድሮች የተራዘሙበትና የተሰረዙበት መጥፎ ትዝታ ጥሎ ያለፈ ነው ማለት ይቻላል። ከቤት ውስጥ ቻምፒዮናው በተጨማሪ በፓሪስ ሊካሄድ የነበረው የአውሮፓ አትሌቲክስ ቻምፒዮና በዚህ ወቅት ለመሰረዝ በቅቷል። ጥቁር አሜሪካዊው ጂዮርጅ ፍሎይድ ሜይዌዘር በፖሊስ በአሰቃቂ ሁኔታ መገደሉን ተከትሎ የዓለም አትሌቲክስ ‹‹የጥቁር ሕይወት ዋጋ አለው›› በሚል በዓለም አቀፍ ደረጃ የተጀመረውን እንቅስቃሴ የተቀላቀለበት ወቅት ነው። የዓለም አትሌቲክስ አዲስ የኦሊምፒክ ተሳትፎ ማረጋገጫ ሂደትን ይፋ ያደረገውም በዚህ ወቅት ነበር። የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ስፖርቱን እያዳከመው በመምጣቱም የዓለም አትሌቲክስ ስፖርቱን ለመደገፍ አዲስ ስትራቴጅክ ፕላን ይፋ አድርጓል። ተጠባቂው የኒውዮርክ ማራቶንም መሰረዙ የተሰማው በዚሁ ወቅት ነው። ሰኔ-ሐምሌ ውድድሮች ለወራት በዓለም ላይ አለመካሄዳቸውን ተከትሎ የስፖርቱ ዓለም በዘርፉ ፖለቲካ ተጠምዶ የቆየበት ጊዜ ነበር። በዚህም ከውድድርና ውጤቶች ይልቅ የተለያዩ ጉዳዮች የስፖርቱ ቤተሰብ መነጋገሪያ ሆነው ሰንብተዋል። በሰኔ ወር ትልቅ መነጋገሪያ ከሆኑ የአትሌቲክስ ጉዳዮች የቀድሞው የማራቶን ባለክብረወሰን ኬንያዊው ዊልሰን ኪፕሳንግ አበረታች ንጥረነገር ተጠቅሞ በመገኘቱ ለአራት ዓመታት ከስፖርቱ መታገዱ ትልቅ ትኩረት ስቦ ነበር። ተቋርጠው የቆዩ የዳይመንድ ሊግ ውድድሮች በወሩ መጨረሻ እየተመለሱ መምጣታቸው ግን በወረርሽኙ ሳቢያ ድብርት ውስጥ ለነበረው የስፖርቱ ቤተሰብ ተስፋ ሆነው ነበር። በዚህም በዙሪክ የተካሄደው የዳይመንድ ሊግ ውድድር ተጠቃሽ ነው። ያም ሆኖ እንደ ቺካጎ ያሉ ታላላቅ የማራቶን ውድድሮች በዚህ ወር ከመሰረዝ አልዳኑም። ወሩ ከመጠናቀቁ አስቀድሞም የዓለም አትሌቲክስ በመሮጫ ጫማዎች ላይ አዲስ ሕግ ይፋ ማድረጉ ይታወቃል። ውድድሮች ከወራት በኋላ በሂደት መመለሳቸውን ተከትሎ ለረጅም ዓመታት ያልተደፈሩ የዓለም ክብረወሰኖች ጭምር ሐምሌ ወር ላይ ተሰብረዋል። በተለይም ዩጋንዳዊው አትሌት ጆሽዋ ቺፕቴጌ ሞናኮ ላይ በቀነኒሳ በቀለ ለአስራ አምስት ዓመታት ተይዞ የቆየውን የዓለም ክብረወሰን በ12፡35፡36 ማሻሻሉ ያልተጠበቀ የዓመቱ አበይት ክስተት ነበር። ነሐሴ ሐምሌ ወር ላይ የታየው ትልልቅ የዓለም ክብረወሰን የማሻሻል ሂደት በነሐሴም ተደግሟል። በተለይም በኢትዮጵያውያኑ አትሌቶች ኃይሌ ገብረስላሴና ድሬ ቱኔ ለረጅም ዓመታት ተይዘው የቆዩት የአንድ ሰዓት ውድድር የዓለም ክብረወሰኖች መሰበራቸው ያልተጠበቀ ነበር። ትውልደ ሶማሊያዊው የእንግሊዝ አትሌት ሞ ፋራህ የወንዶቹን ክብረወሰን ሲያሻሽል ትውልደ ኢትዮጵያዊቷ የኔዘርላንድስ አትሌት ሲፈን ሃሰን የሴቶቹን ክብረወሰን መጨበጥ ችላለች። ኬንያዊቷ አትሌት ፒርስ ጂፕቺርቺር በፓራጓይ ግማሽ ማራቶን የርቀቱን የሴቶች ብቻ የዓለም ክብረወሰን ያሻሻለችበት አጋጣሚም አይዘነጋም። የቀድሞው የዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር ፕሬዚዳንት ሴኔጋላዊው ላሚን ዲያክ በሙስና ቅሌት በፓሪስ ለዓመታት በቁም እስር ቆይተው ፍርድ የተበየነባቸውም በዚሁ ወር ነው። የውድድር ዓመቱን በክብረወሰኖች ታጅቦ ያሳለፈው ስዊድናዊው ምርኩዝ ዘላይ ሞንዶ ዱፕሌንቲስ ከቤት ውጪ ባሉ ውድድሮች በዩክሬናዊው ታሪካዊ አትሌት ሰርጌ ቡካ ተይዞ የቆየውን የዓለም ክብረወሰን በ6 ነጥብ 15 ሜትር ያሻሻለበት አጋጣሚም ትልቅ ነው። የዓለም የማራቶን ክብረወሰን ባለቤት የሆነችው ኬንያዊት አትሌት ብሪጊድ ኮስጌ የለንደን ማራቶንን ለሁለተኛ ጊዜ አሸንፋለች። በዚህ ውድድር ለወራት ሊፋለሙ ቀጠሮ ይዘው ትልቅ ትኩረት የተሰጣቸው ቀነኒሳ በቀለና ኢሉድ ኪፕቾጌ ፍልሚያ አንድ ቀን ሲቀረው ቀነኒሳ በጉዳት ከውድድር ውጪ መሆኑ አሳዛኝ ነበር። ያም ሆኖ የርቀቱ የክብረወሰን ባለቤትና ባለፉት ዓመታት ሽንፈት ያልገጠመው ኪፕቾጌ ባልተጠበቀው ኢትዮጵያዊ አትሌት ሹራ ቂጣታ ከመሸነፉ ባሻገር ሰባተኛ ደረጃን ይዞ ማጠናቀቁ አስገራሚ ነበር።ዩጋዳዊው ቺፕቴግ ቀነኒሳ ለአስራ ስድስት ዓመታት ይዞት የቆየውን የአስር ሺ ሜትር የዓለም ክብረወሰን ቫሌንሲያ ላይ ሲያሻሽል ኢትዮጵያዊቷ ለተሰንበት ግደይ በጥሩነሽ ዲባባ ለአስራ ሁለት ዓመታት የተያዘውን የአምስት ሺ ሜትር የዓለም ክብረወሰን ማሻሻሏ የውድድር ዓመቱ ግንባር ቀደም አበይት ክስተት ሆኖ አልፏል። ኬንያዊቷ ፒርስ ጂፕቺርቺር በፖላንድ ጊዲኒያ የዓለም ግማሽ ማራቶን ቻምፒዮና የርቀቱን የሴቶች ብቻ የዓለም ክብረወሰን መስበሯም ወሩን አስደናቂ አድርጎት አልፏል። መስከረም -ታህሳስ የ2023 የአውሮፓ አትሌቲከስ ቻምፒዮናን ቱርክ ኢስታንቡል ላይ እንድታዘጋጅ ዕድል ባገኘችበት መስከረም ወር በአየርላንድ ደብሊን ሊካሄድ የነበረው የ2020 የአውሮፓ አገር አቋራጭ ቻምፒዮና ከመሰረዙ በቀር በአትሌቲክሱ ዓለም ብዙም አነጋጋሪ ጉዳዮች ሳይፈጠሩ አልፈዋል። ከዚያ በኋላ ባሉት ሦስት ወራት ግን የዓለማችን ፈጣኑ አትሌት ጃማይካዊው ዩዜን ቦልት እንዲሁም የረጅም ርቀት ንግስቷ አትሌት ጥሩነሽ ዲባባ በእውቁ የእንግሊዝ የአትሌቲክስ መፅሔት የምን ጊዜም ምርጥ አትሌት ተብለው መሰየማቸው አብይ ጉዳይ ነበር። ቬንዙዌላዊቷ አትሌት ዩሊማር ሮጃስ እንዲሁም ስዊድናዊው ሞንዶ ዱፕሌንቲስ የዓመቱ ምርጥ አትሌቶች ተብለው ተሸልመዋል። ኬንያዊው ኪቢዎት ካንዲም በዓለም ግማሽ ማራቶን ቻምፒዮና ሲያሸንፍአዲስ ዘመን ታህሳስ 23/2013
https://www.press.et/Ama/?p=38650
1,005
2ስፖርት
ለራስ ሲባል ሌላውን …
መዝናኛ
April 27, 2020
24
ኧሯ! እንዴት ሆኖ እንዴት ሆኖ እኛንማ አይደፍርም! ብለን ነበር ደፈረን። በሩቅ ሆኖ የሰማነው ዜና ገስግሶ መጥቶ አጠገባችን ከደረሰ የወራት እድሜን አስቆጠረ። በሰው ሀገር ሲነገር፤ ሲወራ እኛ ዘንድ የማይደርስ መስሎን ተዘናግተንማል። እኛ ሀገር አይገባም ፤ ጥቁሮችን አይነካም በማለት እራሳችንን በማይሆን ተስፋ እያታለልን ቆይተናል። ቁርጡ ቀን ደርሶ በሀገራችን የቫይረሱን መገኘት እውነታ ሲነገር ሰምተን ላለማመን ያመነታነው ስንቶቻችን እንሆን? ታዲያ አስፈሪ ዝናውን አስቀድሞ በርካቶቻችንን ኮርኩሮ ሃሳብ በማሰንዘር ፤ ከሃሳባችን መደምደሚያ ሳንደርስ ከች ብሎ ጉድ ያደረገን እሱም አይደል ወይ ኮሮና። ስለ ቫይረሱ ያለን እውቀት እንደ ግንዛቤ የሚለያይ ነው። አንዳንዱ ህይወቱ ግድ ሰጥቶ ለራሱ ኖሮ ሌላውን ለማትረፍ የሚጥረው ነው። ሌላው ደግሞ ለራሱም ሆነ ለሌላው ግድ የሌለው ቢነገረው ቢዘከር ሰምቶ እንዳልሰማ አይቶ እንዳላየ የሚሆን ነው። ራሱን በመኖርና ባለመኖር መካከል ከቶ በደመነፍስ እንደሚኖር ሰው ቫይረሱ ምንም እንደሚያመጣ የሚናገርም ዛሬ ድረስ አልጠፋም። ሰውን ለማዳን ራሱን ያልሰሰተውን ተመልክተን እሰየው በርታልን ጓድ እንዳላልን ሁላ ፤ በግዴለሽነት የሚኖረውን ደግሞ በትዝብት እያየን ከማለፍ ለመምከር የሞከርን እንኖራለን። የሚጠነቀቀውም ሆነ ግዴለሹ፤ የአንዱ ጤንነት የሌላው መኖር ዋስትና ነው ። የሰው ልጅ በምድር ላይ የሚኖረው ለራሱ ብቻ አይደለም፤ ለሌሎችም ነው። አንዱ ከሌለ የሌላው መኖር ትርጉም አልባ ነውና ። ህይወት ጣዕም የሚኖራት በመኖር ነው። መኖር ትርጉሟ ሙሉ የሚሆነው አንዳችን ለአንዳችን በሚኖረን አብሮነት ፤ መረዳዳትና መደጋገፍ ነው። ለዚህ ዋንኛው ደግም የኔ ጤንነት ሲጠበቅ የጎረቤት፤ የአካባቢዬ ፤ የሀገር፤ የሁሉም ጤና መሆን ግድ ይላል ። ታዲያ አለመታዘዛችን ከምን የመነጨ ይሆን? ለመኖር ራሳችን ከመጠበቅ ሌላው አማራጭ ይኖር ይሆን። ታላላቆቻችን፤ አባቶቻችን ማድመጥ፤ መደማመጣችንን እሴቶቻችንን ማን ነጠቀን? ለምን ረሳነው? በራሳችን ፈርደን በሌሎችም የመጨከን አባዜን ከየት አመጣነው? የሰውን ልጅ ሳይመርጥ ከምድረ ገጽ እያጠፋ ያለው ይህ ጨካኝ ቫይረስን እንዴት ልባችንን ሊያደነድን ቻለ። ሰው የሚችለውን ነውና የሚታዘዘው እራሳችንን እንመርምር ለመለወጥ መትጋት አለብን። የማንችለውን ትተን የምንችለውን መምረጥ ፤ ዛሬን መኖር ለነገ ተስፋ ነው። የእኛ ጥንቃቄ ለወገን መሆኑ ማመን አለብን። ነጭ፤ ጥቁር፤ ዘመድ፤ ባዕድ እያልን ራሳችንን ሳንከፋፈል ከስጋት ራስን ጠብቆ በማስመለጥ አብሮ ማምለጥ ይቻላልና ነው። ካለበለዚያ ግን “ከኑግ ጋር ያለህ ሰሊጥ አብረህ ተወቀጥ” ከሆነ ጉዳይ የታሪክ ተወቃሽ መሆናችን አይቀርም። መቼም ቫይረስ በሀገራችን ከተከሰተ ማግስት ጀምሮ ብዙ ለውጦችን፣ አዳዲስ ነገሮችን ታዝበናል። ለመከላከል የሚረዱን እጅን በሳሙና ቶሎ ቶሎ በደንብ መታጠብን ፤ ፊት በእጅ አለመንካት፤ አካላዊ ርቀትን መጠበቅ በዋናነት ከህክምና ባለሙያዎች የሚሰጡትን ምክሮች ተግባራዊ ለማድረግ ተሞክሯል። ለራሱ ያለ ራሱ ተጠንቅቆ ሌላውን ለማዳን እየጣረ እየተጋ ታይቷል። ይገርማችኋል! ለዛሬ ትዝብቴ መነሻ የሆኑት ይህንን የሰሙ የማይመስሉ የሰፈሬ ወጣቶች ናቸው። በከተማችን የሚገኙ በርካታ ወጣቶች በጎ ተግባራት ላይ በመሳተፍ ከወገናቸው ጎን የቆሙበትን አይተናል፤ ሰምተናልም። የነገ የሀገሪቱ ተስፋዎች መሆናቸውንም አስመስክረዋል። የኔ ሰፈር ወጣቶች ግን ቫይረስ መኖሩን አልሰሙም!! በአንድ ላይ በጋራ በመሆን መጠጥ ይጠጣሉ ፤ ጫት ይቅማሉ፤ መንገድ ዳር ተዛዝለው በሚባል ሁኔታ ሆነው ያወጋሉ። የቫይረሱ የተከሰተ ሰሞን አልነበሩም፤ ጠፍተው ነበር ። እሰየው አልኩኝ፤ ራሳቸውን ለመከላከል ወስነው ቤት ለመቀመጥ የከተሙ መስሎኝ። አልሰሜን ግባ በለው አሉ። ለካ የቦታ ለውጥ በማድረግ ከሰው አይን ዞር ብለው ነበር። ታዲያ እኔም የግዴታዬን ለመወጣት ወደእነሱ አመራሁ። በእግዜር ስላምታ ተቀላቀልኳቸው። ስለቫይረሱ አስከፊነት የነሱ መጠንቀቅ ለሚወዷቸው ሁሉ ፤ ለወላጆቻቸው፤ ለሰፈራችን ሁሉም እንደሆነ አስረዳኋቸው። ለማዳመጥ ፈቃደኛ ባልሆነ ጆሮ ሰሙኝ ። መልስ አልሰጡኝም። አንደኛው እሺ አለኝ ቀልድ በተሞላበት ፌዝ ። በእውነት አመመኝ። ለምን አትተሳሰቡም እርስ በርሳችሁ እንኳን አትዋደዱም አልኳቸው። እሺ ሌላው ቢቀርስ ለምን አትታዘዙም አልኩት? አቀርቀረው ስልካቸውን መጎርጎር ተያያዙት ። ትቻቸው ስሄድ መታዘዝ ከመሰዋዕትነት ይበልጣል አልኩ ሰምተውኛል፤ ግን ዝምታን መርጠዋል። ለብቻዬ እንዳስብበት የቤት ስራ የሰጡኝ ወጣቶች ዞር ብዬ በማየት ጉዞዬን በሃሳብ ቀጠልኩ። “ለምን ይሆን የተከለከለ ነገር የሚያምረን?” አልኩኝ ለራሴ ። ወደ አፈጣጣራችን ተመለስኩ ለካ አዳምን ከገነት ያስባረረው አታድርግ የተባለው በማድረጉ ነው። እኛም ዛሬ ለመቅጽበት ለሚያልፍ ቀን ብለን አታደርጉ የተባልነውን በማድረግ በጎ ተግባር እንደፈጸመ ጀግና በየአደባባዩ እንታያለን። ማንንም መስማት አንፈልገም፤ እራሳችንን ብቻ ካልሆነ በስተቀር ፤ ራሳችንን በቅጡ አውቀን ብናዳምጥ ጥሩ ነው። በዓለም ያሉ ሀገራት እንደኛ አይነት ተው ተብለው የማይሰሙ ዜጎች በመያዛቸው ነው። ዛሬ ለመስማት የሚቀፍ ዜና እየሰማን የምንገኘው። እነሱ ቢጸጸቱም ወደ ኋላ ሊመልሱት የማይችሉት ነገር ሆኖባቸዋል። ለኛ ትምህርት መሆን አለባቸው። እኛ ላይ በቅድሚያ ያልተፈጸመብን መሆኑን እያመሰገን ከሰማነው፣ ካየነው ቀድሞ መገኘት የግድ ይለናል። ጊዜው ፈጣን ነው ፤ ዛሬ ላይ እንኳን ቆመን ነገን ለማየት በተሰጠን መልካም እድል መጠቀም አለብን። ያለመታዘዛችን ዋጋ እንዳያስከፍል መበርታት ያስፈልገናል። ለዚህም ቀኑ ዛሬ እንጂ ነገ አይደለም። የቤት ስራን ከወዲሁ በመፈጸም ለወገን አለኝታነታችን በመግለጽ እራስን ሆኖ መገኘት፤ ታዝዞ መታዘብ ማስተማር ፤ቀዳሚ ሆኖ ለሌሎች አርአያ በመሆን መስመሩን በመጥረግ ከመስመሩ ያፈነገጡትን መመለስ ይገባል። የዛሬ ሁላችንም አብሮነትና ትብብርን አንዱ ለአንዱ መኖር ግድ ይሆናል። ታላላቆቻችንን በማስቀደም እነሱን አድምጠን ከዚህ አስከፊ አደጋ ማምለጥ ይኖርብናል። አብረን ስንሆን፣ ስንተባበር፣ ስንደማምጥ፤ ስንረዳዳ ያምርብናል። ባህሩን አቋርጠን መሻገር እንችላለን። የሰው ልጆችን እየጠረገ ያለውን አስከፊ ወረርሽን ለመከላከል ወኔ አቅም ጉልበት ይኖረናልና ። መጪው ጊዜ መልካም ዜና የምንሰማበት ጊዜ ይሁንልን ። አዲስ ዘመን ሚያዝያ 19/2012 ወርቅነሽ ደምሰው
https://www.press.et/Ama/?p=31198
695
1መዝናኛ
የ2023 አፍሪካ ዋንጫ ዝግጅት ቀጥሏል
ስፖርት
December 22, 2020
8
 ቦጋለ አበበ ምዕራብ አፍሪካዊቷ አገር ኮትዲቯር የ2023 አፍሪካ ዋንጫን ለማስተናገድ የምታደርገው ዝግጅት በሚፈለገው ደረጃ ቀጥሏል።የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ባለፈው ዓመት ከተከሰተ ወዲህ በርካታ የዓለማችን አገራት ስፖርታዊ ውድድሮችን ከማቆም ባለፈ ዓለም አቀፍና አህጉር አቀፍ ውድድሮችን ለማስተናገድ የሚያደርጉት ዝግጅት ተስተጓጉሏል።የ2023 አፍሪካ ዋንጫን ለማስተናገድ ዕድሉ የተሰጣት ኮትዲቯር ግን ወረርሽኙ ሳያግዳት ዝግጅቷን በተገቢው መንገድ እንደቀጠለች ኢንሳይድ ዘጌምስ አስነብቧል። የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) የግምገማ ቡድን ከሳምንት በፊት ወደ ኮትዲቯር አቅንቶ አገሪቱ እያደረገች የሚገኘውን ዝግጅት የተመለከተ ሲሆን ምዕራብ አፍሪካዊቷ አገር ለአፍሪካ ዋንጫው ተገቢውን ዝግጅት በማድረግ ሂደት ላይ እንደምትገኝ አሳውቋል።በዝግጅት ግምገማ ቡድኑ ውስጥ የካፍ ምክትል ዋና ፀሐፊ አንቶኒ ባፎይ፣ የውድድር ዳይሬክተሩ ሳምሶን አዳሙ፣ የብሔራዊ ቡድን ውድድሮች ማኔጀሩ ኢስማሊ ዋሊ እንዲሁም የአገልግሎትና የጉዞ ዋና ሃላፊው ራንዳ ሚትዋሊ ተካተው ወደ ስፍራው አቅንተዋል። የግምገማ ቡድኑ ከኮትዲቯር ከተመለሰ በኋላ ለኢንሳይድ ዘጌምስ አስተያየታቸውን የሰጡት ምክትል ዋና ፀሐፊው ባፎይ ምንም እንኳን የኮቪድ-19 ወረርሽኝ የዓለም ሕዝብ የጤና ቀውስ በመሆን ቢቀጥልም ያሳደረውን ጫና ተቋቁማ ኮትዲቯር በጥሩ ሁኔታ ዝግጅቷን እንደቀጠለች ማረጋገጫ ሰጥተዋል። ‹‹ጉብኝቱ በደንብ የታሰበበት ነው፣ በጉዟችንና የውድድሩ አዘጋጆች እየሠሩ በሚገኙት ሥራ ረክተናል›› ያሉት ባፎይ አብዛኛው ለውድድሩ የሚገነቡት ስቴድየሞች በ2021 አጋማሽ እንደሚጠናቀቁ ጠቁመዋል።ይህም አዘጋጆቹ እስከ ውድድሩ ድረስ በቂ ጊዜ እንዳላቸው የሚያሳይ ሲሆን ለሙከራ የተለያዩ ጨዋታዎችን የማካሄድ ዕድልም እንደሚኖራቸው ባፎይ አብራርተዋል። የውድድሩ አዘጋጆች በዕቅዳቸው መሰረት እየተመሩ ትክክለኛ ሰዎችን በትክክለኛው ቦታ በማሰራት ተጨባጭ ነገር እንዳሳዩ የጠቆሙት ባፎይ‹‹ ሁሌም የምናገረው ነገር አንድ ነው፣ ትክክለኛውን ሰው በትክክለኛው ቦታ ማስቀመጥ›› በማለት አዘጋጆቹን አድንቀዋል።ኮትዲቯር እ.ኤ.አ 2014 ላይ የ2021 አፍሪካ ዋንጫን እንድታዘጋጅ ዕድሉን ያገኘች አገር መሆኗ ይታወሳል።ይሁን እንጂ የ2019 አፍሪካ ዋንጫን ለማዘጋጀት ዕድሉ የተሰጣት ሌላኛዋ ምዕራብ አፍሪካዊት አገር ካሜሩን 2018 ላይ ውድድሩን ለማዘጋጀት የምትገነባቸው ስቴድየሞች በመጓተታቸውና በወቅቱ በአገሪቱ የነበረው የፖለቲካ አለመረጋጋት ከደህንነነት አኳያ ስጋት ስለፈጠረ የአዘጋጅነት ዕድሉ ለግብጽ ተሰጥቷል።ካሜሩንም በምትኩ የ2021 አፍሪካ ዋንጫን እንድታዘጋጅና ኮትዲቯር የ2023 አፍሪካ ዋንጫን እንድታሰናዳ ሽግሽግ ተደርጓል። በዚህም መሰረት ኮትዲቯር የአፍሪካን ትልቁ የስፖርት መድረክ በተሳካ ሁኔታ ለማዘጋጀት በቂ ጊዜና ዕድል ማግኘት ችላለች።ውድድሮቹንም ከ2023 ሰኔ ወር መጨረሻ አንስቶ በመዲናዋ አቢጃን፣ ቦኬ፣ ኮርሆጎ፣ ሳን ፔድሮ እና ያሙሱክሮ ከተሞች እንደ ምታከናውን ይጠበቃል።
https://www.press.et/Ama/?p=37905
299
2ስፖርት
የባለሀብቶች ተሳትፎ ያልታከለበት የማዘውተሪያ ስፍራዎች ግንባታ
ስፖርት
December 24, 2020
7
ብርሃን ፈይሳወቅቱ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች ግንባታ በዓለም አቀፍ ደረጃ እጅግ የሰፋበት መሆኑን ጥናቶች ያመላክታሉ። የማዘውተሪያዎች ዘመናዊነትና ጥራት የሰለጠኑ ከተሞች አንዱ መለያ እየሆነ ከመምጣቱም ባሻገር ኦሊምፒክ፣ ዓለም ዋንጫ እና የተለያዩ ስፖርት ቻምፒዮናዎችን ለማሰናዳት ዋነኛው መስፈርትም ነው። ሀገሮች ዜጎቻቸው በአእምሮና በአካል የተዋጣላቸውና ብቁ እንዲሆኑም በማዘውተሪያ ስፍራዎች አስፈላጊነትም እምነት ጥለዋል። በመሆኑም የከተሞቻቸውን ዲዛይን ሲያዘጋጁም ሆነ ግንባታውን ሲያከናውኑ ነዋሪዎቻቸው በቂ የጊዜ ማሳለፊያና ስፖርታዊ እንቅስቃሴ የሚከውኑባቸው ስፍራዎች ስለመኖራቸው ያረጋግጣሉ። የአፍሪካ መዲናዋ አዲስ አበባም በዓለም ላይ ካሉና ታላላቅ ጉባኤዎችን ለማስተናገድ ከሚመረጡ እንዲሁም የአህጉር አቀፍ ተቋማት መቀመጫ እንድትሆን ተመራጭ ከሆኑት መካከል ትገኛለች። ይህም ስፖርታዊ ውድድሮችን ለማስተናገድ ምቹ ሁኔታን ቢፈጥርላትም እስካሁን ግን ጉባኤዎችን ብቻ በማካሄድ ተወስናለች። ምክንያቱ ደግሞ ደረጃውን የጠበቀ የማዘውተሪያ ስፍራ የሌላት በመሆኑ ነው። አዲስ አበባ ከተማም ደረጃቸውን የጠበቁ የማዘውተሪያ ስፍራዎች ብቻም ሳይሆኑ በየአካባቢው ለነዋሪዎቿ የሚበቃ የማዘውተሪያ ስፍራ ማግኘትም ፈተና ሆኖባታል። በመሆኑም የየከተማ አስተዳደሩ ስፖርት ኮሚሽን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ትኩረቱን በማዘውተሪያ ስፍራዎች ግንባታ ላይ አድርጓል። ከሰሞኑ ጉባኤውን ያከናወነው የከተማዋ ስፖርት ምክር ቤትም አትኩሮቱን በተለይ በስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች ላይ አድርጎ ነበር። ምክር ቤቱ በጉባኤው ላይ ባቀረበው የ2012 በጀት ዓመት የአፈጻጸም ሪፖርት የአዳዲስና ነባር የማዘውተሪያ ስፍራዎች ያሉበትን ደረጃ በዝርዝር አመልክቷል። በዚህም በበጀት ዓመቱ ብቻ 95 የሚሆኑ 3በ1 እንዲሁም የጥርጊያ ሜዳዎች እንዲገነቡና እንዲታደሱ ተደርጓል። እነዚህም በክፍለ ከተሞች እንዲሁም በ14 የጋራ መኖሪያ ስፍራዎች ላይ የተገነቡና የታደሱ ናቸው። ከፍተኛ ወጪ ተደርጎባቸው የሚገነቡ ደረጃቸውን የጠበቁ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎችን በተመለከተም በዚህ ዓመት ተጠናቀው ወደ አገልግሎት የሚገቡና አዳዲስ የሚጀመሩ መሆኑም ተጠቁሟል። በዚህም የራስ ኃይሉ የመዋኛ ገንዳ እና የአበበ ቢቂላ ስታዲየም የግንባታ ምዕራፍ 99 ከመቶ የተጠናቀቀ ሲሆን፤ በተያዘው በጀት ዓመት ወደ ሥራ ይገባሉ በሚል ይጠበቃል። በሁለቱም የማዘውተሪያ ስፍራዎች የውሃ እጥረት በመኖሩ ምክንያት የከርሰ ምድር ውሃ ለማውጣት እንቅስቃሴ እየተደረገ ይገኛል። የአቃቂ ስታዲየም ግንባታም 70 ከመቶ ደርሷል፤ የአራት ኪሎ እና የጃንሜዳ ማዘውተሪያ ስፍራዎች ግንባታ በቴክኒክ ችግር ተቋርጦ ቆይቷል። በዚህ ዓመት ዕቅድም በዋናነት የማዘውተሪያ ስፍራ ቁጥርን ማሳደግና ሕጋዊነታቸውን ማረጋገጥ ላይ ትኩረት መሰጠቱ በመድረኩ ላይ ተጠቁሟል። በዚህም መሠረት የአቃቂና የአበበ ቢቂላ ስታዲየሞች እንዲሁም የራስ ኃይሉ የመዋኛ ገንዳዎች ግንባታን በዚህ ዓመት ሙሉ ለሙሉ በማጠናቀቅ አገልግሎት ለማስጀመር ታቅዷል። ግንባታው 67 ከመቶ ደርሶ የተቋረጠው የጃንሜዳ ጂምናዚየም እና ወደ ግንባታ ያልገባው የአራት ኪሎ ትምህርትና ስልጠና ማዕከል ሕንፃም በዓመቱ ወደ ግንባታ የሚገቡ ይሆናል። በተለያዩ ክፍለ ከተማዎች አንድ የአትሌቲክስ መንደር እና ሦስት ዞናል ስታዲየሞችን አስገንብቶ ለኅብረተሰቡ ተደራሽ ማድረግም የበጀት ዓመቱ ዕቅድ መሆኑም ተጠቁሟል። የቀረበውን ሪፖርትና ዕቅድ ተከትሎም የምክር ቤቱ አባላት የተለያዩ ሃሳቦችን አንጸባርቀዋል። አጸንኦት የተሰጠው ሃሳብ ግን ከስፖርት ኢንቨስትመንት አንጻር በከተማዋ ባለሀብቱን የማሳተፍ ሂደት የሌለ መሆኑ ነው። የግል ባለሀብቱ በተለይ እጥረት ባለበት የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች ግንባታ ላይ የማሳተፍ አስፈላጊነት ተጠቁሟል። በዚህም ባለሀብቱን ከመጥቀም አልፎ ነዋሪውንም ተጠቃሚ ማድረግ ይቻላል።በከተማዋ የሚስተዋለው የግሉ ተሳትፎ ጂምናዚየሞች ላይ የተወሰነ ነው። በመሆኑም የኦሊምፒክ ስፖርት በሆኑ ሌሎች የቤት ውስጥ ስፖርቶች ላይም ተሳታፊ ለመሆን የሚፈልጉ ባለሀብቶችን በማበረታታት ስፖርቱን መደገፍ ይገባል። ለግል ባለሀብቶች ለስፖርቱ በዋናነት ግብዓት የሚሆኑ ቁሳቁስ ከቀረጥ ነፃ እንዲገቡ ማድረግ አስፈላጊ መሆኑንም በመድረኩ ተጠቁሟል። ከባለሀብቱ ባሻገር የስፖርት ክለቦችም በማዘውተሪያ ስፍራ ልማት ቢሰማሩ ለመንግሥት ላይ ብቻ የተተወውን ዘርፍ ሊደግፉ እንደሚችሉም ተነስቷል። ጉባኤተኞቹ የሚገነቡ ማዘውተሪያዎች ሁሉንም ስፖርቶች ያማከሉ መሆን እንደሚገባቸውም አመልክተዋል። በከተማዋ ከ30 በላይ የሚሆኑ የአትሌቲክስ ቡድኖች እያሉ ለስፖርቱ የሚሆን ማዘውተሪያ ያለው በአዲስ አበባ ስታዲየም ብቻ መገኘቱ ሌላው አሳሳቢ ችግር መሆኑ ተጠቁሟል። ለተነሱት ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ የሰጡት የከተማ አስተዳደሩ ስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነር በላይ ደጀን፤ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች መንግሥታዊ በሆኑና ባልሆኑ አካላት በየአካባቢው ሊጠናከሩ እንደሚገባ ነው ያመለከቱት። እንደ ኮሚሽነሩ ገለጻ፤ የታዳጊ ፕሮጀክት ስልጠናን ለማስፋፋትም ሆነ ተተኪ ስፖርተኞችን ለማፍራት የሚቻለው ማዘውተሪያዎችን ማስፋትና ማልማት ሲቻል ነው። የመዘውተሪያ ስፍራዎች ጉዳይ የሁሉንም ባለድርሻ አካላት ርብርብ የሚጠይቅ ቁልፍ ሥራ በመሆኑ በቅንጅት መስራት ያስፈልጋል። ከሚሽነሩ ትምህርት ቤቶች በአካልም በአእምሮ የበለጸገ ዜጋ ለማፍራት የሚያስችል ስፍራ እንደመሆናቸው 300 የሚሆኑ የሰውነት ማጎልመሻ መምህራን የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ስልጠና እንዲያገኙ መደረጉን ጠቅሰው፣ ይህንን ተከትሎ የመጣው ጥያቄ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎችን የሚመለከት መሆኑን ይጠቅሳሉ። ስለዚህም ማዘውተሪያዎቹን በትምህርት ቤቶች ውስጥ ማልማት እንዲሁም ተማሪዎች ከሚጠቀሙበት ሰዓት በኋላ በሚኖረው ጊዜ የአካባቢው ወጣቶችና ታዳጊዎች የሚጠቀሙበትን ሁኔታ ማመቻቸት እንደሚያስፈልግ ያብራራሉ። ከዚህ ባሻገር በከተማዋ የሚገኙ ነባር ማዘውተሪያዎችን በማደስና አዳዲሶችንም በጥራትና በፍጥነት ለማስገንባት ቢሮው በእንቅስቃሴ ላይ መሆኑንም ኮሚሽነሩ ጠቁመዋል። ለዓመታት ጥያቄ ሲነሳባቸው የቆዩ የማዘውተሪያ ስፍራዎች ግንባታን በአጭር ጊዜ ለማጠናቀቅ እየተሞከረ ነው። ከባድ የሆነው ግን ከዚህ ቀደም የተጀመሩና በግንባታ ላይ የቆዩ ነባር ማዘውተሪያዎችን የጥራት ጉድለት እያለባቸው ወደ ሥራ ማስገባት ነው ሲሉ ያመለክታሉ። ለአብነት ያህል የአበበ ቢቂላ ስታዲየም ሜዳውን ለእግር ኳስ መሙን ደግሞ ለአትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች መስጠት ይቻላል ነገር ግን አሁን የጥራት ጉድለት አለ ይላሉ። በሌሎችም እንዲሁ የዲዛይን ችግር፣ የግንባታ ክፍተት፣ የክትትልና ቁጥጥር ድጋፍ የሚጎድላቸው እንዲሁም በተቀመጠላቸው የጊዜ ገደብ ያልተጠናቀቁም እንዳሉም ይናገራሉ። በእነዚህ ላይ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶበት የሚሰራ ይሆናል ብለዋል።የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባና የስፖርት ምክር ቤቱ ሰብሳቢ አዳነች አቤቤም፤ በከተማዋ ታዳጊዎች የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች በማጣታቸው ባልተገባ ስፍራ እንደሚውሉ ጠቅሰዋል። ይህንን በመረዳትም በየአካባቢው የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች ግንባታ እየተካሄደ መሆኑን ያመለክታሉ። ምክትል ከንቲባዋ ይህ ግን በቂ እንዳልሆነ ተናግረው፣ ከዚህም በላይ መስራት እንደሚገባም ይጠቁማሉ። የጠቅላላ ጉባኤው አባላት በተናጠልም ሆነ በጋራ ኃላፊነትን በመወጣት የተጀመሩትን ውጤታማ ማድረግና በሁሉም አካባቢ ማዳረስ እንደሚገባም አሳስበዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 15/2013
https://www.press.et/Ama/?p=38041
743
2ስፖርት
ቡናን ያለዛፍ ጥላ – በቀርጫንሼ ደበቃ
ሀገር አቀፍ ዜና
January 18, 2021
32
አስቴር ኤልያስስፍራው ሞቃታማ ቢሆንም ቅጥር ጊቢው ግን በቡና ችግኞችና በተለያዩ የፍራፍሬ ዛፎች በመሙላቱ ለአይን አርንጓዴነቱ ደምቆ፤ ለአፍንጫ ደግሞ መልካም መዓዛው ዘልቆ ስለሚመጣ ለጎብኚው ማየትም መማግም ግዴታ ሳይሆን በውዴታ የሚያጣጥመው ነገር ነው። ወዲህ ለቡና ተክሉ የተስተካከለ ውሃ ይደርሰው ዘንድ አዲስ የሆነና የውሃው ልክ በኮምፒውተር የሚታዘዝበት ቴክኖሎጂ ያለበት አንድ ክፍል ይታያል፤ ወዲያ ደግሞ ወደ 750 ሜትር ኪዩብ ውሃ የሚይዝ የውሃው ሪዘርቫይር ይስተዋላል ፤ ቦታው በምዕራብ ጉጂ ዞን አባያ ወረዳ ልዩ ስሙ ደበቃ እርሻ ልማት ነው። የቀርጫንሼ እርሻዎች አስተባባሪ ስራ አስኪያጅ አቶ ደጀኔ ዳባ እንደሚሉት፤ በቀርንጫንሼ ትሬዲንግ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ቀደም ሲል ጥራቱን የጠበቀ ቡና ወደ ውጭ አገር በመላክ ለአገሪቱ የውጭ ምንዛሬ በማስገኘት ረገድ በግንባር ቀደምትነት እየሰራ ነው። ከንግዱ በተጨማሪ ከቅርብ ጊዜ ወደዚህ ጎን ለጎን በቡና እርሻ ልማት ተሰማርቷል። ድርጅቱ፣ በዓለማችን ላይ ዘመናዊ የሆነ በቡና ማምረት ቴክኖሎጂ ጫፍ ከደረሱ እንደብራዚል ካሉት አገራት ባልተናነሰ ዘመናዊ ቴክሎጂን ወይም ዲሪፕ እሪጌሽንን በመጠቀም ወደቡና ልማት እርሻ የገባ ነው። የቡና እርሻው የሚገኘው በምዕራብ ጉጂ ዞን አባያ ወረዳ ልዩ ስሙ ደበቃ እርሻ ልማት ሲሆን፣ያረፈው ደግሞ በ72 ሄክታር መሬት ላይ ነው። በዚህም ላይ 110 ሺህ የቡና ችግኞችን በመተክል ወደ ስራ መግባታቸውን ጠቅሰው፤ በቀጣይም በአንድ ሄክታር ላይ ዘመናዊ የቡና ማፍያ የችግኝ ጣቢያ ወይም ዲጂታል ስፕሪንግ ክለር እሪጌሽ በመጠቀም 600 ሺህ ችግኞችን በማፍላት ለአካባቢው ህብረተሰብም ጭምር ለማደል ወደ ስራ መግባታቸውን ይናገራሉ። ቀደም ሲል በአገራችን ያለው አስተሳሰብ ቡናን ያለጥላ ዛፍ ማልማት አይቻልም የሚል ኋላ ቀር አስተሳሰብ ሲሆን፣ ይህን አስተሳሰብ በአዲስ አስተሳሰብ ለመቀየር እየሰራን ነው ሲሉ ያስረዳሉ። በድርጅቱ አግሮኖሚስት ሆነው የሚሰሩት የሆርቲካልቸር ባለሙያው አቶ ጉተማ ጎቤ በበኩላቸው፤ በድሪፕ እሪጌሽን (ጠብታ መስኖ) በአንድ አይነት መልኩ ውሃ ለቡናው እንዴት ሆኖ ይሰራጫል የሚለውን እንደሚከታተሉ ይናገራሉ። ውሃው ለችግኙ ሲደርሰው ለእያዳንዱ ቡና እኩል የሆነ የውሃ መጠን ነው በሜትር ኪዩብ የተለቀቀው ውሃ ወደ ቡናው ሲሄድ የሚደርሰው በሚሊ ሊትር ተቀይሮ መሆኑን ይጠቅሳሉ። ይህ ቴክኖሎጂ የነበረውን ተልምዷዊ አሰራር ያለዛፍ ቡና መብቀል አይችልም የሚል አስተሳሰብን የሰበረ ነው። ቀደም ሲል ዛፍ ያስፈልግ የነበረው ብዙ ውሃ ስለማይጠጣ የዛፍ ጥላው ያለውን ውሃ እርጥበቱን ጠብቆ እንዲሄድ ስለሚያርገው ነው ይላሉ። አጠቃላይ የቀርጫንሼ ካምፓኒ ስራ አስፈጻሚ አቶ እስራኤል ደገፋ፣ ካምፓኒው የሚሰራው አጠቃላይ የአገራችን ኢኮኖሚ በሚፈልግበት በግብርናና ማኑፋክቸሪንግ ላይ መሆኑን ይገልጻሉ። በግብርናው ላይ ወደ 26 ሺህ የስራ እድሎችን በመፍጠር እንዲሁም ከ56 ሺህ አርሶ አደሮች ጋር የገበያ ትስስር በመፍጠር የሚሰራ ድርጅት እንደሆነም ያመለክታሉ። አቶ እስራኤል እንደሚሉት፤ ላለፉት አራት አምስት ዓመታት ትልቁን የአገሪቱን የቡና ኤክስፖርት ከሁለት አኃዝ በላይ ድርሻ በመውሰድ የሚልከው ይኸው የቀርጫንሼ ኩባንያ ነው። በየትኛውም የኢትዮጵያ ቡና አብቃይ ክልሎችም ሆነ ወረዳዎች ይገኛል። አጠቃላይ ወደ 57 ኢንዱስትሪዎች እንዲሁም ደግሞ ወደ አምስት እርሻዎችን በቡናው ሴክተር ላይ ማኔጅ ያደርጋል። ጉብኝት የተደረገበት የደበቃ እርሻ ጣቢያ፣ ኩባንያው ካሉት እርሻዎች ሁሉ አነስተኛው ነው ያሉት አቶ እስራኤል፣ ነገር ግን እንዴት አድርገን ግብርናን ከተለምዶ አሰራራችን መቀየር አለብን ሲሉ በማሰብ በቡናው ፋርም ትልቅ ደረጃ ላይ የደረሱ አገሮችን ተሞክሮ ከእነእስራኤልና ብራዚል መውሰድ ላይ መሆናቸውን ያመለክታሉ። የወሰዱትም ቴክኖሎጂ ድሪፕ ኢሪጌሽን ሲሆን፣ በአሁኑ ሰዓት በዓለም ላይ የመጨረሻው የሚባለው በግብርናው ዘርፍ የተገኘና ውጤታማ የሆነ የመስኖ ሲስተም ነው ይላሉ። ከዚህ አንጻር በደበቃ ያለው የተሻለው ቴክኖሎጂ  እንደሚያሰኘው ያስረዳሉ። አርሶአደሩ በተለምዶ በሄክታር ቡና የሚያገኘው ከስድስት ኩንታል የዘለለ አይደለም የሚሉት አቶ እስራኤል፣ እኛ በዚህ ቴክኖሎጂ ተጠቅመን ግን በሄክታር እስከ 35 ኩንታል ማሳካት ችለናል ብለዋል። ይህ ሙከራ ደግሞ የመጀመሪያው ሲሆን፣ የሚጠበቀው በሄክታር እስከ 65 ኩንታል ድረስ ነው ብለን እየሰራን ነው ሲሉ ተናግረዋል። ያንን ማሳካት ከቻልን የአገራችንን የውጭ ምንዛሬ ማሳደግ እንዲሁም የአርሶ አደሮችን ገቢ ከፍ ማድረግ ይቻላል ብለዋል። የእኛ ትልቁ እቅዳችን የራሳችን ማሳ ላይ ትልቁን ምርት ማምረት ላይ ብቻ አይደለም። በአቅራቢያው የሚገኙ የአርሶ አደሮችንም ማሳዎች ወደእኛ ቴክኖሎጂ በመቀየር እነርሱም ተጠቃሚ የሚሆኑበትን መሰረት ማደላደልና በፋይናንስም ለመደጎም ሲሆን፣ ይህን ተግባራዊ ለማድረግ ዲዛይን አድርገን ጨርሰናል ይላሉ። በዕለቱ ቀርጫንሼ ትሬዲግ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ ኤክስፖርት ስታንዳርድ የቡና ላቦራቶሪን የመረቁት የግብርና ግብአትና ግብይት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ወይዘሮ አይናለም ንጉሴ እና የኢትዮጵያ ቡና እና ሻይ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አዱኛ ደበላ ሲሆኑ፣ ሚኒስትር ዴኤታዋ በዕለቱ እንደተናገሩት፤ የድርጅቱን የቡና ማዘጋጃ መጋዘንና የቡና መቅመሻ ላቦራቶሪ እንዲሁም እርሻዎቹን ጎብኝተናል። ከዚህ ደርጅት ባለቤት ጋር አርሶ አደሮችም አብረው ነው ያሉት። ለምርት መሻሻል ደግሞ ዋናው አርሶ አደሮቻችን ከባህላዊ የቡና አመራረት ዘዴ በመጠኑም ቢሆን በመቀየር የቡናን ምርታማነት ሊቀየሩ የሚችሉ አሰራሮችን ተግባራ እያደረጉ ነው ያሉት። ቡሌ ሆራ ላይ እንደማየውና ሞዴል አርሶአደሮችም እንዳረጋገጡልን በምርትም፣በአቅርቦትም ሆነ በገበያ ትስሰርም የተሻለ እድል ያለበት አካባቢ መሆኑን ነው ያሉት ሚኒስትር ዴኤታዋ፣ እዚህ የሚሰሩ ባለሀብቶች የአርሶአደሩንም ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ከፍተኛ ጥረት እያደረጉ ስለመሆናቸው ማስተዋል መቻላቸውን ይናገራሉ። እርሳቸው እንደሚናገሩት፤ እንደግብርና ሚኒስቴር የበለጠ ምርትና ምርታማነትን ሊያሳድግ የሚችል ስራ ይሰራሉ። ቡና ወደውጭ በመላክ ረገድ በተለይ ቀርጫንሼ ላለፉት ሁለትና ሶስት ዓመታት የቀዳሚነት ድርሻውን እየተወጣ ነው። በመጋዘን ውስጥ የተመለከትነውም ደረጃውን የማያስለቅቅ ለአገርም ኢኮኖሚ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ሊያደርግ የሚችል ክምችት የያዘ ቡና መኖሩን ነው፤ ለዚህም በጣም ደስተኞች ነን። አርሶአደሮቹ ጥሩ የቴክኖሎጂ ስራ ካላቸው ከግል ሴአልሚዎች ጋር በመቀናጀት ምርታቸውን እንዲያሳድጉ ለማድረግ የሚያስችል የአሰራር ማዕቀፍ መዘርጋት ነው። የተሻለ ገበያ እንዲያገኝ ከማድረግ አኳያ የተዘረጉ አሰራሮች አሉ፤ ትልቁ ነገር አርሶ አደሩ ያመረተውን ምርት ቀጥታ ወደ ገበያ ለማድረስ የሚያስችለው አቅም ገበያ የማፈላለግ ችሎታ የማዳበር ስራ መሰራት ይኖርበታል። እንዲህ ከሆነ በለፋው ልክ ጥቅም እንዲያገኝ ያችለዋልና በዚህ ደረጃ እንቅስቃሴዎች ተጀምረዋል ብለዋል። ዶክተር አዱኛ በበኩላቸው እንደተናገሩት፤ ባለስልጣኑ ቡና ከማብቀል ጀምሮ ውጭ አገር እስከ መላክ ድረስ ያለውን ሂደት በማገዝ እንዲሁም ገበያ በማፈላለግ ረገድ በመስራት ላይ ይገኛል። አርሶ አደሮቻችን እስከ ውጭ አገር በራሳቸው እንዲልኩ ይሰራል። 500 ያህል አርሶ አደሮች ወደውጭ አገር መላክ የሚያስችላቸውን ሰነድ አውጥተዋል። በዚህም እየሄዱበት ነው። ቀርጫንሼ የሰራው ስራ በአርአያነት መጠቀስ የሚያስችል ስራ ነው ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ፣ በቦታው ተገኝተን ያስተዋልነው ነገር ቢኖር ይህን ነው ብለዋል። ይህም ወደሌሎቹም መስፋፋት ያለበት ቴክኖሎጂ መሆኑን ጠቅሰው፤ በዚህ ስራው ደግሞ እንደ መንግስት ድጋፍ እናደርግለታለን ብለዋል።አዲስ ዘመን ጥር 10/2013 ዓ.ም
https://www.press.et/Ama/?p=39687
838
0ሀገር አቀፍ ዜና
ኮቭድ-19- ዳግም የቶኪዮ ኦሊምፒክ ሥጋት
ስፖርት
December 25, 2020
7
ቦጋለ አበበ ጃፓን ከሰባት ዓመታት በላይ ብዙ የለፋችበት የቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ ዝግጅት ካለፈው ዓመት ጀምሮ የዓለም ሕዝብ የጤና ጠንቅ በሆነው የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ምክንያት ለአስራ ስድስት ወራት ተራዝሞ ዘንድሮ ሊካሄድ ቀጠሮ ተይዞለታል። ኦሊምፒኩ በተራዘመው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት እንደሚካሄድም እርግጠኛ ሆነው የውድድሩ አዘጋጆች መናገር ከጀመሩ ሰነባብተዋል። የተለያዩ አገራትም በአዘጋጆቹ ተማምነው የስፖርት ልዑካን ቡድኖቻቸውን እያዘጋጁ ይገኛሉ።የዓለም አቀፉን ኦሊምፒክ ኮሚቴ ጨምሮ የውድድሩ አዘጋጆች አሁንም ድረስ ውድድሩ እንደሚካሄድ እርግጠኛ የሆኑት ወረርሽኙ ኦሊምፒኩ እስኪቃረብ አንድ መፍትሄ ያገኛል በሚልና በሙከራ ላይ የሚገኙትን የተለያዩ ክትባቶች ተማምነው ነው። ያም ሆኖ ሰሞኑን እየወጡ የሚገኙ መረጃዎች ወረርሽኙ እየቀነሰ ከመሄድ ይልቅ በፍጥነት እየተስፋፋ እንደሚገኝ ያመላክታሉ። ጃፓን ውድድሩን በምታካሂድበት ወቅት ከወረርሽኙ ጋር በተያያዘ ከአገሪቱ ዜጎች በበለጠ ብዙ ቁጥር ያላቸው እንግዶች ስጋት ሊሆኑ እንደሚችሉ የገመተች ቢሆንም፣ በተቃራኒው ራሷ ጃፓን የእንግዶቿ ስጋት ልትሆን እንደምትችል በቅርብ የወጡ መረጃዎች እየጠቆሙ ነው።ወረርሽኙ ለዓለም ስጋት ከሆነ ወዲህ ኦሊምፒኩን በዋናነት የምታስተናግደው ከተማ ቶኪዮ ለመጀመሪያ ጊዜ በአንድ ወር ውስጥ ብቻ በቫይረሱ የተጠቁ አስር ሺህ ሰዎች የተገኙባት ሆናለች። ይህም በቀጣዩ ክረምት በሚካሄዱት የኦሊምፒክና የፓራሊምፒክ ውድድሮች ላይ ዳግም ተመሳሳይ ስጋት እንዲፈጠር ያደረገ ሲሆን በብዙዎች ዘንድ ጥያቄ እየተነሳበት ይገኛል።ኦሊምፒኩ ሊካሄድ ስድስት ወራት በቀሩበት በዚህ ወቅት ባለፈው ሐሙስ ብቻ ቶኪዮ በሃያ አራት ሰዓት ውስጥ ስምንት መቶ ሃያ ሁለት ሰዎች በቫይረሱ የተያዙባት ከተማ ሆናለች። ይህም ወረርሽኙ በሀገሪቱ ከተከሰተበት ወቅት ወዲህ የታየ ከፍተኛው ቁጥር ሆኖ ተመዝግቧል። የቶኪዮ ከተማ አስተዳዳሪ ዩሪኮ ኮኢኬ ከጃፓን ታይምስ ጋር በነበራቸው ቃለ ምልልስም የቶኪዮ የጤና ተቋማት ከአቅማቸው በላይ ሕመምተኞችን እያስተናገዱ እንደሚገኙ ተናግረዋል። ‹‹ሆስፒታሎች ተዘግተዋል፣ በዚህ ወሳኝ ወቅት በቅርቡ መሰረታዊ አገልግሎት መስጠት ሊያቆሙም ይችላሉ›› በማለትም በከተማዋ ያለውን ሁኔታ ገልፀዋል።ቶኪዮ ወረርሽኙ ከተከሰተ ወዲህ እስካለፈው ሳምንት መጨረሻ ብቻ ሃምሳ ሁለት ሺህ ሰዎች በቫይረሱ የተጠቁባት ከተማ ስትሆን አምስት መቶ ያህል ሰዎችም ሕይወታቸው አልፏል። በአጠቃላይ በጃፓን ደግሞ እስካፈው ሰኞ ድረስ በአማካይ ከሁለት ሺህ በላይ ሰዎች በቫይረሱ እየተጠቁ እንደሚገኙ መረጃዎች ይጠቁማሉ፤ እስካሁን ከሁለት ሺህ ዘጠኝ መቶ በላይ ሰዎች በቫይረሱ መሞታቸው ታውቋል።የቶኪዮ ተላላፊ በሽታዎች መቆጣጠሪያ ማዕከል ዳይሬክተር ኖሮዪ ኦማጋሪ በበኩላቸው ‹‹የቫይረሱ ሥርጭት ከፍተኛ ደረጃ ላይ ደርሷል፣ ከዚህ የበለጠ ብዙ ሰዎች በቫይረሱ እንዳይጠቁ ጠንካራ እርምጃዎች መወሰድ አለባቸው›› በማለት ለአገሪቱ ጋዜጣ ተናግረዋል።ጥቂት ቀናት በቀሩት የፈረንጆቹ አዲስ ዓመትና የገና በዓል አከባበር ወቅት በርካታ የአውሮፓ አገራት የወረርሽኙን ሥርጭት ለመቀነስ ጠንካራ መመሪያዎችን ከማውጣት ባሻገር በአገር አቀፍ ደረጃ እንቅስቃሴዎችን እስከ መግታት ደርሰዋል። ይህን በመመልከትም ጃፓን በአንፃራዊነት የተሻለ ሁኔታ ላይ እንደምትገኝ የሚናገሩ አሉ። ከቀናት በፊት የእንግሊዝ መንግሥት የጤና ቢሮ ሃላፊ ክሪስ ዊቲይ በአይነቱ ልዩ የሆነና በፍጥነት የመዛመት ባህሪ ያለው የኮቪድ-19 ቫይረስ በአገሪቱ እንደተገኘ ለዓለም ጤና ድርጅት ጭምር በማሳወቅ ጥንቃቄ እንዲደረግ ማሳሰቡ ይታወቃል። በአገሪቱ የቫይረሱ ሥርጭት በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ በመምጣቱም ጠቅላይ ሚኒስትር ቦሪስ ጆንሰን በአዲስ ዓመትና በገና በዓል ዋዜማዎች ወቅት በሚደረጉ መዝናኛዎች ላይ ጠንካራ እግድ አስቀምጠዋል። መዲናዋ ለንደንን ጨምሮ ቫይረሱ በስፋት በተሰራጨባቸው የደቡብ እንግሊዝ ከተሞችም ጠንካራ የተባሉ ገደቦች ተጥለዋል።አስቀድሞ በቫይረሱ ከፉኛ የተጠቃችው ጣሊያንን ጨምሮ ኔዘርላንድስና ጀርመን እስከ አዲሱ ዓመት ድረስ ማንም ከቤቱ እንዳይወጣ እግድ አስቀምጠዋል። አውስትራሊያም ከገና በዓል በኋላ ተመሳሳይ እርምጃ እንደምትወስድ መረጃዎች ጠቁመዋል። በቅርቡ በቤልጂየም ብራሰልስ የተካሄደውን የአውሮፓ ሕብረት ስብሰባ ከተካፈሉ በኋላ የፈረንሳይ ፕሬዚዳንት ኢማኑዔል ማክሮንና የስሎቫኪያው ጠቅላይ ሚኒስትር ኢጎር ማቶቪች እንዲሁም ሌሎች የአገር መሪዎች በኮቪድ-19 መያዛቸው ይታወቃል። ባለፈው ዓመት በቫይረሱ ሥርጭት ስጋት የገባቸው የኦሊምፒክ አዘጋጆች ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ ታላቁን የስፖርት መድረክ ለማራዘም መገደዳቸው ይታወቃል። በዚህም የተነሳ አዘጋጅ ኮሚቴው ሁለት ነጥብ ስምንት ቢሊየን ዶላር ኪሳራ እንደደረሰበት ከወር በፊት አሳውቋል። ወረርሽኙ ዳግም በከፍተኛ ሁኔታ ማገርሸቱን ተከትሎም የቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ ላይ ጥያቄ ተነስቷል። የዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ፕሬዚዳንት ቶማስ ባኽን ጨምሮ የተለያዩ ሃላፊዎች ግን አሁንም ውድድሩን በጥንቃቄ ለማካሄድ ሃሳብ አለወጡም።ቶኪዮ በኦሊምፒኩ ወቅት ወረርሽኙን ለመቆጣጠር በምትወስደው እርምጃ ከዘጠኝ መቶ ስልሳ ሚሊየን ዶላር በላይ ወጪ እንደምታደርግ የተዘገበ ሲሆን፣ የውድድሩ አዘጋጆች ቫይረሱን ለመዋጋት ከአገሪቱ መንግሥት ጋር በየጊዜው ውይይት እያደረጉ ይገኛሉ። በኦሊምፒኩ የሚሳተፉ አትሌቶችና የስፖርት ልዑካን ቡድኖች የፊት ጭምብል ማጥለቅና ርቀትን መጠበቅ እንደሚገባቸው አዘጋጆቹ በቅርቡ ጠቁመዋል፤ ከውድድሩ በኋላ በጃፓን የሚቆዩበት ጊዜ አጭር እንደሚሆንም አሳውቀዋል።እንግሊዝ፣ አሜሪካ፣ ቻይናና ሩሲያን የመሳሰሉ የተለያዩ አገራት ለወረርሽኙ መፍትሄ ይሆን ዘንድ የተለያዩ ክትባቶችን በማምረት የተሳካ ሙከራ እንዳደረጉ መናገር ከጀመሩ ሰንብተዋል። ክትባቱ በምን አይነት ፍጥነት ለዓለም ሕዝብ ተዳርሶ የቶኪዮ ኦሊምፒክ ከስጋት ነፃ በሆነ መልኩ ይካሄዳል የሚለው የብዙዎች ጥያቄ ነው። በኦሊምፒኩ ለመሳተፍ ወደ ቶኪዮ የሚያቀኑ ከቫይረሱ ነፃ የሆኑ አትሌቶች ክትባቱን ለማግኘት ቅድሚያ ይሰጣቸዋል አይሰጣቸውም የሚሉ ጥያቄዎችም ከወዲሁ እየተነሱ ይገኛሉ።የዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ፕሬዚዳንት ቶማስ ባኽ ባለፈው ወር በጃፓን ባደረጉት ጉብኝት ወቅት የተሳካ የኮቪድ-19 ክትባት ተገኘ መባሉን ተከትሎ እንኳን ስፖርተኞች የስፖርቱ አፍቃሪዎች ስቴድየም ገብተው የኦሊምፒክ ውድድሩን ካለ ስጋት እንደሚመለከቱ እርግጠኛ ሆነው ሲናገሩ ተደምጠዋል።የጃፓን መንግሥትና የዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ አትሌቶች የወረርሽኙን ክትባት እንዲያገኙ የተለያዩ ጥረቶችን እያደረጉ ይገኛሉ። ከዚህ ባሻገር በኦሊምፒኩ የሚሳተፉ አትሌቶችና የስፖርት ቤተሰቦች ወረርሽኙን ለመከላከል የተለያዩ ጥብቅ መመሪያዎችን ማክበር እንደሚገባቸው ቀደም ሲል አዘጋጆቹ አሳውቀዋል።ባለፈው ዓመት ወረርሽኙ በኦሊምፒኩ አዘጋጅ ጃፓንም ይሁን በሌሎች አገራት እንዲህ እንዳሁኑ ባልጠነከረበት ወቅት ለመራዘም የተገደደውን ይህን ውድድር፣ ዘንድሮ ወረርሽኙ ‹‹ክትባት ተገኝቶለታል›› እየተባለም መልኩን እየቀያየረ የብዙዎች ስጋት በሆነበት ጊዜ እንዲካሄድ መወሰን ለብዙዎች አልተዋጠም። ዓለም አቀፉ የኦሊምፒክ ኮሚቴውም ይሁን የጃፓን መንግሥት ውድድሩን ለማካሄድ እርግጠኛ ሆነው እየተንቀሳቀሱ የሚገኙትም ኦሊምፒኩ ካልተካሄደ የሚደርስባቸውን ትልቅ ኪሳራ በማስላት ሊሆን እንደሚችል ትችቶች ይሰነዘራሉ።ኦሊምፒኩ ባለፈው ዓመት መካሄድ ሲገባው ወደ ዘንድሮ በመራዘሙ ብቻ ሁለት ነጥብ ስምንት ቢሊየን ዶላር ኪሳራ እንዳደረሰ የቅርብ ጊዜ መረጃዎች ይጠቁማሉ። ይህን ኪሳራ ለመሸፈን የቶኪዮ ከተማ አንድ ነጥብ አንድ ቢሊየን ዶላር ወጪ እንዳደረገ ተዘግቧል፤ የውድድር አዘጋጅ ኮሚቴው አንድ ቢሊየን ዶላር ወጪ አድርጓል። ቀሪውን ሰባት መቶ ሚሊየን ዶላር ደግሞ የጃፓን መንግሥት እንደሚሸፍን ታውቋል። ኦሊምፒኩ ከመራዘሙ አስቀድሞ አስራ ሦስት ቢሊየን ዶላር ወጪ እንደሚጠይቅ ተገልጿል።በዘንድሮው ዓመት ሳይካሄድ ከተራዘመ ወይም ከተሰረዘ ቀድሞ ከተያዘለት በጀት እስከ አራት እጥፍ ኪሳራ ሊያደርስ እንደሚችል መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡አዲስ ዘመን ታህሳስ 16/2013
https://www.press.et/Ama/?p=38136
827
2ስፖርት
ምክር ቤቱ አቅጣጫና ውሳኔ እንደሚያሳልፍ ይጠበቃል
ስፖርት
December 28, 2020
9
ብርሃን ፈይሳ አዲስ አበባ፡- ብሄራዊ የስፖርት ምክር ቤት ነገ የመጀመሪያ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤውን እንደሚያከናውን ተገለጸ። በጉባኤው ላይም አቅጣጫዎችን እንደሚሰጥና ውሳኔዎችንም እንደሚያስተላልፍ ይጠበቃል። የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን በሰጠው መግለጫ እንዳስታወቀው፤ብሄራዊ የስፖርት ምክር ቤቱ ባለፈው ዓመት ህዳር 4 ቀን 2012 ዓ.ም መስራች ጉባኤውን ማካሄዱ ይታወሳል፤ ይሁን እንጂ ኮቪድ 19 በኢትዮጵያ መከሰትን ተከትሎ የመጀመሪያ ጠቅላላ ጉባኤውን በተያዘለት ወቅት ማካሄድ አልተቻለም። በመሆኑም ነገ የመጀመሪያ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤውን ያከናውናል። በጉባኤው ላይም የጉባኤው አባላት የሆኑት፤ የክልልና ከተማ አስተዳደር ርዕሳነ መስተዳድሮች ከንቲባዎች፣ ከዘጠኝ ሚኒስትር መስሪያ ቤቶች የተወጣጡ ሚኒስትሮች፣ የስፖርት ኮሚሽነሮች፣ የሃገር አቀፍ ስፖርት ማህበራት አመራሮች፣ የስፖርት ተቋማት እንዲሁም ለስፖርት ጉልህ ሚና ያላቸው የክብር እንግዶች ይገኛሉ። የጉባኤው አጀንዳዎችም የመስራች ጉባኤውን አጀንዳ ማጽደቅ፣ በወቅቱ የተሰጡ አቅጣጫዎችን አፈጻጸም መገምገም፣ በቀጣይ በትኩረት የሚከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት፣ የ10 ዓመቱ መሪ እቅድና የ2013 በጀት ዓመት እቅድ እንዲሁም ልዩ ልዩ መመሪያዎችን አቅርቦ ማጸደቅ የሚሉት መሆናቸው ተጠቁሟል። አጀንዳዎቹን ተከትሎ አቅጣጫ እንደሚሰጥና ውሳኔዎችም እንደሚያስተላለፉ ይጠበቃል።የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽነር ኤሊያስ ሽኩር ጉባኤው ትኩረት የሚሰጥበት አጀንዳም ምክር ቤቱ በመስራች ጉባኤ ወቅት ያስቀመጣቸው ውሳኔዎችና አቅጣጫዎች አፈጻጸምን በዝርዝር ተመልክቶ መገምገምን የተመለከተ መሆኑን አስታውቀዋል። የሃገሪቷ ስፖርት መሰረታዊ ችግሮችና መፍትሄ የሚል ጥናት በማካሄድ በተዘጋጀው የሪፎርም ሰነድ ምክር ቤቱ ተወያይቶ በዝርዝር እንዲከናወኑ አቅጣጫ የሰጣቸው ጉዳዮች ላይ ግምገማ የሚያካሂድም መሆኑን ተናግረዋል። እንደ ኮሚሽነሩ ገለጻ፤ከአቅጣጫዎቹ መካከል አንዱ ባለድርሻ አካላትን በማወያየት ሰነዱ እንዲዳብር ነበር፤ ይህም እስከ ታችኛው እርከን በመውረድ የማዳበር ስራው ተከናውኗል። ሰነዱ ሲዘጋጅ የተቀመጡት ምክረ ሃሳቦች በእቅድ እንዲካተቱ በተቀመጠው አቅጣጫ መሰረት በ10 ዓመቱ ስትራቴጂክ እና የዓመቱ እቅድ ላይ እንዲካተት ተደርጓል። አሰራሮችን ከመፈተሽና አዳዲስ የአሰራር ማኑዋሎችን ከመፍጠር ረገድም የስፖርት ፖሊሲውን የማሻሻል ስራ ተጀምሯል፣ ሃገሪቷ የሌላት የስፖርት ህግም እየተረቀቀ ነው፣ ሃገር አቀፍ የስፖርት ማህበራት የሚመዘኑበት ስታንዳርድ የማዘጋጀት፣ የማዘውተሪያ ስፍራዎች ስታንዳርድና የስፖርት ፈንድ ሰነድ ማዘጋጀት እንዲሁም የስፖርት መመሪያ በማሻሻል ረገድ ያሉትን ፈትሾ በማስተካከልና የሌሉትን አዳዲስ በማዘጋጀት የተሳካ ስራ ማከናወን ተችሏል። ተጠናቀው ወደ ስራ የገቡ መኖራቸውንና ሌሎች ደግሞ እርከኑን ጠብቆ በሌሎች አካላት መጽደቅ ያለባቸውም በሂደት ላይ ይገኛሉ።የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎችን፣ የስልጠና ማዕከላትና የስፖርት ቁሳቁስን በሚመለከትም ትልልቅ ግንባታዎች በተያዘላቸው ጊዜና በጥራት እንዲጠናቀቁ እየተሰራም መሆኑም በመግለጫው ተጠቁሟል። ከጥርጊያ ሜዳ ጀምሮ በየአካባቢው ያሉ ማዘውተሪያዎችም የባለቤትነት ማረጋገጫ እንዲኖራቸውና እጥረት ባለባቸውም ተጨማሪ እንዲያገኙም እየተደረገ ነው። ያሉት የስልጠና ማዕከላትም በሙሉ አቅማቸው እንዲሰሩ የማድረግ ስራ እየተሰራ ከሚሽነሩ ጠቅሰው፣ በአማራና ኦሮሚያ ክልሎች ከማስፋፋት አኳያ ያለው ተነሳሽነትም መልካም የሚባል መሆኑን ኮሚሽነሩ ይጠቁማሉ። የህዝብ ተሳትፎን በሚመለከትም ኮቪድን እንደ ምክንያት በመጠቀም በህብረተሰቡ ዘንድ መነሳሳትን በመፍጠር ረገድ የተሻለ ጅማሮ ታይቷል ብለዋል። በጉባኤው ላይ በህብረተሰቡ የስፖርት ተሳትፎ ፍትሃዊነትና ተደራሽነት ላይም ውይይት ይደረጋል ተብሏል። በስፖርት አደረጃጀት ላይ ሕዝባዊ አካሉ በምን መልክ ሊደራጅ ይገባዋል የሚለውም ሌላው ውይይት የሚደረግበት መሆኑ ተጠቁሟል። በመግለጫው ላይ እንደተመለከተው፤ በ2011 ዓም አሳሳቢ የነበረው የስፖርታዊ ጨዋነት መጓደልም በወረርሽኙ መከሰት ውድድሮች እስከተቋረጡ ድረስ ውጤታማ ስራዎችን ማከናወን ተችሏል። ኮቪድ 19 በኢትዮጵያ ከተከሰተ ወዲህም በስፖርቱ ላይ ያስከተላቸው ጉዳቶችን እና ቫይረሱ እያለ እንዴት ወደ ስፖርታዊ እንቅስቃሴ መገባቱን ተከትሎ ክትትል ለሚያደርገው ኮሚቴ አቅጣጫ የሚሰጥም ይሆናል። በቀጣይ የሚካሄዱ ሃገር እና ዓለም አቀፍ ውድድሮችን በሚመለከትና ለሚቀጥለው የቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ በምን መልክ ውጤት ማስመዝገብ ይቻላል በሚለው ላይም ምክር ቤቱ ይመክራል።
https://www.press.et/Ama/?p=38365
448
2ስፖርት
የከተማ አቀፍ አካል ብቃት እንቅስቃሴ ተመልሷል
ስፖርት
December 29, 2020
7
ቦጋለ አበበ ከተማ አቀፍ የአካል ብቃት ስፖርታዊ እንቅስቃሴ በአዲስ አበባ አዲሱ ለሚ ኮራ ክፍለ ከተማ በደማቅ ሁኔታ በይፋ ተጀምሯል። የአካል ብቃት እንቅስቃሴው ‹‹ለሀገሬ ሰላም ዘብ እቆማለሁ፤ ለመከላከያ ሰራዊት ቅድሚያ እሰጣለሁ›› በሚል መሪ ቃል በየካ አባዶ የጋራ መኖሪያ ቤቶች አደባባይ ከትናንት በስቲያ የተካሄደ ሲሆን በርካታ ቁጥር ያላቸው የአካባቢው ነዋሪዎችም ተሳታፊ ሆነዋል ። በመርሃ ግብሩ ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የመንግሥት አገልግሎት ሰጪ ተቋማት አስተባባሪ አቶ ጃንጥራር አባይ፣ ‹‹በስፖርት የተገነባ ኃይል የትኛውንም ጠላት መመከት ይችላል፤ በመሆኑም በየትኛውም አካባቢ በተገኘው ቦታ ሁሉ ስፖርታዊ እንቅስቃሴ በማድረግ እራሳችንን ከበሽታ ልንከላከል ይገባል›› ብለዋል። ለዚህም ከተማ አስተዳደሩ ድጋፍ እንደሚያደርግ ገልጸዋል። ‹‹መከላከያችን ባደረገው የሰላም ማስከበር ተልዕኮ በአጭር ጊዜ ውስጥ ድል የተቀዳጀው በስፖርት የተገነባ ስለሆነ ነው፣ መከላከያችንን እያሰብን ሁሌም ስፖርትን ባህላችን ልናደርግ ይገባል›› በማለትም አቶ ጃንጥራር  ተናግረዋል::የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ኤሊያስ ሽኩር በበኩላቸው፣ የማህበረሰብ አቀፍ ስፖርታዊ እንቅስቃሴ በሁሉም የማህበረሰብ ክፍሎች በፍታሐዊነት ተደራሽ እና ባህል እስኪሆን ድረስ ከሚመለከታቸው አካላት በጋራ እንደሚሰሩ ገልጸዋል::በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ምክንያት ለረጅም ወራት ተቋርጦ ከትናንት በስቲያ የተጀመረው ከተማ አቀፍ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ መርሃ ግብር በየሳምንቱ በአስራ አንዱም የአዲስ አበባ ክፍለ ከተሞች በወጣው መርሃ ግብር መሠረት ለአንድ ወር የሚቀጥል ሲሆን በሚቀጥለው ሳምንት በየካ ክፍለ ከተማ እንደሚካሄድ ታውቋል።በአካል ብቃት ስፖርታዊ እንቅስቃሴው ላይ የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ፕሬዚዳንት ዶክተር አሸብር ወልደጊዮርጊስ፣ የአዲስ አበባ ከተማ ስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነር በላይ ደጀን፣ የለሚ ኩራ፣ የቦሌና የየካ ክፍለ ከተሞች ዋና ስራ አስፈፃሚዎች እንዲሁም በርካታ ቁጥር ያላቸው የየካ አባዶ የጋራ መኖሪያ ቤት ነዋሪዎች ተሳታፊ ሆነዋል።የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስፖርት ኮሚሽን የከተማዋን ሁለንተናዊ የስፖርት ልማት፣ የስፖርት ንቅናቄ ፣ የስፖርት ተሳታፊነትና ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ በቁርጠኝነት እየሰራ እንደሚገኝ የተገለጸ ሲሆን ስፖርት ለሰላም፣ ለአንድነት፣ ለፍቅር፣ ለጤንነት፣ ለመቻቻል፣ ለአብሮነት፣ ለልማትና ለትብብር ያለው ፋይድ ታላቅ መሆኑን ስፖርት በተግባር እያሳየ እንደሚገኝም ተጠቁሟል፡፡አዲስ ዘመን ታኅሣሥ 20/2013
https://www.press.et/Ama/?p=38442
264
2ስፖርት
አዳዲስ የአትሌቲክስ ማዘውተሪያዎች ግንባታ ይከናወናል
ስፖርት
December 24, 2020
10
ብርሃን ፈይሳአዲስ አበባ፡- ለአትሌቲክስ ስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራ የሚሆኑ ቦታዎች ምልከታ ተደረገ። ማዘውተሪያዎቹ በአዲስ አበባ አቅራቢያ በሚገኙ አራት ከተሞች ላይ የሚገኙ መሆኑም ታውቋል። በቅርቡ በለገጣፎ ለገዳዲ ከተማ አስተዳደር የተመረቀውን የአትሌቲክስ ስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራ ተከትሎ ሌሎች ግንባታዎችም እንደሚከናወኑ ተጠቁሞ ነበር። በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ ላይ የተገኙት የኦሮሚያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ምክትል ፕሬዚዳንት ሽመልስ አብዲሳ፤ ከለገዳዲ ለገጣፎ ባሻገር በተለያዩ ከተሞች በአጭር ጊዜ ቦታ በማዘጋጀት ተጨማሪ ማዘውተሪያ ስፍራዎች እንደሚገነቡ ጠቁመው ነበር። የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን በድረገጹ እንዳስታወቀው፤ለማዘውተሪያ ስፍራዎቹ ግንባታ በሚሆኑ ስፍራዎች ላይ ሰሞኑን ምልከታ ተከናውኗል። በመልክታው መሰረት ማዘውተሪያዎቹ የሚገነቡት በአዲስ አበባ አቅራቢያ በሚገኙት አራት ከተሞችም ቡራዩ ፣ ሰበታ ፣ ዱከም እና ሱልልታ ይሆናል። ለግንባታውም በቡራዩ 50 ሄክታር፣ በሰበታ 8 ነጥብ 5 ሄክታር፣ በዱከም 23 ሄክታር እንዲሁም በሱልልታ 20 ሄክታር መሬት ተዘጋጅቷል። በምልከታው ላይም የኢፌዴሪ ባህልና ቱሪዝም ሚኒስትር ዶክተር ሂሩት ካሳው፣ ሚኒስትር ዲኤታው ሃብታሙ ሲሳይ፣ የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽነር ኤሊያስ ሽኩር፣ ምክትል ኮሚሽነር ዱቤ ጂሎ፣ የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ፕሬዚዳንት ዶክተር አሸብር ወልደጊዮርጊስ፣ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ደራርቱ ቱሉ እና ምክትል ፕሬዚዳንቱ ገዛኸኝ አበራ እንዲሁም የኦሮሚያ ስፖርት ኮሚሽን አመራሮች ተገኝተዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 15/2013
https://www.press.et/Ama/?p=38042
164
2ስፖርት
የአገር አቋራጭ ሩጫና የፆታ እኩልነት ሙግቶች
ስፖርት
December 26, 2020
9
በታሪክ አጋጣሚ ቀደም ባሉት ዓመታት በተለያዩ የአትሌቲክስ ውድድሮች ወንድና ሴት አትሌቶች በተለያዩ ርቀቶች በተመሳሳይ ውድድር ላይ ሲሮጡ መመልከት የተለመደ ነው። ‹‹ወንዶች የሚሮጡትን ርቀት ሴቶች መሮጥ አይችሉም›› የሚል አስተሳሰብ በነበረበት ዘመን በተመሳሳይ ውድድር ላይ ሴቶች ከወንዶች ያነሰ ርቀት ለመሮጥ ይገደዱ ነበር። እንዲያውም በአንዳንድ ዓለም አቀፍ የውድድር መድረኮች ላይ ወንዶች በሚሮጡበት ርቀት ሴቶች እንደማይወዳደሩ ከታሪክ መረዳት ይቻላል። ለምሳሌ ያህል በታላቁ የዓለማችን የስፖርት መድረክ ኦሊምፒክ ማራቶን አንጋፋና ምናልባትም ከመጀመሪያ አንስቶ የሚካሄድ የውድድር አይነት ቢሆንም ሴቶች በርቀቱ መወዳደር የጀመሩት ዘግይተው ነው።በኦሊምፒክ መድረክ ብቸኛው የጎዳና ላይ ውድድር በሆነው ማራቶን ወንዶች መሳተፍ የጀመሩት እኤአ 1896 ላይ ነው። የሴቶች ማራቶን የኦሊምፒክ ውድድር ውስጥ የተካተተው ግን ዘጠና ዓመታትን ዘግይቶ በ1984 ኦሊምፒክ ነበር። ከማራቶን በተጨማሪም በርካታ በተለይም ረጅም ርቀት ውድድሮች በኦሊምፒክም ይሁን በዓለም ቻምፒዮና ሴቶችን ማካተት የጀመሩት ዘግይተው ነው። ይሁን እንጂ በዘመናዊው የአትሌቲክስ ዓለም ሴቶች ወንዶች በሚወዳደሩበት ርቀት ሙሉ በሙሉ ለማለት በሚያስችል ደረጃ ተወዳዳሪ ናቸው።ከአታካቹ ማራቶን አንስቶ እስከ ተለያዩ የጎዳና ላይ ውድድሮች ሴቶች ወንዶች የሚሮጡትን ርቀት በመሮጥ ብቃታቸውን አስመስክረዋል። ርቀቶቹን ሮጠው  ለማጠናቀቅ የሚፈጅባቸው ሰዓት ከተፈጥሮ ጋር በተያያዘ ከወንዶች የዘገየ ቢሆንም የትኛውንም ርቀት ሴቶች አይሮጡም ብሎ የሚያምን ሰው ፈልጎ ማግኘትም ከባድ የሚመስልበት ዘመን ላይ ተደርሷል። ይሁንና ሴቶች በአገር አቋራጭ ውድድሮች ላይ ከወንዶች ያነሰ ርቀት እንዲሮጡ መደረጉ በአትሌቲክሱ ቤተሰቦች መከራከሪያ አጀንዳ ከሆነ ዓመታት ተቆጥረዋል።እንግሊዛዊቷ የቀድሞ የአገር አቋራጭ ቻምፒዮና የሜዳሊያ ባለቤት አትሌት ጆ ፓቬይ «በአገር አቋራጭ ውድድሮች ሴቶች ከወንዶች ባነሰ ርቀት መወዳደራቸው የፆታ እኩልነትን አያሳይም» የሚል አስተያየት ከሁለት ዓመት በፊት ለስካይ ኒውስ መስጠቷን ተከትሎም የአገር አቋራጭ ውድድር አዘጋጆች ከአትሌቲክስ ቤተሰቡ ጋር ሙግት ገጥመው እንደነበር ይታወሳል። በርካታ የስፖርቱ ባለሙያዎችና የውድድር አዘጋጆችም በጉዳዩ ላይ ሲሟገቱ ይስተዋላል። አገር አቋራጭ ውድድሮች በየዓመቱ በተለያዩ ከተሞች በተለይም በአውሮፓ ይካሄዳሉ። የዓለም አትሌቲክስም በየሁለት ዓመቱ የዓለም አገር አቋራጭ ቻምፒዮና ያዘጋጃል። በእነዚህ ውድድሮች ሴትና ወንድ አትሌቶች በእኩል ርቀት ሲወዳደሩ አይታይም። እኤአ ከ2017 በፊት በዓለም አገር አቋራጭ ቻምፒዮና የሚካሄደው ፉክክር በአራት አይነት መንገድ ተከፍሎ ነው። የመጀመሪያው አዋቂ ወንዶች የሚወዳደሩበት የአስራ ሁለት ኪሎ ሜትር ውድድር ሲሆን አዋቂ ሴቶች ስምንት ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ርቀት ላይ ብቻ ተፎካካሪ ነበሩ። በወጣት ወንዶች መካከል የሚካሄደው ውድድር ደግሞ ስምንት ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ሲሆን ወጣት ሴቶች ስድስት ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ፉክክር ያደርጋሉ። እነዚህ ርቀቶች በዓለም ቻምፒዮናም ይሁን በግል አገር አቋራጭ ውድድሮች በብዛት የተለመዱ ናቸው። አልፎ አልፎ ግን በዓለም ቻምፒዮናም ይሁን በግል ውድድሮች እንደየሁኔታው ወንዶች ከሴቶች እኩል ርቀቶችን የሚሮጡበት አጋጣሚ ሲፈጠር ይታያል። ለአብነት ያህልም በ2017 በዩጋንዳ ካምፓላ ተካሂዶ የነበረው የዓለም አገር አቋራጭ ቻምፒዮናን ማንሳት ይቻላል። በዚህ ቻምፒዮና ለመጀመሪያ ጊዜ አዋቂ ሴቶችና ወንዶች እኩል አስር ኪሎ ሜትር የሸፈነ ውድድር ማድረጋቸው ይታወሳል። «ታዲያ ሴቶች በዚህ ውድድር ከወንዶች እኩል መሮጥ እየቻሉ አነስተኛ ርቀት እንዲሮጡ መደረጋቸው ለመጪው ትውልድ ምን አይነት መልዕክት ያስተላልፋል?» የሚል ከጾታ እኩልነት አኳያ ጥያቄ የሚያነሱ ቁጥራቸው ብዙ ነው።በምስራቅ ለንደን የአትሌቶች ማህበር አባል የሆነችው ማዑድ ሆድሰን በዚህ ውድድር የጾታ እኩልነት መረጋገጥ ካለበት ሴትም ወንድም እኩል ርቀት መሮጥ አለባቸው የሚል አቋም ይዛ ባለፉት ዓመታት ስትከራከር ቆይታለች። ይህን ሃሳቧንም በርካቶች ደግፈውታል። ሆድሰን በጉዳዩ ላይ ለራነርስ ዌብ ከዓመታት በፊት እንደገለፀችው፣ በአገር አቋራጭ ውድድሮች ሴትና ወንድ እኩል ርቀት እስካልሮጡ ድረስ መጪው የአትሌቲክስ ትውልድ በሩጫው ዓለም ሴትም ወንድም እኩል መሆናቸውን ሊረዳ አይችልም። ወንዶች ከፍ ያለውን ርቀት መሮጣቸው በአገር አቋራጭ ውድድሮች የሴቶቹ ፉክክር ከወንዶቹ ያነሰ የሚመስል ትርጉም ይሰጠዋልም ትላለች። ሆድሰን በዚህም ሳታበቃ በጉዳዩ ላይ አንድ መፍትሄ ለማምጣት በኤሌክትሮኒክስ መንገድ ፊርማ አሰባስባ በቀናት ውስጥ ከአንድ ሺ በላይ ተከታዮችን አግኝታለች። ይህ ሃሳብ በፌስ ቡክ ገፅም«አይ ወዝ ኦር አም ራነር» በሚል በተፈጠረ የቡድን ገፅም በርካታ ወንዶች የደገፉት ሲሆን ብዙ ተከታዮች አግኝቶ መነጋገሪያነቱ እየጨመረ መጥቷል።አዳጋች በሆነው የአገር አቋራጭ ውድድር አትሌቶች በጭቃ፤ በዳገትና ቁልቁለት አልፎ አልፎም በበረዶ ይፈተናሉ። ይህን ከግምት የሚያስገቡ በርካታ ሰዎች ሴቶች በውድድሩ እንደ ወንዶች ረጅም ኪሎ ሜትር መሮጥ አይችሉም የሚል አስተሳሰብ እንዲይዙ ያደርጋቸዋል። አንዳንድ ጥናቶች እንደሚያመላክቱት ግን ሴቶች በሌሎች ፈታኝ በሚባሉ ማራቶንና ግማሽ ማራቶን ውድድሮች ላይ ከወንዶች እኩል ርቀት ሮጠው ከሚያስመዘግቡት የሰዓት ልዩነት የተጋነነ አያስመዘግቡም። በቢኬት ዩኒቨርሲቲ የስፖርት ሳይንስና ባዮሜካኒክስ መምህርና ተመራማሪ የሆኑት ብሬን ሃንሌይ ጥናታዊ ፅሁፍ ግን በአገር አቋራጭ ውድድር ሴቶች ከወንዶቹ ባልተናነሰ ተመሳሳይ ርቀት መወዳደር እንደሚችሉ ይጠቁማል። ጥናቱ ልክ እንደ ወንዶቹ የሴቶቹም ውድድር መጀመሪያ ላይ ቀዝቃዛ ፉክክር የሚታይበት ቢሆንም መጨረሻው በፉክክር የታጀበ እንደሚሆን አረጋግጧል። አብዛኞቹ የውድድር አዘጋጆች ግን ሴቶች በዚህ ውድድር ከወንዶች እኩል ርቀት ቢሮጡ መጨረሻው በፉክክር እንደማይታጀብና አሰልቺ እንደሚሆን ስለሚያምኑ ሴቶች አነስተኛ ርቀት እንዲወዳደሩ ያደርጋሉ የሚል ክርክር ይነሳል። ይህ ግን ዞሮ ዞሮ ከፆታ እኩልነት ጋር ባይያያዝ እንኳን በርካታ ወጣት አትሌቶችን ወደ ውድድሩ እንዳይመጡ ምክንያት ሊሆን እንደሚችል መላ ምቶች ይቀመጣሉ። ይህም ርቀቱ በረዘመ ቁጥር በርካታ አትሌቶች እንደ ጎዳና ላይ ረጅም ርቀት ውድድሮች ሁሉ የመወዳደራቸው አጋጣሚ ሰፊ ይሆናል የሚል ነው።የአርባ ስድስት ዓመቷ ጆ ፓቬይ አትሌቲክስን ካቆመች በርካታ ዓመታት ቢቆጠሩም ሴቶች በአትሌቲክሱ ዓለም አስደናቂ ታሪኮችን ከወንዶች እኩል መስራታቸውን በማስታወስ በአገር አቋራጭ ውድድሮችም ከወንዶች እኩል ርቀት መሮጥ እንዳለባቸው ከስካይ ኒውስ ጋር በነበራት ቆይታ ገልፃለች። «ለበርካታ ዓመታት በአስቸጋሪው የማራቶን ውድድር ሴቶች ከወንዶች እኩል ርቀት ሲወዳደሩ ቆይተዋል፤ በአገር አቋራጭ ውድድሮች እኩል ርቀት ያለመሮጣቸው ሴቶች ከወንዶች እኩል አቅም የላቸውም የሚል አመለካከትን ይፈጥራል» በማለትም ፓቬይ አቋም ይዛለች።የማራቶን ባለክብረወሰኗና የቀድሞ የዓለም አገር አቋራጭ ቻምፒዮኗ አትሌት ፓውላ ራድክሊፍ ሰሞኑን በጉዳዩ ላይ በማህበራዊ ሚዲያው የሚደረገውን ክርክር ተቀላቅላ ‹‹ርቀቶች መመሪያ ናቸው፣ የአገር አቋራጭ መወዳደሪያ ቦታዎች ጥሩ ከሆኑ በሁለቱም ፆታ ተመሳሳይ ርቀት ቢሮጥ ችግር የለውም፣ የውድድሩ ተፈጥሯዊ ባህሪ ሆኖ አንዳዶች አጭር ርቀት መሮጥ ሲፈልጉ ሌሎች ረጅም መሮጥ ሊፈልጉ ይችላሉ፣ ወንድም ሴትም ተመሳሳይ ርቀት መሮጥ እንደሚችሉ ግን አምናለሁ›› በማለት ፅፋለች። የአገር አቋራጭ ውድድር አዘጋጆች ይህ ልዩነት ለምን እንደተፈጠረ አሳማኝ ምክንያት ማቅረብ ባይችሉም በተለምዶ ሲወርድ ሲዋረድ የመጣ በመሆኑ ብቻ አሁን ላይ እየተገበሩት እንደሚገኙ ይታመናል። ይህ ግን በአንዳንድ የስፖርት ቤተሰቦች የፆታ ልዩነት እንዳለ ለማሳየት ሆን ተብሎ የተደረገ ሳይሆን የሴቶቹን ፉክክር ረዘም ላለ ሰዓት መመልከት ስለማይፈለግ ነው የሚል ትችት ይቀርባል። የእንግሊዝ አገር አቋራጭ ውድድር ማህበርም ይህ ልዩነት በተለምዶ አሰራር የመጣ መሆኑን በማመን በአገር አቀፍ ውድድር ላይ ሴቶች ከወንዶች እኩል ርቀት መሮጥ እንዳለባቸው ሲከራከርና ተፅዕኖ ሲያሳድር ቆይቷል። በዚህም የእንግሊዝ አትሌቲክስ ማህበርን ድጋፍ ማግኘት ችሏል። የእንግሊዝ አትሌቲክስ ማህበርም ጥያቄውን ወደ ፊት በማምጣት የተለያዩ ሙግቶችን ሲያደርግ ቆይቷል። ለረጅም ጊዜ ጉዳዩ የተዘነጋና ተድበስብሶ ያለፈ ቢመስልም የእንግሊዝ አትሌቲክስ ማህበር ከቀናት በፊት ዳግም ጉዳዩን በማንሳት በጥናት ጭምር አስደግፎ እየተሟገተ ይገኛል። አትሌቲክስ ማህበሩ በፈጠረው ተፅዕኖ በአገሪቱ በሚደረጉ የአገር አቋራጭ ውድድሮች ላይ ለውጦች ማምጣት ቢችልም በዓለም አቀፍ ደረጃ የተለያዩ የውድድር አዘጋጆችን ለማሳመን ተጨማሪ ስራዎች ይቀሩታል። ለዚህም የአውሮፓ አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ላይ የሰራውን ጥናት ሰሞኑን ይፋ አድርጓል። 2016 ላይ ከሃምሳ አንድ የአውሮፓ አገራት አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ሰላሳ ሰባቱ ለጥናቱ ምላሽ የሰጡ ሲሆን ከሰላሳ ሰባቱ ሃያ አንዱ ሴቶችና ወንዶች በአገር አቋራጭ ውድድሮች እኩል ርቀት መሮጥ አለባቸው የሚል እምነት እንዳላቸው ጠቁሟል። አገር አቋራጭ ውድድር እንደ ረጅም ርቀት ውድድሮች ሁሉ በስፋት የሚታወቁት ምስራቅ አፍሪካውያኑ ኢትዮጵያና ኬንያ ቢሆኑም በጉዳዩ ላይ የተነሳው ሙግት ከወደ ምዕራባውያኑ መሆኑ አስገራሚ ነው። የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የቴክኒክ ዳይሬክተር የነበሩትና አሁን የፌዴራል ስፖርት ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር የሆኑት አቶ ዱቤ ጂሎ በአንድ ወቅት ከአዲስ ዘመን ጋር በነበራቸው ቃለ ምልልስ በዚህ ጉዳይ ላይ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ያለውን አቋም አሳውቀው ነበር። አቶ ዱቤ ይህ በሴቶችና በወንዶች አገር አቋራጭ ውድድሮች ላይ ያለው የመወዳደሪያ ርቀት በተለምዶ ሲሰራበት ስለመጣ እንጂ ሴቶች ወንዶች የሚሮጡትን ርቀት መሮጥ ስለማይችሉ የተፈጠረ እንዳልሆነ ያብራራሉ። የርቀቱ ልዩነት የመጣው ቀደም ሲል በውድድሩ ደንብ ላይ የተቀመጠ በመሆኑ እንጂ ከጤናም አኳያ ይሁን ከሌሎች ነገሮች ሴቶች በአገር አቋራጭ ውድድር ከወንዶች ያነሰ ርቀት እንዲሮጡ የሚያደርጋቸው ምንም አይነት አሳማኝ ምክንያት እንደሌለ ገልፀው ነበር። «ሴቶች ከወንዶች እኩል በአገር አቋራጭ ውድድር መሮጥ አለባቸው፤ ማራቶንም ይሁን ግማሽ ማራቶን እኩል እስከ ሮጡ ድረስ በአገር አቋራጭም እኩል ርቀት መሮጥ አለባቸው፤ ይህ ካልሆነ ማራቶንም እኩል ኪሎ ሜትር መሮጥ የለባቸውም» በማለትም አቶ ዱቤ ሃሳባቸውን ሰንዝረው ነበር። የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በየዓመቱ ጃን ሜዳ ኢንተርናሽናል አገር አቋራጭ ውድድሮችን በክልሎችና በክለቦች መካከል እንደሚያካሂድ ይታወቃል። በነዚህ ውድድሮች ወንዶቹም ሴቶቹም እኩል ርቀት የሚሸፍን ውድድር እንዲያካሂዱ ማድረግ ይቻላል ያሉት አቶ ዱቤ፣ ይህን ጥያቄ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ለዓለምአቀፉ አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር ሊያቀርብ እንደሚችልም ጠቁመዋል። ከዚያም ዓለምአቀፍ ማህበሩ አሁን ያለውን ህግ አሻሽሎ በተመሳሳይ ርቀት እንዲወዳደሩ ከፈቀደ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽንም በእኩል ርቀት ውድድሮቹን ለማካሄድ የሚያግደው ነገር እንደሌለ አብራርተዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 17/2013 ዓ.ም
https://www.press.et/Ama/?p=38194
1,192
2ስፖርት
የዓለም አትሌቲክስ በዶፒንግ ጉዳይ ጥርስ አውጥቷል
ስፖርት
December 28, 2020
10
ቦጋለ አበበ ኢትዮጵያ አበረታች ንጥረ ነገሮችን በመጠቀም በስፖርቱ ዓለም በተለይም በአትሌቲክስ ትልቅ ስጋት ካንዣበበባቸው የዓለማችን አምስት አገራት አንዷ እንደሆነች ጉዳዩ የሚመለከታቸው ዓለም አቀፍ ተቋማት ሲያሳስቡ ቆይተዋል። በተቃራኒው ኢትዮጵያ ይህን ስጋት ለመቀነስ ባለፉት ጥቂት ዓመታት በብሔራዊ ደረጃ የፀረ አበረታች ንጥረ ነገሮች ፅሕፈት ቤት አቋቁማ አበረታች ለውጥ ማምጣቷንም የዓለም አቀፉ ፀረ አበረታች ንጥረ ነገሮች ኤጀንሲ መስክሮላታል። ይሁን እንጂ ስጋት አለባቸው ከተባሉት አምስት አገራት ተርታ ለመውጣት ብዙ ስራ እንደሚጠብቃት ይታወቃል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ፀረ አበረታች ንጥረ ነገሮች ጽሕፈት ቤት አትሌቶች አውቀውም ይሁን ሳያውቁ የችግሩ ሰለባ እንዳይሆኑ የተለያዩ ግንዛቤዎችን ከማስጨበጥ ባሻገር የችግሩ ሰለባ ሆነው የተገኙ በርካታ አትሌቶች ላይ የቅጣት ውሳኔዎችን ሲያስተላልፍ ቆይቷል። ባለፈው ሳምንት አጋማሽ እንኳን አትሌት ወንድወሰን ከተማ ማሞና አትሌት እዮብ ኃብተስላሴ ጎሳ የስፖርት አበረታች ቅመሞች (ዶፒንግ) የሕግ ጥሰቶችን በመፈፀም ተጠርጥረው ላለፉት ጊዜያት ጊዜያዊ እገዳ ላይ ሆነው ጉዳያቸውን ሲያጣራ መቆየቱን ገልጿል። በዚህም መሰረት በተካሄደው ተጨማሪ ምርመራ አትሌት እዮብ ኃብተስላሴ ጎሳ እ.ኤ.አ የካቲት 02/2020 ዓ.ም ታይላንድ በተካሄደ ውድድር ላይ (Cathinone) የተባለውን የተከለከለ የስፖርት አበረታች ቅመም መጠቀሙ ተረጋግጧል። በዚህም አትሌቱ እ.ኤ.አ ከሚያዝያ 03/2020 ዓ.ም ጀምሮ ለተከታታይ አራት ዓመታት በማንኛውም ውድድር ላይ እንዳይሳተፍ ቅጣት ተጥሎበታል። በውድድሩ የተገኘው ውጤትና ውጤቱን ተከትሎ የሚሰጥ የእውቅና ሽልማትም እንዲሰረዝ ተወስኗል። በተመሳሳይ መልኩ አትሌት ወንድወሰን ከተማ ማሞ ቀደም ሲል (Cathinone) የተባለውን የተከለከለ የስፖርት አበረታች ቅመም መጠቀሙ በመረጋገጡ እ.ኤ.አ እስከ የካቲት 01/2024 ድረስ በማንኛውም ውድድር ላይ እንዳይሳተፍ እገዳ የተጣለበት መሆኑ ይታወቃል። ይሁን እንጅ አትሌቱ የተሳሳቱ የሰነድ ማስረጃዎችን በማቅረብ የህግ ጥሰት የማጣራት ሂደቱን በተለያየ መልኩ በማስተጓጎልና በድጋሚ ለማጭበርበር በመሞከር ተደራራቢ የህግ ጥሰት በመፈፀም ተጠርጥሮ ጉዳዩ ሲጣራ ቆይቷል። በመሆኑም አትሌት ወንድወሰን ያቀረባቸው ሰነዶች የሐሰት መሆናቸው በመረጋገጡና በፀረ- ዶፒንግ ህጉ አንቀፅ 2ነጥብ5 ላይ የተደነገገውን የፀረ-ዶፒንግ እንቅስቃሴውን የማስተጓጎልና አቅጣጫ የማሳት የህግ ጥሰት መፈፀሙ በመረጋገጡ ቀደም ሲል ከተጣለበት የአራት ዓመት የእገዳ ቅጣት በተጨማሪ የመጀመሪያው ቅጣት ከሚያበቃበት የካቲት 01/2024 ዓ.ም ጀምሮ ለተከታታይ ስምንት ዓመታት እስከ የካቲት 01/2032 ዓ.ም በማንኛውም ስፖርታዊ ውድድር  ላይ እንዳይሳተፍ የእገዳ ቅጣት ተላልፎበታል።የኢትዮጵያ ብሔራዊ የፀረ-አበረታች ቅመሞች ጽሕፈት ቤት በቀጣይም የምርመራና ቁጥጥር ስራውን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቋል። የዓለም አትሌቲክስም ከዶፒንግ ጋር በተያያዘ በስፖርቱ ትልቅ ክብርና ዝና ያተረፉ አትሌቶች ላይ ሳይቀር ጥርስ እንዳወጣ የሚጠቁም አቋም በሳምንቱ መጨረሻ ይፋ አድርጓል። ኢትዮጵያን ጨምሮ የዓለምን አትሌቲክስ በበላይነት የሚመራው ተቋምና ሌሎች አገራት ባለፉት ዓመታት ከዶፒንግ ጋር በተያያዘ በስፖርቱ ትልቅ ክብርና ዝና ካላቸው አትሌቶች ይልቅ እምብዛም በማይታወቁና በአንፃራዊነት በትንንሽ ውድድሮች በሚካፈሉ አትሌቶች ላይ ትኩረት እንዳደረጉ ወቀሳ ሲቀርብባቸው መቆየቱ ይታወቃል።ማህበሩ በተለይም የዓለም አትሌቲክስ የስፖርቱ ስም እንዳይጠለሽና የተለያዩ አጋሮቹን ላለማጣት ሲል በስፖርቱ ትልቅ ስምና ዝና ላላቸው አትሌቶች ሽፋን እንደሚሰጥ ምክንያታዊ ሙግቶችን የሚያቀርቡ በርካታ ናቸው። ለዚህም በስፖርቱ ትልቅ ስም ያላቸው የኦሊምፒክና የዓለም ሻምፒዮን የሆኑ በርካታ የዓለማችን አትሌቶች እምብዛም የችግሩ ሰለባ ሆነው ቅጣት ሲተላለፍባቸው እንደማይስተዋል ያስቀምጣሉ። የዓለም አትሌቲክስ ፕሬዚዳንት ሴባስቲያን ኮ ሰሞኑን በዶፒንግ ጉዳይ አትሌቶች ትልቅ ስምና ዝናቸው ከጥፋተኝነት እንደማያስጥላቸው አስገንዝበዋል። ለዚህም ባለፉት ዓመታት አሜሪካዊው የመቶ ሜትር የዓለም ሻምፒዮን ክርስቲያን ኮሊማንን ጨምሮ በስፖርቱ ትልቅ ዝናና ስኬት ያላቸው አትሌቶች እንደተቀጡ አስታውሰዋል። እንደ ኮ ገለፃ፣ በአበረታች ንጥረ ነገሮች ላይ የሚደረገው ምርመራ እየተሻሻለ በሄደ ቁጥር ዶፒንግ ተጠቅመው ለሚወዳደሩ አትሌቶች ነገሮች ከባድ እየሆኑ ቢሄዱም የችግሩ ሰለባ ላለመሆን እንዲጠነቀቁ ያደርጋቸዋል። በተለይም በመጪው የቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ ቁጥጥሩ ከምን ጊዜውም በላይ የጠበቀ እንደሚሆን ጠቁመዋል። የኮሊማ ቅጣት አትሌቶች የቱንም ያህል በስፖርቱ ስምና ዝና ቢገነቡ አበረታች ንጥረ ነገር ተጠቅመው ከተገኙ ከቅጣት እንደማያመልጡ ማሳያና የዓለም አትሌቲክስ የሚፈራው ነገር እንደሌለ ማረጋገጫ መሆኑንም የእንግሊዝ የቀድሞ የአንድ ሺ አምስት መቶ ሜትር የሁለት ኦሊምፒኮች አሸናፊው ኮ ለአገራቸው መገናኛ ብዙሃን ገልፀዋል። የዓለም አትሌቲክስ እንደ አበረታች ንጥረ ነገሮች ያሉ ጉዳዮችን የሚያጣራ ገለልተኛ ቡድን አቋቁሞ ባለፉት ዓመታት ተጨባጭ ለውጥ እያስመዘገበ እንደሚገኝ የገለፁት ኮ፣ ዓለም አቀፍ ተቋሙ በራስ መተማመኑን በመገንባት ካለአንዳች ፍርሃት አበረታች ንጥረ ነገር የተጠቀሙ የትኞቹንም የዓለማችን አትሌቶች ለማጋለጥ ከልቡ እየሰራ መሆኑን አክለዋል።
