headline
stringlengths
2
1.42k
category
stringclasses
6 values
date
stringlengths
9
35
views
stringlengths
1
7
article
stringlengths
63
36.2k
link
stringlengths
28
740
word_len
int64
16
6.74k
label
class label
6 classes
ሰብዓዊነትን የታጠቀው የአዲስ አበባ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ሀሳብ
ስፖርት
June 19, 2020
13
ስፖርት ሰላም፣ ፍቅር፣ የአብ ሮነትና የአንድነት፣ የመተሳ ሰብ፣ የወንድማማችነት ልዩ መገለጫ ነው። ስፖርት ዘር፣ ሃይማኖት፣ ፆታና ቀለምን አይለይም። በየት ኛውም ሁኔታ ውስጥ የስፖርታዊ እንቅስቃሴ አስኳል ሃሳብ ወዳጅነትና መተሳሰብ መሆኑ ይታወቃል። በታሪክ ገጾች እንደሰፈረውም በሰው ልጅ ታሪክ ባጋጠሙ በጎም ሆኑ መጥፎ ክስተቶች ስፖርት በአጋርነት ተሳትፏል። ስፖርታዊ ክንዋኔዎች ሰላምንና አንድነትን የሚሰብኩ እንደመሆናቸው በማህበራዊ፣ ፖለቲ ካዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች በመግባት ሚናቸውን ሲወጡም ኖረዋል። ስፖርት ሰብዓዊነትን ያነገበ የልግስና ማዕድ መሆኑን ዘመነ ኮሮና በተጨባጭ አሳይቶናል። የቫይረሱ ስጋትነት በዓለም አቀፉ የጤና ተቋም ከተረጋገጠበት ጊዜ ጀምሮ፤ ውድድሮችን ከማቋረጥና ከመሰረዝ ባለፈ የስፖርቱ ተዋንያን በተናጠልም ሆነ በተቋማዊ ደረጃ አበርክቷቸውን ሲወጡ ታዝበናል።በስፖርቱ ዘርፍ ዓለም አቀፍ ዝናን ካተረፉ ግለሰቦች እስከ ዓለም አቀፍ ተቋማት ድረስ ወረርሽኙን ለመመከት እየተደረገ ባለው ርብርብ ከተሳትፎ አልጎደሉም።በተለያዩ ሀገራት ዓለም አቀፉን ወረርሽኝ ለመዋጋት በስፖርቱ ማኅበረሰብ ዘንድ የታየው ተሳትፎ በሀገራችንም ተመሳሳይ ሲሆን ታዝበናል። በኢትዮጵያ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ መከሰት ይፋ ከተደረገበት ከወርሃ መጋቢት መጀመሪያ አንስቶ የስፖርቱ ማህበረሰብ ድርሻ ግዙፍ ነው።በስፖርት ዘርፍ የሚገኙ የመንግሥትና የግል ተቋማት፣ የስፖርት ማህበራት፣ ተጫዋቾች፣ አትሌቶች፣ የእግር ኳስ ክለቦችና ተጫዋቾች ወረርሽኙን ለመከላከል የሚደረገውን ርብርብ ተሳትፎ ሲያደርጉ ነበር።በስፖርት ማህበረሰቡ በኩል ሰብዓዊነትን መሰረት አድርጎ ህዝባዊነትን በመታጠቅ «ወገን ለወገን » ደራሽነቱን በገንዘብና በቁሳቁስ ድጋፍ ሲደረግ የታዘብንበት ሁኔታ ፤ስፖርት ሰላም፣ ፍቅር፣ የአብሮነትና የአንድነት፣ የመተሳሰብ፣ የወንድማማችነት ልዩ መገለጫ የመሆኑን እውነታ በተግባር አስረድቷል።የኮሮና ወረርሽኝ በዓለም ፖለቲካ፣ ኢኮኖሚና ማህበራዊ መስተጋብር ላይ ያሳደረው ተጽእኖ መዘዙ ዓለም አቀፉን የስፖርት ቁመና የኪሳራ መልክ ያላበሰው ነበር ።በስፖርቱ ላይ የደረሰው ከፍተኛ የሆነ የፋይናንስ ቀውስ የተጽእኖው ሰንሰለት ዛሬ ላይ የሚቆም ሳይሆን እስከ ቀጣዮቹ አስር ዓመታት የሚጓዝ እዳን ያስከተለ መሆኑን ነው ጥናቶች ያመላከቱት።በወረርሽኙ ምክንያት ከፍተኛ መቃወስን ካስተናገዱ መካከል የስፖርት ዘርፍ ዋነኛ ነበር።ይህም በስፖርቱ ማህበረሰብ በኩል ወረርሽኙን ለመዋጋት እየተደረገ በሚገኘው ርብርብ እያደረገ ያለው ተሳትፎ ስፖርት ትልቅ ማህበራዊ ኃላፊነትን የተሸከመ ግዙፍ ተቋም መሆኑን ያመላክታል። በዓለም አቀፍ ደረጃ እንደታዘብነው ሁሉ በሀገራችን የስፖርት ማህበረሰቡ ከነጉዳቱ ትልቅ ተሳትፎ ሲያደርግ ነበር።በዘመነ ኮሮና የስፖርት ቤተሰቡ ሰብዓዊነትን ያነገበ ተግባር በይበልጥ ተጠናክሮ እንደቀጠለ የሚያሳይ መረጃ ከአዲስ አበባ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን አካባቢ የወጣው መረጃ ያመላክታል።የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በኮሮና ቫይረስ ( ኮቪድ_19) ወረርሽኝ ምክንያት ለተቸገሩ 300 የሁለተኛ ዲቪዚዮን ክለብ አትሌቶች፣ ዳኞችና አሰልጣኞች የሰብዓዊ ድጋፍና ስለ ቫይረሱ የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሐ ግብር ማዘጋጀቱን አስታውቋል።«ለአትሌቶቻችን እንቁም» በሚል መሪ ቃል በአዲስ አበባ ስታዲየም ዛሬ ማለዳ የሚደረገው የድጋፍና ግንዛቤ የማስጨበጫ መርሐ ግብር የስፖርቱ ቤተሰብና ማህበረሰብ ለሰብዓዊነት ተግባር የሚሰጠው ቦታ ምን ያህል ሰፊና ጥልቅ መሆኑን በዘመነ ኮሮና በይበልጥ የሚያሳይበት እንደሚሆን ተጠቁሟል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት አቶ ቢኒያም ምሩፅ ይፍጠር እንደተናገሩት፤የኮቪድ -19 ወረርሽኝ ስጋት በአትሌቲክሱ ስፖርት እና ስፖርተኞችም ላይ ጥላውን ያጠላ መሆኑን ገልጸዋል ።በመሆኑ ከዚህ ችግር ተሻግረን ነገ የምንፈልገውን ውድድርና ውጤት ለማስመዝገብ ዛሬ መረዳዳት ይኖርብናል።ስለዚህ በሁለተኛ ዲቪዚዮን ክለብ የሚገኙ አትሌቶች፣ አሰልጣኞች፣ የታዳጊ ወጣቶች ፕሮጀክት አሰልጣኞች፣ እና ዳኞች ቁጥራቸው 300 ለሚሆኑ የስፖርቱ ቤተሰቦች በዛሬው እለት የሰብዓዊ ድጋፍ ሊደረግ መሆኑን አመልክተዋል። በኢትዮጵያ አትሌቲክስ የትልቅ ታሪክ ባለቤት ከሆኑት አትሌቶች አንዱ የሆነው ማርሽ ቀያሪው ምሩጽ ይፍጠር ልጅ የሆኑት አቶ ቢኒያም ፤«ነገን እንሻገራለን፣ የምንፈልገውንና የምንወደውን አትሌቲክስ ስፖርታችንን እናስቀጥላለን ዛሬ ላይ በህብረትና በአንድነት ቆመን ልንደጋገፍና ልንረዳዳ ይገባል» ሲሉም ሰብዓዊነትን የታጠቀውን መርሐ ግብር አስፈላጊነት የተናገሩት። የአዲስ አበባ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ለአትሌቲክስ የዘወትር አጋር ከሆነው ከሞሐ ለስላሳ መጠጦች ኢንዱስትሪ አክሲዮን ማህበር ጋር በመተባበር የሰዋዊ ድጋፍና የግንዛቤ ማስጨበጫው የሚከናወን መሆኑንም ነው ያስታወቁት። አዲስ ዘመን ሰኔ 12/2012ዳንኤል ዘነበ
https://www.press.et/Ama/?p=34669
482
2ስፖርት
የ3ሺ ሜትር መሰናክል የመጪው ዘመን ተስፋ
ስፖርት
June 22, 2020
16
ያለፈው የፈረንጆቹ ዓመት በእርግጥም አንድ እውነት በዓለም አትሌቲክስ ልቆ ያንጸባረቀበት ወቅት ነበር። በሦስት ሺ ሜትር መሰናክል ውድድር ለዓመታት ወደ አንድ ወገን ያደላው የበላይነትም ባልታሰበ አቅጣጫ የተጓዘበት ሆኖ ይታወሳል። በበርካታ ዓመታት የአትሌቲክስ ታሪክ ውስጥ የምሥራቅ አፍሪካ አትሌቶች ዓለምን ያስደመሙትና በውጤት ያሸበረቁት በመምና ጎዳና ላይ የረጅም ርቀት ሩጫ ነበር። ለኢትዮጵያ ቀንደኛ ተፎካካሪ ከሆኑት ሃገራት መካከል ቀዳሚዋ ኬንያ በተለይም በ3ሺ ሜትር መሰናክል ሩጫ እስካለፈው ዓመት ድረስ በዓለም ውጤታማና ከሌሎች ተፎካካሪዎቿ ፍፁም የበላይ ነበረች። እአአ በ2019 ግን በዚህ ርቀት ኢትዮጵያም ተስፋ ያላት ሃገር መሆኗን በተለያዩ ውድድሮች ማረጋገጥ እንደተቻለ የዓለም አትሌቲክስ ሰሞኑን በድረ ገጹ ያሰፈረው ሰፊ ሐተታ ይጠቁማል። ለኢትዮጵያ በታላቅ የውድድር መድረክ በርቀቱ የመጀመሪያው ድል የተመዘገበው በዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮና ሲሆን፤ በኳታር ዶሃ በተካሄደው ውድድር ለሜቻ ግርማ በጥቂት ማይክሮ ሰከንዶች ተቀድሞ የብር ሜዳሊያ በማጥለቅ ታሪክ ማስመዝገብ ችሏል። በወቅቱ አትሌቱ 8:01.36 የሆነ ሰዓት ሲያስመዘግብ በኬንያዊው ኮንሴሉስ ኪፕሩቶ የተቀደመበት አጋጣሚ እጅግ የሚያስቆጭ ሆኖ ይታወሳል። በርቀቱ ለኢትዮጵያ ተስፋ ሰጪ የሆነው ሌላኛው ድል ደግሞ በውድድር ዓመቱ ዳይመንድ ሊግ ላይ ነበር የተመዘገበው። ወጣቱ አትሌት ጌትነት ዋለ በርቀቱ ለመጀመሪያ ጊዜ የዳይመንድ ሊግ አጠቃላይ አሸናፊ ከሆኑ አስር የተለያዩ ርቀት ተወዳዳሪ አትሌቶች መካከል አንዱ ሊሆን ችሏል። እነዚህ በዓለም ታላላቅ የአትሌቲክስ ውድድሮች ላይ ኢትዮጵያን በአዲስ ርቀት ተስፋ እንድታደርግ ያስቻሉ አትሌቶች የሚሰለጥኑት በአንድ አሰልጣኝ ስር ነው። ይህ አሰልጣኛቸውም ብሄራዊ ቡድንን የሚወክሉ በርካታ አትሌቶችን በማፍራት ላይ የሚገኘው ተሾመ ከበደ ነው። በተለይ ጌትነት በ3ሺ ሜትር መሰናክል በዓመቱ ያሳየው ብቃት እጅግ አበረታች በመሆኑ ድረገጹ ትኩረት የሰጠው ሲሆን፤ ቀጣዩ የርቀቱ ኮከብ እንደሚሆንም ነው ተስፋውን የገለጸው። አትሌት ጌትነተ ዋለ በደቡብ ምሥራቅ የሃገሪቷ አካባቢ በምትገኘው ሰቀላ የተባለ ስፍራ ስምንት ልጆች ካሏቸው ቤተሰብ መካከል የተገኘ ፍሬ ነው። ዛሬ አትሌት ለመሆኑ ምክንያቱ ደግሞ በየዕለቱ በጠዋት እየተነሳ ከቤቱ በአራት ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ወደሚገኘው ትምህርት ቤቱ የሚያደርገው ሩጫ ነበር። ይህ ልምድም ትምህርት ቤት ውስጥ ለሚካሄዱ የሩጫ ውድድሮች ሲያሳጨው፤ በ13 ዓመቱ በ1 ሺ 500 እና 3 ሺ ሜትር አሸናፊ መሆንም ችሎ ነበር። ይህ ሁኔታ ለቀጣይ የአትሌቲክስ ህይወቱ መንገድ የጠረገለትን አጋጣሚ የፈጠረም ነበር። ይህም ጌትነት በትምህርት ቤቱ ተገኝቶ ብቃቱን ለተመለከተው የኢትዮጵያ ወጣቶች ስፖርት አካዳሚ አሰልጣኝ እይታ ውስጥ እንዲገባ አድርጎታል። ጌትነት ከዚያ በኋላ የሆነውን ሲያስታውስም ‹‹አሰልጣኙ በእኔ ላይ ፍላጎት ስላሳደረ ቤተሰቦቼን አስፈቅጄና የትምህርት ማስረጃዎቼን ይዤ ወደ አዲስ አበባ አብሬው እንድሄድ ጠየቀኝ›› ይላል። ያ አሰልጣኝ ዛሬም ድረስ በስኬቱ ከጎኑ ያለው ተሾመ ሲሆን፤ ለዓመታት በነበራቸው የአብሮነት ቆይታ አትሌቱ በመሰናክል የተሻለ ብቃት እንዳለው መረዳት በመቻሉ ወደዚያው እንዲገባ አድርጓል። እአአ 2016 በተካሄደው ከ20 ዓመት በታች የአትሌቲክስ ቻምፒዮና ደግሞ የአሰልጣኙ ጥረትና የጌትነት ችሎታ በእርግጥም ለስፖርት ቤተሰቡ በግልጽ ሊታይ የቻለበት ነው። ይህ ተስፈኛ አትሌት በፖላንድ ባይዳጎዝ ከተማ በተካሄደ ዓለም አቀፍ ውድድር ተሳትፎ የነሐስ ሜዳሊያ ቢያገኝም፤ በወቅቱ ብቃቱ ያን ያህል ትኩረት ያገኘ አልነበረም። ይሁን እንጂ ሁለተኛ ከወጣው አትሌት በ16 ሰከንዶች የዘገየውና 8፡22.83 የሆነ ሰዓቱ የግሉ ፈጣን ሰዓት ነበር። በወቅቱ የነበረው ብቃት በአትሌቲክስ ቤተሰቡ ዘንድ እምብዛም ትኩረት ባያገኝም በሪዮ ኦሊምፒክ ግን ለብሄራዊ ቡድን ለመመረጥ ዕድሉን አስገኝቶለታል። ወጣቱ አትሌት በታላቁ መድረክ ሃገሩን በመወከሉ ደስ ቢሰኝም በበዛ የጭንቀት ስሜት በመዋጡ እንዳሰበው ሜዳሊያ ማግኘት ሳይችል ቀረ። በባይዳጎዝ በተካሄደው የወጣቶች ቻምፒዮና ብቃቱን ለተረዳው ማናጀሩ ግን ይህ ምንም ማለት አልነበረም። ማናጀሩ ሁሴን ማቄ ‹‹ጌትነት ትልቅ ልብ ያለው አትሌት ነው። በውድድሩ ላይ ሁለት ጊዜ ወድቆ ከሜዳሊያ ሰንጠረዡ ሳይወጣ ለብር ሜዳሊያ በተጠጋ ውጤት ማጠናቀቅ መቻሉ አስደናቂ ነው›› ሲል ይገልጸዋል። ጌትነት በቀጣዩ ዓመትም ውጤታማነቱ እንደቀጠለ ነበር። በሃገር አቀፉ ቻምፒዮና አሸናፊ ከሆነም በኋላ በሄንግሎ በተካሄደው ከ20 ዓመት በታች ውድድር በብሄራዊ ቡድኑ ተካተተ። ውድድሩንም 8፡12.28 በሆነ ሰዓት የክብረወሰን ባለቤት በመሆን አጠናቀቀ። ይኸውም በዚያው ዓመት (እአአ 2017) በተካሄደው የለንደን አትሌቲክስ ቻምፒዮና ሃገሩን እንዲወክል አደረገው፤ በ17 ዓመቱም ልምድ ካላቸው አትሌቶች ጋር ተፎካክሮ ዘጠነኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቀቀ። እአአ በ2018 የውድድር ዓመት በፊንላንድ የወጣቶች ቻምፒዮና ተሳታፊ ቢሆንም፤ ባልተጠበቀ መልኩ በሌላኛው የሃገሩ ልጅ ተቀድሞ የነሐስ ሜዳሊያ ነበር ያጠለቀው። ይህ ተደጋጋሚ የውድድር ልምድም እአአ 2019 የውድድር ዓመት በሚገባ እንዲዘጋጅና ያለውን ብቃት በተገቢ መንገድ እንዲያሳይ አደረገው። የስልጠና ጫናውን በመጨመርም በሳምንት ከ100-120 ኪሎ ሜትር በመሸፈን ልምምዱን ይሠራም ነበር። ከቡድን አጋሩ ለሜቻ ግርማ ጋር ጠንካራ ልምምድ በመሥራታቸውም ሁለቱም የግል ውጤታቸውን ማየትና ለሃገራቸውም ውጤት ማስመዝገብ ችለዋል። ጌትነት ከዓለም አትሌቲክስ ድረገጽ ጋር በነበረው ቆይታም ‹‹ከለሜቻ ጋር በአካዳሚው አብረን የምንኖር ጓደኛሞች ነን። በልምምድ ጊዜ ጠንክረን የምንሠራ በመሆናችን የሥራችንን ፍሬ ልናገኝ ችለናል›› ይላል። የዳይመንድ ሊግ ውድድሮቹን ሲያስታውስም ‹‹ራባት በጭራሽ የሚዘነጋ አይደለም፤ ምክንያቱም ከዚያ ቀደም የምሠራቸውን ስህተቶች ያረምኩበት ውድድር ነው። በቅድሚያ ሩጫውን ለመቆጣጠር ቻልኩ ከዚያም በመጨረሻው ዙር የመጨረሻውን ውሃ በጥንቃቄ በመዝለል ቀዳሚ ሆኜ በአሸናፊነት አጠናቀቅኩ›› ሲል ውጤታማውን ውድድር መለስ ብሎ ያስታውሳል። በውድድሩ ያስመዘገበው ሰዓትም የኢትዮጵያ የርቀቱ ክብረወሰንና በዳይመንድ ሊጉ ሦስተኛው ፈጣን ሰዓት ነበር። አሸናፊ ከሆነም በኋላ ‹‹አሸናፊነቴ ለኢትዮጵያ ትልቅ ድል ነው፤ ምክንያቱም ከዚህ ቀደም በዳይመንድ ሊግ የ3ሺ መሰናክል ውድድር አሸናፊ የሆነ አትሌት አልነበረም። በመሆኑም በራስ መተማመን ሰጥቶኛል፤ ወደፊት ደግሞ ከስምንት ደቂቃ በታች መሮጥ እንደምችል ፍንጭ ያገኘሁበት ነው›› በማለት ስሜቱን ያጋራል። በዓለም ቻምፒዮናው ተሳታፊ የነበረው ጌትነት የአሸናፊነት ቅድመ ግምት ካገኙት አትሌቶች መካከል ቢሆንም፤ ያጠናቀቀው በሜዳሊያ ሰንጠረዡ የቅርብ ርቀት ላይ አራተኛ ሆኖ ነበር። በዓመቱ በተካሄደው የቤት ውስጥ የዙር ቻምፒዮና ተሳትፎውም ከሦስቱ ውድድሮች በሁለቱ አሸናፊ መሆን ችሏል። በብራሰልስ በነበረው የዳይመንድ ሊጉ ማጠናቀቂያ ውድድር ያሳየው ብቃትና አጨራረስ ለዚህ የውድድር ዓመት ይደገም ይሆን በሚል የስፖርቱ ቤተሰብ እንዲጠብቀው ያደረገም ነበር። የእርሱም እቅድ በዚህ ዓመት ሊካሄድ በታሰበው የቶኪዮ ኦሊምፒክ በርቀቱ ታሪክ መሥራት ነበር። ሆኖም በዓለም አቀፍ ደረጃ በተከሰተው የኮሮና (ኮቪድ 19) ወረርሽኝ ምክንያት እንደ ውድድሩ ሁሉ ብቃቱም በቀጠሮ ለሚቀጥለው ዓመት ሊራዘም ችሏል። ሆኖም በቤቱ ውስጥ ሆኖ በሳምንት ሦስት ቀናት ልምምድ ማድረጉን አላቋረጠም። ‹‹በብቃቴ ለመቆየት ማድረግ ያለብኝን እያደረኩ ነው። በቅርቡ ወደ ውድድር እንመለሳለን የሚል ተስፋም አለኝ›› ሲል ተስፈኛው አትሌት ይናገራል። በዚህ ወቅትም ኑሮውን ካደረገባት አዲስ አበባ ወደ ተወለደበት አካባቢ በማቅናት ቤተሰቡን በመርዳት ላይ ይገኛል። ውድድሩ በተመለሰ ጊዜም በ3ሺ ሜትር መሰናክል ኢትዮጵያዊያን ለሌሎች ተፎካካሪ አገራት አትሌቶች ፈተና እንደሚሆኑ እምነቱ ነው። ‹‹በመሰናክል ጠንክረን በመሥራት መልካም ውጤት ማስመዝገብ በመቻላችን ደስተኞች ነን›› የሚለው ጌትነት ይህም የበላይነቱን ለረጅም ጊዜ ይዘውት ለቆዩት ኬንያዊያን ማስጠንቀቂያ መሆኑን ድረ ገጹ በሰፊ ሐተታው መደምደሚያ አስምሮበታል። አዲስ ዘመን ሰኔ 15/2012ብርሃን ፈይሳ
https://www.press.et/Ama/?p=34859
882
2ስፖርት
« የጥቁር ሕይወት ዋጋ አለው»!
ስፖርት
June 21, 2020
24
የምን ጊዜም የቦክስ ስፖርት ንጉሱ መሐመድ አሊ የዓለም የቦክስ ቻምፒዮንና ታላቅ የቡጢ ተፋላሚ ብቻ አልነበረም። የሰብዓዊ መብት ተሟጋች፤ የጥቁር ህዝቦች ሰንደቅ፤ በመላው ዓለም በስፖርትና በታላቅ ስብዕና ተምሳሌትም ጭምር ነው። ብዙዎች ቦክስ ስፖርት ሳይሆን የጥጋበኞች ድብድብ አድርገው ከመሳል አስተሳሰብ አውጥቶ የቦክስን ስፖርት ጥበባዊ ገፅታ በማላበስ ተወዳጅና አሁን ላይ በዓለማችን በአንድ ጊዜ በርካታ ሚሊየን ዶላሮች የሚያሳቅፍ ግንባር ቀደም ስፖርት እንዲሆን ተፅዕኖውን አሳርፏል። ሙዚቀኛም ሆኖ ለሂፕሆፕና ራፕ የሙዚቃ ስልቶች ጉልህ ሚና ተጫውቷል። በቦክስ ስፖርት ታሪክ የምንግዜም ምርጥ ቦክሰኛ የተባለውም በተለያዩ የቡጢ ፍልሚያዎች ዘመን የማይሽራቸው ገድሎችን በማስመዝገብ ነው። መሐመድ አሊ የቦክስ ጓንቱን ሰቅሎ ስፖርቱን በቃኝ ብሎ ከተሰናበተ ከሦስት ዓመታት በኋላ እኤአ በ1984 ከስፖርቱ ልምድ ጋር በተያያዘ ፓርኪንሰንስ በተባለ በሽታ ተይዞ ነበር።ለሰላሳ ሁለት ዓመታት ከዚህ ህመሙ ጋር ሲታገል ቆይቶ ከአምስት ዓመት በፊት በሰባ አራት ዓመቱ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።ባለፉት ሳምንታት በአሜሪካ ሚኒያፖሊስ ከተማ ነጭ ፖሊስ ያልታጠቀ ጥቁር አሜሪካዊ አንገትን በጉልበቱ እረግጦ ለሞት ማብቃቱን ተከትሎ የዓለም ሕዝብ ትኩረት ከኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ወደ ሟቹ ጆዮርጅ ፍሎይድ ጉዳይ ዞሯል።ይህ ዘግናኝ ክስተት ከዓመታት በፊት በተመሳሳይ ቁጣን የቀሰቀሰውና በነጭ የፖሊስ አባላት ጭካኔ የሞተውን ኤሪክ ጋርነርን ያስታወሰ ሆኗል። ኤሪክ በወቅቱ በፖሊስ አንገቱ ተቆልፎ ‹‹እባካችሁ መተንፈስ አልቻኩም›› እያለ ነበር የሞተው። የጂዮርጅ ፍሎይድ አሰቃቂ ግድያ ዛሬም ድረስ በሞተባት አገሩ አሜሪካና ሌሎች የዓለማችን ክፍሎች ትልቅ ቁጣን ቀስቅሶ ይገኛል።በታላላቅ ከተሞችም‹‹ የጥቁር ሕይወት ዋጋ አለው›› የሚሉ መፈክሮች በተለያዩ ሰላማዊ ሰልፎች ተፅዕኖ ፈጥረዋል።አዲስ ዘመን ስፖርትም በሳምንታዊ የስፖርት ማሕደር አምዱ ‹‹የጥቁር ሕይወት ዋጋ አለው›› ብሎ ለጥቁሮች እኩልነት ስለታገለው የቦክሱ ዓለም የምንጊዜም ኮከብ መሐመድ አሊ ሕይወት ላይ ትኩረቱን ለማድረግ ወደደ።መሐመድ አሊ ወደ ቦክስ ሕይወት የመጣበት አጋጣሚ አስገራሚ ነው። የአስራ ሁለት ዓመት ልጅ በነበረበት ወቅት ብስክሌቱ ተሰርቆበት በሊውስቪል ኬንታኪ ለሚገኝ ጆ ማርቲን ለተባለ ፖሊስ አመለከተ።«የሰረቀኝን ባገኘው ልክ አገባው ነበር» ብሎም ምሬቱን ይገልፃል።የቦክስ አሰልጣኝ የነበረው ፖሊስ ትንሹን መሐመድ ራሱን እንዴት ከጥቃት መከላከል መማር እንዳለበት መከረው።የተወሰኑ ስልጠናዎችን ሲወስድ ቆይቶም ብስክሌቱ ከተሰረቀች ከስድስት ሳምንታት በኋላ በሰፈሩ በአንድ አማተር የቦክስ ግጥሚያ ላይ ተሳተፈና በነጥብ አሸናፊ መሆን ቻለ።ይህች አጋጣሚም በዓለም በገነነበት ስፖርት የመሰረት ድንጋይ ነች። መሐመድ የትውልድ ስሙ ካሴስ ክሌይ ቢሆንም በ19ኛው ክፍለ ዘመን ባሮችን ነፃ ለማውጣት በታገሉ ታላቅ ሰው መታሰቢያነት የወጣለት ስም ነበር።ለመጀመርያ ጊዜ የዓለም ከባድ ሚዛን ቻምፒዮን ከሆነ በኋላ በማግስቱ ስሙን ለመቀየር ወሰነ።የነፃነት ታጋዩን ማልኮለም ኤክስ ከጎኑ አድርጎ በሰጠው መግለጫ «ዘ ኔሽን ኦፍ ኢስላም» የተባለውን ተቋም መቀላቀሉን በማሳወቅ የባርያ ስም ይለው የነበረውን ካሴስ ክሌይ በመቀየር በቀድሞ ስሙ ላለመጠራት ወሰነ። በወቅቱ «ኔሽን ኦፍ ኢስላምን» ይመራ የነበረው ኤልጅያህ መሃመድ እኤአ በ1964 ላይ መሐመድ አሊ የሚለውን ስም ካወጣለት በኋላ እሱን በማፅደቅ እስከ ህይወት ዘመኑ መጨረሻ ተጠራበት። ለሃያ አንድ ዓመታት በፕሮፌሽናል ቦክሰኛነት በርካታ የቡጢ ፍልሚያዎችን ከአሜሪካ እስከ አፍሪካ እንዲሁም ሌሎች ዓለማት ላይ የተፋለመው መሐመድ አሊ ለሦስት ጊዜ የዓለም ከባድ ሚዛን ቻምፒዮን ሆኗል።ለመጀመርያ ጊዜ የዓለም የከባድ ሚዛን ቻምፒዮን ለመሆን የበቃውም የሃያ ሁለት ዓመት ወጣት እያለ ነው። ዓለም አቀፍ ደረጃ ባላቸው ፕሮፌሽናል የቦክስ ግጥሚያዎች ላይ ስልሳ አንድ ጊዜ ተሳትፎ ሃምሳ ስድስቱን ማሸነፍም ችሏል። ከነዚህ ድሎቹም ሰላሳ ሰባት ያህሉን ተጋጣሚዎቹን በበቃኝ በመዘረር ነው። አስገራሚው ነገር በሰላሳ አንድ ተከታታይ የቦክስ ግጥሚያዎች ሳይሸንፍ ለመጀመርያ ጊዜ የተሸነፈው የክፍለ ዘመኑ ምርጥ ፍልሚያ በተባለው ግጥሚያ በጆ ፍሬዘር ነበር።በፕሮፌሽናል የቦክሰኛነት ዘመኑም ሽንፈትን የቀመሰው አምስት ጊዜ ብቻ ነው። የመጨረሻው ፍልሚያም እኤአ በ1981 ከትሬቨር ቤሪቢክ ጋር በማድረግ ስፖርቱን በቃኝ ብሏል። አሜሪካ በቬትናም በ1970ዎቹ መጀመርያ ያደረገችውን ጦርነት በመቃወሙ ለሦስት ዓመታት ከፕሮፌሽናል ቦክስ ውድድሮች ታግዶ የቆየው መሐመድ አሊ እገዳው በተጣለበት ወቅት ከአስር የማያንሱ የዓለም ከባድ ሚዛን ቻምፒዮናዎች ባያመልጡት አሁን ካሉት የበለጠ በርካታ ክብሮችን መጎናፀፍ ይችል ነበር። በዚህም ከሰማንያ ሚሊየን ዶላር በላይ ሀብት ማፍራት ችሏል። ለዚህም ሀብቱ ምንጭ ስፖርቱን ከተሰናበተ ወዲህ ግንባር ቀደም ተዋናዮቹ ስሙንና ምስሉን የሚጠቀሙ ከአርባ በላይ ኩባንያዎች ናቸው። ታሪካዊው ኢትዮጵያዊ አትሌት አበበ ቢቂላ በ1960 የሮም ኦሊምፒክ በባዶ እግሩ ሮጦ ለጥቁር ህዝቦች የመጀመሪያውን የማራቶን የወርቅ ሜዳሊያ ሲያስመዘግብ መሐመድ አሊም በቦክስ የወርቅ ሜዳሊያ አጥልቆ ነበር። ሁለቱ ታሪካዊ የጥቁር ህዝቦች ከዋክብት ፊርማቸውን ተለዋውጠውም ነበር። ይሁንና መሐመድ አሊ ይህን የወርቅ ሜዳልያውን ለአገሩ ከማበርከት ይልቅ በሊውስ ቪል ግዛት በሚገኘው የኦሃዮ ወንዝ ጨምሮታል። ሜዳልያውን ለአሜሪካና ለትውልድ ከተማው ሊውስ ቪል ቢቀዳጅም ለጥቁሮች በርገር የመግዛት መብት ባለመኖሩ ተቃውሞውን ለመግለፅ ነበር ይህን ርምጃ የወሰደው። በ1996 አገሩ አሜሪካ ባስተናገደችው የአትላንታ ኦሊምፒክ ችቦውን እንዲለኩስ ከመደረጉ ባሻገር ወንዝ የጨመረው የወርቅ ሜዳልያ ምትክ ሌላ ሜዳሊያ በአንገቱ ተጠልቆለታል። በ1980 በላስቬጋስ በተካሄደ የቡጢ ፍልሚያ በቴክኒካል የበቃኝ ውጤት ቢሸነፍም መሐመድ ትልቁን ክፍያ ስምንት ሚሊየን ዶላር ያፈሰው በዚያ ውድድር ነው።« ራምብል ኢን ዘ ጃንግል» በተባለውና እስካሁንም ከስፖርት ቤተሰቡ አዕምሮ በማይጠፋው በአፍሪካ ምድር በተካሄደው ፍልሚያ መሐመድ አሊ ምን ጊዜም ይታወሳል። እኤአ በ1974 መሐመድ አሊ በሰላሳ ሁለት ዓመቱ ሽንፈትን አይቶ ከማያውቀው ከሃያ አምስት ዓመቱ ጆርጅ ፎርማን ጋር በኮንጎ ኪንሻሳ የቡጢ ፍልሚያ ገጥሞ ነበር። በወቅቱ የኮንጎ ፕሬዝዳንት የነበሩት ሞቡቱ ሴሴኮ ለሁለቱ ቦክሰኞች በኪንሻሳ ከተማ እንዲጫወቱ በነፍስ ወከፍ አምስት ሚሊዮን ዶላር ከፍሏቸው ነበር።መሐመድ አሊ በውድድሩ ስምንተኛ ዙር ላይ በዝረራ ቢሸነፍም ከወጣት ተፋላሚው ጋር ያደረገው እልህ አስጨራሽ የቡጢ ፍልሚያ እስካሁንም ከህሊና የሚጠፋ አይደለም። በ1970 የዶክተር ማርቲን ሉተር ኪንግ መታሰቢያ ሽልማት የተቀበለው መሐመድ አሊ፤ የዓለም አቀፋዊ ወዳጅነት ተምሳሌት ሆኖም ያውቃል። የተባበሩት መንግስታት የሰላም መልዕክተኛ ሆኖም ከ1998 እስከ 2008 በታዳጊ አገራት በመዘዋወር አገልግሏል። በህይወቱ ዙርያ በሚያተኩሩ ጥናታዊና የሙሉ ጊዜ ፊልሞች የሰራ ሲሆን በተለይ ለመጀመርያ ጊዜ በተዘጋጀውና ዘ ግሬተስት በተባለ ፊልም ላይ ተውኗል።የህይወት ታሪኩ ላይ በማተኮር ከተሰሩ ፊልሞች የኦስካር ሽልማት በጥናታዊ ፊልም ዘርፍ ያገኘው «ዌን ዊ ዌር ኪንግስ»ና ዝነኛው የሆሊውድ ተዋናይ ዊል ስሚዝ በመሪ ተዋናይነት የተጫወተው «አሊ» የተባሉት ይጠቀሳሉ።ታላቁን የደቡብ አፍሪካ ነፃነት ታጋይ ኔልሰን ማንዴላ ከእስር እንደተፈቱ በአካል ተገኝቶ ደስታውን ለመግለፅ መሐመድን የቀደመው የለም። በአካል ካገኛቸው ታላላቅ መሪዎች የእንግሊዟ ንግስት ኤልሳቤት፤ የሮማው ሊቃነ ጳጳስ ፖፕ ጆን ፖል፤ የኩባው መሪ ፊደል ካስትሮ እንዲሁም የኢራቁ ሳዳም ሁሴን ይገኙበታል።አይም ዘ ግሬተስትና ስታንድ ባይ ሚ ከዘፈን ስራዎቹ መካከል የሚጠቀሱት ናቸው።በንግግር ችሎታው፤ በልዩ የግጥም ስንኞቹም ተወዳጅነት ያተረፈ መሐመድ አሊ ነው።«በማይሞት እምነትና ፍቅር ዓለም የተሻለ ዓለም መፍጠር እንደሚቻል አሳይቶናል።ሁሌም ቻምፒዮን ነው»።በማለት የቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማን ጨምሮ በርካታ የዓለማችን ተፅዕኖ ፈጣሪና ታላላቅ ሰዎች በቀብር ስነስርዓቱ ላይ ተገኝተው መሐመድን ወደማይመለስበት ሸኝተውታል። እሱ ቢያልፍም ጥቁሮች ዛሬም ድረስ ‹‹የጥቁር ሕይወት ዋጋ አለው›› ብሎ ከዘመናት በፊት ትግሉን የጀመረውን ጀግና ያስቡታል።አዲስ ዘመን ሰኔ 14/2012 ቦጋለ አበበ
https://www.press.et/Ama/?p=34797
902
2ስፖርት
“የትግራይ ሕዝብ የገጠመውን ፈተና ከፌደራል መንግሥት ጎን በመቆም ሊሻገረው ይገባል” ዶክተር ሙሉ ነጋ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ዋና ሥራ አስፈፃሚ
ሀገር አቀፍ ዜና
January 8, 2021
50
ጽጌረዳ ጫንያለው አዲስ አበባ፡- የትግራይ ህዝብ የገጠመውን ፈተና ከፌደራል መንግሥት ጎን በመቆም ሊሻገረው እንደሚገባ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ዋና ሥራ አስፈፃሚ ዶክተር ሙሉ ነጋ ጥሪ አቀረቡ ::የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ዋና ሥራ አስፈፃሚ ዶክተር ሙሉ ነጋ በዓሉን አስመልክተው በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንዳስታወቁት፤ በክልሉ የሕግ ማስከበር ከተጀመረ ጀምሮ በርካታ ሥራዎች እየተከናወኑ ናቸው:: በተለይም ሰላምና መረጋጋትን ከማምጣት አንፃር ጥሩ እንቅስቃሴ አለ፡፡በዓሉን ለማክበር መሰረታዊው ነገር ሰላም ነው:: በዚህ ጉዳይ ላይ ውጤታማ ሥራዎች በመሥራት ላይ ናቸው ያሉት ዶክተር ሙሉ፣ በዓሉን ተመርኩዞ ዋና አስፈላጊ የሆኑት አስቸኳይ ዕርዳታ የሚፈልጉ አካላትን ማገዝ ነው:: ይህም በከፍተኛ ሁኔታ እየተከናወነ ነው ብለዋል :: ብዙ የትግራይ አካባቢዎችም ከመብራትና ስልክ ጀምሮ ችግር የገጠማቸው በመሆናቸው ይህንንም ለማስተካከል ከፍተኛ እንቅስቃሴ እየተደረገ መሆኑን አመልክተው፣ በክልሉ ባንኮች እንዲከፈቱ መደረጉም የዚህ ትኩረት አካል እንደሆነ ጠቁመዋል:: መብራትና ስልክ እንዲሁም ውሃ ያላገኙ አካባቢዎች በዓሉን በጭለማ እንዳያሳልፉ እየተሠራ መሆኑን የሚጠቁሙት ዶክተር ሙሉ፤ በአንዳንድ አካባቢዎች ላይ በመሰረተ ልማት ችግር ምክንያት በተለይም በመንገድ ችግር የዕለት ደራሽ ዕርዳታውን ለማድረስ ችግር ገጥሟል:: ችግሩን በተቻለው ሁሉ በመፍታት ህዝቡ በዓልን በተረጋጋ መንፈስ እንዲያከብር እየተሞከረ ነው ብለዋል:: የገና በዓል ለትግራይ ህዝብ ቀላል አይደለም የሚሉት ዶክተር ሙሉ፤ በችግር ወቅት ውስጥ በመሆናቸው የቀደመ የመረዳዳት ባህላቸውን ተጠቅመው ተደጋግፎ፣ ሰላሙን ጠብቆና ተቃቅፎ ነገ ብሩህ ነውና ችግራቸውን ሊያልፉት እንደሚገባ አመልክተዋል። ሕዝቡ ተረጋግቶ በዓሉን እንዲያከብር ከማድረግ አንፃር በክልሉ የፀጥታ ሃይሉን የማደራጀት ሥራ መጀመሩን የገለፁት ዋና ሥራ አስፈፃሚው፤ የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽንም መመደቡን አስረድተዋል:: በተመሳሳይ በመንግሥት መሥሪያ ቤት ደረጃ የተሳለጠ አገልግሎት ሕዝቡ እንዲያገኝ ለማድረግም የመንግሥት መዋቅሩ ታችኛው ድረስ እንዲሠራ የማድረግ ሥራው ተጀምሯል:: የክልሉ ካቢኔም ሥራውን እየሠራ ይገኛል:: ከሰባት ዞኖች ውስጥም ስድስቱ የዞን አመራሮች ተመድበው እየሠሩ ናቸው:: ሥራውም በሚቀጥለው ሳምንት እንዲጠናቀቅ ተደርጎ በመሥራት ላይ ነው ብለዋል:: የትግራይ ህዝብ የገጠመውን ፈተና እርስ በእርስ ተጋግዞና ከፌደራል መንግሥት ጎን ቆሞ እንዲያልፍ ጥሪ ያቀረቡት ዶክተር ሙሉ፣ መጪው ጊዜ ለትግራይ ህዝብ የሰላም፣ የፍቅር፣ የብልጽግና እንደሚሆን ያላቸውን እምነት ገልፀዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 30/2013