https://www.press.et/Ama/?p=38366
547
2ስፖርት
በቻን ውድድር ስቴዲየሞች በከፊል ለተመልካች ክፍት ይሆናሉ
ስፖርት
December 29, 2020
10
ቦጋለ አበበ በአገር ውስጥ ሊጎች ብቻ የሚሳተፉ ተጫዋቾች የሚሳተፉበት የአፍሪካ ሁለተኛው ትልቁ የእግር ኳስ ውድድር(ቻን) ላይ ደጋፊዎች ስቴድየም ገብተው ጨዋታዎችን እንደሚመለከቱ ተገለፀ። ከመጪው ጥር አጋማሽ ጀምሮ በካሜሩን በሚካሄደው ውድድር የኮቪድ- 19 ወረርሽኝ ቅድመ ጥንቃቄ እርምጃዎችን ተግባራዊ በማድረግ ተመልካቾች ስቴድየም እንዲገቡ የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን(ካፍ) ማሳወቁን ኢንሳይድ ዘ ጌምስ ዘግቧል። ባለፈው ሚያዝያ ወር ሊካሄድ የነበረው የቻን ውድድር በኮቪድ- 19 ስጋት ወደ ዘንድሮው ዓመት መራዘሙ ይታወሳል። የውድድሩን ዝግጅት ለመገምገም ወደ ካሜሩን አማዶ አሂጆ ስቴድየም ያቀኑት የካፍ የግምገማ ቡድን አባላት ለአገሪቱ ስፖርት ሚኒስትር ናርሲስ ሞውሌ ኮምቢ እንደገለፁት ከወር በኋላ በሚካሄደው የቻን ውድድር ወረርሽኙ የሚፈልገውን ጥንቃቄ በማድረግ ተመልካች ስቴድየም እንዲገባ ካፍ ውሳኔ ላይ ደርሷል። እንደ ስፖርት ሚኒስትሩ ገለፃ፣ በውድድሮች ወቅት ጨዋታዎችን የሚያስተናግዱ ስቴድየሞች ከመያዝ አቅማቸው ሃያ አምስት በመቶውን ብቻ ተመልካች እንዲያስተናግዱ ይደረጋል። ካሜሩን በውድድሩ ወቅት በፊፋና በጤና ባለስልጣናት የተቀመጡ መስፈርቶችን ተግባራዊ በማድረግ ተመልካች ስቴድየም እንዲገባ ባደረገችው ጥረት ከካፍ ፍቃድ ማግኘቱንም ጠቁመዋል። ውድድሩ በሚካሄድባቸው የተለያዩ ስቴድየሞች በምድብ ጨዋታዎች ወቅት ስቴድየሞች ተመልካች ከመያዝ አቅማቸው ሃያ አምስት በመቶውን ብቻ እንደሚጠቀሙ የገለፁት ሚኒስትሩ፣ ከምድብ ጨዋታዎች በኋላ በጥሎ ማለፍ ውድድሮች ስቴድየሞች ተመልካች የመያዝ አቅማቸው ወደ ሃምሳ በመቶ ከፍ ሊል እንደሚችል አስረድተዋል። በዱዋላ ከተማ የሚገኘው ስቴድየም በተጎበኘበት የካሜሩን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆሴፍ ኢኦን ንጉቴ ‹‹ውድድሩ ካለፈው ዓመት ተራዝሞ ዘንድሮ በሚካሄድበት ወቅት የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ጉዳይ በአፍሪካ እንደሚሻሻል እርግጠኛ ነኝ›› በማለት መናገራቸው ይታወቃል። የቅርብ ቀናት መረጃዎች እንደሚያመለክቱት በካሜሩን ከሃያ ስድስት ሺ በላይ ሰዎች በኮቪድ-19 የተያዙ ሲሆን አራት መቶ ሃምሳ ሰዎች ሕይወታቸው አልፏል። የካሜሩን ከተሞች መዲናዋ ያውንዴን ጨምሮ ዱአላና ሊምቤ ውድድሩን የሚያስተናግዱ ይሆናል። በዋናው የአፍሪካ ዋንጫ ጨዋታ በሌሎች አገራት ትልልቅ ሊጎች በሚጫወቱ ተጫዋቾች ተሸፍነው የመታየት እድል ያላገኙ በአገር ውስጥ ሊጎች ብቻ የሚጫወቱ ተጫዋቾች እንዲሳተፉ ለማድረግ ካፍ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ተግባራዊ ያደረገው የቻን ውድድር በኮቪድ-19 ምክንያት ካለፈው ዓመት ወደ ዘንድሮው ዓመት ከተሸጋገሩት አንዱ ነው። ካሜሩን በመጪው ሰኔ አጋማሽ ዋናውን የ2021 አፍሪካ ዋንጫ ጨዋታን የምታስተናግድ አገር መሆኗም ይታወቃል። የ2019 አፍሪካ ዋንጫን ለማዘጋጀት 2014 ላይ እድሉ የተሰጣት ምዕራብ አፍሪካዊት አገር ካሜሩን 2018 ላይ ውድድሩን ለማዘጋጀት የምትገነባቸው ስቴድየሞች በመጓተታቸውና በወቅቱ በአገሪቱ የነበረው የፖለቲካ አለመረጋጋት ከደህንነነት አኳያ ስጋት ስለፈጠረ የአዘጋጅነት እድሉ ለግብፅ ተሰጥቷል። ካሜሩንም በምትኩ የ2021 አፍሪካ ዋንጫን እንድታዘጋጅና ኮትዲቯር የ2023 አፍሪካ ዋንጫን እንድታሰናዳ ሽግሽግ መደረጉ ይታወቃል።አዲስ ዘመን ታኅሣሥ 20/2013
https://www.press.et/Ama/?p=38441
331
2ስፖርት
ከተራ – የጎንደር ልዩ ውበት
ሀገር አቀፍ ዜና
January 19, 2021
7
ክፍለዮሐንስ አንበርብርጎንደር አሸብርቃለች:: ተፈጥሮም ሰውም አጅቧታል:: ከተራ ለጎንደር፤ ጎንደርም ለከተራ ውበት ናቸው:: ቆነጃጅት ሽሩባቸውን በባህላዊ አሠራር አስውበው፣ በሐበሻ አለባበስ አምረውና ደምቀው ወደ ማደሪያው የሚሸኙትን ታቦታት ይከተላሉ:: ወጣት ወንዶች በሀገርኛ አለባበስ አምረውና ደምቀው፣ ሽመል ይዘው በሆታ እያደመቁ፤ በእግራቸው መሬት ረግጠው  እየነቀነቁ አቧራው ወደ ላይ ቡን! ቡን! ብሎ በሰዎች መሐል ወደ ላይ ቦለል ሲል እንደ ሰኔ ደመና እየተቆራረጥ ወደ ላይ ሲወጣ አንዳች የተለየ ውበት አለው::ጎንደር ከተማን በዙሪያ የከበበው ተራራ ታቦታቱን ያጅብ ይመስል ደረቱን ነፍቶ የቁልቁሊት እየተመለከተ የተለየ ውበት አላብሷል ለአካባቢው::የጎንደር ታቦታት በሰዎች ብቻ ሳይሆን ተራራ የሚታዘዝላቸው፤ ተራራ የሚከተላቸው ይመስላል::አንዳንዶቹ ደግሞ ፈረስ ላይ ሆነው ጎፈሬ አበጥረው እና በጃኖ ተሞሽረው እየተገማሸሩ፤ ጎንደር እሽሩሩ በሚለው ሙዚቃ ታጅበው ከፈረሶቹ ወገብ ላይ ሆነው እዩኝ እዩን በሚል ሁኔታ በታቦታቱ በቅርብ እርቀት ይጓዛሉ::የሰንበት ተማሪዎች በመለከት፣ በገና እና ከበሮ በታጀበ ህብረ ዝማሬ እያሰሙ ከታቦታቱ ኋላ ኋላ እየተከተሉ ወደ ማደሪያው ሥፍራ ሲሸኙ የጎንደር ከተራ በዓልን ውበት በእጁጉ ያጎላዋል::ካሜራቸውን ደቅነው ወዲህ ወዲያ ዝርው ዝርው የሚሉት ቱሪስቶች የታሪክ አካል ለመሆን የሚያደርጉት ሽሚያ በራሱ ዕይታን ይስባል::ቀሳውስቱ ግራ ቀኝ እያዘመሙ፣ ጽናጽል እየጸነጸሉ ታቦታቱን አጅበው ወደማደሪያው ሥፍራ ሲሸኙ ውበቱን በቃላት ለመግለፅ መሞከር አዳጋች ያደርገዋል::በአራቱም ነፋሳት የሚታጠነው ዕጣን አካባቢውን እንደ ናርዶስ ሽታ እያወደው ጥሩ መዓዛ አላብሶታል::ከተራ በጎንደር አንዳች የማይገለፅ መግነጢሳዊ ኃይል አለው::የአማራ ልዩ ኃይል በየአቅጣጫው ሆነው ከበጎ ፈቃድ ወጣቶች ጋር በመቀናጀት የአካባቢውንና የከተማዋ ሠላምና ፀጥታ ለማስከበር የሚያደርጉት መውተርተር ምንኛ የሀገር ፍቅርና የበዓል ክብር እንዳላቸው ያሳብቃል::እንደ ንሥር አሞራ ዓይናቸውን በርቀት በቅርበት እየላኩ አካባቢውን ይቃኛሉ::የከተራ ውበት በጎንደር፤ የጎንደር ከተማም ውበትም በከተራ ይገለፁ ዘንድ ተዋህደው የተሠሩ ይመስል አንዳቸው ካለአንዳኛው ምሉዕ አይመስሉም::ከተማዋ በዓል በዓል በሚሸቱ ሙዚቃ እና ዝማሬ ተንጣለች::በየህንፃዎቹ አናት ላይ የተሰቀሉት ሰንደቅ ዓላማዎች የከተማውን ድባብ በጠላት ጦር ላይ ድል በተቀዳጀ ማግስት የተገኘ ልዩ ድል አስመስለውታል::ጎንደር በሽለላ እና ቀረርቶም ለምን ይቅርብኝ ያለች ይመስላል::በርካታ ወጣቶች በአፄ ቴዎድሮስ አደባባይ እያቅራሩና እየፎከሩ በሐውልቱ ዙሪያ እየተሽከረከሩ ኢትዮጵያዊ ወኔ የሚቀሰቅሱና ለበዓሉ ድምቀት የሆኑ አያሌ ትዕይንተ ህዝብ ያሳያሉ::ሁሉንም እንቅስቃሴ በአንክሮ ለተመለከተው አንዳች ንዝረታዊ ኃይል አለው::በቃ ጎንደር ድምቅ! ብላለች::ወጣት ይድነቃቸው ታደሰ ከተራ ለእኔ ልዩ ስሜት ይሰጠኛል:: በዓሉ ነብስና ሥጋዬ ተዋህደው ደስታዬ እጥፍ ድርብ የሚሆንበት ነው::በተለይም ደግሞ በጎ አድራጎትን በመከወን ስለማሳልፍ ነብሴ በሐሴት ትረሰርሳለች ይላል::እርሱ ከከተራ እና ጥምቀት መቅረት አይሆንለትም::ጎንደር አፍ አውጥታ ትጠይቀው፤ በአሽሙር ወጋ ታደርገው ይመስል በዓሉን ሌላ ሥፍራ ማሳለፍ አይፈልግም::ወጣት ተረፈ መልካሙ ባለፈው ዓመት የምዕምናን መቀመጫ ደረጃ ተደርምሶ ጉዳት በማድረሱ በከተራውም ሆነ በጥምቀት በዓል ላይ ጥቁር ጥላ አጥልቶ ያላፈ በመሆኑ፤ መሰል ችግሮች እንዳይደገሙ ከከተማው ወጣቶች ጋር በመቀናጀት በጎ ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል::በበዓሉ ወቅት ባህረ ጥምቀት ሄዶ መጠመቅና ከተራ በዓል ላይ መታደም ለእርሱ የፍሰሐ ጥግ ነው:: ከተራና ጥምቀትን በጎንደር ማሳለፍና መታደም የሁልጊዜ ዕቅዱ ነው::ከተራ ብሎም ጥምቀት በዓል የነፍስ የሥጋም በዓል እንደሆነ የሚናገሩት የማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ ሊቀህሩያን አባ ዮሴፍ ደስታ ናቸው:: በዚህ በዓል በርካታ የአገር ውስጥና የአገር ውጭ ታዳሚዎች ወደ ጎንደር የሚመጡ ሲሆን ይህም ለጎንደርና ለአካባቢው ነዋሪዎች ፀጋ ይዞ የሚመጣ እንደሆነ ያብራራሉ::ማህበራዊ እሴቶችን በማጠናከር፣ መንፈሳዊ ሕይወትን በማደስና ነብስን በማረስረስ የሚሰጠው ስሜት ልዩ ስለመሆኑም ያስገነዝባሉ::ሊቀህሩያን አባ ዮሴፍ ደስታ እንደሚሉት፤ የጎንደር ከተራ እና ጥምቀት በዓል ሁሌም አዲስ ሰርክ ልዩ እየሆኑ ዘመናትን አስቆጥረዋል::በቀጣይም የበዓሉ ድምቀት በዚሁ ድባብ እንደሚቀጥል ተስፋ አላቸው::ለዚህም የወጣቶች፣ የምዕምናን ትግስትና ፅናት፣ የሀገር ታሪክ ወዳድነት፣ ለቤተክርስቲያንና የባህል እሴቶች ያላቸው ክብር ህያው ምስክር ስለመሆናቸውም ይገልፃሉ::በዚህ ዓመት የሚከበረው የከተራ እና ጥምቀት በዓል ከመቼውም በላይ ደስታየው የተለየ ስለመሆኑም ይናገራሉ::አገሪቱ ሠላም ሰፍኖባት የኤርትራ ወንድምና እህቶች በበዓሉ ታዳሚ የሚሆኑበት መሆኑም ታላቅ ፍስሐ እንደሆነም ይጠቁማሉ::የከተራ በዓል ሠላማዊና ፍሰሐ እንዲሆንም የመንግሥት አካላት ከአድባራት አስተዳዳሪዎች፣ ከሃይማኖት አባቶች፣ ከወጣቶችና ከሌሎች የሚመለከታቸው ተቋማት ጋር በመናበብ ስለሚሠሩ ሁሉም ነገሩ ሸጋ ነው ይላሉ:: ከተራ እና ጥምቀት በጎንደር ልዩ ስሜትና እንደሚሰጥ በመጠቆም፤ የተቻላቸው ኢትዮጵውያን እንዲታደሙት ይመክራሉ::አዲስ ዘመን ጥር 11 ቀን 2013 ዓ.ም
https://www.press.et/Ama/?p=39749
541
0ሀገር አቀፍ ዜና
” የሱዳን ሃይል በተጠናከረ ሁኔታ ወደ ውስጥ እየተስፋፋ መሄዱ የግድቡን ግንባታ ለማስተጓጎል ነው‘ – ብርጋዴል ጀነራል ዋሲሁን ንጋቱ
ሀገር አቀፍ ዜና
January 17, 2021
48
ዘላለም ግዛው  አዲስ አበባ:- የሱዳን ሃይል በተጠናከረ ሁኔታ ወደ ውስጥ እየተስፋፋ መሄዱ የግድቡን ግንባታ ለማስተጓጎል የተደረገ መሆኑን ብርጋዴል ጀነራል ዋሲሁን ንጋቱ አስታወቁ። ትዕግስቱ ከበቂ በላይ በመሆኑ የሃይል አጸፋ እንደሚያስፈልግ አመለከቱ። የቀድሞ መከላከያ ሰራዊት ባልደረባ ብርጋዴል ጀነራል ዋሲሁን በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንዳስታወቁት ፤ የሱዳን አሁናዊ የመሬት ወረራ ዋናው ግብ በማጠናቀቂያ ምዕራፍ ላይ የሚገኘውን የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታን ለማስቆም፣ ወደ ሃይል ማመንጨት ሂደቱ ከመሸጋገሩ አስቀድሞ ለማስተጓጎል የተወጠነ ሴራ መሆኑን ነው። ኢትዮጵያ የግድቡን ግንባታ ለማጠናቀቅ ተርባይኖቹንም   ተክሎ ሃይል እንዲያመነጩ ስራ ለማስጀመር እያደረገች ያለው ሂደት በምንም ሁኔታ የማይቆም ነው ያሉት ብርጋዴል ጀነራሉ፤ ከሱዳን ድርጊት ጀርባ የግብጽ እና የሱዳን ተባባሪ የሆኑ አንዳንድ የአረብ አገራት እጅ ሊኖርበት እንደሚችል ጥርጣሬያቸውን ገልጸዋል። በመንግስት በኩል እየታየ ያለው ትእግስት ከበቂ በላይ መሆኑን አመልክተዋል። ሱዳን በኃይለስላሴ አገዛዝና በደርግ ሥርዓትም የመስፋፋት አዝማሚያ ታሳይ እንደነበር ያስታወሱት ብርጋዴል ጀነራል፣ በአሁኑ ወቅት ድንበር ጥሶ የገባውን ሃይሏን በሰላም የሚወጣ ከሆነ መልካም፣ ካልሆነ ግን የሃይል አማራጭን መጠቀም እንደሚያስፈልግ አስታውቀዋል። ለሰላም አማራጩ ተገዢ ካልሆኑ ወታደራዊ አቅምን በመጠቀም ማባረር እንደሚገባም ጠቁመዋል። እንደርሳቸው ማብራሪያ፤ ኢትዮጵያ መሬቷ ተወርሮ አሁንም ችግሩን በዲፕሎማሲ ለመፍታት እያደረገች ያለው ጥረት የሚደነቅ ነው። ለጎረቤት አገራት ያላትን ፍቅር፣ የሰላም ፍላጎቷንና ለቀጠናው ሰላም መጠበቅ ያላትን ቁርጠኝነት ያሳያል። ትዕግስቱ፣ ስምምነት ላይ ለመድረስ መሞከሩና በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ድርጊቱን ለማስቆም እና ለማስመለስ መንቀሳቀሱ ተገቢ ነው። መንግስት በከፍተኛ ጥንቃቄ ጉዳዩን ለመያዝ ያለውን ፍላጎት የሚያመለክት እንደሆነም አመልክተዋል። የሱዳን ሉአላዊ ምክር ቤት ሰብሳቢ ሌተናል ጀነራል አብዱል ፈታህ አል ቡርሃን እና የሱዳን ጠቅላይ ሚኒስትር አብደላ ሃምዶክ ወደ አዲስ አበባ በመምጣት ጉብኝት እና ውይይት ማድረጋቸውን፤ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶክተር) እንዲሁም ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ወደ ሱዳን ተጉዘው ተመሳሳይ ጥረት እያደረጉ ባለበት ሁኔታ ፣ ወረራ ማካሄድ ተገቢ አይደለም ብለዋል። የኢትዮጵያ መንግስት ትዕግስት ማድረጉ ከዚህ በላይ አያስኬድም ትዕግስትም ወሰን አለው ያሉት ብርጋዴል ጀነራል ዋሲሁን ፣ፍቅርና የሰላም ፍላጎት ያልገዛውን ሃይል እንደሚገዛ አስታውቀዋል።
https://www.press.et/Ama/?p=39619
274
0ሀገር አቀፍ ዜና
የአትሌቶችን ጥያቄ የሚመልስ ማዘውተሪያ
ስፖርት
December 13, 2020
12
 ብርሃን ፈይሳበኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በኦሮሚያ ክልል ለገጣፎ ለገዳዲ ከተማ የተገነባው የአትሌቲክስ ማዘውተሪያ የአሸዋ ትራክ ተመረቀ። በክልሉ የተለያዩ አካባቢዎችም ተመሳሳይ ማዘውተሪያዎች እንደሚገነቡ ታውቋል።በኦሮሚያ ክልል ለገጣፎ ለገዳዲ ከተማ የተገነባው የአትሌቲክስ ማዘውተሪያ ስፍራ ትናንት ተመርቆ ለአገልግሎት በቅቷል። ግንባታው ለረጅም ርቀትና አጭር ርቀት አትሌቲክስ ስፖርት መለማመጃ የሚውለው የአሸዋ ትራክ እንዲሁም የአትሌቶች ልብስ መቀየሪያ፣ የማረፊያና የንጽህና መጠበቂያ ስፍራን ያጠቃልላል። ከለገዳዲ ለገጣፎ ባሻገር በክልሉ ባሉ የተለያዩ ከተሞችም ተመሳሳይ ማዘውተሪያዎች የሚገነቡ መሆኑም ተጠቁሟል። በምረቃ ስነስርአቱ ላይ የፌዴሬሽኑ ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዚዳንት ኮማንደር ደራርቱ ቱሉ ከአትሌቶች ወቅታዊና አንገብጋቢ ጥያቄዎች አንጻር ለአትሌቲክስ ስፖርት ምቹ ከሆኑት አካባቢዎች መካከል አንዱን በመምረጥ ለምረቃ የበቃውን የለገጣፎ ለገዳዲ የአሸዋ ትራክ ለማስገንባት እንደተቻለ ገልጻለች። ፌዴሬሽኑ ለገጣፎ ለገዳዲ ከተማ አስተዳደር ጋር በተደረሰው ስምምነት መሰረት የዲዛይን ስራ በማሰራትና ለግንባታውም ፌዴሬሽኑ 18 ሚሊየን ብር ወጪ በማድረግ ግንባታው ተካሂዶ ለምረቃ በቅቷል። ትራኩ 1ነጥብ 6 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው ሲሆን፤ ወደ 2ኪሎ ሜትር እንዲያድግ ለቀረበው ጥያቄም የክልሉ መንግስት ፈቃደኝነቱን በመስጠቱ ምክትል ፕሬዚዳንቷ ምስጋና አቅርባለች። ግንባታው ፌዴሬሽኑን ብቻም ሳይሆን ከተማ አስተዳደሩን፣ ክልሉንና ኢትዮጵያንም ጭምር በማበልጸግና የስፖርት ቱሪዝምን በመሳብ ከሃገር ገጽታ በተጨማሪ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታም እንደሚኖረው ጠቅሳ፣ ከፌዴራል መንግስት ጀምሮ ሁሉም አካላት የማዘውተሪያ ስፍራ ችግርን ለመቅረፍ በትኩረትና በርብርብ የሃገር በጎ ገጽታ መገንባት እንደሚኖርባቸው አስገንዝባለች። ማዘውተሪያውን የመረቁት የኦሮሚያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ምክትል ፕሬዚዳንት ሽመልስ አብዲሳ ፌዴሬሽኑ ማዘውተሪያውን በመገንባት በጎ ተግባር መስራቱን አስታውቀዋል። በፌዴሬሽኑ የቀረበውን 1ነጥብ6 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው ትራክ ወደ 2 ኪሎ ሜትር ለማሳደግ የክልሉ መንግስት እንደሚሰራም አረጋግጠዋል። ከለገዳዲ ለገጣፎ ባሻገር በሱሉልታ፣ በቡራዩ፣ ሰበታ እና ገላን ቦታዎችን በአጭር ጊዜ በማዘጋጀት፤ የማዘውተሪያ ስፍራዎች በፌዴሬሽኑ እና በክልሉ መንግስት ድጋፍ እንደሚገነቡም ጠቁመዋል። ይህም አትሌቶችን ከመኪና አደጋ እና ከመሳሰሉት ጉዳቶች ተጠብቀው ልምምዳቸውን እንዲያደርጉ እና ለሃገራቸው ክብር እንዲቆሙ እንደሚያስችሉ አስታውቀዋል።ለእዚህም የክልሉ መንግስት እንደሚሰራ አረጋግጠዋል። የለገጣፎ ለገዳዲ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ወይዘሮ ሃቢባ ሲራጅ፤ በርካታ አትሌቶች ከከተማው የአትሌቲክስ ክለብ በመውጣት በዓለም አቀፍ ደረጃ ውጤት ማስመዝገባቸውን እንዲሁም ለቶኪዮ ኦሊምፒክ ስድስት አትሌቶችንና ሁለት አሰልጣኞች ለብሄራዊ ቡድን መመረጣቸውን ጠቅሰዋል። ይህ ውጤት ሊገኝ የቻለውም በመንግስት በተደረገለት ድጋፍ መሆኑን ተናግረው፤ ፖሊሲው ስፖርት በህዝባዊ አካል እየተመራ በመንግስት እንዲታገዝ ቢሆንም፤ በርካታ የማዘውተሪያ ስፍራዎች የተገነቡት በመንግስት ነው ብለዋል። በዚህም አትሌቶች የመለማመጃ ስፍራ አንድ ለእናቱ ከነበረው የአዲስ አበባ ስታዲየም ወደ አጎራባች ከተሞች በመውሰድ አትሌቶች አማራጭ መሮጫዎችን እንዲያገኙ ተደርጓል ያሉት ከንቲባዋ፤ እንደ ከተማም በስፖርቱ ምክንያት ወደ ማዘውተሪያው የሚጓዙ የሃገር ውስጥና የውጪ ሃገራት አትሌቶች ሰላማቸው ተጠብቆ ማዘውተሪያው ለታለመለት ዓላማ እንዲውል እንደሚሰራ አረጋግጠዋል። መዋዕለ ነዋያቸውን በስፖርት ላይ ለማፍሰስ ለሚፈልጉ ባለሃብቶችም ከምንጊዜውም በላይ ድጋፍ እንደሚሰጥም ገልጸዋል። በእለቱ ከተካሄደው ምረቃ ስነስርአት ጎን ለጎን ፌዴሬሽኑ ለሚያስገነባው ባለ 12 ወለል ህንጻም የመሰረተ ድንጋይ በእለቱ ተቀምጧል። ይህም ጂምናዚየም፣ የህክምና እና የማገገሚያ ማዕከል፣ ከአትሌቲክስ ጋር የተያያዙ አገልግሎቶችን የሚሰጥ እንዲሁም ገቢ የሚያስገኝ እንደሚሆንም ታውቋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 4/2013
https://www.press.et/Ama/?p=37292
397
2ስፖርት
ከቅጣት ያመለጠው ታሪካዊ ጥፋት
ስፖርት
December 13, 2020
13
ቦጋለ አበበእግር ኳስን በመሳሰሉ ተወዳጅና ንክኪ በሚበዛባቸው ስፖርቶች ተጫዋቾች በእንቅስቃሴ ውስጥ እያሉ አውቀውም ይሁን ሳያውቁ በተቃራኒ ቡድን ተጫዋቾች ላይ ጥፋት(ፋውል) ይሰራሉ። እነዚህ ጥፋቶች ከቀላል እስከ ከባድ የአካል ጉዳት ሊያስከትሉ የሚችሉና ያስከተሉበት አጋጣሚም በርካታ እንደነበር መመልከት ይቻላል። በስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች ወቅት ስፖርተኞች መሰል ጥፋት ሲሰሩ ውድድሩን በሚመሩ ዳኞች ከቢጫ የማስጠንቀቂያ ካርድ አስከ በርካታ ጨዋታዎች መታገድ ሊያደርሱ የሚችሉ ቅጣቶች ይከተሏቸዋል። ዳኞች አውቀውም ይሁን ሳያውቁ ከትንሽ እስከ ትልቅ ጥፋቶች በዝምታ ሲያልፉ የሚታይበት አጋጣሚም ጥቂት አይደለም። በዛሬው የስፖርት ማህደር አምዳችንም እኤአ በ1982 የዓለም ዋንጫ ሩብ ፍፃሜ ጨዋታ ወቅት የተከሰተውን ከባድና ታሪካዊ ጥፋት ከቅጣት የዳነበትን አጋጣሚ እንደሚከተለው እንዳስሳለን።ታሪካዊው ፈረንሳዊ ተጫዋች ሚሼል ፕላቲኒ ያሻገራት ኳስ ፓትሪክ ባቲስቶን ከጀርመኑ ግብ ጠባቂ ጋር አገናኘችው። በአጠገቡ ተከላካዮች የሉም፣ ከጨዋታ ውጭ አይደለም። የተከላካይን መስመር ሰንጥቆ ያለፈ ለጎል የተመቻቸ ያለቀለት ዕድል ነበር። ሄራርድ ሹማኸር ኳሷን ማዳን አለበት። አለበለዚያ ጀርመን ለዓለም ዋንጫው ፍፃሜ ላትደርስ ትችላለች። ከባቲስቶ ጋር ፊት ለፊት ተጋፈጠ። በረኛው እየተንደረደረ ኳሷን ተከትሎ ወደ ፈረንሳዊው መጣ። ሁለቱም ወደ አንድ አቅጣጫ ፈጠኑ። ሁለቱም የሀገሮቻቸው ጀግና ለመሆን በየፊናቸው እየሮጡ ነው…።የ1982ቱ የዓለም ዋንጫ ግማሽ ፍፃሜ ጨዋታ ነበር፣ ፈረንሳይ ከምዕራብ ጀርመን። ውጤቱ 1-1 እያለ ባቲስቶ ተቀይሮ ገባ። ከመግባቱ በፊት በተጠባባቂዎች ወንበር ላይ የምዕራብ ጀርመኑ በረኛ ባህሪይ አልተመቸውም ነበር። ከፈረንሳይ ተጫዋቾች ጋር ሲናቆር ታዝቦታል። የበዛ ግልፍተኛነት ይታይበታል። ከደቂቃዎች በኋላ አሰልጣኙ ወደ ጨዋታው አስገቡት። ከሰባት ደቂቃ በኋላም ከሹማኸር ጋር ተፋጠጠ። ፈረንሳዊያን ጎል ሲጠብቁ ሹማኸር ባለ በሌለ ጉልበቱ እንደ ፊጋ በሬ ተንደርድሮ በትከሻውና ዳሌው ተላተመው። ባቲስቶ ከሹማኸር ጉልበት ጋር አልተመጣጠነም። ከወገቡ በላይ ወደኋላው ተገፍትሮ አካሉን ሊቆጣጠር በማይችልበት ኃይል በጀርባው ከመሬት ተደባለቀ። በክርኑ መሬቱን የተደገፈው የቀኝ እጁ፣ ጣቶቹ እንደታጠፉ ቀና ብሎ ቀስ እያለ መሬቱ ላይ አረፈ። ከዚያም ተጫዋቹ በወደቀበት ሳይነቃነቅ በድን ሆነ። ግጭቱ እጅግ ከባድ ስለነበር ባቲስቶ ራሱን ሳተ። ሁለት ጥርሶቹ ወለቁ፣ ሶስት የጎድን አጥንቶቹ ተሰበሩ። በሜዳ ላይ የህክምና እርዳታ ሲደረግለት በተጫዋቹ ዙሪያ ሆነው አሰቃቂውን ጉዳት በቅርበት የሚከታተሉ የፈረንሳይ ተጫዋቾች ፊታቸውን ወደ ሹማኸር መለስ ቀለስ እያደረጉ ቁጣቸውን ይገልፃሉ። በረኛው ግን ከቁብም አልቆጠራቸው። በመጀመሪያ ወገቡን በእጆቹ ይዞ ባለበት ቆሞ ቆየ። ከዚያም ከሌላ የቡድን ጓደኛው ጋር ኳስ እየተቀባበለ ሰውነቱ እንዳይቀዘቅዝ ማድረጉን ቀጠለ። በኦክስጅን ጭምብል ከሜዳ እንዲወጣ ያስገደደ ከባድ ጥፋት ቢፈጽምም አርቢትር ቻርልስ ኮርበር ለሹማኸር ቀይ ካርድ ቀርቶ የማስጠንቀቂያ ካርድ እንኳን አልመዘዙበትም። ከጨዋታው መጠናቀቅ በኋላ በረኛው በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ የባቲስቶ ጥርሶች መውለቃቸውን ሲነግሩት ‹‹እኔ ወጪውን እሸፍናለሁ›› በሚል ስላቅ እብሪተኛነቱን ጨምሮ አሳየ። በወቅቱ አንድ ቡድን መቀየር የሚችለው ሁለት ተጫዋቾችን ብቻ በመሆኑ ሁለተኛው ተቀያሪ በጉዳት ከሜዳ የወጣበት የፈረንሳይ ቡድን አጋጣሚው ለፍፃሜ የመድረስ አቅሙን ክፉኛ አዳከመበት። በጭማሪ ሰዓት ፈረንሳይ አከታትላ ባስቆጠረቻቸው ሁለት ጎሎች 3-1 መምራት ብትችልም፣ አልሞት ባዮቹ ጀርመናዊያን ሁለት ጎሎች አግኝተው በ3-3 የመጨረሻ ውጤት ወደ መለያ ምት ሄዱ። ከዚያም የሹማኸር ምዕራብ ጀርመን ለፍፃሜው በቃች። አጋጣሚው በፈረንሳይ ህዝብ ዘንድ ፀረ-ጀርመን ጥላቻን ፈጠረ። ሹማኸር የፈረንሳይ ቁጥር አንድ ጠላት ሆነ። አንድ የሀገሪቱ ጋዜጣ በሰበሰበው የህዝብ መጠይቅ ሹማኸር ከናዚው አዶልፍ ሂትለር በላይ በዚያች ሀገር እንደተጠላ ተረጋገጠ። የጀርመኑ መራሔ መንግስት ሄልሙት ሽሚድት ቁጣውን ለማቀዝቀዝ ለፈረንሳዩ አቻቸው ፍራንሷ ሚቴሯ የቴሌግራም መልዕክት ላኩ። የጋራ መግለጫ ሊያወጡም ተገደዱ። ተጫዋቾቹም እንዲገናኙ ለማድረግ ሞከሩ። በሰዎች ግፊትም ይሁን ዘግይቶ በመጸጸቱ፣ ሹማኸር ተጎጂው ባለበት ሄዶ ይቅርታ ሊጠይቀው ቢሞክርም በጋዜጠኞች መገኘት ምክንያት ያሰበውን ያህል ሳይሳካለት ቀረ። አሁን ባቲስቶ ከስልሳ ዓመት ያለፈው ጎልማሳ ሆኗል። ጉዳቱ በጀርባ አጥንቱ ላይ የፈጠረው አደጋ እስካሁንም የህመም ስሜት እንዳለው ይናገራል። ራስ ምታት ልማዱ ነው። በቃሬዛ ከወጣ በኋላ የተከናወነውን ቀሪ የጨዋታ ፊልም ላለማየት ወስኖ ቢቆይም በመጨረሻ ከሰላሳ ዓመታት በኋላ ተመልክቶታል። ወደ እርጅናው የተጠጋው ሹማኸርም አሁን ደርሶ በአጋጣሚው መጸጸቱን ይናገራል። ከጨዋታው ሁለት ዓመት በኋላ፣ በ1984፣ ፈረንሳይና ምዕራብ ጀርመን በወዳጅነት መርሃ ግብር ተገናኙ። ከጉዳቱ በኋላ ወደ ጨዋታ የተመለሰው ባቲስቶ በድጋሚ በብሔራዊው ማሊያ ከሹማኸር ጋር በተቃራኒ ቆመ። በመጨረሻ ሁለቱ ሰዎች ማሊያ ተቀያየሩ። ቅይይሩ ግን በህዝብና በሚድያው ፊት ሳይሆን በተጫዋቾች መልበሻ ቤት ውስጥ፣ ብቻቸውን ያደርጉት ነበር።አዲስ ዘመን ታህሳስ 4/2013
https://www.press.et/Ama/?p=37293
561
2ስፖርት
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እየተሰበሩ ከሚገኙ የዓለም ክብረወሰኖች ጀርባ
ስፖርት
December 14, 2020
7
ቦጋለ አበበበኮቪድ-19 ወረርሽኝ ስጋት ለበርካታ ወራት ተቋርጠው የቆዩ ዓለም አቀፍ የአትሌቲክስ ውድድሮች ካለፈው ሐምሌ መጨረሻ ጀምሮ በሂደት ወደ መደበኛ መርሃግብራቸው እየተመለሱ ይገኛሉ፡፡ እነዚህ ውድድሮች በተመለሱበት ጥቂት ወራትም በተለይም የረጅም ርቀት የዓለም ክብረወሰኖች ለማመን በሚቸግር መልኩ ሲሰበሩ እየተስተዋለ ይገኛል፡፡ ይህም የስፖርቱን አፍቃሪዎች ከማነጋገሩ ባሻገር ተንታኞች ጭምር ግራ እንዲጋቡ ያደረገ ክስተት ሆኗል፡፡ በተለይም የዓለም ግማሽ ማራቶን ክብረወሰን ከወረርሽኙ በፊትም ቢሆን ከሌሎች ርቀቶች በተለየ በሁለቱም ፆታ በተደጋጋሚ ሲሰበር መስተዋሉ አነጋጋሪ አድርጎታል፡፡ የዓለም ግማሽ ማራቶን ክብረወሰን በዓለም አትሌቲክስ እኤአ ከ2004 አንስቶ እውቅና እየተሰጠው ከመጣ ወዲህ በወንዶች አምስትና በሴቶች ስድስት የዓለም ክብረወሰኖች ተመዝግበዋል፡፡ ከዚህ ዓመት በፊት በርቀቱ የተመዘገቡ ሰዓቶች በዓለም አትሌቲክስ ‹‹የዓለም ፈጣን ሰዓት›› በሚል ይታወቅ ነበር፡፡ የወንዶች ግማሽ ማራቶን የዓለም ክብረወሰን ባለፈው እሁድ በቫሌንሲያ የተመዘገበ ሲሆን ኬንያዊው አትሌት ኪቢዎት ኬንዲ 57፡32 በሆነ ሰዓት የክብረወሰኑ ባለቤት ሆኗል::የሴቶቹ ደግሞ ባለፈው የካቲት በተባበሩት አረብ ኢሚሬቶች የራስ አል ኪማህ ግማሽ ማራቶን ውድድር ላይ ኢትዮጵያዊቷ አትሌት አባብል የሻነህ በ1፡04፡31 በሆነ ሰዓት ያስመዘገበችው ነው፡፡ ይህም በጥቅምት 2017 ኬንያዊቷ ጆይስሊን ጂፕኮስጌ በቫሌንሲያ ግማሽ ማራቶን ካስመዘገበችው የቀድሞው የዓለም ክብረወሰን በሃያ ሰከንድ የተሻለ ነበር፡፡ በመስከረም 2019 ሌላኛዋ  ኬንያዊት ብሪጊድ ኮስጌ በኒውካስትል ታላቁ ሩጫ 64፡28 በሆነ ሰዓት ከቀድሞው ክብረወሰን በሃያ ሦስት ሰከንድ የተሻለ ፈጣን ሰዓት ብታስመዘግብም የዓለም አትሌቲክስ ለክብረወሰኑ እውቅና አልሰጠውም። እኤአ ከ2011 ጀምሮ የዓለም አትሌቲክስ የሴቶች ግማሽ ማራቶን ክብረወሰኖችን በሴትና በወንድ አሯሯጭ የተመዘገቡ ብሎ በሁለት ከፍሏቸዋል።  በሴት አሯሯጮች የተመዘገበው የርቀቱ ክብረወሰንም በኬንያዊቷ አትሌት ፔርስ ጂፕቺርቺር 1፡05፡16 በሆነ ሰዓት ከወር በፊት በፖላንድ ጊዲኒያ የዓለም ግማሽ ማራቶን ቻምፒዮና የተመዘገበ ነው። ባለፈው ሐምሌ መጨረሻ ለአስራ ስድስት ዓመታት ያልተደፈረው የቀነኒሳ በቀለ የአምስት ሺ ሜትር ክብረወሰን በዩጋንዳዊው አትሌት ጆሽዋ ቺፕቴጌ ሞናኮ ላይ ከተሰበረ ወዲህ የዓለም ክብረወሰኖች በተለይም በረጅም ርቀት ውድድሮች እንደልብ የሚሰበሩ ሆነዋል። ከዩጋዳዊው ያልተጠበቀ ክብረወሰን በኋላ አንድ ወር ባልሞላ ልዩነት ትውልደ ሶማሊያዊው የእንግሊዝ አትሌት ሞ ፋራህ እኤአ 2007 ላይ በጀግናው አትሌት ኃይሌ ገብረስላሴ ተይዞ የቆየው ‹የአንድ ሰዓት ውድድር› የዓለም ክብረወሰን ብራሰልስ ዳይመንድ ሊግ ላይ ከ21፡330 ወደ 21፡285 ተሻሽሏል። በተመሳሳይ ርቀት እንዲሁም በተመሳሳይ ቀንና ውድድር በኢትዮጵያዊቷ አትሌት ድሬ ቱኔ 18፡930 ተይዞ የቆየው የዓለም ክብረወሰን በትውልደ ኢትዮጵያዊቷ የኔዘርላንድስ አትሌት ሲፈን ሃሰን 18፡517 በሆነ ሰዓት ተሻሽሏል። የሁለቱ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች የአንድ ሰዓት ውድድር የዓለም ክብረወሰኖች በተሰበሩ በአንድ ወር ልዩነት ዩጋንዳዊው አትሌት ጆሽዋ ቺፕቴጌ ለአስራ አምስት ዓመታት ያልተደፈረውን የቀነኒሳ በቀለ የአስር ሺ ሜትር ክብረወሰን በ6፡53 ሰከንድ መስበር ችሏል። በተመሳሳይ ቀን ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ለተሰንበት ግደይ በሌላኛዋ ኢትዮጵያዊት አትሌትና የረጅም ርቀት ንግስት ጥሩነሽ ዲባባ ለአስራ ሁለት ዓመታት ተይዞ ሳይሰበር የቆየውን የአምስት ሺ ሜትር ክብረወሰን 14፡06 በሆነ ሰዓት ሰብራዋለች። ኬንያውያን አትሌቶችም ከኮቪድ-19 ወረርሽኝ በኋላ ባንሰራራው የአትሌቲክስ ውድድር የክብረወሰን ተቋዳሽ ናቸው። ለዚህም በዓለም ግማሽ ማራቶን በአርባ ሁለት ቀናት ልዩነት ሁለት የዓለም ክብረወሰኖችን የጨበጠችው ኬንያዊቷ ፔስር ጂፕቺርቺር ትክክለኛ ማሳይ ናት። መስከረም ላይ በፓራጓይ ግማሽ ማራቶን የሴቶችን ብቻ የርቀቱን የዓለም ክብረወሰን በ1፡05፡24 ሰዓት ያሻሻለችው ኬንያዊት አትሌት ከአርባ ሁለት ቀናት በኋላ በፖላንድ ጊዲኒያ የዓለም ግማሽ ማራቶን ቻምፒዮና የራሷን ክብረወሰን በአስራ ስምንት ሰከንድ ማሻሻል ችላለች። እነዚህ ሁሉ ክብረወሰኖች ሲሰባበሩና አትሌቶች በተለየ መልኩ አስደናቂ ብቃት ሲያሳዩ አብዛኛው የስፖርት ቤተሰብ ሁለት ነገሮችን ጠርጥሯል። ይህም በወረርሽኙ ምክንያት አትሌቶች ለረጅም ጊዜ ከውድድር በመራቃቸው ሰፊ የዝግጅት ጊዜ በማግኘት ወደ ውድድር ሲመለሱ ምርጥ ብቃት ሊኖራቸው እንደቻለና በነዚያ የረፍት ጊዜያት በጉዳት ላይ የነበሩ አትሌቶች በበቂ ሁኔታ ማገገም በመቻላቸው እንደሆነ ይታሰባል። ስፖርቱን በጥልቀት የሚመለከቱ በርካታ ተንታኞች ግን ከዚህም የበለጡ ገፊ ምክንያቶች ከክብረወሰኖቹ መሰባበር ጀርባ እንዳሉ ያምናሉ። የልምምድ ስነልቦናና ሂደት በወረርሽኙ ምክንያት እየተለወጠ መምጣቱ ለክብረወሰኖቹ መሻሻል አንድ ምክንያት ተደርጎ ይወሰዳል። ይህም የወረርሽኙ ስጋት ቀደም ብሎ አትሌቶች በርከት ብለው በአንድ አሰልጣኝና በአንድ ካምፕ ውስጥ ሆነው የሚያደርጉትን የተለመደ ዝግጅት ወደ ጎን ትተው በተናጠል በሚመቻቸው ስፍራና በቤታቸው ሆነው እንዲዘጋጁ እድል መስጠቱ ነው። ይህ አጋጣሚ አትሌቶች አንዱ አንዱን ሳይጠብቅ በራሳቸው መርሃግብር መሰረት ወጥ በሆነ መልኩ እስከ አቅማቸው ጥግ ድረስ እንዲዘጋጁ ያስቻላቸው ሲሆን በስነልቦናውም ረገድ ጠንካራ እንዲሆኑ አድርጓል። ለዚህም ከወረርሽኙ በኋላ ክብረወሰኖችን ያሻሻሉ አትሌቶች ቀደም ሲል ይከተሉት የነበረው የልምምድ መልክ በወረርሽኙ ሳቢያ መቀየሩ ለክብረወሰኖች መሻሻል ቁልፍ ሚና እንዳለው የሚያስቀምጡ ባለሙያዎች በርካታ ናቸው። በሌላ መልኩ አትሌቶች በወረርሽኝ ምክንያት ውድድሮች ቢቆሙም የሆነ ጊዜ ላይ እንደሚቀጥሉ አውቀው ዝግጅታቸውን ሳያቋርጡ ተግተው መስራታቸው የክብረወሰን ባለቤት እንዳደረጋቸው ይታመናል። አትሌቶች ወረርሽኙ የጤና ስጋት ቢሆንም መጥፎን አጋጣሚ ወደ ጥሩ ለውጠው ተጠቅመዋል። አቋማቸው እንዳይወርድ በመጠንቀቅ መዘጋጀታቸው ኋላ ላይ ለስኬት አብቅቷቸዋል። በተለይም እቤት የመቀመጥ አስገዳጅ ሁኔታው ቀደም ሲል የነበረባቸውን የተጣበበ የልምምድና የውድድር ጫና በማስቀረቱ በበቂ ሁኔታ እንዲዘጋጁ በር ስለከፈተላቸው በደህናው ጊዜ ማሳካት ያልቻሉትን ክብረወሰን እንዲያሳኩ አድርጓቸዋል። ከወረርሽኙ ጋር በተያያዘ የተፈጠሩ መልካም አጋጣሚዎች እንዳሉ ሆነው የስፖርት ቴክኖሎጂ እየዘመነ መምጣት ለተመዘገቡት ክብረወሰኖች የአንበሳውን ድርሻ እንደሚይዝም ዓለም አቀፍ የስፖርቱ ምሁራን የሚስማሙበት ጉዳይ ነው። ባለፉት ጥቂት ወራት ሲመዘገቡ ያየናቸው በርካታ ክብረወሰኖች አትሌቶች የሚያስመዘግቧቸው ሰዓቶች ላይ ሰፊ ልዩነት በሚፈጥሩ ዘመናዊ የመሮጫ ጫማ እንዲሁም አሯሯጮች በተለይም በመም ውድድሮች ከሰው ይልቅ ቴክኖሎጂ ሆኖ አትሌቶችን እስከ መጨረሻ ድረስ በሚፈለገው ደረጃ በማገዝ የተመዘገቡ ናቸው። ግዙፉ የስፖርት ትጥቅ አምራች ኩባንያ ናይኪ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ የሚያቀርባቸው የመሮጫ ጫማዎች ቀደም ሲል የዓለም ክብረወሰን ሲመዘገብባቸው ከቆዩ የመሮጫ ጫማዎች አንፃር በአትሌቶች ፍጥነት ላይ የጎላ ተፅዕኖ እንዳላቸው አትሌቶችም ይሁን የስፖርት ቤተሰቡ ይስማማሉ። ከዚህ በላይ የጥሩነሽ ዲባባ የአምስት ሺ ሜትር ክብረወሰን በሌላኛዋ ኢትዮጵያዊት አትሌት ለተሰንበት ግደይ እና የቀነኒሳ በቀለ የአምስትና አስር ሺ ሜትር ክብረወሰኖች በዩጋዳዊው አትሌት ጆሽዋ ቺፕቴጌ ሲሰበሩ አትሌቶቹን በአሯሯጭነት ያገዛቸው በመሮጫው መም ዙሪያ የተገጠመው መብራት(Wave-lights) እንደነበር ይታወቃል። ይህ ቴክኖሎጂ አትሌቶቹ በምን ያህል ፍጥነት እያንዳንዱን ዙር ሮጠው ክብረወሰን እንደሚጨብጡ አስልቶ በማሯሯጥ እስከ መጨረሻ ድረስ ደግፏቸዋል። አሯሯጭ በአትሌቲክሱ ዓለም ክብረወሰኖችን ለማስመዝገብ ወሳኙ ነገር እንደሆነ ይታወቃል። አንዳንድ ጊዜ ሴት አትሌቶች በወንድ አሯሯጮች ታግዘውም አሯሯጮች በሚፈለገው ፍጥነት መጓዝ ካልቻሉ ክብረወሰን የማይሰበርበት አጋጣሚ ጥቂት እንዳልሆነ ይታወቃል። አሯሯጩ ቴክኖሎጂ ሆኖ እስከ መጨረሻ ድረስ ወጥ በሆነ ስሌት አትሌቶችን ሲያግዝ ግን የተለየ እንደሚሆን የቅርቦቹ ክብረወሰኖች ምስክር ናቸው።አዲስ ዘመን ታኅሣሥ 5/2013
https://www.press.et/Ama/?p=37367
844
2ስፖርት
ታላቁ ሩጫን በጥንቃቄ
ስፖርት
December 14, 2020
9
 ቦጋለ አበበ የ20ኛው ቶታል ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ጥር 2 ቀን ይካሄዳል። የውድድሩ ምዝገባ ባለፈው ታህሳስ 2 ቀን የጀመረ ሲሆን ፣ተሳታፊዎች በያሉበት የአሞሌን መተግበሪያ በመጠቀም ምዝገባውን እንዲያካሂዱ ተደርጓል ። የመጀመሪያዎቹ 200 ተሳታፊ ተመዝጋቢዎች ለውድድሩ መዘጋጃ የሚሆን የመለማመጃ ቲ-ሸርት በነጻ እንደሚሰጣቸውም የውድድሩ አዘጋጆች ከላኩት መግለጫ ታውቋል። 20ኛው ቶታል ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ በዘንድሮ ውድድሩ ከወትሮው ለየት ባለ መልኩ 12ሺ500 ተሳታፊዎች ብቻ ይኖሩታል። በተጨማሪም የአለም አቀፍ ተሳታፊዎችን ለማካተት ውድድሩ በሚካሄድበት ተመሳሳይ ቀን በቨርቹዋል ውድድር በያሉበት ተሳታፊ እንዲሆኑና የ20ኛውን አመት ክብረ በዓል አብረው እንዲያከብሩ ቅድመ ሁኔታ ተጠናቋል። የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ባወጣው መመሪያ መሰረት ከቀድሞ ተሳታፊ 25 በመቶ ብቻ አሳታፊ የሚያደርገው ታላቁ ሩጫ የሚከተሉትን የኮቪድ-19 ቅድመ ጥንቃቄዎች ተግባራዊ ያደርጋል። ውድድሩ የሚጀመረው በሶስት የተለያዩ ማዕበሎች(አረንጓዴ፤ ቢጫ፤ ቀይ) ይሆናል። ሶስቱ ማዕበሎች ወደ መስቀል አደባባይ የሚመጡበት አቅጣጫ በየቲሸርት ቀለሙ ተለያይቶ የተሰየመ ነው። እያንዳንዱ ማዕበልም ማህበራዊ ርቀትን ለማስጠበቅ ሲባል በ 3 እና በ4 ቡድን ይከፈላል። ሩጫው በሶስት የተለያዩ መነሻ ሰዓታት የሚደረግ ይሆናል፤ ተሳታፊዎች የሚጀምሩበትን ሰዓት እና አብረው የሚሮጡትን ቡድን ለመለየት ከሩጫ ቲ-ሸርታቸው ጋር አብረው የሚወስዱት የደረት የመሮጫ ፊደል ጠቋሚ ይሆናል። እያንዳንዱ ተሳታፊ ከሚመርጠው የቲ-ሸርት ቀለም ባሻገር የመወዳደሪያ የደረት ቁጥር በፊደል የሚወስዱ ይሆናል። ተሳታፊዎች የመሮጫ ቲ-ሸርታቸውን ሲወስዱ አብሮ የሚሰጣቸውን የአፍና አፍንጫ ጭንብል የውድድሩ መነሻ፤ የመሰበሰቢያ ቦታና ውድድሩን ከጨረሱ በኋላ ማድረግ ይኖርባቸዋል። ከዚያም በተጨማሪ ተሳታፊዎች መወዳደሪያ ቦታው ላይ እንደደረሱ እያንዳንዱ ተሳታፊ የሰውነት ሙቀት ልኬት ይደረግለታል።እንዲሁም በውድድሩ መነሻና መድረሻ የእጅ ማጽጃ ሳኒታይዘር ይቀርባል። ‹‹ወፎችን ታሳቢ ያደረገ የሀይል መሰረተ ልማት›› የ2013 የሩጫው መልዕክት ሲሆን፣ ‹‹በርድ ላይፍ አፍሪካ- የነጩ ጆፌ አሞራ ፕሮጀክት›› የዚህ መልዕክት አስተላላፊና አጋር ድርጅት ነው።የዚህን ዓመት ታላቁ ሩጫ ለየት የሚያደርገው የውድድሩ መነሻ መስቀል አደባባይ ሆኖ መድረሻው አትላስ አካባቢ መሆኑ ነው። ተሳታፊዎች ውድድሩ ሊካሄድ 10ቀናት ሲቀሩት የመወዳደሪያ ቲ-ሸርት፤ የመሮጫ የደረት ቁጥር ፊደል እና ጭምብል ምዝገባ ሲያደርጉ በመረጡዋቸው የዳሽን ባንክ ቅርንጫፎች በመሄድ መቀበል ይኖርባቸዋል።  አዲስ ዘመን ታኅሣሥ 5/2013
https://www.press.et/Ama/?p=37370
274
2ስፖርት
የባዶ እግር ትሩፋቶች
ስፖርት
December 15, 2020
16
ብርሃን ፈይሳየበጋማው ወቅት ሞቃታማ የአየር ሁኔታ ጎዳናውን ቢያግለውም፣ ባዶ እግሩን ሮጦ ከማሸነፍ አላገደውም። ጦር ያዘመተችባት ሃገር ሽንፈትን በተከናነበችበት ማግስት ብቻውን ዘምቶ እንደ አንድ ባታሊዮን ጦር አሸንፎ የኢትዮጵያዊያንን አንጀት አራሰ እንጂ፡፡ በእርሱ እግር የተተካውም፤ በቀናት ልዩነት በመም የተካፈለበትን ርቀት ከመጤፍ ሳይቆጥር በማራቶንም ዳግም ሃገሩን በክብር አስጠርቷል፡፡ሌላኛው ደግሞ እስርና ሌላ ኦሊምፒክን ማሳለፍ ተስፋ ሳያስቆርጠው በአንድ ኦሊምፒክ ሁለት የወርቅ ሜዳሊያዎችን በማጥለቅ ዓለምን ‹‹አጀብ›› አሰኝቷል፡፡ሴቶች በኋላ ቀሩ ሶስተኛው ዓለም በዚህ ደረጃ እንደሚገኙ በማይገመትበት ወቅት በአፍሪካ የመጀመሪያውን የኦሊምፒክ ወርቅ ሜዳሊያ የግሏ ያደረገች እንስት የተፈጠረችው በዚህችው ሀገር ነው፡፡በቀደሙት መንገድ የተጓዙ አይበገሬዎች፤ የዓለምን ክብረወሰኖች በመሰባበር ኢትዮጵያ የማትነጥፍ የድል አድራጊዎች እናት መሆኗን አስመስክረዋል፡፡በጉዳት ያልተበገሩ፣ ታላላቆቻቸውን ያከበሩ፣ ሃገራቸውን አስቀድመው፤ ላብ እንባና ደማቸውን ያፈሰሱ ኢትዮጵያዊያን ጀግኖች ጥቂት አይደሉም፡፡አንድን ውድድር መጨረስ ህልም የሆነባቸው ብዙ ሃገራት ባሉባት ዓለም አበበን የተከተሉ የባዶ እግር ትሩፋቶች፤ ህዝባቸውን በደስታ ጮቤ እያስረገጡና የሃሴት እንባ እያስነቡ ስድስት አስርት ዓመታትን ተሻግረዋል፡፡ሜዳሊያና ዲፕሎማ ከማስመዝገብም አልፈው ሃገራቸውን በተሳትፎ ያከበሩ አትሌቶች፣ በቡድን መሪነት፣ አሰልጣኝነት፣ የህክምና እና የቴክኒክ ባለሙያነት እንዲሁም በመገናኛ ብዙኃን ድሉን ለህዝብ በማድረስም ሚና የነበራቸው ጥቂቶች አይደሉም፡፡ይሁን እንጂ እነዚህ የሃገር ባለውለታዎች በሚገባቸው ልክ ሳይከበሩና ሳይመሰገኑ ቆይተዋል፡፡የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽንም ጀግናን ማክበር፤ ለመጪው ትውልድ ብርታት ነውና ከሜልቦርን እስከ ሪዮ ኦሊምፒኮች ሃገራቸውን ለወከሉ ምስጋናውን በልዩ ክብር አበርክቷል፡፡‹‹የባዶ እግር ትሩፋቶች›› በሚል በተካሄደው መርሃ ግብር ላይም ተሳትፎ ላስመዘገቡ አትሌቶችና ባለሙያዎች ከ25ሺ ብር ጀምሮ የሚጨምር የገንዘብና የዋንጫ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል፡፡በህይወት0ቀዳሚዎቹ አትሌቶች፣ አሰልጣኝና ጋዜጠኛም እረፍታቸው በተደረገበት ስፍራ በመገኘት የአበባ ጉንጉን የማኖር ስነስርዓትም ተካሂዷል፡፡ በሽልማት መርሃ ግብሩ ላይም የታላቁ አትሌት ልጅ የትናየት አበበ ቢቂላ የሁለት ሚሊየን ብር ሽልማት ከኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ተቀብሏል፡፡ የሌላኛው ተአምረኛ አትሌት ልጅ ሳሙኤል ማሞ ወልዴ እና የልጅ ልጁ እንዲሁም የድርብ ድሉ ባለቤት ‹‹ማርሽ ለዋጩ›› ባለቤትና ልጃቸው ቢኒያም ምሩጽ ይፍጠር ደግሞ አንድ አንድ ሚሊየን ብር ተበርክቶላቸዋል፡፡ የኢትዮጵያ አትሌቲክስንና ድልን ያወዳጃቸው ጀግናው አትሌት ሻምበል አበበ ቢቂላ ቢሆንም፤ የድሉን ቀጣይነት ያወጀው ሌላኛው ወርቃማ አትሌት ሻምበል ማሞ ወልዴ ነው፡፡ማሞ የአበበን ፈለግ ተከትሎ ሃገሩ የለመደችው እንዳይጎድልባት በላቡ ክብሯን ከማድመቅም አልፎ ለተተኪ አትሌቶችም መንገድ ጠራጊ ሆኗል፡፡ ይህ በድል የተንቆጠቆጠ አትሌት ዛሬ በህይወት ባይኖርም ከሃገሩ የቀረበለትን ምስጋና በልጁ ተረክቧል፡፡ ሳሙኤል ማሞ ወልዴ፤ አባቱን ወክሎ ለተገኘበት መድረክ ከፍተኛ ደስታ እንደተሰማውም ገልጿል፡፡ለሃገሩ ብዙ ዋጋ የከፈለው አባቱ የሚገባውን ያህል ሳይደረግለት አልፏል፤ ቤተሰቦቹም ድጋፍ ይሹ ነበር፡፡ይባስ ብሎ ከ13 ዓመታት በፊት የመቃብር ሃውልቱ ፈረሰ፤ ይህንን ተከትሎም ልጁ በግሉ ብዙ ጥረቶችንም አድርጎ ሰሚ ባለማግኘቱ ትቶት ነበር፡፡አሁን ግን በአትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ኮማንደር ደራርቱ ቱሉ ጥረት ሃውልቱ በድጋሚ በመሰራቱና እውቅናው በመሰጠቱ እንዲሁም ሻምበል ማሞ ካረፈበት ጊዜ ጀምሮ ለቤተሰቦቹ ድጋፍ ላደረጉ ሁሉ ምስጋናውን አቅርቧል፡፡ በኢትዮጵያ አትሌቲክስ የወንዶች ተሳትፎ ቀዳሚ ቢሆንም አሁን ባለው ነባራዊ ሁኔታ ግን የሴት ኦሊምፒያኖች ድል በእኩል ደረጃ የሚጠቀስ ሊሆን ችሏል፡፡ በስፖርቱ ከቀዳሚዎቹና ፈር ቀዳጆቹ መካከል አንዷ በምስጋና መርሃ ግብሩ ላይ ተገኝተው ለሃገራቸው ስላበረከቱት አስተዋጽኦ የዋንጫና የገንዘብ ሽልማታቸውን ወስደዋል፡፡ በአትሌትነትና አሰልጣኝነት ሃገራቸውን አገልግለው በጡረታ ላይ የሚገኙት ወይዘሮ ጽጌ ገብረመሲህ፤ እርሳቸውና መሰሎቻቸውን ተከትለው በየዘመኑ የወጡ አትሌቶች ሃገራቸውን በማስጠራታቸውና በዚሁ ምክንያትም የሽልማት ተካፋይ በመሆናቸው ክብር እንደተሰማቸው ገልጸዋል፡፡ አብዛኛዎቹ ተሸላሚዎች በጡረታ የተገለሉ፣ የተረሱ፣ ወደፊት ወጥተው ያልታዩ አንዳንዶች ደግሞ በሞት የተለዩ ቢሆኑም፤ ሁሉንም አስታውሶና አሰባስቦ ለሽልማት ማብቃት አስደሳች ነው፡፡ወደፊትም ይህን መሰል አትሌቶች አሰልጣኞችና አመራሮችም ጭምር በተመሳሳይ መልኩ እንዲታወሱ፤ በተለይ መገናኛ ብዙሃን የአትሌቲክስ ቤተሰቦች እንዲበረቱ ማስታወስ እንደሚገባቸውም ጠቁመዋል፡፡ በመድረኩ ተገኝተው እውቅናውን ያበረከቱት የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ፤ አበበ ቢቂላና እሱን የተከተሉ አትሌቶች ለሃገራቸው ያበረከቱት አስተዋጽኦ የሚለካ ባይሆንም፣ እንደሚገባቸው አለመከበራቸውን ጠቅሰዋል፡፡ይህ የምስጋና መድረክ መዘጋጀት በርካታ ጉዳዮችን ያስተምራል፤ ከምንም በላይ ኢትዮጵያን አስተዋውቀዋልና ጀግኖች ሊከበሩና ሊዘመርላቸውም ይገባል፡፡ ኢትዮጵያ ስትነሳ አብሯት የሚነሳው አበበ ቢቂላ፤ ዓለምን የማረከ፣ ባዶ እግሩን ሮጦ ኢትዮጵያን ያስተዋወቀ አትሌት ነው፡፡በተለይ ባንዲራዋን ከፍ ያደረገው በጣሊያን ሃገር መሆኑ ድሉን ከሩጫ በላይ ያደርገዋል።ይህም እጅግ የሚያኮራ በመሆኑ ጀግኖቻችንን ማክበር ከእነሱም መማር አለብን ብለዋል፡፡ጀግኖቹን የማያከብር ሃገር ወደፊት ሊሄድ እንደማይችልም ፕሬዚዳንቷ አመላክተዋል፡፡ የኢፌዴሪ ባህልና ቱሪዝም ሚኒስትር ዶክተር ሂሩት ካሰው በበኩላቸው፤ የሃገር ባለውለታ የሆኑ አትሌቶችን ማመስገን አሁን ላሉት አትሌቶች ስንቅ መሆኑን ይገልጻሉ፡፡ ከዚህ ቀደም ቶኪዮ ላይ በተካሄደ የአበበ ቢቂላ ድል 60ኛ ዓመት መርሃ ግብር ላይ እንደተሳተፉ የጠቀሱት ሚኒስትሯ፤ የኢትዮጵያ በበቂ መልክ አለመዘጋጀት ያስረዳ እንደነበረ ያስታውሳሉ፡፡አበበን ከኢትዮጵያ ይልቅ የሚያከብሩት ጃፓናዊያን ህጻናትም ሳቀሩ ስለ እርሱ ይጠይቃሉ ብለዋል፡፡በወቅቱ በቦታው የተገኙ የፌዴሬሽኑ አመራሮች ስንቅ፣ ልምድና አሰራር ተምረው በመመለሳቸው መርሃ ግብሩን ለማዘጋጀት እንዳበቃቸውም አመላክተዋል፡፡ ስፖርት ኢትዮጵያን እንደ ሃገር የገነባት አንዱ ዘርፍ ነው፡፡በባዶ እግር ሮጦ ማሸነፍ ደግሞ ኢትዮጵያዊያን ውስጣዊና አካላዊ ጥንካሬ ያላቸው ህዝቦች መሆናቸውን ያሳየ ነው፡፡ይህም የይቻላል ስነልቦና ያለው ትውልድ ለመፍጠር የሚያስችል ነው ሲሉ አብራርተዋል፡፡ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ኮማንደር ደራርቱ ቱሉ፤ በርካታ ስራዎችን ያከናወኑ የአትሌቲክስ ጀግኖቻችንን ክብር በመሰጠቱ ደስታዋን ገልጻለች፡፡ፈር ቀዳጆቹን አትሌቶች ተከትለው በ13 ኦሊምፒኮች ላይ ሃገራቸውን ያስጠሩ በርካታ አትሌቶችን ማፍራት ተችሏል ያለችው ፕሬዚዳንቷ፣ የአበበ ቢቂላ ከሮም መልስ በጃፓን ቶኪዮም የሜዳሊያ ድል ባለቤት መሆን የቆራጥነትና ጽናትን በማስተማር ድሉን ያስቀጠለ ሆኗል ብላለች፡፡በቶኪዮ 2021 ለሚካሄደው ኦሊምፒክም አትሌቶች በዝግጅት ላይ እንደሚገኙም ገልጻ፣ የባዶ እግር ትሩፋቶች በሚል የተካሄደው መርሃ ግብርም የኦሊምፒክ ባለውለታዎችን ከመዘከር ባሻገር የማይቋረጥ የሃገር ፍቅር ስሜትን ለመፍጠር በማሰብ መሆኑንም አብራርታለች፡፡አዲስ ዘመን ታህሳስ 6/2013
https://www.press.et/Ama/?p=37432
723
2ስፖርት
የቀጣዩ አራት ዓመት የአትሌቲክስ መሪዎች
ስፖርት
December 16, 2020
8
ቦጋለ አበበየኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ከትናት በስቲያ ባደረገው 24ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔ በቀጣይ አራት ዓመታት ፌዴሬሽኑን የሚመሩ ሰዎችን ለይቷል።ከአራት ዓመት በፊት ፌዴሬሽኑን በፕሬዚዳንትነት ለመምራት የተመረጠው ጀግናው አትሌት ኃይሌ ገብረስላሴ ሁለት ዓመት አገልግሎ በራሱ ፍቃድ ስልጣኑን ከለቀቀ በኋላ ሌላኛዋ ጀግና አትሌት ኮሎኔል ደራርቱ ቱሉ በተቀዳሚ ምክትል ፕሬዚዳንትነት ፌዴሬሽኑን ስትመራ ቆይታለች።ከትናንት በስቲያ ማታ በካፒታል ሆቴል በተደረገው ምርጫም ደራርቱ ለቀጣዩ አራት ዓመት ፌዴሬሽኑን በፕሬዚዳንትነት ለመምራት በጠቅላላ ጉባዔው ይሁንታ አግኝታለች።ምርጫው ከመከናወኑ ከሳምንት በፊት ለፕሬዚዳንትነት ለመወዳደር ዕጩ ሆነው በደቡብ ክልል የተወከሉት አቶ ተፈራ ሞላ፣ ለስፖርቱ ቅርበት ያላት ደራርቱ ከመሆኗ ባሻገር ባለፉት ሁለት ዓመታት በተቀዳሚ ምክትል ፕሬዚዳንትነት ፌዴሬሽኑን በመምራት ያደረገችውን ጥረት እንድትቀጥል ከእጩነት ራሳቸውን ማግለላቸው ይታወቃል።በዚህም ደራርቱ በፕሬዚዳንትነት ምርጫ ፉክክሩ ብቸኛ እጩ ሆና በመቅረብ አስቀድሞም ማሸነፏ የተረጋገጠ ነበር።በዚህም ጠቅላላ ጉባዔው በሃያ ሰባት ድምፅና በአንድ ተቃውሞ የደራርቱን ፕሬዚዳንትነት እንዳረጋገጠ በወቅቱ የተገለጸ ቢሆንም ፌዴሬሽኑ ደራርቱ ካለምንም ተቃውሞ በሙሉ ድምፅ ማሸነፍ እንደቻለች ትናንት ገልጿል።በምርጫው በተሰጠው ድምፅ በአንድ ተቃውሞ መመረጧ የተገለጸው በስህተት መሆኑን የጠቆመው ፌዴሬሽኑ በድምፅ አሰጣጥ ወቅት በምርጫ ወረቀት ላይ ድምፅ ሰጪው የራይት ምልክት ማድረግ ሲገባቸው የኤክስ ምልክት በማድረጋቸው መሆኑን አረጋግጧል። ከፕሬዚዳንታዊ ምርጫው ይልቅ ለሥራ አስፈፃሚነት በቀረቡት አስራ ስምንት እጩዎች መካከል የሚደረገው ፉክክር በጉጉት እንዲጠበቅ አድርጎታል።ከአራት ዓመት በፊት በሥራ አስፈፃሚነት ለመወዳደር እጩ ሆኖ ቀርቦ በአንድ ድምፅ ተበልጦ ያልተሳካለት የሲድኒ ኦሊምፒክ የማራቶን ባለድሉ አትሌት ገዛኸኝ አበራ ዘንድሮ በኦሮሚያ ክልል እጩ ሆኖ በመቅረብ ተሳክቶለታል።በተመሳሳይ ኦሮሚያ ክልል እጩ አድርጎ ያቀረባቸው ወይዘሮ ሰሃራ ሃሰን አዲስ የሥራ አስፈፃሚ አባል ሆነው ተመርጠዋል።አማራ ክልል እጩ አድርጎ ያቀረባቸው ወይዘሮ አበባ ዮሴፍም አዲስ የሥራ አስፈፃሚ አባል ሆነው ተመርጠዋል።ወይዘሮ አበባ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሴቶች፣ወጣቶችና ሕፃናት ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ መሆናቸው ይታወቃል።ባለፉት አራት ዓመታት የፌዴሬሽኑ ሥራ አስፈፃሚ አባል ሆነው ሲያገለግሉ የቆዩት ባለሀቱ አቶ በላይነህ ክንዴም ከአማራ ክልል ለሥራ አስፈፃሚነት ተወዳድረው በማሸነፍ የሚቀጥሉ ይሆናል።አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባልነት ያቀረባቸው ሁለት እጩዎችም አሸናፊ መሆን ችለዋል።የስፖርት ሳይንስ መምህሩና በስፖርቱ ውስጥ ለረጅም ጊዜ በማገልገል የሚታወቁት ዶክተር በዛብህ ወልዴ ባለፉት ዓመታትም ሥራ አስፈፃሚ አባል የነበሩ ሲሆን፤ ለቀጣዩ አራት ዓመትም እንደሚቀጥሉ አረጋጠዋል።ሌላኛዋ  የአዲስ አበባ እጩ ወይዘሮ ትልቅሰው ገዳሙም አዲስ ሥራ አስፈፃሚ አባል ሆነዋል።ከፕሬዚዳንታዊ ምርጫው ራሳቸውን በማግለል በሥራ አስፈፃሚነት የተወዳደሩት አቶ ተፈራ ሞላም ከደቡብ ክልል ሥራ አስፈፃሚ ሆነው ተመርጠዋል።ባለፉት ዓመታት በሥራ አስፈፃሚነት ሲያገለግሉ የቆዩት የአፋር ክልል ተወካይ ወይዘሮ ፊዚያ ኢድሪስም የሚቀጥሉበት ዕድል አግኝተዋል።በጠቅላላ ጉባዔው ወቅት ስፖርቱን ባለፉት ጥቂት ዓመታት በመምራት ምስጉን ሥራዎችን እንዳከናወነች በመግለጽ አድናቆት ሲቸራት የነበረችው ደራርቱ ከምርጫው በኋላ ፕሬዚዳንትነቷን በማረጋገጧ ባላት ልምድና እውቀት አገሯን በቅንነት ለማገልገል ቁርጠኝነቱ እንዳላት ተናግራለች።በእጩነት ያቀረባትን ኦሮሚያ ክልል እንዲሁም ከፕሬዚዳንታዊ ምርጫው ራሳቸውን በማግለል እድሉን እንድታገኝ ያደረጉትን አቶ ተፈራ ሞላን አመስግናለች።በቀጣይም ባለፉት ዓመታት ከነባሩ ሥራ አስፈፃሚ ጋር ስፖርቱ የሚፈልገውን ሁሉ ለማድረግ ያደረገችውን ጥረት ከአዲሱ ሥራ አስፈፃሚ ጋር እንደምትቀጥልበት ቃል ገብታለች።ፌዴሬሽኑ በቀጣይ ስምንት ዓመታት የሚመራበት ስትራቴጂክ እቅድ ለጠቅላላ ጉባዔው ቀርቦ የፀደቀ ሲሆን፤ የተለያዩ ሃሳቦች ቀርበውም ውይይት ተደርጎባቸዋል።ፌዴሬሽኑ የተለያዩ እቅዶችን ሲያቀርብ አትሌቶችን በዓለም አቀፍ ውድድሮች ወደተለያዩ አገራት በመላክ ለመወዳደር እንጂ በአገር ውስጥ ዓለም አቀፍ ውድድሮችን የማዘጋጀት እቅድ ለምን አይኖረውም? የሚል ጥያቄ በመድረኩ ከተነሱ ሃሳቦች አንዱ ነው።ለዚህ ጥያቄ በተሰጠው ምላሽም ፌዴሬሽኑ ዓለም አቀፍ ውድድሮችን ወደ ኢትዮጵያ ለማምጣት ጥረት እንደሚያደርግ የተገለጸ ሲሆን፤ ዘንድሮ የአፍሪካ አገር አቋራጭ ቻምፒዮናን ለማስተናገድ እንደታሰበ ተጠቁሟል።ፌዴሬሽኑ በተለያዩ ዓመታዊ የውድድር መርሐግብሮቹ በሚያካሂዳቸው የጎዳና ላይ ውድድሮች የሕብረተሰብ ተሳትፎ አለመኖሩ ለብዙ ጊዜ ሲነሳ የነበረ ጥያቄ ሲሆን፤ ሕዝብ የሚሳተፍባቸው ውድድሮችን ለማካሄድ እቅድ እንዳለ ተጠቁሟል።ፌዴሬሽኑ በሌሎች ጉዳዮች ላይ ተወጥሮ ስልጠናን በመዘንጋት ውጤቶች በሚጠበቀው ደረጃ እየተገኙ እንዳልሆነም ትችቶች ተሰንዝረዋል።አዲሱ የሲዳማ ክልል አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የጉባዔው ተሳታፊ ከመሆኑ ባሻገር በሥራ አስፈፃሚ ምርጫ ላይ አንድ እጩ ባቀረበበት መድረክ በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ምክኒያት ስፖርቱ አስቸጋሪ ጊዜ ማሳለፉ ተገልጿል።ይሁን እንጂ በነዚህ አስቸጋሪ ጊዜያት ፌዴሬሽኑ እቅዶቹን በታሰበው ልክ ማከናወን ባይችልም እጁን አጣጥፎ ሳይቀመጥ በጥንቃቄ የተለያዩ ሥራዎችን ሲያከናውን እንደቆየ ተጠቁሟል።ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በዓለም አቀፍ ውድድሮች ‹‹ይህን ያህል ሜዳሊያዎች እናስመዘግባለን›› ብሎ ማቀድ አዳጋች እየሆነ መምጣቱን የጠቆሙት የፌዴሬሽኑ ፅሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ቢልልኝ መቆያ የስፖርቱ ባህሪ እየተቀየረ እንደሚገኝ አስረድተዋል።በተለይም ኢትዮጵያ በምትታወቅበት የረጅም ርቀት ውድድሮች ሌሎች አገራትም ውጤታማ እየሆኑ መምጣታቸው ለዚህ ፈተና አንዱ ምክኒያት እንደሆነ የገለጹ ሲሆን፤ የሌሎች አገራት የኢኮኖሚ ጥንካሬና የዓለም አቀፍ ውድድር አዘጋጆች የአትሌቶች አበረታች መድሃኒት ተጠቃሚነትን ሽፋን መስጠት ተፅዕኖው ቀላል እንዳልሆነ አብራተዋል።ፌዴሬሽኑ በጉባዔው ከኮቪድ-19 ወረርሽኝ በፊት በነበረው የስፖርቱ እንቅስቃሴ ጥሩ ሥራ ሠርተዋል ያላቸውን ከክልልና ከተማ አስተዳደሮች እንዲሁም ከክለቦች ስምንት ስምንት ተሸላሚዎችን መርጦ እንደየደረጃቸው ገንዘብ አበርክቶላቸዋል።በዚህም የኦሮሚያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ቀዳሚ በመሆን 240ሺ ብር ተሸላሚ ሲሆን፤ የአማራ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን 180ሺ ብር ተሸላሚ ሆኗል።አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር 140ሺ፣ ደቡብ ክልል 100ሺ፣ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ 80ሺ፣ ሐረሪ 60ሺ፣ ድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር 40ሺና ጋምቤላ 20ሺ ብር ተሸላሚ ሆነዋል።ከክለቦች መከላከያ ስፖርት ክለብ ቀዳሚ በመሆን ሦስት መቶ ሺ ብር ተሸላሚ ሲሆን፤ የፌዴራል ፖሊስ ስፖርት ክለብ 240ሺ ብር ሊሸለም ችሏል።ጥሩነሽ ዲባባ አካዳሚ 180ሺ፣ ኦሮሚያ ፖሊስ 140ሺ፣ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 100ሺ፣ ደቡብ ፖሊስ 80ሺ፣ ሲዳማ ቡና 60ሺና ኦሮሚያ ውሃ ሥራዎች 40ሺ ብር ተሸላሚ ሆነዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 7/2013
https://www.press.et/Ama/?p=37493
713
2ስፖርት
ቡድኑ ዝግጅቱን አስቀድሞ መጀመሩ ለውጤታማነት ያግዘዋል
ስፖርት
December 17, 2020
13
ብርሃን ፈይሳ የቶኪዮ 2021 ኦሊምፒክ ከመካሄዱ ወራትን አስቀድሞ ዝግጅት መጀመሩ የተሻለ ውጤት እንዲመዘገብ የሚያደርግ መሆኑ ተገለጸ። በኦሊምፒክ መድረክ ሃገራቸውን ለወከሉ አትሌቶች የተካሄደው የምስጋና መርሃ ግብር፤ ለመጪው ኦሊምፒክ ተሳታፊዎች መነሳሳትን እንደሚፈጥርም ተጠቆመ፣ ከዚህ ቀደም ይደረግ ከነበረው በተለየ ሁኔታ ከወራት በፊት ካምፕ በመግባት የረጅም ጊዜ ዝግጅት ማድረግ በቶኪዮ ኦሊምፒክ የሚሳተፈው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ቡድን የተሻለ ውጤት እንዲያመዘገብ ያስችላል ተብሏል። በ5ሺ ሜትር ሃገሩን ለመወከል በቡድኑ የተካተተው አትሌት ጫላ ከተማ፤ ብሄራዊ ቡድኑ ዝግጅቱን ከጀመረ አንድ ወር እንዳስቆጠረ ይገልጻል። ማረፊያውን በጥሩነሽ ዲባባ ሆቴል ያደረገው ቡድኑ በሰንዳፋ፣ አዲስ አበባ ስታዲየም እና በቃሊቲ ዝግጅት እያደረገ ሲሆን፤ በውድድሩ ወቅት በጃፓን የሚኖረው የአየር ሁኔታ ሞቃታማ ሊሆን ስለሚችል ከባድ ሊያደርገው ይችላል ከሚለው ግምት ባሻገር መልካም ዝግጅት እያደረጉ መሆኑን ያረጋግጣል።እንደ አትሌቱ ገለጻ፤ ከዚህ ቀደም ከወራት በፊት ካምፕ በመግባት ለረጅም ጊዜ ዝግጅት ተደርጎ አያውቅም። ኢትዮጵያ የምትታወቀው በቡድን ስራ ቢሆንም በዝግጅት ወቅት ተለያይቶ መስራት ውጤት እንዲጠፋ አድርጎት ቆይቷል። አሁን ግን ለረጅም ወራት አትሌቱ በአንድ ተሰባስቦ መስራቱ አትሌቶች እንዲግባቡና ለቡድን ስራም የሚያግዝ መሆኑን ያምናል። በአሰልጣኞችና በፌዴሬሽኑ ድጋፍና ክትትል እየተደረገላቸው መሆኑም የተሻለ ውጤት ይመጣል የሚል እምነቱንም አትሌቱ ያንጸባርቃል። ከዚህ ባሻገር ቡድኑ ኮቪድ 19ን በመከላከል ረገድም አስፈላጊውን ሂደት እየተከተሉ መሆኑን አትሌት ጫላ ይጠቅሳል። ያረፉበት ሆቴል ከአትሌቶች ውጪ ሌሎች ሰዎች የማይገለገሉበት ሲሆን፤ በልምምድና በሌሎች እንቅስቃሴዎች ውስጥም ንጽህናቸውንና ርቀታቸውን ከመጠበቅ ጎን ለጎን በጤና ባለሙያዎችም ክትትል እየተደረገላቸው ይገኛል ሲል ያብራራል። ‹‹የባዶ እግር ትሩፋቶች›› በሚል በኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን አዘጋጅነት በቅርቡ የተካሄደው የእውቅናና የሽልማት መርሃ ግብር፤ በቶኪዮ ኦሊምፒክ ተሳታፊ ለሚሆኑ አትሌቶች መነሳሳትን እንደሚፈጥርም በባለሙያዎች ታምኖበታል። በዓለም አቀፍ ደረጃ በተከሰተው የኮቪድ 19 ወረርሽኝ ምክንያት ኦሊምፒክ ለአንድ ዓመት መራዘሙ ይታወቃል። ይህንን ተከትሎም ለቶኪዮ 2021 ኦሊምፒክ አትሌቶችና አሰልጣኞች ከወዲሁ ዝግጅት መጀመራቸውን የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ደራርቱ ቱሉ ጠቁማለች። ለብሄራዊ ቡድን የተመረጡት አትሌቶች ለሁለት ተከፍለው በአሰለፈች መርጋ እና በጥሩነሽ ዲባባ ሆቴል መቀመጫቸውን በማድረግ ዝግጅት እያደረጉ ነው። ይህ በእንዲህ እንዳለ ፌዴሬሽኑ ለቀደሙት የኦሊምፒክ ተሳታፊዎችና ባለድል አትሌቶች እንዲሁም ባለሙያዎች ማበረታቻ ማዘጋጀቱ፤ በቡድኑ ለታቀፉ አትሌቶች ሞራል እንደሚሆን ይጠበቃል። በምስጋና መርሃ ግብሩ ላይ ተገኝተው ለአትሌቶችና ቤተሰቦቻቸው ሽልማት ያበረከቱት የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ፤ ዘመኑ እንዳሁኑ ባልሰለጠነበትና መሰረተ ልማትም ባልተሟላበት ወቅት ኑሮ ከሩጫ ጋር የተያያዘ በመሆኑ አትሌቶች ስልጠናም ሳያስፈልጋቸው በኦሊምፒክ ሮጠው ማሸነፋቸውን ጠቅሰዋል። አሁን ግን ጊዜው እንደዚያ አለመሆኑን ጠቅሰው፣ አትሌቶች ለቶኪዮ ኦሊምፒክ በደንብ መዘጋጀት ይኖርባቸዋል ብለዋል። በኦሊምፒኩ የሚሳተፉ አትሌቶች ሆቴል ቢገቡም ጊዜው እጅግም ሩቅ ባለመሆኑ በደንብ መጠበቅ እንዳለባቸውም ነው ያሳሰቡት። መጪው ኦሊምፒክም በሽልማት መድረኩ ስማቸው የተነሳው አትሌቶች ገድል የሚታደስበት ሊሆን ይገባል ያሉት ፕሬዚዳንቷ፣ ለቶኪዮ በሁሉም መንገድ መዘጋጀት እንደሚያስፈልግም አሳስበዋል። ኢትዮጵያንና አፍሪካን ከፍ ለማድረግና ቶኪዮ ላይ ያሸነፈውን የአበበ ቢቂላን ድል ለማደስ፤ የሚመለከታቸው ሁሉ አትሌቶችን በማዘጋጀትና በመደገፍ ጥረት ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው አስታውቀዋል። በቶኪዮ 2021 በአሸናፊነት በተመሳሳይ መርሃ ግብር ለመገናኘት ፕሬዚዳንቷ ምኞታቸውን ገልጸዋል። የቶኪዮ ኦሊምፒክ መራዘም ለበጎ መሆኑን የሚያመላክቱት ደግሞ የኢፌዴሪ ባህልና ቱሪዝም ሚኒስትር ዶክተር ሂሩት ካሰው ናቸው። የቶኪዮ 2021 ድል ከዚህ ቀደም ከነበረው እጥፍ ድርብ እንደሚሆን የጠቆሙት ሚኒስትሯ፤ ለአትሌቶች፣ አሰልጣኞች፣ አመራሮችና በስፖርቱ ላይ ለሚሰሩት ሁሉ የምስጋና መርሃ ግብሩ የብርታት ስንቅ እንደሚሆናቸው ነው የገለጹት። ከአንድ ዓመት በፊት በቶኪዮ በተካሄደ በሻምበል አበበ ቢቂላ ድል የ20 ኪሎ ሜትር የማስታወሻ ሩጫ ላይ የኢትዮጵያ ዝግጅት መልካም እንዳልነበር ለመታዘብ ተችሏል። በወቅቱ በጃፓን የተገኙ የፌዴሬሽኑ አመራሮች ልምድና አሰራር ተምረው መመለሳቸውን ተናግረው፣ በዚሁ መሰረት በመስራት የጀግና እና የይቻላል ስነልቦና የተላበሰ ህዝብ ያለባት ሃገር መሆኗ ዳግም እንደሚታይም ያላቸውን ተስፋ አንጸባርቀዋል።
https://www.press.et/Ama/?p=37572
486
2ስፖርት
ኦሊምፒክ ኮሚቴ ባለድርሻ አካላትን አመሰገነ
ስፖርት
December 19, 2020
10
ቦጋለ አበበ ባለፈው ህዳር 27/2013 ዓ.ም የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ሁለት አህጉራዊ ስኬቶችን በስፖርቱ ዘርፍ አስመዝግቧል። በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የአፍሪካ ብሔራዊ ኦሊምፒክ ኮሚቴዎች ማህበር (አኖካ) ጠቅላላ ጉባዔን ማስተናገድ የመጀመሪያው ስኬት ነው። ከጉባዔው ጎን ለጎን ለመሪዎች የሚበረከተውን የአኖካ የስፖርት የክብር ኒሻን ሽልማት የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በማሸነፋቸው የሽልማት ሥነሥርዓቱን ማስተናገድ ሌላው ስኬት ነው። ሁለቱን ታላላቅ የስፖርት ኩነቶች ኢትዮጵያ በአንድ ቀን በስኬት እንድታስተናግድ ከኦሊምፒክ ኮሚቴው ጋር በቅርበት በመስራት የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ትልቅ አስተዋፅኦ አበርክተዋል። ለዚህም የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ‹‹ከስኬቴ ጀርባ ነበሩ›› ያላቸውን ባለድርሻ አካላት ከትናት በስቲያ ምሽት ያመሰገነበትን መርሃግብር አዘጋጅቷል። በብዙ የተመሰገኑት የስፖርት መገናኛ ብዙሃንን ጨምሮ የተለያዩ የመንግስትና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት እንዲሁም ግለሰቦች በምስጋና መርሃግብሩ ተገኝተው የምስክር ወረቀት ተቀብለዋል። ለአኖካ ጠቅላላ ጉባዔና ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ሽልማት ሥነሥርዓት ከተለያዩ አገራት የመጡ ከሁለት መቶ ሃምሳ በላይ እንግዶችን ለመቀበል በነበረው ሂደት ውስጥ ጉልህ ድርሻ የነበረው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ትልቅ ምስጋና የተቸረው ሲሆን፣ ቃል አቀባዩ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ የምስክር ወረቀቱን ተቀብለዋል። ‹‹የጠቅላይ ሚኒስትር አብይ የአኖካ ሽልማት የተወሰኑ አገራትና መሪዎች ያገኙት እንደመሆኑ ትልቅ ስኬት ነው›› ያሉት አምባሳደር ዲና ለዚህ ስኬት እውን መሆን የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ዶክተር አሸብር ወልደጊዮርጊስ ትልቅ ስራ በመስራታቸው ሊመሰገኑ እንደሚገባ ገልጸዋል። የአኖካ ጠቅላላ ጉባዔ ካለ እንከን እንዲጠናቀቅም የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ጽሕፈት ቤት ሰራተኞች የተወጡት ትልቅ ሃላፊነት አድናቆት እንደሚገባው ተናግረዋል። ሁለቱ ስፖርታዊ ኩነቶች የአገር ገፅታ የተገነባባቸውና ትልቅ ዋጋ የሚገባቸው መሆኑንም አምባሳደሩ አስረድተዋል። ጉባዔውና የሽልማት ሥነሥርዓቱ የተሳካ እንዲሆን ከተዋቀሩት የመስተንግዶ ኮሚቴዎች መካከል አንዱ የሆነው የኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ጌታቸው ድንቁ በበኩላቸው፣ በወቅቱ ኢትዮጵያ በትግራይ ክልል የሕግ ማስከበር ዘመቻ ላይ እንደነበረች በማስታወስ ስፖርታዊ ኩነቶቹን በስኬት ለማስተናገድ ‹‹ከውጭ ሆኖ የሚመለከተው ብቻ ሳይሆን እኛም ጥርጣሬ ነበረን›› ብለዋል። ሆኖም ሁሉም ባድርሻ አካላት የቤት ስራቸውን በስኬት ተወጥተዋል። ይህም ጥሩ ልምድ፣ ትብብርና መልካም የስራ መንፈስ የታየበት እንደነበር አብራርተዋል። የጠቅላይ ሚኒስትሩ    የስፖርት ትልቅ ሽልማት በቀጣይ የቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ ዝግጅት ትልቅ መነሳሳትን እንደሚፈጥርም አክለዋል። የስፖርት መገናኛ ብዙሃን ከመነሻው አንስቶ ለጉዳዩ ሰፊ ሽፋን በመስጠት ያበረከቱት ትልቅ አስተዋጽኦም ብሮድካስት ባለስልጣንን እንዳስደሰተ ተናግረዋል። ‹‹በኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን እንደዚህ ኮርቼ አላውቅም›› በማለት ምስጋናቸውን የጀመሩት የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ፕሬዚዳንት ዶክተር አሸብር፣ በወቅቱ ከፖለቲካና ከኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ስጋት ጋር ተያይዞ ከነበረው አስቸጋሪ ሁኔታ አንፃር የአገር ገጽታ እንዲገነባና ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ የሚገባቸውን ሽልማት እንዲያገኙ የስፖርት መገናኛ ብዙሃን ላበረከቱት ትልቅ አስተዋፅኦ ምስጋና እንደሚገባቸው ተናግረዋል። አገር አቀፍ የስፖርት ፌዴሬሽኖችና ማህበራት፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር፣ የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን እንዲሁም የተለያዩ ግለሰቦችን በትልቁ ያመሰገኑት ዶክተር አሸብር፣ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ፣ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ደመቀ መኮንን ስፖርታዊ ኩነቶቹ በስኬት እንዲጠናቀቁ የአንበሳውን ድርሻ የሚወስዱ በመሆናቸው ልዩ ምስጋና አቅርበዋል። የፌዴራል ስፖርት ኮሚሽን በተቋም ደረጃም ኮሚሽነሩ ኤልያስ ሽኩርና የተቋሙ ባለሙያዎች ከስኬቱ ጀርባ ለነበራቸው ትልቅ ሚና ተመስግነዋል። በርካታ አገራትና መሪዎች የገፉትን የአፍሪካ ፓራሊምፒክ ቻምፒዮና ኢትዮጵያ ለማዘጋጀት ፍቃደኝነቷን በጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አማካኝነት ማረጋገጧን የጠቀሱት ዶክተር አሸብር፣ በተመሳሳይ በጠቅላይ ሚኒስትሩ ይሁንታ በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ከኦሊምፒክ ስምንት ወራት አስቀድሞ ዝግጅት ሊጀመር እንደቻለ አስታውሰዋል። ይህም በቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ ትልቅ ተነሳሽነትን መፍጠር እንደቻለ አብራርተዋል። ‹‹እንዲህ አይነት ልቡንም በሩንም ለስፖርት ክፍት አድርጎ የሚጠብቅ መሪ ባለበት ወቅት የስፖርቱን ትንሳዔ እውን ካላደረግን መቼም አናደርግም›› በማለትም ፕሬዚዳንቱ የምስጋና ንግግራቸውን ቋጭተዋል። የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ጽሕፈት ቤት ሃላፊ አቶ ዳዊት አስፋው ጉባዔውና የሽልማት ሥነሥርዓቱ በስኬት እንዲጠናቀቅ ላደረጉ ባለድርሻ አካላት ምስጋና በማቅረብ ‹‹ሁለቱን ታላላቅ ስፖርታዊ ኩነቶች እኛ አመጣናቸው እንጂ ትልቁን ሃላፊነት የተወጣችሁት እናተ ናችሁ፣ በቀጣይም በርካታ እቅዶች አሉን፣ አብረን በመስራት እናሳካለን›› ብለዋል። የኢትዮጵያ ቅርጫት ኳስ ፌዴሬሽንም ለዶክተር አሸብር ወልደጊዮርጊስ ላበረከቱት አስተዋጽኦ ልዩ ሽልማት አበርክቷል።አዲስ ዘመን  ታህሳስ 10/ 2013
https://www.press.et/Ama/?p=37676
518
2ስፖርት
በሀገሪቱ የሚስተዋሉ ግጭቶችን ለማስቆም ምክንያታዊ ትውልድ መፍጠር እንደሚያስፈልግ ተጠቆመ
ሀገር አቀፍ ዜና
January 17, 2021
10
መርድ ክፍሉአዲስ አበባ፡- በሀገሪቱ የሚስተዋሉ ግጭቶችን ለዘለቄታው ለማስቆም በምክንያት የሚያምን ትውልድ መፍጠር እንደሚያስፈልግ ተጠቆመ። በአገሪቱ የሚገኙ ወጣቶች በአገር ጉዳይ ምክንያታዊ የሆነ አስተሳሰብን መፍጠር የሚስችላቸው የሙግትና የንግግር መድረክ በአዲስ አበባ ተጀመረ። የብልጽግና ወጣት ሊግ ምክትል ፕሬዚዳንትና የጽህፈት ቤት ኃላፊ ወጣት አክሊሉ ታደሰ ትናንት መድረኩን በንግግር በከፈቱበት ወቅት እንዳስታወቁት ፤ በአገሪቱ በእምነት እና በፖለቲካ ልዩነት እንዲሁም በሌሎች ጉዳዮች ወደ ግጭት እየተገባ ነው። ይህን ለመቀነስና ለማስቆም ምክንያታዊ የሆነ ወጣት መፍጠርና በንግግር የሚያምን ትውልድ መቅረጽ ያስፈልጋል ፤ ለዚህም መድረኩ ተመቻችቷል። የጋራ ባህል፣ እሴት፣ ታሪክ እንዲሁም መተሳስሮች ባይኖሩ ባለፉት ጊዜያት የእርስበርስ ግጭት ለመፍጠር የተሰራጩት የታዘቡ መረጃዎች ሀገርና ህዝብን ከሆነው በላይ ሀገርና ህዝብን ዋጋ ያስከፍሉ እንደነበር አመልክተዋል። በቀጣይም ተመሳሳይነት ችግሮች እንዳይፈጠሩ ምክንታዊ የሆነ ወጣት ለመፍጠር የንግግር መድረኮች እየተዘጋጁ መሆናቸውን ጠቁሟል። የንግግር መድረኮቹ በአገርና በብሄር መንግስት ግንባታ ዙሪያ ያጠነጠኑ መሆናቸውን የጠቀሰው ወጣት አክሊሉ፤ በሰላማዊ መንገድ የትኛውም አስተሳሰብ ያለው ወጣት በመምጣት መነጋገርና መሟገት እንደሚችል አስረድቷል። በማህበራዊ ሚዲያዎች የሚናፈሱ አገር የሚያፈርሱ ወሬዎችን ለማስቆም የንግግር መድረኮች ወሳኝ መሆናቸውን ገልጿል። የአዲስ አበባ ብልጽግና ወጣት ሊግ ፕሬዚዳንት ወጣት አዕምሮ አዱኛ በበኩሉ፤ በምክንታዊ ወጣት የንግግርና የሙግት መድረክ የአገርና የብሄረ መንግስት ምስረታ ሁኔታ መነሳቱ ወጣቱ በጉዳዮቹ ላይ ያለውን አመለካከት ለማስተካከል እንደሚረዳ አስታውቀዋል። በአገሪቱ የአገርና የብሄረ መንግስት ግንባታው ገና ያላለቀና ብዙ የሚቀረው መሆኑን የጠቀሰው ወጣት አዕምሮ፤ የአገርና የብሄረ መንግስት ግንባታውን ለማጠናቀቅ ወጣቱ ምንያታዊ ሆኖ መንቀሳቀስ እንዳለበት ጠቁሟል። ህብረ ብሄራዊ አስተሳሰብንም ለማምጣት በውይይት የሚያምን ወጣት ሊፈጠር እንደሚገባም አመልክቷል። በመድረኩ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፍልስፍና መምህር የሆኑት መምህር ዮናስ ዘውዴ ‹‹የአገርና ብሄረ መንግስት ግንባታ ምንነትና የወጣቱ ሚና›› በሚል መነሻ ጽሁፍ አቅርበዋል። በቀረበው መነሻ ጽሁፍ ላይም ውይይት ተደርጓል።
https://www.press.et/Ama/?p=39630
239
0ሀገር አቀፍ ዜና
በጎንደር የሚከበረውን የጥምቀት በዓል በደማቅ ሥነ- ሥርዓት ለማክበር የዝግጅት ስራዎች መጠናቀቃቸው ተገለጸ
ሀገር አቀፍ ዜና
January 17, 2021
22