https://www.press.et/Ama/?p=39072
281
0ሀገር አቀፍ ዜና
ቢራስ የላችሁም?
መዝናኛ
December 3, 2019
29
መልእክት በእጅጉ የተሳለጠበት ዘመን ቢባል እንደዚህ ዘመን ያለም አይመስለኝም፡፡ በዚህ በኩል የሞባይል ስልክ ዋጋ ከፍተኛ ነው። የሞባይል ስልክ ያስገኘው ጠቀሜታ ተነግሮ አያልቅም፡፡ባሉበት ስፍራ ሆነው መልእክት ያደርስዎታል፤ መለዋወጥም ያስችልዎታል፡፡ በመንገድ፣ በስራ ቦታ፣ በተኙበት፣ ወዘተ ሁሉ መልእክት ከች ይላል፤ እርስዎም መልእክት መቀበል ብቻም ሳይሆን መልእክት ያሻግራሉ፡፡ አጠቃቀሙ ላይ ግን እንከኖች ይስተዋላሉ፡፡ አንዳንድ ሰዎች በሞባይል ስልክ ሲያወሩ በሞባይል እንደሚያወሩም የሚያውቁ አይመስለኝም፤ ይጮሃሉ፡፡ አመል ሊባል ይችላል፡፡ ስልኩ ተመቸኝ ብሎ አጠገብ በተቀመጠና በቆመ ሰው ጆሮ ላይ እየጮኹ ማውራት ምን ይሉታል? በልክ ቢወራ ማንም ምንም አይልም፡፡ በሞባይል ስልክ የሚወራው ከህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ ውጪ ከሆነ መራቅ ይቻላል፡፡ መኪና ውስጥ የሚወራ ከሆነ ግን የት ይደረሳል። እኔ በዚህ ደረጃም ቢሆን የድምጽ ብክለት አለ ነው የምለው፡፡የሚመለከተው አካል ሌላውን አዳርሶ እዚህም ብቅ ቢል መልካም ነው፡፡ እንደ ተሽከርካሪ የፍጥነት ወሰን ሞባይል የሚወራበት ልክ መወሰን ያለበት ይመስለኛል፡፡ ወይም በሞባይል ሲወራ ድምፁ ሰው እንዳይረብሽ ለማድረግ ምን መደረግ እንዳለበት ግንዛቤ ማስጨበጥም የሚያስፈልግ ይመስለኛል፡፡ግንዛቤ ለማስጨበጥ ብዙ ርቀት መጓዝም ላይስፈልግ ይችላል፡፡ አንዳንድ በጆሮ የሚያወሩ የሚመስሉ ሰዎች አሉ፡፡ ከእነሱ መማር ነዋ! በእርግጥ ይህን ሁሉ መንገድ ከሞባይል ጋር መጥተን ይህን ማለት ሊያስቸገር ይችል ይሆናል፡፡ ግን ምን ይደረግ? ከሞባይል ብዙ ኖረውም ያልተለወጡ ብዙ ናቸው፡፡ ልክ አገር ቤት ሆነው እንደሚያወሩት አይነቶች ማለት ነው፡፡ እዚህ ማዶ ሆነው እዚያ ማዶ ያለውን የሚያናግሩ የሚመስሉ ጥቂት አይደሉም፤ ለነገሩ ለቀባሪ አረዱት ነው የሚባለው፤ ታውቋቸዋላችሁ፡፡ ውሸቱ ደግሞ አያድርስ ነው፡፡ ከመገናኛ መርካቶ የሚሄደው አራት ኪሎ ሳይደርስ ሀብተጊዮርስ ነኝ ሲል ይሰማል፡፡ ይህን አይነቱን የስልክ ነጭ ውሸት የሰሙ አንድ እናት የሚሄዱበት አካባቢ የደረሱ መስሏቸው ወራጅ ወራጅ ማለታቸውን የሰማሁ መሰለኝ፡፡ ሰለማያውቀው ነገር አብዝቶ የሚያወራም ጥቂት አይደለም፡፡ በሞባይል የሚወራና የማይወራም አለ፡፡ አንዳንዶች ይህን አልተረዱም፡፡ ገበና መና ቀርቷል፡፡ ገበና ሲያወጡ ደንግጥ የማይሉ ጥቂት አይደሉም፤ በሞባይል ምድጃቸውን መቆስቆስ የሚቀራቸው እንዲሁ ጥቂት አይደሉም፡፡ ከትራንፖርት ሲወረድ የሚደረስበት ሁሉ ይወራል፡፡ እኛ ይህን ሁሉ ለመስማት እየተገደድን ነው። እኔንም የማነጋግረውንም የሚያውቅ የለም ብሎ ምስጢር ማውራትም ተገቢ አይሆንም፡፡የድምጽ ብክለት በህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪዎች ውስጥ በሬዴዮ እና ሙዚቃ አከፋፈትም ይብሳል፡፡ አሁን አሁን ደግሞ አውቶቡሶች ላይ ቴሌቪዥን ይከፈታል ፤ እኔ እንደምገምተው የሚከፈቱት ለተሳፋሪዎች ነው፡፡ ምቾታቸውን ለመጠበቅ፣ ድካም ሳይሰማቸው ያሰቡት ቦታ እንዲደርሱ፡፡ ድምጹ ግን በተመጠነ መልኩ መሆን ይኖርበታል፡፡ እውነታው እንደዚያ ሆኖ ግን አሽከርካሪዎች ለራሳቸው ብለው ነው የሚከፍቱት የሚያስኝ ሁኔታ ነው የሚስተዋለው፡፡ አንዴ ያጋጠመኝን ላንሳላችሁ፤ ከታሪፍ ጋር በተያያዘ ውዝግብ ይነሳል፡፡ተሳፋሪው ትክክል ነበሩ፡፡ ሾፌሩ ‹‹እኛ የምንሰራው በዚህ መልኩ ነው፤ ከፈለግህ ውረድ›› ብሎ ይናገራል፡፡ ተሳፋሪው ‹‹አልወርድም፤ ምን ታመጣለህ፤ መኪናው ያንተ አይደለም፤ህዝብ ለማመላለስ ፈቃድ አውጥተህ እየሰራህ ነው፡፡አረፈህ ንዳ፡፡›› አሉት፡፡ የምሱን አገኝ መሰለኝ ማሽከርከሩን ቀጠለ፡፡ ለራሳቸው ነው የሚከፍቱት የሚለውን ለማብራራት ነው ይህን ያመጣሁት፡፡ምርጫው የራሳቸው ነው፤ የፈለጉትን ጣቢያ ያሻቸውን ሙዚቃ እንዲሁም መዝሙር ይከፍታሉ፡፡ ይህም ትክክል ባይሆንም ሲከፍቱ ሌሎችን በሚረብሽ መልኩ ባይሆን መልካም ነው፤ የሚስተዋለው ግን ከዚህ በተቃራኒው ነው፡፡ክፉኛ እየተረበሹ ናቸው፡፡ መረብሽ ብቻም አይደለም እርስ በርስ የሚጨዋወቱ ካሉም እንዳይደማመጡ እያረጋቸው ነው፤ስልክ የሚያወሩም ካሉ እንዲሁ እንዳይደማመጡ ያደርጋል፡፡ በስንት መከራ ተነግሯቸው ነው ድምጽ የሚቀንሱት፡፡ በተለይ ታክሲዎቹ ታክሲው መሸታ ቤት እስከሚመስል ድረስ ሙዚቃ ይከፍታሉ፡፡ ሙዚቃው ደግሞ ቅጣምባሩ የጠፋ ነው፡፡ ባህላዊ አይሉት ዘመናዊ፣ ወዘተ፡፡ እሱንስ እንዳሻቸው፤ አሁን የከፋው የድምጹ ከጣሪያ በላይ መሆን ነው፡፡ አሽከርካሪ ስለመኪናው ደህንነት የሚከታተለው አንድም በድምጽ ነው ይባላል፡፡ በዚያ የሙዚቃ ጩኸት ውስጥ እንዴት ነው የመኪናውን ድምጽ ተከታትሎ ከአደጋ ራሱንም ተሳፋሪንም እንዲሁም መንገደኛንም መጠበቅ የሚችለው፡፡ከአራት ኪሎ ወደ ሜክሲኮ እየሄድን ባለበት ወቅት ያጋጠመኝን ላንሳላችሁ፤ እንደ መምሸት ብሏል፡፡ ሙዚቃ ጨርሶ መደማመጥ በማያስችል ደረጃ ተከፍቷል፡፡ ከፋቹ በልቡ እየጨፈረ እንደሆነ ተሰማኝ፡፡ አሸሼ ገዳሜው ያንገሸገሸው ተሳፋሪ ታዲያ ረዳቱን ጮክ ብሎ ይጣራል፤ማን ሰምቶ፡፡ መኪና መደብደብ ተከተለ፡፡ ይሄኔ ረዳቱ ሰማ፤ ጆሮውን ወደ ተሳፋሪው ቀስሮ ምን ፈለግህ በሚል ሰሜት ይዞራል፡፡ ተሳፋሪው ቢራስ የላችሁም? ሲል ይጠይቀዋል፡፡ረዳቱ ምንም ሳይል ፊቱን አዞሮ ሾፌሩን የሆነ ነገር ሲለው የሙዚቃውም ድምጽ ትንሽ ተቀነሰ፡፡አዲስ ዘመን ኅዳር 23/2012ዘካርያስ
https://www.press.et/Ama/?p=23488
539
1መዝናኛ
“የኢትዮ -ሱዳን የድንበር ግጭት የአገሪቱን ልማትና ሰላም የማይፈልጉ ኃይሎች ሴራ ነው” ዶክተር ደመቀ አጭሶበአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣ የፖሊቲካል ሳይንስና የዓለም አቀፍ ግንኙነት ትምህርት ክፍል መምህር
ሀገር አቀፍ ዜና
January 8, 2021
33
ዋቅሹም ፍቃዱ አዲስ አበባ፡- ኢትዮጵያና ሱዳን ለዘመናት አብረው በሰላም የኖሩና ሰፊ ድንበር የሚጋሩ ጎረቤት አገራት ቢሆኑም በቅርብ ጊዜ በድንበር አካባቢ የተፈጠረው ግጭት ከድንበር በዘለለ የኢትዮጵያን ልማትና ሰላም የማይፈልጉ ሃይሎች አገሪቱን የማተራመስ ሴራ መሆኑ ተገለፀ:: በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣ የፖሊቲካል ሳይንስና የዓለም አቀፍ ግንኙነት ትምህርት ክፍል መምህር ዶክተር ደመቀ አጭሶ የድንበር ግጭቱን አስመልክቶ በተለይ ለአዲስ ዘመን እንዳስታወቁት፤ የኢትዮጵያና ሱዳን ሰፊ ድንበር የሚጋሩ፣ ለዘመናት በሰላም አብረው የኖሩ ሕዝቦች ናቸው።በአገራችን እየተካሄደ ያለውን የሕግ ማስከበር ሂደት ተከትሎ ሱዳን በድንበር አካባቢ በኢትዮጵያ ላይ ጦርነት መክፈቷ ያልተለመደ ክስተት መሆኑን የጠቆሙት ዶክተር ደመቀ፤ ከግጭቱ በስተጀርባ የአገራችንን ሰላም የማይፈልጉ ግብጾችና የኛው አኩራፊ ሃይሎች መኖራቸው ቅንጣት አያጠራጥርም ብለዋል:: ኢትዮጵያ ከግብጽ ይልቅ የሱዳን ታሪካዊ ወዳጅና አጋር መሆኗን ያመለከቱት ዶክተሩ፤ እ.ኤ.አ በ1973 እስከ 1983 በኮሎኔል ኒሜሪ ዘመን በታሪክ ተረጋግታ የማታውቀው ሀገር ሱዳን ለአስር ዓመታት ያህል በንጉሥ ኃይለ ሥላሴ እገዛ ሰላም ሰፍኖባት እንደነበር አስታውቀዋል:: በወቅቱ አንፃራዊ ሰላም የሰፈነው ኢትዮጵያ በአዲስ አበባ ኮርድ አማካይነት ለደቡብ ሱዳኖች እውቅና ሰጥታ ወደ ፌዴራል መንግሥት እንዲካተቱ በማገዟ እንደሆነም አመልክተዋል::እ.ኤ.አ በ1989 በወታደራዊ መፈንቅለ መንግሥት ሥልጣን በያዙት በኮሎኔል ኦማር አልበሽር ዘመንም በደቡብ ሱዳንና በሱዳን መካከል በተፈጠረው ግጭት፣ በተለይ በዳርፉር ግጭት አስከፊ ሰብዓዊ ቀውስ እንዳይፈጠር የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪ ሃይል ድርሻ ጉልህ መሆኑንም ጠቁመዋል::ሱዳን በዓባይ ወንዝ፣ በድንበር፣ በህዝቦች አሰፋፈር ወይም ትስስርና በሌሎች ጉዳዮች ከኢትዮጵያ ጋር የተሳሰረች በመሆኑዋ፤ አገሪቱን በጥንቃቄ መያዝ እንደሚያስፈልግ ገልፀው፤ የህዳሴው ግድብ ድርድር ፍትሐዊ እንዲሆን ሱዳን ለኢትዮጵያ ያደረገችው ድጋፍ ቀላል ባይሆን ግብጾች ፍላጎታቸውን ለማሳካት ሱዳንን አጥብቀው እንደሚፈልጉ መዘንጋት የለብንም ብለዋል:: በእጅ አዙር ኢትዮጵያን ለመጉዳት ፈልጋ ነው እንጂ፤ ግብጽ በታሪክ የሱዳን አጋዥና ወዳጅ ሆና እንደማታውቅ ይልቁን ከቅኝ ገዥዋ ከእንግሊዝ ጋር በመሆን ደቡብና ሰሜን ሱዳንን በሃይል መግዛቷን ዶክተሩ አስታውቀዋል። እ.ኤ.አ በ1929 እና በ1959 የዓባይ ውሃን አጠቃቀም አስመልክቶ በግብጽና በሱዳን መካከል የተደረገው ስምምነት እንኳ የሱዳንን ብሔራዊ ጥቅም በእጅጉ የሚጋፋ መሆኑን በማስታወስ፤ ግብጽ በታሪክ ሱዳንን ከመጉዳት ወደኋላ ያለችበት ዘመን እንዳልነበር አስታውቀዋል::እንደ ምሁሩ ገለፃ፣ ሱዳን በብዙ ምክንያቶች በርካታ ጥንቃቄ የምትፈልግ ጎረቤት አገር ናት:: አንደኛ ሱዳን በታሪኳ ዘመናዊ /ህዝባዊ/ መንግሥት አቋቁማ ስለማታውቅ በዘመናዊ መንገድ የመደራደር አቅሟ አስተኛ ነው:: በሌላ በኩል ደግሞ ሁኔታን በማየት አቋሟን የምትቀያይር አገር ናት:: በኢትዮጵያ በኩል ነገሮች ጥሩ ሲሆኑ ወደ ኢትዮጵያ ፣ ሲከፋት ደግሞ ከግብጽ ጋር የመወገን አዝማሚያ አላት:: ሌላው ችግሯ ደግሞ አሁን አገሪቱን እያስተዳደሩ ያሉ ሃይሎች በተለይ ወታደራዊ ሃይሉ የውስጥ ችግሩን በማዳፈን ሥልጣን ላይ ለመቆየት ከግብጽ ድጋፍ ለማግኘት ከኢትዮጵያ ጋር የሚጋጨውን የግብጽ አጀንዳ ለማራመድ ይገደዳል ያሉት ዶክተር ደመቀ፤ ለዚህ ማሳያ ደግሞ የሱዳን ሚሊሻዎች በድንበር አካባቢ እየፈጠሩ ያሉት ችግር በቂ ነው ብለዋል::ኢትዮጵያ በታሪክ የሌላውን ድንበር ጥሳ ባታውቅም፣ የግብጽም ሆነ የሌሎች አኩራፊ ሃይሎች ድብቅ ዓላማ ለማክሸፍ፣ የኢትዮጵያ መንግሥት የአገራችን ሉዓላዊነትን ባስከበረ መልኩ የሱዳንንም ጥቅም ባልጎዳ ሁኔታ ታሪካዊ ሁኔታዎችን ግንዛቤ ውስጥ በማስገባት ድንበር የማካለል ሥራ ከወዲሁ መጀመር እንዳለባት ጠቁመዋል። ሰላም ማውረድ በአንድ አገር ፈቃደኝነት ብቻ የሚረጋገጥ ስላልሆነ በሌላኛው ወገን ከዲፕሎማሲ አልፎ በጉልበት ተገፍቶ በአገር ሉዓላዊነት ላይ የሚመጣው ማንኛውንም ጥቃት ለማስተናገድ ታሪካችንም ስለማይፈቅድ መመከት የመጨረሻ አማራጭ እንደሚሆን ገልፀዋል:: አሁን የተፈጠረው ችግር በጥንቃቄ ካልተያዘ በብዙ ነገሮች የተሳሰሩ የምሥራቅ አፍሪካ አገራትንም ቀውስ ውስጥ ሊከት እንደሚችልም ምሁሩ አሳስበዋል::አዲስ ዘመን ታህሳስ 30/2013
https://www.press.et/Ama/?p=39077