 መሃመድ ሁሴን አዲስ አበባ:- በጎንደር ከተማ የሚከበረውን የዘንድሮው የጥምቀት በዓል በደማቅ ሥነ ሥርዓት ለማክበር የዝግጅት ስራዎች መጠናቀቃቸውን የጎንደር ከተማ አስተዳደር ባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት መምሪያ አስታወቀ። በከተማዋ በሚደረገው ክብረ በዓልም የተለያዩ አዳዲስ አሰራሮችን ተግባራዊ ለማድረግ መዘጋጀቱን መምሪያው ገልጿል። በጎንደር ከተማ አስተዳደር በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት መምሪያ ኃላፊ ኃላፊ አቶ አደባባይ ሙሉጌታ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደገለጹት፤ የዘንድሮውን የጥምቀት በዓል በታሪካዊቷ ጎንደር ከተማ ባህላዊና ሐይማኖታዊ እሴቱን በጠበቀ መልኩ በደመቀ ሁኔታ ለማክበር አስፈላጊው ዝግጅት መደረጉንና የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ሙሉ በሙሉ ተጠናቀዋል። የጥምቀት በዓል በሰላምና በደመቀ ሁኔታ እንዲከበር የተለያዩ ኮሚቴዎች ተቋቁመው እየሰሩ መሆናቸውን የገለጹት አቶ አደባባይ በጸጥታ፣ በእንግዳ አቀባበል፣ በባህልና ቅርስ ትውውቅ በቂ ዝግጅት ተደርጓል ብለዋል። ከበዓሉ ዝግጅት ስራዎች ቀዳሚው ስራ የጥምቀተ ባህሩን ቦታ የማስተካከል ጉዳይ መሆኑን የጠቀሱት አቶ አደባባይ፤ ከዚህ አንጻር የቦታው የእድሳት ስራ መቶ በመቶ ተከናውኖ ውኃ የመሙላት ስራው ዛሬ እንደሚጠናቀቅና ለበዓሉ ዝግጁ እንደሚሆን አስታውቀዋል። እንደ አቶ አደባባይ ገለጻ፣ በበአሉ እለት የሚፈጠረውን መጨናነቅ ለመቀነስና ታዳሚው በጥምቀተ ባህሩ ዙሪያ ሳይጨናነቅ መስተናገድ እንዲችል የተለያዩ አዳዲስ አሰራሮች ተግባራዊ ተደርገዋል። ከእነዚህ መካከልም ታዳሚው ከአጥር ውጪ ሆኖ የበዓሉን ክዋኔ መከታተል እንዲችል በአራት አቅጣጫዎች ሰፋፊ ማሳያ ስክሪኖች ተዘጋጅተዋል። ከሀገር ውስጥም ሆነ ከተለያዩ የዓለም ሀገራት ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተው የሚታደሙ መሆናቸውን ጠቁመው፤ ለእነዚህ እንግዶች ማስተናገጃ የሚሆንና ቅርሱን በማይጎዳ መልኩ ተነቃቅለው የሚሰበሰቡና መወገድ የሚችሉ ደህንነታቸው አስተማማኝ የሆኑ የብረት ማያዎች ተሰርተዋል። በመሆኑም የመጡት እንግዶች በቀጥታ ሐይማኖታዊ ክዋኔውን ያለስጋት መከታተል እንደሚያስችላቸውም ነው ያስረዱት። በዩኒስኮ በማይዳሰስ ቅርስነት የተመዘገበውን የጥምቀት በዓል ባህላዊ እሴቱን ጠብቆና እሴት በሚጨምር መንገድ ማክበር ያስፈልጋል ያሉት ኃላፊው፤ ይህን ታሳቢ በማድረግ ለጥምቀተ በዓሉ መዳረሻ ከጥር አንድ እስከ ዘጠኝ ድረስ የበዓል ሳምንት ተከብሯል። ለጎንደር ከተማ ሰላም ውሎ ማደርና ለመልካም አስተዳደሯ የሚሰሩና እየሰሩ የሚገኙ ታላላቅ ሰዎች፣ ወጣቶችና የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎችም የጥምቀት በዓል በሰላም ያለአንዳች ስጋት እንዲከናወን የተሰለፉ በመሆናቸው ምስጋና ይቸራቸዋል ነው ያሉት ሃላፊው። በክብረ በዓሉ ላይ ከ200 ሺህ በላይ ታዳሚዎች ይሳተፋሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ የጠቀሱት አቶ አደባባይ፤ ንግድና ባዛርን ጨምሮ በርካታ ትዕይንቶች የሚከወኑበት ሆኖ በዓለ ጥምቀቱ በደመቀ ሁኔታ መልካም ትዝታን ጥሎ እንዲያልፍ በትኩረት መሰራቱንም አክለው ተናግረዋል። በባለፈው አመት በጎንደር ከተማ በተከበረው የጥምቀት በአል በጥምቀተ ባህሩ አካባቢ ከእንጨት የተሰራ ማማ ተደርምሶ በታዳሚዎች ላይ ጉዳት ማድረሱ ይታወሳል።
https://www.press.et/Ama/?p=39628
322
0ሀገር አቀፍ ዜና
የሃገር ፍቅር ያጀገነው ወታደሩ ኦሊምፒያን
ስፖርት
December 20, 2020
23
ብርሃን ፈይሳየኢትዮጵያ አትሌቲክስንና ድልን ያወዳጃቸው ጀግናው አትሌት ሻምበል አበበ ቢቂላ ይሁን እንጂ፤ የድሉን ቀጣይነት ያወጀው ሌላኛው ወርቃማ አትሌት ሻምበል ማሞ ወልዴ ነው። ማሞ የአበበን ፈለግ ተከትሎ ሃገሩ የለመደችው እንዳይጎድልባት በላቡ ክብሯን አድምቋል፤ ኢትዮጵያዊያን በቀላሉ የማይደፈሩ ጀግኖች መሆናቸውንም ለዓለም አረጋግጧል፡፡ የአሸናፊነት ወኔው ሳይሸረሸር ውጣ ውረዶችን ተሻግሮ የሃገሩን ክብር እንዳስጠበቀ ያለፈ፤ ገድሉም ከኢትዮጵያ የጀግኖች መዛግብት በወርቅ ቀለም የሰፈረ ነው፡፡ ይሁን እንጂ እስካሁንም የሚገባውን ያህል ክብርና ሙገሳ አላገኘምና አዲስ ዘመን በዛሬው የስፖርት ማህደር አምዱ ሊያስታውሰው ወደደ፡፡ ከሰነድ የተገኙ መረጃዎችና ልጁ ሳሙኤል ማሞ ወልዴ ከጋዜጣው ጋር በነበረው ቃለ ምልልስ ስለ ጀግናው አባቱ ያነሳቸው ሃሳቦች ተዋህደው እንደሚከተለው ቀርቧል፡፡ የማሞ ትውልድ በ1924 ዓ.ም ቀድሞ ሸዋ ክፍለ ሃገር ተብሎ በሚጠራው አድአ ወረዳ ድሬድሌ በሚባል ቀበሌ መሆኑን የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ‹‹ኢትዮጵያ በኦሊምፒክ›› በሚል ርዕስ ባሳተመው መጽሄት የሰፈረው የህይወት ታሪኩ ያስነብባል፡፡ እድገቱ ከብት በመጠበቅ፣ እድሜው ሲገፋም እርሻ በማረስ፣ ቆቅ፣ ጅግራ እና ሚዳቋ አድኖ በመሸጥም ነበር፡፡ በአንድ ዕለት ግን ታዳጊው ማሞ እንደ አጎቱ የሚያያቸው ዘመዱ ሊጠይቋቸው መምጣታቸውን ተከትሎ የህይወቱ አቅጣጫ ተለወጠ፡፡ የክቡር ዘበኛ አባል የሆኑት ዘመዱ በለበሱት የደንብ ልብስ በመማረኩ ወደ አዲስ አበባ ወስደውት ውትድርና እንዲያስቀጥሩት ጥያቄ ያቀርብላቸዋል፡፡ እርሳቸው ለጥያቄው የሽንገላ መልስ ቢሰጡትም ልቡ የሸፈተው ማሞ ግን ቀን ጠብቆ በእግሩ ወደማያውቃት አዲስ አበባ ነጎደ፡፡ ያሰበው ተሳክቶም በ1943 ዓ.ም የክብር ዘበኛ አባል በመሆን በልጅነት ልቡ የተማረከለትን የደንብ ልብስ ለመልበስ በቃ፡፡ ለሁለት ዓመታት በኮሪያ የነበረውን ተልዕኮ ፈጽሞ ከተመለሰ በኋላም በአየር ኃይል ግቢ ውስጥ በሚዘጋጀው የሩጫ ውድድር ላይ በማራቶን ተሳትፎ፤ ሻምበል አበበ ቢቂላን ተከትሎ በሁለተኛነት ውድድሩን አጠናቀቀ፡፡ ውጤቱ ታላቅ ተስፋ በማሳደሩም የአትሌቲክስ ስልጠና እንዲከታተልና በሃገር ውስጥ ውድድሮችም እንዲካፈል መንገዶች ተከፈቱለት። በየወቅቱ የሚያስመዘግባቸው ውጤቶችም ለሜልቦርን ኦሊምፒክ ተሳታፊነት አሳጨው፡፡ ሻምበል ማሞ ወልዴ ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ በተሳተፈችበት የሜልቦርን ኦሊምፒክ (እአአ 1956) ተሳታፊ ከነበሩት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አባላት መካከል አንዱ እንዲሆን አስቻለው። የተወዳደረውም በሶስት ርቀቶች ማለትም በ4 በ400ሜትር፣ 800 ሜትር እንዲሁም 1 ሺ 500 ሜትር ነበር፤ ሆኖም እንደሌሎች ተሳታፊዎች ሁሉ ውጤት ሊያስመዘግብ አልቻለም፡፡ የዚያን ጊዜ የአባቱን ሁኔታና ወቅቱን የሚያስታውሰው ሳሙኤል ማሞ ወልዴ፤ ለውጤት እጦት አንዱ ምክንያት የነበረው ወደ አውስትራሊያ ይደረግ የነበረው ጉዞ ስምንት ቀናትን ለመሄድና ለመመለስ ሌላ ስምንት ቀናትን የሚጠይቅ መሆኑን ነው። በጉዞ ላይ የነበረው ድካም ለውጤት ሊያበቃ የሚችል አልነበረምና፡፡ ከአራት ዓመታት በኋላም እስካሁንም በህያውነት የዘለቀ ታሪክ የተጻፈባት ተረኛዋ የኦሊምፒክ አዘጋጅ ሮም (እአአ 1960) መሰናዶዋን አጠናቀቀች፡፡ ኢትዮጵያ በሁለተኛው የኦሊምፒክ ተሳትፎዋ በማራቶን የመጀመሪያውን ሜዳሊያ ከማስመዝገቧም በላይ ውድድሩ ከተካሄደባት ሃገርና ከአበበ ቢቂላ የባዶ እግር ሩጫ ጋር ተያይዞ የዓለም መገናኛ ብዙሃን መነጋገሪያና የጋዜጦች አርዕስትም ሆና ነበር፡፡ የዚህ ታሪክ አካል ለመሆን በዝግጅት ላይ የቆየውና ሃገሩን ዳግም በሌላ ድል ሊያኮራ የተዘጋጀው የክቡር ዘበኛው ወታደር ማሞ ግን ተሳታፊ የመሆን እድሉን ሊያገኝ አልቻለም። ለሃገሩ ሜዳሊያ ለማስመዝገብ የነበረው ህልም እንዳይሰምር ምክንያት የሆነው ደግሞ በሰላም አስከባሪነት ወደ ኮንጎ ይዘምታል በሚል ከቡድኑ ጋር ባለመጓዙ እንደነበር የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ሰሞኑን ‹‹የባዶ እግር ትሩፋቶች›› በሚል ርዕስ ባወጣው መጽሄቱ ያስነብባል፡፡ በቀጣዩ የቶኪዮ ኦሊምፒክ (እአአ 1964) ማሞ የቡድኑ አባል በመሆን በ10ሺ ሜትር ውድድሩን አድርጎ ነበር፡፡ ይሁን እንጂ ሩጫውን ሲመራ ቆይቶ ኩርባ ላይ ተገፍቶ ወድቆ ባቱ በመቁሰሉ ወርቃማው ድል ዳግም ሊያመልጠው ችሏል፡፡ የኦሊምፒክ ወርቅና ሃገሩን በክብር የማስጠራት መሻት እንዲሁም የኦሊምፒክ መንደር ናፍቆቱ ያልወጣለት ወታደሩ አትሌት ሌላ አራት ዓመት ጠብቆ የስፖርት አውድ ፍልሚያውን ከማድረግ ወደኋላ አላለም፡፡ ነፍሱ በማይዳፈን የሃገር ፍቅር ስሜት ነዷልና፤ የሃገሩን ዳር ድንበር ከመጠበቅና ሉዓላዊነቷን ከማስከበርም አልፎ ሃገሩን በክብር ማስጠራት ፍላጎቱ ነበር፡፡ ለዚህም ዝግጅቱን አጠናክሮ በመቀጠል በሜክሲኮ ኦሊምፒክ (እአአ 1968) ዳግም በሃገሩ መለያ ቀረበ፡፡ አስደናቂው ጉዳይ ደግሞ ተሳትፎውን በአምስት ቀናት ልዩነት በመም እና በጎዳና ላይ ርቀቶች ማድረጉ ነበር፡፡ በወቅቱ በአትሌቲክስ ስፖርት በተለይ በማራቶን ስሙ በዓለም ዙሪያ ከናኘው የሃገሩ ልጅ ሻምበል አበበ ቢቂላ ጋርም በአንድነት ተሰለፉ፡፡ ውድድሩም እንደተለመደው በአበበ አሸናፊነት እንደሚያልቅ ቅድመ ግምት አግኝቶ መካሄድ ቢጀምርም እንደተጠበቀው ሊቆይ የቻለው እስከ ርቀቱ አጋማሽ ነበር፡፡ ምክንያቱ ደግሞ እጅግ ተጠባቂውና የአትሌቲክስ ወዳጆችን ቀልብ የገዛው አበበ በጉዳት ምንያት 42 ኪሎ ሜትሩን መሸፈን ባለመቻሉ አቋርጦ መውጣቱ ስለተሰማ ነው፡፡ ይህ ለሌላው ዓለም ህዝብ አስደንጋጭ፤ ለተፎካካሪዎቹ ደግሞ ምናልባትም መልካም ዜና ሊሆን ይችላል፡፡ ጀግኖችን ማፍራት ለማይነጥፍባት ምስራቅ አፍሪካዊቷ ሃገር ኢትዮጵያ ግን ስጋት አልነበረም፡፡ ጥንትም ጀግናን በጀግና የመተካት ልማድ አላትና የአንደኛው ልጇ ጉዳት በሌላኛው ድል የሚተካ መሆኑን በማመንና በልበ ሙሉነት እንደጸናች ነበር፡፡ የተጠበቀው አልቀረም፤ ሌላኛው አትሌት ማሞ ወልዴ የሩጫውን የመጨረሻ መስመር ቀድሞ ረገጠ፡፡ ታሪክን ከስሩ ማወቅ መልካም ነውና በጊዜው የሆነውን የአባቱን ገድል ልጅ ሳሙኤል ወልዴ እንዲህ ይተርካል። ‹‹ማሞ በሩጫው ላይ ሳለ ለየት ያለ እንቅስቃሴ ይመለከታል፤ ይኸውም ከአበበ ውጪ የአሸናፊነት ግምት የተሰጣቸው የሌሎች ሃገራት ሯጮች ሲደሰቱ መመልከቱ አንዳች ጥርጣሬ አሳደረበት። የተፈጠረውን በውል ባለመረዳቱም ሩጫውን ይቀጥላል፤ በዚህ መሃል ግን ሰለሞን ተሰማ የተባለው እውቅ ጋዜጠኛ በጭነት መኪና ሆኖ ስሙን ይጠራዋል፡፡ እንዲህም ይለዋል ‹‹ማሞ ዛሬ ለሃገርህ ታሪክ ስራ፤ አበበ አቋርጦ ወጥቷል››፤ ይሄኔ ታዲያ ኢትዮጵያዊው የአልሸነፍ ባይነት ወኔው ተነሳስቶ በእልህ ለአሸናፊነት በቅቷል፡፡›› ሌላኛው ድል ሲደገምም በክብር የተውለበለበው ባንዲራ አልወረደም ነበር፡፡ ለሰሚ አስደናቂ የሆነው በአንድ ኦሊምፒክ ሁለት የረጃጅም ርቀት ድሎችን ማጣጣም የወሰደው የቀናት ልዩነት ብቻ ነበር፡፡ የስፖርቱ ዓለም አዲስ ክስተት የ10ሺ ሜትር ውድድር በተደረገበት ዕለት የሆነም ነበር፡፡ በዚህ ርቀት ከቀረቡት ተወዳዳሪዎች መካከል አንዱ ኢትዮጵያዊው የማራቶን ባለ ድል ሻምበል ማሞ ወልዴ ነበር፤ የውድድሩ ማስጀመሪያ ድምጽ እንደተሰማ አትሌቶቹ ወደፊት መትመም ጀመሩ፡፡ ጥቂት ሜትሮችን እንደሮጡም ወደፊት የሚገሰግሰው ማሞ ለጥቂት ተጠልፎ ከመውደቅ ተርፎ ሩጫውን ቀጠለ፤ አብዛኛውን ርቀት ከተሸፈነ በኋላ በመሪነት ሌላውን ሲያስከትልም ነበር፡፡ ይሁን እንጂ ሩጫው ሊጠናቀቅ ጥቂት ሜትሮች ብቻ ሲቀሩት ኬንያዊው አትሌት ናፍታሊ ቴሙ ከየት መጣ ሳይባል እጅግ ተቀራራቢ በሆነ ሰዓት ቀድሞት ገባ፡፡ ይህም ማሞ በሁለተኛው ርቀት የብር ሜዳሊያ ሲያስገኝለት በሁለት የኦሊምፒክ ተሳትፎዎች በተለያዩ ርቀቶች ውጤት ማስመዝገቡ በዓለም ብቸኛው አትሌት ስላደረገው አድናቆትን አትርፎለታል፡፡ በኦሊምፒክ ውጤታማ ለመሆን ከፍተኛ ጥረት ማድረግን ይጠይቃል፡፡ በርካታ ሃገራትም ለተወዳዳሪነት ቡድናቸውን በተለያዩ ስፖርቶች በመድረኩ ያሳትፋሉ፤ ይሁን እንጂ ውጤት ማስመዝገብ ጉም እንደመዝገን ሆኖባቸዋል። በአንጻሩ ማሞ ብቻውን በአንድ ኦሊምፒክ ሁለት ሜዳሊያዎችን ቢያጠልቅም፤ በእነዚህ ድሎች ብቻ ሊረካ አልቻለም፡፡ እናም ዳግም ለሌላ ኦሊምፒክ ወደ ዝግጅት ገባ፤ እአአ በ1972 ሙኒክ ኦሊምፒክ ላይም ታየ፡፡ ውጤታማና ዝነኛ በመሆኑ የኢትዮጵያ ልኡክ በኦሊምፒኩ መክፈቻ በተመልካች ፊት ሲያልፍ የሃገሩን ባንዲራ በክብር ይዞ ታይቷል። በወቅቱ እድሜው አርባ ዓመታትን ቢሻገርም ጎልማሳነት ሳያግደው በማራቶን የነሃስ ሜዳሊያ ባለቤት በመሆን ጀግንነቱን በድጋሚ አረጋግጧል፡፡ ማሞ ከኦሊምፒክ ድሎቹ ባሻገር ከ500 በላይ በሚሆኑ በተለያዩ አህጉርና ዓለም አቀፍ ውድድሮች ተሳትፎው ካስመዘገባቸው በርካታ ሜዳሊያዎች ውጪ፤ ዋንጫዎችን፣ ኒሻኖችን፣ ሰዓቶችን፣ ሽጉጦችንና ወርቆችን ተሸልሟል፡፡ በስፔን በተካሄደ የሃገር አቋራጭ ውድድር ላይ በተከታታይ አሸናፊ በመሆኑም ሩጫው በሚካሄድበት ከተማ ሃውልት ቆሞለታል፡፡ ከእነዚህ ሽልማቶች መካከል ከፊሎቹ አሁንም ድረስ በልጁ ሳሙኤል ማሞ ወልዴ እጅ ይገኛሉ፡፡ የተቀሩት ግን ማሞ በህይወት ሳለ በአካባቢው ለሚካሄዱ የወረዳና ከፍተኛ ውድድሮች የራሱን ሽልማቶች አውጥቶ በመስጠቱ ምክንያት የሌሉ መሆኑን ያስታውሳል፡፡ ሳሙኤል አባቱን ሲገልጽ ‹‹ሃገሩን እጅግ የሚወድና መስዋዕትነትንም የከፈለ፤ ነገር ግን ውለታው የተዘነጋ እንዲያውም ጥቃቶችንም ያስተናገደ›› ነበር ይላል፡፡ ማሞ በ1983 ዓም ወደ ስልጣን የመጣውን መንግስት ተከትሎ በሁለተኛው ወር ‹‹የቀይ ሽብር ተጠርጣሪ›› በሚል ነበር ለእስር የተዳረገው፡፡ ሲታሰርና ሲፈታ ቢቆይም ከ1985 ዓ.ም ጀምሮ ግን እስሩ ጸንቶ በ1994 ዓ.ም ነበር የተፈታው፡፡ ሆኖም ከዚያ በኋላ ከአራት ወራት በላይ እድሜው ሊገፋ ባለመቻሉ በግንቦት ወር ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ፡፡ በ1988 ዓ.ም ከቦክሰኛው መሃመድ አሊ ጋር የኦሊምፒክን ችቦ እንዲለኩስ በመመረጡ ከዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ልኡካን ከወቅቱ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ዘንድ ቀርበው እንዲፈታ ቢጠይቁም ‹‹ማሞ ወልዴ ጀግና ነው፤ ሆኖም ወንጀል እንዲሰራ አንፈቅድለትም›› የሚል ምላሽ ተሰጥቷቸው እንደተመለሱ ሳሙኤል ያስታውሳል፡፡ የጀግናውን አትሌት ህልፈት ተከትሎም የስፖርቱ ወዳጅና ባለውለታ የሆኑት የቀስተደመና ስፖንጅ ፋብሪካ ባለቤት አቶ አቤሴሎም ይህደጎ ሃውልት አሰርተውለት ነበር፡፡ ይሁን እንጂ ከ13 ዓመታት በፊት ማንነታቸው ባልታወቀ ግለሰቦች አጽማቸው ጎን ለጎን ያረፈው ጀግና አትሌቶች ሻምበል አበበ ቢቂላ እና ማሞ ወልዴ ሃውልት ሊፈርስ ችሏል፡፡ ይህንን ተከትሎም ሳሙኤል የተለያዩ አካላትን አስተባብሮ የማሞ ሃውልት ዳግም እንዲሰራ ያላደረገው ጥረት እንዳልነበረ ይገልጻል። ነገር ግን የአቅም ውስንነት ምላሽ ከማጣቱ ጋር ተዳምሮ ለዓመታት ጀግናው አትሌት ከመቃብር በላይ ለዋለው ስሙ ማስታወሻ የሚሆነውን ሃውልቱን አጥቶ ቆይቷል፡፡ ከረጅም ጊዜያት በኋላም ሌላኛዋ ጀግና አትሌትና የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ደራርቱ ቱሉ ከሳምንት በፊት በራሷ ተነሳሽነት የማሞንና የአበበን ሐውልት እውን አድርጋዋለች፡፡ ለሃገሩ በከፈለው ውለታም ዛሬ በህይወት ኖሮ ባይቀበልም አንድ ሚሊየን ብር ለቤተሰቦቹ ተበርክቷል፡፡ በዚህ እጅግ የተደሰተው ሳሙኤልም ‹‹ትክክለኛው ሰው በትክክለኛ ቦታው ሲገኝ ምን ሊሰራ እንደሚችል ያመላከተ›› ሲል ደስታውን ያንጸባርቃል፡፡ ይህ የአባቱ ታሪክ በትውልዱ ሰርጾ እንዲኖርና በጽናት ያሳለፋቸው ውጣ ውረዶቹ መነሳሳትን እንዲፈጥርም በመጽሃፍ መልክ ለማሳተም ሃሳብ ቢኖረውም በአቅም ውስንነት ሊያሳካው አልቻለም። ስፖንሰር ቢያገኝ ግን የማሳተም ሃሳብ ያለው መሆኑን ይጠቁማል፡፡ ማሞ ጡረታውን ተከልክሎ እስር ቤት ከገባበት ጊዜ ጀምሮ ቤተሰቦቹ ከመበተን እንዲተርፉ ያደረጉትና አሁንም ለሳሙኤል ስራ ለልጁ ደግሞ የትምህርት እድል የሰጡትን የቀስተደመና ስፖንጅ ፋብሪካ ባለቤት አቤሴሎም ይህደጉ እንዲሁም ልጃቸውን ያመሰግናል፡፡አዲስ ዘመን ታህሳስ 11/2013
https://www.press.et/Ama/?p=37748
1,243
2ስፖርት
አካል ጉዳተኞችን ተደራሽ ያላደረገው ስፖርት
ስፖርት
December 21, 2020
10
 ስፖርት እድሜ ጾታና የሰውነት አቋም የማይለይ አካላዊ እንቅስቃሴና የሰው ልጆች መብት ምት ጭምር ነው፡፡ ይህም ማለት አካል ጉዳተኞችንም አካቶ የአካላዊና አእምሯዊ ጤናን ለመጠበቅ የሚያስችል ሚዛን ነው፡፡ ይሁን እንጂ በብዙ ሃገራት አካል ጉዳተኞችን በስፖርት ማሳተፍ አልተለመደም፡፡ በእርግጥ በዓለም አቀፍ ደረጃ አካል ጉደተኞችን በስፖርታዊ እንቅስቃሴና ውድድር ማካፈል እየተለመደ የመጣው ከ20ኛው ክፍለ ዘመን ወዲህ ነው፡፡ ነገር ግን ይህ እንቅስቃሴ እንደሚጠበቀው ጎልቶ ባለመታየቱ አካል ጉዳተኞችን ለማሰብ ሁሌም በየዓመቱ ህዳር ወር ላይ ይከበራል፡፡ አካል ጉዳተኞች በሁሉም እንቅስቃሴዎች ለመሳተፍ የሚገድባቸው ነገር አለመኖሩን ለማስገንዘብም ከሚከናወኑ ነገሮች መካከል አንዱ ስፖርታዊ እንቅስቃሴ ነው፡፡ ስፖርት ህይወትን በመልካም መንገድ ለመምራት የሚያስችል፣ ጡንቻዎችን የሚያጠነክር፣ ከጉዳት የሚጠበቅና ፈጥኖ ለማገገም የሚረዳ እንዲሁም ድብርትና ተያያዥ የሆኑ ስነ-ልቦናዊ ችግሮችን የሚቀርፍ መሆኑ ይታወቃል፡፡ ይህም በመሆኑ ዓለም አቀፉ የኦሊምፒክ ኮሚቴ በየአራት ዓመቱ ጉዳት አልባ ስፖርተኞችን ካወዳደረ በኋላ አካል ጉዳተኞች የሚካፈሉበትን ‹‹ፓራሊምፒክ›› ያዘጋጃል፡፡ በመላው ዓለምም እንዲህ ዓይነት ውድድሮችና ቻምፒዮናዎች እየታዩ መጥተዋል፡፡ በኢትዮጵያም ይኸው እንቅስቃሴ አካል ጉዳተኞችን በስፋት ተደራሽ ባያደርግም አዲስ አበባን በመሳሰሉ ከተሞችና ሌሎች ክልሎች ላይ ውድድሮች ይካሄዳሉ፡፡ ነገር ግን ስፖርታዊ ውድድርና አካላዊ እንቅስቃሴ ለማድረግ የተዘጋጁ ምቹ ሁኔታዎች በምን ደረጃ ላይ ይገኛሉ የሚለውን መፈተሽ አስፈላጊ ነው፡፡አቶ ንጉሴ ግደይ የአዲስ አበባ አካል ጉዳተኞች ማህበር ፕሬዚዳንት ሲሆኑ፤ በየዓመቱ የአካል ጉዳተኞች ቀንን በማስመልከት ስፖርታዊ ውድድር እየተካሄደ ዘንድሮ አስረኛ ላይ መድረሱን ይጠቁማል። የዚህ መርሃ ግብር መካሄድ አንዱ ምክንያት በከተማዋ የሚኖሩ አካል ጉዳተኞች አካል ጉዳት ከሌለባቸው እኩል በማንኛውም የማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች መሳተፍ እንደሚችሉ ግንዛቤ መፍጠርም ነው። ከእነዚህ ጉዳዮች መካከል አንዱ ስፖርት ሲሆን በዋናነት ለጤናና ለአካል ጥንካሬ ፋይዳው የጎላ በመሆኑ አካል ጉዳተኛ ስፖርተኞችን ለማፍራትም የውድድሩ መካሄድ ጠቀሜታ አለው። አካል ጉዳተኞች ከአካላቸው አንዱ ቢጎድልም ዘወትር አካላዊ እንቅስቃሴ ቢያደርጉ ለቀሪው አካላቸው ብርታት ይሆናቸዋል። አሁን በዓለም ደረጃ እነሱን ያማከሉ የስፖርት አይነቶችም በርካታ ናቸው። እነዚህ ስፖርቶች ላይ ቢሳተፉ ለአካል ጥንካሬ ስነ-ልቦናቸው እንዲገነባ እንዲሁም በራስ የመተማመን ብቃታቸው እያደገ እንዲሄድ ትልቅ አስተዋጽኦ ይኖረዋል። ስለዚህ አካል ጉዳተኞች በሕመም እንዳይጠቁ እንዲሁም ጉዳታቸው እንዳይባባስና ባለበት እንዲቆም እንደሚረዳቸውም ፕሬዚዳንቱ ያስረዳሉ። ከዚህም በተጨማሪ ጥሩ አካላዊ ቁመና እንዲኖራቸውም ይረዳል። በእለት ከእለት እንቅስቃሴያቸውና ከሰዎች ጋር በሚኖራቸው ግንኙነትም ደስተኛ እንዲሆኑ ይረዳቸዋል። አዲስ አበባ ከመቆርቆሯ አንስቶ በፕላንም ሆነ በተግባራዊ ስራው አካል ጉዳተኞችን መሰረት አለማድረጋቸውንም ፕሬዚዳንቱ ያስረዳሉ፡፡ ይህም አካል ጉዳተኞችን ከፍተኛ ዋጋ እየስከፈላቸው ሲሆን፤ በስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎችም ይህንን ማካተት የተጀመረው በቅርቡ ነው፡፡ ከመግቢያ መውጫዎች ጀምሮ ውስጣዊ ይዞታቸውና ቁሳቁሶቻቸውም ጭምር አካል ጉዳተኞችን ከግምት ያስገቡ አልነበሩም፡፡ በተመሳሳይ ወጣት ማዕከላትም ወጣት አካል ጉዳተኞችን ታሳቢ ያደረጉ አይደሉም፡፡ በዚህም ምክንያት እንቅስቃሴያቸውን አስቸጋሪ አድርጎታል፡፡ በመሆኑም ማህበሩ የተለያዩ ግንባታዎች አካል ጉዳተኞችን ታሳቢ አድርገው እንዲካሄዱ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር እየተነጋገረ መሆኑን ፕሬዚዳንቱ ይጠቁማሉ፡፡ በከተማዋ በርካታ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች እንደመኖራቸው በጥናት ተደግፎ ተሻሽለው ሁሉንም ማህበረሰብ ተጠቃሚ የሚሆኑበትን እንዲሁም ተደራሽ የሚሆኑበትን መንገድ በማመቻቸት ላይ ጥረት እየተደረገ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡አዲስ ዘመን ታኅሣሥ 12/2013
https://www.press.et/Ama/?p=37833
399
2ስፖርት
በሲሚንቶ አቅርቦት ሰንሰለቱ ላይ አሁንም ችግሮች እንደሚታዩ ሚኒስቴሩ አስታወቀ
ሀገር አቀፍ ዜና
January 17, 2021
42
አስናቀ ፀጋዬ አዲስ አበባ፡- በሲሚንቶ አቅርቦት ሰንሰለቱ ላይ አሁንም ችግሮች እንደሚታዩ የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር አስታወቀ። በሀገሪቱ የሚታየውን የሲሚንቶ እጥረት በዘላቂነት ለመቅረፍ የተለያዩ ስራዎችን እየሰራ እንደሚገኝም አመለከተ። በንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር የብረታ ብረትና ኬሚካል ሚኒስትር ዴኤታ አማካሪ አቶ ዱጋሳ ዶንሳ ለአዲስ ዘመን እንደገለፁት ፣ሚኒስቴሩ ከስድስት ወር በፊት በምርትና በአቅርቦት በኩል የተፈጠረውን የሲሚንቶ እጥረት መንስኤ ለማጥናት በሀገር አቀፍ ደረጃ ኮሚቴ አቋቁሞ ሲሰራ ቆይቷል። በዚህም በሀገሪቱ ያሉ ፋብሪካዎች ለረጅም ጊዜ የሚቆሙ፣ ገሚሶቹም ያረጁና መለዋወጫ የሚፈልጉ፣ የገበያ ፍላጎታቸውም በሶስት ኢንዱስትሪዎች ላይ መሰረት ያደረጉ መሆናቸውንና አብዛኛዎቹ ግንባታዎችም በተመሳሳይ ወቅት መከናወናቸው ችግሩ እንዲጎላ ማድረጉን ለማረጋገጥ መቻሉን ገልጸዋል። የሲሚንቶ ምርት ፍላጎትና አቅርቦት ልዩነት እንደነበር መረጋገጡን አመልክተዋል። የሲሚንቶ ምርት አቅርቦትና ፍላጎት በኩል ያለውን ልዩነት ለማጥበብ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የተወሰነ ሲሚንቶ ከውጭ ሀገር እንዲገባ መፍቀዱን ጠቁመው ፣ ከዚህ በፊት ተይዞ የነበረው የሲሚንቶ ኢንቨስትመንትም እንዲለቀቅ መደረጉንም አስታውቀዋል። በአማራ ብሄራዊ ክልል ደጀን አካባቢ የሚገኘው አባይ የሲሚንቶ ፋብሪካ ግንባታ እንዲፋጠንም የ20 ሚሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሬ ተፈቅዶለት ግንባታው እየተከናወነ እንደሚገኝም ገልፀዋል። ቀደም ሲል የነበረውን የሲሚንቶ የማምረት አቅም ለመጨመርም የመለዋወጫ እቃዎች ከውጭ ሀገር እንዲገቡ 85 ሚሊዮን ብር መመደቡንም ጠቁመዋል። የክረምቱን ወቅት ተከትሎ በሲሚንቶ ፋብሪካዎች ላይ ያጋጠሙ የተፈጥሮ አደጋዎችና በዘርፉ የሰለጠኑ ባለሙያዎች እጥረቶች እንዳሉ ሆነው እነዚህን ስራዎች በመስራት ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከሲሚንቶ አምራቾች ጋር የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርሞ በበጀት ዓመቱ የሀገሪቱን አጠቃላይ ሲሚንቶ የማምረት አቅም ለማሳደግ ከያዘው 85 በመቶ እቅድ ውስጥ 79 ያህሉን ማሳካት እንደቻለም ገልጸዋል። በነሃሴ ወር መጨረሻ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የሲሚንቶ የመሸጫ መቁረጫ ዋጋ መመሪያ አውጥቶ እንደነበርም አማካሪው አስታውሰው፤ ዋጋው እንደገበያው መሆን እንዳለበት ታምኖ መመሪያው እንዲነሳ መደረጉንም ጠቁመዋል። የዋጋ መመሪያው ከተነሳ በኋላም የሲሚንቶ ዋጋው እንዳልወረደ ነገር ግን መመሪያው እንዳያሻቅብ ማድረጉን የተደረጉ ጥናቶች እንደሚያሳዩ አመልክተዋል። አምና የተመረተውን 8 ነጥብ 5 ሜትሪክ ቶን ሲሚንቶ ወደ 11 ሜትሪክ ቶን በማሳደግ በአቅርቦቱና በፍላጎቱ መካከል ያለውን ክፍተት ለመማጥብ እየተሰራ እንደሚገኝም አማካሪው አስታውቀው፣ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ባስቀመጠው እቅድ መሰረት ባደረገው ጥረት ከዚህ ቀደም በሃይል መቆራረጥ ምክንያት ሲቆም የነበረውን የሲሚንቶ የማምርት አቅም ችግር ሙሉ በሙሉ መፍታቱን አመልክተዋል። ፋብሪካዎች ከውጭ የሚያስገቧቸውን የድንጋይ ከሰል የመሰሉ የኢነርጂ ምንጮችን በሀገር ውስጥ እንዲጠቀሙ ከመአድን ነዳጅና የተፈጥሮ ጋዝ ሚኒስቴር ጋር በመሆን ጥረት መደረጉንም አማካሪው ጠቁመዋል። በዚህም የመሰቦ ሲሚንቶ ፋብሪካን ሳይጨምር በቀን በአማካይ 240 ሺ ኩንታል ማምረት እንደተቻለም ጠቁመዋል። ሆኖም ምርቱ ከወጣ በኋላ የአቅርቦት ሰንሰለቱ ላይ አሁንም ችግሮች እንደሚታዩ አስታውቀዋል
https://www.press.et/Ama/?p=39629
341
0ሀገር አቀፍ ዜና
“የኢትዮ-ሱዳን የድንበር ጉዳይ በሁለትዮሽ ስምምነቶች እና በጋራ የድንበር መድረኮች አማካኝነት መፈታት አለበት” – ይበልጣል አዕምሮ በሱዳን የኢ.ፌ.ዴ.ሪ አምባሳደር
ሀገር አቀፍ ዜና
January 16, 2021
8
በጋዜጣው ሪፖርተር አዲስ አበባ፦ በኢትዮጵያ እና ሱዳን መካከል ያለው የድንበር ጉዳይ ባሉ የሁለትዮሽ ስምምነቶች እና የጋራ የድንበር መድረኮች አማካኝነት በሰላማዊ መንገድ መፈታት እንዳለበት በሱዳን የኢ.ፌ.ዴ.ሪ አምባሳደር ይበልጣል አዕምሮ አሳሰቡ። ከሱዳን የኢትዮጵያ ኤምባሲ ያገኘነው መረጃ እንደሚያመለክተው የሱዳን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እና የብሔራዊ ድንበር ኮሚሽን ተቀማጭነታቸው በሱዳን ለሆኑ ዲፕሎማቲክ ሚሽኖች፣ ቆንስላዎች እና የዓለምአቀፍ ድርጅቶች ተወካዮች ገለጻ አድርጓል። በዚህም ወቅት፣ አምባሳደር ይበልጣል ከዳግልሽ ተራራ በስተሰሜን ከሰፈራ እና ከእርሻ መሬት ጋር  በተያያዘ የተፈጠሩ ችግሮችን ለመፍታት ሁለቱን ሀገራት የሚያስማማ የመፍትሔ ሃሳብ እንዲመጣ የሚደነግገው እና በሁለቱ ሀገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች እ.ኤ.አ. ሐምሌ 18 ቀን 1972 የተደረገው የማስታወሻ ልውውጥ ከፍ ያለ ፋይዳ እንዳለው አስታውቀዋል።በ1972ቱ የማስታወሻ ልውውጥ በተቀመጠው መሰረት የጉዊን መስመርን ዳግም ማካለል ከመጀመሩ በፊት ከዳግልሽ ተራራ በስተሰሜን ከእርሻ መሬት እና ሰፈራ ጋር በተያያዘ የሚነሱ ችግሮችን ለመፍታት የጋራ ልዩ ኮሚቴው ሁለቱን ሀገራት የሚያስማማ የመፍትሔ ሃሳብ ያካተተ ሪፖርት ለጋራ የሚኒስትሮች ኮሚሽን ማቅረብ እንደሚኖርበት አመልክተዋል።የጋራ ልዩ ኮሚቴው ሁለቱን ሀገሮች የሚያስማማ የመፍትሔ ሃሳብ ለማቅረብ ስምንት ዙር ስብሰባዎችን ቢያካሂድም ኃላፊነቱን ገና እንዳላጠናቀቀ ጠቁመዋል። የኢትዮጵያ-ሱዳን ድንበር የጋራ ልዩ ኮሚቴ ስራ ባልተጠናቀቀበት ሁኔታ እና የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት በጥቅምት ወር መጨረሻ ህግ ለማስከበር ወደ ትግራይ ክልል ያደረገውን ስምሪት እንደ መልካም አጋጣሚ መጠቀሙን አምባሳደር ይበልጣል አመልክተዋል። በዚህም የሱዳን ሰራዊት ወደ ኢትዮጵያ ግዛት ዘልቆ በመግባት ንብረት ከመዝረፉ፣ ወታደራዊ እና የእርሻ ካምፖችን ከማቃጠሉ ባሻገር በኢትዮጵያውያን ላይ እስራት፣ ጥቃት እና ግድያ መፈጸሙ እንዲሁም በሺ የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያንን ማፈናቀሉን አስታውቀዋል ፤ ይህ የ1972 የማስታወሻ ልውውጥን በግልጽ የጣሰ ተግባር መሆኑን ገልጸዋል።በሁለቱ እህትማማች ሀገራት ጸንቶ ከቆየው አጋርነት እና ትብብር መንፈስ በተቃረነ መልኩ የሱዳን ሰራዊት አጋጣሚውን በመጠቀም  የኢትዮጵያ ብሔራዊ መከላከያ   ሰራዊት ለቋቸው የወጣ ካምፖችን መቆጣጠሩን ጠቁመዋል።ሱዳን በችግር ውስጥ በነበረችበት ጊዜ ሁሉ ኢትዮጵያ ከሱዳን ህዝብ ጎን መቆሟን ያስታወሱት አምባሳደር ይበልጣል፤ ኢትዮጵያ በውስጥ ጉዳይዋ በተጠመደችበት ወቅት ከሱዳን ሰራዊት የደረሰባት ጥቃት የሚገባት እንዳልሆነ አመልክተዋል።የማስተካከያ እርምጃ በፍጥነት ካልተወሰደ፣ ታይቶ የማይታወቀው የሱዳን ሰራዊት ተግባር የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት ብሎም የጋራ ድንበሩን ዳግም የማካለሉን ስራ የሚያወሳስብ እና ለሁለቱ ሀገራት ህዝቦች እንዲሁም ለቀጠናው ከፍ ያለ አሉታዊ ተጽዕኖ እንደሚኖረው አስታውቀዋል።የኢትዮጵያ እና ሱዳን የድንበር ልዩነቱን ሁለቱ ሀገራት በገቧቸው ስምምነቶች እና ባሉ የጋራ የድንበር መድረኮች መሰረት በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ኢትዮጵያ ቁርጠኛ መሆኗንም አረጋግጠዋል። ለችግሩ ዘላቂ እልባት ለመስጠት ፣ የሱዳን ሰራዊት ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የፈጸመውን ወረራ በመቀልበስ በ1972ቱ የማስታወሻ ልውውጥ በተቀመጠው መሰረት ወደ ቅድመ-ኖቬምበር 2020 (እ.ኤ.አ.) መመለስ እንዳለበት አስታውቀዋል።ከዚህም በተጨማሪ ወደ ድንበር ዳግም ማካለል ከመገባቱ በፊት የጋራ ልዩ ኮሚቴው በ1972 የማስታወሻ ልውውጥ መሰረት ከዳግሊሽ ተራራ በስተሰሜን ከሰፈራ እና እርሻ መሬት ጋር በተያያዘ የተፈጠሩ ችግሮችን ለመፍታት ሁለቱን ሀገራት የሚያስማማ የመፍትሔ ሃሳብ የማቅረብ ስራውን ማጠናቀቅ እንዳለበት አመልክተዋል ።የጋራ ድንበሩን ዳግም ለማካለል ሁለቱ ሀገራት ያቋቋሟቸው የጋራ የድንበር ኮሚሽን፣ የጋራ የቴክኒክ የድንበር ኮሚቴ፣ እና የጋራ ልዩ ኮሚቴ ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ እና ስራቸውን እንዲያጠናቅቁ ማድረግ ተገቢ እንደሆነ ጠቁመዋል ።
https://www.press.et/Ama/?p=39551
407
0ሀገር አቀፍ ዜና
የጎዳና ላይ ሩጫ በቢሾፍቱ
ስፖርት
December 7, 2020
5
ቢሸፍቱ ፦የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ከወራት መቋረጥ በኋላ የመጀመሪያውን አገር አቀፍ የ30 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ አካሂዷል፡፡ ለ7ኛ ጊዜ በቢሾፍቱ ከተማ በተካሄደው በዚህ ውድድር ላይም በአጠቃላይ ነጥብ በሴቶች ኦሮሚያ ፖሊስ በሴቶች ደግሞ መከላከያ ስፖርት ክለብ ቀዳሚ በመሆን አጠናቀዋል፡፡ የመከላከያዋ አትሌት ገበያነሽ አየለ በሴቶች ቀዳሚ ሆና ስታጠናቅቅ፤ የገባችበት ሰዓት ደግሞ 1:47.03 ሆኖ ተመዝግቧል፡፡ የግል ተወዳዳሪዎቹ ብርሃን ምህረቱ እና ንግስት ሙሉነህ ደግሞ ሁለተኛና ሶስተኛ በመሆን ውድድራቸውን ፈጽመዋል፡፡ በወንዶች በኩል የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ክለብ አትሌቱ ኃይለማርያም ኪሮስ የወርቅ ሜዳሊያ ተሸላሚ ሆኗል፡፡ አትሌቱ 30 ኪሎ ሜትሩን ለመሸፈን የፈጀበት ጊዜም 1:31.18 ሆኗል፡፡ 1:31.23 የሆነ ሰዓት ያስመዘገበው ፌዴራል ማረሚያ አትሌት ዴሬሳ ገለታ እና 1:32.08 በሆነ ሰዓት የገባው የመከላከያው ሙስጠፋ ከድር ደግሞ ሁለተኛና ሶስተኛ ሆነው በማጠናቀቅ የብርና ነሐስ ሜዳሊያ ተሸላሚዎች ሆነዋል፡፡ በ7ኛው የኢትዮጵያ 30 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ አጠቃላይ ነጥብም በሴቶች ኦሮሚያ ፖሊስ ስፖርት ክለብ እንዲሁም በወንዶች የመከላከያ ስፖርት ክለብ የዋንጫ ተሸላሚዎች ሆነዋል፡፡አዲስ ዘመን ህዳር 28/2013
https://www.press.et/Ama/?p=36908
139
2ስፖርት
አትሌት ገንዘቤ ዲባባ የቫሌንሺያን የግማሽ ማራቶን አሸነፈች
ስፖርት
December 7, 2020
9
አዲስ አበባ፡- አትሌት ገንዘቤ ዲባባ በስፔን በቫሌንሺያ በተካሄደው የግማሽ ማራቶን ውድድር አሸነፈች። በመካከለኛ እና የአጭር ርቀት ሩጫ የምትታወቀው አትሌት ገንዘቤ ዲባባ ግማሽ ማራቶን ለመጀመሪያ ጊዜ ተወዳድራ አሸናፊ መሆን ችላለች። ጀግናዋ አትሌት ገንዘቤ ዲባባ ውድድሩን ለማጠናቀቅ 1 ሰዓት ከ05 ደቂቃ ከ18 ሴኮንድ ፈጅቶባታል።የገባችበት ሰዓት የቦታው አዲስ ክብረወሰን በመሆንም ተመዝግቧል። ውድድሩን በሁለተኛነት ያጠናቀቀችው ኬንያዊቷ ሼይላ ቼፕኪሩይ ስትሆን፤ ሌላኛዋ ኢትዮጵያዊት ሰንበሬ ተፈሪ ደግሞ ሶስተኛ ሆናለች። የነሐስ ሜዳሊያ ባለቤቷ ሰንበሬ ርቀቱን ለመሸፈን የወሰደባት ሰዓትም 1፡05፡51 ነው። በእለቱ በተካሄደው የሴቶች ማራቶን ደግሞ ኢትዮጵያውያኑ አትሌቶች ከ4-7 ባለው ደረጃ ተከታትለው ገብተዋል። በተመሳሳይ በእለቱ በተካሄደው የወንዶች ማራቶን ኢትዮጵያዊው ብርሃኑ ለገሰ 2፡03፡16 በሆነ ሰዓት ሶስተኛ ደረጃን ወጥቷል።አዲስ ዘመን ህዳር 28/2013
https://www.press.et/Ama/?p=36915
101
2ስፖርት
ከተፋቀርን አባይ ይገደባል ፤ እኛም እንጠግባለን
መዝናኛ
March 9, 2020
44
ተሰልፈን ቆመናል አምባሳደር አካባቢ ታክሲ ተራ።ታክሲዎች ተሳፋሪውን ተራ በተራ እየጫኑ ወደ መድረሻቸው ይጓዛሉ።ተሳፋሪው ሌላ ታክሲ እስኪመጣ ይጠብቃል።አንድ ከፍ የለ ድምፅ በሰልፍ የቆመውን ተሳፋሪ ትኩረት ስቧል።ሁሉም ወደ ተሰማው ድምፅ አማተረ።አንድ ወጣት አንዲት ህፃን ልጅ አቅፎ ተሳፋሪውን ቀረበና በእጁ የያዘውን በፕላስቲክ ማሸጊያ የተለበጠ ወረቀት ላይ የተፃፈ ጽሁፍ ድምፁን ከፍ አድርጎ ያነባል፡፡የተለያዩ ጎዳናዎች ላይ በተደጋጋሚ የሚሰማ ምልዕክት አይነት የመሰለው አይንና ጆሮው መለሰ። ልጁ ቀጥሏል፤ ወረቀቶችን ይዞ ድመፁን ከፍ አድርጎ ያነባል። “ከተፋቀርን አባይ ይገደባል እኛም እንጠግባለን። እባካችሁ ተዋደዱ፤ እርስ በርስ ተፋቀሩ ያኔ ኢትዮጵያ ከፍ ትላለች፡፡” ሰውየው ከፍ ባለ ድምፅ ይናገራል። ይሄን እዚያ ለመሳፈር የቆመው ሁሉ ጆሮ ሰጥቶ ይሰማው ጀምር፡፡ከሰውየው አንደበት የሚፈልቁ ቃላት የተመጠኑና ሁሉም ሰው ሊያዳምጣቸው የሚገቡ በመሆናቸው እንዲቀጥሉ ተመኘሁ።ታክሲ ለመያዝ ተጣድፌ የነበርኩትን ያህል፤ ታክሲ እንዲዘገይ ተመኘሁ።ሰውየው በፈገግታ ተሞልቶ ስለ ፍቅር ታላቅነት ይሰብካል።“እባካችሁ ተዋደዱ ያኔ ለውጥ ይመጣል ተከባበሩ ያኔ ድል ይመጣል….” ስለ ፍቅርና መዋደድ ስለ አብሮነትና ፍቅር በማይጠገብ አንደበቱ ያስረዳል። እናንተዬ ፍቅርን የሚሰብክ አንደበት፣ እድገት የሚያፀና ምክር፣ ህብረትን የሚሰብክ ንግግር ምንኛ ይጥማል።ታክሲ መጣና ተሳፈርኩ። ስራ ረፍዶብኝ ነበረና ቦታውን ሳልወድ ለቀኩ።ሰውየው ግን ከአይምሮዬ አልጠፋም ደጋግሞ ይታሰበኛል።ይህ ሰው ስለዚህ ጉዳይ እንዲናገር ምን አነሳስቶት ይሆን? የጎደለን ፍቅር መሆኑ ከኛ ከፍ ባለ ሁኔታ ገብቶት መንገርስ ላይ ያደረሰው ምን ይሆን? ብዙ አሰብኩ፤ እዚያው ቦታ ሆኜ የጎደለን ፍቅርና መተሳሰብ እንጂ እውነትም አባይ አይደለም ችግርና መከራችንም መገደብ እንችላለን የምር!!።ስለ ፍቅር ብለን እርስ በርስ ብንተጋገዝ ስለ ሀገር ፍቅር ብለን ለሀገራችን በጎ ካበረከትን ምን ሊጎለን ይችላል?ምንም! ለራሴ መልስ ሰጠሁ፡፡ታክሲ ውስጥ ረዳቱ ሒሳብ ሲለኝ ከሄድኩበት ሰመመን ተመለስኩ።አውጥቼ ሁለት ብር ሰጠሁት።“አምስት ብር ነው፡፡” እ…ከሁለት ወደ አምስት ብር ያደገው ከመቼ ጀምሮ ነው? አትነጫነጭ ሁሉም ከፍሏል። “በአቋራጭ ነው የምሄደው ጨምር።” ሹፌሩ በመሀል ረዳቱን ለማገዝ ቃላት መወርወር ጀመረ። “አንተ ሰው ስራ አይደል እንዴ ምን እያልክ ነው ለምን ገባህ እየተናገርን አይደል የጫንክ” ተሳፋሪውን ዞር ብዬ አየሁ ፊቱን ሁሉም ቅጭም ሲያደርግብኝ መኪናው ሙሉ በኔ ያኩረፈ መሰለኝ፤ አውጥቼ ሰጠሁ።እስክሰጠው ድረስ በስድብ እያጥረገረገኝ ነበር። ኦህ! አምላኬ ትግስቱን ስጠኝ ትርፍ ከፍዬም ተሰድቤም ከባድ ነው።ሰልፉ ቦታ ወደነበረው ሰው በሀሳብ ተመለስኩ።“ እርስ በርስ እንከባበር እንዋደድ፣ ፍቅር አተን ነው የተቸገርነው እባካችሁ እንፋቀር፡፡” ንዴቴ ረገበ።ስለፍቅር ብዬ ዝም አልኩ።እኛ ግን ምን ነካን።ፍቅራችን የት ገባ።ረዳቱና ሹፌሩ ግን ያንን ሰው ሰምተውት ይሆን ሲጭኑ እዚያ ቦታ ነበሩና ሳይሰሙት አይቀሩም።ችግሩ አያደምጡትም…። ወዳጄ ስላለን ብቻ የፈለግነው አንበላም እኮ አረ እንዋደድ ተዉ…። አብዝቶ መስገብገብ ምንድነው እንዴ? ሆድ ልክ አልባ ይመስል ሰውን መበደል፣ ሰውን መግፋት የሰውን መሰብሰብ አስጭኖና ቋጥሮ መቃብር ይዞ ላይሄዱት ነገር ኧረ ነውር ነው…!!።ሰው ከተዋደደ በደህነቱ ንፁህ ህሊናውን ይዞ ሊሰፈር የማይችል ደስታን ይጎናፀፋል።ህሊና ቢስ ከሆነ ግን ሰው ከሚለው ስብዕና የራቀ ክፉ አውሬ ከመሆን አይድንም። በክፉ ስራው ሰዎችን ክፉኛ ያቆስላል፣ ከሚታሰበው በላይ ክፋትን ይለምድና ለሰዎች ሴራን ይጎነጉናል ስለሌላው አይጨንቀውም ስለማንም አይገደውም።ይህ ሰው እያደረ ‹‹ሰው ጤፉ›› ነው።ሰውየው ግን አይቶናል ፍቅር በማጣታችን መቸገራችን ከኛ በላይ ገብቶት ጎዳና ላይ መስበክ ተያይዞታል… እንደው በዚህ በጎ ተግባሩ እስከ መቼ ይቀጥል ይሆን? ታድሎ።ውስጡ የሚሰማው ሰላምስ ምን ያህል ይሆን? እኔ ምለው ሰላም ግን ይሰፈራል። ምን ያህል ነው ክብደቱ? ኦህ! ይከብዳል አቻ የሌለው ነገር በምን ሊሰፈር ይችላል።ሰውየው ውስጡ ያ ሰላም ሳስበው ቀናው። ወዳጄ ደስታህ ከእጅህ እንዳይወጣ ባንተ ሰው እንዲደሰት ትፈልጋለህን? ውስጥህ ሰላም ከሆነ ባትበላ ረሀቡ አይቀፈድድህም፣ ባትለብስ የሰው ፍቅር ትሞቃለህ፣ በሰው ክብር ምቾት ይሰማሀል።የትም ጋደም ብትል ለሽ… ብለህ የሚያስቀና እንቅልፍ ትተኛለህ።ሰዎች ብዙ ጊዜ ስግብግብ የሚሆኑት ፈፅሞ ቢያገኙም በማይጠቀሙበት አግኝተውም በማይደሰቱበት መሻታቸው ላይ ነው። ይሰበስባል፣ ላይ በላይ ደራርቦ ከምሮም ከልክ በላይ ያደልባል እድሜውን ሙሉ ያለ እረፍት የሱ ያልሆነን የማይገባውን የሌሎችን እየነጠቀ ባለው ላይ እየጨመረ ቀዶ እንኳን የማይጨርሰው ሀብት ያከማችና ሰላሙን ያጣል።ሰውየው ግን ከየት ተልኮልን ይሆን “ተፋቀሩ ተዋደዱ” ያለው ፍቅር ከኛ መንጠፉ ምን ያህል ቢገባው ነው።ፍቅር አተን እንጂ ምን ይጎለን ነበር።በተጓዘበት በደረሰበት ሁሉ የሚሰብከው መልካም ነገር ስንቶቻችን ይሆን ጆሮ ሰጥነት የምንሰማው ምን ያህሎቻችንስ ነን ከልብ የምናዳምጠው።ዛሬ ላይ የምነሰማው መልካም ነገር ጎሎ ሳንፈልግ የሚቀርበን መጥፎ ዜና በተበራከተበት ለሁሉ ጉዳት መፍትሄ የሚሆነው ፍቅር ማጣታችን ዋንኛው ምክንያ ነው።ፍቅር ውስጥ የማይፈታ ችግር የማይታለፍ ፈተና የለም።መከባበር ውስጥ የማያስችል ጉዳይ የማያግባባ ሀሳብ አይኖርም ግን በተቃራኒው ከኛ ፍቀር ከራቀ ጥላቻ ቦታውን ይወርስና የማያርቅብን ጉዳይ አይኖርም፡፡አዲስ ዘመን የካቲት 30/2012ተገኝ ብሩ
https://www.press.et/Ama/?p=28753
598
1መዝናኛ
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን 12ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔን አካሄደ
ስፖርት
December 7, 2020
8
አዲስ አበባ፦ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን 12ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔውን ትናንት አካሂዷል፡፡ ያለፈው ዓመት ባጋጠሙ በርካታ ውጣ ውረዶች ስፖርቱ አሉታዊ ተጽእኖ ቢደርስበትም የተሻለ አፈጻጸም የተመዘገበበት መሆኑ ተመላክቷል፡፡ በተለይም በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኘውን የካፍ አካዳሚን በማስጠገን ለአገልግሎት መብቃቱ፤ ፌዴሬሽኑ ለብሔራዊ ቡድን ዝግጅት የሚያወጣውን ከፍተኛ ወጪ ታድጓል። የአህጉርና ዓለም አቀፍ ግንኙነትን በማጠናከር ረገድም ጠንካራ ሥራ በመከናወኑ ኢትዮጵያ በሴካፋ የመሪነት ቦታ ማግኘቷም በጉባኤው ላይ መነሳቱን የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን በድረ-ገጹ አስነብቧል፡፡ በጉባኤው በቀረበው የ2012 በጀት ዓመት የአፈጻጸም ሪፖርት ላይም ፌዴሬሽኑ የገንዘብ አቅሙን ማሳደጉ ተገልጧል፡፡ ለዓመታት የክለቦች ጥያቄ የነበረውን የሊግ ካምፓኒ ምስረታ እውን ማድረጉንም እንደ ስኬት ተነስቷል፡፡ በቀረበው ሪፖርት እና የ2013 በጀት ዓመት ዕቅድ ላይም በጉባኤው አባላት ውይይት ተደርጓል፡፡ በመጨረሻም የሲዳማ ክልል የጉባኤው አባልነት ጥያቄን ተቀብሎ በማፅደቅ እና በአጭር ጊዜ ውስጥ በተሻሻለው መተዳደሪያ ደንብ ላይ ለመወያየት እና ለማጽደቅ በሀዋሳ ከተማ አስቸኳይ ጉባኤ እንደሚካሄድ በመወሰን ጉባኤው መጠናቀቁን በዘገባው ተመላክቷል።አዲስ ዘመን ህዳር 28/2013
https://www.press.et/Ama/?p=36914
136
2ስፖርት
የብስክሌት ኮርቻ ቀበኛው
መዝናኛ
March 10, 2020
203
ሌባ ላመሉ ዳቦ ይልሳል እንዲሉ አመለኛ ሌባ ያገኘውን ከመስረቅ ወደኋላ አይልም። ታዲያ ሌብነት ሁሌም አይቀናምና አንድም በሰዎች መደብደብን ባስ ሲልም በፖሊስ መያዝና ለአስር መዳረግን ያስከትላል። ሌባ ከትንንሽ እቃዎች አንስቶ አስከ ከፍተኛ ውድ እቃዎች ድረስ ፤ ከትንሽ አስከ ከፍተኛ ገንዘብ ድረስ ይሰርቃል። አንዳንድ ሌባዎች የሚሰርቋቸው እቃዎች ግን እንግዳና ያልተለመዱ ሆነው ‹‹ምን ሊያደርግላቸው ነው?›› የሰረቁት ያሰኛሉ። ከሰሞኑ ኦዲቲ ሴንትራል ይዞት የወጣው መረጃም ይህንኑ ያመለክታል። ነገሩ እንዲህ ነው፤ የ57 ዓመቱ ጃፓናዊ የከባድ መኪና አሽከርካሪ ሂሮዋኪ ሱዳ ከወራት በፊት በአንድ የባቡር ጣቢያ በርካታ ብስክሌቶች በሚቆሙበት ቦታ ግምታቸው 8 ሺ የጃፓን የን ወይም 75 የአሜሪካ ዶላር የሚያወጡ የሁለት ብስክሌቶች ኮርቻ ወይም መቀመጫ ሲሰርቅ በቅኝት ካሜራ በመታየቱ በፖሊስ በቁጥጥር ስር ሊውል ችሏል። ሱዳ ድርጊቱን መፈ ፀሙን ያመነ ሲሆን ባል ተለመደ ሁኔታ የብስ ክሌት ኮርቻዎችን ወይም መቀመጫዎችን ያውም ለሃያ አምስት ዓመታት ሲሰርቅ መቆየቱን ለፖሊስ አስታውቋል። የሚገርመው ደግሞ የሰረቃቸውን እቃዎች በሙሉ በአንድ ላይ በመሰብሰብ በሚ ማርክ መልኩ እንዳስቀ መጣቸውም ለፖሊስ መና ገሩ ግርምትን ፈጥ ሯል። ‹‹የብስክሌት ኮርቻ ዎችን መስረቅ የጀመርኩት ከዛሬ ሃያ አምስት ዓመት በፊት በቶኪዮና ኦሳካ ነው። ስርቆቱን የጀመርኩትም በሥራ የሚገጥመኝን ውጥረት ለመቀነስ በሚል ሲሆን፣ በኋላ ላይ ግን ኮርቻዎቹን ሰርቄ መሰብሰብ ስጀምር ደስታን አጎናፅፎኛል›› ሲል ሶዳ ለፖሊስ ቃሉን ሰጥቷል። የ57 ዓመቱ የከባድ መኪና አሽከርካሪ የሚሰርቃቸውን የብስክሌት ኮርቻዎች ተከራይቶ ወደሚያስቀምጥበት ቦታ ፖሊሶችን መርቶ አሳይቷል። በቦታው 5 ሺ 800 የሚሆኑና ላለፉት ሃያ አምስት ዓመታት የተሰረቁ ኮርቻዎች መገኘታቸው ተረጋግጧል። የአሽርካሪነት ሞያውን በመጠቀም በጃፓን የተለያዩ አካባቢዎች የሚገኙ የብስክሌት ኮርቻዎችን ሲስርቅ መቆየቱንም ለፖሊሶች አስረድቷል። ከዚህ በፊትም ሌላ ጃፓናዊ በተመሳሳይ በአንድ ዓመት ውስጥ 159 የሚሆኑ የብስክሌት ኮርቻዎችን በመስረቅ መነጋገሪያ ሆኖ እንደነበርም መረጃው አስታውሷል። አዲስ ዘመን መጋቢት 1/2012አስናቀ ፀጋዬ
https://www.press.et/Ama/?p=28828
245
1መዝናኛ
ትራምብ
መዝናኛ
March 5, 2020
25
የአድዋን ድል ለማክበር የትውልዱ ተረኛ ወጣት በነቂስ ወጥቷል:: ያስገመግማል:: ያጉተመትማል:: ሆ በል ይላል:: በባህላዊ አልባሳትና በጥንት አባቶች የጦር ሜዳ አለባበስ ተውቦ ደምቋል:: አባት አርበኞች ጋሻና ጦር ጎራዴ ይዘው ቁጭ ብድግ እያሉ በወኔ ተሞልተው ይሸልላሉ:: ያቅራራሉ:: ይፎክራሉ:: ‹‹በለው ሲል ገዳይ…ያንን ጥልያን ከተረተሩ ከጉድባው ላይ›› እያሉ:: እናቶች ወጣት ሴቶችና ወንዶች የአባቶችን ወኔና ጀግንነት በማወደስ እልልታውን ያቀልጡታል:: እልልል እንደገና:: እልልል እንደገና:: እንደገና:: የዘንድሮው የአድዋ ድል በምኒሊክ አደባባይ ሲከበር ከሰሞኑ የአሜሪካም መንግስት ለግብጽ በማድላት የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የውሀ መሙላት ስራ አሜሪካ የጀመረችው ማደራደር ሳይቋጭ ኢትዮጵያ እንዳታካሂድ የሚል ቀጭን የድፍረት ትእዛዝ ለኢትዮጵያ ማስተላለፉን ሁሉም ኢትዮጵያዊ በነቂስ ሰምቷል:: ክፉኛ አዝኗል:: ተበሳጭቷል:: ቁጣው ገንፍሎ ይታያል:: ይህን የሰሙ አንድ አባት አርበኛ እዛው ጊዮርጊስ ምኒሊክ አደባባይ ላይ ዙሪያቸውን ለነበሩት አባት አርበኞች ከፍ ባለ ድምጽ የአድዋን ድል በኩራት ስናከብር ሌላ ግራዚያኒ ትራምብ የሚባል ደግሞ መጣብን አይደለም ያሉ ግዜ ዙሪያ ገባው በአባት አርበኞች ሽለላና ቀረርቶ አስተጋባ:: እምቢ ለሀገሬ…እምቢ …እምቢ ለጠላት እምቢ…ኢትዮጵያ ሀገሬ …የነብሮች እናት…የአምበሶች እናት …እልፍ ጀግና አለ የሚሞትላት…ማንአባቱ ነው ችሎ ሚደፍራት…እያሉ አባት አርበኞች በፈላ ወኔ በሚፋጅ ቁጣ ወዲያና ወዲህ እየተንቆራጠጡ ወደፊት እየሄዱ ደሞ ወደኋላ እየተመለሱ ይይዙትን ይጨብጡትን አጡ:: ደሞ የማናባቱ ወሮበላ ነው ትራምብ የሚባለው አሉና አንዱ አርበኛ ጠየቁ:: እንጃለቱ አሉና ቆፍጣናዋ የሴት አርበኛ መለሱ:: ምንድነው ደሞ ትራምብ ብሎ ስም ለጠቁ ሌላው አርበኛ:: ይሄ የሰው ሳይሆን የአጋንንት ስም መሆን አለበት አሉ ከአርበኞቹ ጋር የተሰለፉት ባለነጭ ጥምጣሙ መምሬ:: ሁሉም በአንድ ግዜ የተማከሩ ያህል ልክ ነው፤ ልክ ነው ሲሉ በአደባባዩ አስተጋቡ:: እዚህም እዚያም ጭፈራው ሆታው ሽለላው ፉከራው ቀልጧል:: አራዳ ጊዮርጊስ አደባባዩ ያለወትሮው ደምቋል:: ፈክቷል:: አንዳች ግርማ ሞገስ የተደፋበት መስሏል::ይሄ ትራምብ የምትሉት ጨፈረር ኢትዮጵያን ሲጣላ፤ ለመሆኑ ማንን እንደነካ ያውቃል፤ መጥፊያው ደርሶ ነው:: የኢትዮጵያ መሪ አሳዳሪ ጠባቂ ሰው ሳይሆን እግዚአብሄር ነው:: ኢትዮጵያን በመዳፈሩ የአምላክ ፍርድና ታላቅ ቁጣ በእሱም በሀገሩም ላይ ይወርዳል አሉ፤ የቄሱ ጓደኛ መሪጌታ ገብረአምላክ:: የተመካበት መሳሪያ፣ ቴክኒዮሎጂ፣ ሳተላይት፣ መንኮራኩር፣ የስለላ ድሮን በሰማይ በውቅያኖስ በምድር በባህር ያሰማራውና የታበየበት ሰራዊት ኃያልነት ሁሉ በአምላክ ፊት ምንም ናቸው:: እንደ ጉም በኖ ይጠፋል:: ይፈራርሳል:: ሀገሩ ምድረበዳ ትሆናለች:: ሰውም አእዋፍም አይኖርበትም:: ታላላቅ ነን የሚሉት ሀገራት መሪዎችና አለምን ያንቀጠቀጠው ወራሪና እብሪተኛ ሠራዊታቸው ሁሉ በአምላክ ክንድ ይደረመሳል አሉና ዝም አሉ:: መምሬ ቀጠሉና የኢትዮጵያ አምላክ ከነኩት ቁጡ ነው:: ሲያሻው በመሬት መንቀጥቀጥ፤ በመብረቅ፤ በአውሎ ንፋስ፤ በክፉ ማእበል፤ በውሀ ሙላት ይመታቸዋል:: ያጠፋቸዋልም:: እነሱ ከፈጣሪ በላይ ነን ብለው አለምና ምድሪቱን ሁሉ ገዢዎቹ መሪዎቹ አስተዳዳሪዎቹ እኛ ብቻ ነን ብለዋል:: ይሄኔ ነው መፍራት አሉ መምሬ:: እንግዲህ ነገር ሁሉ ለበጎ ነው እንዲሉ መጪውን ሁሉ በጥሞና በማስተዋልና በአርምሞ መጠበቅ ነው አሉ:: በበአሉ ላይ ከአርበኞቹ ጋር የታደሙት ሙሉ ቢጫ ከላይ እስከታች የለበሱ ጸጉራቸው ከአናታቸው ወርዶ መታጠቂያቸው ድረስ የተንዠረገገው በሰንሰለት ወገባቸውን የታጠቁት አባ አለም በቃኝ የተባሉ ባሕታዊ:: አባታችን በህልምዎ ነው በምናብ ነው አርምሞውን ያዩት ሲሉ አርበኞቹ ጠየቋቸው:: ሁለቱንም አይቻለሁ አሉ ባህታዊው ረዥሙን ጫፉ ጦር ያለበትን መቋሚያቸውን ተደግፈው:: አባት አርበኞቹ ለአፍታ በዝምታ ተዋጡ:: ወዲያው የበአሉ ጭፈራና እምቢ ለሀገሬ የሚለው ሆታና መዝሙር አነቃቸው:: ተከብረሽ የኖርሽው በአባቶቻችን ደም…እናት ኢትዮጵያ የደፈረሽ ይውድም…የደፈረሽ ይውደም የሚለው የወጣቶች መዝሙር ጎልቶ ይሰማል:: ይሄኔ አባትና እናት አርበኞች እየፎከሩ ተንጫጩ:: እሳት ቢያንቀላፋ…ገለባ ጎበኘው…ባያውቀው ነው እንጂ ባይጠራጠረው…ዘራፍ የኢትዮጵያ ልጅ…ለነጻነቱ በደም የሚዋጅ… ትራምብ የሚባል ሆዳም አውደልዳይ…የግብጾች አሽከር ከርከሮ መሳይ…ሲያናፋ ቢውል እንደ አህያ…ወግድ ክላ አለው ጀግናው ኢትዮጵያ ብለው ፈከሩ ሸበቶውና ደረታቸው በሜዳሊያ የተንቆጠቆጠው አባት አርበኛ:: በእልልታና በጭብጨባ በሆታ በፉከራ አካባቢው ተደበላለቀ:: ሌላው አርበኛ ተቀበሉና ቀጠሉ:: ለዚያ ሰላቶ ትራምብ ለሚሉት …ለነጫጭባው…ንገር ሂድና…ጦር ልማዱ ነው የኢትዮጵያ ጀግና…ለሀገሩ ይሞታል ደግሞ እንደገና…የታመነ ነው በቃሉ የጸና…ብለህ ንገረው…እስከሚገርመው…ዘራፍ የአምዮ ልጅ የኢትዮጵያ…ከእናቱ በፊት ጥሎ ሚወድቀው …የወኔው ግለት…የሚጋረፈው…ዘራፍ የአባቶቹ ልጅ ….ነበልባል ቋያ… ሰደድ እሳቱ…መጠቃት ሞቱ…መደፈር… ሞቱ …የማይሳሳ ለአንድ ሕይወቱ…ብለህ ንገረው ትራምብ ለሚሉት…ለግብጾች ፈረስ ለሚጋልቡት…ዘራፍ የመይሳው ልጅ የነዮሀንስ የነአባ ዳኘው…የነጎበና የነአባ ዳጨው የነጃገማ የእነ ባልቻ መድፍ አገላባጭ ብቻ ለብቻ…ብለህ ንገረው ለዚያ ለትራምብ እስከሚገርመው እያሉ አርበኛው በቁጣና በጋለ ወኔ እየሸለሉ ሲንደቀደቁ አካባቢው አረገደ:: የአድዋ ድሉን 124ኛ አመት ለማክበር የተሰበሰበው ሕዝብ በሆታ አስተጋባ እምቢ ለሀገሬ እያለ:: የአሜሪካንን መግለጫ ከ2 ቀን በፊት ሕዝቡ ሰምቶ ስለነበር ቁጣውን በባህሉ መሰረት በተለያየ መንገድ ሲገልጽ ውሎ ከአባቶቹ ጋር ወደ ቤቱ ተመለሰ:: ለሀገራቸው ክብር የሚቆሙ ጀግና ወጣቶች ስለተካን ክበር ተመስገን አሉ- አዛውንቶቹ አባትና እናት አርበኞች:: ኢትዮጵያ የታላቁን ህዳሴ ግድብ ውሀ እንዳትሞላ የሚለው የአሜሪካ ድፍረትና ንቀት የተሞላበት ሉአላዊነታችንን የደፈረ አቋም እጅግ ከፍተኛ የማይበርድ ሕዝባዊ ቁጣን ቀሰቀሰና አረፈው አለ አንዱ የበአሉ ታዳሚ ወጣት:: እብሪትና ድፍረት መዘዙ ብዙ ነው አሉ አባት አርበኛ ደጋጋ ሁንዴ:: ኢትዮጵያን መናቅ መድፈር ታላቅ ዋጋ ያስከፍላል ብላችሁ ለትራምብ ንገሩት አሉ ደገሙና ወደ ወጣቶቹ ዞረው:: ወጣቶቹ ይህን ግዜ እንደ መሳቅ ብለው – አባባ አባባ ትራምብ እኮ አማርኛም ኦሮሚኛም አይሰማም አሏቸው:: የት አባቱ አሉና በዛው በሱ ትብታብ ቋንቋው ንገሩት:: ከእኛ ላይ ይውረድ:: ትራምብ ለግብጽ አሽከርም ገረድም መሆን መብትህ ነው በሉት:: ከኢትዮጵያ ትከሻ ግን ይውረድ አሉ መለሱና:: እምቢ ካለ የኢትዮጵያ ታላቅ አምላክ ሳይውል ሳያድር የሚሰጠውን ፍርድ ይጠብቅ እንዲያውም ተውት አሉ- አርበኛ ደጋጋ ሁንዴ:: አዲስ ዘመን የካቲት 26/2012ወንድወሰን መኮንን
https://www.press.et/Ama/?p=28551
715
1መዝናኛ
የእብድ ገላጋይ ያቀብላል ድንጋይ
መዝናኛ
March 10, 2020
55
 በአሁኑ ወቅት ዓለማችን በኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ እየተፈተነች ትገኛለች፡፡ በቫይረሱም ምክንያት ሰው እንደ ቅጠል በእያንዳንዱ ሰከንድ ይረግፋል። በሽታው በትንፋሽና በንክኪ በቀላሉ የሚዛመት መሆኑ ደግሞ ስርጭቱን በቀላሉ ለመቆጣጠር አዳጋች አድርጎታል፡፡ ታዲያ በዚህ የዓለማችን ስጋት በሆነው በሽታ ስጋት የገባው አባወራ ራሱንና ልጆቹን ለማዳን ያደረገው ድርጊት የሰሞኑ የተለያዩ መገናኛ ብዙሃን መነጋገሪያ ሆኖ ነበር፡፡ ነገሩ እንዲህ ነው ግለሰቡ የሊትዌንያ ነዋሪ ሲሆን በኮኖራ ቫይረስ ተይዛለች በሚል ስጋት ባለቤቱን መታጠቢያ ቤት በማስገባት ቆልፎባት፤ እንዳትወጣም የከለከላት ሲሆን ይህ ድርጊቱም ዓለምን ጉድ አሰኝቷል፡፡ ባሳለፍነው የካቲት ወር አጋማሽ በሊትዌንያን ቪሊኒዩስ የሚገኝ ፖሊስ በአካባቢው ከሚገኝ አንድ ስፍራ አስጨናቂ የስልክ ጥሪ ይደርሳቸዋል፡፡ ለፖሊስ የደረሰው ጥሪም በመኖሪያ ቤቷ መታጠቢያ ቤት በባልዋና በሁለት ልጆቿ የተቆለፈባት አንድ እንስት ጥሪ ነበር፡፡ ወደ ጥሪው ቦታ ያመራው የፖሊስ ቡድን ወደ ትዕይንቱ ቦታ ሲደረስ ድርጊቱን የፈፀመው አባወራ ያለአንዳች ፍርሐት የመኖሪያ ቤቱን በር በመክፈት ሚስቱን በመታጠቢያ ቤት እንደቆለፈባት በመግለጽ ይህንንም ያደረገው ከኮሮና ቫይረስ ጥቃት ራሱንና ልጆቹን ለመከላከል አስቦ ያደረገው መሆኑን ተናግሯል፡፡ የአካባቢው ብሄራዊ ፖሊስ ቃል አቀባይ ራሙናስ ማቶኒስ ለጋዜጠኞች እንደገለጹት “አባወራውና ሁለቱ ጎረምሳ ልጆቹ እማወራዋን ከመታጠቢያ ቤት እንዳትወጣ የከለከሏት በኮሮና ቫይረስ ተጠቅታ ሊሆን እንደሚችል እንደምትጠረጥር ስለነገረቻቸው ነው፡፡ ሴትየዋ ወደ ጣሊያን ሄዳ በነበረበት ወቅት ከወደ ቻይና ከመጡ ሰዎችም ጋር ተገናኝታ ስለነበር በዚህም ምክንያት በኮሮና ቫይረስ ተጠቅታ ሊሆን እንደሚችል ስጋት እንደገባት ለባለቤቷ ታጫውተዋለች፤ታዲያ በጉዳዩ ላይ ቀልድ የማያውቀው አባወራም ነገሩን በቸልታ አልተመለከተውም አባወራው በአስቸኳይ አንድ የህክምና ዶክተር ጠርቶ በኮሮና ቫይረስ ተጠቅታ ሊሆን እንደሚችል ስጋቱን ነገረው። ሀኪሙም “የእብድ ገላጋይ ድንጋይ ያቀብላል” እንደሚባለው ሙያውን ዘንግቶ ለሰውየው ሴትየዋን ገለል እንዲያደርጋት ይመክረዋል፡፡ አባወራውም የሀኪሙን ምክር በመስማት ከሁለት ልጆቹ ጋር በመሆን እማወራዋን በመታጠቢያ ቤት በማስገባት ቆለፉባት፡፡ ሰውየው እንደተናገረው በሚስቱ ላይ አንዳች ጉዳት ለማድረስ ወጥኖ የሠራው እንዳልሆነና እንዲያው ዝም ብሎ የዶክተሩን ምክር ተከትሎ ሚስቱ በሽታውን እንዳታሰራጭ ለመከላከል ያደረገው መሆኑን ገልጿል፡፡ በድርጊቱ የተከሰተ ምንም ጥቃት የሌለ ሲሆን በሴትየዋም በኩል የቀረበ ቅሬታ የለም፤ስለዚህ ፖሊስ አምቡላንስ በመጥራ ሴትየዋ በሽታዋን እንድትመረመር ወስዷታል፡፡ በመጨረሻ የባልየው ጭንቀትና ፍራቻ መሠረት የለሽ መሆኑንና ሴትየዋም ተመርምራ ከኮሮና ቫይረስ ነፃ መሆኗ ተረጋግጧል፡፡ ቢሆንም ግን ይህ ክስተት ኮቪድ 19 ምን ያህል ሰዎች ላይ ተፅዕኖ እያደረሰ መሆኑን ያስረዳል፡፡ ሰዎች ራሳቸውን ከበሽታው ነፃ ለማድረግ የትዳር አጋራቸውን መታጠቢያ ቤት ውስጥ ቆልፈው መውጣት ከጀመሩ ጉዳዩ ምን ያህል አሳሳቢ መሆኑን ያሳያናል፡፡ አዲስ ዘመን መጋቢት 1/2012 ኃይለማርያም ወንድሙ
https://www.press.et/Ama/?p=28831
332
1መዝናኛ
ለአዳኞች እጅ የሰጠው ግዙፉ ተኩላ
መዝናኛ
March 24, 2020
36
በሩሲያ በረዷማ አካባቢዎች ላይ በሚገኙ ደኖች ውስጥ ተኩላዎች በብዛት ይኖራሉ። እነዚህ ተኩላዎች ታዲያ በጫካ ውስጥ የሚኖሩ ሌሎች እንስሳትን ይመገባሉ እንጂ ለአካባቢው ነዋሪዎች ብዙም ስጋት አይሆኑም። በሩሲያ አንዲት አነስተኛ መንደር ውስጥ የሚኖሩ ሰዎች ግን በአንድ ግዙፍ ተኩላ ስጋት ገብቷቸው ሲቸገሩ ቆይተው ሰሞኑን እፎይ ብለዋል ሲል ኦዲቲ ሴንትራል ፅፏል። ነገሩ እንዲህ ነው፤ በሩሲያ አሌክሳንደሮቭካ በተሰኘች አንዲት አነስተኛ መንደር ውስጥ የሚኖሩት እነዚህ ሰዎች በተደጋጋሚ ሲያስጭንቃቸው የቆየው አንድ ተኩላ በአዳኞች መመታቱ ሪፖርት ይደረጋል። እንዲህ መንደሪቷን ሲያምሳት የቆየው ተኩላ በአዳኞች መመታቱ ነዋሪዎችን እፎይ ያሰኘ ቢሆንም፣ ተኩላው ባለፉት አርባ አመታት በአካባቢው ውስጥ ያልታየ መሆኑና በዚህ የክረምት ወቅት ሰዎች በሰፈሩባቸው አካባቢዎች ላይ መግባት መጀመሩ አነጋጋሪ ሆኗል። ተኩላው ወደዚች መንደር መግባት ከጀመረ ወዲህ ብዙ ውሾች ቅርጥፍ ጥፍ ተደረገው ተብልተዋል። ከሃያ በላይ የሚሆኑ ላሞች፣ በጎችና ፈረሶችም የዚሁ ተኩላ ሲሳይ ሆነዋል። ተኩላዎች፣ መምጣታቸውን ለማንቃት በየቤቱ በጠባቂነት የተያዙ ውሾችም ይህንኑ ተኩላ በመፍራት ድምፃቸውን አጥፍተዋል። ከዚህ ሁሉ ውድመት በኋላም ተኩላው በአካባቢው አዳኞች በመከራ የተገደለ ሲሆን፣ አዳኞች ተኩላውን ከበው ለማንሳት ሲታገሉ የሚያሳይ ምስል በማህበራዊ ትስስር መለቀቁን ተከትሎ ተኩላው በግዙፉነቱ ወደር ያልተገኘለት መሆኑ ብዙዎችን አስደንቋል። ‹‹ውሾች እንኳን ሊጮሁ ራሳቸውን ነው የደበቁት፤ ምንም አይነት የውሾች ጩኸትም አይሰማም። ለምን እንደሆነ ባላውቅም ምን አልባት ውሾቹ ተኩላውን ፈርተው ሊሆን ይችላል›› ሲል አንድ የመንደሪቷ ነዋሪ ተኩላው ከመገደሉ በፊት የነበረውን ሁኔታ ገልጿዋል። የአካባቢው አዳኞች በኋላ እግሩ ሲቆም መካከለኛ ቁመት ካለው ሰው ጋር እኩል የሚሆነውን ይህን ግዙፍ ተኩላ ለመግደል ሲዘጋጁ የመንደሪቷ ነዋሪዎች ፍርሃት ነግሶባቸው እንደነበር በዘገባው ተመላክቷል። ጉዳዩ በማህበራዊ ትስስር ገፅ መለቀቁን ተከትሎ ደግሞ በርካቶችን አስገርሟል። የዚህ ግዙፍ ተኩላ መገደል በኢንተርኔት የብዙሃንን ትኩረት ያገኘ ጉዳይ ቢሆንም፣የመንደሪቷ ነዋሪዎች ቤታቸውን በከበበው ደን ውስጥ አሁንም የዚሁ አይነት ግዙፍ ተኩላ ሊኖር ይችላል የሚል ስጋት እንዳደረባቸው በዘገባው ተመላክቷል። አዲስ ዘመን መጋቢት 15/ 2012 አስናቀ ፀጋዬ
https://www.press.et/Ama/?p=29010
259
1መዝናኛ
ባይሆን ጥሩ ነበር፤ ግን ሆነ
መዝናኛ
March 23, 2020
33
ሳንፈልግ የሚያስፈግጉን፤ ሳንወድ የሚያስቁን ብዙ ሁነቶች በሰሞኑ በውዝግብ ውስጥ አሳልፈናል። እርግጥ ነው እንደ ማህበረሰብ ለጉዳዮች ያለን ግንዛቤ እጅግ ያነሰ ነው። የኛ ያልሆኑ ነገሮች ደግሞ አዳዲስ ለሚፈጠሩ ጉዳዮች ማለቴ ነው። እንጂማ ስለኛ ከኛ በላይ የሚያውቅ እንደሌለ ዘንግቼው አይደለም። እናም ከሳምንት በፊት ወደ ሀገራች ገባ የተባለው የኮሮና ቫይረስ ብዙዎቻችንን በሀሳብ ኮርኩሮናል። እጅግ ደጋጎችን አይተን “እናንተማ በርክቱልን፤ ስለኛ ህይወት ጣዕም ቅመሞች ናችሁና ጤናችሁ ይብዛልን” እንዳልነው ሁሉ፤ አንዳንድ ጉደኞች “ጉድ!” የሚያስብል ተግባር ውስጥ ገብተው መክረማቸውም ተሰምቷል። እርግጥ ተቆንጥጠዋል አሉ። ቁንጥጫው ተገቢ ነው ግን አይበቃቸውም። የምር በወገን ላይ ለጨከነ ቁንጥጫ ያረካል? በፍፁም። አቤት አቤት ጭካኔ! በወገን ላይ የምር ይደረጋል? ወይ ዘንድሮ! ባይሆን ጥሩ ነበር ወገን፤ መሆን የሌለበት ግን ሆኗል። ባንሰማ ጥሩ ነበር፤ ግን ደግሞ ባንወድም ሰማን። ባይደረግ መልካም ነበር፤ ግን ደግሞ ተደረገ። ስናሳዝን ግን! መተዛዘንናችንንና መተሳሰባችንን ማን ቀምቶን ይሆን? ማንስ ለውጦብን ይሆን? ግን የእኛ የምንለውን እኛነታችንን በ“እኔ” ቀየረብን። “እኔ ከሞትኩ…..ን” ከኛ ጋር ያጋባው ግን ማን ነው? ከዚህ ጋርማ መፋታት አለብን። ጉድ ነው! ይሄ ለማመን ይከብዳል። ወገን ስለወገን ሳይሆን ስለራስህ ብለህ ሰው ሰው ሽተት፤ ካልሆነ ኑሮህ ጣዕም ያጣል። በሰዎች ችግር ለመክበር መጣር ከባድ ነው። በሰዎች ስጋት ነግደህ፤ ለሽሮ የሚጋፋን ረግጠህ ቁርጥ ስጋ ለመብላት መስገብገብ የምር በጣም ያስተዛዝባል። ሰሞኑን የሆነው ይህ ነው። ምስኪኑ፤ የማያውቀው “መዓት መጣብህ” ተብሎ ወደአንተ ዘንድ ለመሸመት ደጅህ የመጣን አቅመ ቢስ ገፈተርክ አሉ። በደህናው ጊዜ ለአንተ መለወጥ የተጋውን ሚስኪን በክፉ ቀኑ ክፉ ሆንክበት ሲባል ለሰሚው ግራ ሆኗል። ኧረ በፍጹም በዚህ ሰዎች በፍቅር በኖሩበት ሀገር ነጋዴ ህዝቡን በክፉ ቀን አይገፋም፤ ሰዎች በአንድነት ጠብቀው ባቆዩት ፍቅር እንዳይበጠስ ሆኖ በተጋመደበት ምድር ነጋዴ በህዝብ ላይ አይጨክንም፤ መነጠል በሚከብድበት፤ መነጠል በማይቻልበት ማህበረሰብ እንዲህ አይደረግም ተብሎ ሙግት ቢገጥሙም እውነቱ የተገላቢጦሽ መሆኑ አስፈርቷል። አንዳንዴ ሳይፈልጉት የሚውጡት ሂስ አለ። ነጋዴ ሆይ “ዋጥ!” ተብለሀል ዋጠው። ይህን አድርገኸው ከሆነ ከባድ ነው። በወገንህ ላይ ጨክነህ ከነበር አጉል ነው። ይህ እውነት ሳይፈልጉትም የመረረ ነው። ወዳጄ! እሰኪ አስበው ምንአልባት የዚህ ህዝብ ቀና መሆን አንተን ጠብቆሀል። የዚህ ህዝብ እያንዳንዱ ጥረት አንተን ጠቅሞሀል። አይንህን አስፍተህ ከተመለከትክ በምንም መልኩ በራስህ የያዝከው አንዳች ነገር እንኳን የለም። ስለራስህ ብታስብ ይህንን ለማድረግ ባላሰብክ፤ ሌላውን ተወው። ስለራስህ ምቾት፤ ስለራስህ ደስታና የተቃና ኑሮ ሌላውን ማኖር ግድ ይልሀል። ወዳጄ ደሀው እኮ ላንተ ውበት ነው። ከመሀሉ ስትቆም አንተን የሚያስጌጥ፤ ደፋ ቀና ብሎ፤ ብዙ አምርቶልህ ትንሽ ጎርሶ የሚያድር፤ ብሎኬት ተቀባብሎ ቤትህን የሚያንፅ፤ ቀለም አስቀስሞ ልጆችህን በእውቀት የሚያበለፅግ፤ ጠዋት ቤትህን አንኳኩቶ ቆሻሻህን የሚያፀዳ፤ የእርሱ መኖር ነው አንተን የሚያኖርህ! እንዲያው ሌላው ይቅር፤ “ማነህ… “ እያልክ የፈለከውን የምታዝዘው፤ “እዚያ ጋ አምጣልኝ እንጂ!” እያልክ የምትጣራው “ሎሌ” ላንተ እንዴት ጠቃሚ መሆኑን ዘነጋህ? ያለ መስተንግዶ መኖር አይከብድህም፤ እንዲያው “ጌታው ምን ልታዘዝህ? ምን ጎደለህ?” የሚልህን አትወድድም? እና እንዴት ብለህ በዚህ ሰው ጨከንክ ታዲያ? ግን ካንተ ጋር በገቢው አነስ የሚል ከጎንህ ከሌለ በምን ትኮፈሳለህ? እንዲያው በሞቴ ወዳጄ ለአንተ ዛሬ እዚህ ላይ መቆም መሰረት ከእስርህ ያለው ያ ወገንህ መሆኑን እንዴት ዘነጋኸው? ኮሮና የሚባል ጉድ መጣልህ ፤እራስህን ጠብቅ፤ መጠበቂያውም እኛውልህ ተብሎ የተነገረውና እራሱን ለማዳን ለሸመታ ወዳንተ የመጣን ምስኪን “አምጣ” እያልክ ስትነጥቀው የዋልከው ገንዘብ እኮ እረፍት አይሰጥህም። ጥረው ግረው የበሉት ነው የሚጣፍጠው፤ በእርግጥ ጣዕም የሚገባህ ከሆነ ያ ነው ትክክለኛ ጣዕም የሚፈጥር፤ ያ ነው የራስ ከሆነ ልፋት ተገኝቶ ሲበሉት የሚጥም፤ ከወገንህ መንጭቀህ የሰበሰብከውን ገንዘብ መሽቶ ጣትህን ከምላስህ ምራቅ እያስነካህ ስትቆጥረው ቫይረሱን ወደ ውስጥህ ብታዘልቀውስ? ከባድ ነው! የተያዝክበት መንገድ እንኳን አጉል ነው። ወዳጄ ትላንት የጨከንክበት ወገንህ መታመምህን ሰምቶ የሚጠይቅህ ይመስልሀል? በፍፁም! ሰው የእጁን ፍሬ ነው የሚበላ፤ ስለ መልካም ውለታህ መልካም ምላሽ ጠብቅ፤ ካልሆነ ግን በተቃራኒው ነው። ሁሉም የተሰፈረ ልኬት አለው። ከዚያ ውልፍች አይልም። ስላግበሰበሰ ከተፈቀደልት አምልጦ ትርፍ አያሻምድም፤ ስለተወው የርሱ የሆነ ድርሻ በሌላ አይቀማም። ወገን ስለራስህ ምቾት ለሌሎችን ምቹ ሁን። ስለራሰህ መልካም ፍፃሜ ስትል መልካምነት ላይ አዘውትር! ሰው በቁርጥ ቀን ይለያል፤ ሳንፈልግ የለየናችሁ እነአጅሬ፤ ያደረጋችሁትን ባናውቅ መልካም ነበር። እናንተም ይሄንን ባታደርጉ ምንኛ በወደድን፤ ተግባር እኮ ጥላ ነው በሄዱበት ሁሉ የሚከተል፤ ሲበርድ ፀሀይ ሆኖ የሚያሞቅ፤ ሲሞቅ ምቾትን የሚፈጥር በጭለማ የፋኖስን ያህል ብርሀን የሚፈነጥቅ፤ የምር መንገድ የሚገራው በበጎነት ነው። ዛሬ ነገ ላይ ታሪክ ነው። ያ ታሪክ፤ ያ ትውስታ ነገ ላይ ሲገለፅ ሁለት መልክ አለው። አንዱ በተወሳ ቁጥር የሚያስፈግግ፤ ሌላኛው ደግሞ ምነው ባልተነሳ፤ አሁን የምር ይህንን የሰው ልጅ ያደርገዋል የሚያስብል፤ ከመጀመሪያው ማህደር ውስጥ እራስን ማስገኘት ነው። ቸር ያሰማን! አዲስ ዘመን መጋቢት 14 /2012 ተገኝ ብሩ
https://www.press.et/Ama/?p=28957
631
1መዝናኛ
ስዕልን በሁለት እጅ
መዝናኛ
March 24, 2020
70
አለማችን ከሊዮናርዶ ዳቪንቺ እስከ ፓብሎ ፒካሶ ድንቅ ሰአሊያንን አፍርታለች። አሁንም በየሃገራቱ በተለያዩ የስነ ስዕል ዘርፎች የስዕል ጥበባቸውን ለዓለም የሚያሳዩ ዝነኛ አርቲስቶች አልጠፉም። ሃገራችንም ብትሆን ሰዓሊና ባለቅኔ ገብረ ክርስቶስ ደስታን ጨምሮ በርካታ አንጋፋና ወጣት የስነ ስዕል ጥበበኞችን አፍርታለች። ሰዓሊያን በተለያየ የስነ ስዕል ዘርፍ የየራሳቸውን የአሳሳል ዘይቤ በመከተል የስዕል ስራቸውን የሚሰሩ ቢሆንም፣ አብዛኞቹ ቀለም ነክረው በዘረጉት ሸራ ላይ የሚቀቡት በአንድ እጃቸው ብቻ ነው። ይሁንና አንዳንድ በተፈጥሮም ሆነ በአደጋ ሁለት እጃቸውን ያጡ ሰአሊያን በአንድ እጃቸው ብቻ ብሩሽ ወይም እርሳስ መጨበጥ ስለማይችሉ ስዕል ለመሳል ሁለቱንም እጆቻቸውን ይገለገላሉ። ኦዲቲ ሴንትራል ሰሞኑን ከወደ አሜሪካ ይዞት ብቅ ያለው መረጃ ደግሞ ሁለት ጤነኛ እጆችን በአንድ ጊዜ በመጠቀም ስዕል መሳል እንደሚቻል ያረጋግጣል። መክሊት ካልሆነና ከላይ ካልተሰጠ በቀር ስዕልን እንዲሁ በቀላሉ በአንድ እጅ እንኳን ለመሳል ያስቸግራል። በሁለት እጅ በአንድ ጊዜ ሲሆን ደግሞ ጭራሽ የማይታሰብ ይሆናል። ለአሜሪካዊው አማተር ሰአሊ ግን ይህ እጅግ የቀለለ ጉዳይ ነው ይላል የኦዲቲ ሴንትራል ዘገባ። እንደ ዘገባው፤ በአሜሪካ ዴትሮይት ግዛት ጠበቃና አማተር ሰአሊው ኮሊን ዳርክ የተለያዩ ቀለሞችን በመጠቀም ጠለቅ ያሉ የስዕል ጥበብ ስራዎችን በሁለት እጆቹ በአንድ ጊዜ የመስራት ችሎታው ረፍዶም ቢሆን፣ የብዙሃንን ትኩረት ለመሳብ በቅቷል። የ42 አመቱ ይህ ጎልማሳ ከታዋቂ የፊልም አክተሮችና ታዋቂ ሰዎች ጀምሮ የተለያዩ እንስሳትንና ተፈጥሮን የሚያሳዩ ስዕሎችን ጨምሮ ልዩ ልዩ የስዕል ስራዎችን ሁለቱን እጆቹን በአንድ ጊዜ በመጠቀም ለማሳል ብዙ አልከበደውም። ኮሊን ይህን በሁለት እጅ በአንድ ጊዜ የመሳል ጥበቡን ሚስጥር ለረጅም ጊዜ ደብቆ ካቆየው በኋላ በአነቃቂ ንግግር ተነሳስቶ የሚሰራቸውን ስዕሎች የሚያሳዩ ፎቶዎችና የቪዲዮ ክሊፖች በኢንስታግራም መልቀቅ ከጀመረ ወዲህ የብዙሃንን ትኩረት ለመሳብ ችሏል። ‹‹የተደረገልኝ ቀና ድጋፍ የስዕል ስራዎቼን ይበልጥ እንድሰራና ችሎታየን እንድጠቀምበት አነሳስቶኛል››ሲልም ተደምጧል። ‹‹በርግጥ የቀኝ እጄ ሲደክም ስዕል ለመስራት የግራ እጄን እጠቀማለሁም›› ብሏል። በአምስት አመቱ ስዕል መሳል የጀመረው ኮሊን ይህን ችሎታውን በመጠቀም በሆሊውድ ፊልም የሚታወቀውን የሃሪ ፖተር ገፀባህሪ፣ ሊዮናርዶ ዳቪንቺን፣ ኮቤ ብሪያንትንና ሩድ ባድረ የተሰኙ ዝነኞችን ከሰራቸው የስዕል ስራዎቹ ውስጥ ይጠቀሳሉ። በእንዲህ አይነቱ ስዕል የመሳል ጥበብ ኮሊን የመጀመሪያው ሰው እንዳልሆነ ዘገባው ገልጾ፣ከዚህ በፊትም ራጃሴና የተሰኘች ኔዘርላዳዊት በሁለት እጆቿ በአንድ ጊዜ ስዕል እንደምትሰራ መዘገቡን አስታውሷል። የስዕል ስራዎቿ በአንዳንድ ወገኖች የውሸት ናቸው በሚል የተፈረጁ ቢሆንም፣ይህን የሚያረጋግጥ ትክለኛ ማስረጃ ግን እስካሁን እንዳልተገኘ ዘገባው አመልክቷል። አዲስ ዘመን መጋቢት 15/ 2012 አስናቀ ፀጋዬ
https://www.press.et/Ama/?p=29017
323
1መዝናኛ
ለአፍሪካ አገራትም ተምሳሌት የሆነው የኢትዮጵያ ስፖርት
ስፖርት
December 8, 2020
9
ብርሃን ፈይሳየአፍሪካ ብሔራዊ ኦሊምፒክ ኮሚቴዎች ማህበር (አኖካ) የዘንድሮ መዳረሻውን ኢትዮጵያን ማድረጉ ይታወቃል፡፡ በኮሚቴው ምስረታ ከፍተኛ አስተዋጽኦ በነበራትና የአፍሪካ መዲና በሆነችው አዲስ አበባ ከትናንት በስቲያ ጠቅላላ ጉባኤውን ከማካሄዱም ባሻገር ለኢ.ፌ.ዴ.ሪ. ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድም በአህጉሩ ከፍተኛ የሆነውን የስፖርት የክብር ሽልማት አበርክቷል፡፡ ኮሚቴውና አባላቱ አጠቃላይ የነበራቸውን ቆይታ በተመለከተም የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. ስፖርት ኮሚሽነር ኤሊያስ ሽኩር ለአዲስ ዘመን አብራርተዋል፡፡በመሪዎች ደረጃ ይህንን ሽልማት ያገኙ ጥቂት መሆናቸውን ኮሚሽነሩ ጠቅሰው፤ ይህም ለኢትዮጵያ ስፖርትና ለስፖርቱ ቤተሰቡ ትልቅ የምስራች መሆኑንም ይጠቁማሉ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩን ለሽልማት ሊያበቋቸው የቻሉና አርአያ ሊያደርጓቸው የሚችሉ መነሻዎች መኖራቸውም ያብራራሉ፡፡ እንደ ኮሚሽነሩ ገለፃ፤ በሀገሪቷ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ሥራዎች አብዛኛዎቹ ከስፖርቱ ጋር የተሳሰሩ መሆናቸውን የእንጦጦ ፓርክን በማሳያነት ማንሳት ይቻላል፡፡ አረንጓዴ ልማት ከስፖርት ጋር በእጅጉ የተቆራኘ እንደመሆኑ በየዓመቱ በቢሊዮኖች የሚቆጠሩ ችግኞችን በመትከል ከዚህ ቀደም አስቸጋሪ የነበሩ አካባቢዎችን ማልማትም ሌላኛው መነሻ ነው፡፡ የጃፓን ኦሊምፒክ ኮሚቴ ዝግጅትን ተከትሎ ብሔራዊ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር ባደረገው ውይይት ያገኘው ቀና ምላሽም ሌላው ምክንያት ነው፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ዝግጅቱን በተመለከተ ሁለት አቅጣጫዎችን ያስቀመጡ ሲሆን፤ የመጀመሪያው ዝግጅቱ ቀደም ብሎ እንዲጀመርና ውጤት እንዲመጣ ማመላከታቸው ነው፡፡ የተሻለ ውጤት የሚመዘገብ ከሆነም መንግሥት የሚሰጠውን ማበረታቻ በማስቀመጥ ተነሳሽነትን ሊፈጥሩ ችለዋል፡፡ ሁለተኛው አቅጣጫ ደግሞ ለአንድ ኦሊምፒክ ብቻም ሳይሆን ለቀጣይ ኦሊምፒኮችም መሰረት መጣል ስላለበት የኦሊምፒክ መንደር መገንባት አስፈላጊ ነው፡፡ በመሆኑም ሀብት ማሰባሰብ አስፈላጊ እንደመሆኑ፤ የራሳቸውን አስተዋጽኦ እንደሚያበረክቱ ቃል ገብተዋል፡፡ በሌላ በኩል በርካታ በየክልሉ የተጀመሩ የስፖርት መሰረተ ልማቶችና ግዙፍ ስታዲየሞች ተጠናቀው ሌሎች መጀመር አለባቸው የሚል አቅጣጫም አስቀምጠዋል፡፡ በመሆኑም ከስታዲየሞች ባሻገር የማሰልጠኛ ተቋማትም በዚህ ማዕቀፍ ውስጥ በማስገባት ሁሉም አመራር ትኩረት እንዲሰጠው አድርገዋል፡፡ ለስልጠና፣ ለውድድርና ለሽልማት አስፈላጊው የገንዘብ ድጋፍ በመንግሥት እየተሰጠ በመሆኑ እንዲሁም ስፖርቱን የሚመሩት መንግሥታዊና ህዝባዊ አካላቱ በነፃነት ነገር ግን በመንግሥት መደገፍ ባለባቸው መልክ ማስኬድ መቻሉም ሌላኛው ምክንያት ነው፡፡ እነዚህ ጉዳዮችም ለስፖርቱ ትልቅ ትኩረት መስጠታቸውን የሚያሳይ መሆኑን በመመልከትም የአፍሪካ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ሽልማቱን ሊያበረክት ችሏል፡፡ ለረጅም ጊዜ ዝግጅት ሲደረግበት የቆየውና በአጠቃላይ በአዲስ አበባ የተካሄዱት የአኖካ መርሐ ግብሮች ለኢትዮጵያ ስፖርት ዕድገት እንዲሁም ለአገር ገጽታ ግንባታ አስተዋጽኦ ያላቸው መሆኑንም ኮሚሽነሩ ያመላክታሉ፡፡ ለቀናት ከአፍሪካና ከሌሎች አገራት የተገኙ የስፖርት አመራሮች ከጉባኤው ባሻገር፤ የኮሚቴው ሥራ አስፈፃሚ አባላት ከኢ.ፌ.ዴ.ሪ. ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ እንዲሁም ከኢ.ፌ.ዴ.ሪ. ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ጋር ተወያይተዋል፡፡ በውይይቱም ወቅት ኢትዮጵያ በአህጉር አቀፍ ደረጃ ምን ሚና ነበራት ወደፊትስ የሚኖራት ሚና ምን ይመስላል በሚለው ላይ ማብራሪያ ተሰጥቷል፡፡ ሥራ አስፈፃሚውም ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ስፖርት ተምሳሌት መሆኗን እንዲሁም መንግሥት ለዘርፉ የሚሰጠው የጎላ ድርሻ፣ ህዝባዊና መንግሥታዊ አካሉ በቅንጅት ስፖርቱን የሚመራበት ሁኔታ እንዲሁም ለስፖርት የሚመድበው በጀት ለሌሎች አፍሪካዊያን አገራት ምሳሌ እንደሚሆን መግለፃቸውንም ኮሚሽነሩ አብራርተዋል፡፡ በአዲስ አበባ የተካሄደው ጠቅላላ ጉባኤም ኢትዮጵያ የትኛውንም አህጉርም ሆነ ዓለም አቀፍ ጉባኤ የማስተናገድ አቅምና ብቃት ያላት ሀገር መሆኗን በግልጽ ያሳየ ነበር፡፡ ከዚህ ባሻገር በሀገሪቷ እየተከናወኑ ያሉ እንቅስቃሴዎችን በዘጋቢ ፊልምም ጭምር በማዘጋጀት ለማስረዳት ሙከራ መደረጉንም ኮሚሽነር ኤሊያስ ሽኩር ጠቁመዋል፡፡አዲስ ዘመን ህዳር 29/2012
https://www.press.et/Ama/?p=36968
411
2ስፖርት
እግራችንን እንሰብስብ፤ ቤታችን እንዝጋ!
መዝናኛ
March 29, 2020
39
 የአለም አቀፍ ስጋት የሆነው የኮሮና ቫይረስ ለመከላከል ለሚደረገው ጥንቃቄ እያሳየነው ያለነው ዝግጁነት እንደ ጣሊያን ዋጋ እንዳያስከፍለን እሰጋለሁ። ብዙዎችም ሊመጣ የሚችለውን ችግር ቀድመው በመተንበይ እያስጠነቀቁን ነው። ነገር ግን አፍንጫው ላይ ነጭ ሽንኩርት፣ ሎሚና ጤናዳምን እስከነቅጠሉ አስሮ ከመሳለቅ በዘለለ ንክኪን ለማቆም የደፈረ የለም። ብዙዎቻችን ኮሮና ኢትዮጵያ አይገባም፤ ቢገባም አይጎዳንም የሚል ፌዝ ይዘን እራሳችን እያታለልን ነው። ማታለል ብቻም ሳይሆን ለሚመጣው ሰደድ እሳት ብዙዎችን አሳልፈን እየሰጠን ነው። ኋላ በኮሮና የተያዝኩት በማንነቴነው ምናምን አይሰራም። በሚገርም ሁኔታ ኮሮና የሚባል ነገር እንኳ በኢትዮጵያ በተቀረው የዓለማችን ክፍልም አለ ብሎ የማያምን ብዙ ሰው አለ። አብዛኛው ሕዝብ ደግሞ ኮሮናን ለማስደሰት እስኪመስል ድረስ እስከ አንድ ኪሎ ሜትር ድረስ የሚጮህ የእጅ ሰላምታ ሲለዋወጡ እየተመለከትን ነው። ሌላው ደግሞ ኮሮናን ለመከላከል ከሥራ ቀርቶ ካፌ ሲያሞቅ ይውላል። አንዳንዱ ሥራ አይገባም ነገር ግን በሠራተኞች ማመላለሻ ሰርቪስ ነጠላውን አጣጥፎ ይገባና ቤተክርስቲያን ያሳልፋል። የተቀረው ከመገናኛ እስከ ሜክሲኮ፤ ከአውቶቡስ ተራ እስከ ቃሊቲ ሰው በብዛት የሚሰበሰብበትን እየመረጠ ሲዘዋወር ይውላል። በሽታው ከሚሰራ ሰው ጋር ነው እንዴ ጥሉ? ይህ እኮ አግባብ አይደለም ስትላቸው መልሳቸውና ራሳቸውን የማታለያ መንገዳቸው «ፈጣሪ አለ» የሚል ነው። «ኢትዮጵያ ትፈተናለች እንጂ አትፈርስም። ይህ የአውሮፓውያን ሴራ ነው» ብለው ይመልሳሉ። እኔም አምናለሁ ፈጣሪ ኢትዮጵያን ይጠብቃል። ግን ደግሞ «አትፈታተኑኝ» ብሏል። ክፉ ቀንንና ጥምዝምዝን ማሳለፍ ጎንበስ ብሎ ነው ይባል የለም? ምን ችግር አለው ፈጣሪያችንን እያመንን ቤታችንን ብንዘጋ? ችግሩ ከየትም ይሁን ከየት ማንም ያምጣው ማን የሚጎዳን ከሆነ በመጠንቀቅ ፈንታ ሌሎችን መኮነን አግባብ አይደለም። ቤትን መዝጋት ብዙ ጥቅሞች ይኖሩታል። መጥፎ ከማየትና ክፉ ከመስማት በጥቂቱም ቢሆን ይቆጥበናል። ፈጣሪን መማፀኛ ሰፊ ጊዜም ይኖረናል። ፈጣሪ ሁሌም አለ። ግን ሰዎች በራሳቸው ስህተትና በማያውቁት ነገር ይሞታሉ። እና የሚሞቱ ኢትዮጵያውያን ፈጣሪ አያውቃቸውም ማለት ነው? ብዙ አታስወሩኝ ከፈጣሪዬ ጋር ታጣሉኛላችሁ። አንዳንድ ሰዎችማ ኮሮናን ደስ ለማሰኘት ካላቸው ከፍተኛ ፍላጎት የተነሳ ከተጣሉት ሰው ጋርም ሳይቀር ሰላምታ ሳይለዋወጡ አይቀሩም። እናም እላለሁ እባካችሁ መመሪያ እናክብር። የኤሲያ ሀገራት ለቻይና ቅርብ እንደመሆናቸው በከፍተኛ ሁኔታ የመጠቃት ዕድል ነበራቸው፤ እነሱ ግን የበላይ አካላትንና ሕግን የማክበር ጠንካራ ባህል አላቸው። ይህም ጠቅሟቸዋል። መንግሥት ያወጣውን ሕግ ተግባራዊ ማድረግ በመቻላቸው በሽታው ሳይስፋፋ ብዙም ሳይጎዱ ማለፍ ችለዋል። አያችሁ ቤታቸውን ዘግተው ፈጣሪያቸውን የሚለምኑ እንዲህ ናቸው። እውነት እናውራ ካልን ብልህነት ይህ ነው! ‹‹በአንድ ድንጋይ ሁለት ወፍ›› በቤት ውስጥ ቁጭ ብሎ ከፈጣሪ ጋር መቀራረብ እንዲሁም ከበሽታው መትረፍ። ‹‹ስንቱን አስታወስኩት ስንቱን አሰብኩት ልቤን በትዝታ ወዲያ እየላኩት አንዴ በመከራው አንዴ በደስታየ ስንቱን ያሳየኛል ይሄ ትዝታየ›› አይደል ያለው መሀሙድ አህመድ ። መሀሙድን ትዝታው ብዙ ነገርን እንዳሳየው ሁሉ እኔንም ኮሮና ብዙ ፀባይ ያላቸው ሰዎችን አሳይቶኛል። አንዳንድ ሰዎችማ ግርም እኮ ነው የሚደርጉት በግድ ስለ ኮሮና ብዙ እንድታስብ ያደፋፍሩሃል። ጣሊያን በቫይረሱ በጣም ብዙ ሰዎች ሞቱ ሲባል «ኢትዮጵያ ስለወረረች ነው» ይላሉ። ግብፅ ሦስት ጀነራሎቿንና በርካታ ዜጎቿን በበሽታው መነጠቋ ታውቋል ሲል ዜናው ሰው ቀበል ይልና ማን ኢትዮጵያን ተንኩሽ አላት። የማይገባትን የአባይን ውሃ ለምን ለእኔ ብቻ ልጠቀም አለች?…ሲል ይጠይቅና ቀጠል አድርጎም አያችሁ አይደል ኢትዮጵያን ፈጣሪ ይወዳታል ይላል። በአንድ የቴሌቪዥን መስኮት ደግሞ በአሜሪካ የሟች ቁጥር ከአንድ ሺ በላይ ደረሰ። በቫይረሱም ከ60 ሺ በላይ ሰዎች ተይዘዋል ሲል ወንድሜ ምን ቢል ጥሩ ነው «አይ ትራምፕ በማያገባህ ገብተህ ሕዝብህን አስጨረስክ አይደል» አለ። ዞር አልኩና ምን ማለት ነው ስለው? «ለምን በግድቡ ዙሪያ ከግብጽ በኩል ወገነ። » ሲል ሳልወድ ፈገግ አልኩ። ስለእውነት ከሆነ ይህ የዋህነት ነው። ፈጣሪ የሁሉም እንጂ ጥቂቶች እንደምናስበው አንዱን ደግፎ ሌላውን የሚበቀል አይደለም። ይህ ሁሉ ምክንያት ድርደራ እራስን ማዘናጊያ ነው። ግን ሁሉንም ትተን እንጠንቀቅ፤ መመሪያዎችን እንተግብር። አሁን ራስን መደለል አቁመን ወደ መጠንቀቁ ካልገባን ተያይዘን ማለቃችን ነው። በቦሊቪያ ከአንድ ቤተሰብ ከቤት እንዲወጣ የሚፈቀድለት አንድ ሰው ነው። ይህ የሆነው ወረርሽኙ እንዳይስፋፋ ታስቦ ነው። ደግሞም ሰዎች የሚያስፈልጋቸውን በእዛ ሰው አማካኝነት እንዲያገኙ ነው። በእኛ ሀገርስ ይህ ሕግ ቢተገበር የሚቀበለው ስንቱ ነው? ከእንትና ብሔር ከአንድ ቤተሰብ ሁለት ሰዎች እንዲወጡ ተፈቅዶላቸዋል። የእንትና ሃይማኖት ተከታዮች እንደልባቸው እየተንቀሳቀሱ ነው። እኛ ተከለከልን መብታችን ተነፈገ ብሎ አቤቱታ የሚያቀርብ አይጠፋም። ግን ሁሉም አይሆንም ከሳሽም ተከሳሽም የማይሰማው ኮሮና ቫይረስ ለወሬ ነጋሬ ሳያስቀር እንዳይጨርሰን መጠንቀቁ ይበጃል። በማንነቴና የእንትን ብሔር ተወላጅ በመሆኔ ማለት ኮሮና ላይ ዋጋ የለውም፤ ዋጋ ያስከፍላል እንጂ። እራስን ፃዲቅ ሌላውን ሀጢአተኛ በማድረግ ኮሮናን ማምለጥ አይቻልም። ኮሮና ቫይረስን ማምለጫው ዋና መንገድ የሚሰጡ መመሪያዎችን በትክክል መተግበር መቻል ነው። ከሁሉም በላይ እግራችንን ሰብስበን ደጃፋችንን ዘግተን የኮሮናን ማህበራዊ ተጽዕኖ እንቋቋም።አዲስ ዘመን መጋቢት 20 ቀን 2012 ዓ.ምሞገስ ጸጋዬ
https://www.press.et/Ama/?p=29384
622
1መዝናኛ
ዶክተር ካትሪን ሀምሊን
መዝናኛ
March 29, 2020
61
   • “የኢትዮጵያ እናቶች እናት” በመባል የሚታወቁና የረጅም አመት የማህጸን ሀኪም በመሆን ያገለገሉ ናቸው። •እ.አ.አ በ1924 ሲድኒ አውስትራሊያ ውስጥ ተወለዱ።•እ.አ.አ በ1959 ወደ ኢትዮጵያ ሲመጡ እቅዳቸው ሦስት ሳምንት የመቆየት ብቻ ቢሆንም በርካታ ሴቶች ህክምና እንደሚያስፈልጋቸው በመገንዘብ ከመሄድ ይልቅ መቆየትን መረጡ።•እ.አ.አ በ1974 አዲስ አበባ ውስጥ የመጀመሪያ የሆነውን የፌስቱላ ሆስፒታል አሰሩ።•ይህ ሆስፒታል ከ45 ሺ በላይ ለሆኑ ኢትዮጵያውያን ሴቶችን ከህመም ፈውሶ መደበኛ ህይወታቸውን እንዲመሩ አድርጓል።•ዶክተር ካትሪን ሴቶችን የመርዳት ተግባራቸው ሴቶችን በማከም ብቻ የተገደበ አልነበረም። አዋላጅ ነርሶችን የማሰልጠን ሕልማቸውን ለማሳካት በ2000 ዓ.ም የሐምሊን አዋላጅ ነርሶች ማሰልጠኛ ኮሌጅ እንዲቋቋም በማድረግ በርካታ ባለሙያዎች በየገጠሩ እንዲሰማሩ ማድረግ ችለዋል።•ለ60 አመት በኢትዮጵያ የፌስቱላ ህሙማንን በማከም ሰርተዋል።•ዶክተር ካትሪን ሃምሊን ከግማሽ ክፍለ ዘመን በላይ ያለ እድሜ ጋብቻንና የተራዘመ ምጥን ተከትሎ በሚከሰት ሽንትንና ሰገራን መቆጣጠር ያለመቻል ችግር ይሰቃዩ የነበሩ በርካታ ሺህ ኢትዮጵያዊያንን ሲታደጉ ኖረዋል።•ዶክተር ካትሪን የአዲስ አበባውን ጨምሮ በሃገሪቱ ስድስት የሃምሊን ፌስቱላ ሆስፒታሎችን በማቋቋም ሴቶች ከሚገጥማቸው የፌስቱላ በሽታ በነጻ ታክመው እንዲወጡ ከማድረግ ባሻገር ይደርስባቸው ከነበረ የመገለልና የስነ ልቦና ስብራት መታደግ ላይ ሰርተዋል።• በበጎ ተግባር ላይ ተሰማርተው የበርካታ ኢትዮጵያውያን ሴቶች ችግርን የቀረፉት ዶክተር ካትሪን ሐምሊን የኢትዮጵያ የክብር ዜግነትና ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ደግሞ የክብር ዶክትሬት ተበርክቶላቸዋል።• ዶክተር ካትሪን ሐምሊን በዋጋ ለማይተመነው አበርክቷቸው በርካታ ሽልማቶችንና ክብሮችን ተቀዳጅተዋል። ከነዚህም መካከል• የቀዳማዊ ኃይለስለሴ የሰብአዊነት ሽልማት • የኦርደር ኦፍ አውስትራሊያ ሽልማት• የቀዶ ጥገና ሀኪሞች ኮሌጅ የክብር ወርቅ ሜዳሊያ ሽልማት• የአውስትራሊያ ከፍተኛ ብሄራዊ ሽልማት • አለም አቀፍ የጤና ምክር ቤት የላቀ አፈፃፀም ሽልማት• የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስነ ህዝብ ሽልማት• የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአውስትራሊያ ማኅበር ሽልማት• የሮተሪ ኢንተርናሽናል አለም አቀፍ የሰላም ሽልማት• የእንግሊዝ ህክምና ማህበር ሽልማት• የሲዲኒ ዩኒቨርሲቲ የክብር ዶክትሬት ሽልማት• የአውስትራሊያና ኒው ዚላንድ ጦር ዘማቾች የሰላም ሽልማት• የታላቁ የቅድስ ጊዮርጊስ የላቀ የወርቅ ሜዳሊያ ሽልማት• የዞንታ አለም አቀፍ ሽልማት• የኤደንብራ የቀዶ ጥገና ሐኪሞች ኮሌጅ የክብር ሽልማት• የሰዎች ለሰዎች ድርጅት የህይወት ዘመን ሽልማት• የ2009 ዓ.ም የበጎ ሰው ሽልማት ከብዙ በጥቂቱ ተጠቃሾች ናቸው።• ከነዚህ ሽልማቶች በተጨማሪ ካትሪን ሐምሊን እ.አ.አ የ1999ና የ2004 የኖቤል ሽልማት እጩ ሆነው ቀርበው ነበር።• እ.አ.አ በ2009 ‹‹ተለዋጭ ኖቤል›› በመባል የሚታወቀውና አስቸኳይ ምላሽ ለሚሹ አለም አቀፍ ፈተናዎች ተግባራዊና ተምሳሌታዊ የሆኑ መፍትሔዎችን ላፈለቁ አካላት የሚሰጠው የ‹‹ራይት ላይብሊሁድ ሽልማት ›› ተበርክቶላቸዋል።• ባለፈው ዓመትም ጠቅላይ ሚንስትር ዶክተር አብይ አህመድ ለሀገራችን በተለይም በፊስቱላ የተጠቁ ሴቶችን ከችግራቸው በመፈወስ ለሰሩት ስራ ሽልማት አበርክተውላቸዋል።• ዶክተር ካትሪን ሀምሊን በ96 አመታቸው መጋቢት 14 ቀን 2012 ዓ.ም ከዚህ አለም በሞት ተለይተዋል። ስርዓተ ቀብራቸውም በጳውሎስ ወጴጥሮስ ቤተክርስቲያን ተፈፅሟል።አዲስ ዘመን መጋቢት 20 ቀን 2012 ዓ.ም
https://www.press.et/Ama/?p=29379
361
1መዝናኛ
አንዳንድ እውነታዎች ስለ ታላቁ ህዳሴ ግድብ
መዝናኛ
March 29, 2020
54
 የኢትዮጵያ ታላቁ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ በ2003 ዓ.ም ተጀመረ።• ግድቡ ሲጠናቀቅ ከ 74 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር ውሃ በላይ ቦታ ይይዛል።• የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ለመሙላት የሚወስድባት ጊዜ እስከ ሰባት አመት ነው።• በሚመጣው ክረምት የውሃ ሙሌት ይጀ መራል። •ታህሳስ 2013 ዓ.ም የመጀመሪያዎቹ ሁለት ተርባይኖች ኃይል ማመንጨት ይጀምራሉ። እያንዳንዳቸው የኃይል ማመንጫ ተርባይን 375 ሜጋዋት በጠቅላላው 750 ሜጋ ዋት ኃይል ለማመንጨ ይችላሉ።• በእያንዳንዱ ኢትዮጵያውያን የገንዘብ መዋጮ የሚገነባና የሁሉም ዜጋ አሻራ ያረፈበት ነው። • ግድቡ ሲጠናቀቅ 6ሺህ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል የማመንጨት አቅም ይኖረዋል።• በርካታ ሕዝብ የኤሌክትሪክ ኃይል እንደልብ በማያገኝባት ኢትዮጵያ ግድቡ ሲጠናቀቅ ዘርፈ ብዙ ጥቅሞችን ይሰጣል። • ከዚህ ባለፈም እያደገ ለመጣው የማኑፋ ክቸሪንግ ዘርፍ ትልቅ እፎይታን የሚሰጥ ይሆናል።• ኢትዮጵያ ግድቡ ሙሉ በሙሉ ኃይል ማመንጨት ሲጀምርላት ለጎረቤት ሀገራት ኮረንቲ መሸጥ ትችላለች። በተለይ ደግሞ ሱዳን፣ ደቡብ ሱዳን፣ ኤርትራና ጂቡቲ ከሕዳሴው ግድብ ጥቅም የሚገኙ ሀገሮች ናቸው።• ታላቁ ህዳሴ ግድብ አጠቃላይ የግንባታ ሒደት 72 በመቶ ደርሷል።• በአሁኑ ወቅት የኤሌክትሮ ሜካኒካል ሥራዎቹ ከ42.3 በመቶ በላይ ተጠናቀዋል።•የሲቪል ስትራክቸር የግንባታ ሒደትም ከ20 በመቶ በላይ አፈጻጸም አስመዝግቧል።•መጋቢት 24 ቀን 2012 ዓ.ም ዘጠነኛ አመት የምስረታ በዓሉን ያከብራል።አዲስ ዘመን መጋቢት 20 ቀን 2012 ዓ.ም
https://www.press.et/Ama/?p=29376
168
1መዝናኛ
የብሔራዊ ስታዲየም ሁለተኛ ምዕራፍ ግንባታ ተጀመረ
ስፖርት
July 31, 2020
20
 አዲስ አበባ ቀደምት ከሚባሉ የኢትዮጵያ ከተሞች ተርታ ብትመደበም፣ መጠሪያዋን ስያሜው ያደረገ ብሔራዊ ስታዲየም ሳይኖራት ዓመታት ተቆጥረዋል፡፡ ዘመናዊ ስታዲየምም መመልከት ብርቅ ሆኖባት ዘመናት አልፈዋል:: አንድ ለእናቱ የሆነው የአዲስ አበባ ስታዲየም የዓለም አቀፍ እግር ኳስ ማኅበር (ፊፋ) ለዚህ ወቅት የሚመጥን አይደለም በሚል ማንኛውንም አኅጉራዊም ይሁን ዓለም አቀፋዊ ውድድሮችን እንዳያስተናግድ ክልከላ ጥሎበታል:: በ2008 ዓ.ም. ታህሣሥ ወር ላይ «ሀ»ብሎ የግንባታውን መሠረት የተጣለለት የአደይ አበባ ስታዲየም አንድ ለናቱ የነበረውን የአዲስ አበባ ስታዲየም ን ያሳርፋል የሚል ተስፋ እንዲሰነቅ ያደረገ ነበር። ለአዲስ አበባ ተጨማሪ ውበትና ኩራት ይሆናል ተብሎ የታሰበውና በአዲስ አበባ ቦሌ ክፍለ ከተማ ገርጂ አካባቢ እየተገነባ ያለው ብሄራዊ ስታዲየሙ፤ የሁለተኛ ምዕራፍ ግንባታ አካል የሆነው የስታዲየሙን ጣራ እና የማጠቃለያ ግንባታ የተለያዩ እንግዶች በተገኙበት ከትናንት በስቲያ በይፋ ተጀምሯል።የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ኤልያስ ሽኩር በሥነ ስርዓቱ ላይ ተገኝተው እንደተናገሩት ፤ በሁሉም የሀገራችን ክልልሎች ከ 12 በላይ ስታዲየሞች በመገንባት ላይ ይገኛሉ ። በአዲስ አበባ እየተገነባ ያለው ግዙፍ አደይ አበባ ስታዲየም ከዚህ ውስጥ አንዱና ዋነኛው ሲሆን ፤ስታዲየሙ ሙሉ ለሙሉ ሲጠናቀቅ ለኢትዮጵያ የእግር ኳስ ተመልካች ትልቅ ብስራት እንደሚሆን ገልጸዋል። የብሔራዊ ስታዲየም ሁለተኛው ምዕራፍ ግንባታ ስፖርት ኮሚሽን ከተቋራጩ የቻይና ስቴት ኮንስትራክሽን ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን ጋር ከወራቶች በፊት በተደረገው ስምምነት መሠረት በታቀደለት ጊዜ ጥራቱን ጠብቆ መጠናቀቅ ይችል ዘንድ አስፈላጊው ክትትልና ቁጥጥር እንደሚደረግ ኮሚሽኑ አስታውቋል፡፡የቻይና ስቴት ኮንስትራክሽን ኢንጂነሪንግ ማኔጂንግ ዳይሬክተር ሚስተር ሚንግ ቾ በበኩላቸው ፤ኩባንያው ግዙፍ ፕሮጀክቶችን በመስራት ከፍተኛ ልምድ ያለው መሆኑን ጠቅሰው የዓለም አቀፍ ስጋት የሆነው የኮሮና ቫይረስ በመቋቋም ስታዲየሙን በተያዘለት ጊዜ ለማጠናቀቅ እንደሚሰሩ አመልክተዋል።«በአሁን ሰዓት የካፍ እና የፊፋን መስፈርት ያሟላ ኢንተርናሽናል ጨዋታዎችን ማስተናገድ የሚያስችል ስታዲየም የለም»ያሉት ደግሞ የኢትዮጵያ እግር ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት አቶ ኢሳያስ ጅራ፤ የአደይ አበባ ስታዲየም የዓለም ዋንጫ ፍፃሜን ማስተናገድ የሚያስችል ስታዲየም እየተገነባ መሆኑን ትልቅ ደስታ እንደፈጠረላቸው ገልጸዋል። የአደይ አበባ ስታዲየም የሁለተኛው ምዕራፍ ግንባታ 900 ቀናት እንደሚፈጅ ተነግሯል ። ለስታዲየሙ መዋቅራዊ ይዘት (የመጀመርያ ምዕራፍ) ግንባታ 2.7 ቢሊዮን ብር ወጪ ተደርጎበታል፣ ለቀሪው ግንባታ ደግሞ 5 ነጥብ 57 ቢሊዮን ብር ያስፈልገዋል ተብሏል:: በስምምነቱ መሠረት ተቋራጩ የተረከባቸው ዝርዝር ሳይቶች ስታዲየሙን ሳር የማልበስ ሥራና የመሮጪያ ትራክ፣ የመገናኛ ብዙኃን ቦታና የጋዜጣዊ መግለጫ ክፍሎች፣ የተለያዩ መሰብሰቢያ አዳራሾችና የቪአይቪ ማረፊያ ክፍሎችና መቀመጫ ወንበሮች፣ አሳንሳሮች፣ ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ የካፌና የሬስቶራንቶች ክፍሎች፣ ለሁለቱም ፆታ አገልግሎት የሚሰጡ መፀዳጃ ክፍሎች፣ የፍሳሽ ማስወገጃና የኤሌክትሪክ መስመሮች፣ የተለያዩ ሰው ሠራሽ ሐይቆች፣ ለአደጋ ጊዜ የሔሊኮፕተር ማረፊያና ዘመናዊ የደኅንነት ካሜራዎች እንዲሁም የሳውድ ሲስተም ገጠማ፣ ቡድኖች ከጨዋታ የሚለማመዱባቸው የተለያዩ ሜዳዎችና የፓርኪንግ አገልግሎት መስጫ የሚውሉ ቦታዎች እንዲሁም ብሔራዊ ስታዲየሙ ከጨዋታ በኋላ ተመልካቾችን ጨምሮ ተሽከርካሪዎች ከአሥር እስከ አሥራ አምስት ባለው ደቂቃ ውስጥ አካባቢውን ለቀው መንቀሳቀስ የሚችሉባቸው መንገዶች ተከተዋል፡፡ ዓለም አቀፍ ደረጃውን ጠብቆ እየተገነባ የሚገኘው የአደይ አበባ ስታዲየም አራት ዋና ዋና በሮች ሲኖሩት፣ በወንበር 62 ሺህ ተመልካቾችን የማስተናገድ አቅም ይኖረዋል፡፡ ለክብር እንግዶች (ቪአይፒ) እና ለሚዲያ አባላት 2 ሺህ ወንበሮችን መያዙን ታውቋል። በቻይና ስቴት ኮንስትራክሽን ኢንጂነሪን ኮርፖሬሽን እየተገነባ የሚገኘውና በውጭ ምንዛሪና መሰል ችግሮች የፕሮጀክቱ የመጠናቀቂያ ጊዜ መጓተቱ ይታወሳል።አዲስ ዘመን ሐምሌ 24/2012 ዳንኤል ዘነበ
https://www.press.et/Ama/?p=36398
431
2ስፖርት
መልስ ያላገኘው የአፍሪካውያን የአገር አቋራጭ ሩጫ ጥያቄ
ስፖርት
July 30, 2020
18
አትሌቲክስን ፈታኝ ስፖርት ከሚያደርጉት ውድድሮች አንዱና ዋነኛው የአገር አቋራጭ ሩጫ ነው። የአገር አቋራጭ ውድድር አትሌቲክስን ፈታኝ ብቻም ሳይሆን ተወዳጅና ቀልብ ሳቢ ካደረጉት ምክኒያቶች አንዱ ነው ቢባል ስህተት አይሆንም። በገባ ወጣ መልክዓምድር፤ ኮረብታና ቁልቁለት እንዲሁም በጭቃና አልፎ አልፎም በበረዶ ክምር መሰናክሎች የታጀበው ይህ ውድድር አትሌቶች ከመምና ከጎዳና ላይ ውድድሮች ወጥተው ራሳቸውን በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የሚፈትኑበት ነው።የአገር አቋራጭ ሩጫ የምስራቅ አፍሪካውያን የበላይነት እየገዘፈበት ከመጣ ጀምሮ ግን ተወዳጅነቱ እየቀነሰ የሚሰጠውም ትኩረት እያነሰ መጥቷል። ይህም ከአውራው የስፖርት መድረክ ኦሊምፒክ እንዲወጣ ከማድረጉ ባሻገር በአፍሪካውያን ላይ የፈጠረው ተጽዕኖ በቀላል የሚታይ አይደለም። የዓለም አገር አቋራጭ ቻምፒዮና በየሁለት ዓመቱ ራሱን ችሎ የሚካሄድ ቢሆንም በዋናው የዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮናም ውጪ ነው። የቀድሞው የዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር የአሁኑ የዓለም አትሌቲክስ በእንግሊዛዊው የቀድሞ የአንድ ሺ አምስት መቶ ሜትር ኮከብ አትሌት ሴባስቲያን ኮ ፕሬዚዳንትነት መመራት ከጀመረ ወዲህ ውድድሩን ወደ ኦሊምፒክ ለመመለስ እንቅስቃሴ መጀመሩ ይታወቃል።የአገር አቋራጭ ሩጫን ወደ ኦሊምፒክ የመመለስ እንቅስቃሴ አሁን የተጀመረ ባይሆንም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ጠንከር ያሉ እርምጃዎች እየተወሰዱ ይገኛሉ። ከዓመት በፊት በአርጀንቲና ቦነ ሳይረስ በተካሄደው የወጣቶች ኦሊምፒክ ጨዋታ ላይ እንዲካተት መደረጉ አንድ ርምጃ እንደነበር ቢታወስም የአፍሪካውያን ጥያቄ አሁንም ድረስ መልስ አላገኘም።የአገር አቋራጭ ሩጫ ለመጨረሻ ጊዜ በኦሊምፒክ መድረክ የተካሄደው እኤአ በ1924 የፓሪስ ኦሊምፒክ ነበር። ቦነ ሳይረስ በወጣቶች የኦሊምፒክ ጨዋታም ቢሆን ይህን ውድድር ከዘመናት በኋላ በአዲስ መልኩ የማዘጋጀቱን እድል አግኝታለች። በዚህ የወጣቶች ኦሊምፒክ የመካከለኛ ርቀት አትሌቶች በተለይም አንድ ሺ አምስት መቶ ሜትር፤ ሦስት ሺ ሜትርና ሁለት ሺ ሜትር መሰናክል ተወዳዳሪዎች የማጣሪያ ውድድር በማድረግ በሁለቱም ፆታ አርባ ስምንት አርባ ስምንት አትሌቶች ተፎካክረውበታል፡፡ ይህም ጅምር አገር አቋራጭ ሩጫ በዋናው የኦሊምፒክ ውድድር እንዲካተት ትልቅ መሰረት ይሆናል ተብሎ ታምኖበታል። የዓለም አትሌቲክስ ፕሬዚዳንት ሴባስቲያን ኮ« የአገር አቋራጭ ሩጫን በኦሊምፒክ መድረክ ማየት የረጅም ጊዜ ፍላጎታችን ነው፤ በቦነ ሳይረስ የወጣቶች ኦሊምፒክ መካተቱም በዋናው ኦሊምፒክ ለማካተት የሚደረገውን ጥረት ያጠናክራል» በማለት ከዓመት በፊት አስተያየት መስጠታቸውን ተከትሎም ትልቅ ተስፋ ታይቶ ነበር። ሴባስቲያን ኮ አገር አቋራጭ ሩጫ በተለይም የመካከለኛ ርቀት አትሌቶች አካል ብቃት የሚታይበት በመሆኑ በኦሊምፒክ መድረክ መካተት እንደሚገባው ፅኑ እምነት አላቸው። በዚህ አቋማቸው መፅናታቸውን ግን እርግጠኛ መሆን አይቻልም፡፡የአገር አቋራጭ ሩጫ በዋናው ኦሊምፒክ መድረክ እኤአ ከ1912 እስከ 1924 በወንዶች መካከል ብቻ ተካሂዶ ነው የተቋረጠው። ከዚህ በኋላ ግን የኦሊምፒክ መርሐግብር መሆኑ ቀርቶ የአትሌቲክስ ጉዳይ ብቻ ሆኖ ቀርቷል። ለዚህ ብዙ ምክኒያቶች በተለያዩ ጊዜዎች የሚቀርቡ ሲሆን ለመጨረሻ ጊዜ በተካሄደው የፓሪስ ኦሊምፒክ ላይ በርካታ አትሌቶች ውድድሩ ከብዷቸው ሲፍረከረኩና ራሳቸውን ሲስቱ ጭምር ነበር። ይሁን እንጂ አገር አቋራጭ ሩጫ በተካሄዱባቸው ሦስት ኦሊምፒኮች የፊንላንድ አትሌቶች የበላይነት እንደነበር በታሪክ ተጽፎ ይገኛል። ከዚህ በኋላ የተፈጠረው የአትሌቲክስ ትውልድ በተለይም በረጅምና መካከለኛ ርቀቶች የአፍሪካውያን የበላይነት እየጎላ የመጣበት እንደመሆኑ በአገር አቋራጭ የዓለም ቻምፒዮናዎችም ይሁን በግል አፍሪካውያን የበላይነቱን ተቆጣጥረውታል። ይህም አገር አቋራጭ ሩጫ ወደ ኦሊምፒክ እንዲመለስ የሚደረገውን ሂደት እንዳዘገየው የሚያምኑ በርካቶች ናቸው። አፍሪካውያን ይህ ውድድር ወደ ኦሊምፒክ እንዲመለስ ብዙ ጊዜ ታግለዋል። ጀግናው አትሌት ኃይሌ ገብረስላሴ፤ የመም ውድድሮችና የአገር አቋራጭ ውድድሮች ንጉሱ አትሌት ቀነኒሳ በቀለና የኬንያው ታሪካዊ አትሌት ፖል ቴርጋት አገር አቋራጭ ውድድር ወደ ኦሊምፒክ እንዲመለስ ትግል ካደረጉት መካከል ይጠቀሳሉ። በተለይም እነዚህ ሦስት ድንቅ የምስራቅ አፍሪካ የምን ጊዜም ኮከብ አትሌቶች እኤአ 2008 ላይ ለወቅቱ የዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ፕሬዚዳንት ጃኩዌስ ሮግ በአንድ ላይ ጥያቄ አቅርበው እንደነበር ይታወሳል። ይህን ሃሳብ የዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበርና በርካታ ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን የደገፉት ቢሆንም ተግባራዊ ሳይሆን ዘመናትን ተሻግሯል።አገር አቋራጭ በኦሊምፒክ መካተት አይኖርበትም የሚሉ ሃሳቦች በብዛት ከምዕራባውያን ዘንድ ሲነሳ ይሰማል። ለዚህም የተለያዩ መላ ምቶችን ያስቀምጣሉ። በዋናነት አገር አቋራጭ ሩጫ የክረምት ኦሊምፒክ ስፖርት እንጂ የበጋ ኦሊምፒክ ስፖርት አይደለም የሚሉ በርካታ ናቸው። አገር አቋራጭ ሩጫ በተለምዶ ከአስር እስከ አስራ ሁለት ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ሲሆን በበጋ ኦሊምፒክ ወቅት መካሄዱ እኤአ በ1924 ላይ አትሌቶች እንደተፍረከረኩት አይነት ችግር ይፈጠራል ወይንም የአየር ብክለት ሊኖር ይችላል የሚል ሃሳብም በስፋት ይነሳል። በሌላ በኩል የመም ውድድሮችና ማራቶን በኦሊምፒክ ስለ ተካተተ አገር አቋራጭ ሩጫ አያስፈልግም ወይንም የሚፈጀው ጊዜ ረጅም ስለሆነ አያስፈልግም የሚሉ ሃሳቦች ሲንፀባረቁ ይስተዋላል። አገር አቋራጭ ሩጫ በኦሊምፒክ መካተት የለበትም የሚሉት ወገኖች ከነዚህ የበለጠ ጠንካራ የመከራከሪያ ሃሳብ ይዘው ሲቀርቡ አይታዩም። እነዚህ የመከራከሪያ ነጥቦች ቢሆኑም በራሳቸው ምክኒያታዊና አሳማኝ ናቸው ተብሎ አይታሰብም። ለምሳሌ ያህል ዋነኛ ምክኒያት የሆነው አገር አቋራጭ ሩጫ የክረምት ኦሊምፒክ ውድድር ነው መሆን ያለበት የሚለው ሃሳብ ከምዕራባውያን ጥቅም ጋር የተያያዘ ስለመሆኑ ማመላከት ይቻላል። አገር አቋራጭ ሩጫ በበጋ ኦሊምፒክ መካሄዱ የአየር ብክለት ሊኖር ይችላል ወይንም ከፍተኛ ሙቀት ይኖራል የሚለው ስጋት በራሱ የኦሊምፒክ አዘጋጅነት ከምዕራባውያን አይወጣም የሚል አንድምታ አለው። በእርግጥ ኦሊምፒክን ከዚህ ቀደም የሚያዘጋጁት አቅም ያላቸው አገራት አብዛኞቹ ምዕራባውያን ቢሆኑም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ወደ ደቡብ አሜሪካና ሌሎች የኤሽያ አገራት እየሄደ ነው። ለዚህም ያለፈውን የሪዮ ኦሊምፒክና መጪውን የቶኪዮ ኦሊምፒክ መጥቀስ በቂ ነው። ከዚህ በኋላም ቢሆን የዓለም ዋንጫን የማስተናገድ አቅም እንዳላቸው ያሳዩ አፍሪካ አገራት እድሉን ያገኛሉ ተብሎ ይጠበቃል። ከዚህ በተጨማሪ ምዕራባውያን በጋ ብለው በሚጠሩት ወቅት የክረምት ወራትን የሚያስተናግዱ አገሮች ኦሊምፒክን ሊያዘጋጁ እንደሚችሉ ልብ መባል አለበት። ከዚህ ጎን ለጎን ውድድሩ ረጅምና አድካሚ በመሆኑ በበጋ ወራት አይመችም የሚለው ሃሳብ በራሱ አርባ ሁለት ኪሎ ሜትር የሚሸፍን የማራቶን ውድድር በበጋ ኢሊምፒክ መኖሩን ልብ ያለው አይመስልም።ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ይህ ሃሳብ ሰፊ እንቅስቃሴ እየተደረገበት የሚገኝ ቢሆንም አሁንም ጠንከር ያለ ግፊት ያስፈልገዋል። አዲስ ዘመን ከሁለት ዓመት በፊት በዚሁ ጉዳይ ላይ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን አመራሮችን አነጋግሮ ጉዳዩን በቅርበት እየተከታተሉ በተገኘው አጋጣሚ ጥያቄ እያቀረቡ እንደሚገኙ ምላሽ መስጠታቸው ይታወሳል። ይህን ሃሳብ አሁንም አጠናክረው ይቀጥላሉ ተብሎ ይጠበቃል። ይህ ጉዳይ የበለጠ አፍሪካውያንን ተጠቃሚ የሚያደርግ በመሆኑ የአፍሪካ አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር (ሲ ኤኤ)፤ የአፍሪካ ኦሊምፒክ ኮሚቴ(አኖካ)፤ የአፍሪካ ተጽዕኖ ፈጣሪ መገናኛ ብዙሃንና ጋዜጠኞች ግፊት ማድረግ አለባቸው ተብሎ ይታመናል። የዓለም አትሌቲክስ ፕሬዚዳንት ሴባስቲያን ኮ ምዕራባዊ ቢሆኑም በአትሌቲክሱ ያሳለፉ በመሆናቸው አገር አቋራጭ ሩጫ ወደ ኦሊምፒክ እንዲመለስ ጥረት እያደረጉ ነው። ይሁን እንጂ በዚህ ውድድር የአፍሪካውያን ብቻ የበላይነት የሚጎላ በመሆኑ ምዕባራውያን ወደ ኦሊምፒክ እንዲመጣ ፍላጎት አላቸው ማለት ይከብዳል።በኦሊምፒክ መድረክ አሜሪካና ምዕራባውያን በርካታ ሜዳሊያ በመሰብሰብ የበላይነት ይዘው የሚያጠናቅቁት በአንድ ስፖርት አይነት ብቻ ከአስር በላይ ሜዳሊያ መሰብሰብ የሚያስችላቸው እድል ስላላቸው ነው። ለዚህም በውሃ ዋና ውድድር አንድ አትሌት ብቻ ከአስር በላይ የወርቅ ሜዳሊያ የሚያፍስበት አጋጣሚ እንዳለ ማስቀመጥ ይቻላል። ምዕራባውያኑ እንዲህ አይነቱ አጋጣሚ በኦሊምፒክ እንዲስፋፋና የበላይነታቸውን ይዘው እንዲዘልቁ ያገኙትን እድል ይጠቀማሉ። አሁንም በቀጣዩ የቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ እንኳን የነሱ ፍላጎት ያለባቸው በርካታ ስፖርቶች እንዲካተቱ ማድረግ ችለዋል። አፍሪካውያንም ከምዕራባውያን ጋር በኦሊምፒክ ተፎካካሪ ሆነው ለመገኘት እንደ አገር አቋራጭ ሩጫ አይነቶችን ሊጠቀሙ ይገባል። አገር አቋራጭ ሩጫ በኦሊምፒክ ቢካተት በውድድሩ አፍሪካውያን የበላይነት ስላላቸው በኦሊምፒክ የሚያገኙት የሜዳሊያ ቁጥርም ከፍ ሊል እንደሚችል ግልፅ ነው።አዲስ ዘመን ሐምሌ 23/2012ቦጋለ አበበ
https://www.press.et/Ama/?p=36334
944
2ስፖርት
የግመሎቹን ቅስም እስከ ወዲያኛው የሰበረው የዓለም ዋንጫ ክስተት
ስፖርት
August 2, 2020
26
የ1982 የዓለም ዋንጫ ለኤሽያዊቷ አገር ኩዌት የእግር ኳሷ ወርቃማ ዘመን ሆኖ ይታወሳል። የዓለም ዋንጫ በመጣ ቁጥር ግን ይህ የኩዌት ወርቃማ የእግር ኳስ ዘመን ሲታወስ አይታይም። እግር ኳስ በተለያዩ ቴክኖሎጂዎች እየረቀቀ ሲመጣ፤ በይነ መረብ ዓለምን ሲያቀራርብና ቀጥታ የቴሌቪዥን ስርጭቶች እንደ ልብ እየሆኑ ሲመጡ እኤአ ከ199oዎቹ ጀምሮ በዓለም ዋንጫ የታዩ ወርቃማ ብሔራዊ ቡድኖች፤ በርካታ ከዋክብቶችና አይረሴ አጋጣሚዎች አሁንም ድረስ በእግር ኳስ አፍቃሪው ዘንድ ይታወሳሉ። ያም ሆኖ ከ1978 የዓለም ዋንጫ አስቀድሞ ከጣሊያንና አርጀንቲና ውጪ ያሉ የእግር ኳስ አፍቃሪዎች ዘንድ ፓውሎ ሮሲና ማሪዮ ኮምፐስን የመሳሰሉ ተጫዋቾች ትልቅ እውቅና ነበራቸው። ከዚህ የዓለም ዋንጫ በኋላም መረጃዎች እንደ ልብ በሌሉበት ዘመን የዲያጎ አርማንዶ ማራዶና ለመጀመሪያ ጊዜ ለአርጀንቲና ተሰልፎ ቤልጂየምን እስከ ገጠመበት ጨዋታ በበርካታ የዓለማችን እግር ኳስ አፍቃሪዎች በቴሌቪዥን መስኮት የመመልከት እድላቸው ጠባብ ቢሆንም ስምና ዝናው ይታወቅ ነበር።የዓለም ዋንጫ አይረሴዎቹ ኮከቦች ሚካዔል ላውድሩፕ፤ ህሪስቶ ስቶቺኮቭ፤ ጂዮርጅ ሃጂና ሌሎችም የጀገኑበት ዘመን ሩቅ ቢሆንም የዓለም ዋንጫ በመጣ ቁጥር ሳይታወሱ የማይታለፉበት ታሪክ አኑረዋል። በተመሳሳይ በብሔራዊ ቡድን ደረጃም የ1966 የሰሜን ኮሪያ፤ በ1982 የአልጄሪያና በ199o የካሜሩን ብሔራዊ ቡድኖች የሚዘነጉ አይደሉም። የኩዌት የ1982 ብሔራዊ ቡድንም ከነዚህ ብሔራዊ ቡድኖች እኩል የሚታወስ ነው። በዛሬው የስፖርት ማህደር አምዳችንም ይህን ብሔራዊ ቡድን ለማስታወስ ወደድን፡፡የ1982 የስፔን የዓለም ዋንጫ የኤሽያን እግር ኳስ አንገት ቀና ያደረገ ድንቅ የብሔራዊ ቡድን ስብስብ ከኤሽያ አልፎ በመካከለኛው ምስራቅና የገልፍ አገራት እግር ኳስ ላይ ትልቅ መነቃቃትን ፈጥሮ ነበር። ይህ ከ197o መጀመሪያ እስከ 198oዎቹ መጀመሪያ ላይ ትልቅ የእግር ኳስ አብዮት የፈጠረ የኩዌት ወርቃማ የእግር ኳስ ትውልድ ኤሽያ እስካሁንም መልሳ ያላየችው ስብስብ ይዞ ነበር። ከ1976 እስከ 1978 በታሪካዊው ብራዚላዊ ማሪዮ ዛጋሎ እንዲሁም ከ1978 እስከ 1982 በሌላኛው ብራዚላዊ ካርሎስ አልቤርቶ ፔሬራ እየሰለጠነ ዓለምን ጉድ ያሰኘ የብሔራዊ ቡድን ስብስብ በድንቅ ባለ ተሰጥኦ ተጫዋቾች የተሞላም ነበር። ከግብ ጠባቂው አህመድ ታራቡልሲ አንስቶ እስከ አብዱላዚዝ አል አንባሪ፤ አህመድ አቡ ሐማድና ግብ አፈንፋኙ ጃሴም ያቆብ እንዲሁም አምበሉ ሳድ አል ሆቲና ፋሳል አል ዳክሂል ድረስ በከዋክብት የተሞላው የኩዌት ብሔራዊ ቡድን ስብስብ ከእግር ኳስ በላይም ትልቅ ፖለቲካዊና ማህበራዊ ተጽዕኖዎች ነበሩት። ይህ ስብስብ በዓለም እግር ኳስ ላይም በትልቅ ደረጃ ተፅዕኖ መፍጠር የቻለ የመጀመሪያው የገልፍ አገራት ብሔራዊ ቡድን ሆኖ ይታወሳል።የኩዌት ወርቃማ የእግር ኳስ ትውልድ በአንድ ጊዜ ተፈጥሮ በዓለም እግር ኳስ ላይ ድንገት ተፅዕኖ የፈጠረ ሳይሆን በሂደት እየተገነባ የመጣ ነው። ለዚህም በኤሽያና በገልፍ አገራት የእግር ኳስ ቻምፒዮና ሃያል የሆኑትን እንደ ኢራን አይነት አስደናቂ የቡድን ስብስብ ያላቸውን አገራት በሂደት አሸንፎ ዋንጫ በማንሳት ነው። ከዚህ በዘለለም ለ198o የሞስኮ ኦሊምፒክ አልፎ እስከ ሩብ ፍፃሜ ድረስ በመጓዝ በርካቶችን አሳምኖ ነው ወደ ዓለም ዋንጫ ማጣሪያ የመጣው።በኤስያ አገራት የዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታዎች ኩዌት ኒውዘላንድ፤ ቻይናና ሳውዲ ዓረቢያ ከሚገኙበት ምድብ በፔሬራ አሰልጣኝነት እየተመራች በቀላሉ ወደ 1982 የዓለም ዋንጫ ማምራት ችላለች። እንደ አጋጣሚ ሆኖ ግን ኩዌት በዓለም ዋንጫው ጠንካራ በሚባል ምድብ ውስጥ ተደለደለች። ይሁን እንጂ በቡድኑ ውስጥ የነበረው ጠንካራ ስነ ልቦና ጠንካራውን ምድብ አልፈው ወደ ጥሎ ማለፍ እንደሚገቡ ትልቅ ተስፋ የሰጠ ነበር።«ግመሎቹ» በሚል ቅጽል ስም የሚታወቀው የኩዌት ብሔራዊ ቡድን የመጀመሪያቸው በሆነው የዓለም ዋንጫ በምድብ ድልድሉ ከሦስቱ አውሮፓውያን አገራት ቺኮስላቫኪያ፤ ፈረንሳይና እንግሊዝ ጋር ነበር የተደለደሉት። ይህ ምድብ ከቺኮስላቫኪያ በስተቀር ፈረንሳይና እንግሊዝ ያላቸው ትልቅ ስም ለግመሎቹ ስጋት ቢሆንም የፔሬራ ልጆች ወደ ቀጣዩ ዙር የማለፍ ትልቅ ተስፋን ሰንቀው ነበር። በተለይም በመጀመሪያው የቺኮስላቫኪያ ጨዋታ ሙሉ ሦስት ነጥብ ይዘው ለመውጣት ግምት የተሰጣቸው ቢሆንም ጨዋታው አንድ ለአንድ በሆነ አቻ ውጤት መጠናቀቁ ያልተጠበቀ ነበር። ይሁን እንጂ ጠንካራዋ ፈረንሳይ በእንግሊዝ ሦስት ለአንድ መሸነፏን ተከትሎ ግመሎቹ ወደ ቀጣዩ ዙር የማለፍ ተስፋቸው እንደገና ነብስ ዘራበት። ያም ሆኖ በሁለተኛው የምድብ ጨዋታ ሚሼል ፕላቲኒ፤ አሊያን ጊረስና ጄን ቲጋና ለፈረንሳይ ግቦችን አስቆጥረው ፈረንሳይ በቀላሉ መምራት ቢችሉም ግመሎቹ ወደ ጨዋታው ተመልሰው ወይ ለማሸነፍ ወይንም የአቻ ውጤት ይዘው ለመውጣት ተስፋ አልቆረጡም። በዚህም ፈረንሳይን ተጭነው በመጫወት በአብዱላህ አል ቦኑሺ የግንባር ኳስ ሦስት ለአንድ መሆን ቻሉ። ይህም ተነሳሽነታቸውን ጨምሮ ሌላ ግብ ለማስቆጠር ጥረት በሚያደርጉበት ሰዓት አንድ ተስፋ አስቆራጭ ክስተት ተፈጠረ። ይህም አለን ጊረስ ከጨዋታ ውጪ የሆነ ግብ ኩዌት ላይ አስቆጥሮ ዳኛው ይሽሩታል ተብሎ ሲጠበቅ ማፅደቃቸው ነበር።ይህች ቅፅበት ግመሎቹን ተስፋ ከማስቆረጧም በላይ በወቅቱም የኩዌት ተጫዋቾች ውሳኔውን በመቃወም ጨዋታውን ሳይጨርሱ ሜዳውን ለቀው ወጥተዋል። በወቅቱ የኩዌቱ ኤሚር ወንድምና የአገሪቱ የእግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት የነበሩት ሼክ ፋሃድ አል አህመድ አል ጃበር አል ሳባህ ከክብር ወንበራቸው ተነስተው ወደ ሜዳ በመግባት በዳኛው ውሳኔ ላይ ያላቸውን ቅሬታ ከተጫዋቾቹ ጋር የገለፁበት አጋጣሚ አይረሳም። በዚህም ዳኛው አሁንም ድረስ የዓለም ዋንጫ አስገራሚ ክስተት ተብሎ እንዲታወስ ያደረገውን አጋጣሚ ያፀደቁትን ግብ በመሻር ጨዋታው እንደገና እንዲጀመር ማድረጋቸው ነበር። ያም ሆኖ ግን ግመሎቹ ወደ ጨዋታው ቢመለሱም ወደ ቀድሞው ተነሳሽነታቸው ሳይመለሱ ቀርተው ፈረንሳይ በመጨረሻ ሰዓት ሌላ ግብ አስቆጥራ አራት ለአንድ ማሸነፍ ቻለች። ከዚህም ቅፅበት በኋላ የኩዌት እግር ኳስ የተሰበረ ቅስም አሁንም ድረስ ሳይጠገን ደብዛው ሊጠፋ ችሏል።የ1982 የስፔን የዓለም ዋንጫ ለኩዌት እግር ኳስ ወርቃማ ዘመን እንደመሆኑ መጠን ደብዛው የጠፋበት አጋጣሚም ሆኖ ይታወሳል። አብዛኞቹ የኩዌት ተጫዋቾች እድሜያቸው የገፋ እንደመሆኑ ከዚያ የዓለም ዋንጫ በኋላ ሌላ ተዓምር ሳያሳዩ ጫማቸውን ለመስቀል ተገደዋል። በእርግጥ የተወሰኑ ተጫዋቾች ከዚያም ወዲያ የተወሰኑ ዓመታትን ተጫውተዋል። እነዚህ ተጫዋቾች ከዓለም ዋንጫው በኋላ በገልፍ አገራት ቻምፒዮና እኤአ 1986ና 1990 ላይ ዋንጫ ማንሳት ቢችሉም ኩዌት የዓለም ዋንጫ ማጣሪያን ለማለፍ የተቃረበችበት ወቅት እንኳን አልተከሰተም። ከዚህም በኋላ እኤአ በ1990 ኩዌት በኢራቅ የተወረረችበትና ቀጥሎም የገልፍ አገራት ጦርነት የተከሰተበት አጋጣሚ የአገሪቱን እግር ኳስ ከተነቃቃበት ወደ ገደል ገፍትሮታል። በፖለቲካ ጣልቃ ገብነት ብሔራዊ ቡድኑ በተደጋጋሚ በፊፋ እገዳ እየተጣለበትም ከድጡ ወደ ማጡ ሲገባ ታይቷል። የኩዌት እግር ኳስ አፍቃሪዎችም የወርቃማ ትውልዳቸው ከዋክብቶችን አል ዳክሂል፤ ያቆብ እንዲሁም አል አንባሪን በማስታወስ የዓለም ዋንጫ በመጣ ቁጥር ይደሰታሉ።አዲስ ዘመን ሐምሌ 26/2012  ቦጋለ አበበ
https://www.press.et/Ama/?p=36497
808
2ስፖርት
የስፖርት ማህበራትን ለመከለስ መመሪያ እየተዘጋጀ ነው
ስፖርት
August 1, 2020
9
ዘመናዊ ስፖርት ወደ ኢትዮጵያ ከገባ አንድ ምዕተ ዓመት ሊያስቆጥር መቃረቡን ሰነዶች ያሳያሉ። ይሁን እንጂ ስፖርት በኢትዮጵያ በዕድሜው ልክ እንዲሁም ከዓለም ነባራዊ ሁኔታ አንጻር መድረስ ካለበት ስፍራ እንዳልደረሰ አፍን ሞልቶ መናገር ይቻላል። ስፖርት የአንድ ሀገር እድገት መለኪያ ከሆኑ ጉዳዮች አንዱ ቢሆንም፤ በኢትዮጵያ የህዝቡን ጥቅምና ፍላጎት አስጠብቋል ለማለት አያስደፍርም። ለስፖርቱ እድገትም ሆነ መዳከም ድርሻ ያላቸው የተለያዩ ምክንያቶች ቢኖሩም ስፖርቱን የሚመሩ አካላት ጥንካሬና ብቃት ግን ወሳኝነት እንዳለው ይታመናል። ይሁን እንጂ እስካሁንም ድረስ በዚህ አቅጣጫ ሳይሆን በራሳቸው ጥረት የተሻለ ብቃት ያሳዩትን ስፖርተኞች በውድድር ላይ ማሳተፍ ላይ ያተኮረ አካሄድ እየተተገበረ ይገኛል። ስፖርትን ለልማት ከማዋል ይልቅ ውድድሮችን ብቻ ኢላማ ያደረገ አካሄድም ስፖርቱ በሚፈለገው ልክ እንዳያድግ ያደረገ ገፊ ምክንያት ሆኖ በተደጋጋሚ ይነሳል። የአገራችን ስፖርት ከየት ተነስቶ ወደ የት ማምራት እንዳለበት የሚያሳይ የስፖርት ፖሊሲ አቅጣጫ በ1990 ዓ.ም ተቀርጿል። ነገር ግን በፖሊሲው በተቀመጠው ልክ በተጨባጭ ስኬታማ የሆነ ሂደት ባለማሳየቱ በአሰራሩ ላይ ፍተሻ ማድረግ አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል። በዚህም መሰረት በጥናት ላይ የተመረኮዘ ብሄራዊ የስፖርት ሪፎርም በቅርቡ በኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን መዘጋጀቱ ይታወቃል። በሪፎርሙ ምክረ ሃሳብ መሰረትም መመሪያዎች በመከለስና በመሻሻል ላይ ይገኛሉ። ሪፎርሙ ካመላከታቸው ነጥቦች መካከል አንዱ የሆነው አደረጃጀቱን የሚመለከት ሲሆን፤ በተለይ መንግስታዊው አካል ላይ ክፍተት መኖሩን አመላክቷል። በኢትዮጵያ 30 የሚሆኑ የስፖርት ፌዴሬሽኖችና አሶሴሽኖች ይገኛሉ። ከፌዴራል እስከ ቀበሌ ባለው አደረጃጀትም በጥቅሉ 397 ፌዴሬሽኖችና የስፖርት ማህበራት እንዳሉ ይታመናል። ከእነዚህ ማህበራት መካከል ራሳቸውን ችለው ከመንግስት ድጎማና ድጋፍ የተላቀቁት ግን ሁለቱ ብቻ ሲሆኑ፤ አትሌቲክስና እግር ኳስ ፌዴሬሽኖች በዋናነት ይጠቀሳሉ። የተቀሩት እስካሁንም የመንግስትን ድጎማ የሚጠብቁ በሁለት እግራቸው ያልቆሙ ሲሆኑ፤ በግላቸው የሚያደርጉት እንቅስቃሴም አነስተኛና የተገደበ ነው። ለዚህና ለስፖርቱ አለማደግ በዋናነት እንደ ምክንያት የሚያነሱትም በመንግስት በኩል የሚመደብላቸውን አነስተኛ የበጀት ድጎማ ነው። ነገር ግን የየስፖርት ዓይነቱን በኃላፊነት የሚመሩትና በየደረጃው የሚገኙ የስፖርት ማህበራት (ፌዴሬሽኖች) ካሉባቸው ችግሮች ባሻገር ከራሳቸው ድክመት የተነሳ ስፖርቱ እንዲዳከም ምክንያት እንደሆነ ይታመናል። አሁን ባለው ሁኔታ ፌዴሬሽኖቹ ራሳቸውን ከተረጂነት ነጻ ለማውጣት ያላቸውን እድል ተጠቅመው ለውጥ ለማምጣት የሚፍጨረጨሩት ጥቂቶች ናቸው። መልካም ተሞክሮ ካላቸው ሌሎች ፌዴሬሽኖች ልምድ ለማግኘት የሚችሉበት መንገድም ዝግ መሆኑ ይስተዋላል። አንዳንድ ስፖርቶች በህዝቡ ዘንድ በቅጡ ያልታወቁና ተደራሽነታቸውም በአሳሳቢ ደረጃ ላይ የሚገኙ ሲሆን በማህበር ታቅፈው የመንግስትን በጀት ለብክነት የሚዳርጉም አሉ። በአንጻሩ መልካም ድልና የተሻለ ውጤት ሊመዘገብባቸው የሚችሉ ስፖርቶች ደግሞ እንቅስቃሴያቸው የተገደቡ ሆነዋል። ሌሎች ደግሞ በተወሰኑ አካላት ተሸብበው እድገታቸው ቀጭጮ እንዲቀር ሆነዋል። ስፖርቱ በህዝቡ ዘንድ ተስፋፍቶ ጥቅም የሚገኝበት እንዲሁም በሀገር ደረጃ ውጤት እንዲመዘገብበት ካስፈለገም እነዚህ ችግሮች በቅድሚያ ሊቀረፉ እንደሚገባ ብዙዎች ይስማማሉ። በመሆኑም ሀገር አቀፉን የስፖርት ማህበራት ማቋቋሚያ መመሪያ ማሻሻል አስፈልጓል። ባለፈው ሳምንት ኮሚሽኑ ባካሄደው ጠቅላላ ጉባኤ ላይ የተሻሻለው መመሪያ ረቂቅ በኮሚሽኑ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሰለሞን አልዩ ለተሳታፊዎቹ የቀረበ ሲሆን አስተያየትም ተሰጥቶበታል። በገለጻው ላይ እንደተመላከተው ከሆነም ለመመሪያው መሻሻል አስፈላጊ የሆኑት ምክንያቶች፤ በሪፎርሙ የተሰጠው ምክረ ሃሳብ፣ የማህበራዊ ወቅታዊ አቋም፣ ያሉባቸውን ችግሮች ለመፍታት እንዲሁም የስፖርት ምክር ቤቱ የውሳኔ አቅጣጫ ናቸው። የማህበራቱን አሰራሮችና አደረጃጀቱን በመፈተሽ ተገቢውን መስፈርት አሟልተው እንዲሄዱ ማድረግም አላማው ነው። አብዛኛዎቹ ማህበራት ተገቢውን መስፈርት ሳያሟሉ የማህበር ስያሜ ብቻ በመያዝ እውቅና አግኝተው የሚንቀሳቀሱ በመሆናቸው ውጤታማ መሆን አልቻሉም፤ በመሆኑም ዳግም ዕውቅና ማግኘት አስፈልጓቸዋል። መሆኑም ማሻሻያው የተለያዩ ሂደቶችን ተከትሎ ሊዘጋጅ ችሏል። ይኸውም ነባሩን መመሪያ መሰረት በማድረግ፣ የሌሎች ሀገራትን ተሞክሮ በመዳሰስ፣ ዓለም አቀፍ አሰራሮችን በመመልከት እንዲሁም ያጋጠሙ ተጨባጭ ሁኔታዎችን በመውሰድ መሆኑንም በመድረኩ ተጠቁሟል። በስራውም የኮሚሽኑ፣ የተለያዩ ፌዴሬሽኖች እንዲሁም የኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ ባለሙያዎች ተሳታፊዎች ነበሩ። መመሪያው ከያዛቸው ሃሳቦች መካከል አደረጃጀትና ስያሜን የሚመለከት ሲሆን፤ በክልል ያሉ ፌዴሬሽኖች ‹‹አሶሴሽን›› ከዚያ በታች ያሉት ደግሞ ‹‹ኮሚቴ›› በሚል ቢጠሩ ለአሰራር አመቺ እንደሚሆኑ ተመልክቷል። የፌዴሬሽን ማቋቋሚያ መስፈርትን በተመለከተም የቡድንና የግል ስፖርቶችን በራሳቸው አሰራር መሰረት እውቅና የሚያገኙበት ሁኔታም ተካቷል። በዚህም የቡድን ስፖርቶች የሚያወዳድሯቸው ቢያንስ ስድስት ክለቦች ሊኖሯቸው እንደሚገባ፤ በአርት ስፖርቶች 10 ማዕከላት እንዲሁም በግል ስፖርቶች 250 የተመዘገቡ ስፖርተኞች ሊኖሩ ይገባል። ደረጃውን የጠበቀ የውድድርና የስልጠና ቁሳቁስ መኖሩ ሲረጋገጥ፣ የሀብት ምንጭ ሲኖራቸው እና የሂሳብ አያያዝ ሥርዓት የዘረጉ ሊሆኑም ይገባቸዋል። የሀገር አቀፍ ስፖርት ፌዴሬሽኖች የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባላት እጩ አቀራረብ፣ የመምረጫ መስፈርት እንዲሁም ተግባርና ኃላፊነትም በመመሪያው ተካቷል። በዚህም የኮሚቴዎቹ የስራ ዘመን አራት ዓመት ብቻ ሲሆን፣ በድጋሚ የሚመረጡትም ለአንድ የስራ ዘመን ብቻ ይሆናል። ይህም ቀድሞ በተለያየና በተበታተነ ሁኔታ ይከናወን የነበረው ምርጫ አንድ የኦሊምፒክ ጨዋታ በተጠናቀቀ ሶስትና አራት ወራት ውስጥ ጠቅላላ ጉባኤ በመጥራት ምርጫ እንዲከናወን የሚያስገድድ ነው። ከዚህ ጋር የተካተተው መመሪያም የትኛውም የስራ አስፈጻሚ ሊያገለግል የሚችለው በአንድ ስፖርት ላይ ብቻ መሆኑን የሚያመለክት ነው። የማህበራት ፈቃድ አሰጣጥ፣ እድሳትና መፍረስን በተመለከተም በምን መልኩ ይከናወናል የሚለውን የተሻሻለው የመመሪያ ረቂቅ በዝርዝር አስቀምጧል። የኦሊምፒክና ፖራሊምፒክ ኮሚቴዎች፣ የከፍተኛ ትምህርት ስፖርት ማህበር እንዲሁም የጤና ስፖርት ማህበር በበኩላቸው የተለያዩ ስፖርቶችን አቅፈው የሚያካሂዱ ማህበራት እንደመሆናቸው ከሌላው የተለዩ መሆናቸውም ተገልጿል። በመመሪያው ዝግጅት ላይ ተሳታፊ የነበሩትና ገለጻውን ያደረጉት የጽህፈት ቤቱ ኃላፊ አቶ ሰለሞን አልዩ ምላሽ የተነሱ ሃሳቦች ላይ ምላሽ ሰጥተዋል። መድረኩ የተዘጋጀው ግብዓት ለመሰብሰብ እንደመሆኑ በተለያዩ አካላት ዘንድ የተለያዩ እይታዎች ይፈጠራሉ። በመሆኑም ጠቃሚ የሆኑትን ለማካተት ያስችላል፤ የስፖርቱ አደረጃጀት በምን መልክ ሊቃኝ ይገባል በሚለው ላይ ጠቃሚ ሃሳቦች እንጂ ፍላጎቶችን ለማስተናገድ እንደማይቻልም አሳስበዋል። አደረጃጀቶቹ ያሉባቸውን ክፍተቶች በመሙላት አደረጃጀቱን ለማጠናከር ይቻላል፤ ስለዚህም የተሰጡት ግብረ መልሶች በሰነዱ የሚካተቱ ይሆናል። በተጨማሪም መድረኩ የተዘጋጀው በምክር ቤት በተቀመጠው አቅጣጫ መሰረት በመሆኑ መንግስት ወደፊትም ለማህበራቱ እገዛና ድጋፍ ከማድረግ ወደኃላ እንደማይልም አመላክተዋል። በኮሚሽኑ ምክትል ኮሚሽነር ዱቤ ጂሎ በበኩላቸው ይህ የቀረበው ረቂቅ መመሪያ ወደ ክልሎች ወርዶ የራሳቸውን ደንብና መመሪያ እንዲያወጡ የሚደረግ መሆኑን ገልጸዋል። ማህበራቱ የየራሳቸውን መመሪያና ደንብ ካዘጋጁ በኋላም በዚህ ላይ ተመስርተው ክልሎች በስታንዳርዱ መሰረት የሚተዳደሩ ይሆናል፤ በመሆኑም በመድረኩ የተንጸባረቁ ሃሳቦች ጠቃሚ መሆናቸውን አስረድተዋል። አዲስ ዘመን ሐምሌ 25 ቀን 2012 ዓ.ምብርሃን ፈይሳ
https://www.press.et/Ama/?p=36457
794
2ስፖርት
አይጦችን ከአገልግሎት ክፍያ ለማምለጫ
መዝናኛ
February 18, 2020
21
 በተለያዩ ሀገራት የሚገኙ ሆቴሎች እንደ የደረጃቸው ለደምበኞቻቸው አገልግሎቶችን ያቀርባሉ።ለአገልግሎቶቻቸውም ደምበኞቻቸውን ያስከፍላሉ።ደምበኞችም በሆቴሎቹ ቆይታቸው ከያዙት አልጋ ጀምሮ እስከተጠቀሟቸው ምግቦችና መጠጦች ድረስ ክፍያ መፈፀም ይጠበቅባቸዋል። ይሁን እንጂ አንዳንዴ ደንበኞች በሆቴሎች ውስጥ ያሻቸውን ተጠቅመው ሲያበቁ ሂሳብ ሲጠየቁ ድንጋጤ ውስጥ የሚገቡ፤ ለመክፈልም የሚያንገራግሩ አይጠፉም።ለተጠቀሙበት አልጋ፣ ምግብ፣ መጠጥና ሌላም የአገልግሎት ክፍያ ሳይፈፅሙ እንዲሁ በነፃ ከሆቴሉ ውልቅ ብለው ለመውጣት የሚዳዱም አልፎ አልፎ አይታጡም።ኦዲቲ ሴንትራል ከሰሞኑ ይዞት የወጣው መረጃም የሆቴል አገልግሎቶችን በሚገባ ተጠቅሞ ክፍያ ሳይፈጽም ስለተገኘ አንድ ግለሰብ አስነብቧል። የሰላሳ ሰባት አመቱ አሜሪካዊው የኡታ ግዛት ጎልማሳ ሪያን ቀልቡ ባረፈባቸው ሆቴሎች ሁሉ በመግባት ከአልጋ ጀምሮ የሚፈልገውን አገልግሎት በሙሉ ተጠቅሞ ምንም አይነት ክፍያ ሳይከፍል በተደጋጋሚ ውልቅ ብሎ ይወጣል።ሂሳብ ሳይከፍል የሚወጣው ግን ተደብቆ ወይም በስፖንሰር ተከፍሎለት አይደለም፤ በአይጦች እንጂ።እዚህ ላይ የእርሱ ከሆቴሎች በነፃ ተስተናግዶ መውጣት ከአይጦች ጋር ምን አያያዘው ሊሉ ይችላሉ።እውነታው ግን አይጦቹ ሪያንን ከከባድ ወጪ ያዳኑት መሆኑ ነው። ነገሩ ወዲህ ነው፤ ሪያን በቅድሚያ ወደ ሆቴሎች ሰተት ብሎ ይገባል። ከዛም አልጋ ይይዛል።ጥቂት ቆይቶም ከውጭ ወደሆቴሉ በሳጥን ደብቆ የሚያስገባቸውን አይጦች በያዘው ክፍል ውስጥ ይለቃቸዋል። በመቀጠልም ከሆቴሉ ስታፍ ለአንዱ ስልክ በመደወል በሆቴሉ የንፅህና አያያዝ ዙሪያ ቅሬታውን ያቀርባል፤ ይጮሃል። ታዲያ በዚህ ጊዜ የሆቴሉ ስራ አስኪያጆች የሆቴላቸው ስም እንዳይጠፋ ‹‹የአልጋ ሂሳብ አናስከፍልህም፤ የምግብና የመጠጥ ወጪህንም እኛ እንሸፍንልሃለን›› ይሉታል።እንዲህ አይነቱን የማታለያ ድርጊት በተደጋጋሚ በመፈፀምም ሪያን በተለያዩ ሆቴሎች በሚገኙ አልጋዎች ላይ በነፃ ተኝቷል፤ ሌሎች የምግብና የመጠጥ አገልግሎቶችን እንዳሻው ተጠቅሟል። መቼም እንዲህ አይነቱ የማታለያ ተግባር ሁሌም አያዋ ጣምና በዚህ ድርጊት በሶስት ሆቴሎች ላይ የጠረጠረው ፖሊስ ሪያንን በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያደረገበት ይገኛል። ሪያን እንዴት በፖሊስ ሊያዝ እንደቻለ በግልፅ የተነገረ ባይኖርም በሁለት ሆቴሎች የመኝታ ክፍሎች ወስጥ አይጦቹን ስለመልቀቁ ግን ራሱ አምኗል።ሌብነትና ማጭበርበርን ጨምሮ አምስት ክሶች እንደሚጠብቁትም ተነግሯል። አዲስ ዘመን የካቲት 10/2012 አስናቀ ፀጋዬ
https://www.press.et/Ama/?p=27458
255
1መዝናኛ
ባድሚንተን-ትኩረት የተነፈገ ተወዳጅ ስፖርት
ስፖርት
August 3, 2020
10
 በስፖርቱ ዓለም ጥሩ የአካል ብቃት፣ሰውነትን እንደ ልብ የማዘዝ ችሎታ፣ፅናት፣ጥንካሬና ፍጥነትን ከሚሹ ጨዋታዎች መካከል ባድሚንተን ዋነኛው ነው። ከሜዳ ቴኒስ ወይንም ከጠረጴዛ ቴኒስ ጋር ተመሳሳይ አጨዋወትን የሚጋራው የባድሚንተን ስፖርት በብሪታኒያና ህንድ እንደጎለበተ የሚነገር ቢሆንም በአውሮፓዊቷ አገር ዴንማርክ ትልቅ ዝና አለው። ይህ ስፖርት ተወዳጅነቱን እያሰፋ በኤሽያ አገራት በስፋት መዘውተሩን ተከትሎም ባለፉት ጥቂት የማይባሉ ዓመታት የቻይና የበላይነት የሚንፀባረቅበት ሆኗል። እኤአ 1992 በባርሴሎና የበጋ ወራት ኦሊምፒክ ተካቶም በአራት የውድድር ዘርፎች አገራት ተፎካካሪ ሆነውበታል። በነጠላ ወንዶች፣ ነጠላ ሴቶች፣ በቡድን ሴቶችና በቡድን ወንዶች ኦሊምፒክ ላይ የነበረው ፉክክር አድጎም በድብልቅ ፆታ አምስተኛ የመወዳደሪያ ዘርፍ ለመሆን ጊዜ አልፈጀበትም። የባድሚንተን ስፖርት በኢትዮጵያ በይፋ መቼ እንደተጀመረ ሰነዶችን ማግኘት አይቻልም። ይሁን እንጂ ይህ ስፖርት በ1940ዎቹ መጨረሻ አካባቢ በታወቁ አንዳንድ ትምህርት ቤቶች፣ የሚሲዮን ተቋማትና በወጣት ወንዶች ክርስቲያናዊ ማህበር (ወክማ) አካባቢ በውጭ አገር ዜጎችና መምህራን አማካኝነት እንቅስቃሴው እንደተጀመረ ከፌዴሬሽኑ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። በተለይም የባድሚ ንተን ስፖርት በ1970 ዎቹ ገደማ ከወክማ ባሻገር በህንድ ኤምባሲ ውስጥ በስፋት መዘውተር እንደ ጀመረ ይነገራል። በህዳር ወር 1978 ዓ.ም ስፖርቱ በአደራጅ ኮሚቴነት ተዋቅሮ በሂደት 1982 ዓ.ም ላይ አደረጃጀቱ ወደ ፌዴሬሽን አድጓል። ከዚህም በኋላ ከ1986 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ የኢትዮጵያ ቻምፒዮናን በውድድር ደረጃ ማከናወን ችሏል። ባለፉት ዓመታትም በአገራችን በሚካሄዱ እንደ መላ ኢትዮጵያ ጨዋታዎች፣የመንግሥት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የስፖርት ፌስቲቫል፣የታዳጊ ወጣቶች የምዘና ውድድሮችና ሌሎችም ፉክክሮች ላይ የምንመለከተው ስፖርት መሆን ችሏል። ከኦሊምፒክ ስፖርቶች መካከል አንዱ የሆነው የባድሚንተን ስፖርት በተለይም በኤሽያ አገራት በስፋት የሚዘወተር ብቻ ሳይሆን እነዚህ አገራት በብዛት ኦሊምፒክ ላይ ተሳትፈው በሜዳሊያ ሰንጠረዥ የአገራት ፉክክር ውስጥ የሚገቡበት የስፖርት አይነት ነው። የባድሚንተን ስፖርት አሁን ላይ በአገራችን ብዙ እውቅና ከሌላቸው የስፖርት አይነቶች አንዱ ሆኖ እናገኘዋለን። የአገራችን መገናኛ ብዙሃንም አብዛኞቹ ለዚህ ስፖርት ትኩረት ሲሰጡት አይታይም። ስፖርቱን በቅርበት ከሚያውቁት ባሻገ ርም አብዛኛው ህዝብ ባድሚንተን ምን እንደሆነ ግን ዛቤ አለው ለማለት ይቸግራል። በአጠቃላይ የባድሚንተን ስፖርት በአገራችን ካለመስፋፋቱ ባሻገር ሌሎች የኦሊምፒክ ስፖርቶች በሚጓዙበት የእድገት ደረጃ ላይ የሚገኝ ነው ለማለት አይቻልም። ለመሆኑ ይህ ስፖርት እንደ እግር ኳስና አትሌቲክስ ባይሆን እንኳን ሌሎች ደካማ የሚባሉት ስፖርቶች በሚንቀሳቀሱበት ደረጃ ለመንቀሳቀስ ለምን ተሳነው?፣ ክለቦችን መስርተው የሊግ ውድድሮችን በቀጣይነት ለማስኬድ ዳዴ ከሚሉት አንዳንድ ፌዴሬሽኖችስ በምን ይለያል? የሚሉ ጥያቄዎች በስፖርት ቤተሰቡ ዘንድ ይነሳሉ። የስፖርቱ አፍቃሪዎች ከስፖርቱ ባህሪ ተነስተው ለነዚህ ጥያቄዎች ምላሽ ሲሰጡ የባድሚንተን ትልቁ ችግር መሰረተ ልማት እንደሆነ ያብራራሉ። የባድሚንተን ስፖርት በባህሪው ከቤት ውስጥ ስፖርቶች መካከል አንዱ በመሆኑ የተሟላ መሰረተ ልማት የሚጠይቅ ነው። ስለዚህ ስፖርቱን ለማስፋፋትና ለማዘውተር ቢያንስ መሰረታዊ የሆነ አዳራሽ ወይም ጅምናዚየም ያስፈልጋል። የባድሚንተን መጫወቻዋ ላባ(በተለምዶ እፉየ ገላ የምትመስል መጫወቻ) በጨዋታ ወቅት በንፋስ ምክንያት አቅጣጫ የመለዋወጥ ባህሪ ስላላት ስፖርቱን ከቤት ውጭ ማድረግ አስቸጋሪ ነው። ይህን ስፖርት ለመጫወት አዳራሹ ወይንም ጅምናዚየሙ ቢያንስ ሰባት ሜትር ከፍታ ያለውና ሁለት ጨዋታዎችን በአንድ ጊዜ ማካሄድ የሚያስችል መሆን እንዳለበት ዓለም አቀፍ ህጉ ይደነግጋል። በአገራችን አብዛኞቹ ስፖርቶች ከቤት ውጭ ሊዘወተሩ ይችላሉ። ባድሚንተን ግን ቤት ውስጥ ብቻ የሚደረግ ውድድር በመሆኑ በቀላሉ እንዳይዘወተርና እንዳይስፋፋ እንቅፋት መሆኑን የስፖርቱ ቅርብ ሰዎች ይናገራሉ። ከአዲስ አበባና ድሬዳዋ ከተሞች በስተቀር ስፖርቱን ሌሎች ክልሎች ላይ እንደልብ ማካሄድና ማስፋፋት የሚያስችል መሰረተ ልማት የለም። በአዲስ አበባ ወክማ ውስጥ ባድሚንተን በስፋት እንደሚዘወተር ይታወቃል። ነፃ የሆኑ አዳራሾች ወይም ጅምናዚየሞች ቢኖሩ ስፖርቱ የሚፈልጋቸው ሌሎች ቁሶችን በቀላሉ ማግኘት እንደሚቻል ይታመናል። በእርግጥ የባድሚንተን ስፖርትን እንደ ቮሊቦልና ቅርጫት ኳስ አይነት ስፖርቶች ከቤት ውጪ ማዘውተር የሚቻልበት እድል ዝግ አይደለም። ይሁን እንጂ ባድሚንተንን ከቤት ውጭ ማዘውተር ስፖርቱን በፕሮፌሽናል ደረጃ ለማሳደግና ውጤታማ ለመሆን እንደማይቻል እውን ነው። አገር አቀፍ ፌዴሬሽኑ ስልጠናዎችን ለመስጠት አይደለም አገር አቀፍ ውድድሮችን ለማካሄድ እንቅፋት ከሆኑበት ነገሮች ዋነኛውም ይሄው ማዘውተሪያ ስፍራው መሆኑም ይታመናል። ስፖርቱ እጅግ የሚወደድና የብዙዎችን ቀልብ ሊስብ የሚችል ነው። በአገራችን በተለያዩ ውድድሮች ላይ እንደሚታየውም ወጣቱ ስፖርቱ ላይ ትልቅ ፍላጎት አለው። በተለይም በለጋ እድሜ ላይ የሚገኙ እድሜያቸው አሥራ አንድና አሥራ ሁለት አካባቢ የሚገኙ ታዳጊዎች ለባድሚንተን ስፖርት ከፍተኛ ፍላጎት አላቸው። ሁኔታዎች ተመቻችተው እንደ ስፖርት ለሁሉም እድሜያቸው የገፋ ሰዎች ቢያዘወትሩትም ይመከራል። የባድሚንተን ስፖርት በደንብ ትኩረት ተሰጥቶት ተከታታይ ስልጠናና በርካታ ውድድሮች ቢደረጉ ቢያንስ በአፍሪካ ደረጃ በሚካሄዱ ውድድሮች ትልቅ ለውጥ ማምጣት እንደሚቻል ይታመናል። አሁን ባለው ሁኔታ ስፖርቱ ከነችግሮቹ እንኳን ውጤቱ ብዙ ባይሆንም በመላ አፍሪካና ሌሎች ዓለም አቀፉ ጨዋታዎች መሳተፍ እየተቻለ ይገኛል። መንግሥት ስፖርቱን በተመለከተ ሥራው በዋናነት ስፖርቱን ማስፋፋት ነው። የልማት ሥራዎችን መስራት ደግሞ ያለበት ፌዴሬሽኑ ነው። ፌዴሬሽኑን ሊመሩ የሚችሉ ደግሞ ሥራ አስፈፃሚዎች ተቀምጠዋል። እነዚህ ሥራ አስፈፃሚዎች ሃብት አሰባስበው ስፖርቱን በደንብ በማህበረሰቡ ውስጥ እንዲያስፋፉ ትልቅ ድርሻ ያላቸው ህዝባዊ አካል ናቸው። መንግሥት እንደማንኛውም የስፖርት ፌዴሬሽን ለባድሚንተንም ድጋፍ ያደርጋል። እንዲያውም መንግሥት አሁን የሚያደርገው ድጋፍ ከስፖርቱ እንቅስቃሴ አንፃር ጥሩ የሚባል እንደሆነ ማስቀመጥ ይቻላል። ባድሚንተን የኦሊምፒክ ስፖርት እንደመሆኑ እንደሌሎች መሰል ስፖርቶች በታዳጊ ወጣቶች የተለያዩ ፕሮጀክቶችና በአካዳሚ ደረጃ ሰፊ እንቅ ስቃሴ ሲደረግበት አይታይም። ባድሚንተን በሁሉም ክልሎች በታዳጊ ወጣቶች ፕሮጀክት ከሚሰራባቸው ስፖርቶች አንዱ ሆኖ እየተሰራ ይገ ኛል። ፌዴሬሽኑም በየዓመቱ የሚደረጉ የፕሮጀክቶች የምዘና ውድድሮችም ተሳታፊ ነው። በታዳጊ ፕሮጀክት ደረጃ የሚሰራባቸው በአካዳሚ ደረጃ ግን ስልጠና የማይሰጥባቸው ሌሎች ስፖርቶችም አሉ። በባድሚንተን ስፖርት በግለሰቦች የሚመሰረቱ ቡድኖች አሉ፣ እንደ ክለብ ግን ተደራጅተው የሚንቀሳቀሱ አይደሉም። በዚህ ሁኔታ በባድሚንተን ስፖርት በተለያዩ ክልሎች የታዳጊ ወጣቶች ፕሮጀ ክቶችን ቀርፆ መንቀሳቀስ እንደ አገር ስፖርቱን ከመጥፋት ሊታደግ ይችላል። ይሁን እንጂ ከነዚህ ፕሮጀክቶች የሚወጡ ታዳጊዎች ወደ አካዳሚ ገብተው ከዚያም ወደ ክለብ መሸጋገር ካልቻሉ ከስፖርቱ ጋር ያላቸው እህል ውሃ የሚዘልቀው እስከ ምዘና ውድድር ድረስ ነው። ይህ ደግሞ ብዙ ወጣቶች ወደ ስፖርቱ እንዳይመጡ እንቅፋት መሆኑ አይቀርም። ክለቦች ከሌሉ ከፕሮጀክት የሚወጡ ታዳጊዎች ተጎጂ ሊሆኑ እንደሚችሉ ቢታመንም ከፕሮጀክት ከወጡ በኋላ ሌላ ማረፊያ የላቸውም። በአገር አቀፍ ደረጃ በሚካሄዱ ውድድሮች ክልላቸውን ወክለው መሳተፍ አንዱ አማራጫቸው መሆኑ ግን ይታመናል። ከባድሚንተን ጋር በተመሳሳይ በጀት ይንቀሳቀሱ የነበሩ በርካታ ፌዴሬሽኖች ክለቦችን በማቋቋምና ውድድሮችን በብዛት በማድረግ ራሳቸውን እያሳደጉ እንደሚገኙ ብዙ ማስረጃዎችን ማቅረብ ይቻላል። በአገራችን ከታሪካቸውም አንፃር የኳስ ስፖርቶች ላይ ትኩረት የማድረግ ልምድ ስላለ የኳስ ስፖርቶችና ባድሚንተን እኩል ማየት ተገቢ አይደለም። የኳስ ስፖርቶች የሚባሉት እግር ኳስ፣እጅ ኳስ፣ቅርጫት ኳስ ወዘተ በሚሊተሪ አካባቢ ሰፊ መሰረት ስላላቸው እነሱን ለማሳደግ ከባድሚንተን አይነት ስፖርቶች አኳያ ብዙ ልፋት እንደማይጠይቅ የሚሞግቱ የስፖርት ቤተሰቦች ጥቂት አይደሉም። የባድሚንተን ስፖርት በርካታ ችግሮች ቢኖ ሩበትም በአንዳንድ ክልሎች መሰረታዊ ነገር ሳይሟ ላላቸው ጭምር እየሰሩ ነው። ስፖርቱ የመሰረተ ልማት እጥረት ቢኖርበትም ፌዴሬሽኑ በተቻለው አቅም ከዓለም አቀፍ ፌዴሬሽኑ ከሚያገኛቸው የቁሳቁስ ድጋፍ ተነስቶ ለክልሎች ድጋፍ እየሰጠ ነው። ይህ ስፖርቱ እንዲያንሰራራ ትልቅ እድል ነው። የመሰረተ ልማት ጉዳይ የባድሚንተን ስፖርት ብቻም ሳይሆን የበርካታ ስፖርቶች እንቅፋት እንደመሆኑና ከአገር አቅም ጋር የተያያዘ መሆኑ ችግሮች በአንድ ጀምበር ሊፈቱ አይችሉም። ያም ሆኖ ኢትዮጵያ በስፖርቱ መሰረተ ልማት ግንባታ ረገድ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ትኩረት ሰጥታ እየሰራች ለመሆኗ በተለያዩ ክልሎች ግዙፍ ስቴድየሞችን ጨምሮ ጅምናዚየምና ሌሎች መሰረተ ልማቶችን ማስተዋል ይቻላል። ባድሚንተንን ለመሳሰሉትና በመሰረተ ልማት ችግር በአገራችን መራመድ ያልቻሉት ስፖርቶችም የነዚህን መሰረተ ልማት ግንባታዎች መጠናቀቅ በተስፋ የሚጠበቁ ይሆናል።አዲስ ዘመን ሐምሌ 27/2012 ቦጋለ አበበ
https://www.press.et/Ama/?p=36543
973
2ስፖርት
የሚወዱት -ሲወደድ” ደስ ይላል!