452
0ሀገር አቀፍ ዜና
የተፃፈበትን የብር ኖት አትቀበሉ በሚል እየተሰራጨ ያለው መረጃ መሠረተ ቢስ መሆሙ ተገለፀ
ሀገር አቀፍ ዜና
January 8, 2021
12
 በጋዜጣው ሪፖርተር አዲስ አበባ ፦ የተፃፈበትን የብር ኖት አትቀበሉ በሚል እየተሰረጨ ያለው መረጃ መሠረተ ቢስ መሆኑን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ አስታወቀ።ባንኩ ለዝግጅት ክፍሉ በላከው መግለጫ እንደሚታወቀው፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ አዲስ የብር ኖት አሳትሞ ሥራ ላይ አውሏል። ከመስከረም 6 ቀን 2013 ዓ.ም እስከ ታህሳስ 6 ቀን 2013 ዓ.ም በመላ አገሪቱ የብር ኖት ቅያሪ ሲያካሂድ ቆይቷል፡፡የብር ኖት በከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ የሚታተም የሕዝብ ሀብት መሆኑን በመግለጫው የጠቆመው ባንኩ፣ የብር ኖቱ በጥንቃቄ ተይዞ ሕብረተሰቡ ለረጅም ጊዜ ሊገለገልበት እንደሚገባ አመልክቷል። ከዚህ አንፃር ሆን ተብሎ ወይም በቸልተኝነት በብር ኖት ላይ ጉዳት እንዳይደርስበት እንዲሁም ብዛት ያለው ገንዘብ ሕግን ባልተከተለ መልኩ ያለአግባብ እንዳይከማች ለማድረግ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ መመሪያ ቁጥር CMD/01/2020 ማውጣቱ አስታውሷል፡፡በመሆኑም፣ የብር ኖቱ ረጅም ጊዜ እንዲያገለግል በማስብ) በብር ኖቱ ላይ መፃፍ፣ መቅደድና በቀለም ማበላሸት፣ የትኛውንም ዓይነት ጉዳት ማድረስና ምልክቶቹን ያለፈቃድ ማባዛት የተከለከለና በሕግ የሚያስጠይቅ መሆኑን አስታውቋል።ለማስታወቂያሥራ ከተፈለገ ለማባዛት የባንኩን ፈቃድ ማግኘት አስፈላጊ መሆኑን ጠቁሞ፣በጣም የተጎዱ የብር ኖቶች ሲያጋጥሙ ከዝውውር ስለሚወጡበት ሁኔታ ዝርዝር መመሪያ እየተዘጋጀ መሆኑን ገልጿል።ባንኩ መመሪያውን ወደ አማርኛ በማስተርጎምና በማብራራት ስለብር ኖት አጠቃቀም በየጊዜውለህብረተሰቡ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራ የሚሠራ መሆኑን አመልክቶ፣ “የተፃፈበትን የብር ኖት አትቀበሉ” እየተባለ የሚናፈሰው ወሬ መሠረተ ቢስ መሆኑን አስታውቋል፡፡አዲስ ዘመን ታህሳስ 30/2013
https://www.press.et/Ama/?p=39076
177
0ሀገር አቀፍ ዜና
በመተከል ዞን የማንቡክ ከተማ ነዋሪዎች የፀጥታ ኃይል አባላት ሰንጋዎችን አበረከቱ
ሀገር አቀፍ ዜና
January 8, 2021
18
 መተከል (ኢዜአ) በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን የማንቡክ ከተማ ነዋሪዎች በዞኑ ሕግ በማስከበር ሥራ ላይ ለሚገኘው የፀጥታ ሃይል አባላት ለገና በዓል 210 ሺህ ብር ወጪ የተደረገባቸው ስድስት የእርድ ሠንጋዎችን አበረከቱ።በፌዴራል መንግሥት የተቋቋመው ግብረ ሃይል በመተከል ዞን ፀረ ሰላም ሃይሎችን በማደንና በአካባቢው ዘላቂ ሰላምና መረጋጋት ለመፍጠር እየሠራ ይገኛል።ግብረ ሃይሉ ከዞን እስከ ቀበሌ ባለው መዋቅር በተንኮልና ሴራ ውስጥ የገቡ አመራሮችን የማጥራት፣ ህዝባዊ አንድነትን የማጠናከርና ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ችግሮችን የመፍታት ሥራዎችን አጠናክሮ ቀጥሏል። በአካባቢው በዜጎች ላይ ጥቃት በመፈፀም በተለያዩ አካባቢዎች የሚንቀሳቀሱ ሽፍቶችን በማደን ለሕግ የማቅረብ ሥራም በማከናወን ላይ ነው።ግብረ ሃይሉ ባከናወነው ተግባር በርካታ አካባቢዎች ወደ ቀደመ ሰላማቸው እየተመለሱ ሲሆን ህዝባዊ የውይይት መድረኮችም በመካሄድ ላይ ናቸው።በዚህም ደስተኞች ነን ሲሉ አስተያየታቸውን የሰጡ በዞኑ ዳንጉር ወረዳ የማንቡክ ከተማ ነዋሪዎች ተናግረዋል።ነዋሪዎቹ ለፀጥታ ሃይሉ ያላቸውን ድጋፍ ለማሳየት የበዓል መዋያውን ማበርከታቸውን ገልፀዋል።ግብረ ሃይሉ በአካባቢው ስላመጣው አንፃራዊ ሰላም ደስተኞች መሆናቸውን የገለፁት ነዋሪዎቹ፤ ድጋፋቸው እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።በዳንጉር ወረዳ ህዝቡ ባደረገው ውይይት ህዝብን ከህዝብ የማጋጨትና ማንነትን መሰረት ያደረገ ጥቃት እንዲፈፀም ያደረጉ አካላት ተለይተው እርምጃ እንዲወሰድባቸው ጠይቀዋል።የአካባቢው ማህበረሰብ ማንኛውንም በዓል በጋራ የማክበርና የአብሮነት ልምድ እንዳለው የገለፁት የአካባቢቅው ሽማግሌዎች “የገና በዓልን በለመድነው አብሮነት እያከበርን ነው” ብለዋል።ማህበረሰቡ የለገሰውን ስጦታ የተረከቡት ሻለቃ ፍቃዱ ጃፍራ ለተደረገው ድጋፍ ሁሉ በሠራዊቱ ስም አመስግነዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 30/2013
https://www.press.et/Ama/?p=39087
185
0ሀገር አቀፍ ዜና
በአፍሪካ የጋራ የነፃ ገበያ መመስረት የኢንቨስትመንት ፍሰትን እንደሚያሳድግ ተገለፀ
ሀገር አቀፍ ዜና
January 8, 2021
19
ራስወርቅ ሙሉጌታአዲስ አበባ፦ በአፍሪካ የጋራ የነፃ ገበያ መመስረት የኢንቨስትመንት ፍሰትን ለማሳደግና ግሽበትን ለመቀነስ ብሎም የእውቀት ሽግግር እንዲስፋፋ ለማድረግ እንደሚረዳ ተገለፀ። የአፍሪካ የጋራ የነፃ ገበያ ትስስር በጥንቃቄ ከተመራ እያንዳንዱን የአፍሪካ ሀገር ተጠቃሚ እንደሚያደርግም ተጠቆመ። በዩኒቲ ዩኒቨርሲቲ ኢኮኖሚክስ ትምህርት ክፍል መምህር የሆኑት ዶክተር ደመላሽ ሀብቴ በጋራ የነፃ ገበያ ዙሪያ ከአዲስ ዘመን ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ፣ በአፍሪካ አገራት መካከል የተቀናጀ የኢኮኖሚ ግንኙነት ባለመኖሩ አህጉሪቱ ከሰማንያ በመቶ በላይ የንግድ እንቅስቃሴዎች እያደረገች ያለችው ከአውሮፓ፣አሜሪካና እስያ አገራት ላይ ጥገኛ በመሆን ነው። በዚህም የተነሳ አህጉሪቱ ደካማ የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ፣ ከፍተኛ የዋጋ ግሽበት የሚከሰትባትና ዝቅተኛ የእውቀት ሽግግር የሚስተዋልባት ሆና ቆይታለች። ከዚህ ቀደምም የአፍሪካ አገራት እርስ በእርስ ያላቸውን የንግድ ትስስር ለማሳደግ የተሠሩ ጅምሮች ቢኖሩም ውጤታማ ባለመሆናቸው እስከ አሁን እርስ በእርስ ያላቸው ግንኙነት ከሃያ በመቶ የዘለለ አልነበረም ያሉት ዶክተር ደመላሽ፤ በተመሳሳይ ደረጃ የሚገኙ የኢንዱስትሪ ግብአቶችንም ሆነ እንደ ነዳጅ ያሉ ያለቀላቸውን ምርቶች አፍሪካ አገራት ውስጥ በስፋት እየተመረቱ ቢሆንም ሌሎች ተጠቃሚ ጎረቤት አገራት የሚያስገቡት ካደጉት አገራት ነው ብለዋል። በአህጉሪቱ የተጠናከረ የንግድ ልውውጡና የዳበረ የነፃ ገበያ ተፈጥሮ የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴው የተቀላጠፈ እንዲሆንና በሚጠበቀው ደረጃ እንዲያድግ የአፍሪካ አገራት የንግድ ልውውጥ በጋራ ነፃ ገበያ ሊጠናከርና ሊስፋፋ ይገባዋል ብለዋል። በተጨማሪም የአፍሪካ የጋራ የነፃ ገበያ መመስረትና ወደተግባር መግባት አፍሪካ እንደ አህጉር ከሌላው ዓለም ጋር ለሚኖራት የንግድና ሌሎች ኢኮኖሚያዊ ግንኙነቶች በር የሚከፍት እንደሚሆንም አመልክተዋል። ነፃ ገበያው በአሁኑ ወቅት በስፋት የሚታየውን ወደመካከለኛው ምሥራቅና ሌሎች አገራት የሚደረገውን የሰው ኃይል ፍልሰት ወደአፍሪካ እንዲሆን ያግዛል ያሉት ዶክተር ደመላሽ፤ ከዚሁ ጋር በተያያዘ የእውቀት ሽግግሩም በየደረጃው የተቀላጠፈ እንዲሆን ይረዳል፤ በአገራት መካከል የሚኖረውም የዲፕሎማሲ ግንኙነት የተጠናከረ እንዲሆን ያግዛል ብለዋል። የአፍሪካ አገራት የጋራ የነፃ ገበያ ከመሰረቱ ከፈለጉ በዶላር ወይንም በራሳቸው በሀገራቱ የመገበያያ ገንዘብ እንዲሁም እቃ በእቃ የመገበያየት ዕድሉ ስለሚኖራቸው የውጭ ምንዛሬ እጥረትን እንደሚቀንስ ጠቁመው፤ ይህም ሆኖ የመንግሥት ታክስ ሊቀንስ ይችላል እንዲሁም በአገራቱ መካከል የተመጣጠነ ዕድገት ባለመኖሩ የሚፈጠር ጫና ሊኖር እንደሚችል አመልክተዋል።የአፍሪካ የጋራ የነፃ ገበያ ትስስር በጥንቃቄ እየተቆጣጠሩ መሥራት፣ ትልልቅ ተቋማትን መገንባትና ጥራት ያላቸውን ምርቶች በማምረት ለጠንካራ ውድድር መዘጋጀት ከተቻለ እያንዳንዱ የአፍሪካ አገር ተጠቃሚ ይሆናል ሲሉም ዶክተር ደመላሽ ተናግረዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 30/2013
https://www.press.et/Ama/?p=39078
303
0ሀገር አቀፍ ዜና
የአዲስ ዘመን ስፖርት ትዝታዎች
ስፖርት
June 9, 2020
30
በ1933 ዓ.ም ተቋቁሞ በየእለቱ ለአንባቢያን የሚደርሰው አዲስ ዘመን ጋዜጣ ባለፉት ሰባ አምስት ዓመታት በስፖርቱ ዙሪያ የተለያዩ የአገር ውስጥ ውድድሮችንና ታላላቅ ዓለም አቀፍ የስፖርት መድረኮችን በመከታተል ታሪካዊ ዘገባዎችን አስነ ብቧል። ከታላቁ የስፖርት መድረክ ኦሊምፒክ አንስቶ እስከ ዓለም ዋንጫና የአፍሪካ ዋንጫ እንዲሁም የዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮናዎች ድረስ በርካታ አይረሴ ዘገባዎችን ለአንባቢዎቹ እንካችሁ ብሏል። አዲስ ዘመን አሁን ሰባ ዘጠነኛ ዓመቱን እያከበረ በሚገኝበት በእዚህ ወቅት ካለፉት ሰባት አስርት ዓመታት በላይ በተለይም ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ መድረኮች ኦሊምፒክንና የአፍሪካ ዋንጫን በመሳሰሉት መድረኮች በደመቀችባቸው ዘመናት ለንባብ ያበቃቸው ታላላቅ ዘገባዎች የስፖርቱ ማህደር አንድ አካል ናቸው። ከነዚህ ታሪካዊ ዘገባዎች መካከልም በተወዳጁ የአፍሪካ ዋንጫ በተለይም ኢትዮጵያ ባነሳችው ዋንጫ ወቅት የነበረውን ታሪካዊ ዘገባ እየቀነጨብን መለስ ብለን እንመለከታለን።አዲስ ዘመንና የአፍሪካ ዋንጫ ትዝታዎቹኢትዮጵያ የአፍሪካ እግር ኳስ የመሰረት ድንጋይ ያኖረች አገር እንደመሆኗ መጠን የመድረኩን ጣፋጭ ድል ለአንድ ጊዜም ቢሆን መጎንጨት ችላለች። ኢትዮጵያ በወርቃማ የእግር ኳስ ዘመኗ የአፍሪካ ዋንጫን ከአምስት አስርት ዓመታት በፊት ማንሳት ስትችል አዲስ ዘመን ጋዜጣ ኢትዮጵያ አዘጋጅ አገር እንደመሆኗ መጠን ከመስተንግዶው ጀምሮ እስከ ዋንጫው ፍፃሜ ዘገባዎችን ለአንባብያን ሲያደርስ የነበረ ግንባር ቀደም የህትመት ውጤት ነበር። ጥር 6 ቀን 1954 የአፍሪካ ዋንጫ አስተናጋጇ ኢትዮጵያ የመክፈቻ ጨዋታውን ከቱኒዚያ ጋር ያደረገችውን ጨዋታ እውቁ የስፖርት ጋዜጠኛ ሰለሞን ተሰማ ጥር 9 ቀን 1954 ለአንባቢያን በበቃው አዲስ ዘመን ጋዜጣ የስፖርት አምድ ላይ ያቀረበው ዘገባ የሚከተለውን ይመስል ነበር። « የሦስተኛው ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫ የፉትቦል ውድድር ጥር 6 ቀን 1954 ዓም ከቀትር በኋላ በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ስታድዮም ላይ በኢትዮጵያና ቱኒዚያ ብሔራዊ ቡድን መካከል ተጀምሮ የኢትዮጵያ ቡድን 4ለ2 ማሸነፉን ከጨዋታው ስፍራ በመገኘትና በራዲዮን በመስማት ሴት ወንዱ፤ ልጆችና ሽማግሌዎች ተባብለው ሳይከፋፈሉ መላው የኢትዮጵያ ህዝብ ከልብ የተደሰተ በመሆኑ ሰሞኑን በመስሪያ፤ በመኖሪያ፤ በሆቴልና በቡና ቤቶች፤ በገበያና ንግድ ሱቆች፤ በሴይቼንቶና በአውቶብስ ውስጥ እንዲሁም በልዩ ልዩ አደባባዮች የሚወራው ወሬ አንዳችም ጣልቃ ሳይገባበት የኢትዮጵያን ቡድን አድናቆት የተመልካችን ሁኔታና ይኽንኑ የመሳሰሉ ወሬዎች ብቻ ናቸው»። ሰለሞን የጨዋታውን መክፈቻ በእዚህ መልኩ ካካተተ ከቀናት በኋላ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በተመሳሳይ ውጤት ግብፅን በፍፃሜ ጨዋታ በመርታት እስካሁን የምንጠቅሰውን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ትልቅ ስኬት ማስቀረት ችሏል። በወቅቱም አዲስ ዘመን ማክሰኞ ጥር 15 ቀን 1954 ዓም ባወጣው እትሙ የፊት ገፅ ላይ « ቀልጣፋው የኢትዮጵያ ምርጥ ቡድን የግብፅን ቡድን 4ለ2 አሸነፈ» በሚል ርእስ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ለቡድኑ አምበል ሉቺያኖ የአፍሪካ ዋንጫውን ሲያበረክቱ የሚያሳይ ፎቶ ግራፍ ይዞ ወጥቷል። የዘገባው መግቢያም የሚከተለውን ይመስላል« ለ3ኛው የአፍሪካ ዋንጫ የሚደረገው የእግር ኳስ ውድድር ጥር 13 ቀን 1954 ዓም ባለፈው እሁድ ቁጥሩ ከ5o ሺህ የማያንስ ህዝብ በተሰበሰበበት በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ስታድዮም ተደርጎ ፤ የኢትዮጵያ ምርጥ ቡድን የግብፅን ብሔራዊ ቡድን 4ለ2 አሸንፎ የአፍሪካን ዋንጫ ወስዷል። በሁለቱ አፍሪካዊ ቡድኖች መካከል የሚደረገውን ውድድር ለማየት በስታድየሙ ውጭና ግቢ አሰፍስፎ ይጠብቅ የነበረው ተመልካች ታሪካዊ አቀባበል የሚመሳሰል ነበር። ውድድሩ ከመጀመሩ በፊት ግርማዊ ንጉሰ ነገስት ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ የኢትዮጵያ ንጉሰ ነገስት መንግሥት ወራሽ ልዑል መርዕድ አዝማች አስፋ ወሰንን፤ ልዑል ራስ እምሩንና ሌሎችንም የክብር ተከታዮቻቸውን አስከትለው በፖሊስ ሰራዊት ሞተር ብስክሌተኞች ታጅበው ከስታድየም ደረሱ»።በኢትዮጵያ እግር ኳስ ከፍተኛ ንቅናቄን በፈጠረው የ2o13 የደቡብ አፍሪካ ዋንጫም አዲስ ዘመን ከዘመኑ ጋር ተጉዞ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከሰላሳ አንድ ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካ ዋንጫ ሲመለስ በርካታ ጨዋታዎችን ተከታትሎ ዘገባዎችን ለአንባቢ አቅርቧል። በአሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው እየተመራ ቤኒንን ከእዚያም ሱዳንን በመጨረሻ የማጣሪያ ጨዋታ በደርሶ መልስ ውጤት ዋልያዎቹ ድል አድርገው ወደ አፍሪካ ዋንጫ ሲመለሱ ጥቅምት 3ቀን 2oo5 ዓም ይዞት በወጣው እትሙ በፊት ገፁና በስፖርት ባለቀለም ገፁ የአሰልጣኞች፤ ተጫዋቾችና ደጋፊዎች ስሜትን የሚገልፁና በቃለ መጠይቅ የዳበሩ በርካታ ዘገባዎችን ማቅረብ ችሏል።አዲስ ዘመን ሰኔ 1/2012  ቦጋለ አበበ
https://www.press.et/Ama/?p=34012
511
2ስፖርት
‹‹በአስቸጋሪ ጊዜ ውስጥም ቢሆን የግል ባለሀብቱ ከስፖርቱ ጎን ሊቆም ይገባል›› -አቶ ነብዩ ሳሙኤል ፈረንጅ
ስፖርት
June 10, 2020
23
በዛሬው የስፖርት ገፅ አምዳችን ከአንድ እንግዳ ጋር ጭውውት ለማድረግ ወደን አንድ ርዕሰ ሃሳብ መዘናል። የጋበዝናቸው የስፖርቱ ባለውለታ በፈተና ውስጥም ሆኖ የስፖርቱን ዘርፍ በተለይ የግል ባለሃብቱ ሊደግፈው እንደሚገባ የራሳቸውን የህይወት ተሞክሮ በማንሳት አጫውተውናል። እኛም የስፖርቱን ወዳጅ ስኬታማ እንቅስቃሴና የወቅታዊ ጉዳይ ምክረ ሃሳብ በዚህ መንገድ አስቀምጠነዋል። አቶ ነብዩ ሳሙኤል ፈረንጅ በአሜሪካን አገር ኑሯቸውን ያደረጉ ቢሆኑም ኢትዮጵያዊ ዜግነታቸውን ግን አልቀየሩም። በዲስትሪክት ኦፍ ኮሎምቢያ ዩኒቨርስቲ የኮምፒውተር ሳይንስ ትምህርት አጥንተው ዲግሪያቸውን ይዘዋል። ለዓመታት የተለያዩ የግል ስራዎች ሲሰሩም ቆይተዋል። ባለትዳር እና የአራት ልጆች አባት ሲሆኑ አሁን በአገራቸው ላይ በኮንስትራክሽን እና በሌሎች ዘርፎች ላይ ተሰማርተው እየሰሩ ይገኛሉ። በተለይ ደግሞ የጎልፍና የብስክሌት ስፖርቶችን ለማሳደግ በሚደረገው ጥረት ላይ ሰፊ አበርክቶ እንዳላቸው የስፖርቱ ባለሙያዎች ሲናገሩ ይደመጣል። «ትምህርት ቤት በነበርኩበት ጊዜ የመንግስቱ ወርቁ፣ ሉቺያኖ ቫሳሎ፣ የበረኛው ጌታቸው ዱላ አድናቂ ነበርኩ» በማለት የሁለተኛ ደረጃ ተማሪ በነበሩበት ዘመን በአገር ውስጥ ትልቅ ስፍራ የነበራቸው እግር ኳስ ተጫዋቾች ይሳቡ እንደነበር ጊዜውን መለስ ብለው እያስታወሱ አጫውተውናል። ስፖርት ወዳድነታቸው ዘርፉን እንዲደግፉ ገፊ ምክንያት ሆኗቸዋል። በተለይ የብስክሌት፣ የጎልፍና ጠረጴዛ ቴኒስ ስፖርት ላይ ባላቸው ጠንካራ ተሳትፎ ይታወቃሉ። አሁንም ድረስ በአዲስ አበባ ደረጃ የሁለቱም የበላይ ጠባቂ ናቸው። የብስክሌት ስፖርት አቶ ነብዩ በርካታ ፈተናዎች የተጋረጠበትን የአዲስ አበባ ብስክሌት ፌዴሬሽን ከአመራሮች ጋር በመተባበር እየደገፉት ይገኛሉ። ከስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች አካባቢ የማይጠፉት ሰው እንዴት ወደ ብስክሌቱ ዘርፍ ሊመጡ ቻሉ? ምን አይነት ተግባራትስ እስካሁን ድረስ አከናውነዋል። አቶ ገረመው ደንቦባ በኢትዮጵያ የሳይክል ስፖርት ጅማሮ ትልቅ ስፍራ አላቸው። እኚህን አንጋፋ ሰው ማመስገን ክብር ለሚገባው ተገቢውን ክብር ከመስጠት ባለፈ ስፖርቱ እንዲነቃቃ ትልቅ እድል የሚከፍት በመሆኑ፤ ከአዲስ አበባ ስፖርት ኮሚሽን እንዲሁም ከብስክሌት ፌዴሬሽኑ ጋር በመተባበር የሃሳቡ ጠንሳኝና ቀዳሚ ስፖንሰር በመሆን 623 ኪሎ ሜትር የሸፈነ የመጀመሪያው «ጉዞ ወደ አባይ የሳይክል ቱር» በማዘጋጀት እኚህ አንጋፋ ሰው በክብር እንግድነት እንዲገኙ እና ለወጣት ስፖርተኞቹ ብርታት እንዲሆኑ ማድረግ ችለዋል። ከአንድ ዓመት በፊትም የኢትዮ-ኤርትራን የሰላም ስምምነት ምክንያት በማድረግ ከአዲስ አበባ አስመራ አገር አቋራጭ የብስክሌት ስፖርት ቱር ከኮካ ኮላ ኢስት አፍሪካን ቦትሊንግ ጋር በመተባበር እንዲካሄድ የአንበሳውን ድርሻ ወስደዋል። በዚህ ከሺህ በላይ ኪሎ ሜትሮች የሸፈነ ውድድር ላይ 150 የሚጠጉ ወጣት ብስክሌተኞች፣ጋዜጠኞችና የሚመለከታቸው የስፖርት አካላት ተሳታፊ ሆነዋል። በጊዜው ከሌሎች ስፖርቶች ቀዳሚ በመሆን በብስክሌትና የጠረጴዛ ቴኒስ ሰላም የማብሰር ፈር ቀዳጅ ብስራት ሲሰማ እኚሁ የዘርፉ ወዳጅ ባለሀብት ዋናው መንገድ ቀያሽ ነበሩ። የጎልፍ ስፖርት አዲስ ምዕራፍ በአዲስ አበባ ጎልፍ ክለብ ጨዋታ በማድረግ የሚታወቁት አቶ ነብዩ ስፖርቱ በኢትዮጵያ ውስጥ ተስፋፍቶ ዓለም አቀፍ እውቅና እንዲያገኝ ትልቁን ድርሻ በመውሰድ ከፊት መስመር ተሰላፊ ናቸው። ከእንግሊዝ ኤምባሲ ጎልፍ ኮርስ፣ ከኮሚሽነር ዘሪሁን ቢያድግልኝ ፣ በአሁኑ ሰአት የኢትዮጵያ ጎልፍ ፕሬዚዳንት ከሆነው ከአቶ አበባው ቢሆነኝና ሌሎች የኮሚቴ አባላቶች ጋር በመሆን የመጀመሪያውን የጎልፍ ማህበር እንዲቋቋም አድርገዋል። የጎልፍ ስፖርትም ልክ እንደሌሎቹ ፌዴሬሽኖች ሁሉ በአገር ውስጥም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅና እንዲያገኝ በቻሉት አቅም ደግፈዋል። አሁንም እየደገፉ ይገኛሉ። «በወቅቱ ብዙ ኢትዮጵያዊ ጎልፈኞች አልነበሩም። ከ60 በመቶ በላይ አባላቱ የውጪ ዜጎች ነበሩ» በማለት ለስፖርቱ መሰረተ ለመጣል ብዙ ስራዎች መስራታቸውን ያስታውሳሉ። በራሳቸው ድርጅትና የገንዘብ ወጪም የመጀመሪያውን ስፖንሰር ማድረግ ችለዋል። በግል ከመደገፍ ባሻገርም ስፖንሰሮች በማምጣት ጉልህ ድጋፍ አድርገዋል። በወቅቱ የአዲስ አበባ ስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነር የነበሩት አቶ ዘሪሁን ቢያድግልኝም ከእርሳቸው ጋር በመሆን ለምስረታው እና ህጋዊ ፍቃድ ማውጣቱ ላይ ትልቅ ስራ መስራታቸውን ይናገራሉ። ባለፉት ጥቂት ወራት ውስጥ በኮሮና ወረርሽኝ ምክንያት በርካታ ስፖርቶች ምንም አይነት እንቅስቃሴ እንዳያደርጉ በመንግስትና በፌዴሬሽኖች አማካኝነት እገዳ ተጥሎባቸዋል። በዚህ ምክንያት አዲስ እንቅስቃሴ እየተስተዋለ አይደለም። የአዲስ አበባ እና የኢትዮጵያ የጎልፍ ማህበራት የዚህ ክልከላ አካል ናቸው። ሆኖም ስፖርት ማህበራዊ ሃላፊነት መወጣትንም ስለሚጨምር በወረርሽኙ አማካኝነት ቀጥተኛ ተጋላጭ ለሆኑ ድጋፍ የሚፈልጉ ወገኖች እርዳታ የማስተባበር ስራዎችን ከመስራት አልቦዘኑም። የዚህ ስፖርት ቀጥተኛ ተሳታፊ የሆኑ አባላት እርዳታ በማሰባሰብ ለመንግስት ገቢ አድርገዋል። በተጨማሪ በጎልፍ ክለቡ ለሚገኙ ሰራተኞች ወረርሽኙ የፈጠረባቸውን ጫና ለመቀነስ በሚል (በአቶ ነብዩ ሳሙኤልን አስተባባሪነት) የፋሲጋ ሰሞን ከመቶ ሺ ብር በላይ በመሰብሰብ አጋርነታቸውን አሳይተዋል። የአጭር ጊዜ ግብን ለማሳካት የስፖርቱ ወዳጅና ደጋፊ የሆኑት አቶ ነብዩ ዓለም አቀፍ ልምድን በማጣቀስ ወቅቱን ባገናዘበ መንገድ ጥንቃቄ ሳይለይ የጎልፍ ስፖርት መቀጠል እንዳለበት ይናገራሉ። ይሄ የእለት ጉርሳቸውን ለመደጎም የሚጥሩ ደጋፊ ሰራተኞችን ኑሮ ለመደጎም እንደሚያስችል ይጠቅሳሉ። መንግስት ባወጣው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መመሪያ መሰረት ጎልፍ መጫወት ማቆማቸውን ይጠቅሳሉ። ሆኖም የጎልፍ ክለብ ማኔጅመንት በቅርቡ ከሱዳን ለመጡ ዜጎች ማቆያ እፈልገዋለሁ በማለት ማንም በግቢው ውስጥ እንዳይገባ መከልከሉን ይናገራሉ። በዚህ ምክንያት 168 ሰራተኞችና በሺህ የሚቆጠሩ ዜጎች የሚዝናኑበት ስፍራ ስራውን እንዳቆመ ይገልፃሉ። ሰራተኞቹም ከአገልግሎት ክፍያ (ሰርቪስ ቻርጅ) የሚያገኙት ገቢ በመቋረጡ ችግር ውስጥ መሆናቸውን ያነሳሉ። ለማቆያ በጎልፍ ክለቡ ግቢ ውስጥ የሚገኙት ዜጎች ከ3 የማይበልጡ በመሆናቸው አጠቃላይ ግቢውም በጣም ሰፊ ከመሆኑ አኳያ ማቻቻል ቢቻልና ስፖርታዊ እንቅስቃሴውም ሆነ ሬስቶራንቱ በጤና ጥበቃ ሚኒስቴር መመሪያ መሰረት በጥንቃቄ ቢቀጥል መልካም መሆኑን ያነሳሉ። ‹‹የጎልፍ አባላቱና ሌሎች ዜጎች በተንጣለለው ግቢ ውስጥ ተራርቆ በባለሙያ በኬሚካል እየተፀዳ የሩጫና እርምጃ ስፖርት ከዚህ ቀደም ይደረግ ነበር›› የሚሉት አቶ ነብዩ፤ አሁን ሙሉ ለሙሉ እንዲቆም መደረጉን ይገልፃሉ። ኢትዮጵያ ደረጃውን የጠበቀ ባለ 18 ጉድጓድ የጎልፍ ማዘውተሪያ ስፍራ እንዳላት አንስተውም፤ ይህ ቦታ በርካታ ሚሊዮን ዶላር ወጥቶበት የተሰራ መሆኑን ይናገራሉ፡፡ የአፍሪካ ህብረትን ጨምሮ በርካታ ዓለም አቀፍ ተቋማት መቀመጫ የሆነችው ኢትዮጵያ በዚህ መልካም አጋጣሚ መጠቀም እንዳለባትም ያምናሉ፡፡ ‹‹ጎልፍ ኮርሱ የተሰራው በንጉሱ ጊዜ ነበር። ሆኖም በደርግ ጊዜ የቡርዧ ጨዋታ ነው በሚል ተከልክሎ ስፍራው የራሺያ ወታደራዊ ካምፕ ሆኖ ቆይቷል›› የሚሉት አቶ ነብዩ፤ ስርአቱ ሲቀየር በኢህአዴግ ጊዜ ከነበረው ስታንዳርድ ይበልጥ ተሻሽሎ በ18 ጉድጓድ ደረጃውን በጠበቀ መንገድ ተሰርቶ እስካሁን ድረስ አገልግሎት እየሰጠ እንደሆነም ያነሳሉ። የጎልፍ ክለቡ በባህልና ስፖርት ቱሪዝም ሚኒስቴር ስር ሆኖ አገልግሎት መስጠት ቢጀምር የውጪ ምንዛሬን ለማግኘትና ቱሪዝምን ለማሳደግ ጠቀሜታ አለው የሚል ምክረ ሃሳብም ያነሳሉ። 34 የጎልፍ ማዘውተሪያ ያላት ጎረቤት አገር ኬኒያ እንዲሁም ታይላንድ ጎልፍን ከቱሪዝም ጋር በማያያዛቸው ተጠቃሚ መሆናቸውንም በምሳሌነት ይጠቅሳሉ። ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አሕመድ በተለይ በቤተ መንግስት ‹‹አንቲክ›› የሆኑ የአገር ሃብቶችን በማልማት ለምሳሌ ያህል በቤተ መንግስት ‹‹የአንድነት ፓርክን››፣ ‹‹የእንጦጦ ፓርክ››፣ ‹‹የሸገር ወንዞችን የማስዋብ ፕሮጀችክ›› እና ሌሎች አካባቢዎች ላይ ግንባታ አከናውነው ለአገር ጥቅም እንደቀየሩት በምሳሌነት መውሰድ እንደሚቻልም ይጠቁማሉ። ጎልፍንም በዚህ መንገድ ተመልክቶ ያለውን ሃብት መጠበቅና ይበልጥ ማልማት ያስፈልጋል የሚል ሃሳብም ያነሳሉ። በአሁኑ ሰአት የቱሪዝም ዘርፉን ሊያነቃቁ የሚችሉ መሪዎች ስላሉ ይበልጥ የሚደግፍ እንደሆነም ይናገራሉ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ በዘንድሮ ክረምት ከ5 ቢሊዮን በላይ ችግኝ እንዲተከል ጥረት እንደሚያደርጉት ሁሉ ይህንን የአገር ሃብት የሆነውን ‹‹ለምለማማ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራ›› በተገቢው ሚኒስትር መስሪያ ቤት ስር እንዲተዳደር በማድረግ ለያዝነው የብልፅግና ጉዞ አጋዥ እንዲሆን እንዲያመቻቹት ይጠይቃሉ። ‹‹የአዲስ አበባን ጎልፍ ክለብ የመከላከያ ፋውንዴሽን ቢያስተዳድረውም ልንኮራበት የሚገባ በእጃችን ያለ ሀብት ነው›› የሚሉት የስፖርቱ ወዳጅ በቱሪዝም ረገድ የሚያስገኘው ጥቅም ይበልጥ በባለሙያዎች ተጠንቶ አሁን ካለው የተሻለ እንዲሆን መሰራት ይኖርበታል ይላሉ። የአዲስ አበባ ከንቲባ የሆኑት ወጣቱ (በርሳቸው አባባል ኢነርጃይቲኩ) ኢንጅነር ታከለ ኡማ የጎልፍ ስፖርት ቢስፋፋ የሚያስገኘውን የቱሪዝም መነቃቃት በሳይንሳዊ መንገድ ቢያስጠኑትና እንዲስፋፋ አመራር እንዲሰጡ ጥያቄያቸውን ያቀርባሉ። በጥቅሉ የሁሉም ዜጎች አላማ ኢትዮጵያ ከድህነት ተላቅቃ ወደ ብልፅግና ለመውሰድ ስለሆነ ጉዳዩን ሊታሰብበት ይገባል ይላሉ። አቶ ነብዩ ሃሳባቸውን ሲያጠቃልሉ በአገራችን የሚገኙ ባለሃብቶች የተለያዩ ስፖርቶችን በመደገፍ፣ ስፖንሰር በማድረግና ግዜያቸውን በመስጠት ቢሳተፉ፤ ወጣት የሆነውን ትውልድ አምራች ዜጋ እንዲሆን አስተዋፅዖ ማበርከት ይቻላል ይላሉ። ለምሳሌ ያህል የአዲስ አበባ ጎልፍ ክለብ ባቋቋመው ኮሚቴ ምክንያት ባለፉት 13 ዓመታት ከኢትዮጵያ አየር መንገድ፣ የኤሜሬትስ አየር መንገድ፣ኬኒያ ኤርዌይስ፤ ሚድሮክና ቢጂአይ እንዲሁም ከኤምባሲዎች ዙምባቢዌ፣ስፔን፣ ቼክ ሪፐብሊክና ከአሜሪካ ኤምባሲዎች በርካታ ሚሊዮን ገንዘብ በማሰባሰብ ስፖርቱን ለመደገፍ እንደተቻለ ያነሳሉ። በመሆኑም በተመሳሳይ ባለሃብቶች ያላቸውን አቅምና ሃብት ለዚህ በጎ ዓላማ ይጠቀሙበት ሲሉ ምክረ ሃሳባቸውን በመናገር ይቋጫሉ። አዲስ ዘመን ሰኔ 3/2012ቦጋለ አበበ
https://www.press.et/Ama/?p=34121
1,065
2ስፖርት
ለእግር ኳስ አሰልጣኞች ስልጠና ሊሰጥ ነው
ስፖርት
June 9, 2020
15
በኢንስትራክተር አብርሃም መብራቱ እና በአሰልጣኝ አምሳሉ ፋንታሁን አማካኝነት በሀገራችን ላሉ የእግር ኳስ አሰልጣኞች ስልጠና ሊሰጥ መሆኑ ተነገረ።የአሰልጣኞች ስልጠናው በካፍ ኢንስትራክተር እና የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን አሰልጣኝ በሆነው አብርሃም መብራቱ የተዘጋጀ ሲሆን በዋናነትም በኢንስትራክተሩ ይሰጣል ተብሏል። በተጨማሪም በርካታ ኢትዮጵያውያን አሰልጣኞች ወደ አሜሪካና ስፔን ተጉዘው ስልጠና እንዲወስዱ ከዚህ ቀደም ሲያመቻቹ የነበሩት በአሜሪካ የሳክሬም የእግር ኳስ አካዳሚ ሴቶች ዳይሬክተር እና አሰልጣኝ አምሳሉ ፋንታሁን አማካኝነት ከአስር ቀናት በኋላ ይሰጣል። ስልጠናው በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ተሳታፊ ክለቦች ለሚያሰለጥኑ አሰልጣኞች በዋናነት የተዘጋጀ መሆኑ ተገልጿል። በተጨማሪም በሴቶች እግር ኳስ ላይ ለተሰማሩ አንድ አንድ አሰልጣኞች የሚካተቱበት እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል።የአሰልጣኝ ስልጠናው በዋናነት የሚያጠነጥነው አሰልጣኞች አሁን ካለው ሁኔታ በመነሳት ራሳቸውን ማሻሻል በሚኖርባቸው ሁኔታዎች፣ በሀገራችን እግር ኳሳዊ ሃሳቦች፣ በአሰልጣኝነት ብቃት ላይ ይሆናል። ስልጠናው በኮቪድ -19 ምክንያት ስፖርታዊ ውድድሮች በመበተኑ በቤታቸው እያሳለፉ የሚገኙ አሰልጣኞች ከሙያው እንዳይርቁና፤ ውድድር ሲጀመር ከዜሮ እንዳይነሱ በማድረግ መነቃቃት የሚፈጥር መሆኑን ሶከር ኢትዮጵያ ዘግቧል ። የፕሪሚየር ሊግ ክለቦች አቋማቸውን እየፈተሹ ይገኛሉ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ተሳታፊ የሆኑ በርካታ ክለቦች የአቋም መፈተሻ ጨዋታዎችን እያደረጉ ይገኛሉ።በኮቪድ -19 ወረርሽኝ ምክንያት ተቋርጦ የነበረው ፕሪሚየር ሊጉ ከቀናት በኋላ ወደ መደበኛ ውድድር ሊመለስ መሆኑን ተከትሎ ክለቦቹ ቀደም ብለው የአቋም መፈተሻ ጨዋታዎች እያደረጉ መሆኑን ቢቢሲ ዘግቧል።አለም ዓቀፍ ስጋት በሆነው የኮሮና ወረርሽኝ ምክንያት ፕሪሚየር ሊጉ ዳግም ለመመለስ እኤአ ሰኔ 10 ቀን 2020 ቀጠሮ ተይዟል።ክለቦች ወደ መደበኛ ጨዋታቸው ሊመለሱ ቀናት የቀሩት በመሆኑ ወደ ነጥብ ጨዋታ ከመግባታቸው በፊት አቋም መፈተሻዎችን እያደረጉ ይገኛሉ።በአለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ተመልካች እንዳለው የሚነገርለት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ሰኔ 10 ይጀመራል።ፕሪሚየር ሊጉ ከተቋረጠ ከወራት በኋላ ወደ ውድድር መመለሱ በክለቦችና ተጫዋቾች ላይ የሚያደርሰውን ተጽእኖ ለመቀነስ ከዛ በፊት በርካታ የሊጉ ክለቦች እርስ በእርስ አልያም ከሌሎች ክለቦች ጋር የአቋም መፈተሻ ግጥሚያዎችን በማድረግ ላይ እንደሆኑ ታውቋል። በፕሪሚየር ሊጉ ተሳታፊ ከሆኑ ክለቦች አንዱ የሆነው ማንችስተር ዩናይትድ በኦልድ ትራፎድ ሃሪ ማጉዌር በአምበልነት የመራው ቡድን በሜዳው በብሩኖ ፈርናንዴስ የሚመራውን ቡድን ገጥሟል። በአቋም መፈተሻ ጨዋታው የሃሪ ማጓየር ቡድን የብሩኖ ፈርናንዴዝን ስብስብ 2 ለ 0 መርታት ችሏል። ከወራት በኋላ ማርከስ ራሽፎርድ እና ፖል ፖግባ ደግሞ ወደ ሜዳ ተመልሰዋል።የማይክል አርቴታ መድፈኞቹ ግን ከእርስ በእርስ ግጥሚያ ይልቅ የቻምፒየን ሺፕ ክለብን በሜዳቸው ማስተናገድን መርጠዋል። ከቻርልተን ጋር የወዳጅነት ግጥሚያ ያደረጉት አርሰናሎች 6-ለ0 በሆነ ሰፊ ውጤት ማሸነፍ ችለዋል።ከዚህ በተጨማሪም ቼልሲ፣ ሊቨርፑል፣ ዌስት ሃም አስቶን ቪላ እና ኒው ካስል ዩናይትድም ከ10 ቀናት በኋላ ለሚጀመረው ሊግ እራሳቸውን ዝግጁ ለማድረግ እርስ በእስር ግጥሚያ የሚያደርጉ ክለቦች መሆናቸውን ቢቢሲ ዘግቧል። አዲስ ዘመን ሰኔ 2/2012
https://www.press.et/Ama/?p=34005
356
2ስፖርት
የጥፋት ስትራቴጂስቱና ዋነኛው የጁንታ መሪ ስብሃት ነጋ በቁጥጥር ስር ዋለ
ሀገር አቀፍ ዜና
January 9, 2021
15
ራስወርቅ ሙሉጌታአዲስ አበባ፦ የጥፋት ስትራቴጂስቱና ዋነኛው የጁንታ መሪ ስብሃት ነጋን ጨምሮ ሌሎች የጥፋት ቡድኑ አመራሮች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የሀገር መከላከያ ሰራዊት አስታወቀ። የመከላከያ ሰራዊት ኃይል ስምሪት መምሪያ ኃላፊ ብርጋዴር ጀነራል ተስፋዬ አያሌው ትናንት እንዳስታወቁት፣ በአገራችን ላለፉት 27 ዓመታት የማተራመስ ስትራቴጂ የነደፈ ያስተባበረና ያደራጀ በመጨረሻም ጦርነት እንዲቀሰቀስ በማድረግ በሀገራችን ሰራዊት ላይ እጅግ ዘግናኝ ጦርነት በመክፈት ሰራዊቱን ያስጨፈጨፈው የጁንታው ቁንጮ፣ ስብሃት ነጋ በቁጥጥር ስር ውሏል።ለሰው ልጅ እጅግ አስቸጋሪ የሆነ ሰርጥ ውስጥ በቁጥጥር ስር መዋሉን የገለጹት ብርጋዴር ጀነራል ተስፋዬ፣ የጥፋት ቡድኑ አባላት በሰርጡ ውስጥ ተሸክመው በማስገባት ደብቀውት እንደነበርም አመልክተዋል። ጀግናው የሀገር መከላከያ ሰራዊትና ሌሎች የፌዴራል የፀጥታ አካላት በጋራ ባደረጉት ፍተሻና አሰሳ፣ ከተደበቀበት በማውጣት በቁጥጥር ስር እንዳዋሉትም ጠቁመዋል። ከመከላከያ የከዱ ሌሎች ከሃዲ የጁንታው አባላት ከስብሃት ነጋ ጋር አብረው በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የጠቆሙት ኃላፊው፣ አባላቱ ከመከላከያ በመክዳት የጁንታውን ታጣቂ ኃይል በማዋጋትና በማሰልጠን እኩይ ዓላማቸውን ለማስፈፀም ሲሰሩ እንደነበር አስታውቀዋል። የጁንታውን አመራር ዙሪያ ጥበቃ ሲያስተባብሩ ቆይተው በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ብርጋዴር ጀነራል ተስፋዬ ገልፀዋል። ጁንታውን ለመያዝ በተካሄደው ኦፕሬሽን የጁንታውን አመራሮች ለመከላከል በአካባቢው ጥበቃ ላይ የነበረ ታጣቂ ኃይል መደምሰሱን አስታውቀዋል።እንደ ብርጋዴር ጀነራል ተስፋዬ መግለጫ፤1. የጁንታው ቁንጮ አመራርና የጥፋት ስትራቴጂስት፣ ስብሃት ነጋ 2. ሌተናል ኮሎኔል ፀአዱ ሪች- የስብሃት ነጋ ባለቤትና ቀደም ሲል በጦር ኃይሎች ሆስፒተል ሃኪም የነበረች፣ በኋላም በጡረታ የተገለለች 3. ኮሎኔል ክንፈ ታደሰ- ከመከላከያ የከዳ 4. ኮሎኔል የማነ ካህሳይ- ከመከላከያ የከዳ 5. አስገደ ገ/ ክርስቶስ -ከመሃል ሀገር ተጉዞ ቡድኑን የተቀላቀለና ለጊዜው ኃላፊነቱ ያልታወቀ 6. አምደማርያም ተሰማ ተወልደ፣ የክልሉ የቅሬታ ሰሚ ፅ/ቤት ኃላፊ የነበረ፤7. ኮማንደር በርሄ ግርማ፣ የክልሉ ልዩ ኃይል ሎጀስቲክ ኃላፊ የነበረ በቁጥጥር ስር ውለዋል።ከተደመሰሱትና ከተያዙት በተጨማሪ የሜጀር ጀነራል ሃየሎም አርአያ ባለቤት የነበረችና ኑሮዋን በአሜሪካ አድርጋ የቆየች በኋላም ወደ አዲስ አበባ በመምጣት ወደ ጁንታው ተቀላቅላ የነበረች፣ ወይዘሮ አልጋነሽ መለስ ጁንታውን በመያዝ ኦፕሬሽን ሂደት ውስጥ ለማምለጥ ስትሞክር ገደል ገብታ ሕይወቷ ማለፉን ብርጋዴር ጀነራል ተስፋዬ አያሌው ገልፀዋል።በተመሳሳይ ዜና አራት የጁንታው ከፍተኛ አመራሮች ከነአጃቢዎቻቸው መደምሰሳቸን፤ ዘጠኝ የጁንታው ከፍተኛ አመራሮች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የመከላከያ ኃይል ስምሪት መምሪያ ኃላፊ ብ/ጄኔራል ተስፋዬ አያሌው ከትናንት በስቲያ ማስታወቃቸው ይታወሳል፡፡በዚህም መሰረት፣1. የጁንታው ቃል አቀባይ ሴኩቱሬ ጌታቸው፣ የሰሜን ዕዝን በ45 ደቂቃ ውስጥ መብረቃዊ ጥቃት በመፈጸም ከጥቅም ውጪ አድርገነዋል ሲል በትግራይ ቴሌቪዥን የተናገረ ፤2. ዘርአይ አስገዶም የቀድሞው የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ሥራ አስኪያጅና የብሮድካስት ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር የነበረ፤3. አበበ አስገዶም የድምጸ ወያኔ ኃላፊ የነበረ፤4. ዳንኤል አሰፋ የክልሉ ፋይናንስ ቢሮ ኃላፊ የነበረ ከሹፌሮቻቸውና ከጥበቃዎቻቸው ጋር በጀግናው የመከላከያ ሰራዊት፣ በፌዴራል የጸጥታ ተቋማትና በትግራይ ሕዝብና በክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር በተደረገ የተቀናጀ ዘመቻ መደምሰሳቸውን ብርጋዴል ጀኔራል ተስፋዬ አስታውቀዋል።ከተደመሰሱት በተጨማሪም 9 የጁንታው ቁልፍ አባላት በቁጥጥር ስር የዋሉ ሲሆን እነሱም፣1. ወይዘሮ ቅዱሳን ነጋ የቀድሞ የክልሉ አፈጉባኤ የነበረች፣2. ዶክተር ሰለሞን ኪዳኔ የቀድሞ የትግራይ ክልል ከተማ ልማት ቢሮኃላፊና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትራንስፖርት ቢሮ ኃላፊ የነበረ፣3. አቶ ተክለወይኒ አሰፋ የማረት ሥራ አስፈጻሚ የነበረ፣4. አቶ ገብረመድህን ተወልደ የክልሉ ንግድ ቢሮ ኃላፊ የነበረ፣5. አቶ ወልደጊዮርጊስ ደስታ የክልሉ መንገድ ትራንስፖርት ቢሮ ኃላፊ የነበረ፣6. አምባሳደር አባዲ ዘሙ በሱዳን የኢትዮጵያ የቀድሞ አምባሳደር የነበረና የጁንታውን ፖለቲካ ክንፍ የተቀላቀለ፣7. አቶ ቴዎድሮስ ሃጎስ የመለስ አመራር አካዳሚ ፕሬዚዳንትና የኢፈርት ቦርድ ኃላፊ የነበረ፣8. ወይዘሮ ምህረት ተክላይ የክልሉ ምክር ቤት ሕግ አማካሪ የነበረች እንዲሁም9. አቶ ብርሃነ አደም መሃመድ የክልሉ የንብረትና ግዢ ሥራ ሂደት ኃላፊ የነበረ ነው። የህወሓት ጁንታ ባለስልጣናት በቁጥጥር ስር የዋሉት በጫካና ዋሻ ለዋሻ ሲንቀሳቀሱ በተደረገ ጠንካራ አሰሳ መሆኑን የገለጹት ብርጋዴር ጀኔራሉ፣ የአገር መከላከያ ሰራዊት እነዚህ የጁንታው ቁልፍ የጥፋት ቡድን አባላት እንዲደመሰሱና በቁጥጥር ስር እንዲውሉ ያላሰለሰ ድጋፍ ላደረገው መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ምስጋናውን አቅርቧል። ሰራዊቱ ወንጀለኞቹን አድኖ ለመያዝ ቃል በገባው መሰረት ግዳጁን እየተወጣ መሆኑን አመልክተው፣ የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጅ የሆነው ጀግናው የመከላከያ ሰራዊት የጀመረውን ቀሪ የጁንታውን ርዝራዦችን አድኖ ለመያዝና በሕግ ተጠያቂ ለማድረግ የጀመረውን ጥረት አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል። ሕዝቡ እያደረገ ያለውን ድጋፍና ተሳትፎ አጠናክሮ እንዲቀጥልም ጥሪ አቅርበዋል።