መዝናኛ
February 24, 2020
27
እነ ኒያላና ጓደኞቹ በመወደዳቸው፤ ዋልያና ቤተሰቦቹ አልቀመስ በማለታቸው አኮረፉ አሉ። ሰው የሚወደው ነገር ሲወደድ ደስ ሊለው ነው የሚገባው፤ አይደል? ምን ነካቸው? ሰሞኑን በፀደቀው አዋጅ ምክንያት አኩራፊዎች በዝተዋል ሲሉ ተገረምኩ። የእነ ሀበሻ አድናቂዎች የእነ ግስላ ቲፎዞዎች እንዲያው ምን ነካችሁ? ሰው ወዳጁ ወደላይ ከፍ እንዲልለት በብርቱ ሲመኝ እንዴት የወደዳችሁት ነገር መወደዱን ጠላችሁት ግን? አኮረፉ ‘ለምን? አሉ’ ሲሉኝ እኔ አላመንኩም ነበር። ግን አመንኩ፤ በቢራ መወደድ ማዘናችሁ፤ በሲጃራ ዋጋ ማሻቀብ ማኩረፋችሁ በገጠመኜ እኔም ታዘብኩ። አቤት ግን ግፋችሁ! ቆይ ስንት ሀገራዊ የሆኑ ውድ ውድ ስሞችን ተሸክመው እንዴት እስከ ዛሬ እንደረከሱ ይገርመኛል። ዋልያ የተሰኘ ብርቅዬ እንስሳችን መጠሪያው አድርጎ፣ ኒያላ የተባለው ተወዳጅ ልዩ ብርቅዬ እንስሳን የፓኮው ስያሜ አድርጎ አራክሶ ሲቸበችም ዝም ያልነው እኮ ስያሜያቸውን አይተን እንጂ ውስጡ ያሉትን ጤናን አቃዋሽ ጉዶችን አክብረን አልነበረም። ስለጤፍ መወደድ፤ ስለ ኑሮ ጣራ መንካት ግድ ሰጥቶት የማያውቅ ሰው እንዴት ሲርበው በልቶ፤ ጠግቦ ለሚጠጣው ኦክስጂን ሰልችቶኛል ሲጃራ ነው አምሮቴ ብለው ያኮርፋል? በነገራችን ላይ፤ ሱሰኞቹ “እኛን ብቻ ለምን?” በማለት ሲሞግቱ ነበር አሉ። በጫትና ሌሎች ነገሮች ላይም ታክስ ይጨመር፤ ካልሆነ ከሌላው በተለየ የእኛ መብት ተገፋ፤ በደል ተፈጸመብን” በማለት ሲሟገቱ ከረሙ የሚል ጭምጭምታ ሰምተናል። ስለትውልድ ሲታሰብ፤ የትውልዱን መለወጥ ሀገራዊ ለውጥ መሆኑ ይታመንበታልና ትውልድ ገዳይ፤ ሀገር አጠልሺ የሆኑ አሉታዊ ተፅዕኖ የሚፈጥሩ ጉዳዮችን ማስቆም፤ አሊያም የሚቀንሱበትን መንገድ ማበጀት ከሀገሬው የሚጠበቅ ነውና ጠቃሚው ተተገበረ። እርግጥ ይህ ሲታሰብ መልካምነቱ የማይካድ፤ ውጤቱም አመርቂነቱ የማይታበይ ሀቅ ነው። ታዲያ ጠጪዎች ይሄንን ማን ጋረደባቸው? ስለ ሀገሩ የሚያስብ፤ ስለ ትውልዱ የሚጨንቀው እንዴት “እኔ ፍላጎቴን ላስታግስ እንጂ ስለሌላው ምን ገዶኝ” ይላል? ሰው ሀገሩንና ህዝቡን ሊወድድ ለውጡንም ሊመኝ ይገባል። ሀገራዊ ለውጥንና እድገትን የወደደ ደግሞ ስለ ሀገሩ መልካም ያስባልና እንዴት መልካም የሆነ ሀገራዊ ነገር ይጠላል? እናም ውዶቼ ሀገራዊ ራዕይ ያለው የትውልድን መልካም ፍሬ ማየት የሚወድድ ጥሩ ያልሆኑ ነገሮችን የሚያርቅ አዋጅ አይደለም ሊያሳድድ ሊደግፍ ይገባል። ትልቅ ሀገራዊ አላማ ያለው ስለ ለውጥና እድገት በእጅጉ የሚመኝ ሲጃራን “እምቢ” አልኮልን “አይ” ማለት ነው ያለበት፤አንድ ታወቂና በዓለም አቀፍ ደረጃ ቁንጮ የሆነ አየር መንገድ በደንበኞች አያያዝና በመስተንግዶው ተወዳጅ ስለሆነ ብዙ መንገደኞች ይመርጡት ነበር። አንድ ሰው ከመኖሪያ አካባቢው ወደ ሌላ አገር መሄድ ይፈልግና ይህን አየር መንገድ ይጠቀማል። በአውሮፕላን ውስጥ አስተናጋጆች ደንበኞችን በልዩ ትህትና እያስተናገዱ ወደአንደኛው ሰው ይጠጋሉ። ቀድሞ የጠቀስነው ተጓዥ አጠገብ የደረሰች አንዲት መልከ መልካም አስተናጋጅ፤ ወደሰውዬው ቀርባ በእጇ የያዘችውን መጠጥና ብርጭቆ ታቀርባለች።የአስተናጋጇ ፍላጎት የደንበኛዋ ጉዞ በፍስሀ እንዲሞላና ሳይሰላች እንዲያሳልፍ ነውና ፈገግታ ተላብሳ አንድ ውድ የአልኮል መጠጥ ከብርጭቆ ጋር አቀረበች። ሰውዬውም እጅግ ትህትና በተሞላበት ሁኔታ ይቅርታ ጠይቆ እንደማይጠጣ ይገልፅላታል። አስተናጋጇ ከዚያ በፊት ይህንን ውድ መጠጥ በፍቅር ይጠጡት የነበሩ ደንበኞቿን እያሰበች በማነፃፀር እየተገረመች ሰውዬውን ትመለከተውና በድጋሚ ጠጋ በማለት “ሌላ አይነት መጠጥ ይሁንልዎ” ብላ ትጠይቀዋልች። ሰውዬው ግን ከአቋሙ ሳነቃነቅ በድጋሚ አለመፈለጉን ይነግራታል።አስተናጋጇ ደንበኛው በሆነ ጉዳይ ተከፍቶ እንጂ ይህንንማ አያልፈውም ነበር በማለት ለአለቃዋ ሄዳ ስለ ጉዳዩ ትነግረዋለች። አለቃዋም ከርስዋ ይበልጥ በመገረም “በሌላ በሚምያር ብርጭቆና ማራኪ በሆነ መልኩ በድጋሚ አቅርቢለት” በማለት ያዝዛታል አስተናጋጅዋን፤ አደረገችው። ግን የተለወጠ ነገር የለም። ይሄኔ አለቅየው እራሱ ቀርቦ ሰውዬውን ማናገር ይጀምራል።“ጌታዬ ችግር አለ? መስተንግዶዋችን አልተመ ቸዎትም? ምን እናስተካክል?” እያለ ትህትና የተላበሱ ተከታታይ ጥያቄዎችን ያቀርባል። ሰውዬው ፈገግታ በተሞላበት መንገድ ምላሹን ሰጠ። “አይ መስተንግዶዋችሁም በጣም ጥሩ ነው፤ ነገር ግን እኔ መጠጥ አልጠጣም” ይለዋል። ይሄኔ ኃላፊው ተገርሞ “እንዴ ለምን?” ብሎ ጠየቀው። ለዚህ ምላሽ ግን የሰጠው መልሶ እራሱን በመጠየቅ ነበር። “እስኪ ለኔ ልትሰጠኝ ካሰብከው ፊት ለፊት ባለው በር ከፍተህ ግባና ለፓይለቱ ስጠው በኔ ፋንታ ይጠጣ” ብሎ ጠቆመው።ይሄኔ ኃላፊው “እንዴ! እሱማ እንዴት ይጠጣል? ይሄን ማደረግማ አይችልም የስንት ሰዎችን ህይወት አደጋ ላይ ሊጥል ይችላል። ስለዚህ እሱ የመጠጥ ሽታም ሊደርስበት አይገባም።” በማለት ፓይለቱ በመጠጣቱ ሊደርስ የሚችለው አደጋ ዘረዘረ። ተጓዡም የሚፈልገው እንዲህ እንዲለው ነበርና በመልሱ ላይ የራሱን አስተያየት በማከል የማይጠጣበት ምክንያት ተናገረ። “ወዳጄ እኔ የራሴ የሆነ ልዩ ዓላማ አለኝ አላማዬን ከስኬቱ እንዳደርስ ጥንቁቅ መሆን አለብኝና “ፈፅሞ አልጠጣም” ያልኩት ለዚህ ነው። በማለት መለሰለት።እናም ዓላማ ያለው፤ እሩቅ መጓዝ ያሰበ እርግጥም እራሱን ሆኖ የትኛውም ቦታ ይደርሳል። ሰሞኑን የወጣውን የኤክሳይዝ ታክስ ተከትሎ በመጠጥና በዘር ማንዘሮቹ፤ በሲጃራና በግብረ አበሮቹ ላይ የተደረገውን የታክስ ጭማሪ ጥቅም በትክክል ከተረዳን ጠጪዎችንና አጫሾችን ቢያስከፋም እነሱኑ የሚያድን መራራ መርፌ ነው። እናም በደንብ መውጋት/መወጋት ነው። ኧረ እንዲያውም ከፍ አድርጎ። ቸር ይግጠመን! አዲስ ዘመን የካቲት 16/2012ተገኝ ብሩ
https://www.press.et/Ama/?p=27764
611
1መዝናኛ
የሚወዱት -ሲወደድ” ደስ ይላል!
መዝናኛ
February 23, 2020
26
እነ ኒያላና ጓደኞቹ በመወደዳቸው፤ ዋልያና ቤተሰቦቹ አልቀመስ በማለታቸው አኮረፉ አሉ። ሰው የሚወደው ነገር ሲወደድ ደስ ሊለው ነው የሚገባው፤ አይደል? ምን ነካቸው? ሰሞኑን በፀደቀው አዋጅ ምክንያት አኩራፊዎች በዝተዋል ሲሉ ተገረምኩ። የእነ ሀበሻ አድናቂዎች የእነ ግስላ ቲፎዞዎች እንዲያው ምን ነካችሁ? ሰው ወዳጁ ወደላይ ከፍ እንዲልለት በብርቱ ሲመኝ እንዴት የወደዳችሁት ነገር መወደዱን ጠላችሁት ግን? አኮረፉ ‘ለምን? አሉ’ ሲሉኝ እኔ አላመንኩም ነበር። ግን አመንኩ፤ በቢራ መወደድ ማዘናችሁ፤ በሲጃራ ዋጋ ማሻቀብ ማኩረፋችሁ በገጠመኜ እኔም ታዘብኩ። አቤት ግን ግፋችሁ! ቆይ ስንት ሀገራዊ የሆኑ ውድ ውድ ስሞችን ተሸክመው እንዴት እስከ ዛሬ እንደረከሱ ይገርመኛል። ዋልያ የተሰኘ ብርቅዬ እንስሳችን መጠሪያው አድርጎ፣ ኒያላ የተባለው ተወዳጅ ልዩ ብርቅዬ እንስሳን የፓኮው ስያሜ አድርጎ አራክሶ ሲቸበችም ዝም ያልነው እኮ ስያሜያቸውን አይተን እንጂ ውስጡ ያሉትን ጤናን አቃዋሽ ጉዶችን አክብረን አልነበረም። ስለጤፍ መወደድ፤ ስለ ኑሮ ጣራ መንካት ግድ ሰጥቶት የማያውቅ ሰው እንዴት ሲርበው በልቶ፤ ጠግቦ ለሚጠጣው ኦክስጂን ሰልችቶኛል ሲጃራ ነው አምሮቴ ብለው ያኮርፋል? በነገራችን ላይ፤ ሱሰኞቹ “እኛን ብቻ ለምን?” በማለት ሲሞግቱ ነበር አሉ። በጫትና ሌሎች ነገሮች ላይም ታክስ ይጨመር፤ ካልሆነ ከሌላው በተለየ የእኛ መብት ተገፋ፤ በደል ተፈጸመብን” በማለት ሲሟገቱ ከረሙ የሚል ጭምጭምታ ሰምተናል። ስለትውልድ ሲታሰብ፤ የትውልዱን መለወጥ ሀገራዊ ለውጥ መሆኑ ይታመንበታልና ትውልድ ገዳይ፤ ሀገር አጠልሺ የሆኑ አሉታዊ ተፅዕኖ የሚፈጥሩ ጉዳዮችን ማስቆም፤ አሊያም የሚቀንሱበትን መንገድ ማበጀት ከሀገሬው የሚጠበቅ ነውና ጠቃሚው ተተገበረ። እርግጥ ይህ ሲታሰብ መልካምነቱ የማይካድ፤ ውጤቱም አመርቂነቱ የማይታበይ ሀቅ ነው። ታዲያ ጠጪዎች ይሄንን ማን ጋረደባቸው? ስለ ሀገሩ የሚያስብ፤ ስለ ትውልዱ የሚጨንቀው እንዴት “እኔ ፍላጎቴን ላስታግስ እንጂ ስለሌላው ምን ገዶኝ” ይላል? ሰው ሀገሩንና ህዝቡን ሊወድድ ለውጡንም ሊመኝ ይገባል። ሀገራዊ ለውጥንና እድገትን የወደደ ደግሞ ስለ ሀገሩ መልካም ያስባልና እንዴት መልካም የሆነ ሀገራዊ ነገር ይጠላል? እናም ውዶቼ ሀገራዊ ራዕይ ያለው የትውልድን መልካም ፍሬ ማየት የሚወድድ ጥሩ ያልሆኑ ነገሮችን የሚያርቅ አዋጅ አይደለም ሊያሳድድ ሊደግፍ ይገባል። ትልቅ ሀገራዊ አላማ ያለው ስለ ለውጥና እድገት በእጅጉ የሚመኝ ሲጃራን “እምቢ” አልኮልን “አይ” ማለት ነው ያለበት፤አንድ ታወቂና በዓለም አቀፍ ደረጃ ቁንጮ የሆነ አየር መንገድ በደንበኞች አያያዝና በመስተንግዶው ተወዳጅ ስለሆነ ብዙ መንገደኞች ይመርጡት ነበር። አንድ ሰው ከመኖሪያ አካባቢው ወደ ሌላ አገር መሄድ ይፈልግና ይህን አየር መንገድ ይጠቀማል። በአውሮፕላን ውስጥ አስተናጋጆች ደንበኞችን በልዩ ትህትና እያስተናገዱ ወደአንደኛው ሰው ይጠጋሉ። ቀድሞ የጠቀስነው ተጓዥ አጠገብ የደረሰች አንዲት መልከ መልካም አስተናጋጅ፤ ወደሰውዬው ቀርባ በእጇ የያዘችውን መጠጥና ብርጭቆ ታቀርባለች።የአስተናጋጇ ፍላጎት የደንበኛዋ ጉዞ በፍስሀ እንዲሞላና ሳይሰላች እንዲያሳልፍ ነውና ፈገግታ ተላብሳ አንድ ውድ የአልኮል መጠጥ ከብርጭቆ ጋር አቀረበች። ሰውዬውም እጅግ ትህትና በተሞላበት ሁኔታ ይቅርታ ጠይቆ እንደማይጠጣ ይገልፅላታል። አስተናጋጇ ከዚያ በፊት ይህንን ውድ መጠጥ በፍቅር ይጠጡት የነበሩ ደንበኞቿን እያሰበች በማነፃፀር እየተገረመች ሰውዬውን ትመለከተውና በድጋሚ ጠጋ በማለት “ሌላ አይነት መጠጥ ይሁንልዎ” ብላ ትጠይቀዋልች። ሰውዬው ግን ከአቋሙ ሳነቃነቅ በድጋሚ አለመፈለጉን ይነግራታል።አስተናጋጇ ደንበኛው በሆነ ጉዳይ ተከፍቶ እንጂ ይህንንማ አያልፈውም ነበር በማለት ለአለቃዋ ሄዳ ስለ ጉዳዩ ትነግረዋለች። አለቃዋም ከርስዋ ይበልጥ በመገረም “በሌላ በሚምያር ብርጭቆና ማራኪ በሆነ መልኩ በድጋሚ አቅርቢለት” በማለት ያዝዛታል አስተናጋጅዋን፤ አደረገችው። ግን የተለወጠ ነገር የለም። ይሄኔ አለቅየው እራሱ ቀርቦ ሰውዬውን ማናገር ይጀምራል።“ጌታዬ ችግር አለ? መስተንግዶዋችን አልተመ ቸዎትም? ምን እናስተካክል?” እያለ ትህትና የተላበሱ ተከታታይ ጥያቄዎችን ያቀርባል። ሰውዬው ፈገግታ በተሞላበት መንገድ ምላሹን ሰጠ። “አይ መስተንግዶዋችሁም በጣም ጥሩ ነው፤ ነገር ግን እኔ መጠጥ አልጠጣም” ይለዋል። ይሄኔ ኃላፊው ተገርሞ “እንዴ ለምን?” ብሎ ጠየቀው። ለዚህ ምላሽ ግን የሰጠው መልሶ እራሱን በመጠየቅ ነበር። “እስኪ ለኔ ልትሰጠኝ ካሰብከው ፊት ለፊት ባለው በር ከፍተህ ግባና ለፓይለቱ ስጠው በኔ ፋንታ ይጠጣ” ብሎ ጠቆመው።ይሄኔ ኃላፊው “እንዴ! እሱማ እንዴት ይጠጣል? ይሄን ማደረግማ አይችልም የስንት ሰዎችን ህይወት አደጋ ላይ ሊጥል ይችላል። ስለዚህ እሱ የመጠጥ ሽታም ሊደርስበት አይገባም።” በማለት ፓይለቱ በመጠጣቱ ሊደርስ የሚችለው አደጋ ዘረዘረ። ተጓዡም የሚፈልገው እንዲህ እንዲለው ነበርና በመልሱ ላይ የራሱን አስተያየት በማከል የማይጠጣበት ምክንያት ተናገረ። “ወዳጄ እኔ የራሴ የሆነ ልዩ ዓላማ አለኝ አላማዬን ከስኬቱ እንዳደርስ ጥንቁቅ መሆን አለብኝና “ፈፅሞ አልጠጣም” ያልኩት ለዚህ ነው። በማለት መለሰለት።እናም ዓላማ ያለው፤ እሩቅ መጓዝ ያሰበ እርግጥም እራሱን ሆኖ የትኛውም ቦታ ይደርሳል። ሰሞኑን የወጣውን የኤክሳይዝ ታክስ ተከትሎ በመጠጥና በዘር ማንዘሮቹ፤ በሲጃራና በግብረ አበሮቹ ላይ የተደረገውን የታክስ ጭማሪ ጥቅም በትክክል ከተረዳን ጠጪዎችንና አጫሾችን ቢያስከፋም እነሱኑ የሚያድን መራራ መርፌ ነው። እናም በደንብ መውጋት/መወጋት ነው። ኧረ እንዲያውም ከፍ አድርጎ። ቸር ይግጠመን!አዲስ ዘመን የካቲት 16 / 2012 ዓ.ም ተገኝ ብሩ
https://www.press.et/Ama/?p=27729
614
1መዝናኛ
ሱራ ሱራ !
መዝናኛ
February 27, 2020
30
ሱራ ሽቅብ ሽቅብ ያቃስታል። ግዝፈቱ ያስጨንቀዋል። ልብስ አይበቃውም። የጫማው ቁጥር 48 ነው። የትከሻው ስፋት የሰውነቱ ግዝፈት የቁመቱ ርዝመት የሰማይ ስባሪ አስመስለውታል። አባ ግድየለሽ ሱራ ወግ ጨዋታ ይወዳል። ሰው አያስቀይምም። ውፍረቱ አስፈሪ አስደንጋጭ ነው።የሰፈሩ ሰው ልጆች ሲያለቅሱና ሲረብሹ ዋ ሱራን ነው የምንጠራው ሲባሉ ያውቁታልና በፍርሀት ርደው ጭጭ ነው የሚሉት። ሲደሰትም ሲከፋም ሱራ የአላህ ልጅ፤ የአላህ ወዳጅ የሚለው ነገር አለው። ለወላጆች ምነው ምነው ሕጻናቱ እንዲጠሉኝ እንዲፈሩኝ ባታደርጉ ምን አደረኳችሁ ይላል – ሱራ። በዛ ቁመቱና ውፍረቱ ሲንጎማለል ሲታይ የሞላለት ቱጃር ይመስላል። ጫማ ሰፊው ሱራ በቀን ሰርቶ ከሚያገኘው ውጭ ምንም የለውም። እጁ ሲያጥር ደምበኞቹ ከሆኑት ሴቶች ይበደራል። የድሀ ገንዘብ አታድርገኝ ይላሉ – እማማ ጌጤ። ከቀናት በኋላ ሴቶቹ ከች ይሉና ብር መልስ ይሉታል። አንተ ሱራ ስማ እንጂ የተበደርከውን አታመጣም፤ አላበዛኸውም እንዴ እያሉ ሴቶቹ ወገባቸውን ሲነቀንቁበት ይጨነቃል። ሂጂ እዛው ምን ወገብሽን ትሰብቂያለሽ ይላል ሱራ፤ ሶርሷራው። ተናገር ምንድነው ሂጂ እዛው አንተ አይደለህም እንዴ ስንቱን … ይሉታል። ኧረ በሕግ አምላክ ስሜን አታጥፉ አልደረስኩባችሁም ይላል እንደ ማፈር ብሎ።ጫማው መስፊያ ጎን ያሉት እማማ ጌጤ ይቺ ሙጢ አሁን እውነት ሱራ ቢጠጋት ትተርፋለች፤ ሹል አፍ ሙጢ እንደው መቀላመድ ትወዳለች ልጄ አሉና አጉተመተሙ። የመንደሩ ሴቶቹ የተቦተረፈ ጫማቸውን ይዘው ስፋልን እያሉ የሚወስዱት ለሱራ ነው። ብዙ የሴት ወዳጆች አሉት። አንዳንዶቹ የሚበላው ቋጠር አድርገው ያመጡለታል። አላህ እናንተን ባይጥልልኝ ኖሮ ምን እሆን ነበር ይላል ሱራ። ሱራ የሰማይ ስባሪው ሲሉት እናንተ ኮስማኖች በልታችሁ አይጠጋችሁ፤ ነገር ስትበሉ ውላችሁ ታድራላችሁ ፤ታዲያ ሱራ ምን ያድርጋችሁ ይላል። መኖሪያ ቤቱ የቀበሌ ቤት ነች። ግን ማንንም አያስገባም። ቤት ውሰደን ሱራ ሲሉት ደሞ ምን ቀራችሁ፤ ከእኔ ቤት ምን ጉዳይ አላችሁ ይላል። ቤት እየመጡ እሱ ሲሰራ እየተቀመጡ በዚህ መዘዝ ድሮ ምን እንደመጣበት ሱራ ሲያስታውሰው ይዘገንነዋል። ራሱ አብስሎ ይመገባል። አንዳንዴ በጎርናና ድምጹ ያንጎራጉራል። ሱራ የአላህ ወዳጅ… የአላህ ልጅ እያለ። ተናግረው ሊያናግሩት ሲነካኩት አሁን ከእኔ ምን ታገኛላችሁ ተውኝ ስራ የላችሁም ይላል። ጫማ መስፋቱን ይቀጥላል። ይህን ዝምታ የወረሰው በደርግ ዘመን ከደረሰበት ችግር በመነሳት ነው። በማያውቀው ነገር ሊሞት ነበር። ጫማ የሚሰፋባት አንዲት ክፍል የኪራይ ቤት ነበረችው። ከበውት የሚውሉ የሚያመሹም ነበሩ።ፖለቲካ አይወድም። እሱ ጋ የሚገቡና የሚወጡት ወጣቶች በዛን ዘመን ኢህአፓዎች ነበሩ። ወረቀት የሚበትኑ፤ ግድግዳ ላይ ቀለም የሚቀቡ፤ በቀይ ቀለምና በቀይ ጨርቅ ሀገሩን የሚያሸበርቁ። በፌስታል አምጥተው ሱራ የማያውቀውን እቃ ወረቀት ምናምን አመጣን ሱራየ ይቺ እዚህ ጋ ትቀመጥ ሲሉት ሱራ በመጡ ሰአት ተመልሰው ይወስዱታል እያለ ጫማውን መስፋት ይቀጥላል። የሚያውቀው ነገር የለውም ምስኪኑ ሱራ። እቃቸውን አይነካም። ተጠራጥሮም አይሸፍንም። በል ሲለው ያንጎራጉራል። ሱራ የአላህ ወዳጅ የአላህ ልጅ የምትለዋ ቃል ከአፉ አትጠፋም። በዚህ ይታወቃል። ጊዜው 1969ዓ.ም ነው። አዲስ አበባ መርካቶ አካባቢ። ሀገር ምድሩ ታምሷል። አንድ ቀን ቀበሌው የኢሕአፓ ወጣቶችን እያሳደደ ማሰር ሲጀምር እንዴ እነሱማ ተሰብስበው የሚውሉት ሱራ ጫማ ሰፊው ቤት ነው የሚል ጥቆማ አብዮት ጠባቂዎች ይሰጣሉ። ይታሰር ተብሎ ጠመንጃ ተሸክመው ሱራ ጋ ይሄዳሉ። ሱራ አይሞቀው አይበርደው አባ ግዴለሽ። እንደውም ቤቱ ይከበብ ተብሎ ከውጭ ብዙ ጥበቃዎች ይከቡታል። ሱራ ጫማውን አቀርቅሮ ይሰፋል። መሳሪያ ደግነው ዘው ብለው ገቡ። እጅ ወደ ላይ አሉት። ሱራ የአላህ ወዳጅ አለና ጠመንጃው ምን ያደርጋል ለአንድ ድሀ ጫማ ሰፊ የእኔ እጅ ስራ ይዟል ለምንድነው እጄን ወደላይ የማደርገው በእንጀራዬ ለምን መጣችሁ ይላቸዋል። ና ውጣ አንተ ኢህአፓ አሉት። ሱራ መለሰ ምንድነው ኢሕአፓ አላቸው። እሱንማ አንተ ታውቃለህ በደምብ ትመልሳለህ አሁን እስረኛ ነህ ና ውጣ ቀበሌ እንሂድ አሉት። ተውኝ ቢል ማን ሰምቶት። እያመረሩ ሄዱ። ሌሎች ሱራ ቀበሌ ሂድላቸውና ቃልህን ስጥ ምን ትሆናለህ አሉት። ሱቁን ቆለፈና በብዙ አብዮት ጠባቂዎች ታጅቦ የሠማይ ስባሪው ሱራ ቀበሌ ጽህፈት ቤት ገባ። ግቢው ውስጥ እሱ ጋ ገባ ወጣ ከሚሉት ወጣቶች ውስጥ የታሰሩ እንዳሉ አየ። ጮክ አለና ምን ሰርቃችሁ ነው የተያዛችሁት አላቸው። አብዮት ጥበቃዎቹም ወጣቶቹም ሳቁ። ሱራ ለምርመራ ገባ። ጠያቂዎቹን ያውቃቸዋል። የጫማ ደምበኞቹ ናቸው። ጫማቸው ሲቀደድ የሚሰፋላቸው።ሱራ አንተም አሉት። ተገረመና ምን አላቸው። ኢህአፓ አሉት። ምንድነው የምትሉት እሱን ሰውየ አላውቀውም። ቅድምም አብዮት ጥበቃዎቹ እንደሱ አሉኝ። የእኔ የጫማ ደምበኛ አይደለም። አሰርቶ አያውቅም። እኔም አላውቀውም አላቸው። ሱራ የአላህ ወዳጅ የአላህ ልጅ አለ ሰው በተሰበሰበበት። እስኪጣራ ታስረህ ትቆያለህ አሉት። ክፉኛ አዘነ። አላህ እንደ ስራየ ይስጠኝ፤ በተንኮል ለወነጀሉኝም ፍርዱን ይስጥ አለ- ደገመና። እስር ቤቷ ውስጥ ግዙፉ ሱራ አንገቱን አዝምሞ ገባ። ታሳሪው በተጨናነቀው ቤት ውስጥ ለሱራ ተጣበው ቦታ ሰጡት። ግድግዳውን ደገፍ ብሎ እንደቆየ ድብን አድርጎ እንቅልፍ ወሰደው። ማንኮራፋት ጀመረ።ቢጠሩት መች ሰምቶ። ለሊቱን እነዛን ልጆች ወደማይታወቅ ስፍራ ወስደዋቸዋል። ሲነቃ ልጆቹ የሉም። የሰፈሩ ሰው ሱራ ቀበሌ መታሰሩን ሲሰማ በእጅጉ አዘነ። ከፊሉ አሽሟጠጠ። ደሞ ሱራ ብሎ ፖለቲከኛ እያለ። ጠጅ ቤት መነጋገሪያ ሆነ። ሱራ ታሰረ— ሱራ ታሰረ — ባዩ በዛ። የሰፈሩ ሰው ጫማ የሚሰፋላቸው ሴቶች እየተጋገዙ ምግብ ያቀብሉት ጀመር። ቀለብ የማያገኙት እስረኞች ረሀባቸው ጠፋ። ሱራ ሱራ አሉት አቤት አላቸው። እንኳን ታሰርክ እንዲያውም መውጣት የለብህም አሉት። ተንከትክቶ ሳቀ። አንተ በመታሰርህ እስር ቤቱ ምግብ በምግብ ሆነ ሲሉት ቀበል አደረገና እኔ ፖለቲካ አላውቅም። ጫማ ሰፊ ነኝ። እኔን በሀሰት በወነጀሉኝ ሰዎች ላይ አላህ ፍርድ ይስጥ፤ ሱራ የአላህ ወዳጅ የአላህ ባሪያ አለና አይኖቹ በእምባ ተሞሉ። አይዞህ ሱራ አሉት። አይዞህ አይዞህ ሱራ። ለሊት በቀበሌያቸው አካባቢና ዙሪያ የቀለጠ ተኩስ ተሰማ። እስረኞቹ በተኙበት ይሰማሉ። ሱራ አላህ –አላህ ይላል። የመትረየሱ ድምጽ ተረረረረረም ሲል ሱራ አላህ ድረስ፤ የታሰሩት ልጆች አውጣን አውጣን ሆነ። አይነጋ የለም በጭንቅ ነጋ። ጠዋት ለሽንት ሊወጡ ሲሉ ሱራ ነበር የቀደመው። ያገኛቸውን ሰዎች ምንድነው ጉዱ አላቸው። መጥተው ፈጅተውን ሄዱ፤ አመለጡ አሉት። እነማን ናቸው አላቸው – ሱራ። ኢህአፓዎቹ ናቸዋ አሉት። ሰው ተጎዳ ብሎ ጠየቀ። ምን ሰው ተረፈ ብለህ ነው። በቀደም አንተን ከሱቅህ አስረው ያመጡህ በሙሉ ሞተዋል አሉት። ምን አለ ሱራ ደንግጦ። ደገመና ሱራ የአላህ ወዳጅ የአላህ ልጅ። እቺ ኢህአፓ የምትሏት አላህ ነች እንዴ አለ ሱራ። ሰዎቹ በሳቅ አሽካኩ። ሱራ ሱራ።ወንድወሰን መኮንንአዲስ ዘመን የካቲት 19/2012
https://www.press.et/Ama/?p=27990
819
1መዝናኛ
የአርባ ሰባት ዓመታት ትዝታ የቀሰቀሰው ቀለበት
መዝናኛ
February 25, 2020
68
 ብዙ ጊዜ ጌጣጌጦች ጠፉ ሲባል ቢሰማም ፈልጎ የማግኘቱ ጉዳይ እንደ መግዛቱ ቀላል አይሆንም። በተለይ የወርቅ ጌጣ ጌጥ ጠፍቶ የመገኘት እድሉ ጠባብ ነው።ወርቅ ውድና ተፈላጊ እንደመሆኑ ያገኘውም ሰው ቢሆን የጠፋበትን ባለቤቱን አፈላልጎ ይሰጣል ብሎ መጠበቅ የዋህነት ነው።ሊገኝ የሚችልበት እድል አንድና አንድ ብቻ ነው። ሰው እጅ ያልገባ ከሆነ ብቻ።ይህ ሲሆን ከእለታት አንድ ቀን ሊገኝ ይችል ይሆናል። የጌጣጌጦች መጠን አነስተኛ መሆን ከሚጠፉበት ቦታ ውስብስብነት ጋር ተዳምሮ የመገኘት እድላቸውንም በእጅጉ ያጠበዋል። በዚህም የጠፉት ጌጣጌጦች ከናካቴው ተሰውረው ሊቀሩ አልያም ጥቂት ጊዜ ፈጅተው ባጋጣሚ ሊገኙ ይችላሉ ።ጌጣጌጦች ከጠፉ ረጅም አመታትን አስቆጥረው ሲገኙ ግን ግርምትን ያጭራሉ። ስካይ ኒውስ ከሰሞኑ ከወደ አሜሪካ ይዞት ብቅ ያለው መረጃም ይህንኑ ሃቅ ያረጋግጣል። በ1973 ገና አፍላ ወጣት የነበረችው ዴብራ ሜኬና ብረንስዊክ ሜይን በተሰኘችው የአሜሪካ የባህር ዳርቻ ከተማ በሚገኝ አንድ የእቃ ማስቀመጫ ክፍል ውስጥ ባሏ ያደረገላትን ቀለበት ትጥላለች። ቀለበቱ ከጠፋ ከአርባ ሰባት አመታት በኋላም በቅርቡ በአንድ የብረት ሰራተኛ በፊንላንድ ደን ውስጥ ተቀብሮ ተገኝቷል። ሜኬና በአሁኑ ወቅት 63 ዓመቷ ሲሆን፣ በሞርስ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪ እያለች በፖርትላንድ ውስጥ ቀለበቱ እንደጠፋባት ባንጎር የተሰኘው ጋዜጣ በወቅቱ ዘግቦ እንደነበር ድረገጹ አስነብቧል። ትምህርት ቤቱን የሚለይ ምልክት ያለበት ይኼው ቀለበት የቀድሞ የሜኬን ባል በትምህርት ቤትና በኮሌጅ ተገናኝተው ሲያወሩ ያበረከተላት እንደነበር ታውቋል። ባለቤቷ ሻውን ለስድስት አመታት ያህል ከያዘው የካንሰር ህመም ጋር ሲታገል ቆይቶ በ2017 ህይወቱ እስካለፈበት ጊዜ ድረስ ባልና ሚስቶቹ ለአርባ አመታት ያህል በትዳር መቆየታቸውም ተጠቅሷል። ሸዋን የኮሌጅ ትምህርቱን ሳያጠናቅቅ ቀለበቱን ለሜኬን የሰጣት ሲሆን፣ ሆኖም መጋዘን ውስጥ በድንገት እንደጣለችው አስታውሳለች።የብረት ሰራተኛው ቀለበቱን ከተቀበረበት እስካገኘበት ጊዜ ድረስ ተረስቶ እንደነበርም ገልፃለች። የብረት ሰራተኛው ሰማያዊ ፈር ያለውን ብራማ ቀለበት ሲያገኝ የብረት መመርመሪያ ተጠቅሟል፤ ብዙ ጊዜ ያገኝ የነበረው ግን የብረት ኩባያ ወይም ቁራጭ ብረት እንደነበረም የፊንላንድ ሚዲያ ዘግቧል። በቀለበቱ ላይ የተፃፈውን የትምህርት ቤት ምልክትና የምርቃ አመተ ምህረት በመያዝ አልሙኒ ከተሰኘ ማህበር ጋር እንደተገናኘም ሚዲያው ጠቅሷል። በዚሁ መሰረት መኬን ከረጅም አመታት በፊት የጠፋባት ቀለበት እንደተገኘና መውሰድ እንደምትችል በስልክ ሲነገራት እምባ እንደተናነቃትና የወጣትነት የፍቅር ጊዜዋን እንዳስታወሳት ገልፃለች። ‹‹ቀናነት በጎደለበት በዚህ ዘመን እንደዚህ አይነት ሰዎችን ማግኘት በጣም ይከብዳል›› ስትልም ተደምጣለች። ‹‹በአለማችን ጥሩ ሰዎች አሉ፤ ስለዚህ ተጨማሪ ጥሩ ሰዎችን እንፈልጋለንም›› ብላለች። ሜኬና ከጠፋ ረጅም አመታትን ያስቆጠረው ቀለበት እንዴት በፊንላንድ ደን ውስጥ ሊገኝ እንደቻለ ምንም የምታውቀው ምክንያት እንደሌለ አስታውቃለች። ምን አልባት ባለቤቷ ሹዋን በ1990ዎቹ አካባቢ አብዛኛውን ጊዜውን በፊንላንድ ያሳልፍ በነበረበት ወቅት እሱን ብላ ስትሄድ ቀለበቱ አካባቢው ላይ ሳይጠፋ እንዳልቀረ ጠቅሳለች። አዲስ ዘመን የካቲት 17/2012አስናቀ ፀጋዬ
https://www.press.et/Ama/?p=27863
357
1መዝናኛ
ኮሮና ቫይረስን በአሻንጉሊት
መዝናኛ
February 25, 2020
49
የኮሮና ቫይረስ በተለያዩ የአለም ክፍሎች እየተስፋፋ መምጣቱን ተከትሉ ህዝቦች በከፍተኛ ስጋት ውስጥ ወድቀዋል። አለም አቀፍ የሰዎች እንቅስቃሴም እንደወትሮው ሊሆን አልቻለም። በተለይ ደግሞ የቫይረሱ መገኛ በሆነችው ቻይና ሰዎች ቫይረሱ እንዳይዛቸው በተቻላቸው አቅም ሁሉ ራሳቸውን ለመከላከል ጥረት እያደረጉ ይገኛሉ። ከሰሞኑ በሀገሪቱ ደቡብ ምእራብ ሲሽዋን ግዛት በሚገኝ አንድ ሆስፒታል ህሙማንን ለመጎብኘት የመጣችና ስሟ ያልተጠቀሰ አንዲት ወይዘሮ ራሷን ከኮሮና ቫይረስ ለመከላከል ያደረገችው ጥረት ግን ብዙዎችን አስፈግጓል ሲል ኦዲቲ ሴንትራል በድረገፁ አስፍሯል። በማህበራዊ ትስስር ገፅ በተለቀቀው በዚህ አጭር ቪዲዮ ወይዘሮዋ ከፊትለፊት ለማየት የሚያስችል አነስተኛ የመስታወት መስኮት ያለው ግዙፍ የቀጭኔ ቅርፅ ያለው የፕላስቲክ አሻንጉሊት ልብስ ለብሳ በሆስፒታል ውስጥ ስትንቀሳቀስ ትታያለች። ‹‹ለምን ይህን ግዙፍ የፕላስቲክ ቀጭኔ አሻንጉሊት ልብስ ለበሽ? የሚል ጥያቄ ይቀርብላታል። ወይዘሮዋ የኮሮና ቫይረስ በቻይና ከመከሰቱ በፊት አባቷ በመተንፈሻ አካል ችግር በሆስፒታሉ ብዙ ጊዜ ህክምና ሲከታተሉ አጥብቃ ትጠይቃቸው እንደነበር አስታውሳ፣የኮሮና ቫይረስ ከተከሰተ በኋላ አባቷን መጠየቋን አቁማ መቆየቷን ተናግራለች። በቅርቡ ግን ይህች ወይዘሮ አባቷን ለመጠየቅ ወደ ሆስፒታሉ ትመጣለች። በወቅቱም ሃኪሞች ፊቷን እንድትሸፍንበት የህክምና ጭምብል ይሰጧል።እሷ ግን ጭምብሉ የአገልግሎት ጊዜው ያለፈበት ነው በሚል ስጋት የኮሮና ቫይረስን በአስተማማኝ መልኩ ለመከላከል ግዙፉን የቀጭኔ አሻንጉሊት ልብስ ለመልበስ እንደወሰነች ገልፃለች። ‹‹ሃኪሞቹ የሰጡኝ የህክምና ጭምብል የአገልግሎት ጊዜ ያለፈበት ነው። በገበያ ላይም እንደልብ አይገኝም። በመሆኑም አሻንጉሊቱን ለመልበስ ተገድጃለሁ›› ስትልም ወይዘሯዋ ተናግራለች። ይህን እንግዳ ድርጊት የታዘቡት የሆስፒታሉ ሰራተኞችም ቪዲዮ በመቀረፅና በማህበራዊ ትስስር ገፅ በመልቀቅ በርካታ ቻይናውያን ፈገግ አሰኝተዋል። አዲስ ዘመን የካቲት 17/2012አስናቀ ፀጋዬ
https://www.press.et/Ama/?p=27860
208
1መዝናኛ
ዝም ስንል
መዝናኛ
February 24, 2020
26
አቶ አንድአርጋቸው የ75 አመት እድሜ ባለፀጋ ነበሩ። እኝህ አዛውንት ደስተኛ ሆነው የሚኖሩና በጣም የሚያስቀና ቤተሰብ ያላቸው ሰው ነበሩ። ከብዙ አመታት በኋላ ልጆቻቸው አድገው የራሳቸውን ኑሮ በመመስረት ወደ ተለያየ አካባቢ ሄዱ። ባለቤታቸው እና የልጆቹ እናት ከብዙ አመታት በፊት በሞት ስለተለየቻቸው በመንደሩ ውስጥ በብቸኝነት እና በሀዘን ብዙ ጊዜያቸውን ያሳልፉ ጀመር። አቶ አንዳርጋቸው አብዛኛውን ጊዜያቸውን በብቸኝነት ቢያሳልፉም፤ የልጅ ልጆቻቸው በአመት በአል እና በእረፍት ጊዜያቸው አያታቸውን ሊጠይቁ ይመጡ ነበር። በዚህ ወቅት እጅግ ደስተኛ እና ተጫዋች ይሆኑ ነበር። በአንደኛው እለት አቶ አንዳርጋቸው ቀጣዩን ቀናቶች ደስተኛ ሆኖ የሚያሳልፉበት ጊዜ ተፈጠረ። ምክንያቱም አራቱ የልጅ ልጆች ሊጠይቋቸው የሚመጡበት ወቅት በመሆኑ ነበር። የልጆቹን መምጣት በጉጉት ሲጠብቁ የነበረው አዛውንት ቤቱን ማፅዳት፣ እቃዎቹን በአዲስ መልክ ማስተካከል፣ የአትክልት ስፍራዎቹን ማሰማመር ጀመሩ። ምክንያቱም እነሱን ሊጠይቋቸው የሚመጡት ልጆች ደስተኛ እንዲሆኑ ስለሚፈልጉ ነበር። የልጅ ልጆቹ የሚወዱትን የምግብ አይነትም አዘጋጅተው ይጠብቋቸው ነበር። በዚህ ጊዜ ሚስቱ ከመሞቷ በፊት የሰጠችውን «የእጅ ሰአት» ባጋጣሚ ጣሉ። ሆኖም ግን ሰአቱን ከእጃቸው ላይ መጥፋቱን ማስተዋል አልቻሉም። ሚስታቸው ከሞተች በኋላ ሰአቱን በጣም ነበር የሚወዱት ከእጃቸው ላይም እንዳይጠፋ በጣም ይጠነቀቁ ነበር። በልጅ ልጆቻቸው መምጣት በጣም ደስተኛ የሆኑት የእድሜ ባለፀጋ የሰአቱን ከእጃቸው ላይ መጥፋት ሳያስተውሉ ለቀጣዮቹ ሁለት ቀናት በደስታ እና በጨዋታ አሳለፉ። በሶስተኛው ቀን ግን ሰውነታቸውን ለማፅዳት መታጠቢያ ቤት ሲገቡ ከእጃቸው ላይ እንደሌለ ተገነዘቡ። በጣም በማዘንም እንደ አይናቸው ብሌን የሚሰስቱትን ሰአት በመጣላቸው ተበሳጩ። ለመጨረሻ ጊዜም የት ቦታ አድርገውት እንደነበር ለማስታወስ ሞከሩ። ቤቱን ለማፅዳት ሲሞክሩ ሊጠፋ እንደሚችልም ገመቱ። በግቢው ውስጥ የሚገኝ የእቃ ማከማቻ ቤት ውስጥ ሊሆን እንደሚችልም ጠርጥረው እዛው ለመፈለግ ወሰኑ። በአያታቸው ግራ መጋባት እና መናደድ የተገረሙት ልጆች፤ ምን እንዳጋጠማቸው ጠየቋቸው። እሳቸውም « ከአያታችሁ የተሰጠኝን እና በህይወቴ ትልቅ ግምት የምሰጠውን ሰአቴን ጣልኩት፤ ልክ ልቤን እንደጣልኩት ነው የሚሰማኝ። ይመስለኛል እቃ ማከማቻ ቤት ውስጥ የጣልኩ ይመስለኛል » በማለት ነገራቸው። ልጆቹም በሁኔታው ማዘናቸውን በመግለፅ፤ በፍለጋው እንደሚተባበሩ ገለፁላቸው። ልጆቹ እና አያታቸው አላስፈላጊ እቃ በብዛት የሚከማችበት ቤት ውስጥ ሊገኝ እንደሚችል ወስነው ፍለጋቸውን ቀጠሉ። ሰአቱን ለማግኘት ሁሉንም እቃ ለማየት ሙከራ አደረጉ። ሆኖም ግን የጠፋውን የእጅ ሰአት ሊያገኙት አልቻሉም። ያረጁ መፅሀፍት፣ ወንበር፣ ጠረጴዛ እንዲሁም በርካታ ቁሳቁሶች በቤት ውስጥ ተከማችቶ ስለነበር ፍለጋቸውን አስቸጋሪ አድርጎባቸው ነበር። ለ ሁለት ሰአታት ያክል ሲፈልጉ ቆይተዋል። በሁኔታው እጅግ ያዘኑት አቶ አንዳርጋቸው የልጅ ልጆች ፍለጋቸውን ማቆም እንደሚኖርባቸው አስረዷቸው። ውዱን ሰአት ከእንግዲህ ሊያገኙ እንደማይችሉ ተገንዝበው ነበር። ልጆቹም በሁኔታው በጣም አዘኑ። ሆኖም ግን አያታቸው በተፈጠረው ሁኔታ እንዳያዝኑ በተቻላቸው መጠን ሊያፅናኑን ሞከሩ። ከልጅ ልጆቹ አንደኛዋ የሆነችው እና ፅጌ የምትባለዋ አስተዋይ ልጅ፤ አስቀድመው ሁሉም የእጅ ሰአቱን ሲፈልጉ የነበረበት ቤት ተመልሳ ትሄዳለች። በሁኔታው የተገረሙት አያቷ እና ወንድሞቿ ይህንን ለምን እንደምታደርግ ይጠይቋታል። ምክንያቱም እስኪሰለቻቸው ድረስ ሰአቱን ለማግኘት ሙከራ አድርገው አልተሳካላቸውም ነበር። ፅጌም ወንድሞቿ እና አያቷ ወደ እቃ ማከማቻው ቤት ሲሄዱ እንዳይከተሏት ነግራቸዋለች። ምንም አይነት ድምፅም እንዳያሰሙ ታስጠነቅቃቸዋለች። በሁኔታው የተገረሙት ወንድሞቿ እና አያቷም ፍላጎቷን ለማሳካት ይስማማሉ። ፅጌ በዝግታ ወደ እቃ ቤቱ አመራች። በሩን ከፍታም ወደ ቤቱ አንደኛው ጥግ በማምራት ያገኘችው መቀመጫ ላይ ለ25 ደቂቃዎች በቤቱ ውስጥ ከተቀመጠች በኋላ አያቷ እና ወንድሞቿ ወደሚገኙበት አካባቢ አመራች። ሁሉም ግን ከፊት ለፊታቸው በሚያዩት ነገር ተገርመው ነበር። ምክንያቱም ፅጌ ለሁለት ሰአት ያክል ለፍተው ሲፈልጉት የነበረውን የአያታቸውን ሰአት ማግኘት ችላ ነበር።አቶ አንዳርጋቸው በፍቅር የሚወዷት ባለቤታቸው የሰጠቻቸው ሰአት በመገኘቱ እጅግ በጣም ደስተኛ ነበሩ። አገኘዋለሁ ብሎም አልገመተም። ከምንም ነገር በላይ የባለቤታቸው ስጦታ እስከ ህይወታቸው ፍፃሜ እንዲቆይ ፍላጎታቸው ነበር። በሁኔታው በጣም የተደሰቱት አያቷም፤ ፅጌን ሰአቱን እንዴት እና የት ቦታ ላይ እንዳገኘችው ጠየቋት። ፅጌ ለአያቷ እንዲህ ስትል መለሰች «አያቴ በበጋ ወራት ትምህርት ቤት በጣም የምንወደው አስተማሪያችን ሁል ጊዜ ዝም የማለት ጥቅሞችን ይነግረናል። ሁሌ ባይሆንም አንዳንድ ወቅት ዝምታ አስፈላጊ መሆኑን ያስረዳናል። ለምሳሌ እሱ ሲያስተምር በጥሞና እንድናዳምጠው ይመክረናል» በማለት መለሰችለት። አያቷም ግራ በመጋባት መንፈስ « ታዲያ ይሄ ከእጅ ሰአቱ መገኘት ጋር ምን አገናኘው?» ሲሉ ጠየቋት። ፅጌ ለአያቷ ጥያቄ በድጋሚ ምላሽ ሰጠች «አያቴ የእጅ ሰአቱን ስንፈልግ እየተጯጯህን እና እቃዎችን ከወዲያ ወዲህ እያንኳኳን ነበር። ትንሽ በመሆኑም የት ቦታ ተደብቆ እንደነበር ለማወቅ አልቻልንም። ሆኖም ግን እኔ ለሁለተኛ ጊዜ ስሄድ ብቻዬን ነበርኩ። እቃዎቹን በማንኳኳትም ልፈልገው አልሞከርኩም። ቁጭ ነበር ያልኩት። ምክንያቱም የእጅ ሰአቱ ሲቆጥር «ቲክ… ቲክ… ቲክ…» የሚል ድምፅ ያሰማ ነበር። ዝም በማለቴም ይህንን ድምፅ መስማት ችያለሁ» በማለት በፈገግታ በመሞላት አስረዳቻቸው። አያቷም በሁኔታው በመደነቅ አቅፈው ግንባሯን በመሳም አመሰገኗት። በዝምታና በጥሞና ነገሮችን መከታተል፤ ረጋ ብሎ ሁሉንም ነገር ማየትና መመርመር ትክክለኛ ውሳኔ ላይ ለመድረስ እንደሚያስችልም ለሁሉም አስተማረች። አሁን በሀገራችን ያለው ሁኔታም ይሄንን የሚጠይቅ ነው። አዲስ ዘመን የካቲት 15/ 2012  ዳግም ከበደ
https://www.press.et/Ama/?p=27792
645
1መዝናኛ
አማራጭ ሃሳብ አምጡ!
መዝናኛ
March 1, 2020
27
ከብዙ ጊዜያት በፊት በአንድ አገር ውስጥ የሚኖሩ ማህበረሰቦች ነበሩ። እነርሱንም የሚያስተዳድር አንድ ንጉሥም ነበር። ይህ ንጉሥ የሚያስተዳድራቸውን ነዋሪዎች በደስታ ያኖራቸው ነበር። በእሱ የአገዛዝ ዘመን ሁሉም ነዋሪዎች በነፃነት ተገቢውን ነገር በማድረግ በሰላም ኑሯቸውን ይመራሉ። ንጉሣቸው እርሱ በመሆኑም በጣም ደስተኞች ነበሩ። በአንድ ወቅት ንጉሡ በአገሪቷ ላይ የሚገኙ ታሪካዊ ቦታዎችን፣ የአምልኮ ስርዓት የሚፈፀምባቸው ቤተክርስቲያናትን እንዲሁም እርሱ በአገዛዙ ወቅት ያልተመለከታቸውን እና በርቀት ያሉ አካባቢዎችን ለመመልከት ይወስናል። እዚህ ውሳኔ ላይ የደረሰው እርሱ የሚያስተዳድራቸውን ቦታዎች ለማወቅ እና ሁሉም ስፍራዎች ምቹ እና የማህበረሰብ ክፍሎችም በሰላም እና በተድላ መኖራቸውን ለማረጋገጥ ስለፈለገ ነበር።ንጉሡ ጉብኝቱን በእግሩ በመጓዝ ለማድረግ ይወስናል። አገልጋዮቹን እና አብረውት የሚጓዙ ቤተሰቦቹንም ከእርሱ ጋር በእግራቸው እንዲጓዙ አደረገ። ንጉሡ ይህንን ለማድረግ የወሰነበት ምክንያት በቀላሉ የሚያስተዳድራቸውን የማህበረሰብ ክፍሎች እንዲያገኝ ስለሚያስችለው ነበር። በዚህ የተነሳ እርሱ ጉብኝት በሚያደርግባቸው አካባቢዎች የሚያገኛቸው የማህበረሰብ ክፍሎች ንጉሣቸውን በማግኘታቸው እና ከእርሱም ጋር በማውራታቸው ፍፁም ደስተኛ ሆኑ። እነርሱ በዚህ ንጉሥ ስር ስለሚተዳደሩ እና ቅን ልቦና ያለው መሪ ስላላቸው ደስተኞች ሆኑ። ይህ ቅን ንጉሥ በርካታ የአገሩን አስደናቂ ቦታዎች መመልከት ቻለ። ታሪካዊ ቦታዎችን፣ የእምነት ስፍራዎችን በተፈጥሮ የተዋቡ አካባቢዎችን እንዲሁም በርካታ ባህል ያላቸው የማህበረሰብ ክፍሎችን ማግኘት በመቻሉ በጣም ደስተኛ ሆነ። አገሩ እጅግ የበለፀገች በመሆኗም የሚያምነውን አምላክ አመሰገነ። ይህ ንጉሥ በሚደርስበት አካባቢ ሁሉ እጅግ በከበረ ሁኔታ አቀባበል ይደረግለት ነበር። ነዋሪዎቹም ቅን እና ለማህበረሰቡ ከልቡ አሳቢ በመሆኑ እጅ እየነሱ ያመሰግኑታል። ከብዙ ቀናት የጉብኝት ቆይታ በኋላ ጉብኝቱን አጠናቀቀ ወደ መኖሪያ ስፍራውም ደስተኛ ሆኖ ተመለሰ። እርሱ የሚያስተዳድራቸው ሰዎች በተድላ እና በደስታ መኖራቸውንም በዓይኑ አይቶ መመስከር ቻለ። ሁሉም ነዋሪዎች ኑሯቸውን ያለምንም ችግር ይመሩ ነበር። አብዛኞቹ በግብርና ሥራ፣በከብት ማርባት እና በብረታብረት ምርት ላይ አድርገው ነበር። ኑሯቸውን የሚያቀልላቸው አዳዲስ ማሽኖች ይፈጥሩ እና ይገለገሉባቸውም ነበር። ነገር ግን ይህ ንጉሥ በጉብኝቱ ወቅት አንድ ያዘነበት እና ቢስተካከል ብሎ ያሰበው ጉዳይ ነበር። ረጅም ርቀት በመጓዝ ጉብኝት ባደረገበት ወቅት እግሩን በጣም ታሞ ነበር። እግሩን የሚከላከልለት ምንም ነገር ስላልነበረም በጣም ለሚያስጨንቅ ህመም ተዳርጓል። የውስጥ እግሩም ቆስሎ መሬት ለመርገጥ በጣም ተቸግሮ ለትንሽ ጊዜም ቆየ። ባለሟሎቹ እና ቤተሰቦቹ በተፈጠረው ነገር በጣም በማዘን በቶሎ እንዲያገግም ዕርዳታ ያደርጉለት ጀመር። ከህመሙ እንዳገገመ አንደኛውን ሚኒስትሩን በመጥራት ስለተፈጠረው ነገር አናገረው። እንዲህም አለው «አገሪቷ ላይ ያሉትን ታሪካዊ፣ ተፈጥሯዊ እና ሃይማኖታዊ ስፍራዎች በመመልከቴ በጣም ደስተኛ ነኝ። ህዝቦቼም በተድላ እና በደስታ በመኖራቸው እረክቻለሁ። ነገር ግን አንድ ጉዳይ አላስደሰተኝም። ይህም የተጓዝንበት መንገድ በጣም የማይመች እና ኮሮኮንቻማ ነበር። ጠጠር እና ሹል ድንጋዮችም ይበዙበት ነበር። እኔ ለጥቂት ግዜያት በእነዚህ አካባቢዎች ስጓዝ ይህ ችግር አጋጥሞኛል። ነገር ግን ሁል ጊዜ በእነዚህ መንገዶች የሚገለገሉት ህዝቦቼ ምን ያክል ይሰቃያሉ? ይህ ጉዳይ ለህዝቤ ምቾትን የሚቀንስ እንደሆነ ተረድቻለሁ። ነገሩ በጣም አሳስቦኛል» አለው። ለሚኒስትሩ ይህን ካለው በኋላ እንዲህ በማለት ትዕዛዝ ሰጠ « በሁሉም መንገዶች ላይ የበሬ ቆዳዎችን አንጥፉ። በዚህ ምክንያት ህዝቦቼ እንዲሰቃዩ አልፈልግም። ይህን ቆዳ ካነጠፋችሁ ግን ሁሉም ሰው በምቾት መንቀሳቀስ ይችላል» አለው። ሚኒስትሩ ንጉሡ ይህን ሲል በመስማቱ በጣም ግርምት እና ጥያቄ ተፈጠረበት። ምክንያቱም የንጉሡን ትዕዛዝ በማክበር እነዚህ ቆዳዎች እንዲነጠፉ ቢደረግ በጣም በብዙ መቶ ሺ የሚገመቱ ከብቶች መሞት ይኖርባቸዋል። ይህ ደግሞ አርሶአደሩ ለወተት ምርት እና ለግብርና ሥራ የሚጠቀምባቸውን ከብቶች ሊያጣ ይችላል። በመንገዶቹ ላይ ቆዳውን ለማንጠፍ ደግሞ በጣም ብዙ ገንዘብ የሚጠይቅ እና ከባድ ነበር። የአገሪቷን ሀብትም በቀላሉ የሚያጠፋ ነበር። በዚህ የተነሳም ከንጉሡ ትዕዛዝ ሲቀበልና ሲወያይ የነበረው ሚኒስትሩ ለሥራ አጋሮቹ ሃሳቡን አጋራቸው። እነሱም በእርሱ ስጋት ተስማሙ። በርካታ ገንዘብ እና በብዙ ሺ የሚቆጠሩ ከብቶች መጥፋቱ አሳሳቢ ሆነባቸው። ሚኒስትሮቹ በጉዳዩ ላይ በጣም ተጨንቀው መፍትሔ በማፈላለግ ላይ ሳሉ፤ ከመካከላቸው የነበረ አንድ ብልህ ሚኒስትር ሃሳብ እንዳለው ተናገረ። ይህን መፍትሔም ለንጉሡ ማቅረብ እንዳለባቸው ተስማምተው ሰውዬው ወደ ንጉሡ ዘንድ ሄደ። ሚኒስትሩ አማራጭ ነው ብሎ ያቀረበውን ሃሳብ ንጉሡ ጠየቀው። ሚኒስትሩም እንዲህ በማለት መለሰለት «ንጉሥ ሆይ መንገዱን በቆዳ ከመሸፈን ይልቅ፤ ለምን በእግር ልክ ተስተካክሎ የተቆረጠ ቆዳ ሁሉም ሰው አያደርግም። ይህ ሲሆን አንድ ቆዳ ብዙ የእግር ሽፋኖችን መሥራት ይችላል» በማለት መለሰለት። ይህ ብልህ ሚኒስትር ባቀረበው ሃሳብ ንጉሡ በጣም ተገረመ። ሃሳቡም በጣም ትክክል እና በቶሎ መተግበር ያለበት ጉዳይ እንደሆነ ተናገረ። ለሚኒስትሩ አድናቆት እና ሽልማት አበረከተለት። በቶሎም ለራሱ ሁለት ከቆዳ ላይ የተቆረጡ መሸፈኛ ጫማዎችን አዘዘ። ህዝቦቹም ልክ እርሱ እንዳደረገው ጫማ እንዲያደርጉ እና እራሳቸውን ከጉዳት እንዲጠብቁ ጠየቃቸው። ህዝቦቹም ንጉሣቸው ከልቡ እንደሚያስብላቸው በማወቃቸው እና የቀረበላቸውን ሃሳብ ስላስደሰታቸው በሃሳቡ ተስማሙ። ከዚያን ጊዜ ጀምሮም ህዝቡ በተለያየ ፋሽን ጫማዎችን ማድረግ እና እግሮቹን ከጉዳት መከላከል ጀመረ። የተሻለ አማራጭ ሃሳብ ያለው ሁልጊዜም ተመራጭ ነው።አዲስ ዘመን የካቲት 22/2012ዳግም ከበደ
https://www.press.et/Ama/?p=28167
634
1መዝናኛ
ደንበኞች የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ያልተጠቀምንበትን የታሪፍ ክፍያ እያስከፈላቸው መሆኑን አመለከቱ
ሀገር አቀፍ ዜና
January 13, 2021
12
– አገልግሎቱ በደንበኞች የሚቀርቡ ማናቸውንም ቅሬታዎች ለመፍታት ዝግጁ መሆኑን አስታወቀ በጋዜጣው ሪፖርተሮች አዲስ አበባ፡- የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ያልተጠቀሙበትን የኤሌክትሪክ አገልግሎት እያስከፈላቸው መሆኑን የአዲስ አበባ ነዋሪዎች አመለከቱ። አገልግሎቱ በበኩሉ በደንበኞች የሚቀ ርቡ ማናቸውንም ቅሬታዎች ለመፍታት ዝግጁ መሆ ኑን አስታወቀ። የጋዜጣው ሪፖርተር በሰሜን አዲስ አበባ ሪጅን ቁጥር ሁለት አገልግሎት መስጫ ማዕከል ያነጋገራቸው የአገልግሎቱ ደንበኛ ምንተስኖት ፍሬው፣ “ቤቴ የንግድ አይደለም፤ ነገር ግን በየወሩ የምከፍለው ከአንድ ሺህ ብር በላይ ነው።አሁን ደግሞ እጥፍ ጨምሮ መጥቷል። ይህ ሁሉ ያልተጠቀምኩበት ነው። ሰሞኑን ብመላለስም ደረሰኝ አልመጣም እያሉ ከሥራዬ እያስተጓጎሉኝ ነው።ችግራችንን ለመናገር የሚሰማን ሰው የለም።በተከታታይ አራት ቀን መጥቼ መፍትሔ አላገኘሁም፤ መስተንግዶው ደካማ ነው።መንግሥት ይህንን ተቋም እታች ድረስ ወርዶ መቆጣጠር አለበት።ክፈል ከተባልክ መክፈል ነው፤ ከዚህ ውጪ ሰሚ የለም” ሲሉ ምሬታቸውን ያስረዳሉ።ከዚህ በፊት አምስት ሺህ ብር ቆጠረ ተብዬ ዋናው መስሪያ ቤት ስሄድ አምስት ሺ ብሩ ስህተት ነው የቆጠረው ሰባት ሺህ ብር ነው ተብዬ ከስድስት ሺህ ብር በላይ ከፍያለሁ። በየወሩ አስር አስር ብር ሲቆጥር ሄጄ ሳመለክት ቀደም ሲል ከዚህ እላፊ ከፍለህ ስለሆነ አሁን የቆጣሪ ግብር ብቻ ነው የምትከፍለው ተባልኩ።መጨረሻ ላይ ግን ውዝፍ ክፍል አሉኝ።ከዚያ በኋላ የምከፍለው ብር በጣም ያማርራል ይላሉ።ይመርመርለኝ ስል ብር ክፈል ተብዬ ከፈልኩ፤ ከዚያ ብመላለስ ብመላለስ መፍትሔ በማጣቴ ተውኩት።እንደገና ቆጣሪ ይቀየርልኝ ብዬ ሳመለክት ከቀበሌ አጽፍ ተባልኩ፤ አጽፌ ስሄድ ከነጭራሹ ያንተ ፋይል የለም ብለው አናስተናድህም አሉኝ፤ የምሄድበት አካል አጥቼ ተቸግሬ ነው ያለሁት ብለዋል። በዚያው ጣቢያ ሌላኛው ቅሬታ አቅራቢ ሃምሳ አለቃ መስፍን ተሾመ ፣የችግሩን አሳሳቢነት እንዲህ ሲሉ ይገልጻሉ፤ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የሚተዳደርበት ህግ ያላቸው አይመስለኝም።ጠይቀን የሚያስረዳንም አካል የለም።መቁጠሩ ብቻ ሳይሆን አለመተላለፉ ሌላኛው ችግር ነው።ተሯሩጠን እያደርን ጊዜያችን ያለ አግባብ እየባከነ ነው።ቆጣሪው ቆጥሮ ወደ ሲስተም አልተላለፈም በማለት በራሳቸው ችግር ምክንያት መጥተው አገልግሎት እንዳናገኝ እና የተለያዩ ቅጣቶችን ይጥሉብናል ብለዋል። ለመንግሥት ብር ለመክፈል ለምነን መሆን የለበትም፤ መጥተው በትክክል አንብበው ተገቢውን ክፍያ ሊጥሉብን ይገባል። ቀድም ሲል ሁለት መቶ ብር ይቆጥር ነበር፤ አሁን ምክንያቱን ሳናውቀው በዕጥፍ እንድንከፍል ተደርገናል።የተከሉትን ቆጣሪ በትክክል አይቆጣጠሩትም፤ አያነቡትም ሲሉ ቅሬታቸውን ይገልጻሉ።ላለፉት ሁለትና ሦስት ወር አልተነበበልኝም የሚሉት ስማቸው እንዲጠቀስ ፍቃደኛ ያልሆኑ ቅሬታ አቅራቢው ሳምንቱን ሙሉ ሥራ ፈትቼ ብመላለስም ቅሬታዬን መርምሮ መልስ የሚሰጠኝ አካል አላገኘሁም ብለዋል።በየወሩ የሚቆጥረው እየጨመረ ነው፤ ነገር ግን ለማን ማመልከት እንዳለብን ጠፍቶኝ በግራ መጋባት ውስጥ ነኝ።ከሥራ ገበታችን እየተስተጓጎልን ተሰልፈን ብንውልም ምክንያት ፈጥረው ሳንስተናገድ እንባረራለን። መንግሥት መፍትሔ ካልፈለገልን ችግሩ አሳሳቢ ከመሆኑም በላይ ሳንጠቀም በግዴታ እንድንከፍል እየተደረግን ሲሉም ምሬታቸውን ገልጸዋል፡፡ለቀረቡ ጥያቄዎች ምላሽ የሰጡን የኢትዮጵያ ኤሌከትሪክ አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ሽፈራው ተሊላ እንዳሉት ተቋሙ ከ2011 ዓ.ም ታህሳስ ጀምሮ ለተከታታይ አራት ዓመት የሚቆይ የታሪፍ ማስተካከያ እያደረገ ሲሆን፤ በቅርቡም በታህሳስ ወር ሦስተኛውን ዙር ማስተካከያ አድርጓል።ይህ ደግሞ አገልግሎቱን ለማሻሻል ወሳኝ ነው። አገልግሎቱ አሁንም ቢሆን የሚያስከፍለው ታሪፍ ከሌሎች አገራት ጋር ሲነፃፀር በጣም አነስተኛ ነው ያሉት አቶ ሽፈራው፤ ለአብነትም ይህንን ማስተካከያ ስናደርግ አንድ ኪሎ ዋት ሃወር ኤሌክትሪክ የመሸጫ ዋጋ 1ነጥብ 8 የኤሪካ ሳንቲም እንደነበርና በወቅቱ ግን ኬንያ ለአንድ ኪሎ ዋት ሃወር 15 ሳንቲም ታስከፍል እንደነበር ጠቅሰዋል፡፡በሌላ በኩል አገልግሎቱ ታሪፍ ማሻሻያ እያደረገ ቢሆንም የአገልግሎት ማሻሻያ ሥራዎች ገና ብዙ ሥራ እንደሚቀራቸው የጠቀሱት አቶ ሽፈራው ሆኖም የአገልግሎት ጥራት ለማምጣት እየተሠራ ነው ብለዋል።ለዚህም በዘንድሮ በጀት ዓመት ለጥገናና ለአቅም ማሻሻያ አንድ ቢሊየን ብር የሚጠጋ በጀት ተመድቦ እየተሠራ እንደሆነ ጠቁመዋል፡፡በሌላ በኩል አንዳንድ ደንበኞች የማይገባ ክፍያ መጠየቃቸው ትክክል አለመሆኑን አቶ ሽፈራው ጠቁመው፤ የይጣራልኝ ጥያቄ ሲያቀርቡም በቅድሚያ ክፈሉ የሚል አሠራር አለመኖሩን ተናግረዋል።ነገር ግን እንዲህ የሚያደርጉ ካሉ ተቋሙ ለማስተካከል ዝግጁ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ አቶ ሽፈራው እንደጠቆሙት ቆጣሪ በየወሩ መነበብና በዚያ መሰረት ክፍያ መፈፀም አለበት።ይህ ካልሆነ ግን ደንበኞች በየደረጃው ቅሬታቸውን ማቅረብ አለባቸው።ከዚህ ውጪ ግን የተጠራቀመ ሂሳብ እንዲክፈሉ ማድረግ ትክክል ባለመሆኑ እንዲህ ዓይነት ችግሮች ካሉ መታረም አለባቸው ብለዋል፡፡ተቋሙ ከደንበኞች ለሚነሱ ማናቸውም ቅሬታዎች በየደረጃው ተገቢውን ምላሽ ለመስጠትና ችግሮች ካሉ ለመፍታት ዝግጁ ነው ያሉት አቶ ሽፈራው ለዚህም ህብረተሰቡ ህጋዊ አሠራርን ተከትሎ ለሚያጋጥሙ ችግሮች እስከ ማዕከል ድረስ ቅሬታውን ማቅረብ እንዳለበትም አሳስበዋል፡፡ አዲስ ዘመን ጥር 5 ቀን 2013  ዓ.ም
https://www.press.et/Ama/?p=39377
563
0ሀገር አቀፍ ዜና
በአማራ ክልል ከ328 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት የሚሸፍን የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ተጀመረ
ሀገር አቀፍ ዜና
January 13, 2021
7
ሰላማዊት ውቤ አርማጮሆ፦ በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግሥት በዘንድሮ የተፈጥሮ ሀብት ልማትና ጥበቃ ሥራ በክልሉ ሁሉም አካባቢዎች በሚገኝ ከ328 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ላይ ተግባራዊ እንደሚሆን የአማራ ቤሄራዊ ክልላዊ መንግሥት ግብርና ቢሮ አስታወቀ። በሥራው 4 ነጥብ 6 ሚሊዮን ዜጎች እንደሚሳተፉ ገለጸ። በቢሮው የተፈጥሮ ሀብት ልማት ጥበቃና አጠቃቀም ዳይሬክተር ተወካይ እስመለዓለም ምህረት ለጋዜጣው ሪፖርተር እንዳስታወቁት ከትላንት ጀምሮ እንደ አካባቢው ተጨባጭ ሁኔታ ከ20 እስከ 30 ለሚደርሱ ቀናት የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ሥራው በክልሉ ሁሉም አካባቢዎች በሚገኙ ከ328 ሺህ ሄክታር በላይ በሆኑ የማሳ፣ የቦረቦር መሬቶችና የተራራ ሥፍራዎች ስነ ሕይወታዊ ሥራዎች ይከናወናሉ።በተጨማሪም በክልሉ ሁሉም አካባቢዎች ከ1 ነጥብ 6 ቢሊዮን በላይ ችግኞች ተፈልተው ከ182 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ላይ የመትከል የስነሕይወታዊ ሥራ የሚሠራ መሆኑን የጠቆሙት ተወካዩ ፣ በሥራው 4 ነጥብ 6 ሚሊዮን የክልሉ አርሶ አደሮች፣ ባለሙያዎች፣ ባለድርሻ አካላትና የተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎች ይካፈላሉ ብለዋል።የተፈጥሮ ሀብት ሥራ ከዚህ ቀደም የግብርና ሥራ ተደርጎ ይወሰድ እንደነበረ የጠቀሱት ኃላፊው፣ ሥራው የሁሉንም ርብርብ የሚጠይቅ በመሆኑ ይሄ ዓይነቱ አስተሳሰብ መቅረት እንዳለበት አሳስበዋል። ባለሀብቱ በእርሻ መሣሪያም ሆነ መኪናውን ለሥራው የሚያስፈልጉ ግብዓቶችን ለማጓጓዝ እንዲውሉ በመፍቀድ እንዲተባበርና የራሱን አስተዋፅኦ እንዲያደርግም ጥሪ አቅርበዋል።የተፈጥሮ ሀብት ልማትና ጥበቃ ሥራው ስነ አካላዊ፣ ስነ ሕይወታዊ፣ ዘላቂነትና ተጠቃሚነትን ያካተተ እንደሆነና የሥራው የመጨረሻ ግብም አፈር መቆለል፣ድንጋይ መካብና ጉድጓድ መቆፈር ሳይሆን ተጠቃሚነትን ማምጣትና የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ እንደሆነ አመልክተዋል። ሥራውን ለማከናወን ባለፉት ወራቶች ሥራው የሚሠራባቸውን አካባቢዎችና ከ8 ሺህ 300 በላይ ተፋሰሶች የመለየት፣ ክፍተት ያለባቸውን ባለሙያዎች የማሰልጠንና ለሥራው የሚያስፈልጉ ግብዓቶችን የማዘጋጀትና ሕብረተ ሰቡን የማወያየት ሥራዎች ሲሠሩ መቆየታቸውን አስታው ሰዋል። የተፈጥሮ ሀብት ልማት ጥበቃ ሥራ መነሻው ታች ከተፋሰስ መሆኑን የጠቀሱት ተወካዩ ፣ ይሄው ዝግጅት እስከ ቀበሌ መውረዱን አስታውቀዋል። ባለፈው ሳምንት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድርና የግብርናው ዘርፍ ኃላፊዎች ባሉበት መግባባት ላይ ተደርሶ የጋራ መደረጉንና ትላንትና በይፋ መጀመሩን ጠቁመዋል። ቀደም ሲል ቦረቦር የነበሩ፣የተራቆቱ መሬቶችና ተራራዎች የነበሩና በተፈጥሮ ሀብት ሥራው በመለወጥ አትክልትና ፍራፍሬ፣ የእንሰሳት መኖ፣ለማገዶ እንጨት የሚውሉ ዝሪያዎች የለሙባቸውና የእንሰሳትና የንብ እርባታ እየተካሄደባቸው የሚገኙ ሥፍራዎች በፌዴራል፣ በክልል፣በዞንና ከተለያዩ አካባቢዎች በመጡ አመራሮችና ባለሙያዎች ተጎብኝተውና ልምድ ተቀስሞባቸዋል ብለዋል።“ሥራው ዓመቱን ሙሉ የሚሠራ ነው›› ያሉት ተወካዩ፣ በአማራ ክልል የተፈጥሮ ሀብት ልማትና ጥበቃ ሥራ በተደራጀና በንቅናቄ መልማት የጀመረዉ በ2003 ዓ.ም መሆኑን አስታውሰዋል።›› ‹‹ከንቅናቄው በፊት የክልሉ የደን ሽፋን 6 ነጥብ 5 በመቶ ነበር›› ያሉት ተወካዩ እስከ አሁን በተሠራዉ ሥራም የክልሉ የደን ሽፋን ወደ 14 ነጥብ 6 በመቶ ከፍ ማለቱን ተናግረዋል። ዕድገቱን ዘላቂ ለማድረግ የዘመቻ ሥራው ከተጠናቀቀ በኋላም የተገኘውን ተሞክሮ በመቀመር በቀጣይ በግል ማሳና በሌሎች አካባቢዎች በቋሚነት ተጠናክሮ የሚሠራ መሆኑን አመልክተዋል። የተፈጥሮ ሀብት ልማት ጥበቃ ሥራ እንደ ሀገር ከጥር 1/2013 ጀምሮ በይፋ መጀመሩና እንደ አካባቢው ተጨባጭ ሁኔታ እየተካሄደ መሆኑ ይታወቃል።የአፈርና ውሃ ጥበቃ ሥራው የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ አገኘሁ ተሻገር በተገኙበት በማዕከላዊ ጎንደር ዞን ላይ አርማጭሆ ወረዳ ችራ ቀበሌ በሶኒ ተፋሰስ ነው። በሥነ-ሥርዓቱ የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሳኒ ረዲ ጨምሮ ሌሎች የፌዴራል፣ ክልልና ዞን ከፍተኛ አመራሮችም ተገኝተዋል። አዲስ ዘመን ጥር 5 ቀን 2013  ዓ.ም
https://www.press.et/Ama/?p=39389
424
0ሀገር አቀፍ ዜና
የጁንታው ከፍተኛ አመራሮች መያዝ የህግ የበላይነትን በተግባር ያረጋገጠ መሆኑ ተገለጸ
ሀገር አቀፍ ዜና
January 13, 2021
28
ሞገስ ተስፋ አዲስ አበባ፡- የጁንታው ከፍተኛ አመራሮች መያዝ የህግ የበላይነትን በተግባር ያረጋገጠ እንደሆነ አዲስ ዘመን ያነጋገራቸው አንዳንድ የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ።ለተንኮል ሸራቢ አካላትም ትልቅ ትምህርት የሰጠ መሆኑን አመለከቱ፡፡ አዲስ ዘመን ያነጋገራቸው የአዲስ አበባ ነዋሪ የሆኑት አቶ ጌትነት ደምሌ እንደገለጹት፣ በቁጥጥር ስር የዋሉ የጁንታው ከፍተኛ አመራሮች ለ27 ዓመታት ሀገርን እመራለሁ በሚል አምባገነናዊ የአገዛዝ ቀንበራቸውን በህዝብ ጫንቃ ላይ በግድ በመጫን ህዝብን በዘር፣ ኃይማኖት እና በጎሳ እያጋጨ ሀበት ሲመዘበሩ የነበሩ የጥፋት መሃንዲሶች ናቸው። በስልጣን ዘመናቸው ዜጎቿ በየቦታው የሚገደሉባት፣ በቋንቋ የሚጋጩባት፣ አንዱ ብሔር አንዱን በጥላቻ እንዲያይ ያደረገ ክፉ አረም የዘሩ መሆናቸውን ጠቁመው፣ እነዚህ የሀገር ቀንደኛ ጥላቶች ከስልጣን በተገፉ ማግስትም ከኛ ውጪ ሀገርን የሚመራ ኃይል የለም በሚል እብሪት በአደባባ ሲደነፉ የነበሩ ናቸው። የእነሱ መያዝ የዘሩትን በተግባር እንዲያጭዱ የሚያደርግ ትልቅ ትርጉም ያለው ክስተት ነው ብለዋል፡፡ ‹‹ሥራ ለሠሪው›› እንደሚባለው የለኮሱት እሳት ራሳቸውን አቃጥሏቸዋል ያሉት አቶ ጌትነት ፣ የእኩይ ተግባር ቀያሾቹ መያዝ ለሀገሪቱ ሁለንተናዊ ለውጥ ትልቅ ፋይዳ አለው ብለዋል። ቀጣዩ ዘመን የህግ የበላይነት በተግባር የሚታይበት፣ ሀገር የምትለወጥበት ፣ በግለሰብ ደረጃም የተሻለ ኑሮ ለመኖር፣ ሠርቶ ለማደግ እና ለመለወጥ ለሚፈልግ ዜጋ ትልቅ የዕደገት እና የለውጥ ዘመን እንዲሆን የተሻለ ዕድል የሚፈጥር እንደሚሆን አመልክተዋል። እንደ አቶ ጌትነት አስተያየት፣ መንግሥት የህግ ማስከበር ዘመቻውን በታላቅ ሀገራዊ ወኔ እና ትብብር በተሞላበት ሁኔታ የሰላማዊ ዜጎችን ደኅንነት በመጠበቅ፣ ብዙ ንብረት ሳይወድም በትንሽ መስዋዕትነት በድል መወጣቱ ትልቅ ስኬት ነው።ለዚህ ስኬት ቀጣይነት ደግሞ መንግሥት ብቻ ሳይሆን ሁሉም ዜጋ ባቅሙ ጠንክሮ በመሥራት የጎደለውን በመሙላት ሊንቀሳቀስ እንደሚገባ ጠቁመዋል። መንግሥት ህግን ለማስከበር እየወሰደ ያለውን ዕርምጃ የሚመጥን ትክክለኛ መረጃ በመገናኛ ብዙሃኑ ለህዝቡ እንዲደርሱ መደረጉ በራሱ ትልቅ ስኬት መሆኑን አመልክተው ፣ የህግ ማስከበር ዘመቻው ሀገርን በቁማር እና ተንኮል መምራት የጊዜ ጉዳይ ካልሆነ በስተቀር ተጠያቂነት ማስከተሉ እንደማይቀር ያስተማረ ነው። ጁንታዎች በሠሯቸው ሥራዎች ኪሳራ እንጂ ትርፍ አላገኙም። ይህም ሀገርን ካለችበት ማማ ለማውረድ ለሚሠሩ ትልቅ መማሪያ እንደሆነ ገልጸዋል። ሌላኛዋ የአዲስ አበባ ነዋሪ የሆኑት ወይዘሮ ገነት አለማየሁ በበኩላቸው ፣ የጁንታው ከፍተኛ አመራሮች ለበርካታ ዓመታት በህዝብ ላይ ያስከተሉት ጥፋት ሳያንስ ከስልጣን ከተገለሉ ማግስት ነፃነቱን እንደማንኛውም ኢትዮጵያዊ ተገፎ ከቆየው የትግራይ ህዝብ ጉያ ገብተው በሰላም መቀመጥ አቅቷቸው ለዳግም ጥፋት የደገሱት የጥፋት ድግስ ራሳቸውን እንዳጠፋቸው አመልክተዋል። ጁንታው በስልጣን በቆየባቸው ዓመታት በተለይም በሴቶች ላይ ከፍተኛ የሰብዓዊ መብት ጥሰት መፈፀሙን አመልክተው ፣ የጥፋት ቡድኑ በቁጥጥር ስር መዋሉ የጊዜ እንጂ የቡድን ጀግና እንደሌለ በተጨባጭ ያሳየ ነው ብለዋል። የህግ የበላይነት ምን ማለት እንደሆነም ለቡድኑ ብቻ ሳይሆን ለሌሎች ትምህርት የሰጠ መሆኑን ገልጸዋል። አቶ ስዩም ይሁኔ የተባሉት ልላኛው መዲናዋ ነዋሪ ፣በሀገሪቱ ያሉ ስልጣን ለመያዝ እውቅና የተሰጣቸው ፓርቲዎችም ከጁንታው አመራሮች ትምህርት በመያዝ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ እና የህዝብ ጥቅም መረጋገጥ ቢሠሩ ቀጣይነት ላላው ሰላም መስፈን ትልቅ ዋጋ ይኖረዋል ብለዋል።ከጀርባ ሆነው ግጭት ለመፍጠር ነገር በመጥመቅ፣ በማስታጠቅ ሀገሪቱ የተረጋጋች እንዳትሆን አቅደው ሲሠሩ የነበሩ የህዝብ ጠላቶች መያዛቸው ለህዝብ ሰላም መረጋገጥ እና ቀጣይነት ያለው የሀገር ዕድገት ለማስመዝገብ ትልቅ መደላ ድል እንደሆነ አስታውቀዋል። ሀገርን ሲያውኩና መጥፎ ሥራ ሲሠሩ የቆዩት አመራሮች መያዝ የህግ የበላይነት ያረጋገጠ ፣ ማንም ሰው ከህግ በላይ ላለመሆኑ ማሳያ ነው ያሉት አስተያየት ሰጪው፣ መንግሥት በቀጣይ ለሚወስደው የህግ ማስከበር ዕርምጃ የህዝብ ድጋፍ ወሳኝ በመሆኑ ለትክክለኛ ፍትህ ዘብ በመሆን ከስጋት ተላቀን ልማቱን እንድናስቀጥል መንግሥት እና ከህዝብ ከቀደመው በተሻለ ተቀራርበው መሥራት እንዳለባቸው አሳስበዋል። አዲስ ዘመን ጥር 5 ቀን 2013  ዓ.ም
https://www.press.et/Ama/?p=39385
474
0ሀገር አቀፍ ዜና
የኮሮና ቫይረስን በቃሪያና በርበሬ?
መዝናኛ
February 6, 2020
460
ዓለም ሰሞኑን ከቻይና ተነሳ በተባለው ኮሮና ቫይረስ መታመስ ይዛለች። ዓለም አቀፉ ሚዲያ በስፋት እየዳሰሰውም ይገኛል። ኮሮና ቫይረስ የዓለማችን ቁጥር አንድ አሸባሪ ቫይረስ ሆኖ ተከስቷል። እንደ አልቃይዳ፤ አልሻባብ፤ ዓለምን ማሸበሩን ቀጥሏል።‹‹የጨነቀ ነገር መላው የጠፋ፤ ደሞ ምን ጉድ አመጡብን?›› አሉ አዛውንቷ እማማ አለሚቱ። ‹‹ከዚህ ከሚወራው መአት አምላክ ይጠብቀን እንጂ ምን ሊባል ይችላል›› አሉ በፍርሀት ጎብጠው። ‹‹ደሞ በትንፋሽ፣ በንክኪ ይተላለፋል የሚሉት ነው እኮ የበለጠ የሚያሸብረው። እንዴት እንዴት ልንሆን ነው። የእኛ ኑሮ እንደሁ በጣም የተቀራረበ፣ የተነካካ አንዱ ከሌላው መራቅ የማይችልበት ነው፤ ብቻ እሱ ይሰውረን›› አሉና አማተቡ። ቤታቸው ውስጥ ከጎናቸው የተቀመጡት ባለቤታቸው አቶ ደቻሳ ‹‹መቆየት ደጉ ስንት ጉድ አየን፤ የባሰ አታምጣ ማለት ይሻላል አለሚቱ›› አሉ። ‹‹እኛስ እሺ። ገና ምኑንም ያላዩት ሕጻናት ወጣቶች እንዴት ሊሆኑ ነው የእነሱ ያሳስበኛል›› አሉ ደቻሳ። ልጆቻቸው በሙሉ ባህር ማዶ ከተሻገሩ ዓመታት ተቆጥረዋል። አውሮፓና አሜሪካ ይኖራሉ። እዛው ከተለያዩ ሀገራት ዜጎች ጋር ተጋብተው ወልደው ከብደዋል። እንደው እንዴት ይሆኑ ይሆን ምን ይሻላል በሚል አባትና እናት ተጨንቀዋል። እናትና አባት ቶሎ ቶሎ ስልክ ወደ አውሮፓ ይደውላሉ። አቤት እማዬ፤ አቤት አባዬ፤ ሲሉ ከወዲያ እንዴት ናችሁ ለመሆኑ ይሄ አዲሱ ተውሳክ ከምን ደረሰ ይሉና ይጠይቃሉ። እኛ እኮ አሸባሪ ብለነዋል። እማዬ ምን ሆንሽ እዚህ ምንም የለም መንግስት እየተቆጣጠረው ነው ሰላም ነው›› ሲሏቸው ‹‹እልል እሰየው እመብርሀን የት ሄዳ ልጆቼን ትጠብቃለች›› ይላሉ። አቶ ደቻሳም እንዲሁ። ‹‹ጎረቤታቸው ያሉት አዛውንት ይሄን የሰሞኑን የአዲስ በሽታ ወሬ ሰምተው በፍርሀት ተውጠዋል። የእሳቸው ልጆች ሀገር ውስጥ ናቸው። ‹‹ማን አላችሁት የበሽታውን ስም›› አሉና ለመጥራት ለመስማትም ፈሩ። በየትና እንዴት አድርጎ እንደሚመጣ ነቅተው የሚጠብቁ ይመስላሉ። ‹‹በዱላ አይመታ፤ ሂድ ውጣ አይባል፤ ምን ጉድ መጣብን›› አሉ እነ አቶ ደቻሳና ወ/ሮ አለሚቱ። ቤታቸው ብቅ ያሉት አቶ ዘበርጋም ይናገራሉ። ዘበርጋ ቀጠሉ ‹‹የት አባቱንስና ኮረና ፎረና የለም። እኛ እኮ እግዚአብሔር የሰጠን ብዙ መድሀኒት አለን። ነጭ ሽንኩርት፤ ዝንጅብል፤ ቃሪያ ፤ፌጦ፤ ጥቁር አዝሙድ፤ ጤና አዳም ወዘተ›› እያሉ ዘረዘሩት። ‹‹ምናባቱንስና ደሞ ለቻይና በሽታ ማን ይሸበራል፤ ድምጥማጡን ነው የምናጠፋው፤ ደፍሮ እኛ ሀገር አይገባም ኤድያ አትሸበሩ ካለ መድኃኒዓለም›› አሉ ጭንቀታቸውን ትተው በልበሙሉነት። ‹‹የእኛ የአበሻ አረቄም እኮ ለእንዲህ አይነቱ የተስቦና የመጋኛ በሽታ ፍቱን መድኃኒት ነው፤ በእሱ እናቃጥለዋለን፤ የምን መረበሽ ነው አሉ።›› አቶ ደቻሳ ነገሩ ከትከት አድርጎ አሳቃቸው። ‹‹እንግዲህ እስከዛሬ የጠበቀን አምላክ ያውቃል። መቼም የማያመጡብን የማንሰማው መአት የለም። ኤድስ የመጣብን ከፈረንጅ ሀገር ነው። ሌላ ሌላም። በቴሌቪዥን ኢቦላ እንዲህ አደረገ ሰው ፈጀ ደም አስተፋ ሲሉ ሁሉ እንሰማለን። ይኸው ደግሞ አዲሱ በሽታ በትንፋሽ በጉንፋን በትኩሳት ወዘተ ይለያል ይላሉ።››‹‹የት ሄደን እንኑርላቸው እስቲ ሰው በገዛ ሀገሩ መኖሪያ ያጣል እንዴ?›› አሉ ወ/ሮ አለሚቱ። አቶ ደቻሳ ቀጠሉና ‹‹ውጭ ያሉት ልጆቼ አንድ ጊዜ በዚህ ጉዳይ ሲያወሩ ፈረንጆቹ በሽታ የሚያመርት ፋብሪካ አላቸው ሲሉ ጆሮዬን ጣል አድርጌ ሰምቼአለሁ። ይሄ ነገር ያሳስበኛል። ዓለምን ለማጥፋት ቆርጠው የተነሱ ነው የሚመስለኝ ዝም ብዬ ባልተማረ ህሊናዬ ሳስበው አሉና ዝም አሉ። እኔም ቀልድ መስሎኝ እንጂ ሰምቼአለሁ›› አሉ ወይዘሮ አለሚቱ። ዘበርጋ ቀጠሉና የሁሉም በሽታ መነሻ እንስሶቹ ናቸው። ሊቀመላእክቱ ችግሩን አጥፍቶ ቢገላግለን ምን አለበት›› አሉ በጣም ተበሳጭተው። ‹‹በእኛ ዘመን ድሮ እንዲህ አይነት ጉድ አይተን ሰምተን አናውቅም። የጠና በሽታም አናውቅ። ግፋ ቢል ደማከሴውን፤ ጤና አዳሙን፤ ነጭ ባሕር ዛፉን አረግሬሳውን ቆርጠን ታጥነን ቶሎ መዳን ነበር። የበሽታው መብዛት አይነቱ ስሙ ጉድ ያሰኛል። ይህን ሁሉ ጉድ ድሀ እንዴት ይችለዋል። ሰውም በጣም ተሸበረ›› እያሉ ሲያወጉ ጎረቤታቸው ማንችሎት ሞቅ ብሎት እንዴት ናችሁ? ብሎ ገባ። እርስ በእርስ ተያዩና አመሉን ስለሚያውቁ የታፈነ ሳቅ ሳቁ። አባግድየለሽ ነው ማን ችሎት። ‹‹አዳሜ የምን መፍራት ነው ሞት እንደሁ አይቀር አላቸው። ሁሉም ደነገጡ። አዲስ መጣ ያሉት በሽታ ነው የሰው ሁሉ ወሬ። ጠጅ ቤቱን ጠላ ቤቱን ሰፈሩን መንደሩን ሁሉ የሞላው። እኛና እሱ እንተዋወቃለን። አይነካንም። አንንነካውም። መድኃኒቱ ጠጅና አረቄ መጠጣት፤ ቃሪያና በርበሬ አብዝቶ መብላት ብቻ ነው አዳሜ ትጨነቂያለሽ ምንም የለም›› አላቸው።‹‹ምን ትጨነቃላችሁ እናንተ ዘጠና ዓመት ውስጥ ናችሁ ለምኑ ብላችሁ ነው አላቸው። ወይዘሮ አለሚቱ የእድሜ ነገር ሲነሳ አይወዱም። አዋልደሀል አሉት። ምን ማዋለድ ያስፈልጋል እናንተ እኮ ሉሲ ስትወለድ የነበራችሁ ናችሁ›› አላቸው። አዲስ ዘመን ጥር 28/2012ወንድወሰን መኮንን
https://www.press.et/Ama/?p=26779
569
1መዝናኛ
ልጃገረድነትን ማስመሰል የቻለው የ40 ዓመት ጎልማሳ
መዝናኛ
February 4, 2020
33
ስለ አንድ ነገር አይቶ መናገር ይቻላል፤ ሰምቶም እንዲሁ። አንዳንዴ ግን ያዩትንም የሰሙትንም ማመን ይከብዳል። ኦዲቲ ሴንትራል በቅርቡ ይዞት የወጣ መረጃ እንዳመለከተው፤ በምስሉ ላይ የምትመለከቱት የጃፓን ልጃገረድ የሚመስል ሰው፣ በመካከለኛ እድሜ ላይ የሚገኝ አባወራ ነው። በዊኪፒዲያ ላይ እንደተጠቀሰው፤ ታኩማ ታኒ የተባለው ይህ ጃፓናዊ ድምጻዊ የተወለደው እኤአ በ1977 ነው። ይህ መረጃ ግን ይህን ሰው በፍጹም አይገልጸውም። ሁሉም የግለሰቡ ምስሎች ተማሪ ልጃረገድ ነው የሚመስሉት። ታኩማ ከወጣትነቱ አንስቶ ለኪነጥበብ ከፍተኛ ዝንባሌ ነበረው። ገና በህጻንነት እድሜውም ፓያኖ እና የድምጽ መሳሪያዎችን አጥንቷል። በመለስተኛ ሁለተኛ ደረጃ የትምህርት እድሜውም ግጥም መጻፍ ጀማምሯል። በ28 ዓመቱ ደግሞ ድምጻዊ በመሆን በተዋቂ የጃፓን ባንድ ውስጥ ሰርቷል። ታኩማ በ34 ዓመቱ ደግሞ ልጃገረድ ተማሪ ለመምሰል ይወስናል። ከዚያም ጊዜ አንስቶ ይህን ማስመሰሉን በሚገባም ያደርገዋል። የ40 ዓመት ጎልማሳ በሆነበት በአሁኑ ወቅት ሳይቀር ልጃገረድ መምሰል በሚገባ ችሏል። በዚህም ብዙዎችን በማህበራዊ ሚዲያ እስከ ማደናገር ደርሷል። በህይወቱ ስኬታማ ከሆነባቸው ክንውኖቹ መካከል ልጃገረድ በመምሰል ያከናወናቸው ይበልጣሉ ያለው መረጃው፣ 1 ነጥብ 62 ሜትር እንደሚረዝም፣ 47 ኪሎ ግራም እንደሚከብድ፣ የጫማ ቁጥሩም በአማካይ ከሚታወቀው ቁጥር ያነሰ መሆኑን ያብራራል፤ ይህም ልጃገረድ ለመሆን ያደረገውን ጥረት እንዳሳካለት ይጠቁማል። መረጃው እንዳመለከተው፤ ታኩማ ልጃገረድ ለመምሰል ሲል ሜካፕ መጠቀሙ እንዲሁም ፎቶ ግራፎቹ እጅ ስራ ያያቸው መሆናቸው የማይካድ ቢሆንም፣ ለተላበሰው የልጃገረድነት ባህሪ የዓመታት ልምዶቹ ከፍተኛ ስፍራ የሚሰ ጣቸው ናቸው። አመናችሁም አላመናችሁ ይህ ጥረቱ፣ የ40 ዓመት ጎልማሳውን ታኩማ የተለያዩ ሙያዎች ባለቤት እንዲሆን አስችለውታል። ያለው መረጃው፣ በዚህ የልጃገረድነት ገጸ ባህሪው በጃፖን የቴሌቪዥን ጣቢያዎች በተደጋጋሚ ለመታየት እንዲሁም የፉጂ ቲቪ ቫይኪንግ የአልባሳት ውድድር ሽልማትን በማሸነፍ ለመሸለም በቅቷል። ሙዚቀኛ ብቻ አይደለም። አቱኮስቬት ቶክዮ የተሰኘ የሴቶች ልብስ ፋሽን በመመስረትም ስራ ፈጠሪ መሆን ችሏል፤ ልብሶቹን በማስተዋወቅም በሞዴልነት ይሰራል። ልጃገረድ መመሰል መቻሉ በብዙዎች ዘንድ ተቀባይነት እንዲያገኝ አስችሎታል። በዚህ የተነሳም ብዙዎች ታኩማን የ40 ዓመት ሰው እንዲሁም ባለትዳር አርገው እንዳይቀበሉት አርጓል። እኤአ በ2016 ተማሪነት በተላበሰው መስሉ ህጻን አቅፎ የተነሳውን ፎቶ እና ‹‹እኔ አባት ነኝ›› የሚል መልእክት በማያያዝ በኢንተርኔት የለቀቀው መረጃም ብዙዎችን አስደንግጧል። ‹‹በህይወት ዘመንህ ምን መስራት እንዳለብህ ለሰዎች እያሳየሁ ነው›› ያለው ታኩማ፣ ‹‹ሌሎች ስለአንተ አለባበስና ስለመሳሰሉት ምን ይላሉ ብለህ እንዳትፈራ›› ሲልም ያሳስባል። የምትለብሰው ከእድሜህና ከጾታህ ጋር የሚሄድ እና የማይሄድ ስለመሆኑም ብዙም ትኩረት አትስጥ ያለው ታኩማ፣ ህይወትን በመሰለህ መንገድ ምራ ሲልም ያስገነዝባል። አዲስ ዘመን ጥር 26/2012
https://www.press.et/Ama/?p=26632
325
1መዝናኛ
ኮሚሽኑ ስኬታማ ሥራ ማከናወኑን አስታወቀ
ስፖርት
July 20, 2020
11
የኮሮና ወረርሽኝ (ኮቪድ 19) በየዘርፉ የተለያዩ ተጽእኖዎችን ማድረሱ ግልጽ ነው። ከእነዚህ ዘርፎች መካከል አንዱ የሆነው ስፖርት ሲሆን፤ ጠቅላላ እንቅስቃሴው ተገቶ እንዳልነበር ለመሆን ተገዷል።በርካታ ስፖርታዊ ውድድሮች፣ ስልጠናዎች፣ ጉባኤዎችና ሌሎች ክንዋኔዎች በቫይረሱ ስጋት ምክንያት ሲሰረዙና ሲራዘሙ መቆየታቸው ይታወቃል። ነገር ግን የተለያዩ አገር አቀፍና ዓለም አቀፍ የስፖርት ተቋማት ለተቋረጡት ስፖርታዊ ኩነቶች አማራጮችን በመፈለግ እንቅስቃሴ ሲያደርጉ ቆይተዋል።እንደ መፍትሄ ባስቀመጧቸው ሃሳቦች ታግዘውም ክፍተታቸውን ሲሸፍኑ ሰንብተዋል፡፡ይህ በመላ ዓለም ጥላውን ያጠላው ወረርሽኝ ወደ ኢትዮጵያ መግባቱ ከተረጋገጠበት ጊዜ አንስቶም በርካታ እርምጃዎች በስፖርቱ አካባቢ ሲወሰድ ተስተውሏል። ስልጠናዎች፣ የውድድር ዝግጅቶች፣ ውድድሮች፣ ስብሰባዎችና ሌሎች ጉዳዮች መቋረጣቸው የግድ ቢሆንም፣ ስፖርቱን በበላይነት የሚመራው የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን እና ጥቂት የስፖርት ማህበራትና ተቋማትም በሌላ አቅጣጫ ከተለመዱት ኩነቶች ውጪ የሆኑ ተግባራት ላይ አተኩረው ቆይቷል፡፡ነገር ግን በወቅታዊው ችግር ተቋማቱ በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት ባስቀመጡት መርሐ ግብር መሰረት ያከናወኗቸው እንዲሁም ያልሸፈኗቸው እቅዶች መኖራቸው አይቀርም።ኮሚሽኑ በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት ዘርፈ ብዙ ስራዎችን ሲያከናውን መቆየቱን የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር አቶ ዱቤ ጂሎ ይገልጻሉ። በተለይ በትኩረት ሲከናወን የቆየው የስፖርቱን ሁለንተናዊ ችግር ሊቀርፍ የሚችለውን ጥናት ወደ ተግባር በመቀየር ላይ ነው። ሃገር ዓቀፉ የስፖርት ሪፎርሙን ለመተግበር በሚያስችል ሁኔታ ግብረ ኃይል በማቋቋምና እቅዶችን በማውጣት በውድድር፣ በስልጠና፣ በማዘውተሪያ ስፍራና አደረጃጀት ዙሪያ ያሉ ችግሮችን በመገምገም ስራዎች በዓመቱ ውስጥ ተከናውነዋል። የስፖርት መተዳደሪያ ደንቦችን እንዲሁም ስታንዳርዶችን በማዘጋጀት፣ የስፖርት ማህበራት ያሉበትን ደረጃ የማውጣት፣ ስፖርቱ የሚመራበት አደረጃጀት ላይ ዶክመንት የማዘጋጀት፣ የስፖርት ማህበራት አደረጃጀት ላይ ክለሳ ማድረግም በበጀት ዓመቱ ተችሏል።በመንግሥት በኩል ከፍተኛ በጀት ተመድቦለት በመካሄድ ላይ የሚገኘው ብሄራዊ ስታዲየም ግንባታ፣ የካፍ እግር ኳስ ማሰልጠኛ ማዕከል እድሳት እንዲሁም በሲኤምሲ በሚገኘው ቦታ ላይ የማዘውተሪያ ስፍራ የመስራት እቅድ ላይም ኮሚሽኑ ሲሰራ መቆየቱንና ይህም ስኬታማ እንደነበር ምክትል ኮሚሽነሩ ያብራራሉ።በዓመቱ በርካታ ስራዎች ቢከናወኑም በአንጻሩ ከወረርሽኙ ጋር በተያያዘ በታቀደው መሰረት ለመፈጸም ያልተቻሉ ጉዳዮችም መኖራቸው አልቀረም።ይኸውም የዓለም፣ አህጉርና ሃገር አቀፍ ውድድሮችን ማካሄድ እና በክልሎች የሚገኙ ፕሮጀክቶችን ለመገምገም አለመቻል ነው።ከጥቂት የእግር ኳስ ሊጎች በቀር በዓለም ደረጃ ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች ዝግ መሆናቸውይታወቃል።በኢትዮጵያም የተሻለ እንቅስቃሴ የሚያደርጉት የእግር ኳስና አትሌቲክስ ስፖርቶች እንደቀደመው በመርሐ ግብራቸው መሰረት መስራት አልቻሉም።ሃገሪቷ የምትታወቅበት አትሌቲክስ ኦሊምፒክን ጨምሮ በርካታ ዝግጅት ሲያደርግ ቢቆይም፤ በወቅታዊው ሁኔታ ብሄራዊ ቡድኑን ለመበተንና ስልጠናዎችን ለማቋረጥ ተገዷል። በእግር ኳስም ተመሳሳይ ሁኔታ ያለ ሲሆን፤ ከማህበር ባለፈ በግላቸውም ስፖርተኞች ከቀደመው ጊዜ ገቢያቸው እንዲቀንስ አድርጓል። ነገር ግን በአንጻራዊነት ሲታይ በእነዚህ ስፖርቶች ያለው እንቅስቃሴ የተሻለ ሊባል የሚችልና ተጓዳኝ ስራዎችን እያከናወኑ መሆኑን ምክትል ኮሚሽነሩ ይጠቁማሉ።ቀድሞም እምብዛም እንቅስቃሴ ያልነበራቸው ሌሎች ስፖርት ማህበራት ደግሞ በዚህ ወቅት ይበልጥ ተዳክመዋል።በመሆኑም የስፖርት ኮሚሽን ዋነኛው ሥራ እነዚህን ማጠናከር ይሆናል።አብዛኛዎቹ ፌዴሬሽኖች ከላይ እስከ ታች ያለውን አደረጃጀት ማስተካከል አይደለም የውስጥ ውድድራቸውንም በትክክል መምራት ያልቻሉበት ሁኔታ መኖሩን በግምገማ ተለይቷል። በመሆኑም በአዲሱ በጀት ዓመት ስፖርቱን ከሚመሩት የጽህፈት ቤት ኃላፊዎች ጀምሮ በትኩረት ለመስራት እቅድ ተይዟል።እንደሚታወቀው ለፌዴሬሽኖቹ በመንግሥት በኩል የሚመድበው ዓመታዊ ድጎማ እጅግ አነስተኛና ለሚሰሯቸው ስራዎች በቂ ባለመሆኑ ለመንግሥት ጥያቄ በማቅረብና ጭማሪ በማድረግ በአቅም እንዲጠናከሩ ይሰራል።በኢትዮጵያ ስፖርት መርሐ ግብር መሰረት ይህ የክረምት ወቅት ስልጠናዎችና ውድድሮች ተጠናቀው የታዳጊ ወጣት ፕሮጀክቶች ስልጠና የሚመዘንበት እንዲሁም ክለቦችና የማሰልጠኛ ተቋማት ደግሞ ምልመላ የሚያደርጉበት ነበር።ታዲያ በዚህ ውድድር ማካሄድ በማይቻልበት ወቅት ከታዳጊዎች ምልመላ ጋር በተያያዘ በኮሚሽኑ የታሰበ አማራጭ መንገድ ስለመኖሩም ምክትል ኮሚሽነሩ ማብራሪያ ሰጥተዋል።ሃገር አቀፉ የስፖርት ሪፎርም ምልመላን በተመለከተ የተለዩ ስፍራዎች መኖራቸውን ያመለክታል።እንደየስፖርት ዓይነቶቹ የተሻለ ችሎታ የሚገኝባቸው ስፍራዎች በጥናት ላይ ተሞርክዞ ተቀምጧል። በመሆኑም ከቫይረሱ ጋር በተያያዘ የመንግሥትን ውሳኔና የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን በመመልከት በባለሙያዎች ስራው የሚከናወን ይሆናል።የኮሮና ወረርሽኝ የስፖርቱን ዘርፍ ሙሉ በሙሉ ጎድቷል፤ እንቅስቃሴዎችንና ውድድሮችን ገድቧል።በስፖርተኞችና ሃገራትም ላይ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ችግሮችን አስከትሏል፤ ይህም አደጋ ነው።ነገር ግን ይህ ጊዜ ያልፋል በሚል ተስፋ ሁሉም በአንድነት እየተጠባበቀ ይገኛል።መንግሥትም ሁኔታዎችን በማገናዘብ ምላሽ ይሰጣል የሚል ተስፋ አለ፤ ይህን ወቅት በመሻገርም ስፖርቱን ወደነበረበት የስፖርት ቤተሰቡም ወደ ተመልካችነቱ የሚመለስበት ጊዜ ሩቅ አይሆንም።በመሆኑም ይህንን ጊዜ በጋራ ለማለፍ ራስን ከቫይረሱ መጠበቅ እንዲሁም የአካል ብቃት እንቅስቃሴ በማድረግ እንዲቆዩም ኮሚሽኑ ጥሪ አቅርበዋል።አዲስ ዘመን ሐምሌ 13/2012 ብርሃን ፈይሳ
https://www.press.et/Ama/?p=35740
553
2ስፖርት
ቶማስ ባኽ ተጨማሪ ዓመታት የመቆየት ፍላጎት አላቸው
ስፖርት
July 20, 2020
14
ዘጠነኛው የዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ፕሬዚዳንት ቶማስ ባኽ በቀጣይ ዓመት በሚካሄደው የኮሚቴው ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ የመሳተፍ ፍላጎት እንዳላቸው አስታወቁ። ላለፉት ስምንት ዓመታት ኮሚቴውን የመሩት የ66 ዓመቱ ባኽ በድጋሚ የሚመረጡ ከሆነም ለቀጣይ አራት ዓመታት በፕሬዚዳንትነታቸው የሚቆዩ ይሆናል። በህግ ትምህርት የዶክትሬት ዲግሪ ያላቸውና በስፖርቱ ዓለምም የተዋጣላቸው ቶማስ ባኽ ኮሚቴውን መምራት የጀመሩን እአአ በ2013 ነበር።በምዕራብ ጀርመን የተወለዱት ቶማስ ባኽ በትምህርት ከፍተኛ ደረጃ የደረሱ ቢሆንም ሀገራቸውን በሻሞላ ስፖርት በታላቁ የኦሊምፒክ መድረክ (እአአ 1976 በተካሄደው የሞንትሪያል ኦሊምፒክ) የወርቅ ሜዳሊያ በማጥለቅ ሊያስጠሩ ችለዋል።በሦስት የዓለም ቻምፒዮና ተሳትፎዎችም አንድ የወርቅ ፣አንድ የብር እና አንድ የነሃስ በድምሩ ሦስት ሜዳሊያዎችን ለሃገራቸው አስገኝተዋል።ከስፖርቱ ወደ አመራርነት የገቡት እአአ 2006 ሲሆን፤ የጀርመን ኦሊምፒክ ስፖርት ኮንፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት በመሆንም ነበር። ከዚያ በሂደት ዓለም አቀፉን የኦሊምፒክ ኮሚቴ በመቀላቀል በተለያዩ ሃላፊነቶች አገልግለዋል። እአአ በ2013 በተካሄደው 125ኛው የኦሊምፒክ ኮሚቴ ጠቅላላ ጉባኤ ወቅት የፕሬዚዳንትነት ምርጫ ላይ ተሳታፊ ሆነዋል።በምርጫውም አብረዋቸው የቀረቡትን አምስት እጩዎች በሰፊ የድምጽ ልዩነት በማሸነፍ የፕሬዚዳንትነት መንበሩን ሊቆናጠጡ ችለዋል።ለቦታውብቁ ሆነው በመገኘታቸውም ተጨማሪ አራት ዓመት ተሰጥቷቸው ለስምንት ዓመታት ሊያስተዳድሩ ችለዋል፡፡በቀጣዩ ዓመት በሚካሄደው ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ላይም ከኮሚቴው አባላት ተጨማሪ እድል የሚሰጣቸው ከሆነ ለማስተዳደር ፈቃደኛ መሆናቸውን ሮይተርስ በድረገጹ አስነብቧል። ‹‹የኮሚቴው አባላት በድጋሚ የፕሬዚዳንትነት እድል የሚሰጡኝ ከሆነ የምንወደውን ኦሊምፒክ ለማገልገል ዝግጁ ነኝ›› ሲሉም ማረጋገጫ ሰጥተዋል። ከኮሚቴው አባላት በስልጣን እንዲቆዩ ጥያቄ የቀረበላቸው መሆኑን ደግሞ ኢንሳይድ ዘ ጌምስ የተባለው ድረገጽ አስነብቧል።ፕሬዚዳንቱ አክለውም ‹‹እገዛችሁ ለቀጣይ ሥራ የሚያነሳሳኝ ይሆናል›› ብለዋል። ባኽ ከሌሎች ፕሬዚዳንቶች ልዩ የሚያደርጋቸው በኦሊምፒክ ተሳታፊና ውጤታማ በመሆናቸው ሲሆን፣ በስልጣን ዘመናቸው ካሳለፏቸው አስቸጋሪ ሁኔታዎች መካከል በዋናነት የሚጠቀሰው በመንግሥት ጭምር የሚደገፈው የሩሲያ አትሌቶች የአበረታች ቅመሞች ተጠቃሚነት ቅሌት ሩሲያ በኦሊምፒክ መድረክ እንዳትሳተፍ ማድረጋቸው ግንባር ቀደሙ ነው።ሌላኛው ደግሞ በዚህ ወቅት በመላው ዓለም በተከሰተው የኮሮና ወረርሽኝ ሳቢያ ተራዝሞና ተሰርዞ የማያውቀውን ኦሊምፒክ ለአንድ ዓመት እንዲራዘም ማድረግ ነው።አዲስ ዘመን ሐምሌ 13/2012 ብርሃን ፈይሳ
https://www.press.et/Ama/?p=35754
261
2ስፖርት
“ከፍተኛ የክብር ኒሻን ሽልማቱ ከጀነራል ብርሃኑ ጁላ አልፎ ለአገርም ትልቅ ትርጉም ያለው ነው” – ብርጋዴር ጀነራል ተስፋዬ ሀብተማርያም የህብረተሰባዊት ኢትዮጵያ የጀግና ሜዳይ ተሸላሚ
ሀገር አቀፍ ዜና
January 13, 2021
16
 እፀገነት አክሊሉአዲስ አበባ፦ ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ጀነራል ብርሃኑ ጁላ ከጅቡቲ መንግሥት የአገሪቱን የመጨረሻ ደረጃ ከፍተኛ ኒሻን መሸለማቸው ከግለሰቡ አልፎ ለአገርም ትልቅ ትርጉም ያለው መሆኑን የህብረተሰባዊት ኢትዮጵያ የጀግና ሜዳይ ተሸላሚ ብርጋዴር ጀነራል ተስፋዬ ሀብተማርያም ገለጹ።ብርጋዴር ጀነራል ተስፋዬ ሀብተማርያም ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ እንደገለጹት፣ ሽልማት ማለት አንድ ሰው ለሠራው ሥራ ላበረከተው አስተዋጽዖ እውቅና መስጠት ነው፤ በተለይም እንደዚህ አይነት የእውቅና ሽልማቶች ሲበረከቱ ለግለሰቡ ብቻ ሳይሆን ለአገርም የሚኖራቸው ክብር በጣም ትልቅ ነው። በውትድርና ዓለም ላይ ላሳለፍን ሰዎች የእውቅና ሽልማት ማለት ለአገርም ለራስም ምን ዓይነት ትርጉም እንዳለው በሚገባ እንረዳለን ያሉት ብርጋዴር ጀነራል ተስፋዬ፣ ስሜቱ በጣም ከባድ የሚጥለው ኃላፊነትም ትልቅ ነው ብለዋል። እውቅናው በሰራዊቱ ላይ የሚያሳድረው ተነሳሽነት ከፍተኛ ከመሆኑም በላይ የሞራል ድጋፍ እንደሆነም አስታውቀዋል። ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ብርሃኑ ጁላን የክብር ኒሻን ሽልማት ማግኘታቸውን መስማታቸው እጅግ እንዳስደሰታቸው የገለጹት ብርጋዴር ጀነራል ተስፋዬ፣ ከደስታም አልፈው በአገራቸው መከላከያ ሠራዊት ከፍተኛ ኩራት እንዲሰማቸው እንደሆኑም አመልክተዋል። ሠራዊቱ በተለይም በህግ ማስከበር ዘመቻ ላይ ከፍተኛ የሆነ የህይወትና የአካል መስዋዕትነትን ከፍሏል፤ በጣምም አስደናቂ ጀግንነት በአጭር ጊዜ በትንሽ ወጪ አሳይቷል ፤ ከዚህ አንጻር ሽልማቱ ቢያንስበት እንጂ የሚበዛበት አይደለም ብለዋል። የጎረቤት አገር ጅቡቲ መንግሥት በዚህ መልኩ ሠራዊታችንን ሲያከብርና እውቅና ሲሰጥ የኢትዮጵያ መንግሥትም ዝም ማለት የለበትም ያሉት ብርጋዴር ጀነራል ተስፋዬ፣ ለእነዚህ ጀግኖች የሚገባቸውን ክብርና እውቅና መስጠት እንደሚያስፈልግ ጠቁመዋል። ይህ ሽልማት ሠራዊቱ የህይወት የአካል የደምና የላብ መስዋዕትነት የከፈለበት፣ የዚህ ሁሉ ውጤት ነው፤ እርሳቸውም ለሰጡት አመራር ላወጡት እቅድ የሚገባቸው ነው ፤ ግን ደግሞ የሳቸው ሽልማት የሠራዊቱ ብሎም የኢትዮጵያ ነው። ሽልማቱ እንኳን በቦታው ላይ ሆነው ተጋድሎ ለፈጸሙ ቀርቶ እኛ ጡረቶኞቹን ያስደሰተ ልባችንን ያሞቀ እንኳን ኢትዮጵያዊ አልፎም ወታደር ሆንን ያስባለ ነው ብለዋል። ይህ ዓይነቱ ስጦታ የተለመደ አይደለም የሚሉት ብርጋዴር ጀነራል ተስፋዬ ከዚህ አንጻርም ከፍተኛ ክብር የሚገባው ሠራዊቱንም ለበለጠ ሥራ ትጋት ቆራጥነትና አገር ወዳድነት የሚያነሳሳ ስለመሆኑም ተናግረዋል።የጁንታው መሰሪ አካሄድ በዚህ ዓይነቱ ጀግንነት መስመር ማስያዝ ባይቻል ኖሮ ችግሩ ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው ጎረቤቶቻችን ይተርፍ ነበር ።ህንንም ጠንቅቀው ያውቃሉ ፤ ከዚህ አንጻርም ሽልማቱ “የእኛን ችግር ፈታችሁልን፣ እናንተ ሰላም ስትሆኑ ነው እኛ በሰላም መኖር የምንችለው “ የሚል መልክዕክትም ያለው ነው ብለዋል። ሠራዊቱ በጎረቤት አገራት እየተዘዋወረ በሚያደርገው የሰላም ማስከበር ሥራ ከፍተኛ እምነት እንዳደረባቸውም ማሳያ እንደሆነ ገለጸዋል። “ብላቴ ላይ አየር ወለድና ኮማንዶዎች ሲመረቁ በክብር እንግድነት ተገኝቼ ነበር ፤ በወቅቱም ባየሁት ነገር በአመራሮቹ ብቃት፣ በሙያዊ ክህሎታቸው፣ በስነ ስርዓታቸው እጅግ ከመደሰቴና ከመኩራቴም በላይ ሠራዊቱን የሚበግረው ምንም ኃይል እንደማይኖር ተናግሬ ነበር።አሁንም ጁንታው ለረጅም ዓመታት የተዘጋጀበትን ምሽግ ንዶ ይህንን የመሰለ ውጤት ማምጣቱ የግምቴን ትክክለኝነት አሳይቶኛል “ ብለዋል። ኢትዮጵያ አሁን የገጠማትን ዓይነት ችግር ምን ጊዜም ሊገጥማት እንደሚችል ታሳቢ በማድረግ ሠራዊቱን አሁን ካለው አቋም እንዳይለቅ ከዚህም በላይ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ እንዲታገዝ ማድረግ ያስፈልጋል፤ ይህንን ማድረግ ከቻልን ምንም የሚገታን ኃይል አይኖርም ሲሉም ተናግረዋል። አዲስ ዘመን ጥር 5 ቀን 2013  ዓ.ም
https://www.press.et/Ama/?p=39376
406
0ሀገር አቀፍ ዜና
ከሌሊሶ ሜዳ እስከ ማልታ ደሴት
ስፖርት
July 21, 2020
11
በደቡብ ክልል ከምባታ ጠምባሮ ዞን ዋና ከተማ ዱራሜ ነው የተወለደችው። ሰባት ልጆች ላፈሩት እናት እና አባቷ አምስተኛ ልጅ ስትሆን፤ ከልጅነቷ ጀምሮ ነበር በኳስ ፍቅር የወደቀች። የእግር ኳስ መሰረቷን የጣለችው ተወልዳ ባደገበችበት ዱራሜ ከተማ በሰፈር ውስጥ ነው። ከሰፈር የተነሳው የኳስ ህይወት ከሀዋሳ ከተማ አንስቶ በደደቢት እና ብሔራዊ ቡድን በግብ አስቆጣሪነት ስሟ እስከመነሳት የደረሰም ነበር፤ የኢትዮጵያ ሴቶች ብሄራዊ ቡድንና በማልታ ቢርኪርካራ እግር ኳስ ቡድን አጥቂ ሎዛ አበራ። የሎዛ የእግር ኳስ ህይወቷ ሀ፣ሁ ከሌሊሶ ሜዳ ይጀምራል። የዱራሜዋ የትናነቷ ታዳጊ ባደገችበት ሠፈር ካሉ ወንድ እኩዮቿ ጋር እየተጋፋች በመጫወት ነበር የጀመረችው። ከወንዶች ጋር ሴት ሆና መጫወቷና ብቃቷ ለብዙዎች ግርምት ከመፍጠር ባሻገር ከሠፈሯ ‘ሌሊሶ’ ሜዳ አሁን ያለችበት ትደርሳለች ብለው ብዙዎች አልገመቱም። ሎዛ በኳሱ ወንዝ ተሻጋሪ ታሪክ መስራትን እንደምትችል በልቧ የነበረውን መሻትና ወኔ በአንድ ወቅት ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንዲህ ብላ ነበር ። «በእግር ኳስ ሃገሬን ወክዬ ዓለም አቀፍ መድረክ ላይ መጫወት የልጅነት ህልሜ ነው። ይሄንኑ ህልሜን እውን ለማድረግ እልህ አስጨራሽ ፈተናዎችን በመጋፈጥ እውን አድርጌዋለሁ» ስትል ገልፃለች። በሎዛ የልጅነት የኳስ ህይወት ውስጥ የነበሩት ማህበራዊ ተጽእኖዎችን ትልቁ ፈተና ፈጥሮባታል። ኳስ ያላት የበዛ ፍላጎት በቤተሰቦቿ ዘንድ ይህ የተወደደ አልነበረም። «ትምህርትሽን አጥብቀሽ መያዝ ነው ያለብሽ»የሚል ምክር አዘል ቁጣ አስከትሎባታል። «ከምንም ነገር በፊት ፍላጎት ይቀድማል። እግር ኳስ መጫወት ከሆነ ፍላጎታችን፤ ያንን ፍላጎታችንን ለማሳካት ሳይደክሙ መሥራት። ሌላም ከሆነ እንደዚሁ። ተስፋ ሳይቆርጡ እደርሳለሁ ያሉበት ቦታ እንደሚደረስ ሁሌም ለአእምሮ መናገር፤ ራስን ማሳመን፤ ሥራን ማክበር ማለትም አንድ ሙያ የሚጠይቀውን ዲሲፕሊን መከተል ያስፈልጋል» የምትለው ሎዛ ትምህርቷን ሳትለቅ ኳሱን ጠበቅ ማድረጉን አማራጭ አድርጋ ገፋችበት። በኳሱ የነበራት ተሳትፎ የከንባታ ዞንን ወክላ የመጫወት አጋጣሚን ፈጠረላት። ይህም የሎዛን ከልጅነት ህልሟ የሚያደርሷት ባቡር ውስጥ መግባቷን ያረገገጠ ነበር። የመጀመሪያ ፕሮፌሽናል ኳስ ተጫዋች ነት የተጀመረበት ይህ አጋጣሚ፤ ወደ ክልል አሻገራት። ደቡብ ክልልን ወክላ ለመላው ኢትዮጵያ ውድድር እንድትሳተፍ ሆነ። ለዱራሜዋ ህልመኛ በአደማ የተካሄደው ውድድሩ የባቡሩ ጉዞ ሃዲዱን ጠብቆ እየተጓዘ መሆኑን ያመላከተ ነበር። ሎዛ በመላው ኢትዮጵያ የነበራት እንቅስቃሴ በሐዋሳ ሴቶች እግር ኳስ ቡድን አሠልጣኝ የሆነው ዮሴፍ ገብረወልድ እይታ ውስጥ አስገብቷታል። ከሌሊሶ ሜዳ የተነሳው የኳስ ህይወቷ መዳረሻውን በሐዋሳ እግር ኳስ ክለብ አደረገ። ፈጣኑ የሎዛ ጉዞ ኢትዮጵያ ፕሪሚዬር ሊግ ላይ ታሪክ መስራቱን ተያያዘው። ሎዛ ከሐዋሳ ጋራ ዋንጫ ባታነሳም በቆየችባቸው ሁለት ተከታታይ ዓመታት የክለቡ ኮከብ ጎል አስቆጣሪ ነበረች። በሐዋሳ የፈነጠቀው የኳስ ህይወት ታሪክ፤ ቀጣይ ማረፊያውን ደደቢት ላይ አደረገ። ሎዛ በኢትዮጵያ የሴቶች እግር ኳስ ታሪክ ውስጥ በርካታ ክዋክብቶች የሚገኙበት ክለብን መቀላቀሏ በፍጥነት የበለጠ ጎልታ የመውጣት እድልን አስገኘላት። በደደቢት ቤት ክለቡ እስከፈረሰበት ጊዜ አራት ዓመታትን ቆይታ አድርጋለች። በእነዚህ ዓመታት በተከታታይ ኮከብ ጎል አስቆጣሪ መሆን ችላለች። ክለቧን ለሶስት ተከታታይ ዓመት ደግሞ የሴቶች ፕሪሚዬር ሊግ ሻምፒዮና እንዲሆን አስችላለች። የሎዛ የኳስ ህይወት ከፈረሰው ደደቢት ባህር ማዶ በመሻገር ሲውዲን አርፏል። ከብሔራዊ ቡድኑ የቀድሞ አምበል ቱቱ በላይ ጋር አብራ ወደ ሲውዲን አቅንታ፤ የሁለት ወር የሙከራ ልምምድ ማድረግ ጀመሩ። በሲውዲን የሚገኙ ሮዘንጋርድ እና ፒቲያ አይ ኤፍ ለአራት ወራት ያክል ቆይታ ማድረግ ቢችሉም፤ ሳይሳካ በመቅረቱ ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል። የዱራሜዋ ባለህልም ወንዝ የተሻገረው ህልሟ ከቆይታ በኋላ መዳረሻውን በማልታ ደሴት ከፍተኛ ሊግ ላይ ለሚሳተፈው ቢርኪርካራ አድርጓል። ከሠፈሯ ‘ሌሊሶ’ ሜዳ አሁን ያለችበት ትደርሳለች ብለው ብዙዎች ያልገመቷት ሎዛ፤ በማልታ ደሴት አዲስ ታሪክ መስራት ጀምራለች። በአውሮፓ የምትጫወት የመጀመሪያዋ ሴት ኢትዮጵያዊት እግር ኳስ ተጫዋች መሆን የቻለችው ሎዛ፤ በጥበበኛ እግሮቿ ሌላ ታሪክ በመስራት ነበር የውድድር ዓመቱን ያጠናቀቀችው። የግብ አዳኟ ሎዛ አበራ የኳስ ህይወት ከሌሊሶ ሜዳ እስከ ማልታ ደሴት የተሻገረ ስኬት ማስመዝገብ ችሏል። በእግር ኳሱ ተስፋ ሠንቀው እየተንቀሳቀሱ ለሚገኙ ለሀገራችን ሴት እግር ኳስ ተጫዋቾች ላይ ከፍተኛ የሆነ መነቃቃት ይፈጥራል ባይነን።አዲስ ዘመን ሐምሌ 14/2012 ዳንኤል ዘነበ
https://www.press.et/Ama/?p=35843
519
2ስፖርት
ዓለም አቀፉ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ከአቶስ ጋር ውሉን አራዘመ
ስፖርት
July 23, 2020
5
 ዓለም አቀፉ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ከግዙፉ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ኩባንያ አቶስ ጋር ያለውን የስፖንሰርሺፕ ስምምነት ማራዘሙን ገለፀ። አዲሱ ውል እስከ 2024 እንደሚዘልቅም ሁለቱ ተቋማት ባለፈው ሳምንት ስምምነት ላይ መድረሳቸው ታውቋል። ኮሚቴውና ኩባንያው እኤአ ከ1989 ጀምሮ አብረው እየሰሩ እዚህ ደርሰዋል። የፈረንሳዩ አቶስ ኩባንያ የዓለም አቀፉ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ግንባር ቀደም ስፖንሰር በመሆን 2014 ላይ ለስድስት ዓመታት የሚዘልቅ ውል ማሰሩ የሚታወስ ነው። የሁለቱ አካላት አዲስ ስምምነት ለ2022 የቤጂንግ የክረምት ኦሊምፒክና ለ2024 የፓሪስ የበጋ ኦሎምፒክ ውድድሮች የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ መሰረተ ልማቶችን ማሟላትን ያካተተ መሆኑ ተነግሯል። ይህ የስፖንሰርሺፕ ስምምነት የቶኪዮ 2020 ኦሎምፒክ መራዘሙን ተከትሎ ዓለም አቀፍ ኮሚቴው ከገጠመው ኪሳራ በጥቂቱም ቢሆን ሊያገግምበት የሚችል መልካም አጋጣሚ እንደሆነ ተጠቁሟል። ‹‹በዚህ አስቸጋሪ ወቅት የዓለም አቀፍ አጋሮቻችን ድጋፍና በራስ መተማመን ከምን ጊዜውም በላይ አስፈላጊ ነው›› በማለት ቶማስ ባኽ አስተያየት ሰጥተዋል። ፕሬዚዳንቱ አክለውም ዓለም አቀፍ ኮሚቴው የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ኩባንያ የሆነው አቶስ ውድድሮችን ዘመኑ በሚፈቅደው ቴክኖሎጂ በማገዝ የሚያደርገው ድጋፍ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ያላቸውን እምነት ገልፀዋል። ቶማስ ባኽ የአቶስ ኩባንያ ከኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ አጋርነቱ ባሻገር የኦሎምፒክን መርህ በዓለም ሕዝብ ዘንድ ለማስረፅ በሚደረገው እንቅስቃሴ አጋር ሆኖ በመዝለቁም ምስጋናቸውን አቅርበዋል። ኩባንያው የኦሎምፒክን እንቅስቃሴ እኤአ ከ2001 ጀምሮ እየደገፈ እንደሚገኝ ይታወቃል። በፓሪስ ሰሜን ምዕራብ ቢዞንስ አካባቢ በሚገኘው የአቶስ ኩባንያ ተገኝተው የውል ስምምነቱን የፈረሙት ቶማስ ባኽ በፈረንሳዩ ፕሬዘዳንት ኢማኑኤል ማክሮን አቀባበል ተደርጎላቸዋል። የፓሪስ 2024 ኦሎምፒክን እንዲሁም የወቅቱ አሳሳቢ የጤና ጉዳይ የሆነው ኮቪድ 19 ዙሪያም ምክክር ማድረጋቸው ታውቋል። የአቶስ ኩባንያ ዋና ስራ አስፈፃሚ ኤሊ ጂራርድ ከዓለም አቀፉ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ጋር ባለፉት ሦስት አስርት ዓመታት በአጋርነት ሲሰሩ ቆይተው ውላቸውን በማራዘማቸው የተሰማቸውን ደስታ ገልፀዋል። ዋና ስራ አስፈፃሚው አክለውም ኦሊምፒክንና የኦሊምፒክ ጨዋታዎችን በቴክኖሎጂ በማገዝ ወደ ፊትም ኩባንያው ጠንክሮ እንደሚሰራ አብራርተዋል። በሁለቱ አካላት መካከል የታደሰው ውል የዓለም አቀፉ ፓራኦሎምፒክ ኮሚቴንም የሚያካትት ነው። አቶስ ኩባንያ በርካቶቹ የኦሎምፒክ ስፖንሰሮች ፓራኦሎምፒክ ኮሚቴውን ለመደገፍ ሲያመነቱ 2018 ላይ ስፖንሰር ለመሆን ፍቃደኝነቱን ማሳየቱ ይታወሳል። አቶስ ኩባንያ በ2018 ፒዮንግያንግ የክረምት ኦሎምፒክ ወቅት ‹ክላውድ› የተባለ ቴክኖሎጂ ይፋ በማድረግ ስራ ላይ ያዋለ ሲሆን በተራዘመው የቶኪዮ 2020 ኦሎምፒክም ይህን ዘመናዊ ቴክኖሎጂ ይጠቀማል ተብሎ ነበር። ባለፈው ሰኔ ዓለም አቀፉ ኦሎምፒክ ኮሚቴ የቶኪዮ ኦሎምፒክ በመራዘሙ ስድስት መቶ ሃምሳ ሚሊየን ዶላር ኪሳራ እንደሚገጥመው የተነገረ ሲሆን ይህን ኪሳራ ለማካካስ እንደ አቶስ ያሉ አጋሮቹን ድጋፍ ከምን ጊዜም በላይ ይፈልጋል። የቶኪዮ 2020 ኦሎምፒክ ለአስራ ስድስት ወራት በመራዘሙ ምክንያት የአዘጋጅ አገሯ ጃፓን መንግስትና የዓለም አቀፉ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ገና ከጅምሩ በርካታ ውስብስብ ችግሮች ውስጥ መዘፈቃቸው ሲነገር ቆይቷል። የኦሎምፒክ ውድድሩ በዓለም ላይ ከፍተኛ ስጋት በፈጠረው የኮሮና ቫይረስ ስርጭት ጋር ተያይዞ ወደ ቀጣዩ ዓመት መራዘሙ ግድ መሆኑ ከታመነበት ወቅት አንስቶ አዘጋጆቹ በርካታ ፈተናዎችን መጋፈጣቸው የማይቀር ሆኗል። በተለይም ላለፉት ሰባት ዓመታት የበለጠ ዝግጅት ሲደረግበት የቆየው የኦሎምፒክ ውድድር መራዘሙ ከፍተኛ የገንዘብ ኪሳራ ማስከተሉ የአዘጋጆቹ ራስ ምታት እንደሚሆን ቀድሞም የታወቀ ነው።ይህ ከፍተኛ የገንዘብ ኪሳራ የጃፓን መንግስትንም ይሁን ዓለም አቀፉ ኦሎምፒክ ኮሚቴን በእጅጉ ሊፈትን እንደሚችል በባለሙያዎች አስተያየት ሲሰጥበት የቆየ ሲሆን ሁለቱ አካላት ኪሳራውን ለማካካስ እንደሚደጋገፉና ሌሎች ባለድርሻ አካላትም ለዚህ እንዲዘጋጁ ጥሪ ሲያቀርቡ ቆይተዋል።የዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ እንዲህ አይነት ችግሮች ሲገጥሙት ትልቅ ተቋም እንደመሆኑ የመድህን ዋስትና እንዳለው ይታወቃል። አሁን የገጠመው ግን ካለው የመድህን ዋስትና አቅም በላይ በመሆኑ ነው እዚህ ችግር ውስጥ የተዘፈቀው። ስለዚህ የመድህን ዋስትናው በሕጉ መሰረት የሚሸፍነው ኪሳራ እንዳለ ሆኖ ተጨማሪ ኪሳራውን የሚያካክስበት አንድ ነገር መፈጠሩ የግድ ይሆናል፡፡አዲስ ዘመን ሐምሌ 16/2012 ቦጋለ አበበ
https://www.press.et/Ama/?p=35901
482
2ስፖርት
የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጣና እና ተስፋው
ሀገር አቀፍ ዜና
January 11, 2021
17
ጽጌረዳ ጫንያለው የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጣና ለአፍሪካውያን ትልቅ ተስፋ የሚሰጥ መሆኑን የምጣኔ ሀብት ባለሙያው ይናገራሉ::የአፍሪካ ነፃ ንግድ ሰነዱም ይህንኑ የሚያረጋግጥ ነው::በዲላ ዩኒቨርሲቲ የምጣኔ ሀብት መምህሩ ዶክተር ዳዊት ሀዬሶ እንደሚናገሩት፤ በአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጣና አስፈላጊ የሚሆንበት ዋናው ምክንያት እንደ አህጉር የእርስ በእርስ ንግድ ትስስሩ በጣም ዝቅተኛ በመሆኑ እና ይህንን ወደ ከፍታ ለመመለስ ነው::ከዚያም ባሻገር ምርትና ምርታማነትን ለመጨመር፣ ሰፊ የገበያ አማራጭ ለመፍጠር፣ ጥራት ያለው ምርት ለማግኘትና ለማቅረብ፣ ተጨማሪ ገቢ ለሠራተኛው፣ ለባለሀብቱና ለሸማቹ ለማስገኘት ይጠቅማል::በሌላ በኩል ሕገወጥ ንግድን ይቀንሳል፤ ግብር የሚከፍሉ ነጋዴዎችን ያበራክታል::ንግዱን ነፃ እንቅስቃሴ እንዲኖረው በማስቻል ተመጣጣኝ ዋጋ ገበያው ላይ እንዲኖርም ያደርጋል::በተለይ በአፍሪካ አገራት ያለውን የሰው ሃይል ከመሸጥ አኳያ ከፍተኛ ፋይዳ አለው::ይህ ማለት በሁለት መልኩ ሊሆን ይችላል::አንዱ የሥራ ዕድል በመፍጠር ሲሆን፤ ሁለተኛው በምርታማነት ደረጃ ሌሎች የሚገዙበትን ዕድል ይሰጣል::እንደ አፍሪካ ያለው ችግር ተመሳሳይ በመሆኑም አንዱ ከአንዱ ጋር ተመጋጋቢ ሆኖ ከላይ ወደታች ያለውን አሠራር ያስቀራል ይላሉ::ከአፍሪካ ጥሬ ዕቃ ሄዶ አውሮፓ ወይም እስያ ላይ ተመርቶ መልሶ በዝቅተኛ ታክስ ለአገር ውስጥ ይቀርባል::ይህ ነፃ የንግድ ቀጣና ተግባራዊ መደረጉ አምራቹ ሳይቀር አፍሪካ ላይ እንዲፈጠር ያደርጋል::የቁጠባ ባህልን ከፍ በማድረግ የውጭ ምንዛሬን ዝውውር ያፋጥናል::የውጭ ምንዛሬ እጥረትንም የሚቀንስ መሆኑን ይናገራሉ::እንደ አየር ትራንስፖርት ላሉ አገልግሎቶችም የሚሰጠው ጥቅም ከፍተኛ እንደሆነ የሚጠቁሙት ዶክተር ዳዊት፤ ከገበያ፣ ከእውቀት ሽግግር፣ ከውጭ ንግድ ዕድገት አንፃርም ጠቀሜታው ከፍተኛ መሆኑን ያነሳሉ::የነፃ ቀጣናው ስምምነት መረጃ እንደሚያሳየው ደግሞ፤ የዓለም ንግድ ድርጅት ከተመሰረተ እ.ኤ.አ ከ1994 በኋላ አሁን የተመሰረተው የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጣና ትልቁ ሲሆን፤ 54 አገራትን አቅፏል። 1 ነጥብ 3 ቢሊዮን ሕዝብን ይይዛል፤ 3 ነጥብ 4 ትሪሊየን ዶላር በአጠቃላይ ምርት ይዞ አህጉሩን እርስ በእርስ ያስተሳስራል::በዚህ ሁሉ የማደግ ሁኔታን ያመቻቻል::የእርስ በእርስ የንግድ ልውውጡን ከነበረበት 16 በመቶ ወደ 33 በመቶ ያሳድገዋል ተብሎ ይታመናል::የንግድ ሚዛን ጉድለቱንም ከ50 በመቶ በታች ይቀንሰዋል::ለአህጉሩ 2 ነጥብ 8 ቢሊዮን ዶላር በዓመት የተጣራ ገቢ ያስገኛል ::እንደ መረጃው ከሆነ፤ የሸማቾች ገንዘብ ወጪ የማድረግ አቅምን 2036 ነጥብ 7 ትሪሊየን ዶላር እንዲደርስ ያደርገዋል::ይህ ሆነ ማለት የገንዘብ ዝውውሩ የተረጋጋ እንዲሆን ያግዛል::በዚህም ምርትና ምርታማነት በከፍተኛ ሁኔታ ይጨምራል::የታሰበው የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጣና ውጤታማ እንዲሆን ብዙ ተግባራት መከናወን እንዳለባቸው የሚገልፁት ዶክተር ዳዊት፤ የኢትዮጵያ የንግዱ ማህበረሰብን ተወዳዳሪ ለማድረግ በተለይም አብዛኛው ምርት የግብርና በመሆናቸው የኢንዱስትሪው ዘርፍ ላይ መሥራት ያስፈልጋል::ውጤታማ የምንሆንባቸውን ምርቶች ወደገበያ ለማቅረብ የማያስችሉ ልማዳዊ አሠራሮች ወይም ቢሮክራሲዎችን መቀነስ ይገባል::ያለንን ሀብት ማውጣት ላይም መሠራት አለበት::እንደ አፍሪካ የንግድ ሕጉን ማሻሻል፣ ተመሳሳይ የታክስ ታሪፍ ማስቀመጥ፣ ለነጋዴዎች የነፃ ቪዛ ሂደቱን ማስተካከልም አስፈላጊ መሆኑን ይናገራሉ::እ.ኤ.አ በ2018 የወጣ መረጃ እንደሚያመላክተው፤ የአፍሪካ አገራት የእርስ በእርስ የንግድ ትስስር ከአጠቃላይ የንግድ ልውውጡ 19 በመቶ ብቻ ነው::ይህ ሲታይ ከ80 በመቶ በላይ የንግድ ልውውጡ የሚደረገው ከአፍሪካ ውጭ እንደሆነ ያመላክታል::የአውሮፓ አገራት የእርስ በእርስ የንግድ ልውውጥ 69 በመቶ ይሸፍናል::እስያውያንም እንዲሁ 59 በመቶ የእርስ በእርስ ንግድ ልውውጥ ያደርጋሉ::አፍሪካ ውስጥ ግን በጣም ዝቅ ያለ በመሆኑ የንግድ ሚዛን ጉድለት ያስከትላል::ስለዚህም አህጉሩ እነዚህንና መሰል ችግሮችን ለመፍታት አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣናዎችን መመስረት አስፈልጓቸዋል::ሁኔታው በሚገባ ከተሰራበት በቀጣይ እንደ አገርና አፍሪካ ብቻ ሳይሆን እንደ አለምም በንግዱ ዘርፍ ታዋቂና ኃያል የሆኑ አገራት ይወጣሉ::የሕዝብ ተጠቃሚነትም በዚያው ልክ ይረጋገጣል::ከድህነት የመላቀቁም ሁኔታ ይመቻቻል::
https://www.press.et/Ama/?p=39249
439
0ሀገር አቀፍ ዜና
የጁንታው መያዝ መንግስት እየወሰደ ላለው የሕግ ማስከበር ትልቅ ስኬት እንደሆነ ተገለፀ
ሀገር አቀፍ ዜና
January 11, 2021
33
ሞገስ ተስፋ አዲስ አበባ፡- የጁንታው ቁንጮ አቦይ ስብሃት መያዝ መንግስት እየወሰደ ላለው የሕግ ማስከበር ትልቅ ስኬት እንደሆነ አንዳንድ የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች ገለፁ።ኢትዮጵያ በሴራ እና ተንኮል እንደማትፈርስ በተግባር ያረጋገጠ እንደሆነም አመለከቱ ።አዲስ ዘመን ያነጋገራቸው አቶ ውብሸት ጌታሁን እንዳሉት፣የጁንታው ቁንጮ የሆኑት አቶ አቦይ ስብሃት ኢትዮጵያ ልትፈርስ ነው እያሉ በመንግስት መገናኛ ብዙሃን ሳይቀር ሲሰብኩ የነበሩ ናቸው::ነገር ግን በሴራ እና በተንኮል ኢትዮጵያ እንደማትፈርስ አይተዋል ያሉት አቶ ውብሸት፣ የግለሰቡ መያዝ ብለዋል::የመከላከያ ሰራዊት እየወሰደ ያለው ሕግን የማስከበር ዘመቻ ፣ የሀገሪቱን ሉዓላዊነት ለሚዳፈሩ እና ለወንጀለኞች ትልቅ ማስተማሪያ እንደሆነም አመልክተዋል ። ጁንታዎቹ በሥልጣን ዘመናቸው እጃቸው በብዙ ንጹሃን ደም የተጨማለቀ ቢሆንም መንግሥት ወደ ብቀላ ሳይገባ በሕግ የበላይነት በመተማመን እና በሕገ መንግሥቱ መመራት እየወሰደ ያለው ሕግ የማስከበር እርምጃ ለሕግና ለሕገመንግስታዊ ሥርዓት ያለውን ታማኝነት ማሳያ መሆኑን ገልፀዋል:: ጁንታዎች አልመው ኢትዮጵያ ትፈርሳለች ብለው ሲናገሩ የማያፍሩ ሰዎች ናቸው የሚሉት አቶ ውብሸት፣ ሕዝብ ሲኖር ባለሥልጣን ይኖራል፣ ባለሥልጣን ሆኖ ለመኖር ደግሞ ሕዝብ መኖር አለበት::ሀገር ማለት ደግሞ ሌላ ነገር ሳይሆን ሰው ማለት ነው ብለዋል::እነዚህ ጁንታዎች ሥልጣን ተቆናጠው በኖሩበት ዘመን አብዮታዊ ዲሞክራሲ በሚል አንዱ ከአንዱ ጋር በሰላም እንዳይኖር አቅደው በጥላቻ ሲሰሩ እንደነበር አስታውሰው ፣ከስልጣን ከተወገዱ ማግስትም እኛ ስልጣን ካልያዝን በስተቀር ሀገር ትፈርሳለች ብለው በድፍረት ከመናገር በዘለለ አቅደው በተግባር ሀገር ለማፍረስ ሲሰሩ እንደነበር ጠቁመዋል ::እንደ አቶ ውብሸት ገለፃ ፣ጁንታው ‹‹ እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል›› በማለት ሀገርን ለመበተን ቢሰራም ህልማቸው ሳይሳካ ቀርቷል::ለስልጣናቸው ማራዘሚያ በተደጋጋሚ ትልልቅ የሀገሪቱ ብሔሮችን በማጋጨት ሲጥሩ ነበር ::ይህ ሁሉ ሳይሳካላቸው ከዚህ በፊት የዘሩትን እያጨዱ ነው ብለዋል ::የጥፋት ቡድኑ በአብዮታዊ ዲሞክራሲ ጭንብል ሲንቀሳቀስ ቢቆይም ፣ በዲሞክራሲ በፍፁም የማያምን ፣ በጥፋት የተተበተበ መሆኑን በመከላከያ ሰራዊት ላይ የወሰደው አሳፋሪ ጥቃት ትልቁ ማሳያ እንደሆነ ገልጸዋል::ሌላኛዋ የአዲስ አበባ ነዋሪ ወይዘሮ ትህትና በላይ በበኩላቸው ፣ኢትዮጵያን ለማፍረስ ከውጪም ከውስጥም ብዙ ሴራዎች ተሸርበዋል፣ ነገር ግን በቁርጥ ቀን ልጆቿ እና በፈጣሪዋ ታግዛ የቆየች ሀገር መሆኑዋን አመልክተዋል ::አሁንም መንግስት የወሰደው የደህንነት ተቋማትን የማጠናከር እርምጃ ተቋማቱ በሙሉ እግራቸው እንዲቆሙና የሕግ የበላይነትን እንዲስከብሩ ማድረግ የሚስችል አቅም እንደፈጠረላቸው በተጨባጭ ማየት እየቻልን ነው ብለዋል::በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል እየተወሰደ ባለው የህግ ማስከበር እርምጃ አንጋፋው የተንኮል ቀያሽ እና ስትራቴጂስት መያዙ ትልቅ ድል ነው ያሉት ወይዘሮዋ፣ ይህም በተለይም ሕግ የሚያስከብሩ ተቋማት እንደሀገር እየተጠናከሩ መምጣታቸው አመላካች እንደሆነ ጠቁመዋል :: የሀገርን ደህንነት አደጋ ላይ ለመጣል ሲሰሩ የነበሩ ቁልፍ አመራሮች በሕግ ቁጥጥር ስር መዋላቸው በሕግ ማስከበሩ ዘርፍ ትልቅ ስኬት እንደሆነ የገለፁት ፣የአዲስ አበባ ነዋሪው አቶ ይሁኔ ገበየሁ፣ በጁንታው የተንኮል ሴራ በርካታ ኢትዮጵያውያን በአሰቃቂ ሁኔታ እንዲገደሉ መደረጉን አስታውሰዋል::የጥፋት ቡድኖችን መልምለው፣ በማሰልጠን ፣ በማስታጠቅ እና ለጥፋት ስምሪት በመስጠት ዋነኛ ተዋንያን እንደነበሩ ገልጸው ፣ የጁንታው አድራጊ ፈጣሪ እና የተንኮል ቁልፍ ቀያሽ መያዙ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ጥፋቶችን ሲያደርሱ የነበሩ ቡድኖች እንዲጠፉ ያደርጋል ብለዋል። ቀሪዎቹን የጁንታው ተፈላጊ አባላት ለቃቅሞ ለሕግ ማቅረብ ጥልቅ አቅም ይፈጥራል ፣ በአጭር ጊዜ ውስጥ በመላው ሀገሪቱ ሰላምን ለማረጋገጥ የግለሰቡ መያዝ ወሳኝ ድል እንደሆነ ገልፀዋል::አሁን ተረኝነት የሚያስከትለውን መዘዝ ያየንበት ጊዜ ነው፣ ተረኛ ነኝ ብሎ ሀገር ላይ ማሴር፣ የሀገሪቱን ሕዝቦች መከፋፈል፣ ከሕግ አግባብ ውጪ ዜጎችን መቅጣት ውጤቱ ምን እንደሆነ በተጨባጭ ያየንበት በመሆኑ ከዚህ መማር ያስፈልጋልም ብለዋል ::ስልጣን ያዝኩ ብሎ አንዱን ጠቅሞ ሌላውን መጉዳት ውጤቱ ኪሳራ እንጂ ትርፍ እንደማያስገኝ በማሰብ ለአንድነት፣ ለዲሞክራሲ ለሕግ የበላይነት እና ለፍትህ ያለምንም አድሎ መስራት ከመሪዎች እንደሚጠበቅም አሳስበዋል::
https://www.press.et/Ama/?p=39248
472
0ሀገር አቀፍ ዜና
በግማሽ የበጀት ዓመቱ ለግድቡ ግንባታ በአዲስ አበባ ከተማ ከ1 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር በላይ ተሰበሰበ
ሀገር አቀፍ ዜና
January 11, 2021
11
በጋዜጣው ሪፖርተር አዲስ አበባ ፦ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ በግማሽ በጀት ዓመቱ ከአዲስ አበባ ከተማ ከ 1 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር በላይ መሰብሰቡ ተገለፀ:: የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ሕዝባዊ ተሳትፎ ማስተባበሪያ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ምስክር ነጋሽ እንደገለጹት÷ በስድስት ወራት በከተማው በቦንድ ግዢ ሽያጭ እና በስጦታ የተሰበሰበው ገንዘብ ባለፉት 8 ዓመታት በድምሩ ከተሰበሰበው የሚበልጥ ነው::ከ2003 ዓ.ም ሐምሌ ወር እስከ 2012 ዓ.ም ሐምሌ ወር ባሉ ዓመታት በከተማዋ የተሰበሰበው 1 ነጥብ 1 ቢሊየን ብር እንደነበር ጠቁሟል :: ለገቢው ማደግ ምክንያት መንግስት ፕሮጀክቱን በግልፅነት መምራት መቻሉ እንደሆነ አመልክተዋል::ፕሮጀክቱ ላይ የነበሩ ችግሮች ይፋ ተደርገው የማስተካከያ እርምጃ በመውሰድ በሕዝብ እና በመንግስት መካከል መተማመን እንዲፈጠር መደረጉንም አስታውቀዋል::የግድቡ የመጀመሪያ ዙር የውሃ ሙሌት በስኬት መከናወንም ማህበረሰቡ ከፍተኛ ድጋፍ እንዲያደርግ መነቃቃት መፍጠሩንም ጠቁመዋል::በ2013 ዓ.ም በጀት ዓመት 789 ሚሊዮን ብር እሰበስባለሁ ያለው ከተማ አስተዳደሩ በግማሽ ዓመት ውስጥ 1 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ መቻሉንም አመልክተዋል ::
https://www.press.et/Ama/?p=39247
140
0ሀገር አቀፍ ዜና
ስፖርቱ የማገገሚያ ድጎማ እንዲያገኝ እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ
ስፖርት
July 22, 2020
7
የኮቪድ 19 ወረርሽኝ የዓለም ወቅታዊው ሁኔታ፤ የሰውን ልጅ ሁለንተናዊ እንቅስቃሴ፣ አስተሳሰብና ልማድ እንዲቀየር ምክንያት ሆኗል፡፡ በዚህ መንስኤነትም አካላዊና አእምሯዊ ጤናን ከመጠበቅና ከማዝናናት ባለፈ ከፍተኛ ገንዘብ የሚዘዋወርበት ስፖርትም በቀድሞ ቁመናው ላይ እንዳይገኝ ሆኗል፡፡ በዘርፉ በዓለም ደረጃ እአአ በ2011 ከተገኘው ገቢ በ45 በመቶ የላቀ ትርፍ ከሁለት ዓመታት በፊት መገኘቱን ወርልድ ኢኮኖሚክ ፎረም ያመላክታል፡፡ ይህ እአአ በ2018 የተገኘው 471ቢሊዮን ዶላር በዚህ ዓመት በእጅጉ ሊያድግ እንደሚችልም አመላካች ነበር፡፡ ይሁን እንጂ ባልተጠበቀ ሁኔታ ተከስቶ መላውን ዓለም ባዳረሰው የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ 19) ምክንያት እንቅስቃሴው ሊገታ ችሏል፡፡ እንደ ሌላው ዓለም ሁሉ የኢትዮጵያ ስፖርትም መዳከም አሳይቷል፡፡ በእንቅስቃሴው መገታት በስፖርተኞች፣ ክለቦች፣ ማሰልጠኛ ማዕከላት፣ አወዳዳሪዎችና ሌሎች ባለድርሻዎች መካከል የነበረው ሰንሰለት በቫይረሱ ተጠቅቷል፡፡ በጥቂት ውድድሮች ሽልማት በሚሊዮን የሚቆጠር ገንዘብና የውጭ ምንዛሪ ለሀገር ያስገኙ ከነበሩ አትሌቶች፤ ‹‹ነገ ያልፍልኛል›› በሚል እሳቤ ከኑሮ ጋር እስከሚታገሉት ጀማሪ ስፖርተኞች ድረስ የጉዳቱ ሰለባ ሆነዋል፡፡ ከአቅማቸው በላይ የሆኑትም ከበጎ ፈቃደኞች ተደጓሚ ሆነዋል፡፡ የስፖርት ማህበራትም ከውድድሮችና ስፖንሰሮች ማግኘት የሚገባቸውን ሳያገኙ ቀርተዋል፡፡ ይህንን አሳሳቢ ሁኔታ ያጤነው የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽንም ወረርሽኙ በዘርፉ ላይ ያሳደረውን ጫና በማመዛዘን እንዲሁም በተወሰነ መልኩ የሚያገግምበትን ሁኔታ ለማመቻቸት የሚረዳ ሥራ በማከናወን ላይ ይገኛል፡፡ በጉዳዩ ላይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ ማብራሪያ የሰጡት ምክትል ኮሚሽነር ዱቤ ጂሎ፤ ከኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ጋር በተያያዘ እንደ ንግድ ሁሉ ስፖርትም ጉዳት ያስተናገደ ዘርፍ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ ስፖርተኞች ቀድሞ የሚያገኙትን ገቢ ማግኘት ባለመቻላቸው፣ ክለቦች የመፍረስ አደጋ የተደቀነባቸው በመሆኑ መሰል ጉዳዮችን ከግምት በማስገባት ከመንግሥት ማገገሚያ የሚሆን የገንዘብ ድጋፍ እንዲለቀቅ ጥያቄ መቅረቡንም ይገልጻሉ፡፡ ኮሚሽኑ ለመንግሥት ያቀረበው የዳሰሳ ጥናት ‹‹ኮሮና ቫይረስ በስፖርቱ ልማት ላይ ያሳደረው ተጽእኖ የማገገሚያ ስልት›› የሚል ሲሆን፤ ጥናቱ የተከናወነውም የሌሎች ሀገራትን ተሞክሮ በመቀመር ጭምር ነው፡፡ በዚህም እንግሊዝ፣ ናይጄሪያ፣ ኬንያ እና የመሳሰሉት ሀገራት በወረርሽኙ ወቅት ለማገገሚያ የተጠቀሙትን ስልት ለመዳሰስ መሞከሩንም አመላክተዋል፡፡ የኢትዮጵያ ስፖርት ሕዝባዊ መሠረት ያለው እንደመሆኑ በስፖንሰርና በስታዲየም ገቢ ከሚያገኙት ገንዘብ ባለፈ ለከተማ ክለብ ስፖርተኞች ደመወዝ የሚከፈለው ከሕዝብ ከሚሰበሰበው ታክስ ነው፡፡ ይህም ማለት አብዛኛውን ገንዘብ የሚሸፍነው መንግሥት ነው፡፡ ከወቅቱ ነባራዊ ሁኔታ ጋር በተያያዘ ውድድሮችን ማካሄድ ባለመቻሉ በዘርፉ ያለው  እንቅስቃሴ አስቸጋሪ ሆኗል፡፡ ይህንን ጊዜ ለመሻገርም ከስፖርት ማህበራቱ ጋር በመተባበር ስትራቴጂ በመንደፍና ጥያቄውን ለመንግሥት በማቅረብ ኮሚሽኑ ምላሽ በመጠባበቅ ላይ ይገኛል እንደሚገኝ ጠቁመዋል፡፡ ጥናቱ ስፖርተኞች በምን መልክ ወደሥልጠናና ውድድር ይመለሱ፣ እንዴትስ ፈቃድ ይሰጣቸው የሚለውን በመነሻነት መያዙንም ነው ምክትል ኮሚሽነሩ የሚጠቅሱት:: እንደ ኮሚሽንም ሀገር አቀፍ የስፖርት ማህበራቱ መርሃ ግብራቸውን እንዲያቀርቡም መመሪያ ተላልፏል፡፡ በኢትዮጵያ ስፖርት የሚንቀሳቀሰው የገንዘብ መጠን በውል አይታወቅም፡፡ ይህም መሰል ጥናቶች ላይ ተጽእኖ ማሳደሩ አይቀርም፡፡ ነገር ግን እያንዳንዱ ፌዴሬሽን ይብዛም ይነስም በስፖንሰር የሚያገኙት ገቢ ይኖራል፤ ሆኖም በዓመት ይህን ያህል ይገኛል የሚለው በውል አይታወቅም፡፡ ለአብነት ያህል የአትሌቲክስ ፌዴሬሽን ኢንተርናሽናል እና የሀገር ውስጥ ስፖንሰሮች ቢኖሩትም ከወቅታዊው ሁኔታ ጋር በተያያዘ በትክክል ለማወቅ የሚቻልበት ሁኔታ አዳጋች ነው፡፡ ቢሆንም ቅድመ በግምቶችን በማስቀመጥ ጥናቱ መከናወኑንም ነው ምክትል ኮሚሽነሩ ያስረዱት፡፡ የኮሮና ወረርሽኝ የስፖርቱን ዘርፍ ሙሉ በሙሉ ጎድቷል፤ እንቅስቃሴዎችንና ውድድሮችን ገድቧል፡፡ በስፖርተኞችና ሀገራትም ላይ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ችግሮችን አስከትሏል፤ ይህም አደጋ ነው፡፡ ነገር ግን ይህ ጊዜ ያልፋል በሚል ተስፋ ሁሉም በአንድነት እየተጠባበቀ ይገኛል፡፡ መንግሥትም ሁኔታዎችን በማገናዘብ ምላሽ ይሰጣል የሚል ተስፋ አለ፤ ይህን ወቅት በመሻገርም ስፖርቱን ወደነበረበት የስፖርት ቤተሰቡም ወደ ተመልካችነቱ የሚመለስበት ጊዜ ሩቅ አይሆንም፡፡ በመሆኑም ይህንን ጊዜ በጋራ ለማለፍ ራስን ከቫይረሱ መጠበቅ እንዲሁም የአካል ብቃት እንቅስቃሴ በማድረግ እንዲቆዩም ምክትል ኮሚሽነሩ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡አዲስ ዘመን ሐምሌ 15/2012ብርሃን ፈይሳ
https://www.press.et/Ama/?p=35809
478
2ስፖርት
የጎደለን…
መዝናኛ
January 19, 2020
35
በአንድ ነገር አምናለሁ። ግራ በገባው ዓለም ላይ አብዛኞቻችን የጎደለን ‹‹ትእግስት›› ነው። ይሄ እኔ የማምንበት ሀቅ ነው። ትእግስት በቀጥታ ከእምነታችን ጋር እንደሚያያዝም አውቃለሁ። ይህ ጉዳይ አንድ ነገር ያስታውሰኛል። አሁን በሕይወት የሌለው አያቴን። ምድር ላይ ያሉ እንቅፋቶችንና መሰናክሎችን በሙሉ አይኔ ማየት እንዲችል አይኔን የገለጠልኝ መሪዬ። የሕይወት መመሪያ ቁልፉን ያቀበለኝ ይህ ታላቅ ሰው በአንድ የተባረከ ቀን የእምነት እና የትግስት ሃያል ቁርኝትን ሊያሳየኝ ቻለ። እምነት ‹‹የማይታየውን ማየት መቻል ሲሆን›› ትእግስት ደግሞ ‹‹በልቦና ያዩትን እውነት እስኪገለጥ የመጠበቅ ሃይል›› እንደሆነ ገለጠልኝ። የበጋው ወር ሲገባደድ ሰማይ የመሬት ንቃቃትን ለመድፈን ‹‹በሕይወት ውሀ›› ምድርን ሲያረሰርስ፤ በእናቴ ግፊት ሁሌም አያቴን ለመጠየቅ ወደ ገጠሩ ክፍል የመሄድ ልምድ አለኝ። ከመኪና ጥሩንባ ጩኸት፤ ከአርማታ ጫካ ተላቅቄ ትክክለኛው የሕይወት ኡደት ከሚከወንባት ውብ የተፈጥሮ ክፍል ጋር የምገናኘው ያን ጊዜ ነበር። ይህ ስሜት ውስጤ እንደቀረ የማስታውሰው አሁን ላይ መለስ ብዬ ለማስተዋል ስሞክር ትዝታው ሲጎሻሽመኝ ነው። ታዲያ ማስተዋል በጎደለው የልጅነት ጊዜዬ ላይ ለአያቴ ቀለል ያሉ ለእኔ ግን ፈታኝ የሆኑ ጥያቄዎችን አከታትልበት ነበር። በአንዱ የክረምት ወቅት እንዲህ ሆነ። አያቴ በጠዋቱ ከመኝታዬ አስነስቶ እርስቱ ወደሆነው ወደ አንድ ሰፊ ሜዳማ ስፍራ ይዞኝ ሄደ። ብቻችንን አልነበርንም። ነገ ዋርካ የሚሆኑ፤ ዛሬ ግን ፍሬ የሚሆኑ በርካታ የዘር ፍሬዎችን ይዞ ነበር። ችግኝ ሆነው ነገ ዛፍ የሚሆኑ። እንደዛሬው ግን የፖለቲካ ትርፍ የሌላቸው የተፈጥሮ ማድመቂያ እፅዋቶች። ሁሌም ይህን የማድረግ ልምድ ቢኖረውን ከእኔ ጋር ግን በዚህ መልክ ፍሬን ከአፈር አዋህደን አናውቅም ነበር። እንዲያው ዘርን ለመበተን ብቻም ወደ ስፍራው እንዳልወሰደኝ ቆየት ብሎ ነበር የገባኝ። በእኔ ለጋና በእርሱ የሰከነ እእምሮ ውስጥ በርካታ ጉዳዮች እየተብሰለሰሉ ፍሬውን ከአፈሩ ጋር አቀላቀልን። በጊዜው ከአያቴ ጋር የነበረኝ ቆይታ አስደሳች ነበር። የዘር ፍሬን ከመሬት ማዋሃድ የሚሰጠው ደስታ ልዩ ነበር። እውነት ለመናገር ደግሞ ከሁሉም በላይ ያጓጓኝ የተከልናቸው ፍሬዎች ከምድር ከርስ ውስጥ እየተፈለቀቁ ሲወጡ ማየት ነበር። ተከላውን ጨርሰን ወደ ቤታችን ተመለስን። እኔ ተመለስኩ ከምል ግን በድኔ ተመለሰ ብል ይቀለኛል። ምክንያቱም ሀሳቤ የነበረው የተከልናቸው ፍሬዎች ላይ ነበር። እንዴት እና መቼ ይበቅሉ ይሆን? ያስጨነቀኝ ጥያቄ ነበር። ከሁለት ሰዓት ቆይታ በኋላ አያቴን ትቼ የተከልናቸው ፍሬዎች ወደሚገኙበት ስፍራ አቀናሁ። ከሜዳው ለመድረስ ልቤ እስኪፈርስ መሮጤን አስታውሳለሁ። በቦታው ስደርስ ግን ከእኔና አያቴ የእግር ጫማ ምልክት፤ ተቆፍረው አፈር ከለበሱ ጉድጓዶች ውጪ ምንም መመልከት አልቻልኩም። ልፋታችን መና የቀረ መሰለኝ። ምንም አረንጓዴ ነገር አልታይህ አለኝ። ተስፋ ቆረጥኩ። ‹‹በቃ የተከልናቸው ፍሬዎቹ አልበቀሉም›› ብዬ ተከዝኩ። ከአንዱ ጉድጓድ ውስጥ አፈር የለበሰውን ፍሬ አውጥቼ ከፀሐይ ትይዩ ካደረኩት በኋላ አንጋጥጬ አየሁት ምንም የበቀለ ነገር አይታየኝም። መልሼ ወደ ጉድጓዱ ተክዬው ወደ ቤት ተመለስኩ። አያቴ ፊቱን ወደ መግቢያው በር አዙሮ፤ ጀርባውን ለጠዋት ፀሐይ ሰጥቶ፤ ኩታውን ደርቦ ከበረንዳው ላይ መጽሐፉን ይኮመኩማል። ልጅ ሆኜ ‹‹ኢትዮጵያ›› እሱን ትመስለኝ ነበር። እውነትም ተፈጥሮን የተረዳ፣ ወግ ባህሉን የጠበቀ ኩሩ ኢትዮጵያዊ ነበር። እንባ ያቀረሩ አይኖቼን ከፊቱ አቅርቤ ‹‹አባባ የተከልናቸው ዛፎች አልበቀሉም። ደርቀዋል›› አልኩት። ቀና ብሎ ሲያየኝ እንባዬን ዘረገፍኩት። አባባ የልጅነት ጭንቀቴን እና ጉጉቴን በተረዳ አንደበት ፈገግ እያለ፤ እንባዬን ከጉንጬ ላይ በመዳፉ እየጠረገ ‹‹ልጄ አትቸኩል። ሂደቱን ለተፈጥሮ ተውላት። ችግኞቹ ይበቅላሉ። ከኛ የሚጠበቀውን አድርገናል። አሁን ተራው የተፈጥሮ ነው›› በማለት ጊዜው ገና መሆኑን ነገረኝ። ‹‹በጥረትህ እምነት ይኑርህ የተከልከው ፍሬ እንደሚበቅል እመን›› ሲልም በውብ አንደበቶቹ አስረዳኝ። ከሳምንት በኋላ አያቴ እንደተለመደው በጠዋት ቀስቅሶ ችግኞቹን ወደተከልንበት ስፍራ ይዞኝ ሄደ። በልጅነት አዕምሮዬ በጊዜው የተመለከትኩት ነገር አስደሳች ነበር። ችግኞቹ አናታቸውን ከቀበረው አፈር ፈልቅቀው አውጥተው ስፍራውን በአረንጓዴ ቀለም ሞልተውታል። ደስ የሚል ትእይንት ነበር። አያቴ ቀጠለ ‹‹አየህ ልጄ ፍሬው ቅጠል ለመሆን የሳምንት ጊዜ ፈጅቶበታል። በሕይወት ውስጥ እንዲሁ ጊዜ የሚፈልጉ በርካታ ጉዳዮች አሉ። ያንተ ድርሻ ሂደቱን ማመን እና የድርሻህን መወጣት ነው። ከዚያ ውጤቱ እስኪመጣ በትእግስት መጠበቅ›› በማለት የሕይወት ክህሎትን አስተማረኝ። በአያቴ አጭር ቋንቋ ሂደቱን ማመን ‹‹ትእግስት›› ማለት ነው። የዘራነውን እንደምናጭድ በልቦናችን ማወቅ ደግሞ ‹‹እምነት››። ለካ አያቴ ሁሌም ያለቦታው ፈጠን ፈጠን ሲሉበት የማይወደው እና ‹‹የጅብ ችኩል ቀንድ ይነክሳል›› እያለ የሚተርተው ወዶ አይደለም። ይሄ የገባኝ ከላይ ያጫወትኳችሁ የችግኙ ጉዳይ ዓመት ከሞላው በኋላ ነበር። ከወዲያኛው ማዶ ስልክ አቃጨለ። አያቴ ነበር ለእናቴ የደወለው። ጥቂት ተጨዋውተው መነጋገሪያውን ለኔ አቀበለችኝ። በስልኩ ውስጥ እንዲህ የሚል ድምፅ ሰማሁ ‹‹ልጄ የተከልናቸው ችግኞች አድገው ትልልቆች ሆነዋል ስታያቸው እንደምትደሰት እርግጠኛ ነኝ››። አያቴ ይህን ሲለኝ ከዓመት በፊት ከጉድጓድ አውጥቼ አንጋጥጬ መብቀል አለመብቀሏን የተመለከትኳትን ፍሬ አስታውሼ ለራሴ ፈገግ አልኩ። ዛሬስ? ጊዜው አልፎ ዓመታት ቢነጉድም የእኔም ሆነ የማህበረሰባችን መሠረታዊ ችግር የትእግስት እና የእምነት ማጣት ነው። የተፈጥሮን ኡደት አለመከተል። በመቸኮላችን ከስጋው ይልቅ ቀንድ መንከስ። ማወቅ ያቃተን አንድ ጉዳይ አለ። የምንተክለው መጥፎም ሆነ ጥሩ ፍሬ ጊዜውን ጠብቆ መብቀሉ እንደማይቀር ማመን አልቻልንም። ሂደቱን አልጠበቅንም! መልካም ፍሬዎች በአንድ ጊዜ አይበቅሉም። የክፋት ፍሬዎችም እንዲሁ። ስኬታማ ሰዎች አይን ባወጣ ሌብነት ካልሆነ በቀር በአንድ ሌሊት ሀብት አያከማቹም። እውቅናም ሆነ እውቀት በአንድ ምሽት አይገኙም። የእኔና የአብዛኛዎቻችን ችግር ይህ ነው። ስኬትም ሆነ ውድቀት በአንድ ቀን ጥረት የሚመጡ ይመስለናል። መች ይሄ ብቻ ሆነ። ዛሬ የስኬት ፍሬ ዘርተን ነገ በቅሎ ማየት እንሻለን። የተፈጥሮን ኡደት መጠበቅ አቅቶን የዘራነውን እየነቀልን በትእግስት ማጣት ወጥመድ ውስጥ እንወድቃለን። ጎጠኞች የዘሩት የክፋት መንገድ በአንድ ምሽት እንደ አረም ተነቅሎ ካልተጣለ ብለን በድብርት ማቅ ውስጥ እንወድቃለን። እምነት እናጣለን። ለዘመናት የበቀለው መልካም የአንድነት ፍሬ በዓመታት የአረም ዳዋ የሚለብስና የሚነቀል ይመስለናል። ፍርሃት ውስጥ እንዘፈቃለን። ማስተዋል አቅቶን ለአያቶቻችን ጆሮ ነፍገን። ሀሳቤን ይህን ጠይቄ ልደምድም። ‹‹ትእግስታችን እስከምን ድረስ ነው?›› በተለይ ደግሞ የማህበራዊ ድረ ገፅ ልክፍት ላይ የወደቅነው ወጣቶች። ዛሬ አስበን ውጤቱ ለነገ የምንጠብቅ። ቀንድ ነካሾች። በአንድ ሌሊት አገር የሚገነባ፤ በንጋታው አገር የሚፈርስ የሚመስለን። በአንድ ወቅት ግርግር በማንነታችን፣ በቤተሰባችን፣በጓደኛችን፣ በአገራችን ፣በሥራችን ፣በጥረታችን እምነት ያጣን። ‹‹የጅብ ችኩሎች፤ ቀንድ ነካሾች›› በተፈጥሮ ሂደት ‹‹ለምን እምነት፤ ለምን ትእግስት አጣን?››!! ሰላምአዲስ ዘመን  ጥር 10/2012ዳግም ከበደ
https://www.press.et/Ama/?p=25859
801
1መዝናኛ
የገዳ ስርዓት – የኦሮሞ ሕዝብ የትልቅነቱ ምልክትም ሀብትም
ሀገር አቀፍ ዜና
January 11, 2021
15
አስቴር ኤልያስ ስፍራው በተለያዩ የሴቶችና የወንዶች አልባሳት ደምቋል::በአልባሳቱ ላይ ገኖ የሚታየው ነጭ ቀለም በመሆኑም አስተውሎ ለተመለከተው ዙሪያ ገባውን የፈካ ማሽላ አስመስሎታል::በተለያዩ ድንኳኖች ውስጥ ደግሞ የጉጂ የባህል ምግቦች እንዲሁም የተለያዩ ጌጣጌጦችና አልባሳት ለእይታ ቀርበዋል::በዚሁ ስፍራ አምስት የጎጆ ቤቶች በመደዳ ተሰድረው ይታያሉ::ስፍራው በምዕራብ ጉጂ ዞን ቡሌ ሆራ ከተማ የጉጂ ኦሮሞ የባህል ስርዓት የሚካሄድበት ቦሌ ሀገላ ነው ::በዕለቱ የገዳ ስርዓቱን ደረጃ የሚያሳይ ትርዒት በስፍራው የተካሄደ ነው ፣ እነዚህም ደበሌ፣ ቀሬ፣ ኩሳ፣ ራባ፣ ዶሪ፣ ገዳ፣ ባቱ እና ዩባ የተባሉት ናቸው ትርዒቱን ያቀረቡት::በዕለቱ መርሐግብሩን በንግግር የከፈቱት የኢፌዴሪ ባህልና ቱሪዝም ሚኒስትር ዴኤታ ወይዘሮ ፈርያት መሀመድ እንደሚሉት፤ ኢትዮጵያ የብዙ ባህል ባለቤት ናት::የኦሮሞ ህዝብ ደግሞ ከትውልድ ወደትውልድ ሲያስተላልፍ የመጣው የገዳ ስርዓት አንዱ ነው ፣ ይህም የገዳ ስርዓት እንደ እሬቻ፣ ስንቄ፣ ሞጋሳና ሌሎችንም በርካታ እሴቶችን በውስጡ የያዘ ነው::እነዚህም እሴቶች ለኦሮሞ ብሎም ለአገሪቱ ሕዝቦች ወንድማማችነት እንዲጠናከር የሚያግዙ ናቸው ::የገዳ እሴቶች ውበታቸውንም ጥንካሬያቸውንም ጠብቀው ከትውልድ ወደትውልድ እንዲተላለፉ የሁሉም ድርሻ ነው የሚሉት ሚኒስትር ዴኤታዋ፣ ሚኒስትር መሥሪያ ቤታቸው ከክልሉ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ጋር በመሆን በቅንጅት እንደሚሰራም ነው ያረጋገጡት::የኦሮሚያ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ አቶ ከበደ ዴሲሳ በበኩላቸው፤ የገዳ ስርዓት ለኦሮሞ ሕዝብ ሀብቱም ምልክቱም መሆኑን ይናገራሉ::ኦሮሞ በዚህ ሥርዓት ሲተዳደር እንደነበር ሁሉ ዛሬም በመተዳደር ላይ እንደሚገኝም ጠቅሰው፤ በዚህ ሥርዓት ውስጥ መብት እንዳለ ሁሉ ግዴታ መኖሩን ያመለክታሉ::በተለይም ደግሞ ሰላማዊ የሆነ የስልጣን ሽግግርን አጥብቆ ስለሚከተል በዚህም ዓለም እንደሚያውቀው ነው የተናገሩት::እርሳቸው እንዳሉት፤ ይህ ስርዓት ቀደም ሲል በተወሰነ ደረጃ ተዳክሞ ነበር::ይሁንና በተሰሩ ጠንካራ ስራዎች አማካይነት በዩኔስኮ ከመመዝገቡም በተጨማሪ በክልል ደረጃ ከአንድ እስከ ስምንተኛ ክፍል ትምህርት የሚሰጥ ሲሆን፣ በዩኒቨርሲቲ ደረጃም እስከ ሶስተኛ ዲግሪ እየተሰጠ መገኘቱ ይበል የሚያሰኝ ጉዳይ ሆኗል::በመሆኑም ኦሮሞ አሊያም ኢትዮጵያ ብቻ የሚኮራበት ሳይሆን አህጉሪቱ አፍሪካ እንዲሁ የምትኮራበት ስርዓት ነው::የምዕራብ ጉጂ ዞን ምክትል አስተዳዳሪ አቶ ከድር ኤሌሞ በበኩላቸው፤ የሕዝቦችን አንድነት ይበልጥ ለማጠናከር ባህልን ማክበር ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰው፤ የገዳ ስርዓት ደግሞ የኦሮሞ ሕዝብ የሚተዳደርበት የዴሞክራሲ መሰረት የሆነ በመሆኑ ሊከበርም ከትውልድ ወደትውልድ ለማሸጋገር በሚደረገው ሂደት መተባበርም ተገቢ መሆኑን አስረድተዋል::የዴሞክራሲ መሰረት የሆነውን የገዳ ስርዓት ማጠናከር የሕዝብን አንድነት ለማጠናከር ትልቅ ሚና እንዳለውም ተናግረዋል::በዕለቱ ያነጋገርናቸው ወጣት ነጌቱ ደስታ እና ወጣት ሌሎ ሂርባዬ በየበኩላቸው፤ የገዳ ስርዓትን ለማስቀጠል በመጀመሪያ ግንዛቤን ከፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው የተናገሩት::በተለይ የዴሞክራሲ መሰረት ነው የተባለውና በተግባሩም እየታየ የሚገኘው ይኸው ስርዓት በዩኔስኮ መመዝገቡ ብቻ በራሱ የዴሞክራሲን ስርዓት እንደማያስቀጠል ጠቅሰው፤ ስርዓቱን በማስቀጠል ረገድ ከወጣቱ ብዙ እንደሚጠበቅ ነው ያመለከቱት::የገዳ ስርዓት መለያ ምልክታቸው እንደሆነም ይናገራሉ::የገዳ ስርዓት አንደኛውን ትውልድ ከሌላኛው ትውልድ የሚያያዝ መሆኑን የጠቀሱት ደግሞ ሌላኛዎቹ ወጣቶች ጫልቱ ደስታ እና ገመዴ ገናሌ ናቸው::ወጣቶቹ የገዳ ሥርዓት በዩኒቨርሲቲ ደረጃ መሰጠት መጀመሩ ለቅብብሎሽ ትልቁን ሚና የሚጫወት ስለመሆኑም ጠቅሰዋል::እነርሱ የተማሩት ከቤተሰቦቻቸው እንደመሆኑ እነሱም በቀጣይ ለትውልድ ለማስተላለፍ ያላቸውን ቁርጠኝነት ይናገራሉ:: ከትናንት በስቲያ የገዳ ስርዓት ለዓለም ቅርስነት የተመዘገበበትን 4ኛ ዓመት የመታሰቢያ በዓል ምክንያት በማድረግ የተዘጋጀ የገዳ ፓናል ውይይት በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የተካሄደ መሆኑ የሚታወስ ሲሆን በትናትናው ዕለት ደግሞ የጉጂ ባህልን የሚያመለክቱ የተለያዩ ዝግጅቶች ተካሂደዋል::ወጣቶች የገዳ ስርዓት የኦሮሞ ሕዝብ ሀብትም ምልክትም ነው የሚሉት::
https://www.press.et/Ama/?p=39254
429
0ሀገር አቀፍ ዜና
ጥምቀትና ሎሚ
መዝናኛ
January 21, 2020
36
ጥምቀት በህብረ ቀለማት ያሸበረቀና በልዩ ልዩ ክንዋኔዎች የተሞላ፤ ከሊቅ እስከ ደቂቅ የሚሳተፍበት፤ እንደሌሎቹ በዓላት በቤት ውስጥ የተገደበ ሳይሆን በአደባባይ የሚከበር ብዙዎች በጋራ የሚታደሙበት ክብረ በዓል ነው። ከሃይማኖታዊ ሥርዓቱ ባሻገር ባህላዊ ወግና ሥርዓቶችን አጣምሮ ያቀፈ፤ ከከተራ አንስቶ እስከ ጥምቀት ዕለቱ የተለያዩ ትዕይንቶች የሚስተናገዱበት ታላቅ በዓል ነው። በተለያዩ የተዋቡ አልባሳት የደመቁ ካህናትና ዲያቆናት በዓሉን ያደምቁታል። «ለጥምቀት ያልሆነ ቀሚስ ይበጣጠስ» እንደተባለው ሁሉ፤ በበዓሉ ለመታደም ከተለያዩ ስፍራዎች የመጡ ምዕመናን ከሌላ ክብረ በዓላት በተለየ መልኩ አዳዲስ አልባሳትን በመልበስ፤ አለበለዚያም ያላቸውን በደንብ አጥበው ለብሰው አምረው፣ አጊጠውና ደምቀው ታቦታቱን ያጅባሉ። በተለያየ የዕድሜ ክልል ውስጥ ያሉ የበዓሉ ታዳሚዎች በቡድን በቡድን ሆነው የተለያዩ ሃይማኖታዊና ባህላዊ ህብረ ዝማሬዎችና ጭፈራዎች ያከናውናሉ። እንደየአካባቢ ባህል የአከባበር ሥርዓቱ ቢለያይም ወጣቶች በአንድነት የሚያሳዩት ትዕይንት፤ ህብረ ቀለማዊ ጨዋታቸው በልዩ ልዩ ቋንቋዎች የሚያቀርቡበት መንገድ ልብ ይማርካል።በዓሉ የሰው አእምሮን በመግዛት ጥሎት በሚያልፍው አይረሴ ትዝታ አጓጊና ተናፋቂ ከመሆኑም ባሻገር፤ ስዕላዊ እይታ ይፈጥራል። ዘፈኖች፣ ጭፈራዎችና ውዝዋዜዎችም ይከወኑበታል። የሌላ እምነት ተከታዮችም ትዕይንቶቹን ለመካፈል ወደ በዓሉ ስፍራ ይነጉዳሉ። ለወጣቶች በትዳር ለመተጫጨት በር ከፋች መሆኑ የሚነገርለት የጥምቀት በዓል፤ ከድሮ ጀምሮ ሲወርድ ሲዋርድ የመጣው የሎሚ ውርወራ ታሪክም ከዚህ ጋር አብሮ መነሳቱ አይቀሬ ነው። በማህበረሰቡ እንደሚታወቀው በአብዛኛው የጥር የጋብቻ ወር ከመሆኑ ጋር ተያይዞ የመተጫጫው መንገዶች ቢለያይም ጥምቀት ግና ዋነኛው ነው። ጥምቀትና ሎሚ የማይለያዩና አብረው የሚነሱ መሆናቸው ለመተጫጨት በሚፈልጉ ሁለት ጥንዶች መካከል የሚከወኑ ክዋኔዎች አንድ ስለሚያደርጋቸው ነው። ሎሚ ወርዋሪው ጉብል የሚፈልጋትንና ልቡ የከጀላትን ወጣት ካገኘ ይወረውርና ፍቅሩን ይገልጻል። በዕለቱ አምረው የሚገኙት ወጣቶቹ አጋጣሚውን ወደ መልካምነት በመቀየር አብረው ይጫወታሉ፤ ይደሰታሉ። ጥምቀት ላይ ተጫጭተው ለትዳር የበቁ፤ ወልደው የከበዱ፤ ጥንዶች ብዛት ቤቱ ይቁጠረው እንጂ ስለ ብዛቱ ለመተንበይ ጥናት ይጠይቃል። ይህ ባህል በገጠር አካባቢ ትውፊትነቱ በተወሰነ መልኩ ቢቀየርም ዛሬም ድረስ የሎሚ ውርወራና የመተጫጨት ተግባር የሚከወንባቸው አካባቢዎች አሉ። ይህ ባህላዊ የመተጫጫ ክዋኔ የትወናና ስነቃል ወጉን ጠብቆ ከትውልድ ወደ ትውልድ ሲተላለፍ የኖረ ነው። ዛሬ ዛሬ ይህ ደማቅና ተናፋቂ ባህል እየተረሳ፤ የእኛ ባልሆኑ መጤ ባህሎች እየተተካ መሄዱ፤ የአደባባይ ምስጢር ከሆነ ውሎ አድሯል። ይህ ለምን ሆነ? ብሎ የሚጠይቅ ባለመኖሩ በወረርሽኝ ልማዶች የተጠመዱ ወጣቶች ባህላቸውን ረስተው ርቀው ከሄዱ ሰነባብተዋል። የወጣቶች ለትዳር መተጫጨት እንዳለ ሆኖ የተረሳው ግን የሎሚው ጉዳይ ነው። አብዛኞቹ ወጣቶች ስለሎሚ ሲጠየቁ ይህ ‹ቀርቶ ሌላ ዘፈን መጥቶ› ዓይነት ምላሽ ይሰጣሉ። ወጣቱ በሎሚ ፈንታ፤ በአፕል ስልክና በሊሞዚን ቁልፍ እየተተካ መሆኑን ከመናገር ባሻገር አፕሉም ሆነ የሊሞዚን ቁልፉ ሲወረወርና ጥንዶች ሲያስተጫጩ አይታዩም። ሎሚን የቀየረውስ አፕል በምን ተመርጦ ነው? ለሚለው ጥያቄም ወጣቶች ምላሽ ከዘመናዊነት ጋር ከማያያዝ በዘለለ የሚሰጡት አጥጋቢ ምላሽ የለም። ጥምቀት ሲመጣ አሁን አሁን በተለየ መልኩ ወጣቱን ሲማርከው የሚስተዋለው እና ሳይነሳ መታለፍ የሌለበት በአዲስ አበባ በጃንሜዳ የሚታየው የሀርሞኒካ ጭፈራ ነው። ይህንን የሚቃወሙ ቢኖሩም እንዴት እና ከየት መጣ? ቢቀጥልስ ምን ጥቅምና ጉዳት ሊኖረው ይችላል? የሚለውን ለአጥኚዎች እንተወውና ወደ ዋና ጉዳይ ስንመለስ የሎሚ ውርወራንና የጥምቀት በዓልን በማስተሳሰር ሎሚው እና በዓሉ ወደ ፌስቲቫል በማሳደግ፤ ለቱሪዝም መስብህነት በመጠቀም፤ ባህል በማስተዋወቅ፤ የገቢ ምንጮችን ለማሳደግ የሚቻልበትን መንገድ ለመፍጠር መጣር ግድ ይላል። የጥምቀት በዓል በተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣ የሳይንስና ባሕል ድርጅት ዩኔስኮ በቅርቡ በማይዳሰሱ ባህላዊ ቅርሶች ተመድቦ ዓለምአቀፍ እውቅና ማግኘቱና መመዝገቡን ይታወቃል። ይህንንም ተከትሎ የዘንድሮውን በዓል ለማክበርና ለመታደም ከሀገር ውስጥም ሆነ ከውጭ የሚመጡ በርካታ ቱሪስቶች ይኖራሉ። ይህንን አጋጣሚ በመጠቀም ከሃይማኖታዊ ሥርዓት ባሻገር ባህላዊ እሴትን በማሳደግ እና በማስፋት ለቱሪዝም መስህብነት በማዋል ትርፋማ መሆን ይቻላል በማለት የጠፋው የሎሚ ባህል ተመልሶ የቱሪስት መስህብ ሆኖ ለመገናኘት ያብቃን እያልን በዚሁ እንሰናበታቸሁ በቸር ያገናኝን። አዲስ ዘመን ጥር 11 /2012 ወርቅነሽ ደምሰው
https://www.press.et/Ama/?p=25918
500
1መዝናኛ
ከድጡ ወደ ማጡ
መዝናኛ
January 21, 2020
14
ሰዎችን ከሱስ ለማላቀቅ የማይፈነቀል ድንጋይ የለም። ምክር፣ ህክምና፣ ለደግ ሲባል ማግለል እና የመሳሰሉት ሁሉ ይሞከራሉ። በተለይ ቤተሰብ ቤቱን ቆሌ ያራቀውን ይህን ችግር ለመፍታት ብዙ ይጥራል። ይህ ጥረት ጥቂቶችን ሲታደግ ቢስተዋልም፣ ያደቆነ ሰይጣን ሳያቀስ አይተውም እንዲሉ ይህን ሁሉ አሸንፈው እስከ ህይወት ፍጻሜያቸው ሱሰኛ የሚሆኑ ሰዎች ግን በርካታ ናቸው። ሜክሲኮዊቷ የባሏ መሸተኛነት መሆን በእጅጉ ያስመርራታል። መከረች ዘከረች አልሆን አላት። ቢራ መጨለጡን ሊተው ባለመቻሉ ከዚህ ችግር ሊገላግላት የሚችለውን መላ ማፈላለግን ትመርጣለች። አንድ ቀንም አንድ ሀሳብ ብልጭ ይልላታል። ቢራ እርም እንዲል ያረገዋል ያለችውን መላም ተግባራዊ ለማድረግ ትወስናለች። ሚቼል ኤን የተባለችው ይህች የሜክሲኮ ሲናሎአ ከተማ ነዋሪ፣ ለእዚህ ውሳኔዋ መሳሪያ ይሆኑኛል ስትል ያሰበቸውን ውህድ ከእንግሊዝ ጨውና ከዘይት መሰል ነገር ታዘጋጃለች። ንጥረ ነገሮቹ ቀስ በቀስ ሥራቸውን እንዲያከናወኑ ያስችላል ያለችውን ቅመማም ታደርጋለች። ለእዚህም የተለያዩ ድረ ገጾችን እስከማንበብ ትደርሳለች። ውሳኔዋን ስራ ላይ ለማዋልም ባለቤቷ ጆሴ በራያን ሳያይ ጥቂት ጠብታዎችን በቢራ ጠርሙሶቹ ውስጥ ትጨምራለች። ያህን ያላየው ባለቤቷም እንደ ወትሮው ቢራውን መጨለጡን ይቀጥላል። ቀስ በቀስ ግን ባልተለመደ መልኩ ሆዱን መታመም ይጀምራል፤ ክፉኛ ማስቀመጥም ይጀምረዋል። እሱ ግን ብዙም እንደ ችግር አልተመለከተውም። ሚቼል ግን ተቅማጡ የሆነ አለርጂ ያስከተለው ሳይሆን አይቀርም ስትል ትገልጽለታለች። ችግሩ ምንአልባትም ከአልኮሆል ጋር ሊያያዝ እንደሚችልም ትጠቁመዋለች። እሱ ግን የምትለውን ከቁብ ሳይቆጥር አሁንም እንደ ወትሮው መጠጣቱን ይቀጥላል። ለሆድ ህመሙም ማስታገሻ እየወሰደ መጨለጡን ይቀጥላል። ባለቤቱ ይህ ነገር አይሆንም መጠጣትህን አቁም ትለዋለች፤ተቅማጡ ቢያስቸግረውም መጸዳጃ ቤቱ አጠገቤ እስከ ሆንኩ ድረስ ይህ አያስጨንቀኝም እያለም በባለቤቱ እየቀለደ ይጠጣል። ሚቼል ግን የባለቤቷን ፌዝ ወደ ጎን በመተው አሁንም ሌላ መላ ማፈላለግን ስራዋ ታደርጋለች። በቢራው ውስጥ የምትጨምረውን ንጥረ ነገር መጠን በመጨመርም ቢራውን ማቅረብ ትጀምራለች። በቀጣዩ ቀን የባለቤቷ ተቀማጥ አሳሳቢ እየሆነ ይመጣል። መጸዳጃ ቤት ለመድረስ እንኳ እድል የሚሰጥ አልሆን ይለዋል። እሷም ጉዳዩ በጣም ያሳስባትና በአቅራቢያቸው ወደ ሚገኝ ሆስፒታል ይዛው ትሄዳለች። ጆሴ በምርመራ ወቅት ለሀኪሞች ችግሩ ምናልባትም ከሚጠጣው ቢራ ጋር የተያያዘ ሊሆን እንደሚችል ይገልጽላቸዋል፤ ከህመሙ ለመፈወስ ሲል ሁለተኛም ቢራ በደረሰበት እንደማይደርስ ያረጋግጥላቸዋል። ቢራው ሆዱን ከማሳመም በተጓዳኝ መቀመጥ እንደከለከለውና ሰላም እንደነሳው ይነግራቸውና አለመጠጣቱን እንደሚመርጥ ይገልጽላቸዋል። ቫንጋርዲያ የተሰኘው የሜክሲኮ ጋዜጣ ጉዳዩን አስመልክቶ እንደሰራው ዘገባ፣ ያቀደችው ያልተሳካላት ይልቁንም ሌላ ጣጣ ያመጣባት ባለቤቱ በሰራችው ድርጊት ትጸጸታለች፤ ባሏ ቢራ እንዲጠላ ለማድረግ በቢራ ውስጥ ባእድ ነገር መጨመሯን በመግለጽ ለተቀማጡ ምክንያቱ እሷ መሆኗን ታስታውቃለች። ጉዳዩ ፖሊስ ዘንድ ይደርስናም ጆሴ ባለቤቱ ከፍታ በምታቀርብለት ቢራ ጠርሙስ ውስጥ አንዳንዴ ባእድ ነገር ይመለከት እንደነበር ለፖሊስ ገልጾ፣እሱ ግን ይህን ያህል ጎጂ ነገር ሊሆን ይችላል ብሎ አስቦም ገምቶም እንደማያውቅም ይናገራል። ፖሊስም ሚቼል በፈጸመችው ድርጊት በተጠ ርጣሪነት በቁጥጥር ስር ያውላታል፤ በእዚህ ድርጊቷም ፍርድ ቤት ቀርባ ቅጣት ሊጣልባት እንደሚችልም ፖሊስ መግለጹን ኦዲቲ ሴንትራል የተሰኘው ድረገጽ መረጃ ያመለክታል። የሚወዱትን ሰው ከችግር ለመታደግ ሲባል የሚወሰድ እርምጃ ሌላ ችግር እንዳያስከትል መጠንቀቅ እንደሚገባ ዘገባው ያመለክታል። አዲስ ዘመን ጥር 12/2012ዘካርያስ
https://www.press.et/Ama/?p=25947
399
1መዝናኛ
193 አትሌቶች ከዓለም አትሌቲክስ የገንዘብ ድጋፍ ተጠቃሚ ይሆናሉ
ስፖርት
June 25, 2020
9
የዓለም አትሌቲክስ ከዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ፋውንዴሽን ጋር በመተባበር በኮሮና ቫይረስ ሥርጭት ምክንያት ከውድድር በመራቃቸው የገንዘብ ችግር ሊገጥማቸው ይችላል ለተባሉ አትሌቶች ድጋፍ እንደሚያደርግ ባለፈው ሚያዝያ መጨረሻ ማሳወቁ ይታወሳል። የዓለም አትሌቲክስ ለዚሁ ድጋፍ እንዲውል አምስት መቶ ሺህ ዶላር ማዘጋጀቱ የሚታወቅ ሲሆን ይህን ድጋፍ ለአትሌቶች ለማድረስ የዓለም አትሌቲክስ ፕሬዚዳንቱ ሴባስቲያን ኮ በሊቀመንበርነት የሚመሩት የባለሙያዎች ቡድን ተቋቋሞ በስድስት ዞኖች በተከፋፈለው የዓለም አትሌቲክስ አባል አገራት የሚገኙ አትሌቶች የሚያቀርቡት የድጋፍ ጥያቄ ተጣርቶ ዕርዳታው መሰጠት ጀምሯል። በዚህም መሠረት መቶ ዘጠና ሦስት አትሌቶች ተለይተው ድጋፉ እንደደረሳቸው ታውቋል። ዕርዳታው የሚሰጣቸው አትሌቶች ከሃምሳ ስምንት የዓለም አትሌቲክስ አባል አገራት ፌዴሬሽኖች የተለዩ ሲሆን እያንዳንዳቸው በመጀመሪያው ዙር ድጋፍ ሦስት ሺህ ዶላር እንደሚደርሳቸው ተጠቆሟል። የድጋፍ ጥያቄውን ለማቅረብ የተሰጠው ቀነ ገደብ ባለፈው የፈረንጆች ግንቦት ሰላሳ ቀን የተጠናቀቀ ሲሆን ሁለት መቶ ስልሳ አንድ አትሌቶች የድጋፍ ጥያቄውን አቅርበው ጉዳዩን የሚመረምረው የባለሙያዎች ቡድን በተቀመጠው መስፈርት መሠረት አጣርቶ መቶ ዘጠና ሦስት አትሌቶች ድጋፉን እንዲያገኙ ውሳኔ አሳልፏል። የባለሙያዎቹ ቡድን ድጋፉን ለመስጠት በዋናነት ከተመለከታቸው መስፈርቶች መካከል አንድ ድጋፍ የሚሻ አትሌት በቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ አገሩን ለመወከል የተመረጠ መሆን እንዳለበት፣ ለገጠመው የገንዘብ ችግር አሳማኝ ማስረጃ ማቅረብ የሚችል፣ ካለፈው የውድድር ዓመት አኳያ የሚያገኘው ገቢ በእጅጉ የቀነሰና ከአበረታች መድሃኒት ተጠቃሚነት ጋር በተያያዘ ምንም አይነት ክስ ያልቀረበበት መሆን እንደሚገባው ጠቁመዋል። በተጨማሪም በየትኛውም የውድድር አይነት በዓለም አትሌቲክስ የደረጃ ሰንጠረዥ ከአንድ እስከ ስድስት ባለው ውስጥ ስማቸው የሰፈረ አትሌቶች፣ በ2019 በየትኛውም የወርቅ ደረጃ ባለው የጎዳና ላይ ውድድር እስከ ስድስት ባለው ደረጃ ያጠናቀቁ እንዲሁም በ2019 የዳይመንድ ሊግ ውድድሮች እስከ ስልሳ ሺህ ዶላር ድረስ ሽልማት ያገኙ አትሌቶች የድጋፍ ጥያቄያቸው ተቀባይነት እንደሌለው ታውቋል። ድጋፉን የሚያገኙ አትሌቶች ወይም አገራት ስም ያልተጠቀሰ ሲሆን ጥያቄያቸው ተመርምሮ ድጋፍ የሚደረግላቸው አትሌቶች በዚህ ሳምንት መጨረሻ ገንዘቡ እንደሚደርሳቸው ተጠቁሟል። የዓለም አትሌቲክስ ፕሬዚዳንት እንዲሁም የዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ፋውንዴሽን ሊቀመንበር ሴባስቲያን ኮ ይህን ድጋፍ ለአትሌቶች ለመስጠት እንደታሰበ በሰጡት መግለጫ ወቅት እንዳስቀመጡት፣ የገንዘብ ድጋፉ ባለፉት ጥቂት ወራት ከውድድር በመራቃቸው ምንም አይነት ገቢ አጥተው የገንዘብ ቀውስ ውስጥ ለገቡ አትሌቶች ይውላል። እ.ኤ.አ በ1986 በሞናኮው ልዑል አልበርት ሁለተኛ አማካኝነት በአትሌቲክስ ስፖርት ለሚገጥሙ ችግሮች የበጎ አድራጎት ሥራዎችን ለማከናወን የተቋቋመው የዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ፋውንዴሽን ካለው በጀት ላይ ቀንሶ አትሌቶች በኮሮና ቫይረስ ምክንያት ለገጠማቸው ችግር ድጋፍ እንዲውል ማድረጉ ይታወቃል። ድጋፉን ለመስጠት ከተቋቋመው ኮሚቴ መካከል የቀድሞው የኦሊምፒክ የ1500 ሜትር አሸናፊው ሞሮኳዊ አትሌት ሂቻም ኤልግሩዥ፣ የምርኩዝ ዝላይ የዓለም ቻምፒዮኗ ካተሪና ስቲፋኒዲ (የዓለም አትሌቲክስ ኮሚሽንን ወክላ)፣ የዓለም አትሌቲክስ ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል ሱኒል ሳብሃርዋልና ኤቢይ ሆፍማንና ሌሎችም ተካተዋል። ‹‹ሂቻም ኤልግሩዥ ይህን የድጋፍ ሃሳብ በማቅረቡና ልዑል አልበርት ይህን ፕሮጀክት እውን ለማድረግ ላበረከተው ጠንካራ ድጋፍ ላመሰግናቸው እወዳለሁ›› በማለት ሃሳባቸውን ያሰፈሩት ሴባስቲያን ኮ፣ በዚህ አስቸጋሪ ወቅት ከዓለም አትሌቶች ጋር በተለያየ መንገድ የቅርብ ግንኙነት እንዳላቸው በመጠቆም ዓለም አቀፍ ውድድሮች በመሰረዛቸው በርካታ አትሌቶች የገቢ ምንጫቸው እንደ ደረቀና የገንዘብ ችግር እንደገጠማቸው አብራርተዋል። በኮሮና ቫይረስ ምክንያት የዓለም አትሌቲክስ ውድድሮች በእጅጉ መጎዳታቸውን ያስታወሱት ኮ፣ አትሌቶች ገቢያቸው ከውድድር የሚያገኙት ሽልማት እንደመሆኑ በዓመቱ መጨረሻ የተወሰኑ ውድድሮችን በማካሄድ ስፖርቱንና አትሌቶቹን እንዳይዳከሙ የማድረግ ተስፋ እንዳላቸው ተናግረዋል። አትሌቶችን ለመደገፍ አሁን ከተያዘው በጀት ባሻገር የስፖርት ቤተሰቡ በሚያደርገው ድጋፍ ተጨማሪ የረድኤት ሥራዎች እንደሚከናወኑም ጠቁመዋል። ልዑል አልበርት ሁለተኛ በበኩላቸው ፋውንዴሽኑን ከመሠረቱ ከሰላሳ አምስት ዓመታት በላይ እንደሆነ በማስታወስ የፋውንዴሽኑ አላማ አትሌቲክስን ማበረታታትና ብሔራዊ አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች እንዲሁም አትሌቶች በችግር ጊዜ የገንዘብ ዋስትና እንዲኖራቸው ማድረግ መሆኑን ጠቁመዋል። በዚህም መሠረት ፋውንዴሽኑ ባለፉት ዓመታት ሰላሳ ሚሊየን ዶላር ለተመሳሳይ አላማ እንዳዋለና አሁንም አትሌቶች በሚቸገሩበት በዚህ ወቅት ሊደርስላቸው በመቻሉ የተሰማቸውን ደስታ ገልፀዋል። ይህ ድጋፍ አትሌቶች ኦሊምፒክን ጨምሮ ለዓለም አቀፍ ውድድሮች የሚያደርጉትን ዝግጅት እንዳያቋርጡና በገጠማቸው ችግር ውጥረት ውስጥ እንዳይገቡ ሊረዳቸው እንደሚችልም አክለዋል። የቀድሞው የ1500 ሜትር የዓለም ክብረወሰን ባለቤትና የድጋፉ ሃሳብ አመንጪ አትሌት ኤልግሩዤ በበኩሉ፣ የኮሮና ቫይረስ በሁሉም ዓለም ሕዝብ ላይ ትልቅ ኢኮኖሚያዊ ተጽዕኖ እንዳሳደረ በማስታወስ ሁሉም የዓለም ሕዝብ ይህን ችግር ለመጋፈጥ በጋራ የሚቆምበት ወቅት አሁን መሆኑን አብራርቷል። የዓለም አትሌቲክና ፕሬዚዳንቱ የድጋፍ ሃሳቡን በቅንነት ስለተቀበሉትም ምስጋናውን አቅርቧል። ዓለም አቀፍ ውድድሮች በመታገዳቸውም በርካታ አትሌቶች ሊደርስባቸው የሚችለውን የኢኮኖሚ ጫና በማሰብ ይህን በጎ ተግባር መፈፀም እንደሚያኮራም ተናግሯል፡፡አዲስ ዘመን ሰኔ 18/2012 ቦጋለ አበበ
https://www.press.et/Ama/?p=35069
583
2ስፖርት
ከቤሌር ሜዳ እስከ ቤልጂየም የዘለቀው ኮከብ
ስፖርት
June 28, 2020
16
በኢትዮጵያ እግር ኳስ አፍቃሪ ልብ ውስጥ በብዙ የሚታወስ ነው። እግር ኳስን ከልጅነት እስከ እውቀቱ ተጫውቷል። አሁንም ቢሆን ከክቧ ኳስ አልራቀም። የቅዱስ ጊዮርጊስ እግር ኳስ ክለብ የቡድን መሪ ሆኖ አገልግሏል። ባዩ ሙሉ። የመጀመሪያውን የምሥራቅ አፍሪካ የታዳጊዎች ቻምፒዮና ለኢትዮጵያ ዋንጫ ይዘው ከመጡ ተጫዋቾች መካከል አንዱ ሲሆን በጊዜው የእርሱ ድርሻ ጉልህ ነበር። ከዚህም ሌላ ኬንያ ባዘጋጀችው «የሴካፋ ቻምፒዮና» ላይ ኮከብ ተጫዋች ሆኖ ለመመረጥም በቅቷል። በምሥራቅ አፍሪካ ውድድር ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ ከአገር ውጪ ሩዋንዳ ላይ ዋንጫ ስታነሳ በፍፃሜው ጨዋታ ላይ የማሸነፊያዎቹን ሁለት ግቦች አስቆጥሯል። ባዩ ለቅዱስ ጊዮርጊስ ሁለት ዓመት በዋናው ክለብ ተሰልፎ ተጫውቷል። በፕሮፌሽናል ተጫዋችነትም ቢሆን በር ከፋች ነው። በቤልጂየም አገር ለረጅም ጊዜ ለተለያዩ ክለቦች ተጫውቷል። አንጋፋዋ የቀበና ቤሌር ሜዳ ካበቀለቻቸው የአገር ባለውለታዎች ተርታም የሚመደብ ነው። እኛም በዛሬው የስፖርት ማህደር አምዳችን የዚህን ተጫዋች ህይወት በስፋት ለመዳሰስ ወደድን። የልጅነት ትውስታ የቤሌር ሜዳ በኢትዮጵያ በተለይም በአዲስ አበባ ተወላጆች ዘንድ ትልቅ ቦታ አለው። ቀበና መድሀኒ ዓለም ቤተክርስቲያን አካባቢ የሚገኘው ይህ ሜዳ በርካታ አንጋፋ የእግር ኳስ ተጫዋቾችን አፍርቷል። ቤሌር በርካታ አንጋፋ ተጫዋቾች የወጡበት ነው። ሜዳው እግር ኳስን ከንጋት ጀምሮ ሰማዩ ለአይን እስኪይዝ ድረስ የአካባቢው ተወላጆች እና ከሌላ ሰፈር የሚመጡ ታዳጊዎች ዛሬም ድረስ የሚጫወቱበት ነው። የያኔው ታዳጊ ባዩ ደግሞ ከዚህ ሜዳ ጀርባ በሚገኙ መንደሮች ውስጥ ነበር ተወልዶ ያደገው። ጊዜውም 1971 ዓ.ም ነው። ንጉሴ ገብሬን፣ ሰለሞን ሀይለ ማሪያምንና ሲሳይ ሽፈራውን የመሳሰሉ አንጋፋ ተጫዋቾችን ተመልክቶ ኳስ እያቀበለ ነው ያደገው። ባዩ እግር ኳስ በልጅነት ልቦናው ውስጥ ትልቅ ስፍራ እንዲኖረው አንጋፋ ተጫዋቾች ድርሻ ነበራቸው። ለቤሌር ታዳጊዎች እግር ኳስ ከምንም ነገር በላይ ነው። እንደ መዝናኛ፣ ጊዜ ማሳለፊያ እና ተስፋ ያለው ጎበዝ እግር ኳስ ተጫዋች የመሆን ህልምን እንደማሳኪያ ያገለግላል። በዚህ እድል ውስጥ ያለፈው ባዩ በፍቅር ከሚያንከባልላት ኳስ ጋር የእድሜ ዘመን ወዳጅነትን መስርቷል። ከትምህርት ቤት መልስ እንዲሁም በእረፍት ቀን በቤሌር ሜዳ ላይ ከእድሜ እኩዮቹ ጋር ይጫወታል። ውድድሮችን ከሌሎች የአካባቢ ልጆች ጋር ያደርጋሉ። የአካባቢው ሰዎች እና እግር ጥሏቸው በስፍራው የሚያልፉ ሰዎችም ይህን ፍልሚያ ልክ እንደ ስታዲየም በመክበብ ይመለከቱ ነበር። ይህ ደግሞ ለታዳጊው ትልቅ ተጫዋች ለመሆን ህልም ለነበረው ባዩ ትልቅ የሞራል ስንቅ ነበር። አዲስ መንገድ ባዩ የ7ተኛ ክፍል ተማሪ ሆኗል። 12ተኛ ዓመቱንም ይዟል። በሰፈሩ እግር ኳስ ውድድሮችን ቀበሌ ያዘጋጅ ነበር። በዩ እድሜ ደረጃው ቡድኖች ተዋቅረዋል። እሱ እድሜው ገና ቢሆንም የእግር ኳስ ችሎታው ጥሩ ስለነበር በ«ቢ» ቡድኑ ውስጥ ሊመረጥ ቻለ። የእድሜ ልዩነቱ እጅግ ሰፊ ቢሆንም አብሯቸው ልምምድ ያደርግ ነበር። ለአንድ ዓመት ያክል በዚህ ስብስብ ውስጥ ውድድሮችን እና ልምምድ ሲሰራ ቆየ። ሆኖም ግን ቡድኑ በተለያዩ ምክንያቶች ፈረሰ። እነ ባዩም የመበተን አደጋ ገጠማቸው። ነገር ግን የሰፈር ልጆች ተሰባስበው አዲስ ቡድን በግላቸው ጥረት አቋቋሙ። አሰልጣኝ በራሳቸው ሾመው የቀበሌውን ማሊያ ማግኘት ስለቻሉ ልምምዳቸውን ቀጠሉ። ቀይና ሰማያዊው የቤሌር ልጆች መለያ የባዩ የመጀመሪያ ቡድን ሆነ። ከሰፈራቸው እየወጡ ውድድሮችን ማድረግ ጀመሩ። ከ6 ቀበሌ፣ ከላይ ሰፈር ቀበና ልጆች፣ ከአራት ኪሎ እና ከሾላ ልጆች ጋር ውድድር ማድረግ ጀመሩ። ባዩ በወቅቱ የፊት መስመር ተጫዋች በመሆን በጨዋታ ላይ ብዙ ጎሎችን ያስቆጥር ነበር። ያልተጠበቀው አጋጣሚ ጊዜው 1985 ዓ.ም ነበር። ባዩ እና እግር ኳስ እስካሁን የግንኙነታቸው ገመድ አልተበጠሰም። እንዲያውም ወዳጅነታቸው ይበልጥ ጠንክሯል። በሳምንት ሶስት ጊዜ በቤሌር ሜዳ ከጓደኞቻቸው ጋር ልምምድ ያደርጋሉ። አንጋፋውን የጣሊያን ቡድን ጁቬንትስ ስም የያዘ ክለብ አቋቁመዋል። የ14 ዓመት ታዳጊው ባዩ እና ጓደኞቹ እንደተለመደው ልምምድ ለመስራት በቤሌር ሜዳ ተገኝተዋል። በአዲስ አበባ ተወዳጅ ስለሆነ ትልልቅ የእግር ኳስ ክለቦች አልፎ አልፎ በዚህ ስፍራ እየመጡ ልምምድ ያደርጉ ነበር። ክለቦቹ ታዳጊ ልጆችንም ይመለምሉ ነበር። የዚያን እለት ደግሞ ተራው የአንጋፋው እና ተወዳጁ ቅዱስ ጊዮርጊስ ነበር። በአጋጣሚ በስፍራው ተገኝቷል። አሰልጣኝ ስዩም ከበደ የሚያሰራቸው የቅዱስ ጊዮርጊስ የ«ሲ» ቡድን ልጆች ነበሩ። መለማመጃ ሜዳ በማጣታቸው በዚህ ስፍራ ተገኝተዋል። እነ ባዩ ደግሞ በሜዳው ላይ እየተጫወቱ ነበር። በጊዜው ስዩም ሜዳውን ለልጆቹ እንዲለቀቅ ሲጠየቅ ባዩና አንዳንድ ጓደኞቹ ጊዮርጊስ ትልቅ ክለብ ስለነበር ወደ ዳር ወጡ። አንዱ ጓደኛቸው ግን ‹‹አሻፈረኝ »አለ። በወቅቱ ሜዳው ላይ አለመግባባት በመፈጠሩ የባዩ ቡድን እና የጊዮርጊስ ቡድን ግጥሚያ እያደረጉ ልምምድ እንዲያደርጉ ተገደዱ። ይህም አጋጣሚ ደግሞ ያልተጠበቀ ነገር እንዲከሰት አደረገ። ጨዋታው ተጀምሯል። ሜዳውን አንለቅም ያሉት የቤሌር ታዳጊዎች የቅዱስ ጊዮርጊስ ክለብን ታዳጊዎች እየገጠሙ ነው። አሰልጣኝ ስዩም የሚያለማምዳቸው ልጆች ብቻ ሳይሆን ከዚያኛው ወገን ያሉትንም በጥሞና ይመለከታል። በድንገት የአንድ ታዳጊ ኳስ አያያዝ እና አጨዋወት ትኩረቱን ሳበው። ይሄ ታዳጊ ከቤሌር ሜዳ የበቀለው የ14 ዓመቱ ባዩ ነበር። ስዩም ጨዋታውን አቋርጦ ወደሱ እንዲመጣ አደረገው። የመጀመሪያ ጥያቄው «ለክለብ ትጫወታለህ» የሚል ነበር «አረ በፍፁም» በማለት ባዩ መለሰ ። በድጋሚ ወደ ሜዳው እንዲገባ እና እንዲጫወት ጠየቀው። ባዩ አሁንም በተመሳሳይ ድርጊት ማራኪ የእግር ኳስ እንቅስቃሴ አደረገ። ስዩም የባዩን ችሎታ በማድነቅ ለትልቅ ክለብ ይጫወት እንደሆነ በድጋሚ ጠየቀው። እሱ ግን በሰፈር ካቋቋሙት ክለብ ውጪ እንደማይጫወት አስረግጦ ነገረው። አጨዋወቱ ልምድ ያለው እና ታዋቂ ክለቦች ጋር የሚጫወት ይመስል ነበር። በቅዱስ ጊዮርጊስ ታዳጊ ቡድን ውስጥ ለመሰለፍ ጊዜ ያልወሰደበት ባዩ በዚያው ዓመት ቡድኑ ቻምፒዮን በመሆኑ ድሉን ከጓደኞቹ ጋር አጣጣመ። በወቅቱ በነበረው እግር ኳስ ከታዳጊ ቡድኑ ወደ «ቢ» እና ዋናው ቡድን ለማደግ ቢያንስ ከ3 እና ከአራት ዓመት በላይ ይወስድ ነበር። ሆኖም ባዩ ወደ ቢ ቡድን ለመሸጋገር ይህን ጊዜ አልወሰደበትም ነበር። ሁለት የውድድር ዘመን እንዳሳለፈ ለዋናው ቡድን ለልምምድ ተጠራ። በወቅቱ ብሄራዊ ቡድኑ ለኢንተርናሽናል ጨዋታ 9 ልጆችን ከቅዱስ ጊዮርጊስ መውሰዱ ለባዩ ወደ ዋናው ቡድን መሄድ ትልቅ እድል ከፍቶ ነበር። ባዩ ለዋናው ቡድን ቢመረጥም የልምምድ ሰዓቱ ከትምህርቱ ጋር በመጋጨቱ መቅረት ጀመረ። ወቅቱ 1987ዓ.ም ነው። እሱ ደግሞ የ11ኛ ክፍል ተማሪ ሆኗል። የዋናው ቡድን አሰልጣኝ አስራት ሀይሌ በባዩ ብቃት እና ታዳጊነት ተስቧል። እሱን ማጣት ባለመፈለጉም ሙሉ ለሙሉ ካምፕ እንዲገባ ጠየቀው። ባዩ አስራት የሰጠውን እድል ለማመን አልቻለም። ማንም በዚህ ፍጥነት ለዋናው ቡድን ተመርጦ አያውቅም። ለእግር ኳስ ጨዋታ ከፍተኛ ፍቅር ስላለው የአሰልጣኝ አስራትን ጥያቄ በደስታ ተቀብሎም ወደ ካምፕ ገባ። ይህ ደግሞ ከአንጋፋዎቹ ሙሉጌታ ከበደ፣ ተስፋዬ ኡርጌቾ፣አሸናፊ ሲያይ እንዲሁም ዮሴፍ ሰለሞንን ከመመሳሰሉ ተጫዋቾች ጋር እግር ኳስ መጫወት አስችሎታል። በቅዱስ ጊዮርጊስ ቤት በተቀያሪነት ያገኘው የመሰለፍ እድል ሌላ በር ከፈተለት። የአሰልጣኝ ስዩም አባተ አይኖች በባዩ እግሮች ላይ አረፉ። ወደ ኬንያ ለሚጓዘው ታዳጊ ብሄራዊ ቡድን ተሰላፊ እንዲሆን ተመረጠ። አሁን አገሩን ሊወክል ነው። ይሄ ሂደት የእውነትም ባዩ ለእግር ኳስ መፈጠሩን ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ነበር። በኬንያ ሞንባሳ በተካሄደው የታዳጊዎች የሴካፋ ውድድር ሁሉንም ጨዋታዎች ላይ በመሰለፍ እንዲሁም በፍፃሜው ጨዋታ ሁለት ግቦችን ከመረብ በማሳረፍ ታሪክ መስራቱን ጀመረ። በ1988 ዓ.ም በቅዱስ ጊዮርጊስ ቤት ባዩ ሙሉ የመሰለፍ እድል አገኘ። በመሀል ተጫዋችነት እና በግራ መሀል ተከላካይነት ሙሉ ዓመቱን ተጫወተ። በታዳጊ ብሄራዊ ቡድኑ ላይ ያሳየው ምርጥ ብቃት አሰልጣኝ ስዩም አባተን ከማስደሰቱም በላይ ክለቡ እምነት እንዲጥልበት አድርጎ ነበር። የእግር ኳስ ህይወቱም ወደፊት በእድገት መስመር ላይ መክነፉን ቀጠለ። በዚያ ዓመት የኢትዮጵያ ቻምፒዮና፣ የአሸናፊዎች አሸናፊን ጨምሮ የጥሎ ማለፉን ዋንጫ ባዩ ከክለቡ ጋር ለመሳም በቃ። ብሄራዊ ቡድኑን መወከል ቀጥሏል። ኮካኮላ ምስራቅና መካከለኛው አፍሪካ የታዳጊ ዋንጫ ላይ በ1988ዓ.ም መጨረሻ ላይ ተሳታፊ ሆነ። በዚህ ቡድን ላይ ባዩ አምበል ከመሆኑ ሌላ ኢትዮጵያ ቻምፒዮን ስትሆን በኮኮብ ተጫዋችነት ተመርጧል። ውድድሩ ደግሞ ተጨማሪ ሲሳይ ይዞለት ብቅ ብሏል። ባዩ ምን ገጥሞት ይሆን? ያልተሄደበት መንገድ የኮካ ኮላ የምስራቅ እና መካከለኛው አፍሪካ የታዳጊ ዋንጫ ላይ ዓለም አቀፍ ደላሎች ተገኝተው ተጫዋቾችን የመመልመል ስራ ይሰሩ ነበር። ይህ አጋጣሚ የመልማዮችን አይን በባዩ ላይ እንዲያርፍ አደረገ። ይሄ ደግሞ የፕሮፌሽናል እግር ኳስ ተጫዋች የመሆን ህልሙን ያሳካበት ጅምር ነበር። መልማዩ ወደ ቤልጂየም ክለቦች ሄዶ ሙከራ እንዲያደርግ ጥያቄውን አቀረበለት። ከእርሱ ጋር የቡድን አጋሩ ጌትነት ሞት ባይኖር እጩ ተመራጭ ነበር። 1989 ዓ.ም ባለፈው ክረምት ለባዩ የመጣው እድል እውን የሆነበት ነበር። በውድድር ዘመኑ መሀል ላይ ለሙከራ ወደ ቤልጂየም እንዲሄድ ጥሪ ቀረበለት። አስፈላጊውን ጉዳይ አጠናቆም ወደ ቤልጅየም አቀና። በዚያም ለቤልጄሙ ሎክረን ክለብ ፈረመ። ባዩ በወቅቱ እድሜው ትንሽ ነበር። በዚያ ላይ የአገሪቷን ቋንቋ አይችልም። በክለቡ ለአንድ ዓመት ከመንፈቅ ቢፈርምም በወቅቱ የተለያዩ አለመግባባቶች ይፈጠሩ ነበር። ተገቢውን ጥቅማጥቅም አለመክፈላቸው አንዱ ችግር ነው። ይሄ ጉዳይ ተደምሮ በዚያው በቤልጅየም ባዩን የሚፈልግ የ3ተኛ ዲቪዚዮን ክለብ ለመፈረም ቻለ። ባዩ አሁን ላይ ሆኖ የቤልጅየም ቆይታውን ያስታውሳል። የእግር ኳስ ደረጃቸው ከፍተኛ እንደነበር ይናገራል። ዘረኝነትን የመሰሉ አንዳንድ ችግሮች ይገጥሙት እንደነበረ ግን አይደብቅም። ችግሮቹን ተቋቁሞም ፕሮፌሽናል እግር ኳስ ተጫዋችነቱን አሳክቷል። ቤልጅየም ለሶስት ዓመታት ቆይታ ካደረገ በኋላ ለእረፍት ወደ አገሩ የመምጣት እድል ገጠመው። በ1992 ዓ.ም «ፕሮፌሽናል ተጫዋች ለመሆኔ ትልቅ መሰረት ጥሎልኛል» በማለት ሁሌም ከሚያመሰግነው አሰልጣኝ አስራት ሃይሌ ጋር በድጋሚ ተገናኘ። አስራት በወቅቱ የብሄራዊ ቡድኑ አሰልጣኝ በመሆን ይሰራ ነበር። ባዩ ብሄራዊ ቡድንን ወክሎ እንዲጫወትም ፍላጎት ነበረው። ሆኖም በጊዜው ብቸኛው ፕሮፌሽናል ተጫዋች መሆኑ እየታወቀ ብሄራዊ ቡድኑን ወክሎ እንዲጫወት ጥያቄ ሲያቀርብ ያገኘው ምላሽ ተገቢ አልነበረም። ፌዴሬሽኑ ባዩን በአገር ውስጥ ባሉ ክለቦች ተጫውተህ መታየት አለብህ የሚል ምላሽ በመስጠት ቅሬታ ፈጥረውበት ነበር። አሰልጣኝ አስራት ሃይሌ ግን የባዩን የእግር ኳስ ክህሎት በሚገባ ያውቅ ስለነበር ቡድኑን እንዲቀላቀል ይፈልግ ነበር። በወቅቱ ፌዴሬሽኑ ለባዩ የሰጠው ምላሽ የአገር ውስጥ ስፖርት ቤተሰብን እና የመገናኛ ብዙሀንን ያነጋገረ ነበር። በነገሩ ቅር የተሰኘው ባዩም ወደ ክለቡ መመለስ ስለነበረበት ወደ ቤልጅየም ተጓዘ። ከአንድ ወር በኋላ ግን ከኢትዮጵያ አንድ የስልክ ጥሪ ደረሰው። ከእግር ኳስ ፌዴሬሽን ነበር። ብሄራዊ ቡድኑ የሴካፋ ውድድር ስላለበት ለውድድሩ መጋበዙ ተገለፀለት። ኢትዮጵያ ሄዶ በነበረ ሰዓት ጉዳዩ በአለመግባባት ቢጠናቀቅም ጥሪውን እንቢ ማለት አልፈለገም። ምክንያቱም አገሩን ወክሎ እንዲጫወት ነው የተጋበዘው። በ1994 ዓ.ም ዋናው ብሄራዊ ቡድን ለሴካፋ ውድድር ወደ ሩዋንዳ ይጓዛል። ባዩም ከፌዴሬሽኑ ጥሪ ደርሶታል። ሆኖም ግን ቡድኑን የተቀላቀለው ጉዞው ሊደረግ አንድ ቀን ሲቀረው ነበር። ከቡድኑ ጋር ልምምድ ባያደርግም ፕሮፌሽናል ልምዱ ከጓደኞቹ ጋር በቶሎ እንዲላመድ አስችሎታል።በአምስት ጨዋታ ላይ አራት ግቦችን በማስቆጠርም ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ ዋንጫውን እንድታነሳ የአንበሳውን ድርሻ ተወጣ። በወቅቱ ብሄራዊ ቡድኑ ዋንጫውን ወደ አገሩ ይዞ ሲመጣ በአዲስ አበባ እና በተለያዩ ክልል ከተሞች ከፍተኛ ፈንጠዝያ ተፈጥሮ ነበር። እርሱም ለረጅም ጊዜ አገሩን ወክሎ ስኬታማ መሆን ምኞቱ ስለነበር በውጤቱ የልቡ ደረሰ። ባዩ ሙሉ የሴካፋን ዋንጫ ከአገሩ ጋር ካነሳ በኋላ በተለያየ ጊዜ ጥሪ እየደረሰው ለብሄራዊ ቡድን ተሰልፏል። ከቤልጅየም ወደ የመን በመጓዝም በታይዝ ከተማ የአል ሳከር ክለብን ተቀላቅሎ ለ3ዓመታት ተጫውቷል። የአል ሳከር ክለብ ከ37 ዓመት በኋላ ዋንጫ ሲያነሳ ዮርዳኖስ አባይ ከአሰልጣኝ ስዩም ከበደ ጋር በመሆን ክለቡን ባለታሪክ አድርገውታል። በየመን ቆይታው ስኬታማ ጊዜን ካሳለፈ በኋላ ወደ ቤልጄም በመመለስ ለአር አር ሲ ጌልት ፈርሞ ረዘም ላሉ ዓመታት ተጫውቷል። ቤሌር ሜዳ ላይ የተጠነሰሰው የባዩ የእግር ኳስ ህይወት የግዴታ አንድ ቦታ መጠናቀቅ ነበረበት። በይፋም እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ2014 ጫማውን ሰቅሏል። ከተጫዋችነት እራሱን ቢያገልም ሙሉ ለሙሉ ግን ከእግር ኳስ ህይወት አልራቀም። በቅዱስ ጊዮርጊስ ክለብ ውስጥ በቡድን መሪነት አገልግሏል። ከቀድሞ ክለቡ ጋር በድጋሚ በሌላኛው የህይወት መስመርም ተገናኝቷል። አዲስ ዘመን ሰኔ 21/2012ቦጋለ አበበ
https://www.press.et/Ama/?p=35264
1,504
2ስፖርት
የኦሊምፒክ ቀን በወርቃማ ኦሊምፒያኖች
ስፖርት
June 25, 2020
11
የዓለም ኦሊምፒክ ቀን እ.ኤ.አ ከ1948 ጀምሮ በየዓመቱ በዓለም አቀፍ ደረጃ በተለያዩ አገራት ይከበራል። ይህም የኦሊምፒክ አባት በሆኑት ፒየር ዲ ኩበርቲን አማካኝነት በአዲስ መንፈስ የተመሠረተውን የኦሊምፒክ ጨዋታ ለማሰብ ይሁን እንጂ በዓሉ ሲከበር ስፖርታዊ እንቅስቃሴ ማከናወን ተፈጥሮዊ መብት በመሆኑ ሁሉም ሰው ዕድሜ ፣ ፆታ ፣ ዘር እና ሃይማኖት ሳይገድበው በሁሉም ቦታ በግል እና በጋራ ስፖርታዊ እንቅስቃሴ በማድረግ በመቀስቀስ እና በማስተማር ጭምር ነው ።የዓለም ኦሊምፒክ ቀን ‹‹ኦሊምፒክ ለሰው ልጆች ጤንነት መልሶ መቋቋም እና ትብብር›› በሚል መሪ ቃል ባለፈው ማክሰኞ በኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ቅጥር ግቢ ውስጥ በተለያዩ ዝግጅቶች ተከብሮ ሲውልም ጀግናው አትሌት ሃይሌ ገብረሥላሴና ከማሞ ወልዴ በኋላ በኦሊምፒክ ማራቶን ለኢትዮጵያ ብቸኛውን የወርቅ ሜዳሊያ ሲድኒ ላይ ያስመዘገበው ገዛኸኝ አበራን የመሳሰሉ ወርቃማ ኦሊምፒያኖች ደምቆ ውሏል። እነዚህ የኦሊምፒክ ጀግኖች በኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ሳቢያ ከተራዘመው የቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ ጋር በተያያዘ ኢትዮጵያን ለመወከል ሲዘጋጁ የነበሩ ወጣት አትሌቶች አስከፊው ጊዜ እስኪያልፍ ራሳቸውን እንዲጠብቁና አቋማቸውም እንዳይወርድ ጠንክረው በመሥራት ከልምምድ መራቅ እንደሌለባቸው ምክራቸውን ለግሰዋል። ያለፉት ሁለት የዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮናዎች ላይ በአምስት ሺ ሜትር የነገሰው አትሌት ሙክታር ኢድሪስ እንዲሁም በዶሃው ቻምፒዮና ሙክታርን ተከትሎ በመግባት የብር ሜዳሊያ ያጠለቀው ወጣቱ አትሌት ሰለሞን ባረጋ፣ ሰንበሬ ተፈሪና በወርልድ ቴኳንዶ ለመጀመሪያ ጊዜ በቶኪዮ ኦሊምፒክ ኢትዮጵያን የሚወክለው ሰለሞን ቱፋ የታላላቆቻቸውን ወርቃማ ኦሊምፒያኖች ምክር በሥፍራው ተገኝተው ተቀብለዋል። በክብረ በዓሉ ላይ የተገኙት የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. ስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ኤሊያስ ሽኩር፣ የስፖርት ቤተሰቡ የኦሊምፒዝም ፍልስፍናን የዕለት ከዕለት መመሪያው በማድረግ ተግባራዊ ሊያደርገው እንደሚገባ ተናግረዋል። ኦሊምፒዝም ሰላምን፣ ንፁህ ወንድማማችነትን ፣ እርስ በእርስ መግባባትን እና ትብብርን የሚያስተምር በመሆኑ ሁሉም የስፖርት ቤተሰብ የዕለት ከዕለት መመሪያው ሊያደርገው ይገባልም ብለዋል ።‹‹ወቅቱ በጣም አስቸጋሪ እና ፈታኝ በመሆኑ ይህን ክፋ ጊዜ ወደ መልካም አጋጣሚ በመቀየር ተባብረን እና ተደጋግፈን የወረርሽኙን ጉዳት መቀነስ ይገባል›› ያሉት ኮሚሽነሩ በመሆኑም የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ እያደረገ ያለው ድጋፍ ሊመሰገን የሚገባውና ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ገልፀዋል። ስፖርቱ ወደነበረበት እንዲመለስ እና በወረርሽኙ ምክንያት ለተጎዱ የስፖርት ቤተሰቦች መደገፍ የሚያስችል የማገገሚያ ስትራቴጂ ተዘጋጅቶ ለመንግሥት መቅረቡንም አቶ ኤሊያስ አስታውቀዋል።የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ፕሬዚዳንት ዶክተር አሸብር ወልደጊዮርጊስ በበኩላቸው፣ የዘንድሮውን የኦሊምፒክ ቀን ለማክበር የተደረገው ሰፊ ዕቅድ በወረርሽኙ ምክንያት ቢስተጓጎልም ከመቸውም ጊዜ በላይ በዚህ አጣብቂኝ ጊዜ ውስጥ በመሆን በዓሉን ሲከበር ለአትሌቶቻችን ፣ ለአሰልጣኞቻችን እና ለሙያተኞች ያለንንን ክብር የምንሰጥበት ብቻ ሳይሆን የኦሊምፒክ እንቅስቃሴ የተወለደበትን የምናስታውስበት ዕለት መሆኑን አስታውቀዋል።ዶክተር አሸብር አያይዘውም፣ በኮሮና ወረርሽኝ ምክንያት የቶኪዮ ኦሊምፒክ የተራዘመ ቢሆንም ይህን ድል ወደ መልካም አጋጣሚ መቀየር ከተቻለ ለሥራዎቻችን እና ለዝግጅቶቻችን በቂ ጊዜ ይፈጥርልናል ብለዋል ። ኮሚቴው በዓሉን ሲያከብርም 60 ለሚሆኑ የቀድሞ ስፖርተኞች ማለትም ለ41 ቬትራን አትሌቶች እና 19 ከተለያዩ ፌዴሬሽኖች ለተውጣጡ የቀድሞ ስፖርተኞች የዱቄት፣ መኮሮኒ፣ ዘይት እና ሳሙና ድጋፍ አድርጓል። በተጨማሪም ጤናማ ስፖርት እና ስፖርተኛ ሊገኝ የሚችለው ከጤና አካባቢ መሆኑን በማመን የችግኝ ተከላ ሥነ ሥርዓት ተካሂዷል።አዲስ ዘመን ሰኔ 18/2012 ቦጋለ አበበ
https://www.press.et/Ama/?p=35067
399
2ስፖርት
ስፖርት – ሰብዓዊነትን ጋሻ ያደረገ ማኅበራዊ ክዋኔ
ስፖርት
June 26, 2020
17
ስፖርት የሰላም፣ ፍቅር፣ የአብ ሮነትና የአንድነት፣ የመተሳሰብ፣ የወንድማማችነት ልዩ መገለጫ ነው። ስፖርት ዘር፣ ሃይማኖት፣ ፆታና ቀለምን አይለይም። በየት ኛውም ሁኔታ ውስጥ የስፖርታዊ እንቅስቃሴ አስኳል ሃሳብ ወዳጅነትና መተሳሰብ መሆኑ ይታወቃል። በታሪክ ገጾች እንደሰፈረውም በሰው ልጅ ታሪክ ባጋጠሙ በጎም ሆኑ መጥፎ ክስተቶች ስፖርት በአጋርነት ተሳትፏል። ስፖርታዊ ክንዋኔዎች ሰላምንና አንድነትን የሚሰብኩ እንደመሆናቸው በማህበራዊ፣ ፖለቲ ካዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች በመግባት ሚናቸውን ሲወጡም ኖረዋል። ስፖርት ሰብዓዊነትን ያነገበ የልግስና ማዕድ መሆኑን የአለም ህዝብ እየፈተነ ባለው የኮሮና ወረርሽኝን ለመዋጋት ሲደረግና እየተደረገ ባለው ርብርብ ላይ በስፖርት ቤተሰቡ በኩል የታየው ተሳትፎ ትልቅ ማሳያ ይሆናል።የኮቪድ -19 ወረርሽኝ የአለም ህዝብን እንደ ቅጠል ከማርገፍ በተጨማሪ በተለያዩ መስኮች ላይ ይህ ቀረሽ የማይባል መቃወስን አስከትሏል።የስፖርት ኢንደስትሪው ደግሞ ዋነኛ ሠለባ ከሆኑ መስኮች በግንባር ቀደምነት ይጠቀሳል። የቫይረሱ ስጋትነት በዓለም አቀፉ የጤና ተቋም ከተረጋገጠበት ጊዜ ጀምሮ፤ ውድድሮች ተቋርጠዋል፤ ተሰርዘዋል። ይህን ተከትሎ የአለምን ኢኮኖሚ በማንቀሳቀስ ረገድ ግንባር ቀደም ተጠቃሽ የሆነው የስፖርት ኢንደስትሪውን በአጭር ጊዜ ለከፍተኛ የፋይናነስ ቀውስ ዳርጎታል።በአለም ስፖርት ላይ የተፈጠረው ከፍተኛ መቃወስ ግን የስፖርቱን ማኅበረሰብ የሰብዐዊነት ውሃ ልክ ከመሆን አላደናቀፈውም ነበር።የስፖርት ቤተሰብ በወረርሽኙ ጉዳት ከመቆዘም ይልቅ ,፤ የሰብዐዊነት ጋሻን በማንሳት አለምን ከጭንቅ ለማውጣት በሚደረገው ርብርብ ሰፊ ተሳትፎ ሲያደርግ ነበር፤እያደረገም ይገኛል። በስፖርቱ መስክ ዓለም አቀፍ ዝናን ካተረፉ ግለሰቦች እስከ ዓለም አቀፍ ተቋማት ድረስ ወረርሽኙን ለመመከት እየተደረገ ባለው ርብርብ ሲያደርጉ የነበረው ተሳትፎ ትልቅ ቦታ አጊንቷል።የስፖርቱ ዘርፍ ባለድርሻ የሚባሉት አካላት በተናጠልና ተቋማዊ በሆነ መልኩ ድጋፍ ለሚሹ ድጋፍ በማድረግ እንዲሁም ገንዘብ በማሰባሰብ ወረርሽኙን የመዋጋት ሂደቱን በፊት አውራሪነት ሲመሩ ታዝበናል።በተለያዩ ሀገራት ዓለም አቀፉን ወረርሽኝ ለመዋጋት በስፖርቱ ማኅበረሰብ ዘንድ የታየው ተሳትፎ በሀገራችንም ተመሳሳይ ሲሆን ታዝበናል። በኢትዮጵያ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ መከሰት ይፋ ከተደረገበት ከወርሃ መጋቢት መጀመሪያ አንስቶ የስፖርቱ ማህበረሰብ ድርሻ ግዙፍ ነው። በስፖርት ዘርፍ የሚገኙ የመንግሥትና የግል ተቋማት፣ የስፖርት ማህበራት፣ ተጫዋቾች፣ አትሌቶች፣ የእግር ኳስ ክለቦችና ተጫዋቾች ወረርሽኙን ለመከላከል የሚደረገውን ርብርብ ተሳትፎ ሲያደርጉ ነበር።በዘመነ ኮሮና የስፖርቱ ማኅበረሰብ ሰብዐዊነትን መሰረት ያደረገው እንቅስቃሴ እንደቀጠለ ይገኛል። በኢ.ፌ.ዴ.ሪ ስፖርት ኮሚሽን አስተባባሪነት ሚያዝያ 17 ቀን 2012 ዓ.ም የተጀመረውን «ማዕድ ማጋራት» መርሃ ግብር ሶስተኛው ዙር ከትናንት በስቲያ በአዲስ አበባ ትንሿ ስታዲየም ተጀምሯል።የስፖርቱ ማኅበረሰብ ህዝባዊነት የሚያረጋግጥ መሆኑ የተነገረለት ሶስተኛው ዙር ማዕድ የማጋራት መርሃ ግብር ሲጀመር ፤ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ኤሊያስ ሽኩር እንደተናገሩት፤ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ መከሰት የመደጋገፍ እና የመረዳዳት የቀደመ ባህላችንን የበለጠ እንዲጎለብት አድርጓል።የኮሮና ቫይረስ ወደ ሀገራችን ከገባ ጀምሮ ወረርሽኙን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የስፖርቱ መንግስታዊ እና ህዝባዊ አደረጃጀቶች፣ ታዋቂ አትሌቶች፣ የደጋፊ ማህበራት፣ በአጠቃላይ የስፖርት ቤተሰቡ ህብረተሰቡን በማንቃት እና ኢኮኖሚያዊ ጫናውን ለመቋቋም የሚያግዝ የገንዘብ ድጋፍ በማድረግ ማህበራዊ ኃላፊነታቸውን በመጣት ላይ ያደረጉትን ተሳትፎ ጠቅሰዋል። የስፖርቱ ማኅበረሰብ ድጋፍ ተጠናክሮ የሚቀጥልና የምገባ መርሃ ግብሩ መጀመር ለዚሁ ማሳያ ይሆናል ብለዋል። የጎዳና ላይ የሚገኙ ወገኖቻችንን በተወሰነ መልኩ ለማገዝ አንድ ወር የሚቆይ የምገባ መርሃ ግብሩ ይሄንኑ ሚና መሰረት ባደረገ መልኩ መጀመሩን የተናገሩት አቶ ኤልያስ፤ በስታዲየም ዙሪያ መርሃ ግብሩ እንዲደረግ የተመረጠበትን ምክንያት መኖሩን አመልክተዋል። «በወቅታዊ የኮሮና ወረርሽኝ ምክንያት ስርጭቱን ለመቆጣጠር ሲባል በተለይ ስታዲየም ዙሪያ የሚገኙ ባር እና ሬስቶራንቶች መዘጋታቸው እና በአካባቢው ያለው እንቅስቃሴ መቆሙ ይታወቃል። ሬስቶራንቶች መዘጋታቸውን ተከትሎ ከሬስቶራንቶች ተመላሽ የሚሆኑ ምግቦችን ይጠቀሙ የነበሩ የጎዳና ተዳዳሪዎችም ሆነ በስታዲየም አካባቢ የተለያዩ ነገሮችን በመሸጥ ይተዳደሩ የነበሩ የህብረተሰብ ክፍሎች ለከፋ ችግር ተጋልጠዋል። በመሆኑም ጊዜው የከፋ ችግር ላጋጠማቸው የህብረተሰብ ክፍሎች እጃችን የምንዘረጋበት፤ የጋራ መከራችንን በመተጋገዝ የምናልፍበት መሆኑን በማመን እና ማህበራዊ ኃላፊነታቸውን ለመወጣት ነው »ሲሉ አብራርተዋል። አቶ ኤልያስ በመጨረሻ የተጀመረው ተግባር የሚቋረጡ ሳይሆን በቀጣይም እነዚህ ወገኖቻችን በዘላቂነት ህይወታቸውን ሊመሩበት በሚችሉ ጉዳዮች ላይ የስፖርት ቤተሰቡ በሙሉ አቅሙ የሚደግፍ መሆኑን አመልክተዋል። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን፣ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን እና የቢጂ አይ ኢትዮጵያ አመራሮች በጋራ በመሆን ባስተላለፉት መልዕክት ደግሞ፤ የምገባ መርሃ ግብሩ በቀጣይ ተጠናክሮ እንዲቀጥል አስፈላጊውን ሁሉ እንደሚያደርጉ አስታውቀዋል።በስፖርት ኮሚሽን አስተባባሪነት የተጀመረው ማዕድ የማጋራት መርሃ ግብሩ 3ኛ መጀመሩን በዘመነ ኮሮና የስፖርቱ ማኅበረሰብ ሰብዐዊ ተግባር ተጠናክሮ መቀጠሉን ያመላክታል ተብሏል።ሰኔ 17 ቀን 2012 ዓ.ም የተጀመረው ሶስተኛው ዙር «ማዕድ ማጋራት» መርሃ ግብሩ 300 የጎዳና ተዳዳሪዎችን ለአንድ ወር ያህል እንደሚመገቡ ታውቋል።በኢ.ፌ.ዴ.ሪ ስፖርት ኮሚሽን ከኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን፣ ከኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን እና ከቢ. ጂ አይ ኢትዮጵያ በጋራ በመሆን የመጀመሪያው ዙር ሚያዝያ 17 ቀን 2012 ዓ.ም ጀምሮ ለአንድ ወራት የዘለቀ ነበር።የስፖርት ተቋማቱ ጠቅላይ ሚኒስቴር አብይ አህመድ ያቀረቡትን «የማዕድ ማጋራት ብሄራዊ ጥሪን»ተከትሎ መርሃ ግብሩን የጀመሩት ሲሆን፤ 300 የጎዳና ተዳዳሪዎችን ለአንድ ወር ያህል በመመገብ ሀሳቡን ተግብረውታል።ሁለተኛ ዙር ግንቦት 17 ቀን 2012 ዓ.ም ጀምሮ ለአንድ ወር ያህል ተግባራዊ ተደርጎ በመጠናቀቁ ፤ሶስተኛው ዙር መርሃ ግብር ከሰኔ 17 ቀን 2012 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ሐምሌ 16 ቀን 300 የጎዳና ተዳዳሪዎችን በምገባ መርሃ ግብሩ ተጠቃሚ እንደሚደረጉ ታወቋል።በ3ኛው ዙር የምገባ ፕሮግራም የኢትዮጵያ መድን ድርጅት 600 ሺ ብር ድጋፍ በማድረግ የወገን አጋርነቱን ማሳየቱ ተነግሯል። የምገባ መርሃ ግብሩን ለሶስተኛው ዙር ማስቀጠል መቻሉ የስፖርቱ ማህበረሰብ በዘመነ ኮሮና ማህበራዊ ኃላፊነትን በመወጣት እንደ ከዚህ ቀደሙ ሁሉ የተጠናከረ ተሳትፎ እያደረገ መሆኑን አመላካች ሆኗል። የመርሃ ግብሩ ተግባራዊነት ጠቅላይ ሚኒስቴር አብይ አህመድ ያቀረቡትን «የማዕድ ማጋራት ብሄራዊ ጥሪን» ወደ መሬት ከማውረድ በተጨማሪ፤ ስፖርት -ሰብዐዊነትን ጋሻ ያደረገ ማኅበራዊ ክዋኔ መሆኑን በተግባር እንዲረጋገጥ ያረጋገጠ መሆኑን ብዙዎች መስክረውለታል።አዲስ ዘመን ሰኔ 19/2012ዳንኤል ዘነበ
https://www.press.et/Ama/?p=35130
728
2ስፖርት
የአትሌቲክሱ ዓለም ከወራት በኋላ የሚጠብቀው የዓለም ክብረወሰን
ስፖርት
June 27, 2020
13
የዓለም ታላላቅ ስፖርት መድረኮች በኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ 19) ወረርሽኝ ምክንያት ለበርካታ ወራት ከቆሙበት ለመቀጠል ጥረት እያደረጉ እንደሚገኙ ባለፉት ሁለት ሳምንታት ለመመልከት ተችሏል። የእግር ኳሱ ዓለም ታላላቅ ሊጎች በዝግ ስቴድየምም ቢሆን ጨዋታዎችን እያስቀጠሉ ካንቀላፉበት እየነቁ ይገኛሉ። በዚሁ ወረርሽኝ ሳቢያ ክፉኛ የተጎዳው የዓለም አትሌቲክስ እንቅስቃሴም ከጥቂት ወራት በኋላ ታላላቅ ዓለም አቀፍ ውድድሮችን ለመመለስ ከወዲሁ እንቅስቃሴ መጀመሩ ለዓለማችን አትሌቶች መልካም ዜና ሆኗል። በተለይም የዓለማችን ኮከብ አትሌቶች በጉጉት የሚጠብቁት ዓመታዊው የዳይመንድ ሊግ ውድድር እንደሚመለስ መገለፁን ተከትሎ ለወራት ከውድድር ርቀው ለተቀመጡት አትሌቶች የምሥራች መሆኑ አይቀርም። በኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ የተነሳ የዓለም አትሌቲክስ ዓመታዊ መርሃግብሮች በተያዘላቸው ጊዜ ሳይካሄዱ በመቅረታቸው ተዘበራርቀዋል። የዓለም አትሌቲክስ ይህንን ለመካስም በጊዜያዊነትም ቢሆን እንደ ዳይመንድ ሊግ ያሉ ውድድሮች መርሃግብርን ለመከለስ ተገዷል። በብራሰልስ የሚካሄደውም ውድድር ከተከለሱት መርሃግብሮች መካከል የሚጠቀስ ነው። ዳይመንድ ሊጉ ወደ ውድድር ሲመለስ በመጪው የፈረንጆች መስከረም ወር መጀመሪያ እንደሚካሄድ የሚጠበቀው የብራሰልስ ዳይመንድ ሊግ ከወዲሁ ትኩረት አግኝቷል። እንግሊዛዊው የኦሊምፒክና የዓለም ቻምፒዮናዎች ጥምር የወርቅ ሜዳሊያ ባለቤቱ አትሌት ሞሐመድ ፋራህ ከ2017 ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ መም ውድድሮች ተመልሶ በብራሰልስ ዳይመንድ ሊግ ተፎካካሪ እንደሚሆን መናገሩን ተከትሎ ውድድሩ ትኩረት ማግኘት ችሏል። የሰላሳ ሰባት ዓመቱ ፋራህ ወደ ውድድር ከመመለሱ በተጨማሪ በ21 ነጥብ 285 ኪሎ ሜትር ፉክክሩን ከአንድ ሰዓት በታች ለማጠናቀቅና አዲስ የዓለም ክብረወሰን ለማሻሻል መዘጋጀቱን ተከትሎ የብራሰልስ ዳይመንድ ሊግ ከወዲሁ በጉጉት እንዲጠበቅ አድርጓል። የርቀቱ ክብረወሰን በጀግናው አትሌት ሃይሌ ገብረሥላሴ የተያዘ ሲሆን ከአስራ ሦስት ዓመታት በፊት እ.ኤ.አ 2007 ኦስትራቫ ላይ ማስመዝገቡ ይታወሳል። በብራሰልሱ ውድድር የአውሮፓ የአስር ሺህ ሜትር የብር ሜዳሊያ አሸናፊው አትሌት በሽር አብዲ ከፋራህ ጋር እንደሚፎካከር የተገለፀ ሲሆን ኢትዮጵያውያንና ኬንያውያን የርቀቱ ፈርጦችም በቅርቡ ውድድሩን እንደሚቀላቀሉ ይጠበቃል። ‹‹ከልምምድ አጋሬ በሽር አብዲ ጋር ውድድሩን ከአንድ ሰዓት በታች በማጠናቀቅ የዓለም ክብረወሰን ለማስመዝገብ እየተዘጋጀን ነው፣ ይህ ለእኔ ትልቅ አጋጣሚ ነው፣ በብራሰልስ ከዚህ ቀደም ባደረኳቸው ውድድሮች ጥሩ ትዝታዎች አሉኝ፣ ብራሰልስ ላይ ፈታኝ ሰዓት መሮጥ ይቻላል፣ ሁሉም ነገር ቀላል ነው›› በማለት ፋራህ ለመገናኛ ብዙሃን አስተያየቱን ሰጥቷል። በተመሳሳይ በሴቶች መካከል በሚካሄደው ውድድር ግን ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ተፎካካሪ ከመሆን ባለፈ አዲስ የዓለም ክብረወሰን ለማስመዝገብ መዘጋጀታቸውን የውድድሩ አዘጋጆች ገልፀዋል። በዚህም አትሌት አባብል የሻነህ እና ብርሃኔ ዲባባ ተጠባቂ ሆነዋል። 18 ነጥብ 517 ኪሎ ሜትር የሚሸፍነው ውድድር የዓለም ክብረወሰን የተመዘገበበት ጊዜ ከአስራ ሁለት ዓመታት በፊት እ.ኤ.አ 2008 ላይ ሲሆን ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ድሬ ቱኔ የክብረወሰኑ ባለቤት መሆኗ አይዘነጋም። በዚህ የውድድር ዓመት የዓለም ግማሽ ማራቶን ክብረወሰንን በ1፡04፡31 ሰዓት መስበር የቻለችው አባብል የሻነህ ለአስራ ሁለት ዓመታት ያልተደፈረውን የድሬ ቱኔን ክብረወሰን እንደምታሻሽል ግምት የተሰጣት ሲሆን በማራቶን 2፡18፡35 የሆነ የራሷ ምርጥ ሰዓት ያላት ብርሃኔ ዲባባም ብራሰልስ ላይ ለክብረወሰን ተጠባቂ ሆናለች።አዲስ ዘመን ሰኔ 20/2012 ቦጋለ አበበ
https://www.press.et/Ama/?p=35203
379
2ስፖርት
የካፍ አካዳሚ ወደ አገልግሎት የመመለስ ተስፋ
ስፖርት
June 29, 2020
16
 የኢትዮጵያ እግር ኳስ እድገት ለመቀጨጩ በርካታ ምክንያቶች ሊዘረዘሩ ይችላሉ። ከእነዚህ መካከል አንዱና ትልቁ ምክንያት ሆኖ በተደጋጋሚ የሚነሳው ታዳጊዎችን ለማሰልጠን የሚያበቃ አካዳሚ አለመኖሩ ነው። በእርግጥ ከጥቂት ዓመታት ወዲህ በአገር አቀፍ ደረጃ በተገነቡ የስፖርት ማሰልጠኛ ማዕከላትና አካዳሚዎች የተለያዩ ስልጠናዎች ደረጃቸውን ጠብቀው በተገነቡ የማሰልጠኛ ማዕከላት መሰጠት ጀምረዋል። ይሁን እንጂ በተገነቡት ዘመናዊ የማሰልጠኛ ማዕከላት እግር ኳሱን ከቁልቁለት ጉዞ ታድጎ አንድ ርምጃ ወደ ፊት የሚያራምድ ፍሬ ማፍራት እንዳልተቻለ ለማንም የተሸሸገ እንዳልሆነ መገንዘብ ይቻላል። የተገነቡትን ዘመናዊ የማሰልጠኛ ማዕከላት ፍሬ እንዲያፈሩ በአግባቡ እንዳልተሰራባቸው አንዱ ማሳያ በአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን(ካፍ) የተገነባውና ከአስር ዓመት በላይ አገልግሎት ሳይሰጥ የቆየው የካፍ እግር ኳስ አካዳሚ ነው። በአዲስ አበባ ከተማ ልዩ ስሙ አያት አካባቢ የሚገኘው አካዳሚው ግንባታው የተጀመረው በ1997 ዓ.ም ሲሆን፤ በሶስት ዓመት ለማጠናቀቅ ነበር የታቀደው። ሆኖም ግንባታው በመዘግየቱና ከተጠናቀቀም በኋላ አገልግሎት መስጠት አለመጀመሩ በርካታ መዋዕለ ንዋይ የፈሰሰበትን መሰረተ ልማት አገልግሎት ሳይሰጥ እንዲባክንና ጉዳት እንዲደርስበት ሆኗል። የስፖርት ቤተሰቡ በዚህ የተነሳ ተደጋጋሚ ቅሬታ ሲያቀርብ ቆይቷል። ይህንንም ተከትሎ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በተካሄደ እንቅስቃሴ አካዳሚው ስራ አስኪያጅ ተመድቦለትና ለብልሽት ለተዳረጉ ስራዎች እድሳት ተደርጎባቸው ተስፋ ማሳየት ጀምረዋል። ባሳለፍነው ሳምንት መጨረሻም የስፖርት አመራሮች እንዲሁም የስፖርት ማህበራት ኃላፊዎች በቦታው ተገኝተው ጉብኝትና የችግኝ መትከል መርሃ ግብር አካሂደዋል። በወቅቱም አካዳሚው ስላለበትና ቀጣይ እጣ ፈንታው ምን እንደሚሆን ማብራሪያ ተሰጥቷል። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት አቶ ኢሳያስ ጂራ፤ የልህቀት አካዳሚው 15 ዓመት እንደሆነው በማስታወስ፣ ካፍ በአህጉሪቷ የእግር ኳስ ልህቀት አካዳሚውን ለመገንባት ሲነሳ የመረጣቸው አገራት ካሜሩን፣ ሴኔጋል እና ኢትዮጵያ መሆናቸውን ይናገራሉ። በወቅቱ የካፍ ፕሬዚዳንት የነበሩት ኢሳ ሃያቱ ካሜሮናዊ በመሆናቸው በአገራቸው የሚገነባውን ተመሳሳይ አካዳሚ ግንባታ ወደራሳቸው በማድላት በዲዛይኑ መሰረት በጥሩ ሁኔታ እንዲጠናቀቅ ማድረጋቸውን አቶ ኢሳያስ ያስረዳሉ። በዚህ ወቅትም ሁሉም መሰረተ ልማት የተሟላለትና ስፖርተኞችን እያፈራ እንደሚገኝ ይናገራሉ። በሴኔጋል የተገነባው ተመሳሳይ አካዳሚም ቢሆን ከዋና ከተማዋ ዳካር 80 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የአገሪቱ መንግስት ገንዘብ በመመደብና በማደስ ብሄራዊ ቡድናቸውን ያሳርፉበታል። የኢትዮጵያው አካዳሚ እስካሁንም ድረስ ባለበት የቆየ ሲሆን ከወራት በፊት ካፍ የባለቤትነት መብት እንዲሰጥ ለፌዴሬሽኑ ደብዳቤ ጽፎ ነበር። በዚህም መሰረት የሰነድ ርክክቡ ተጠናቆ የውልና ማስረጃ ስራዎች በመከናወን ላይ እያለ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ በመከሰቱ ሊቋረጥ ችሏል። ወደፊት ከኢፌዴሪ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር በመተባበርና ሂደቱን በማጠናቀቅ ህጋዊ ይሆናል ተብሎም ይጠበቃል። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ይህን እያደረገ በነበረበት ወቅትም ጎን ለጎን ዘርፈ ብዙ ስራዎችን ሲያከናውን እንደነበረ ፕሬዚዳንቱ አቶ ኢሳያስ ያስታውሳሉ። የጀርመኑ ክለብ ባየርሙኒክ የአካዳሚውን ሜዳ እንዲያሰራ፣ ጂአይዜድ ደግሞ ሁለት የተፈጥሮና አንድ የሰው ስራሽ ሜዳዎችን ለመስራት ቃል መግባታቸውን ጠቁመዋል። በተለያዩ ደረጃዎች የሚገኙ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ብሔራዊ ቡድኖችን ለተለያዩ ጨዋታዎች ለማዘጋጀት በሆቴሎች እንዲያርፉ ከፍተኛ ገንዘብ ወጪ እንደሚደረግ ይታወቃል። ከዚህ በኋላ ግን በዚህ አካዳሚ በማሳረፍ ዝግጅታቸውን እንዲያደርጉ ማድረግ እንደሚቻል አቶ ኢሳያስ ተናግረዋል። ከእግር ኳስ ባሻገር ያሉ ስፖርቶችም ብሄራዊ ቡድናቸውን ማሳረፍ የሚችሉበት አጋጣሚ እንዳለ ተገልጿል። ከዚህ ባሻገር በኢትዮጵያ አርፈው ወደ ሌሎች አገራት የሚጓዙ ብሄራዊ ቡድኖች በአካዳሚው እንዲያርፉ በማድረግ ተጨማሪ ገቢ ለማግኘት እንደሚቻልም ጠቁመዋል። ይህንን ለማድረግ ግን የሚያስፈልጉ ቅድመ ሁኔታዎችን ማሟላት ያስፈልጋል። ይኸውም የልምምድ ሜዳ እና የጉድጓድ ውሃ መሆኑን ለመንግስት ጥሪ ተደርጓል። ይህ ሲሆንም የፌዴሬሽኑን ጽህፈት ቤት አካዳሚው ወዳለበት ስፍራ ለማዘዋወር እንደሚያመች አቶ ኢሳያስ አብራርተዋል። የቀድሞውም ሆነ የአሁኑ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ጽህፈት ቤት የሚገኝበት አካባቢ መሐል ከተማ እንደመሆኑ የእግር ኳስ እንቅስቃሴ ለማድረግ አይታሰብም። አፍሪካን ጨምሮ በሌሎች አገራት ስፖርቱ ሙሉ በሙሉ የሚንቀሳቀሰው በአንድ አካባቢ በተገነባ ዘመናዊ የስፖርት ማዕከል ነው። ይህ አካዳሚ እያለ ግን አገልግሎት መስጠት ሳይጀምር የመፍረስ አደጋ ተጋርጦበት ነበር። የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን ባደረገው ጥረትና በመደበው 2 ሚሊዮን ብር ግን በድጋሚ ሊታደስችሏል። በቀጣይም መንግስታዊ አካላት ለትውልድ ሊተላለፍ የሚችለውን አካዳሚ ሊጠብቁ እንደሚገባ አቶ ኢሳያስ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል። የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ፕሬዚዳንት ዶክተር አሸብር ወልደጊዮርጊስ በበኩላቸው፤ የአካዳሚው ግንባታ የተጀመረው እርሳቸው የፌዴሬሽኑ ስራ አስፈጻሚ እያሉ መሆኑን አስታውሰው፣ ለዓመታት በዚህ ሁኔታ ውስጥ አልፎ አሁን እድሳት ሲደረግለትም በስፖርቱ ውስጥ መሆናቸውን ተናግረዋል። በመሆኑም ይህ ለእግር ኳስ እድገት እንዲሁም ስፖርተኞችን ለሚያፈራ አካዳሚ ኮሚቴው የሚጠበቅበትን የሚወጣ መሆኑን ጠቁመዋል። የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነሩ ዱቤ ጂሎ፤ ከወራት በፊት አካዳሚውን በጎበኙበት ወቅት አሳዛኝ ሁኔታ መመልከታቸውን ያስታውሳሉ። በወቅቱም ከፌዴሬሽኑ ፕሬዚዳንት ጋር በመሆን ወደ ስራ መግባት እንደሚኖርበት ተነጋግረዋል። በተከናወነው ስራም አሁን የተሻለ ሁኔታ ላይ ሊገኝ ችሏል። ስለ ስፖርት ሲታሰብ ዋናው ጉዳይ የማዘውተሪያ ስፍራዎች በመሆናቸው ኃላፊነት ያለበት ኮሚሽኑ አካዳሚው ስልጠና እንዲጀምር በትኩረት በመስራት ላይ እንደሚገኝም ጠቁመዋል። አካዳሚው እንዲገነባ ያደረጉ አካላት ምስጋና የሚገባቸው ቢሆንም ለ15 ዓመታት ያለ ስራ መቀመጡ ግን ጥፋት ነው ሲሉም አቶ ዱቤ ተናግረዋል። በመሆኑም ይህንን ለማረም በቁርጠኝነት መነሳታቸውን አረጋግጠዋል። አካዳሚውን ለማፍረስ ሙከራ ያደረጉትንም የሚቃወሙና ማስተካከያ ማድረግ የሚያስፈልግ መሆኑንም ጠቁመዋል። በእርሳቸው ሃሳብ ላይ ያከሉት የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽነር አቶ ኤሊያስ ሽኩር በበኩላቸው፣ የስፖርት ማዘውተሪያ ማዕከላትን መንከባከብ አስፈላጊ መሆኑን ጠቁመዋል። ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች ለስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች መሬት ከመስጠት ባሻገር በቀጣይነት አብሮ መስራት አስፈላጊ ነው። የተገነቡና እየተገነቡ ያሉ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎችና የስልጠና ማዕከላት ከተልእኳቸው አንጻር በሙሉ ኃይላቸው እየሰሩ አይደለም። በሌላ መልኩ በየአካባቢው የተገነቡት ማዕከላት ለማህበረሰቡ ተገቢውን አገልግሎት መስጠት አለባቸው። በመሆኑም በየአካባቢው ያሉ የስልጠና ማዕከላትና አካዳሚዎች ተገቢውን ግልጋሎት እንዲሰጡ ማድረግ ተገቢ ነው። በተለያዩ አካባቢዎች ውድ የሆነው መሬት ለስፖርት እንዲውል ቢሰጥም እንደ ካፍ አካዳሚ ሁሉ ለዓመታት ታጥረው መቀመጥ የለበትም። መንግስት፣ ህብረተሰብ እንዲሁም የስፖርት ቤተሰቡም በስፖርት ስም የተቀመጡ መሬቶችንና ግንባታዎችን ወደ ስራ እንዲገቡ ማድረግ እንዳለባቸው አሳስበዋል። የኢፌዴሪ ባህልና ቱሪዝም ሚኒስትር ዶክተር ሂሩት ካሳው በበኩላቸው፤ አካዳሚው የእግር ኳስ ፌዴሬሽኑ ብቻም ሳይሆን የኢትዮጵያ ህዝብ ሀብት መሆኑን ጠቁመዋል። የአካባቢውን ማህበረሰብም ተጠቃሚ በማድረግ ገቢ ማስገኘት የሚቻልም ይሆናል። እስካሁን አካዳሚውን አለመጠቀም ‹‹ምን ዓይነት እንደሆን ያሳያል›› ያሉት ሚኒስትሯ፤ መንግስት ቦታውን ሰጥቶ መስራት ያለበት አካል በሚገባው ቦታ አለመገኘቱ አሳዛኝ መሆኑን ይገልጻሉ። ቦታውን ከተረሳበትና ከተጎዳበት በማስተካከል አሁን ያለበት ላደረሱ አካላትም ምስጋና ይገባል።አዲስ ዘመን ሰኔ 22/2012 ብርሃን ፈይሳ
https://www.press.et/Ama/?p=35323
813
2ስፖርት
«የስብሃት ነጋ በቁጥጥር ስር መዋል ትልቅ የፖለቲካ ድል ነው» – አቶ መስፍን ደሳለኝ የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ምክትል ሊቀመንበር
ሀገር አቀፍ ዜና
January 10, 2021
46
እፀገነት አክሊሉአዲስ አበባ፦ ለዚህ ሁሉ መሰሪነትና ለጥፋት ስትራቴጂው ህወሓት ጁንታው አገር እንዲያተራምስ በማድረግ የትግራይ ክልልም አሁን ለገባበት ምስቅልቅል የአቶ ስብሃት ነጋ መሰሪነት ትልቁን ቦታ የሚይዝ በመሆኑ የእርሳቸው በቁጥጥር ስር መዋል ትልቅ ፖለቲካዊ ድል መሆኑን የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ አስታወቀ። የፓርቲው ምክትል ሊቀመንበር አቶ መስፍን ደሳለኝ ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ እንደገለጹት ፣አቶ ስብሃት ነጋ በውሸትና በወንጀል እንዲሁም ለራሳቸው ከሚገባው በላይ ዋጋ ሰጥተው ሕዝቡ ውስጥ የገቡ ፣ከዛም አልፎ አንዳንዶች እስከማምለክ ድረስ የደረሱላቸው ግለሰብ ናቸው፤ መላው ሕዝብ እንደሚያውቀውም ከነቤተሰባቸው እንደውም እስከ ዘር ማንዘራቸው ስልጣንን ተቆጣጥረው ትግራይን እንዲሁም ኢትዮጵያን በእጅ አዙር ሲመሩ ኖረዋል ።ለእርሳቸውና ለዘሮቻቸው ስልጣን ማራዘሚያም የትግራይ ሕዝብ ትልቅ ማጥ ውስጥ እንዲገባ መገደዱን ያመለከቱት አቶ መስፍን ፣ የግለሰቡ መያዝ የፖለቲካዊ ድል ነው እንደውም እግዚአብሔር አገሪቱን ከከፋ ጥፋት ለመታደግ ያሰበም ይመስለኛል ብለዋል።እንደ አቶ መስፍን ገለጻ ፣ የህወሓት የትግል ታሪክ ሲነሳ መልካም ጎን የነበረው ቢሆንም እንደ አቶ ስብሃት ነጋ ያሉ ጽንፍ የያዙ ሰዎች ትግሉን ወዳልሆነ አቅጣጫ በመምራታቸውና በዓለም ላይ መጥፎ የፖለቲካ ታሪክ ያላቸውን የእነ “ስታሊን” ን አካሄድ በመከተላቸው የመጠፋፋት። የመጠላለፍ ፖለቲካ ውስጥ ገብተው የትግራይ ህዝብ ትግል ፍሬ እንዳያፈራ እንዲሁም አሁን ለገባበት ትልቅ ችግር መንስኤ መሆናቸውን አብራርተዋል።ለዚህ ሁሉ መሰሪነትና ለጥፋት ስትራቴጂው የህወሓት ጁንታ አሁን አገርን ለማተራመስ ለገባበት መንገድ ትልቅ አስተዋጽኦ እንደነበራቸው የገለጹት አቶ መስፍን፣ አሁን በቁጥጥር ስር መዋላቸው ደግሞ በትግራይም በመላው አገሪቱም የህወሓት ጁንታ ተመልሳ ትመጣለች በማለት በተስፋ የሚጠብቁ ሞኞች ተስፋቸውን ቆርጠው ወደራሳቸው እንዲመለሱና ሥራቸውን እንዲቀጥሉ እንደሚያደርግም ጠቁመዋል።አቶ ስብሃት ነጋ በጣም ተንኮለኛ። በቀለኛ። በሰፈር የሚያስቡ በአምባገነናዊ ዴሞክራሲ የተሸፈኑ ከመሆናቸውም በላይ የህወሓትንም ታሪክ አበላሽተዋል ያሉት አቶ መስፍን፣ ለዚህ ሁሉ ችግርም ዋናው ተጠያቂና ምክንያት እርሳቸው ናቸው።በመካከላቸው አንዳንድ በአስተሳሰባቸው ሻል ያሉ ችግሩ እዚህ ከመድረሱና ወደጦርነት ከመገባቱ በፊት በሰላማዊ መንገድ እንደራደር የሚል ሃሳብን ሲያቀርቡ ተጽዕኖ በማድረጋቸው ምክንያት ይህ ጦርነት ተጀምሮ የሰው ህይወት ጠፋ ፣ ንብረት ወደመ ብለዋል።አቶ ስብሃት የራሳቸው ቡድን። ኃይል ።ሰላይ ያላቸው በሁሉም ቦታዎች በሃይማኖቱም በባህሉም በታሪኩም ላይ ገብተው የፈለጉትን ነገር የማድረግ አቅም የፈጠሩ ናቸው ያሉት አቶ መስፍን፣ ከዚህ የተነሳ ሰውየውን እንደ አንድ ሰው ብቻ ማሰብ በጣም ከባድ ነው።በቁጥጥር ስር መዋላቸውም ትልቅ ነገር የሚሆነው ከዚህ አንጻር እንደሆነም አብራርተዋል። “የትግራይ ህዝብ ለ 17 ዓመት በዱር በገደሉ ያደረገውን ተጋድሎ ። የገበራቸውን ልጆቹን ደም በከንቱ ያስቀሩ፣ ሁሉንም ድካሙን በዜሮ እንዲባዛ ያደረገው የእኚህ ሰው ሴራና ተንኮል ነው፤ አሁን የችግሩ ምንጭ በመነቀሉ ከዚህ በኋላ ክልሉም ሰላም ሰፍኖበት ወደ ልማትና መልሶ ግንባታው ይገባል “ ብለዋል ።አሁን ከባለፈው ታሪካችን ተምረን ብዙ ነገሮችን ማሻሻል መተው የሚገባን መተው ያለብን ይመስለኛል ያሉት አቶ መስፍን፣ ምክንያቱም የሴራ ፖለቲካ የመጠላለፍና ጥሎ የማለፍ አካሄድ ለእነ አቶ ስብሃት ነጋም እንዳልጠቀመ እየታየ ነው፤ በትግራይም ሆነ በመላው የአገሪቱ ክፍል እኛና እናንተ እየተባለ የሚሄድ ፖለቲካ ከዚህ በኋላ ማብቂያው እንደሚሆን አመልክተዋል ።ጊዜያዊ አስተዳደሩም በመተማመን ላይ የተመሰረተ እንደጀመረው ሁሉን አቀፍ የሆነ፣ ማንንም ያላገለለ እና የጋራ ጥቅምን የሚያስጠብቅ ሊሆን እንደሚገባ አመልክተው ፣ ይህ መሆን ከቻለ ፍትህ ማስፈን። ዴሞክራሲን ማምጣት እንደሚቻል ገልጸዋል ። እኛም እንደ ፓርቲ አንድነቷንና እኩልነቷን አስጠብቃ የምትቀጥል አገር እንድትኖር ጠንክረን እንሰራለን ብለዋል።በቀደመው ጊዜ ከፍተኛ የሆነ ብልሽት ከገጠማቸው ተቋማት መካከል መከላከያ ሰራዊት አንዱ ነበር ያሉት አቶ መስፍን ፣አሁን መከላከያ የታነጸበት አካሄድ በጣም አስገራሚ የአጭር ጊዜ ስራ ውጤት የማይመስል የሕዝብ አለኝታ እንዲሆን ማድረግ ያስቻለ እንደሆነ አስታውቀዋል ።በዚህ የሕግ ማስከበር ዘመቻ ላይም ያሳየው አገር ወዳድነት ፣ቆራጥነትና ለመስዋዕትነት መዘጋጀት አስገራሚ ከመሆኑም በላይ እነዚህን ለሁለት ዓመት ሲዘጋጁ የነበሩ የጥፋት ቡድኖችን ከተቀበሩበት ጉድጓድ በዚህ መልኩ እያደነ ማምጣቱ የሚደነቅ ነው ብለዋል ።በቀጣይም የትግራይን ክልል በማረጋጋት ሰላሙን በማረጋገጥ መልሶ ማቋቋም ላይ ከፍተኛ ድርሻውን እንደሚወጣ ጥርጥር እንደሌላቸው ገልጸዋል።የቀሩት የጁንታው ቡድን አባላትም ከዚህ በኋላ ወዴትም መሄድ ምንም ማድረግ እንደማይችሉ ተገንዝበው በሰላም እጃቸውን ሰጥተው ለፍርድ ቢቀርቡ ለእነሱም መልካም ነው፤ አልያ ግን የተዳፈሩት የመከላከያ ሰራዊት በፍጹም ጀግንነት ከተደበቁበት ጉድጓድ ፈልፍሎ እንደሚያወጣቸው መገንዘብ እንዳለባቸውም አመልክተዋል።አዲስ ዘመን ጥር 2 ቀን 2013 ዓ.ም
https://www.press.et/Ama/?p=39214
553
0ሀገር አቀፍ ዜና
‹‹ለሱዳን ትንኮሳ ቸኩለን ምላሽ መስጠት አይገባንም›› -ዶ/ር ኢንጅነር ጥላሁን ኤርዱኖ የታሪክና የጂኦግራፊ መምህር የነበሩና በአሁኑ ጊዜ በአዳማ ዩኒቨርሲቲ የካርታ ምህንድስና መምህር
ሀገር አቀፍ ዜና
January 9, 2021
41