https://www.press.et/Ama/?p=39156
554
0ሀገር አቀፍ ዜና
የላቁ ስፖርተኞችና ብቃት ያላቸው የስፖርት ባለሙያዎችን ለማፍራት
ስፖርት
June 11, 2020
14
በስፖርት ማሰልጠን፣ መምራትና ማስተባበር ተሳታፊ የሆኑ ባለሙያዎች ለስፖርት እድገትና ውጤታማነት ከፍተኛውን ድርሻ እንደሚጫወቱ እሙን ነው። በዚህ ምክንያትም ሀገር አቀፉ የስፖርት ሪፎርም ፍኖተ ካርታ እንደ ግብ ከያዛቸው ዋና ዋና ጉዳዮች መካከል አንዱ ባለሙያዎችን በብዛትና በጥራት ማፍራት ነው። የማዕከላዊው ስታትስቲክስ ኤጀንሲ በ2004 ዓ.ም ባወጣው መረጃ መሠረት በወቅቱ 2ሺ376 ዳኞችና 2ሺ476 አሰልጣኞች እንደነበሩ ያመላክታል። ከዚያ በኋላ ባሉት ዓመታት ደግሞ በተለያዩ የስፖርት ሙያ ዘርፎች 30ሺ560 ባለሙያዎችን በአጭር፤ 2ሺ388 ባለሙያዎችን ደግሞ በረጅም ጊዜ ሥልጠና ለማፍራት መቻሉ በፍኖተ ካርታው ሰፍሯል። ይሁን እንጂ ሥልጠናውን ለተገቢው ባለሙያ ከማድረስ አኳያ፣ በብሔራዊ ፌዴሬሽኖች ደረጃቸውን የጠበቁ የሥልጠና ማኑዋሎች አለመኖር፣ የሥልጠናው ግብ አለመታወቅና ተያያዥ አለመሆኑ፣ የንድፈ ሃሳብና የተግባር ሥልጠናው አለመመጣጠን፣ በምዘና እና ፈቃድ አሰጣጥ ላይ ችግሮች መኖር፣ ቅንጅታዊ አሠራር ባለመኖሩ የሥልጠና አሰጣጥ ባለድርሻ አካላት አለመናበብ፣ ተመሳሳይ እና በማይሰሩበት ሙያ ሥልጠና መውሰድ እንዲሁም መሰል ችግሮች መኖራቸውንም ሰነዱ ያመላክታል። ይህንን ችግር ለመቅረፍም ፍኖተ ካርታው ወጥ የሆነ የባለሙያዎች የእድገት መሰላል፣ የሥልጠና ካሪኩለም እንዲሁም የሥልጠና ማኑዋል በብሔራዊ የስፖርት ማህበራት ማዘጋጀት እንደሚገባም በመፍትሄነት ያስቀምጣል። በዚሁ መሠረትም የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን የላቁ ስፖርተኞችንና ብቃት ያላቸውን የስፖርት ባለሙያዎችን ለማፍራት፤ ብሔራዊ የሥልጠና ሞዴል እና አገር አቀፍ የስፖርት ባለሙያዎች የእድገት መሰላል እየተዘጋጀ መሆኑን አስታውቋል። ባለሙያዎች በአጭርና መካከለኛ ጊዜ ሥልጠና እንዲሁም በረጅም ጊዜ ትምህርት ብቃታቸው እየተሻሻለ አቅማቸው እየተገነባ ሊሄድ ይገባል። በመሆኑም የሀገር አቀፍ የስፖርት ሪፎርም ጥናቱ ውጤት የሆነውንና የለውጥ ሃሳቦችን ለማስተግበር የሚያስችሉ ሰነዶች ዝግጅት መጀመሩን በኮሚሽኑ የትምህርት እና ሥልጠና ዳይሬክተር አቶ ሲሳይ ሳሙኤል ማስገንዘባቸውንም ኮሚሽኑ በድረ ገጹ አስነብቧል። የስፖርት ባለሙያዎች ልማት እና ጥራት አንዱ የሀገሪቷ ስፖርት ልማት ማዕዘን ነው። የስፖርቱን ችግር ይፈታል የተባለው የስፖርት ሪፎርም ፍኖተ ካርታው ለይቶ ካስቀመጣቸው ዘጠኝ ዋና ዋና ምሰሶዎች አንዱም የስፖርት ባለሙያዎች ልማት እና ጥራት ነው። ለአንድ ሀገር ስፖርት እድገት የባለሙያዎች ብቃት፣ ጥራት እና አቅርቦት እጅግ ወሳኝ መሆኑን የሪፎርም ፕሮግራሙ ያመላክታል። በመሆኑም ባለሙያዎች በአጭር እና መካከለኛ ጊዜ ሥልጠና እንዲሁም በረጅም ጊዜ ትምህርት ብቃታቸው እየተሻሻለ አቅማቸው እየተገነባ ሊሄድ እንደሚገባ የጥናት መርሃ ግብሩ ይጠቁማል። በሰነድ ዝግጅቱ ላይም ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት፣ ከስፖርት ፌዴሬሽኖች፣ ከሥልጠና ማዕከላት፣ ከብሔራዊ ቡድን አሰልጣኞች እና ሌሎችም በዘርፉ ከፍተኛ ልምድና እውቀት ያላቸው ምሁራን ተሳታፊ እንደሚሆኑም ታውቋል። አጠቃላይ ዝግጅቱን በተመለከተም በኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን የጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሰለሞን አልዩ የሥራ መመሪያ ተሰጥቶ ወደ ሥራ መገባቱም ተጠቁሟል።አዲስ ዘመን ሰኔ 4/2012 ብርሃን ፈይሳ
https://www.press.et/Ama/?p=34184
331
2ስፖርት
ያልተዘጋው የፓሪሱ ዶሴ
ስፖርት
June 12, 2020
20
 እ.ኤ.አ ሰኔ 7 ቀን 1933 በሴኔጋል ዳካር ከተማ አንድ ህጻን ተወለደ። በፈረንሳይ ቅኝ ግዛት ስር በነበረችው ሴኔጋል መወለዱ ለቤተሰቦቹ ቅር ቢያሰኝም፤ ከህጻኑ አይኖች ያነበቡት ተስፋ መጽናናትን የሰጣቸው ነበር። የህይወት ውጣ ውረዱም ደስታን ከሀዘን እያፈራረቀ ቀጠለ። በሴኔጋል ምድር የበቀለው ህፃን የህይወት ውጣ ውረድን በመጋፈጥ፤ በአንካራ የልጅነት ጊዜውን አሳልፏል። በጊዜ ቅብብሎሽ ልጅነቱ ወደ ወጣትነት ሽግግር አደረገ። ከልጅነት ጀምሮ የሚፍለቀለቀው የስፖርት ፍቅር በዘመን ሳይሻር አብሮ ያደገ ነበር። በአንካራ ህይወት ቀላል አልነበረምና በፈታኙ የህይወት መንገድ ነገን የተሻለ ለማድረግ መጓዝ አማራጭ እንደሌለው በማመን ጉዞው ቀጠለ። ከልጅነት ጀምሮ ለስፖርት የነበረው ፍቅር ግን ወጥ በሆነ መስመር የተጓዘ ነበር። በስፖርት ፍቅር መሰረት የተገነባው የህይወት ኡደት የስኬት ቁልፍንም በስፖርቱ አማካኝነት እስከ መጨበጥ የደረሰ ታሪክ ባለቤት ናቸው የቀድሞ የዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ማህበር ፕሬዚዳንት ላሚን ዲያክ።ላሚን ዲያክ ስፖርትን እንደ መሰላል በመጠቀም ስኬትን መጨበጥ ከቻሉ ጥቂት አፍሪካዊያን ውስጥ ይመደባሉ። የ86 ዓመት አዛውንቱ ላሚን ዲያክ በህይወት ፈተና ውስጥ ሳይሰናከሉ ያደረጉት ጉዞ ለዚህ ደረጃ መዳረሻ እንደሆናቸው «በሥራ ዘመኔ ከፍተኛ የፖለቲካ ፈተናዎች ገጥመውኝ ነበር።ዓላማ ስለነበረኝ ሁሉም አልፏል፣ ስለ አፍሪካ አንድነት በማውራት ጊዜውን ሁሉ ተጠቅመናል»ሲሉ ይደመጣሉ። ሴኔጋላዊው ዲያክ ወደ ዓለም አቀፍ አትሌቲክስ አመራርነት በመምጣት ሀገራቸውን ከማስጠራታቸው ቀደም ብሎ በዝላይ ውድድር ሀገራቸውን ሲያስጠሩ ነበር። በወጣትነት ዘመናቸው በዝላይ ውድድር ሃገራቸውን በተለያዩ ዓለም አቀፍ መድረኮች በመወከል ተሳትፈዋል። ከብዙዎቹ በጥቂቱ እኤአ 1950 በፍረንሳይ በተካሄደው የአትሌቲክስ ቻምፒዮን በመሳተፍ ባለድል ሆነዋል። ዲያክ በተደጋጋሚ የቻምፒዮናነት ክብር ባለቤት መሆን የድልን ጣዕም ለሀገራቸው በማቅመስ ትልቅ ታሪክ መስራታቸው ይነገራል።ሴኔጋላዊያን እርሳቸው ካስመዘገቧቸው ድሎች መካከል በተለይ በዝላይ ውድድር ከ1957 እስከ 1960 የምዕራብ አፍሪካን ክብረወሰን መያዝ የቻሉበት አጋጣሚ ትልቅ ስፍራ ይሰጡታል።የአፍሪካን እግር ኳስ በማነቃቃት ግንባር ቀደም የሆነችው ሴኔጋል ያበቀለቻቸው ላሚን ዲያክ በአትሌቲክሱ የተወዳዳሪነት ጊዜያቸውን ካጠናቀቁ በኋላ ወደ ስፖርቱ አመራርነት ነበር ያዘነበሉት።በዚህም የተሳትፎ ደረጃቸውን በፍጥነት ማሳደግ ችለዋል። እኤአ 1999 እስከ 2013 የአለም ዓቀፍ ኦሎምፒክ ኮሚቴ አባል በመሆን አገልግለዋል።በኦሎምፒክ ኮሚቴ አባል በመሆን ሲያደርጉ የነበረው ተሳትፎ ወደ ሌላ ምዕራፍ ያሸጋገራቸው ነበር።እኤአ 1995 የዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ማህበር ፕሬዚዳንት እንዲሸጋገሩ መሰላል ሆኗቸዋል። የላሚን ዲያክ ወደ መሪነት መምጣት በሴናጋል ብቻም ሳይሆን በአፍሪካዊያን ዘንድ ትልቅ ደስታን የፈጠረ ነበር።የዓለምን አትሌቲክስ በአፍሪካዊያን መመራቱ አዲስ ታሪክ ከመሆኑ ባሻገር፤ ለአፍሪካዊያን የይቻላል መንፈስን ያወረሰ ተብሏል።የዲያክ የዓለምን አትሌቲክስ የመምራት ሂደት ለ16 ዓመታት ነበር የተጓዘው።እኤአ በ2015 ላሚን ዲያክ ስልጣናቸውን ለተመራጩ ለሴባስቲያን ሎርድ ኮ አስረክበዋል።ሴኔጋላዊው ላሚን ዲያክ በስልጣን ዘመናቸው በአትሌቲክሱ ዓለም የተበላሹ የአመራር ክፍተቶችን እንዳሉ በስፋት የሚነሳ ቢሆንም ከሞላ ጎደል ጥሩ ሥራዎችንም ማከናወናቸውን አብሮ ይነሳል።በተለይ ለአፍሪካ አትሌቲክስ የነበረቸው አበርክቶ የሚጠቀስና እስከ ሽልማት የተሻገረ ነበር።በአህጉሪቱ የአትሌቲክስ ስፖርት ላይ የሚያጠነጥነው «አፍሪካ አትሌቲክስ ፋውንዴሽን »ለላሚን ዲያክን እውቅና በመስጠት ረገድ ግንባር ቀደም ነበር። የዓለም አቀፉ የአትሌቲክስ ፌዴሬሽን ማህበር ፕሬዚዳንት በመሆን ላሚን ዲያክ ባገለገሉባቸው ዓመታት የአፍሪካ አትሌቲክስ ህዳሴ መሆን ጉልህ ድርሻ ነበራቸው። ለዚህም እውቅናና ሽልማት ይገባቸዋል ሲል አመስግኗቸዋል።የአፍሪካ አትሌቲክስ ኮንፌዴሬሽን በተመሳሳይ እውቅናውን አልነፈጋቸውም።እኤአ መጋቢት 4 ቀን 2015 የኮንፌዴሬሽኑ የሥራ አስፈፃሚዎች 26ኛውን ጠቅላላ ጉባኤውን በአዲስ አበባ በተካሄደበት ወቅት ለዲያክ ምስጋናና እውቅና ቸሯቸዋል። በወቅት ኮንፌዴሬሽኑ፣ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን፤ የኢትዮጵያ ስፖርት ኮሚሽን በጋራ የእውቅና እና የስንብት ዝግጅት በማድረግ ለአበረከቷቸው አመስግነዋቸዋል።ዲያክ በፈተና የተሞላውን ጉዞ በድል መወጣት ቢችሉም፤ የህይወት ፈተና አላበቃም ነበር። የአለም አትሌቲክስ መሪነት ዘመናቸው ጨርሰው ስልጣናቸውን ካስረከቡ ማግስት ወደ ሌላ ፈተና ተሻገሩ። የአለም ዓቀፍን አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበርን ለ16 ዓመታት የመሩት ላሚንዲያክ መንበረ ስልጣናቸውን ባስረከቡ ማግስት በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው በ86 ዓመታቸው ፍርድ ቤት ነበር የቆሙት። ዲያክ በፈረንሳይ ፓሪስ የቁም እስረኛ ሲሆኑ፤ እኤአ ጥቅምት 4 ቀን 2015 ጀምሮ በፓሪስ ፍርድ ቤት ዲያክ የሩስያ አትሌቶች አበረታች መድሃኒት መውሰዳቸውን ለመደበቅ ረብጣ ሽልንግ ተቀብለዋል፤ የምርጫ ድምፅን በገንዘብ ገዝተዋል፤በሕገ-ወጥ ገንዘብ ዝውውር ጋር ተያይዞ ነበር ክስ የተመሰረተባቸው። በተጠቀሱት ወንጀሎች ዲያክን ጨምሮ አራት ግለሰቦች ተከሳሽ ሲሆኑ፤ የዲያክ ልጅ ፓፓ ማሳታ ዲያክ አንዱ ነው። ፓፓ ማሳታ ሴኔጋል ሆኖ የክስ ሂደቱን እየተከታተለ ይገኛል። ሴኔጋል ልጅዬውን አሳልፋ ለፈረንሳይ እንድትሰጥ ጥያቄ ቢቀርብም ሴኔጋል አሻፈረኝ ብላለች።በዚህ መሰረት ፓፓ ማሳታ አባቱንና እሱን ነፃ ያወጣል ያለውን ማስረጃ ለፍርድ ቤቱ በማስገባት ሙግቱን እያደረገ ቢሆንም፤ የክሱ ሂደት አላግባብ መጓተቱን ተከትሎ ወላጅ አባቱ ላሚን ዲያክ ለእንግልት መዳረጋቸውን እየተናገር ይገኛል።