ማህሌት አብዱል አዲስ አበባ፡- ሱዳን በኢትዮጵያ ግዛት ላይ ላደረገችው የመሬት ወረራ ትንኮሳ ፈጥኖ የኃይል ምላሽ መሥጠት እንደማይገባ የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ መምህር ዶክተር ኢንጅነር ጥላሁን ኤርዱኖ አስታወቁ፡፡ዶ/ር ኢንጅነር ጥላሁን ኤርዱኖ ለአዲስ ዘመን እንዳስታወቁት፤ የሱዳን ጦር በኢትዮጵያ ግዛት ላይ ለፈፀመው የመሬት ወረራ ቸኩሎ የኃይል ምላሽ መሥጠት ከጥቅሙ ይልቅ ጉዳቱ ያመዝናል። በተለይም ውስጣዊውን ችግር በተሟላ ሁኔታ መፍታት ባልተቻለበት በዚህ ወቅት ወደ ኃይል ምላሹ መግባት አገሪቱን ያላሰበችው አደጋ ውስጥ ሊጥላት ይችላል፡፡እንደእርሳቸው ገለፃ፤ ሱዳንም ሆነች ግብፅ በኢትዮጵያ ላይ እያደረጉት ያሉት ትንኮሳ ዋነኛ አላማ የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታን ለማስተጓጎል ነው፡፡ በተለይም ሱዳን የቅኝ ግዛት ውልን በማጣቀስ ያደረገችው ትንኮሳ ግድቡ የሚገነባበትን አካባቢ ሰላም በማወክ ውሃውን ከግብፅ ጋር ብቻ የመጠቀም ፍላጎታቸውን ለማስቀጠል ከመሻት ነው፡፡ ከትንኮሳ በስተጀርባም የግብፅ ወታደራዊ መንግሥት እጅ ያለበትና ከፍተኛ ድጋፍ የሚደረግለት ነው፡፡ ‹‹የሱዳን ዋነኛ ፍላጎት ቸኩለን እንድንገጥማት ነው›› ያሉት ዶክተር ጥላሁን ይህንን ማድረጉ ደግሞ አገሪቱ ካለችበት ፖለቲካዊ ችግር ጋር ተዳምሮ ከፍተኛ ዋጋ ሊያስከፍል እንደሚችል ሥጋታቸውን ተናግረዋል፡፡ በመሆኑም የኢትዮጵያ ሕዝብና መንግሥት የትንኮሳውን ዋነኛ አላማ በመረዳት ትክክለኛውን ጊዜ መጠበቅ እንደሚገባው አመልክተዋል፡፡መላው ኢትዮጵያውያንም እንደከዚህ ቀደሙ ሁሉ ለአገራቸው ሰላም በህብረት መቆም እንደሚገባቸው የተናገሩት ዶክተር ጥላሁን ለዚህ ደግሞ በብሔርና በጎሳ ለመለያየት የሚደረገውን የጠላት ኃይሎች ጥረት እንዳይሰምር በጋራ ሊሰሩ እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡ ዶክተር ጥላሁን እንደሚሉት ጠላቶቻችን ሌላ በጣም ጽንፈኛ የሆነ ጠላት ይፈጥሩልናል እንጂ በፍፁም አይተኙልንም፡፡ ይሄ በግርግር መሬት እናስመልሳለን የሚል ቢሆንም ዋነኛ አላማው ግን ኢትዮጵያን ሰላም በማሳጣት የህዳሴ ግድባችንን ግንባታ ማስተጓጎል ነው፡፡ ሱዳን ሁልጊዜ መሆን የምትፈልገው ከአሸነፈው ጋር ነው፡፡ ኢትዮጵያ የፖለቲካ የበላይነቱን ስትይዝ ኢትዮጵያ ያለችውን ትቀበላለች፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ ችግር ሲፈጠር ከግብጽ ጋር ነው የምትጎዳን ብለዋል ዶክተር ጥላሁን፡፡ እንደ ዶክተር ኢንጂነር ጥላሁን ገለጻ፤ የግብፅና የሱዳን መንግሥታት ወታደራዊ ናቸው። የሁለቱም አመራሮች ወደ ስልጣን የመጡት በመፈንቅለ መንግሥት ነው፡፡ ወታደራዊ መንግስቱ ኢኮኖሚውን ይዞ ነው ያለው፡፡ ከጎረቤት ጋር በሰላም መኖር አይችሉም፡፡ ሲቪል መንግሥት እንዲኖር አይፈለግም፡፡ ስለዚህ እነዚህ አገሮች ኢትዮጵያ አንድነቷን ካፀናች በምንም ተዓምር አያሸንፏትም፡፡ ግን እጃቸው ረጅም በመሆኑ ለሰላማችን መደፍረስ የሚመጡበት መንገድ አይታወቅም፡፡የውጭ ጠላቶቻችንን ማሸነፍ የምንችልበትና ያለን ብቸኛ መፍትሔ የኢትዮጵያን ሕዝብ አብሮነት መመለስ ነው ያሉት ዶክተር ጥላሁን፤ በቋንቋም ሆነ በብሔር መከፋፈላችንን ማስቀረት ይገባናል ብለዋል፡፡ ምክንያቱም ቋንቋ ከመግባቢያነት ያለፈ ጥቅም ኖሮት አያውቅም ብለዋል፡፡ሁለቱ አገራት በዴሞክራሲያዊ ምርጫ የተመሰረተ ፖለቲካ አካሂደው አያውቁም፡፡ ስለዚህ የውስጥ የፖለቲካ ችግር ሲፈጠር የሕዝባቸውን ቀልብ ለመስረቅ ሲሉ ችግራቸውን ለኢትዮጵያ ይሰጣሉ። ሁሉንም ነገር ከአባይ ጋር ያያዙታል። በሱዳን በኩልም በዳቦም ሆነ በሌላ መልኩ የሚነሳውን ሕዝባዊ ተቃውሞ ለማስረሳት ሲሉ ተመሳሳይ ድርጊት ይፈፅማሉ ብለዋል ዶክተር ኢንጂነር ጥላሁን፡፡ይሁንና አሁን ከያዙት መሬት በተጨማሪ ገፍተው እንዳይመጡ የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት በተጠንቀቅ ሊቆምና ዳር ድንበሩን ማስጠበቅ እንደሚገባው ዶክተር ኢንጂነር ጥላሁን አስገንዝበዋል፡፡ በተጨማሪም መንግሥት ግድቡ በሚገነባበት ቤኒሻንጉል ክልል አስተማማኝ ሰላም በመፍጠር የወራሪዎቹ አገር የማተራመስ አጀንዳ ከግቡ እንዳይደርስ ሚናውን እንዲወጣ አሳስበዋል።ከዶክተር ኢንጂነር ጥላሁን ኤርዱኖ ጋር የተደረገውን ሙሉ ቃለምልለስ ገጽ 6 ላይ ይከታተሉ።
https://www.press.et/Ama/?p=39157
406
0ሀገር አቀፍ ዜና
ከግልባብ ፍሬ
መዝናኛ
December 30, 2019
15
አንድ ገበሬ ናቸው። በዘመናቸው ሮጠው ያሻቸውን አድረገዋል፤ አንሰተው ጥለው እንዳላለፉ ሁሉ ዕድሜ ገሰገሰና ጉልበታቸው ከዳቸው። ጊዜ ሲገፋ አቅማቸው ሲደክም እጅ ሰጡ። በወጣትነታቸው ሌላውን የጦሩት ያህል ተረኛ መሆን ግድ አላቸው። ግን ደግሞ እድለኛ አልነበሩምና ‹‹ጧሪዬ ይሆናል›› ብለው ተስፋ የጣሉበት አንድያ ልጃቸው እስር ቤት ይገባል። ለዚያው ለገበሬ ወሳኝ በሆነው የአዝመራ ወቅት። ይህ ወቅት ገበሬው አቅሙን አሟጦ የሚጠቀምበት ነውና ሽማግሌው መሬታቸው ጦሙ ማደሩን ሲረዱ ሀሳብ ገባቸው። እናም ለልጃቸው ‹‹ልጄ አቅሜ እንደደከመ ጉልበቴ እንደዛለ ታውቃለህ። ዘንድሮ አንተም የለህ መሬቱ ፆሙን ማደሩ ነው። የአንተ መታሰርና ከእኔ መለየትን ሳስብ መጪው ጊዜ አስጨንቆኛል። በርሃብ መሞቴ ነው። መሬቱን ማን ቆፍሮና አለስልሶ አዝመራውን ይዘራልኛል? ችግር ውስጥ ወድቄብሃለሁ።›› በማለት ወደ እስር ቤት ደብዳቤ ላኩ። ልጃቸው የአባቱን መልዕክት አንብቦ ምላሽ ፃፈ። ‹‹አባቴ ዘንድሮ ሌላ ሰው የሚያግዝህ ቢኖር እንኳን የአዝመራውን ቦታ እንዳታስቆፍረው። አይዞህ! አምላክ ሌላ መፍትሄ ያቀርብልናል። የገደልኳቸውን ሰዎች የቀበርኩት እዚያ ቦታ ላይ ስለሆነ በፍፁም እንዳይቆፈር ሌላ ሰው ከቆፈረው ማስረጃ ይገኝብኛል፤ አደራ›› ብሎ መልዕክቱን ይመልሳል። ይህ መልዕክት ከተላከ ከጥቂት ቀናት በኋላ አባት ለልጃቸው በድጋሚ ደብዳቤ ላኩ። ‹‹ልጄ በጣም አመሰግንሃለሁ፤ ባለፈው የላከው ደብዳቤ እኔ ዘንድ ከመድረሱ በፊት ፖሊሶች አይተው ነበርና ማሳውን ሲቆፍሩ ከረሙ። ምንም አይነት ሬሳ ግን አላገኙም፤ ይህንን ያደረከው ቁፋሮው በዘዴ በእነሱ እንዲፈፀም አስበህ መሆኑን ተረድቻለሁ። እናም እነሱ በቆፈሩት ማሳ ላይ አዝመራዬን ዘርቼ እፎይ ብያለሁ። ልጄ እዚያም ሆነህ እገዛህ ስላልተለየኝ እጅጉን አመሰግናለሁ›› አሉት።እናም ምን ለማለት ነው ወዳጆቼ፤ የቀረበንን መጥፎ አጋጣሚ በመላ ብናልፈው አጋጣሚውን በመልካም ብንጠቀመው መልካም ነው። ‹‹የተወረወረብህን ጠጠር ለቅመህ መልሰህ ከመወርወር ይልቅ መሸጋገሪያ ድልድይ ስራበት›› የሚል ምክር ተደጋግሞ ይደመጣል። ልክ ነው። ስለማን ብለን መጥፎ አጋጣሚዎችን መጥፎነታቸው ላይ ብቻ በማተኮር እንቆዝማለን? ይልቅ መጥፎ ገጠመኙን እራሱን መግጠም የተሻለ ነው። በየዕለት እንቅስቃሴያችን የገጠመን አስቸጋሪ ጉዳይ ወደ ጥሩ አጋጣሚና ጥቅም የመለወጥ ልማዳችን ምን ያህል ይሆን? ያሰብነው አልሰምር፤ ያቀድነው አልሳካ ቢለን ፈፅሞ ወደ ተስፋ መቁረጥ መገባት የለበትም። ስንት ነገር ከፊታችን እያለ በአንድ ሙከራ መሳካት አለመሳካት እጅ ከተሰጠማ መነሻችን ላይ ለጉዳዩ የሰጠነው ቦታ ትልቅ መሆኑ እንጂ ገና ስናስበው ላይሳካ እንደሚችል አላስተዋልንም ማለት ነው። በነገራች ላይ ሙከራ የሚሳካው አልፎ አልፎ እንጂ ሁሌም አይደለም፤ የስኬታማ ሰዎች ገጠመኝና የህይወት ውጣ ውረድ ብንመረምር መንገዱ አልጋ ባልጋ ሆኖለት ያለፈ አይገጥማችሁም። በጉዛችን ውስጥ ወደኛ የሚቀርቡን መጥፎ አጋጣሚዎች ወደ መልካም ገጠመኝ መለወጥ እርግጥ የሚያወሩትን ያህል ቀላል አይደለም። ነገር ግን አንዴ ያ መጥፎ አጋጣሚ ወደኛ መጥቷልና ፈጥሮብን የሚያልፈው ጉዳት ከመቀበል ይልቅ ወደ በጎ አጋጣሚ መለወጡ ግድ ይለናል። ብዙ ጊዜ የበጎ ነገሮች አልያም የግኝቶች መነሻ አስቸጋሪ ወይም መጥቶ አጋጣሚዎች ናቸው። እንደውም በችግር ምክንያት የተፈጠሩ መፍትሄዎች የሰው ልጅ ኑሮ ሲያቀሉ በተደጋጋሚ አስተውለናል። ዛሬ ላይ አለም ጭለማን የረታበት ብርሃን ወይም መብራትን የፈጠረው ቶማስ ኤድሰን እጅጉን ጭለማ ይፈራ እንደነበር እናውቅ ይሆን? ጭለማን መፍራት ደግሞ ጭለማን ለመግፈፍ እንዲማስን አደረገውና መፍትሄ ወለደለት።እናም መከራ መፍትሄን ይወልዳል፤ ፍርሃት ማምለጫን ያበጃል። ድህነትን አጥብቆ የሚፈራ ሰው ከድህነት ለመውጣት ብርቱ ጥረት ያደርጋል። እራሱን ለመለወጥ ለሊት እና ቀን ሲማስን እራሱን የተሻለ ቦታ ላይ ለማድረስ ሁሌም ሲፍጨረጨር የተሻለ ቦታ ላይ መገኘቱ አይቀሬ ነው። እየንዳንዱ መጥፎ ገጠመኞቻችንን ወደ እድል እና መልካም አጋጣሚ መቀየር መቻላችን ጥቅሙ ያየለ የሚያደርገው ለዚሁ ነው። ውዶቼ አንድ ነገር ካስተዋልን ብዙ ጊዜ የኛ ስኬት መቃረቢያ የሚሆኑ ጉዳዮች ትኩረት የሰጠንባቸውና እንዳይደናቀፉብን ጠንቃቃ የሆንባቸው ጉዳዮች ናቸው። ስለ ጉዳይ አስልተን መመርምር ጉዳዩን ጠንቅቀን ማወቅና በዚያ ዙሪያ ያለንን ሁኔታ ምቹ ማድረግ እንዳለብን ፍላጎታችን ያስገድደናል። የጀመርነውን ጉዳይ ከዳር ለማድረስ መውተርተራችን ፍሬ ያፈራል። ነገር ግን ስኬትን አልመን የጀመርነው ጉዳይ ዋነኛ እና ወሳኝ ነው። ያመንበትን ሳይሳካልን ቢቀር አለመሳካቱን መነሻ አድርገን ያልተሳካበት ምክንያት መመርመር ተገቢ መሆኑ አያጠያይቅም። ያ ጉዳይ የኛ የመጨረሻ አማራጭ አድርገን መውሰዳችን የመጀመሪያው ስህተት ነው። አለም በብዙ ገጠመኞች የተሞላች ለሰው ልጆች ሰፊ ዕድልን ይዛ የቀረበች ሆና ሳለ የኛ ምልከታ ውስን ይሆንና አንድ መንገድ ላይ ብቻ ችክ እንላለን። ያ መንገድ ደግሞ የሚጓዙበት ብዙዎች ናቸውና የተጣበበ ሆኖ ይጠብቀናል። አስፍቶ መመልከትና ሌሎች አማራጮችን ማየቱ የኛ ልምድ ሊሆን ይገባል። በጥረታችን ውስጥ የሚገጥመንን ጋሬጣ መመንጠር የሚያስችል አቅም ይዞ መገኘትና መፋለም፤ ይህን የማድረግ አቅምን ከፈጠርን ሌላ ዘዴ መዘየድና ችግሩን እራሱ በመፍትሄነት መጠቀሙ ልምድ ብናደርግ መንገዶች ሁሉ ይቀናሉ። አዲስ ዘመን ታህሳስ 20/2012ተገኝ ብሩ
https://www.press.et/Ama/?p=24906
594
1መዝናኛ
በድምጽ መስጫ ሳጥን የገባው ቀለበት
መዝናኛ
December 31, 2019
38
በሀገሮች መሪዎችን ለመምረጥ ምርጫ እንደሚካሄድ ይታወቃል። ለእዚህም ዜጎች ድምጻቸውን ይሰጣሉ ፤ ድምጽ በሚሰጥበት ስፍራ ምንም አይነት ሁከት ሊፈጠር አይገባም። በእዚህ አካባቢ ድምጽ በሚሰጡበት ወቅት ወርቅ፣ ገንዘብ ፣ወዘተ ቢጠፋ ያዙኝ ልቀቁኝ ብሎ መጮህ አይቻልም፤ ሊያስጠይቅ ይችላል። ወርቅን ያህል ጠፍቶ ታዲያ እንዴት ዝም ይባላል ትሉ ይሆናል። ያሎት አማራጭ ተረጋግቶ በሰከነ መንፈስ ችግሩን ለሚመለከታቸው አካላት አሳውቆ ድምፁ እስኪጠናቀቅ በትእግስት መጠበቅ ነው።በፈረንጆቹ ባለፈው ታኅሳስ መባቻ በእንግሊዝ ትራፎርድ ምክር ቤት ድምጽ ለመስጠት የተገኘች አንዲት እንግሊዛዊት ከወላጅ እናቷ በስጦታ የተበረከተላትን የወርቅ የጣት ቀለበት ድምጽ ሰጥታ እንደወጣች ከጣቷ ላይ ታጣዋለች። ብዙ ስታፈላልግም ትቆያለች። የቀለበቱ መጥፋት በእጅጉ ያሳስባታል። ለእናቷ ምን ብላ እንደምትነግራትም ግራ ይገባታል። ቻርሎቴ የተባለችው ይህች እንግሊዛዊት ጓደኛዋ በአንድ የፌስ ቡክ ገጽ ላይ በድምጽ መስጫ ሳጥን ውስጥ ቀለበት ስለጣለ ሰው መረጃ መልቀቁን እስከ ገለጸላት ድረስም የት እንደጣለችውም ማስታወስ አልቻለችም። ቻርሎቴ ማንችስተር አቅራቢያ በሚገኘው በክሎቬራል መጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት ድምፅ እስከሰጠችበት ሰአት ድረስ ቀለበቱ ጣቷ ላይ አንደነበር ታስታውሳለች። ጓደኛዋ መረጃውን እስከላከላት ድረስም ቀለበቱ በድምፅ መስጫ ሳጥን ውስጥ ስለመግባቱም አላወቀችም።ነገሮችን መለስ ብላ ስታሰላስል ድምጽ በሰጠችበት ወቅት ሳንቲም የወደቀባት መስሏት እንደነበር አስታወሰች። ጓደኛዋ የሰጣትን መረጃ መሰረት በማድረግም ድምጽ ወደ ሰጠችበት ትራፎልድ ምክር ቤት ትደውላለች፤ ቀለበት እንደጠፋባትም ትገልጻለች። እነሱም በከተማው መሰብሰቢያ አዳራሽ እንዲቀመጥ ማድረጋቸውን ይገልጹላታል። ቀለበቱ በጠቋሚ ጣቴ ላይ ነበር ፤ ድምፄን ሰጥቼ እጄን ጎትቼ ሳወጣ ሳጥን ውስጥ ወድቆ ሊሆን ይችላል ስትል ትገልጻለች። ቀለበቱ አመልካች ጣቴ ላይ ነበር፤ ጣቴ ላይ ላላ ያለም ነበር፤ ለእዚህም ነው ድምጽ ስሰጥ በቀላሉ ከጣቴ ወልቆ ወደ ድምጽ መስጫ ኮሮጆ ውስጥ የገባው ያለችው ቻርሎቴ ፣በመገኘቱ በጣም መደሰቷን ተናግራለች። ‹‹የእናቴን ፊት እንዴት አያለሁ ብዩ ሳስብ ነበር፤ ለወደፊቱ እንዳይጠፋብኝ በደንብ ተጠንቅቄ እይዛለሁ። ምክር ቤቱ ላደረገልኝ ትብብር አመሰግናለሁ። “ስትል ገልጻለች።አዲስ ዘመን ታህሳስ 21 ቀን 2012 ዓ.ምኃይለማርያም ወንድሙ
https://www.press.et/Ama/?p=24956
257
1መዝናኛ
የአሰፋ ሳይንቲስት ውብ ወጎች
መዝናኛ
January 2, 2020
50
 ክፍል ሁለትባለፈው ሳምንት ክፍል አንድ ዝግጅታችን አሰፋ ሳይንቲስትን አስመልክቶ ጥቂት ወጎች ነበሩን። በጨለማው ዘመን የበሩት ፕሮፌሰር አሰፋ በፈረንሳይ ሀገር ኬሚስትሪ ያጠኑ ተመራማሪ ኢትዮጵያዊ ምሁር ነበሩ። እውቀቱ ገፋ ገፋ፤ ከመር ከመር ያደርጋቸው ነበር። ግን እኮ የቤተክህነቱንም ትምህርት ከግእዝ እስከ አራራይ የአማርኛውን ሰምና ወርቅ ጭምር ፈትለው ይገምዱት ነበር። ይሄ ምርምር የሚጠላውን ለማወቅ ጉጉት የሌለውን ደግሞ ‹‹ደናቁርት፤ ደነዝ፤ የሰው አጋሰስ፤ ሰው ነኝ›› ብሎ እኔ አሰፋ ሳንቲስት ሲሉ ካካታና ሳቅ ይበዛል። አሰፋ በተማሪው ዘንድ ምን አሉ? ምን ተናገሩ? እየተባለ እንደ አለቃ ገብረሃናም ፍቅር ዘርፈዋል፤ ይወደዳሉ። ተማሪ መሳቅ፤ መሳቅ፤ አብዝቶ መሳቅ መተረብ በተፈጥሮው ይወዳል። ሲጫወቱ አፍ ያስከድናሉ። በብዛት ወጋቸው ሕልማቸው ሃሳባቸው ሁሉ ሳይንስና ሳይንስ ብቻ ላይ ያተኩራል። ፈረንሳይ ከተማሩ ኢትዮጵያውያን ተማሪዎች ጋር ወጋቸው ብርቱ ነው። ለነገሩ ጃንሆይስ አሳምረው ፈረንሳይኛ ይናገሩ አልነበር። ሳባ— ዊ– ሳባ፤ ሲ– መርሲ–መርሲ– ቦኩ እንዲሉ። አሰፋ ሳይንቲስት ነገር ካልመሰላቸው ነቋሪም ነበሩ። ሸንቆጥ፤ ላጥ አድርገው ደርሰው ያጥረገርጋሉ። ሲያሻቸው በቅኔ ይደበድባሉ። በውስጠ ወይራ አማርኛ አያድርስ ነው። ድንዙዝ እንዲሉ መሪጌታ ማን ይፈታዋል ብለህ ነው ምርቃት ይሁን እርግማን ከአዋቂዎች በቀር። ብትሰደብም መሳቅ ነው። አሰፋ ሳይንቲስት የሚያስተምሩበት ስንቱን ታላላቅ ኢትዮጵያዊ ያፈራው የተፈሪ መኮንን ትምህርት ቤት የዘመኑ ካምብሪጅ ነበር። ኮከብ፤ ቀንዲል አውራ።ታላላቅ የጦር መሪዎች ጀነራሎች፤ ፓይለቶች፤ ማሪኖች፤ ሚኒስትሮች፤ የዩኒቨርሲቲ መምህራን፤ የሕክምናና ሌሎችም ዶክተሮች ወዘተ ተምረው ተመርቀው የወጡበት በዘመኑ እጅግ ታዋቂ ስሙ የገነነ የተጠራ ትምህርት ቤት ነበር፤ ተፈሪ መኮንን። አሰፋ ሳይንቲስት ቁመተ አጭር፤ ቁንን እንደነበሩ የሚያውቁአቸው ይናገራሉ። በዚያ ዘመን ስለሳይንስና ምርምር የሚያውቁ ሰዎች አልነበሩም። ግፋ ቢል የሰይጣን ስራ ነው የሚባልበት ነበር። አጤ ምኒሊክ ከውጭ ፊልም አስመጥተው በግድግዳ ላይ እንዲታይ ሲያስደርጉ የሰዎቹን ምስል በስክሪኑ ላይ ያዩት አያቶቻችን እያማተቡ ‹‹በስመ አብ–ወ– ወልድ ወ–መንፈስ ቅዱስ እነዚህ ሰይጣኖች ናቸው›› በማለታቸው ነበር ፊልም ቤቱ ሰይጣን ቤት የተባለው።መኪናም ስልክም ሲገባ እንዲሁ የሰይጣን ስራ ነው የሚል ተቃውሞው የበረታ ነበር። በዚያም ዘመን ነው አሰፋ ሳይንቲስት የኖሩት፤ የሰሩት፤ ምርምር አድርገው ሮኬት ለማስወንጨፍ የሞከሩት። በራሳቸው ምርምር በሀገር በቀል እቃዎች በመጠቀም ሮኬት ወደ ጨረቃ ለማስወንጨፍ የሞከሩ የመጀመሪያው ኢትዮጰያዊ። ስራቸው የሚታወቀው የሚደመመው ግሩም እምግሩማን አሰፋ ሳይንቲስት የተባለላቸው የተጨበጨበላቸው ሰው። አሰፋ ሳይንቲስት በኢትዮጵያ የጠፈር ምርምር ታሪክ ውስጥ አንድ ቀን ብርሃን ሆነው ይገለጣሉ። ታሪካቸው አምሮ ይጻፋል። ምርምራቸው ዶክመንቶቻቸው ቢፈተሹ አንድ ቦታ ሊያደርሱ ይችላሉ። ‹‹አሴ፤ አሰፋ ሳይንቲስት›› እያሉ ነው ራሳቸውን የሚጠሩት። ሌሎችም እንዲሁ። ለዛ ያለው ወግ አዋቂ ስለነበሩ በእርሳቸው ንግግር ተማሪው ይመሰጣል፤ ይደመማል፤ ያውካካል። ሲያሻቸውም ይጨምሩበታል። አለማድነቅ አይቻልም። ግሩም ድንቅ ።አንድ ጊዜ አሰፋ ሳይንቲስት ክፍል ውስጥ ገብተው ማታ ሕልም ማየታቸውን ይናገራሉ። ተማሪው እንደተለመደው አፉን ከፍቶ ያዳምጣል። ተኝተው ከአልጋቸው ግርጌ ታላቁና ኃያሉ መልአክ ቅዱስ ገብርኤል የተንቆጠቀጠ ወርቅ ልብሱን ለብሶ ሰይፉን እንደያዘ ቆሞ ‹‹አሰፋ ሳይንቲስት ሲለኝ በመደንገጥ ተርበትብቼ አቤት ብዬ ተነሳሁ። እንካ ይሄ የአቶሚክ ቦምብ መስሪያ ፎርሙላ ቀመር ነው ተጠቀምበት አለኝ። በድንጋጤ ተውጬ እንደተቀበልኩ ተሰወረብኝ።›› እሺ አለ ተሜ አፉን ክፍቶ። ‹‹ይሄን ሚስጢር ለመከላከያ ሚኒስትርና የፈረንሳይ ተማሪ (ፍራንኮ ፎን) ለሆነው ለጀነራል አቢይ ወዳጄ ስለሆነ ሄጄ ነገርኩትና እባክህ ጃንሆይ ጋር እንድቀርብ አድርገኝ አልኩት›› አሉ።ጀነራል አቢይ ቀጠሮ አስይዞ አሰፋ ሳይንቲስትን ንጉሱ ዘንድ ይወስዷቸዋል። እጅ ይነሳሉ። ጉዳይህ ምንድነው አሰፋ ሳንቲስት ተብለው ሲጠየቁ በተለመደው ሥርዓት ለጥ ብለው ንጉሰ ነገስቱን እጅ ይነሳሉ። ቀጥለው በሕልማቸው የተነገራቸውን የቦምብ ፎርሙላ ቀመር ይናገራሉ። ‹‹እናሳ›› ሲባሉ ጃንሆይ እንድሰራ ይፈቀድልኝ ይላሉ። አሰፋ ሳይንቲስት አንድ አይናቸው በፈንጣጣ ሕመም በልጅነታቸው ጠፍቷል። በዚህም ትልቅ የአይን መነጽር ያደርጋሉ። ይሄን ንጉሱ ያውቃሉ። ንጉሱ በዙፋናቸው ሆነው ካዳመጡ በኋላ ለአሰፋ ሳይንቲስት መልስ ይሰጣሉ። ‹‹እሺ ልጃችን አሰፋ ሳይንቲስት አንተን ይህን ስራ ብሎ መፍቀድ ለኢትዮጵያ አንድ አይን ነህ፤ አንድ አይናችንን ማጥፋት ነው የሚሆንብን›› የሚል መልስ ሰጡ። አሴ በመጡበት ተመለሱ። ባለቅኔዋ ሀገሬ እንዴት ነሽ። ተማሪው ታሪኩን ሲጨርሱ ቅኔው ስለገባው በክፍሉ ከፍተኛ ሳቅ እየሳቀ አውካካ። አሰፋ ሳይንቲስት በክፍል ሲያስተምሩ ተማሪው የሚናገሩትን ለመስማት በናፍቆትና በጉጉት ይጠብቃል። ቀጠሉ ደግሞ በሌላ ቀን ተማሪዎች ክፍል ገብተው። ‹‹ሰማችሁ ተማሪዎች›› አሉ አሰፋ ሳይንቲስት ። ‹‹ከተማርኩበት ፈረንሳይ ሀገር ፓሪስ ከተማ በሚደረገው የሳይንቲስቶች ጉባኤ ላይ እንድገኝ ደብዳቤ ደርሶኛል›› ካሉ በኋላ ደብዳቤውን ለተማሪዎች እንዲህ ብለው አነበቡ። ‹‹ለተከበርከው ውድ ወዳጃችን ወንድማችን አሰፋ ሳይንቲስት፤ እንደምን ከርመሀል፤ በፈረንሳይ ፓሪስ ከተማ የዓለም ሳይንቲስቶች ስብሰባ ስለሚካሄድ በዚሁ ስብሰባ ላይ እንድትገኝ በክብር ተጋብዘሃል። አክባሪህ ራስቤልድ።›› ብለው የፈራሚውን ታዋቂ የፈረንሳይ ሳይንቲስት ስም ያነባሉ። ተማሪው ፍንድት ብሎ በሳቅ ያውካካል። ያ ፈረንሳዊ ሳይንቲስት የሞተው ከ100 ዓመት በፊት ነበር። በዚያ ዘመን በሕይወት የለማ። አሴን አለማድነቅ አይቻልም። አሰፋ ሳይንቲስት ከትምህርት ቤት መልስ ሁል ጊዜ ማታ ማታ ሲዝናኑ የሚያመሹት ከጥንት ጀምሮ ታዋቂ በሆነው የአራት ኪሎው ቱሪስት ሆቴል ነበር። ተመርቀው ስራ የያዙ ተማሪዎቻቸው በብዛት ቱሪስት ሆቴል ነበር የሚርመሰመሱት። አሰፋ ሳይንቲስት ሲመጡ ወጉ ጨዋታው ይደራል። ተጋብዘው ጠጥተው ሲጨርሱ አሰፋ ሳይንቲስት ተነስተው ውልቅ ብለው ነው የሚሄዱት። አመላቸው ይታወቃል። ሲጀመር ተማሪዎቻቸው ስላሉ ማንም ሂሳብ አያስከፍላቸውም። ከተጋበዙ በኋላ አመሰግናለሁ ፤ ደህና እደሩ የሚል ቃል ከአሴ አፍ አይወጣም። ብለውም አያውቁ። ተማሪዎቹ እርስ በእርስ መከሩና አሰፋ ሳይንቲስት መቼም የሚለው አያጣ ቆይ እስቲ ብለው አንዱ ተማሪያቸው እንዲናገራቸው ተወከለ። አንድ ቀን ምሽት እዛው ቱሪስት ሆቴል እየተዝናኑ እያሉ ‹‹ጋሼ አሰፋ ሁሌ ግዜ እንጋብዝዎታለን ወደቤት ሲሄዱ አመሰግናለሁ እንኳን አይሉም፤ ለምንድ ነው?›› ይላቸዋል። ምን አልክ አሉት። እየሳቀ ደገመላቸው። እዛው አራት ኪሎ ቱሪስት ሆቴል ውስጥ ነበሩ። ‹‹ሰማሁህ ፤ሰማሁህ፤ ና፤ና ተከተለኝ›› ብለው ከሆቴሉ ይዘውት ይወጣሉ። ከሆቴሉ ፊት ለፊት ተኮልኩለው የሚሰሩትን ሊስትሮዎች አየሃቸው ብለው ያሳዩታል። አዎን አየኋቸው ብሎ መለሰ። ‹‹ይኸውልህ እኔ አሰፋ ሳንቲስት ባላስተምርህ ኖሮ እንደነሱ ሆነህ ትቀር ነበር። ስለዚህ የምትጋብዙኝ የልፋቴን ዋጋ ነው። ምስጋና አያስፈልገውም›› ብለው እርፍ። ተመለሱና አብረው ወደ ሆቴሉ ገቡ። ‹‹ምን አለ አሴ?›› አሉ ውስጥ የነበሩት ጓደኞቹ። ‹‹እሱን ማን ይችላል›› አላቸው። በመሃል እንደተለመደው ደህና እደሩም አመሰግናለሁ ሳይሉ አሰፋ ሳይንቲስት ውልቅ ብለው ወደቤታቸው እብስ አሉ። አዲስ ዘመን ታኅሣሥ 23/2012 ወንድወሰን መኮንን
https://www.press.et/Ama/?p=25046
808
1መዝናኛ
የመጸዳጃ ቤት ቆይታን ለማሳጠር
መዝናኛ
December 31, 2019
31
ዘመናዊ መጸዳጃ በሀገራችን ብዙም አልተስፋፋም ቢባል ዋሾ አያሰኝም፤ ይህን እጥረት መንግሥትም በሚገባ ያውቀዋል። ከዚህ አኳያም የመጸዳጃ ቤት አገልግሎትን በከተማ ለማስፋፋት እየተሰራ ይገኛል። በከተሞች የህዝብ፣ የመንግሥትና የሆቴል መፀዳጃ ቤቶች በስፋት የሚስተዋሉ ሲሆን፣ የመኖሪያ ቤቶች መጸዳጃ ቤቶች በስፋት እየዘመኑ ናቸው። በገጠርም በዚሁ ላይ ግንዛቤ በማስጨበጥ ሰዎች ጤናቸውን ለመጠበቅ በመጸዳጃ ቤት እንዲገለገሉ ለማድረግ በተለይ በጤና ኤክስቴንሽን ሰራተኞች በኩል እየተሰራ ነው። በከተሞች በተለይ በህዝብ መጸዳጃ ቤት አጠቃቀም ላይ ግን ተግዳሮቶች ይስተዋላሉ። መጸዳጃ ቤቶችን በንጽህና እና በአግባቡ አለመጠቀም አንድ መሰረታዊ ችግር ነው። መጸዳጃ ቤት ገብቶ ቶሎ አለመውጣት ሌላው ችግር ነው። አንዳንዶች ከጤና ጋር በተያያዘ በተለይ ድርቀት ያለባቸው ናቸው ይባላል መጸዳጃ ቤት እነዚህ ሰዎች መጽሀፍ ፣ጋዜጣ ወዘተ፣ ይዘው በመግባት እያነበቡ ብዙ ይቆያሉ። ሞባይላቸውን ይዘው ገብተው ኢንተርኔት ይሁን ሌላ የሚከታተሉም ጥቂት አይደሉም። ይህ አይነቱ የመጸዳጃ ቤት አጠቃቀም በተለይ በሆቴሎችና በህዝብ መጸዳጃ ቤቶች ተጠቃሚዎች ላይ አሉታዊ ተጽእኖ ያሳድራል። የእነዚህ ተገልጋዮች ተግባር የራሳቸውንም የሌላውንም ተጠቃሚ ጊዜ ያባክናል። ይህ ችግር የሌሎች ሀገሮችም ችግር ነው። ችግሩ አሳሳቢ እየሆነ መምጣቱን ተከትሎም አዲስ የመጸዳጃ መቀመጫ ዲዛይን ብሪታኒያ ውስጥ እስከ መስራት መደረሱን ኦዲቲ ሴንትራል ድረ ገጽ ሰሞኑን ይዞት በወጣ መረጃ አስነብቧል። ይህ መቀመጫ ሰዎች መጸዳጃ ቤት ውስጥ ከአምስት እስከ ሰባት ደቂቃ በላይ እንዳይቆዩ የሚያደርግ ነው። ይህ የመጸዳጃ ቤት መቀመጫ እንደ ሌሎቹ መቀመጫዎች ምቾት የሚሰጥ ባለመሆኑም ሰዎች ተቀምጠው እንዲያነቡም ሆነ ሞባይል እንዲነካኩ ብዙም እድል አይሰጥም ይለናል መረጃው። መቀመጫው ዲዛይን የተደረገው በእንግሊዛዊው መሀንዲስ ማሃቢር ጊል ሲሆን፣ ከመደበኛው መጸዳጃ መቀመጫ በ13 ዲግሪ ቁልቁል ያጋደለ ነው፤ ሰዎችም በዚሁ ልክ አጋድለው እንዲቀመጡ የሚያደርግ በመሆኑ ምቾት ይነሳል። ጊል የዚህ መቀመጫ ሃሳብ የተከሰተለት መጸዳጃ ቤት ተጠቃሚዎችን ምቾት ስለሚነሳቸው ቶሎ ጣጣቸውን ጨርሰው እንዲወጡና የኪስ ስልክ እያዩ ጋዜጣ ወይም እያነበቡ እንዳይቆዩ በማሰብ ነው። የተቀጣሪዎችን የሥራ ሰዓት ማስፋት ለሚፈልጉ ነጋዴዎችም መልካም አጋጣሚ መሆኑን ይገልጻል።“በእንግሊዝ ብቻ በአንድ የሥራ ቀን ሰራተኞች አለአግባብ የሚያባክኗቸው ጊዜያት የኢንዱስትሪና የንግድ ባለሀብቶችን በዓመት 4 ቢሊዮን የእንግሊዝ ፓውንድ እንደሚያስወጣቸው ይገመታል።” ሲል ሚስተር ጊል ጠቅሶ፣ አዲሱ የመጸዳጃ ቤት መቀመጫ ሠራተኞቻቸው በመጸዳጃ ቤት አለአግባብ የሚያጠፉትን ጊዜ በማዳን ቀጣሪዎች የበለጠ ሀብት እንዲያፈሩ ያስችላል ይላል።አዲሱ መቀመጫ ለትርፍ ባልተቋቋመው የብሪቲሽ መጸዳጃ ቤቶች ማኅበር ተቀባይነት ያገኘ ሲሆን ፤ ማኅበራዊ ሚዲያዎች ግን የመጸዳጃ መቀመጫውን ዲዛይን በስላቅ አጣጥለውታል ።በመጸዳጃ ቤት ለረጅም ጊዜ መቆየት አይገባም ሲል በድረ ገፅ ላይ አስተያየቱን የሳፈረው ጊል፣ ለእዚህም ሲል አጨቃጫቂውን የመፀዳጃ ቤት መቀመጫ ዲዛይን መስራቱን ለዊርድ መጽሔት ጠቁሟል። አንዳንዴ ሠራተኞች በመጸዳጃ ቤት ተኝተው እንደሚገኙም ጠቅሶ፣ በሕዝብ መጸዳጃ ቤቶችም ወረፋዎች እየበዙ ተራ የሚጠብቁ ተገልጋዮች ሲቆጡ እንደሚሰማ ይገልጻል። በአገልግሎት ላይ ያለው የመጸዳጃ ቤት መቀመጫ ለተጠቃሚዎች ጤና የሚሰጥ እና ተክለ ሰውነትን የሚያሻሽል እንደሆነ ጊል ቢያምንም ፣ አዲሱ የመጸዳጃ ቤት መቀመጫ ግን ቀጣሪዎችን ከኪሳራ እንደሚታደግም ተናግሯል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 21 ቀን 2012 ዓ.ም ኃይለማርያም ወንድሙ
https://www.press.et/Ama/?p=24949
394
1መዝናኛ
ፕሬዚዳንቱ ከስልጣን እንዲባረሩ የአሜሪካ ሕገመንግሥት 25ኛው ማሻሻያ እየተጠቀሰ ነው
ሀገር አቀፍ ዜና
January 9, 2021
10
በኃይሉ አበራከትናንት ወዲያ የዶናልድ ትራምፕ ነውጠኛ ደጋፊዎች የመንግሥት መቀመጫና የሁለቱ ምክር ቤቶች አዳራሾች የሚገኙበትን ግዙፉን የካፒቶል ሒል ህንጻን ጥሰው መግባታቸውን ተከትሎ ከፍተኛ የሴኔት ምክር ቤት አባላት ፕሬዚዳንቱ ከስልጣን እንዲባረሩ እየጠየቁ መሆኑን ቢቢሲ ዘግቧልበዘገባው መሰረት የአሜሪካ ሕገመንግሥት 25ኛው አሜንድመንት ወይም ማሻሻያ እየተጠቀሰ ሲሆን፤ ይህ ማሻሻያ አንድ የአሜሪካ ፕሬዚዳንት አካላዊ ወይም አእምሯዊ ጤና ከራቀው ምክትል ፕሬዚዳንቱ ቦታውን በተጠባባቂነት ተረክቦ አገሪቱን እንዲመራ ያዛል።ሆኖም ይህ እንዲተገበር የምክር ቤቱ አፈጉባኤ ናንሲ ፔሎሲን ጨምሮ በትንሹ ስምንት የካቢኔ አባላት በጉዳዩ ላይ መስማማት አለባቸው። ነገር ግን ይህ የመሆን እድሉ ለጊዜው ጠባብ ነው ተብሏል።የትራምፕ ነውጠኛ ደጋፊዎች ካፒቶል ሒልን ጥሰው ሲገቡ ታህታይና የላዕላይ ምክር ቤት አባላት የባይደንን መመረጥ ከግዛት ተወካዮች የማረጋገጥ ሥነ ሥርዓት ላይ ተገኝተው ይህንኑ በማካሄድ ላይ ነበሩ። አፈ ጉባኤ ናንሲ ፔሎሲና ምክትል ፕሬዚዳንት ማይክ ፔንስም በሸንጎ ላይ ተገኝተው ነበር።ይህንን ለአሜሪካ እንግዳ የሆነ ድርጊት ተከትሎ የሕግ መምሪያ ምክር ቤት አፈ ጉባኤዋ ናንሲ ፔሎሲ 25ኛውን የሕገ መንግሥት ማሻሻያ በመጥቀስ ትራምፕ አሜሪካንን ለመምራት ብቁ ስላልሆኑ ከዋይት ሐውስ እንዲባረሩ ጥያቄ አቅርበዋል።ይህን ጥያቄ በርካታ ዲሞክራቶችና ጥቂት ሪፐብሊካኖች ጭምር ድጋፍ ሰጥተውታል። የሴኔት ዲሞክራት ተጠሪ ቸክ ሹመር ትራምፕ አመጽ በማቀጣጠላቸው ከሥራ ሊባረሩ ይገባል፤ “ምክትል ፕሬዚዳንቱ እና ካቢኔው ይህንን ለማድረግ የማይፈልጉ ከሆነ፣ ኮንግረሱ ዳግመኛ ፕሬዚዳንቱን ከሥልጣን እንዲነሱ ለማድረግ መሰብሰብ አለበት” ብለዋል።ዶናልድ ትራምፕ ከዋይት ሐውስ እንዲወገዱ እንቅስቃሴ የተጀመረ ሲሆን ለድርጊታቸው ክስ እንዲመሰረትባቸውም ናንሲ ፒሎሲ ጥሪ አድርገዋል። ክሱ ተፈጻሚ እንዲሆን ግን ዲሞክራቶች የሪፐብሊካኖችን ድጋፍ ማግኘት አለባቸው። ምክንያቱም ክሱ እንዲፈጸም የምክር ቤቱ ሁለት ሦስተኛው ድምጽ ስለሚያስፈልግ ነው። ይህ የመሳካት እድሉም አነስተኛ ነው።25ኛው አሜንድመንት ፕሬዚዳንቱ ኃላፊነቶቹን መወጣት በማይችልበት ጊዜ ምክትል ፕሬዚዳንቱ ስልጣኑን በጊዜያዊ ፕሬዚዳንትነት ተረክቦ እንዲያስተዳድር ይፈቅዳል። በአሁኑ ሰዓት መነጋገሪያ እየሆነ ያለው የዚህ አሜንድመት አንቀጽ አራት ነው። ይህ አንቀጽ ምክትል ፕሬዚዳንቱ እንዲሁም የካቢኔው አብላጫ አባላት ፕሬዚዳንቱ ኃላፊነታቸውን መወጣት አልቻሉም ብለው እንዲወስኑ እድል ይሰጣቸዋል። ፕሬዚዳንት ትራምፕ ከሥልጣናቸው እንዲወርዱ ቢደረግ ምክትል ፕሬዚዳንት ማይክ ፔንስ አገሪቱን እንዲመሩ ይደረጋል። ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ፊርማቸው ያረፈበትን ደብዳቤ መላክ የሚጠበቅባቸው ሲሆን፣ ሴኔቱም ፕሬዚዳንቱ ሥልጣንና ኃላፊነታቸውን ለመወጣት ብቁ አይደሉም ሲል ያፀድቃል።ፕሬዚዳንቱ በኮቪድ-19 ተይዘው በነበረበት በጥቅምት ወር ላይ አገሪቱን ለመምራት ሕመማቸው አያስችላቸውም በሚል ተነስቶ ነበር። በዚሁ ወቅት የተወካዮች ምክር ቤት አባል የሆኑት ናንሲ ፔሎሲ፣ በ25ኛው አሜንድመንት ላይ መሰረት ያደረገ እና የፕሬዚዳንቱን ጤና ለሥራ ብቁ መሆን አለመሆኑን የሚፈትሽ ሕግ አስተዋውቀው ነበር።25ኛው አሜንድመንት በፈረንጆቹ አቆጣጠር በ1967፣ ጆን ኦፍ ኬኔዲ ከተገደሉ አራት ዓመት በኋላ፣ ፕሬዚዳንቱ በተለያየ ምክንያት ሥልጣንና ኃላፊነታቸውን ባልተወጡ ወቅት ማን ይተካቸዋል የሚለውን ጥያቄ ለመመለስ በሚል ጸድቋል።በዚህም የተነሳ በርካታ ፕሬዚዳንቶች ይህንን የሕግ ማሻሻያ [አሜንድመንት]፣ በይበልጥ ደግሞ በጊዜያዊነት ሥልጣንን ለምክትላቸው ማስተላለፍ የሚፈቅደውን ክፍል፣ አንቀጽ ሦስትን ተጠቅመውበታል።በ2002 እና በ2007 ፕሬዚዳንት ጆርጅ ደብሊው ቡሽ የአንጀት ህክምና በሚያደርጉበት ወቅት ምክትላቸው እንዲተኳቸው አድርገዋል። ፕሬዚዳንት ሮናልድ ሬገን በ1985 ለካንሰር ህክምና ሆስፒታል በገቡበት ወቅት ተመሳሳዩን አድርገዋል። ነገር ግን እስከ ዛሬ ድረስ 25ኛው አሜንድመንትን በመጠቀም የትኛውም ፕሬዚዳንት ከሥልጣን እንዲወርድ ተደርጎ አያውቅም።አዲስ ዘመን ጥር 01/2013
https://www.press.et/Ama/?p=39204
418
0ሀገር አቀፍ ዜና
ወራጅ
መዝናኛ
January 6, 2020
16
ረዳትና ሹፌር የታክሲ የአውቶቡስ ወይም የሌላ መጓጓዣ መሪ ጠምዛዥና መላሽ የበር በረኛ አሳላፊ ናቸው። መገኛቸው እርግጥ እዚህ ፅሁፍ ላይ የወከሉት የወሬያችን ማጣፈጫ የጉዛችን ትዝብት መነሻና ፈጣሪዎች ናቸው። አብዝተው እኛነታችንን ያሳዩናል፤ አግዝፈው ማንነታችንን በእነርሱ ውስጥ ያጎሉልናል። እርግጥ ረዳትና ሹፌር መነሻቸው ማህበረሰብ መድረሻውም ህዝብ ስለሆነ እኛን በደንብ ያውቁናል። እኛም እነርሱ የሚያውቁንን ያህል ባናውቃቸውም በምልከታና በውሏችን በግምትና በሚናገሩት የሆነ ቦታ ላይ መመደቢያ እውቀት አላጣንላቸውም። የትውውቃችን ልዩነት ቢሰፋ አያስገርምም፤ እነርሱ እኛ መተዳደሪያቸው ስለሆንን ያለኛ ህይወት ምናቸውም አይደለም። እርግጥ እኛም በእርነሱ መሪነት መጓዛችን አልቀረምና መንገድ አመላካቻችን ናቸው። የሚቀንሱልን ድካም ሲታወስ ደግሞ እኛም ያለነሱ ህይወት ምን ያህል እንደምትከብድብን አያጠያይቅም። ደጋግሜ ስመለከታቸው ሹፌርና ረዳት አንድ ይመስሉኛል። ረዳቱ ሹፌሩን ሹፌሩ ከረዳቱ ጋር ያላቸው ግንኙነትና ተነጣጥለው ከእኛ ጋር ያላቸው ጉዳይ ሁሉ ከማስበው ጉዳይ ጋር መመሳሰላቸው ይበዛል። አይን አስመልክቶ አዕምሮ አስተውሎ ጉዳችን እየተመነዘረ ሲታይ እውነትም የማይመሳሰል ልዩነት የለም። የቅርባችን የሆኑትን ሹፌርና ረዳትን ሳስብ አንድ ነገር ጋር ተመሳሰሉብኝና ከማለፍ ላጋራችሁ ወደድኩ። ውዶቼ እኔ ረዳትና ሹፌሩ እንትናን እና እንትናን መሰሉኝ አልልም ፅሁፌን ስታነቡ ግን ስለ ማን እያወራሁ እንደሆነ እጅግ ይገባችኋል። በእርግጥም እኔም እናንተም እዚያው ውስጥ ስላለን አንድ መጓጓዣ ውስጥ በምናብ ይዣችሁ ልገባ ነው። ሹፌርና ረዳቱ መነሻዎቼ ተግባርና ስራቸው ደግሞ ማማሰያዎቼ ናቸው። የታሰበኝን በእርነሱ ውስጥ ማሳየት ፈለኩ፤ተከተሉኝ። ፀሀይ ጮራዋን ስትፈነጥቅ ከያለበት በማለዳ ተነስቶ በአጋጣሚ ሁሉም እዚያ ቦታ ላይ ተገኝቷል። እሩቅ ተጓዥ አብሮ ነጓጅ መሆኑን ተረድቶ በጋራ ስምምነት ጉዞውን ለማድረግ በመልካም ፍቃደኝነት አብሮ ለመዝለቅ ተገናኝቷል። መጓዣው ያለ ስጋት የተፈለገበት ማድረስ የሚያስችል አቅም አለው። ሹፌሩ ካልተዘናጋ ረዳቱ የእውነት አጓጓዥ ከሆነ ተጓዡ ስለ መጓጓዣው ካሰበ በእርግጥም ምቹ ነው። ረዳቱ “የሞላ… የሞላ” እያለ ይጣራል። ለካ ሰዎች መሀል የነበረው ሹፌር የሞላው መኪና ላይ ለማሟያነት ተመልቶ ገብቶ ከፊት ቦታውን ይዞ ኖሯል። በሹፌሩ ጠያቂነትና ረዳቱ በሰጠው ምላሽ ሁሉም ተሳፋሪ ቦታውን መያዙ ተሰማ። ተሳፋሪው ልሳነ ብዙ ነው፤ በየራሱ መናገሪያ የጋራ ስለሆነው ጉዳይ ይነጋገራል። ሹፌሩን ተማምኖ ሁሉም መንገዱን ቀጥሏል። ተሳፋሪው እርስ በእርሱ ለመግባባት በጋራ አብሮ የሚያስጉዘውን ተስፋ የጋራ የሆነ አላማን ሰንቋል። ሁሉም ያሰበው እስከ መጨረሻ አብሮ በጋራ መድረስ ነው። መጓጓዣው ወደ ፊት ይሄዳል። መሪው አንዳንዴ ብቻ ከኋላ ድምፅ ሲሰማ ወደ ኋላ እየተመለከተ አብዝቶ ወደፊቱ ብቻ እያየ መጓጓዣውን ይመራል።ጉዞው አድካሚ ነው። መንገዱ ብዙም የተቃና ባይሆንም፤ የተሳፋሪውን የጋራ ጉዞ የሚደናቅፍን ጋሬጣ ግን በመተጋገዝ እያለፍነው ቀጥለናል። የጉዞው ትልቁ ፈተና የሆነው ረዳቱ ነው። በእግጥም ከሹፌሩ ለተሳፋሪ የሚቀርበው ረዳቱ ስለሆነ ለተሳፋሪው ክፉ ሆኖ የሚታየው ብዙውን ጊዜ ረዳቱ ነው። እርግጥ ሹፌሩ ረዳቱን ሿሚ ስለሆነ ከሹፌሩ ጋር ነጥሎ አይጠላውም። ለይቶም አይወደውም። ረዳቱና ሹፌሩ በበለጠ ግንኙነታቸው የጠበቀ ነው። ረዳቱ ከተሳፋሪው አንድም ሳይቀር የሚፈለግበትን ተቀብሎ ለሹፌሩ አስተላልፏል። ግን ደግሞ በየመሃሉ ‹‹ሂሳብ ያልከፈለ አለ›› ብሎ መጠየቁን ቀጥሏል። ያልከፈለ የሚጠበቅበትን ያላዋጣ አንድም እንደሌለ ጠንቅቆ ያውቀዋል። ነገር ግን የያዘውን እያጎደለ የተሰጠውን እየቀነሰ ያልከፈለኝ አለ ወይ የሚለውን ጥያቄውን ይደጋግማል። አጠገቡ ባለው መጮህ በቀረበው ማሳበብ የተለመደ ነውና ሁሉም ረዳቱን ይገላምጣል። ረዳቱ ሲነካ ሹፌሩ ጋር መድረሱ አይቀርም። ጩኸቱ ሲከር ድምፁ ሲጎላ ግን ሹፌሩም ወደ ተሳፋሪው መመልከቱ አልቀረም። ተሳፋሪው በረዳቱ ንግግር በሽቋል። ‹‹እንዴት መክፈላችሁን እያወቀ ያልከፈለ አለ›› ብሎ ይጠይቃል።ተሳፋሪው እርስ በእርሱ ባይጠራጠርም አንዳንዱ ላይ “ያልከፈለ ይኖር ይሆን?” የሚል የተሳሳተ ሀሳብ ወደ አዕምሮው ብቅ ያለ ይመስላል። እራሱ የከፈለ እንጂ ሌላ ያልከፈለ ወይም ያላዋጣ ያለ የሚመስለው ከመሀል አልጠፋም። ደግነቱ አብዛኛው ተሳፋሪ መክፈሉን ያውቃል። የረዳቱ ‹‹ያልከፈለ አለ?›› የሚል ተደጋጋሚ ጥያቄ፤ ያልከፈለ ይኖር ይሆን እንዴ አሰኝቶት እንጂ አንዱ ለሌላው ሌላው ለአንደኛው መክፈሉን ያውቃል።ተሳፋሪው በተለያየ ቋንቋ እያወራ ይግባባል። የተለያየ የባህል ስብጥር ያለው ቢሆንም አይጣረስም። እንደውም አንዱ ባንዱ ሳይዳቀል አንዱ በሌላው ሲሞላ ልዩ ይሆናል። በውይይት በመግባባት ጉዞውን ቀጥሏል። ሹፌሩ የተሳፋሪውን ሁኔታ ለመቃኘት አንዳንዴ ዞር ሲል መጓጓዣው በትክክል መንዳት ይሳነውና ይንገጫገጫል። ያኔ ተሳፋሪው ወደ ሹፌሩ ያማትራል። ‹‹ቀስ ብለህ ንዳ እንጂ፤ በሰላም መግባት እንፈልጋልን።›› የሚለው ይበዛል። ቀስ ሲል ደግሞ ‹‹አይችልም እኮ ለምን መሪውን ለሌላ ሰው አይሰጠውም›› የሚለውም አልጠፋም። “ወራጅ አለ?” የረዳቱ ሌላ ጥያቄ፤ ምን ማለቱ ነው። ተሳፋሪው አልጎመጎመ።የምን ወራጅ ብሎ ጥያቄ ማቅረብ ነው። ሁሉም አብሮ ሊጓዝ ተስማምቶ፤ ሁሉም አብሮ እስከመጨረሻ ሊሻገር ተነጋግሮ፤ ወራጅ አለ ማለት ምንድን ነው። ተው እንጂ ረዳት ቀስ ቀስ..ሹፌሩንም አታደናብር። ህዝቡ በብዙ ይህን ማለት ፈለገ። አንድ ተጓዥ ተናገረ። ይሄን ያለው በሌላው ተደገፈ። ሹፌሩና ረዳቱ ተሳፋሪውን ይዘው ጉዞዋቸውን ቀጥለዋል። አልፎ አልፎ በተሳፋሪው ግራ መጋባት ጉዞአቸው ጋብ እያለ መልሶ እየቀጠለ ወደ ፊት በጋራ መጓዙን ቀጥለዋል። የሹፌሩ መዘናጋት በተሳፋሪው እሪታ እየተቃና የረዳቱ ‹‹ወራጅ አለ›› ማለት ካልበዛ፣ ተሳፋሪው ያልደረሰን ተሳፋሪን ‹‹ውረድ›› ብሎ ካላደናበረ ሁሉም ከዳር በጋራ ለመድረስ ጉዞውን ቀጥሏል። እርግጥም ይህ ከሆነ መንገዱ ይሰምራል። አበቃሁ ቸር ይግጠመን።አዲስ ዘመን ታህሳስ 27/2012 ተገኝ ብሩ
https://www.press.et/Ama/?p=25216
655
1መዝናኛ
እንዲህ ቢባል ምን ችግር አለው?
መዝናኛ
January 5, 2020
37
በአውሮፓውቷ አገር ኖርዌይ ለትምህርት ከአንድ ዓመት በላይ ቆይቶ የመጣ አንድ ጓደኛዬ የነገረኝ ነገር ትዝ አለኝ፡፡ በነገራችን ላይ ውጭ አገር ቆይቶ የመጣ ሰው ሳገኝ ቀድሜ የምጠይቀው የህዝቡን ሥነ ልቦና ነው፡፡ እንዲያው ይሄ ርዕስ በርዕስ መነቋቆር የሰለጠኑት አገሮችም አለ ይሆን የሚለውን ለማወቅ ስለምፈልግ፡፡ እናም ይሄ ጓደኛዬ የነገረኝ ነገር በሀገረ ኖርዌይ ያስተዋለው ህዝቡ ሐሜትና መነቋቆር ጉዳዩ እንዳልሆነ ነው፡፡ አለ ከተባለም አድናቆት ነው፡፡ ከከንቲባው ጀምሮ በከተማዋ ውስጥ ያለ የትኛውም ባለሥልጣን ሲሰደብና ሲወቀስ አይወዱም፡፡ ለባለሥልጣኖቻቸው ትልቅ ክብር አላቸው፡፡ ይሄን ነገር በእኛ አገር ቢሆን ብየ አሰብኩት፡፡ አንድ ከሌላ አገር የመጣ ዜጋ ባለሥልጣኖቻችንን ሲያብጠለጥል ብንሰማው በደስታ የሚፍለቀለቀው አይበልጥም? እሰየው አብጠለጠለልን አንልም ነበር? መወቀስ ያለባቸው ቦታ ላይ መወቀስ የለባቸውም እያልኩ አይደለም፡፡ ችግሩ ግን ወቀሳችንም አድናቆታችንም ምክንያታዊ አይደለም፡፡ ሌላውን ሰው የሚያናድድ እየመሰለን ነው፡፡ከሰሞኑ ማህበራዊ ገጽ ላይ ከዳግማዊ አፄ ምኒልክ እስከ ዶክተር አብይ አህመድ ያሉ የአገሪቱን መሪዎች የሚያመሰግን አንድ ፎቶ አየሁ፡፡ ከእያንዳንዱ መሪ ፎቶ ሥር የሚያስመሰግናቸው ሥራ ተጽፏል፡፡ የፎቶው አቀማመጥ በሥልጣን ዘመናቸው ቅደም ተከተል ነው፡፡ በነገራችን ላይ ይሄ ነገር ብርቅ የሆነው ካለው ወቅታዊ ብሽሽቅ አንፃር እንጂ ብርቅ መሆን የነበረበት ሆኖ አይደለም፡፡ ግን ጠዋት ማታ የምናየው አንዱ ሌላውን ሲያጣጥል ነው፡፡ የሚያደንቅም የሚወቅሱትን ለማናደድ ነው፡፡ አንዱን መሪ ለማድነቅ ሌላውን ማጣጣልና መሳደብ ግዴታ መስሏል፡፡ ግን እንዲህ ሁሉንም በሥራቸው ማመስገንም ይቻል ነበር፡፡ ጥፋት ብቻ እናውራ ከተባለ በእያንዳንዱ መሪ ዘመን የተፈፀመ ብዙ ጥፋት አለ፡፡ ግን ምነው የሠሩትን ጥሩ ሥራስ ብናወራላቸው?እዚህ ፎቶ ላይ፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድን ‹‹ጠፈርን የደፈረ›› ይላል፡፡ በቅርቡ ኢትዮጵያ ሳተላይት አምጥቃለች፡፡ ሳተላይት ማለት የአንዲት አገር የብልጽና እና የሥልጣኔ ማሳያ ነው፡፡ የመዘመን ምልክት ነው። ኢትዮጵያ ደግሞ በኋላቀርነትና በድህነት ስሟ ሲጠራ የቆች አገር ናት፡፡ ስለዚህ የዚች አገር ስም በእንዲህ አይነት ነገር ሲጠራ ጀግንነት ነው፡፡በአቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ ፎቶ ሥር ‹‹ሥልጣኑን በሰላም የለቀቀ›› ይላል፡፡ እንደሚታወቀው የአፍሪካ አገራት ስማቸው ተደጋግሞ የሚጠራው በምርጫ ማጭበርበርና በ‹‹ሥልጣን አልለቅም!›› ጦርነት ነው፡፡ የአፍሪካ መሪዎች የሚታወቁት የሥልጣን ሽግግር በተደገረ ቁጥር አሻፈረኝ ሲሉና ግጭት ሲቀሰቀስ ነው፡፡ የራሷ የኢትዮጵያ የዘመናት ታሪክም ይሄው ነው፡፡ ሥርዓቶች ሁሉ የተቀያየሩት በጦርነት ነው፡፡ አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ ግን በራሳቸው ፈቃድ ሥልጣን ለቀቁ። አቶ ኃይለማርያምና ዶክተር አብይ ተቃቅፈው የኢትዮጵያን ሰንደቅ አላማ ተረካከቡ፡፡ ይሄ አቶ ኃይለማርያምን ጀግና ያሰኛቸዋል፡፡በአቶ መለስ ዜናዊ ፎቶ ሥር ‹‹ዓባይን የደፈረ›› ይላል። ለዘመናት የዘፈንና የፉከራ ምንጭ ሆኖ የኖረው ዓባይ የኃይል ምንጭ ሊሆን የመሰረተ ድንጋይ የተቀመጠለት በአቶ መለስ ዜናዊ ነው፡፡ በርሃብና በድህነት የምትታወቅ አገር ከዓለም ግዙፍ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች አንዱ የሆነውን የህዳሴ ግድብ ጀመረች፡፡ ኢትዮጵያዊ የአገር ፍቅር ታየበት። የማይደፈር የመሰለውን ዓባይ መገደብ ተጀመረ፡፡ ይሄ አቶ መለስ ዜናዊን ጀግንነት የሚያሰኝ ነው፡፡ በኮሎኔል መንግሥቱ ኃይለማርያም ፎቶ ሥር ‹‹የሀገርን ዳር ድንበር ያስጠበቀ›› ይላል፡፡ የደርግ ዘመነ መንግሥት ስሙ የሚነሳው በጨቋኝነቱና በጨፍጫፊነቱ ነው፡፡ በዚህ ሁሉ ውስጥ ግን የኮሎኔል መንግሥቱ ኃይለማርያምን የሀገር ፍቅር ብዙዎች የመሰከሩት ነው፡፡ የደርግ ሥርዓትን ታግሎ ያሸነፈው ኢህአዴግ መሪ የሆኑት ራሳቸው አቶ መለስ ዜናዊ ኮሎኔል መንግሥቱ ኃይለማርያምን ‹‹በሀገሩ ጉዳይ አይደራደርም›› ብለው ነበር፡፡ ደርግ በዘመኑ የነበሩ ወረራዎችን ተቋቁሞ የአገሩን ዳር ድንበር አስጠብቋል፡፡ ይሄም ኮሎኔል መንግሥቱ ኃይለማርያምን ጀግና ያሰኛቸዋል፡፡ በዳግማዊ አፄ ምኒልክ ፎቶ ሥር ‹‹ጣሊያንን የደፈረ›› ይላል፡፡ አንዲት አፍሪካዊት አገር አንዲት አውሮፓዊትን አገር ትደፍራለች ብሎ የማይታሰብበት ዘመን ነበር፡፡ የአውሮፓ ኃያልን ማን አለብኝ ብለው የአፍሪካ አገራትን ልክ እንደ ሸቀጥ መከፋፈል ጀመሩ፡፡ ኢትዮጵያ ላይ ሲደርሱ ግን አልተሳካም። ኃያልን አገራት ያልጠበቁት ሽንፈት አጋጠማቸው፡፡ ነጭ በጥቁር ተሸነፈ፡፡ ታሪክ ተቀየረ፡፡ የአፍሪካ ጥቁር ህዝቦች ‹‹ለካ ነጭን ማሸነፍ ይቻላል›› አሉ፡፡ እነሆ ኢትዮጵያን አይተው የአፍሪካ አገራትም ነፃ ወጡ፡፡ ይሄ ዳግማዊ አፄ ምኒልክን ጀግና ያሰኛል፡፡አንድ ነገር ልብ ይባልልኝ፡፡ የተጠቀሰው ጀግንነታቸው ይሄ ብቻ ሆኖ አይደለም፡፡ በፎቶ ተቀነባብሮ ያየሁትን መነሻ አድርጌ ስለሆነ እንጂ፡፡ ማህበራዊ ገፆች ላይ እንዲህም ማመስገንና ማድነቅ ይቻላል የሚለውን ለማሳየት እንጂ የመሪዎች ሥራ ይሄ ብቻ ሆኖ አይደለም፡፡ በሌላ በኩል ይሄኛው ሥራቸው ነው መቅደም ያለበት የሚል ሐሳብም ሊነሳ ይችላል፡፡ ግን እንዳልኩት ነው፡፡ መነሻዬ ፎቶው ላይ ያየሁት ነው፡፡ ያደረገው አንድ ግለሰብ ሊሆን ይችላል፤ በፓርላማ የፀደቀ ወይም የምሁራን ውይይት የተደረገበት አይደለም፡፡ እንደ ምሳሌ ነው የተነሳ፡፡ ጀግና የሚያሰኙ ሥራዎች አሏቸው ለማለት ነው፡፡ የጀግና ችግር የለብንም፡፡ ያለብን የራስን የሆነ ነገር የማክበር ችግር ነው፡፡ የመሪዎቻችን፣ የሳይንቲስቶቻችን፣ የአርቲስቶቻችን ጀግንነት የሚታየን ፈረንጅ ሲሸልማቸው ነው፡፡ የመሪዎቻችን ነገር ጭፍን የፖለቲካ አስተሳሰብ ስለተጫነው የክርክርና የጭቅጭቅ ምክንያት ሆኗል፡፡ የሚያሳዝነው እኮ ደግሞ የዋናዎቹ የመገናኛ ብዙኃንም አጀንዳ ይሄው መሆኑ ነው፡፡ የሚያሳዝነው እኮ ትልልቅ ሰዎች ራሱ አጀንዳቸው ይሄው መሆኑ ነው፡፡ የማህበራዊ ገፆች ብቻ ቢሆን እኮ ቀላል ነበር፡፡ የተራ ሰዎች ብቻ ቢሆን እኮ ይሻል ነበር። ትልልቅ የሚባሉ ሰዎች ራሱ ንግግር የሚያደርጉት አንዱን ለማመስገን አንዱን በመሳደብ ነው፡፡ አቶ ዕገሌን ለማመስገን የግድ አፄ ዕገሌ መሰደብ አለበት፡፡ አፄ ዕገሌን ለማድነቅ የግድ አቶ ዕገሌ መሰደብ አለበት፡፡ ይሄው ነው የፖለቲከኞቻችንም ሆነ የምሁራኖቻችን ትንታኔ፡፡ እስኪ ማድነቅና ማመስገንንም እንልመድ! አፄ ዕገሌን ሳንሳደብ አቶ ዕገሌን ማድነቅ ወይም አቶ ዕገሌን ሳንሳደብ አፄ ዕገሌን ማድነቅ እንቻል! መልካም በዓል፡፡አዲስ ዘመን ታህሳስ 26/2012ዋለልኝ አየለ
https://www.press.et/Ama/?p=25183
691
1መዝናኛ
ኢትዮጵያ በአፍሪካ መድረክ ተሳታፊ ክለብ የሌላት ብቸኛ አገር ሆናለች
ስፖርት
June 18, 2020
20
የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ 19) ወረርሽኝ እንደሌሎቹ ማህበራዊ፣ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ኩነቶች ሁሉ የዓለምን ስፖርት ውጥንቅጡን አውጥቶታል፡፡ ታላላቅ የዓለማችን ሊጎች የሚይዙትን የሚጨብጡትን አጥተው ከርመዋል፡፡ ከሳምንት በፊት አንስቶ ግን የዓለማችን ታላላቅ ሊጎች ወደ ውድድር እየተመለሱ ስፖርቱም እያገገመ ይመስላል፡፡ ወትሮውንም ችግር የማያጣት አፍሪካ የዚህ ችግር ገፈት ቀማሽ መሆኗ ነገሩን በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ እንደሚያደርግባት ቀድሞም የተገመተ ቢሆንም የአንዳንድ አገራት የእግር ኳስ መሪዎች አስቸጋሪውን ወቅት በብልሃትና በበሰለ አመራር ሰጪነት ለመሻገር ጥረት ማድረጋቸው አልቀረም፡፡ የቡርኪናፋሶ እግር ኳስ ተሞክሮም ለዚህ ጥሩ ምሳሌ መሆኑን መመልከት ይቻላል፡፡ ቡርኪናፋሶ እንደሌሎቹ የዓለማችንም ይሁን የአፍሪካ አገራት ሰሞንኛ ማህበራዊ ሁኔታዋ ጤነኛ አልነበረም። አፍሪካ ውስጥ በከፍተኛ ሁኔታ የኮሮና ቫይረስ ያጠቃቸው ፖለቲከኞች ተመዝግበውባታል። የቡርኪናፋሶ መንግሥት ይህ ቫይረስ ተስፋፍቶባቸዋል ብሎ ካወጀባቸው ቦታዎች መካከል የስፖርት ማዘውተሪያ ቦታዎች ይገኙበታል፡፡ ጅምናዚየም ፣ የኳስ መጫወቻ ሜዳዎች ለዚህ ተጠቃሽ ከሚባሉት ቦታዎች ውስጥ ይገኛሉ። ስለዚህ ይህንን አደጋ ለመቀነስ እና ለማህበረሰቡ ዋስትና ለመስጠት ሊጉን ሰርዞ የተለያዩ ውሳኔዎችን አሳልፏል፡፡ የዘንድሮው የውድድር ዓመት እንደማ ይጠናቀቅ እና በዚሁ ውጤት እንደሚያልቅ፣ ሁሉም ክለቦች በውል ውስጥ የሚገኙ ተጫዋቾቻቸውን ውል እንዲያከብሩላቸው እና እስከውል ማለቂያው ድረስ ደመወዝ እንዲከፍሉ፣ ማንኛውም ክለብ ያለምንም በቂ ምክንያት ምንም አይነት የክለብ አባላት ቅነሳ እንዳያደርግ፣ የትኛውም ተጫዋች ተበደልኩ ቢል ለፌዴሬሽኑ ፅህፈት ቤት እንዲያመለክት፣ ከሁሉም በላይ በዘንድሮ 2019 የውድድር ዘመን በኢንተርናሽናል መድረክ አገሪቱን የወከሉት ቡድኖች ማለትም (ራሂሞ ኤፍ ሲ) እና (ሳሊታስ) የተባለው ክለብ በክለቦች ኮንፌዴሬሽን ጨዋታ በሚመጣው ዓመት አገሪቱን እንዲወክሉ አድርጓል። ይህንን ያደረገውም የዘንድሮ ልፋታቸው ሽልማት እንኳን ቢሆን ብሎ በማሰብ ነው ። አሱማ ሲሪማ የቡርኪናፋሶ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ናቸው፡፡ ይህንን ውሳኔ ሲወስኑ ሁሉንም እንደሚያስማማ በማሰብ መሆኑን ተናግረዋል:: ቡርኪናፋሶን የወከሏት ቡድኖች የተገኙት አምና ባስመዘገቡት ውጤት ነው ። ይህ አንዳንዴ የተቀመጠን ህግ እና አሰራር ወቅቱ በሚፈቅደው ነገር እንደሚጠመዘዝ ማሳያ ነው ። የኢትዮጵያ ሊግ ካምፓኒ ምንም አይነት ቡድን ኢትዮጵያን በኢንተርናሽናል ውድድር አይወክልም የሚል ውሳኔ ከወር በፊት አስተላልፏል። ይህ እንደ አገር በድጋሚ ሊጤን የሚገባው ውሳኔ እንደሆነ በርካቶች አስተያየት ሰጥተውበታል፡፡ ውሳኔው ስህተት መሆኑን ወሳኞቹ አካላት ቢያምኑም የተወሰደ ርምጃ የለም፡፡ ይህንንም ተከትሎ ኢትዮጵያ በአፍሪካ መድረክ ተሳታፊ ክለብ የሌላት ብቸኛ አገር ሆናለች፡፡ የደቡብ አፍሪካው ሱፐር ስፖርት ከቀናት በፊት ‹‹ኮሮና እና የአፍሪካ ሊጎች›› በሚለው ሰፊ ዘገባው በኮሮና ወረርሽኝ ምክንያት ከሶስት ወራት በላይ ተቋርጦ የነበረውን የአፍሪካ አገሮች ወረርሽኙ ባይጠፋም የሊግ ውድድሮች ቀስ በቀስ ከተቋረጠበት እያስጀመሩ እንደሆነ አስነብቧል። ሱፐር ስፖርት በሰፊ ዘገባው አያይዞም ኢትዮጵያ ከሌሎች አገሮች በተለየ መልኩ ሊጓን ሙሉ ለሙሉ መሠረዟን እና በሯን መዝጋቷን አስነብቧል። በዚህም ኢትዮጵያ በቀጣይ ዓመት ክለቦቿ በአፍሪካ ውድድር ባለመሣተፍ ብቸኛዋ አገር መሆኗ ተረጋግጧል:: በኢንተርናሽናል ውድድሮች ኢትዮጵያን ወክለው የሚሳተፉት ቡድኖች ከየትም ወገን ይምጡ የሚወክሉት ሊጉን ነው ። ሊጉ ደግሞ በድግግሞሽ በየዓመቱ ኢትዮጵያን በጥራት የሚወክሉ ቡድኖችን ይፈልጋል። ይህንን ጥራት ለማምጣት ደግሞ የቡድኖችን የኢንተርናሽናል ተሳትፎ መንገድ መቁረጥ ሌላ ፈተና ይዞ እንደሚመጣ ሳይታለም የተፈታ ነው፡፡ ይህን መቁረጥ በአንድ ዓመት የኢንተርናሽናል ልምድ በጥሩ ብቃት ላይ የሚገኝን ተጫዋች ራሱን የማሳየት ተስፍ ማጨለሙ አይቀርም፡፡ የክለቦችን የአስተዳደራዊ ዝግጅት ደረጃ ከፍ የማድረግ ልምድ ማሳነስም ሌላኛው ኪሳራ ነው፡፡ እንደ ላይቤሪያ፣ ደቡብ ሱዳን እና ቡርኪናፋሶ ያሉ የአፍሪካ አገራት የዘንድሮ ፕሪሚየር ሊግ ውድድራቸውን ቢያቋርጡም በአፍሪካ ውድድሮች ላይ የሚወክሏቸው ክለቦች አሏቸው። በዚሁ ወረርሽኝ ሳቢያ ከአፍሪካ ክፉኛ ተጎጂ የሆነችው ግብፅም ብትሆን ሊጓን ሙሉ በሙሉ ለመዝጋት አልተጣደፈችም፡፡ እንዲያውም ከትናንት በስቲያ የአገሪቱ ስፖርት ሚኒስትር አሽራፍ ሶቢሂ ሁሉም የእግር ኳስ ክለቦች ከአንድ ሳምንት በኋላ ልምምድ እንዲጀምሩ ማሳሰባቸው እየተዘገበ ይገኛል፡፡ አዲስ ዘመን ሰኔ 11/2012ቦጋለ አበበ
https://www.press.et/Ama/?p=34598
485
2ስፖርት
የለንደን ማራቶን ሊሰረዝ ይችላል
ስፖርት
June 18, 2020
17
በቀጣዩ መስከረም ሊካሄድ ቀጠሮ የተያዘለት ‹‹የግሬት ኖርዝ ረን›› ግማሽ ማራቶን ውድድር መሰረዙን ተከትሎ ጥቅምት ላይ እንደሚካሄድ የተነገረው የለንደን ማራቶንም ሊሰረዝ እንደሚችል ጥርጣሬ ፈጥሯል:: በእንግሊዝ አገር ከሚካሄዱ የጎዳና ላይ ውድድሮች መካከል ትልቁን ስፍራ የሚይዙት ሁለቱ የማራቶንና ግማሽ ማራቶን ውድድሮች ከኮሮና ቫይረስ(ኮቪድ 19) ወረርሽኝ ስጋት ጋር በተያያዘ ቀደም ብሎ ከሚካሄዱበት ወቅት እንዲራዘሙ ተደርጎ በቀጣዩ መስከረምና ጥቅምት ወር ሊካሄዱ ቀጠሮ ተይዞ ነበር፡፡ ዘንድሮ አርባኛ ዓመቱን የያዘው ‹‹ግሬት ኖርዝ ረን›› የግማሽ ማራቶን ውድድር ከመሰረዙ አስቀድሞ በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ስልሳ ሺ ተሳታፊዎችን በመያዝ በብሪታኒያ ትልቁ የጎዳና ላይ ውድድር መሆን ችሏል፡፡ ከሰላሳ አንድ ሚሊዮን ዶላር በላይ ከውድድሩ በመሰብሰብ ለበጎ አድራጎት እንዲውል ለማድረግ ታስቦ የነበረ ቢሆንም በኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ሳቢያ እንዳልተቻለ አዘጋጆቹ ገልፀዋል፡፡ ይህንንም ተከትሎ ውድድሩ ሊሰረዝ እንደቻለ የሮይተርስ ዘገባ ያመለክታል:: ውድድሩ ለኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ የሚደረገውን ጥንቃቄ ከግምት በማስገባት እንዲካሄድ አዘጋጆቹ ከጤና ባለሙያዎች እንዲሁም ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ተቀናጅተው በመስራት ጥረት ቢያደርጉም እንዳልተሳካ አሳውቀዋል፡፡ በዚህ ታላቅ ውድድር ባለፈው ዓመት እንግሊዛዊው የኦሊምፒክ ጥምር የወርቅ ሜዳሊያ ባለቤት የሆነው አትሌት ሞሐመድ ፋራህ ለስድስተኛ ተከታታይ ጊዜ ሲያሸንፍ ኬንያዊቷ የማራቶን ባለክብረወሰን ብሪጊድ ኮስጌ የውድድሩን ክብረወሰን በማሻሻል ጭምር ማሸነፏ ይታወሳል፡፡ ይህ የግማሽ ማራቶን ውድድር መሰረዙን ተከትሎ ጥቅምት ላይ ሊካሄድ የታሰበው ትልቁ የለንደን ማራቶንም ሊሰረዝ እንደሚችል ተገምቷል፡፡ የለንደን ማራቶን እንደወትሮው ቢሆን ባሳለፍነው ሚያዚያ ላይ የዓለማችን የርቀቱ ኮከቦችን ያፋልም ነበር፡፡ በተለይም በወንዶች የማራቶን ባለክብረወሰኑ ኬንያዊው ኢሉድ ኪፕቾጌና የርቀቱ ሁለተኛው ፈጣን አትሌት ቀነኒሳ በቀለ በዚህ ውድድር የሚያደርጉት ፉክክር በብዙዎች ዘንድ በጉጉት ሲጠበቅ ነበር፡፡ ውድድሩ መሰረዝ አለመሰረዙን ግን አዘጋጆቹ የገለፁት ነገር የለም፡፡ በርካታ የማራቶን የዓለም ክብረወሰኖች የሚ ሻሻሉበት የበርሊን ማራቶን በዚህ ዓመት የመሰረዝ ወይም የመራዘም እድል ያልገጠመው ብቸኛው ውድድር ነው ማለት ይቻላል፡፡ ይህ ታላቅ የማራቶን ውድድር የኮሮና ቫይረስ በዓለም ላይ ከመከሰቱና ከመስፋፋቱ አስቀድሞ መስከረም ወር ላይ በመካሄዱ የሌሎቹ ታላቅ ውድድሮች እጣ ፋንታ ሳይገጥመው ቀርቷል፡፡ ያም ሆኖ የኮሮና ቫይረስ ስርጭት እስካሁን የሚያቆመው ባለመኖሩና ወደ ፊትም መፍትሄ ማግኘቱ አጠራጣሪ እየሆነ በመምጣቱ በቀጣዩ መስከረም የበርሊን ማራቶን የመካሄዱ ጉዳይ አጠራጣሪ ሆኗል፡፡ የውድድሩ አዘጋጆች ባለፈው ወር እንደጠቆሙትም፣ ውድድሩን በተለመደው ወቅት ለማካሄድ እስካሁን ውሳኔ ላይ መድረስ አልቻሉም፡፡ ውድድሩን ለማካሄድ ወይም ለማራዘም ውይይት እየተደረገ ሲሆን ውሳኔ ላይ ለመድረስ ጊዜ እንደሚያስፈልጋቸው አሳውቀዋል፡፡ የጀርመን መንግስት በኮሮና ቫይረስ ስጋት እስከ መጪው ጥቅምት ወር መጨረሻ ከአምስት ሺ ሰው በላይ የሚሰበሰብባቸው ማንኛቸውም መርሐግብሮች ማገዱን ተከትሎ የውድድሩ አዘጋጆች ውሳኔ ላይ ለመድረስ እንደተቸገሩ ጠቁመዋል፡፡ እንደ በርሊን ማራቶን ሁሉ ዋነኞቹ የዓለማችን የማራቶን ውድድሮች ከሆኑት አንዱ የቦስተን ማራቶንም በተመሳሳይ ምክንያት መካሄድ ከነበረበት ወቅት የመራዘም እድል እንደገጠመው ይታወሳል፡፡የበርሊን ማራቶን አዘጋጆች ውድድሩ ካለው ስፋትና ከሚያሳትፈው የሰው ብዛት አኳያ የሚካሄድበት እድል መኖር አለመኖሩን በማጥናት ላይ የሚገኙ ሲሆን ውሳኔ ላይ ለመድረስም የተወሰነ ጊዜ እንደሚያስፈልጋቸው አሳውቀዋል፡፡ ለዚህም የውድድሩ አዘጋጆች አሁን ላይ በቫይረሱ ስጋት የተነሳ በሙሉ ኃይላቸው ተገናኝተው መስራት አለመቻላቸው አንዱ እንቅፋት መሆኑን ገልፀዋል፡፡ በርካታ የዓለም ክብረወሰኖች የሚመዘገቡበት የበርሊን ማራቶን 2018 ላይ ኬንያዊው ኢሉድ ኪፕቾጌ 2፡1፡39 የሆነ አዲስ የዓለም ክብረወሰን በርቀቱ እንዳስመዘገበበት ይታወሳል፡፡ ባለፈው መስከረም ደግሞ ቀነኒሳ በቀለ ይህን ክብረወሰን ለማሻሻል በሁለት ሰከንድ የዘገየ ሰዓት ማስመዝገቡ አይዘነጋም፡፡ አዲስ ዘመን ሰኔ 11/2012 ቦጋለ አበበ
https://www.press.et/Ama/?p=34601
443
2ስፖርት
በ «አረንጓዴ አሻራ» መርሃ ግብሩ የስፖርት ቤተሰቡ አሻራ
ስፖርት
June 19, 2020
26
በኢትዮጵያ የደን ልማት ለማጎልበት የሚያስችለው የዘንድሮ «አረንጓዴ አሻራ» መርሃ ግብር ግንቦት 30 ቀን 2012 ዓ.ም በይፋ መጀመሩ ይታወሳል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ መርሃ ግብሩን ሲያስጀምሩ፤ በዘንድሮ ዓመት የችግኝ ተከላ መርሐ ግብር አምስት ቢሊዮን ችግኞችን ለመትከል እቅድ መያዙን ተናግረዋል። ሁሉም ኢትዮጵያዊ ችግኞችን እንዲተክል «አሻራችንን በማኖር ለኢትዮጵያ አረንጓዴ ምንጣፍ እንዘርጋ» ሲሉ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ ችግኝ ተከላ መርሐ ግብርን አስጀምረዋል። የጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርን ጥሪ መሰረት በማድረግ በዘጠኙም ክልሎችና በሁለቱም ከተማ አስተዳደሮች የሚገኙ ተቋማት፣ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ጥሪውን በመቀበል አረንጓዴ አሻራቸውን በማሳረፍ ላይ ይገኛሉ። የ2012ዓ.ም አረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርን ተግባራዊ ካደረጉት ተቋማት መካከል ደግሞ የአዲስ አበባ ስፖርት ኮሚሽን በግንባር ቀደምነት ይጠቀሳል። በ2012 ዓ.ም የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብሩ 156 ሺህ ችግኞች በመትከል ለሀገር አቀፍ ስኬቱ የበኩሉን ሚና ለመወጣት እቅድ ይዞ ሲንቀሳቀስ ነበር የቆየው። በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የበጀት ዓመቱን መርሃ ግብር በቅርቡ ማስጀመራቸውን ተከትሎ ፤ ኮሚሽኑ የስፖርት ቤተሰቡንና ማህበረሰቡን የሚያሳትፈውን መርሃ ግብር ሰኔ 10 ቀን 2012 ዓ.ም በይፋ አስጀምሯል። መርሃ ግብሩም «ለስፖርት ልማት አረንጓዴ አሻራችንን እናስቀምጥ» በሚል መሪ ቃል በይፋ ተጀምሯል። ለአረንጓዴ ልማቱ አሻራ የስፖርት ቤተሰቡ አሻራ ለማሳረፍ እድል የሚከፍተው መርሃ ግብሩ በቦሌ ክፍለ ከተማ ሰሚት ኮንደሚኒየም ሁለተኛ በር በሚገኘው የስፖርት ማዘወተሪያ ስፍራ በታላቅ ድምቀት ሊጀመር። በመርሃ ግብሩ ማስጀመሪያ ላይም የአዲስ አበባ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ኢንጂነር ታከለ ኡማ፣ የኢትዮጵያን ባንዲራ በዓለም አቀፍ መድረክ ከፍ እንዲል ያደረጉ አትሌቶች፣ የእግር ኳስ ብሔራዊ ቡድን ተጫዋቾች፣ አሰልጣኞችና ደጋፊዎች ተገኝተዋል። በአዲስ አበባ ስፖርት ኮሚሽን አስተባባሪነት የተሰናዳውን አረንጓዴ አሻራን የማሳረፍ ትግበራው ከሰሚት ኮንዶሚኒየም የተነሳው የተከላ መርሃ ግብሩ በመቀጠል በሌሎች የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች የችግኝ ተከላ መርሃ ግብሩ ተከናውኗል። ኢንጂነር ታከለ ኡማን ጨምሮ በርካታ የስፖርት ቤተሰቦችን በማካተት የኮረና ቫይረስ ተጋላጭነት በማይኖረው መልኩ እንዲሁም ጥንቃቄ በታከለበት ሁኔታ ችግኝ በመትከል ለስፖርቱ ልማት አረንጓዴ አሻራቸውን አሳርፈዋል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዮናስ አረጋይ በመርሃ ግብሩ ማስጀመሪያ ሥነ ሥርዓት ወቅት ፤ ለስፖርተኛውና ለስፖርት ቤተሰቡ የሚያስፈልገው ንፁህ አየርና ጤናማ ለመሆን ችግኝ መትከል አስፈላጊ መሆኑን ተናግረዋል። «የስፖርት ማዘውተሪያዎች በኮንክሪት ብቻ ሳይሆን በአረንጓዴ ተክሎችም መዋብ አለባቸው። ስለዚህ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብሩን በቀሪ ወራትም አጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን አስገንዝበዋል። «በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብሩ በከተማዋ በሚገኙ የስፖርት ማዘውተሪያዎች ከአንድ ሚሊዮን በላይ ችግኞችን ለመትከል ዕቅድ ተይዞ ወደ ተግባር ተገብቷል። በዚህ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር 34 የስፖርት ፌዴሬሽኖች የሚሳተፉ ይሆናል» ብለዋል። በከተማዋ የስፖርት እንቅስቃሴው ላይ ተጨባጭ ለውጥና ውጤት በአጭር ጊዜ ውስጥ እየተመዘገበ መሆኑን አክለው የገለጹት አቶ ዮናስ ፤ ለዚህም ስኬታማ ስራዎችን ማከናወን መቻሉን ተከትሎ እንደሆነ ገልጸዋል። ለስፖርቱ ስኬታማነት የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ ኢንጂነር ታከለ ኡማ አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑንና የሚሰሩትን ስራ በአብሮነት በመሆን ሲደክሙ እንደነበር ገልጸዋል። ኢንጂነር ታከለ ኡማ ለመዲናዋ ስፖርት እድገት መነቃቃት እንዲሁም በአረንጓዴ አሻራው መርሃ ግብር ላይ አሻራቸውን በማሳረፍ ላበረከቱትና ወደፊትም ለሚያበ ረክቱት የመሪነት ሚና አመስግነዋል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ኢንጂነር ታከለ ኡማ በበኩላቸው፤ ስፖርት እና አረንጓዴ ቦታ እንደማይነጣጠሉ ተናግረዋል። ይህን በመገንዘብ በዚህ አስቸጋሪ ወቅት ችግኝ በመትከል አረንጓዴ አሻራቸውን ለማኖር የተገኙ ስፖርተኞችን አመስግነዋል። «በአረንጓዴ አሻራ ላይ የስፖርት ቤተሰቡ ችግኝ በመትከል በመንከባከብና በማሳደግ ከተማችንን ማስዋብ ፣ ማሳመርና ንፁህ አየር በማግኘት ውጤታማ ስፖርተኛ እንዲሆኑ መትጋት ይኖርባቸዋል» ብለዋል። የስፖርት ቤተሰቡና ማህበረሰቡ በከተማዋ ሁለንተናዊ ለውጥ ላይ እያደረጉት ያለውን አስተዋፅኦ እና ርብርብ አጠናክረው እንዲቀጥሉም ኢንጂነር ታከለ ለስፖርት ቤተሰቡና ማህበረሰቡ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል። በተጨማሪም በመርሃ ግብሩ ለይ የተገኙት የኢትዮጵያ ቡናና ቅዱስ ጊዮርጊስ ክለብ ተወካዮች አዲስ አበባን አረንጓዴ ለማ ድረግ በሚደረጉ እንቅስቃሴዎች በቀዳሚነት እንደሚሰለፉ ተናግረዋል። በተመሳሳይ አረንጓዴ አካባቢ ከአትሌቶች የሥልጠና ቦታ ጋር የተቆራኘ በመሆኑ በዛሬው ዕለት አረንጓዴ አሻራቸውን በማኖራቸው ደስተኛ መሆናቸውን አትሌት ገንዘቤ ዲባባና አትሌት ጌጤ ዋሚ የገለጹ ሲሆን ፤ ችግኝ ከመትከል ባለፈ ተገቢ እንክብካቤ ማድረግ እንደሚገባም አመልክተዋል። አዲስ ዘመን ሰኔ 12/2012ዳንኤል ዘነበ
https://www.press.et/Ama/?p=34666
545
2ስፖርት
ላሚን ዲያክ የአራት ዓመት እስር እንዲፈረድባቸው ተጠየቀ
ስፖርት
June 20, 2020
18
በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው ፓሪስ ውስጥ በቁም እስር ላይ የሚገኙት የቀድሞው የዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር ፕሬዚዳንት ላሚን ዲያክ አራት ዓመት የእስር ቅጣት እንዲተላለፍባቸው ተጠየቀ፡፡ የሰማንያ ሰባት ዓመቱ አዛውንት ላይ ክስ የመሰረቱት የፈረንሳይ አቃቤ የላሚን ዲያክ ልጅ በሆኑት ፓፓ ማሳታ ዲያክ እንዲሁም የዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር የቀድሞ የማርኬቲንግ አማካሪ ላይ የአምስት ዓመት እስርና የአምስት መቶ ሺ ፓውንድ ቅጣት እንዲተላለፍባቸው ለፍርድ ቤት ጥያቄ እንዳቀረቡ ሮይተርስ ትናንት ዘግቧል፡፡ አዛውንቱ ላሚን ዲያክ እድሜያቸው መግፋቱን ተከትሎ የእስር ቅጣት ከተላለፈባቸው ሕይወታቸው በወሕኒ ቤት ሊያልፍ እንደሚችል በመጠቆም ጠበቆቻቸው ፍርዱ እንዲቀል መጠየቃቸው ታውቋል፡፡ የመጨረሻው የፍርድ ሂደት ላይ የተሰየመው የፈረንሳይ ፍርድ ቤት ውሳኔ ለማስተላለፍም ለመጪው መስከረም ቀጠሮ ይዟል፡፡ እኤአ ከ1999 እስከ 2015 የዓለም አቀፉን አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር የመሩት ላሚን ዲያክ መንበረ ስልጣናቸውን ባስረከቡ ማግስት በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው በሰማንያ ስድስት ዓመታቸው ነበር ወደ ፓሪስ ባቀኑበት ወቅት በቁጥጥር ስር የዋሉት፡፡ የሃምሳ አራት ዓመቱ ልጃቸው ፓፓ ማሳታም ዓለም አቀፍ ማህበሩን ተገን አድርጎ ህገ ወጥ ገንዘብ ህጋዊ በማድረግና ስልጣናቸውን አላግባብ በመጠቀም እንዲሁም በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው አባት ወህኒ ሲወርዱ ልጅየው ወደ ትውልድ አገሩ ሴኔጋል ተመልሶ የፍርድ ሂደቱን ባለበት እንዲከታተል የተደረገው፡፡ ይሁን እንጂ ፓፓ ማሳታ በመጨረሻው የፍርድ ቤት ውሎ ችሎት ሳይቀርብ ቀርቷል፡፡ ይህም ላሚን ዲያክን እንዳስቆጣ ተዘግቧል፡፡ አባትና ልጅ ቀደም ሲል ከተጠረጠሩበት ወንጀል በተጨማሪ የሩሲያውያን አትሌቶችን የአበረታች ንጥረ ነገር ምርመራ ውጤት በማሸሽ የተጠረጠሩ ሲሆን ጠበቆቻቸው ወደ አገራቸው ሴኔጋል ተመልሰው የክስ ሂደቱን እንዲከታተሉ ያቀረቡት ጥያቄ በፈረንሳይ ፍርድ ቤት ውድቅ ተደርጎ እንደነበር ይታወሳል፡፡ ፓፓ ማሳታ፣ የቀድሞው የሩሲያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ቫሌንቲን ባላክኒቼቭ እንዲሁም የቀድሞ የሩሲያ አትሌቲክስ አሰልጣኝ አሌክሲ ሜልኒኮቭ እኤአ 2016 ላይ በዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር ከስፖርቱ እድሜ ልክ እንዲርቁ ማገዱ ይታወሳል፡፡ ቫሌንቲን ባላክኒቼቭና አሰልጣኝ አሌክሲ ሜልኒኮቭ በዚሁ የክስ ሂደት ውስጥ ጉዳያቸው እየታየ ቢሆንም የፈረንሳይ መንግስት ለረጅም ጊዜ በያዘው ምርመራ ለፍርድ ለመቅረብ ፍቃደኛ ሳይሆኑ ቀርተዋል፡፡ በክስ ሂደቱ ከአዛውንቱ ዲያክ በተጨማሪ አማካሪያቸው የነበሩት ሃቢብ ሲሴና የቀድሞው የዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር የአሁኑ (የዓለም አትሌቲክስ) ፀረ አበረታች መድሃኒት ጉዳዮች መሪ የነበሩት ገብርኤል ዶል ጉዳይ እየታየ ይገኛል፡፡ ዲያክ በተጠረጠሩበት ወንጀል ጥፋተኛ ሆነው ከተገኙ እስከ አስር ዓመት የሚዘልቅ እስር ሊፈረድባቸው እንደሚችልና ቀሪ የእድሜ ዘመናቸውን ወሕኒ ሊያሳልፉ እንደሚችሉ መረጃዎች ወጥተዋል፡፡ የፈረንሳይ የፋይናንስ አቃቤ ህግ ቢሮ እኤአ 2018 ላይ እንዳሳወቀው ዲያክ ስፖርትን ተገን አድርገው በሴኔጋል ለፖለቲካ ቅስቀሳ የሚውል ገንዘብ ከሩሲያ መንግስት ተቀብለዋል፡፡ ለዚህም የሩሲያውያን አትሌቶችን የአበረታች ንጥረ ነገር ምርመራ ውጤት በመሸሸግ ተደራድረዋል፡፡ በዚህ ድርድር ወቅትም ዲያክ ሞስኮ ካስተናገደችው የ2013 የዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮና ቀደም ብለው ውድድሩን ከሚያሰራጩ የቴሌቪዥን ጣቢያዎችና ስፖንሰሮች ጋር በገንዘብ ተደራድረዋል፡፡ አዲስ ዘመን ሰኔ 13/2012ቦጋለ አበበ
https://www.press.et/Ama/?p=34738
376
2ስፖርት