የክስ ሂደቱ ከተጀመረ አምስት ዓመት ቢያስቆጥርም መቋጫ እንዳላገኘ ገልጿል።በዲያክም ሆነ እርሱ በቀረበበት ክስ ላይ በቂ የሆነ ማስረጃ የሌለ በመሆኑና ካለወንጀላቸው ክስ የተመሰረተ ነው ሲል ቅሬታውን ያሰማል። በጠበቆቻቸው በኩል ይሄው በተደጋጋሚ እየተነሳ ሲሆን ወደ አገራቸው ሴኔጋል ተመልሰው የክስ ሂደቱን እንዲከታተሉ ጥያቄ እያቀረቡ ይገኛሉ።በፈረንሳይ ፍርድ ቤት ግን ውድቅ ተደርጓል። የፈረንሳይ ፍርድ ቤት ከአምስት ዓመት በፊት የተጀመረው የዲያክ የክስ ሂደቱ መፍትሄ ለማበጀት በፈረንጆቹ አዲስ ዓመት ማግስት እንዲታይ ቀጠሮ ይዞ ነበር። ፍርድ ቤቱ በተለያዩ ምክንያቶች ወደ ሰኔ ወር እንዲዛወር አድርጎታል። በፈረንሳይ በቁም እስር ላይ የሚገኙት የ87 ዓመቱ ላሚን ዲያክ በቀጠሮ መሰረት ባሳለፍነው ሰኞ ፍርድ ቤት መቅረባቸው ተሰምቷል።የፓሪሱ ፍርድ ቤትም በቀድሞዋ የአለም አትሌቲክስ ፕሬዚዳንት ላሚኔ ዲያክ ላይ ከሩሲያ ጋር በመመሳጠር ከዶፒንግ ጋር ተያይዞ በፈጸሙት ወንጀል ተጠያቂ ለማድረግ የተመሰረተባቸውን የክስ ሂደትን ተከታትሏል።ፍርድ ቤቱ በዲያክ ላይም ዶፒንግን በሶስት ሚሊዮን ዩሮ በመለወጥ ሲል ክስ የመሰረተባቸው መሆኑን ሮይተርስ ዘግቧል። የ 87 ዓመቱ ላሚን ዲያክ ፊታቸውን ጭምብል በመሸፈን ፍርድ ቤት ተገኝተው የክስ ሂደታቸውን ተከታትለዋል።የፓሪሱ ፍርድ ቤትም ለቀጣዮቹ ስድስት ቀናት ችሎት ተሰይሞ የክስ ሂደቱን እንደሚሰማ ማስታወቁን አትቷል።የፍርድ ቤቱ ፕሬዚዳንት ንግግር፤ «ሴኔጋላዊው ዲያክ በሙስና ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር ከዋሉ ዓመታት ቢቆጠሩም ወንጀሉ ጥልቅ ምርመራ የሚፈልግ ከመሆኑ ጋር እንደሚያያዝ አስታወቋል።ዓመታትን በፈጀው ምርመራም የተዘበራረቀና ውስብስብ የሙስና ወንጀል መፈጸሙን የሚያረጋግጡ ማስረጃዎች ተገኝተዋል። በተያዙት ሰነዶችም ከአውሮፓ እስከ እስያ እና አፍሪካ የተዘረጋ ጠንካራ የሆነ የወንጀል ሰንሰለት መኖሩን የሚያረጋግጡ ናቸውን»ሲሉ ማስረዳታቸውን ዘገባው አካቷል። የፓሪስ ፍርድ ቤት በዲያክ ላይ የሰበሰበውን ማስረጃዎች መሰረት በማድረግ ለመጀመሪያ ጊዜ በስድስት ቀናት ችሎት እነዚህን ማስረጃዎችን በማቅረብ ወደ ውሳኔ እንደሚኬድ ፍርድ ቤቱ ማስታወቁን ጽፏል።በፈረንሳይ ፍርድ ቤት ክስ የተመሰረተባቸው ላሚን ዲያክ በተጠረጠሩበት ወንጀል ጥፋተኛ ሆነው ከተገኙ እስከ 10 ዓመት የሚዘልቅ እስር ሊፈረድባቸው ይችላሉ ተብሏል። አዛውንቱ ዲያክ ቀሪ የእድሜ ዘመናቸውን ወሕኒ ሊያሳልፉ እንደሚችሉ ተነግሯል። ነገር ግን ከተከፈተ አምስት ዓመታት የሆነው የፓሪሱ ዶሴ የሚዘጋበት እለት አጓጊ እንደሆነ ቀጥሏል።አዲስ ዘመን ሰኔ 5/2012 ዳንኤል ዘነበ
https://www.press.et/Ama/?p=34246
854
2ስፖርት
የቢሮ ሕንፃው ያሰጋቸው ሄልሜት አጥልቀው የሚኖሩ ህንዶች
መዝናኛ
November 19, 2019
27
መንግሥት ከህዝብ ከሚሰበስበው ግብር የዜጎችን መሠረታዊ ፍላጎት ማሟላቱ ግድ ነው፡፡ ቢሮ ውስጥ ቁጭ ብለው የመንግሥት የዕለት ተዕለት ሥራ እየሠሩ ደግሞ በአለቆቻቸው ችላ ከተባሉ የኪራይ ሰብሳቢነት ችግር አለ ማለት ነው፡፡ ወይም አመራሩ ምንዝሩን (የበታቹን ሠራተኛ) በማማረር አልያም አለቃው በመደናበር ግዴታውን ያለመወጣቱ ማሳያ ነው፡፡ ሕንፃቸው እያሰጋቸው መሆኑን ለመንግሥትና ለመገናኛ ብዙኃን ተደጋጋሚ አቤቱታ ሲያቀርቡ የነበሩ ህንዳውያን ተሰላችተው ‹‹ለቢሮ ሥራቸው ሄልሜት አጥልቀው መሥራት ጀመሩ፡፡›› ይለናል የኦዲቲ ሴንተራል ዘገባ፡፡ በግሌ የአለቆችን ቸልተኝነት ብንቅም የህንዳውያን ምንዝሮች ሥራን ግን አደንቃለሁ፡፡ እኛ ብንሆን ኖሮ ሕንፃ ለመደርመስና ሕይወት ለማፍሰስ እንሮጥ ነበር፡፡ ህንዳውያኑ ሀገራቸውን ስለሚወዱ መንግሥት ቢሮክራሲ በማብዛት ችላ ቢላቸውም ለሀገራቸው ለመሥራት ግን አልቦዘኑም፤ ሀገራቸውንም ችላ አላሉም፡፡ በህንድ ኡተር ፓራዳሽ ግዛት ባንዳ ከተማ የሚገኙ እነዚህ የመንግሥት ሠራተኞች የሞተር ሳይክል ሄልሜት (የራስ ቅልን ከአደጋ መከላከያ) አጥልቀው የቢሮ ሥራ እየሠሩ በቅርቡ በማኅበራዊ ድረ ገፅ የብዙዎችን ትኩረት ስበው ነበር፡፡ ምናልባት የሕንፃው ጣራ በላያቸው ላይ ሊራገፍ ቢችል ተብሎ መሆኑን የኦዲቲ ሴንተራል ዘገባ አስረድቷል፡፡ በከተማው የኤሌክትሪክ ክፍል ቅጥር ሠራተኞች ትልልቅ የሞተር ሳይክል ሄልሜት ለጭንቅላታቸው አጥልቀው ቢሯቸው ሲሠሩ የሚያሳዩ ፎቶዎችን ማኅበራዊ ትስስር ገፆችና የህንድ ዜና አገልግሎት ተጋርተውታል፡፡ አብዛኛዎቹ ምንጮች የመንግሥት ተቀጣሪዎቹ የሞተር ሳይክሎች ደጋፊ ወይም አቃፊ አይደሉም። ቀስ በቀስ እየተፈረካከሰ ያለው ጣራ ግን እንዳይጎዳቸው ጭንቅላታቸውን ለመከላከል ሊሆን ይችላል፡፡ ከዓመታት በፊት ለሪፖርተሮች የጽህፈት ቤቱ ሕንፃ እንደሚያሰጋቸው ቢናገሩም ማንም መፍትሔ የሚሰጥ አልተገኘም፡፡ እናም የራስ ቅላቸውን ከአደጋ ሊከላከል የሚችለውን ሄልሜት አጥልቀው ወደ ቢሮ እየገቡ ለመሥራት ወስነው ተገበሩት፡፡ ‹‹ይህን መሰል ሁኔታ ያጋጠመን እኔ ከተቀላቀልኩ ከሁለት ዓመት በፊት ነው፡፡ ለባለሥልጣኖች ጽፈን ነበር ግን ጆሮ ዳባ ልበስ አሉን፡፡›› ሲሉ ከተቀጣሪዎች መካከል ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ ግለሰብ ለህንድ ዜና አገልግሎት ተናግረዋል፡፡ የዛሬይቱ ህንድ የተባለ ጋዜጣ እንደዘገበው፤ የጽህፈት ቤቱ ሠራተኞች አንዲት ስንስዝር ያጋነኑት ነገር የለም፡፡ በቤቱ መካከል ጣራው እንዳይፈረካከስ የሚረዳ ምሰሶ ወይም አምድ ቢኖረውም ጣራዎቹ በቀዳዳዎች የተሞሉ ናቸው፡፡ የሚገርመው በህንድ ቢሮዎች የሞተር ሳይክል ሄልሜት አጥልቀው የሚገቡ ሠራተኞች በዜና ሲዘገብ የመጀመሪያው አይደለም፡፡ እኤአ ከ2017 ወዲህ በተሰነጣጠቀ የመንግሥት ሕንፃ ውስጥ ስለሚሠሩ ሠራተኞች ቢሀር በሚባል አካባቢ በተመሳሳይ መልኩ የቢሮ ሥራቸውን ለመሥራት በስጋት ሄልሜት ለማጥለቅ እንደተገደዱ ተዘግቦ እንደነበር የኦዲቲ ሴንተራል ዘገባ ያመለክታል፡፡አዲስ ዘመን ህዳር 05 ቀን 2012 ዓ.ም ኃይለማርያም ወንድሙ
https://www.press.et/Ama/?p=22780
311
1መዝናኛ
ዲግሪን በዘጠኝ ዓመት
መዝናኛ
November 19, 2019
32
 በሀገራችን ባለው አሠራር ሕፃናት ቅድመ መደበኛ ትምህርት መከታተል የሚጀምሩት በአራት ዓመታቸው እንደሆነ ይታወቃል፤መደበኛ ትምህርት እንዲጀመሩ የሚጠበቀው ደግሞ በሰባት ዓመታቸው ነው፡፡ ይህ በከተሞች እየተሠራበት ሲሆን፣ በገጠር እና በአንዳንድ ከተሞች ግን የቅድመ መደበኛ ትምህርት ጉዳይ በቄስ ትምህርት ቤት እና ቁርአን ትምሀርት ቤቶች የሚሸፈን እንደ መሆኑ የአጸደ ሕፃናት ትምህርት አለ የሚባል አይደለም፡፡ አንዳንድ ሕፃናት ግን ከሰባት ዓመታቸው በፊት ትምህርት እንዲጀምሩ ሲደረግ ይስተዋላል፡፡ ትምሀርት የጀመሩት በአምስት ዓመታቸው መሆኑን የሚገልጹ ያጋጥማሉ፡፡ እነዚህ ተማሪዎች 12ኛ ክፍልን መቼ ጨርሰው መቼ የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን እንደሚይዙ መገመት አይከብድም፡፡ በአምስት ዓመታቸው አንደኛ ክፍል ቢገቡና ብርቱ ሆነው አስራ ሁለተኛ ክፍልን በሰዓቱ ቢያጠናቅቁ ከ21 ዓመታቸው በፊት የመጀመሪያ ዲግሪ ለመያዝ አይችሉም፡፡ በ7 ዓመታቸው የሚገቡት ደግሞ መቼ ሊጨርሱ እንደሚችሉ እናስብ፡፡ በእኛ ሀገር አንዳንዶች ትምህርት ቤት ሊገቡ በሚችሉበት ዕድሜ የመጀመሪያ ዲግሪ የያዙ ታዳጊዎች ያጋጥማሉ፡፡ ኤንዲቲ የተሰኘው ድረ ገጽ በቅርቡ ይዞት የወጣ ዘገባ እንዳመለከተው የአምስተርዳም ነዋሪው የዘጠኝ ዓመት ሕፃን የመጀመሪያ ዲግሪውን በቅርቡ እንደሚይዝ ይጠበቃል። በዚህም በዓለም የመጀመሪያ ዲግሪ ያየዘ በሕፃንነቱ መያዝ የቻለ ብቸኛው ሕፃንም ለመባል በቅቷል።፡ በኤይንሆቭን ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ትምህርቱን ሲከታተል የቆየው ለውረንት ሲሞንስ የተባለው ይህ ሕፃን የመጀመሪያ ዲግሪውን የሚይዘው በኤሌክትሪካል ምህንድስና ነው፡፡ ሕፃኑ የመጀመሪያ ዲግሪውን በሚቀጥለው ወር እንዳጠናቀቀም ፣ከሦስት ወራት በኋላ ሦስተኛ ዲግሪውን ለመያዝ ትምህርት እንደሚጀምርም ተናግሯል፡፡ እናቱ ሊዲያ የልጁ አያቶችና መምህራን ልዩ ተሰጥኦ እንዳለው ሁሌም ይናገሩ እንደነበር ስትገልጽ፣ አባቱ አሌክስንደር ሲሞንስ በበኩሉ ልጁ በእርግጥም መረጃ በመያዝ በኩል ማንም አይደርስበትም ሲል ገልጿል፡፡ ሎውረንት ገና ምኑ ተይዞ ይላል፡፡ ለዘ ቴሌግራፍ በሰጠው አስተያየትም ወደ ካሊፎርኒያ በመሄድ ትምህርቱን ለመቀጠል ይፈልጋል፤አባቱ ግን እንግሊዝ ሄዶ ቢማርለት እንደሚመርጥ አስታውቋል፡፡ የ37 ዓመቱ የጥርስ ሀኪም የሆነው አባቱ ‹‹ኦክስፎርድና ካምብሪጅ በአንግሊዝ ዋና ዋናዎቹ ዩኒቨርሲቲዎች መሆናቸውን በመጥቀስ፣ ከእነዚህ ዩኑቨርሲቲዎች በአንዱ ገብቶ ቢማር ምርጫው መሆኑን አስታውቋል፡፡ ላውረንት ሲሞንስ ለሲኤንኤን በሰጠው አስተያየት በቀጣይም ማጥናት የሚፈልገው ኤሌክትሪካል ኢንጂነሪንግ መሆኑን ጠቅሶ፣ በተወሰነ ደረጃ የህክምና ትምህርት መማርም ይፈልጋል፡፡ ቤተሰቦቹ በሕፃንነቱና በእውቀቱ መካከል የሆነ ሚዛናዊ ነገር እንደሚፈልጉ ሎረንት ገልጾ፣ እሱ ደግሞ ለትምህርቱ ከሚሰጠው ትኩረት በተጓዳኝ የተለየዩ ጨዋታዎችን መጫወት፣ ከጓደኞቹ ጋር መሆን እንደሚወድ ይናገራል፡፡ በኢንስታግራም በኩል ከ11 ሺህ በላይ ተከታዮች አንዳሉት ተናግሮ፣ በዚህም አማካይነት የህይወትን የተለያዩ ጎኖች እንደሚመለከት ያብራራል፡፡ እስከ አሁን ባለው መረጃ መሰረት በዓለም በልጅነቱ የመጀመሪያ ዲግሪ በመያዝ የሚታወቀው ሚካኤል ኬርኒይ የተባለ ታዳጊ ሲሆን ፣ዲግሪውን የያዘውም በአስር ዓመቱ መሆኑን መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡አዲስ ዘመን ህዳር 9/ 2012 ዓ.ም ዘካርያስ
https://www.press.et/Ama/?p=22776
335
1መዝናኛ
ኢትዮጵያ፣ ኬንያና ሶማሊያ በጁባላንድ ኮሪደር በጋራ መስራት በሚቻልበት አግባብ ላይ ተወያዩ
ሀገር አቀፍ ዜና
January 6, 2021
12
በጋዜጣው ሪፖርተር አዲስ አበባ፦ ኢትዮጵያ፣ ኬንያና ሶማሊያ በሚዋሰኑበት ድንበር በጁባላንድ ኮሪደር በጋራ መስራት በሚቻልበት አግባብ ላይ ተወያዩ፡፡ከመከላከያ ሰራዊት ያገኘነው መረጃ እንደ ሚያ መለክተው ፣ኢትዮጵያ፣ ኬንያና ሶማሊያ በሚዋሰኑበት ድንበር በጁባላንድ ኮሪደር በጋራ መስራት በሚቻልበት አግባብ ላይ ውይይት ተካሂዷል ፡፡በውይይቱ በቀጣናው ስላለው ወቅታዊ የጠላት እንቅስቃሴ የመከሩ ሲሆን በቀጣናው በጋራ ለመስራት መግባባት ላይ ደርሰዋል፡፡በውይይቱ ላይ የሴክተር ሁለት አዛዥ ብርጋዴር ጄኔራል ጄማ፣ የሴክተር ስድስት ምክትል አዛዥ ኮሎኔል ማኩርጋ ፓናርድ፣ የ5ኛ ሞተራይዝድ ዋና አዛዥ ኮሎኔል አሰፋ መኮንን፣ የጁባላንድ ክልል ከፍተኛ የጦር መኮንኖችና የፌደራል ኤስ ኤን ኤ ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም የጁባላንድ የፀጥታ ዘርፍ ኃላፊዎች ተገኝተዋል፡፡የጁባ ላንድ ምክትል ፕሬዚዳንት ማህሙድ ሰይድ ሶማሊያ ፣ ኢትዮጵያና ኬንያ ወንድማማች ህዝቦች መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡የአዋሳኝ ድንበር ቦታዎች ላይ ሰላምና መረጋጋት እንዲኖር የጋራ ጠላት የሆነውን አልሸባብን በጋራ መዋጋት ይገባልም ብለዋል፡፡በሶማሊያ የአፍሪካ ህብረት ሰላም አስከባሪ ሃይል (አሚሶም) የሴክተር ስድስት ምክትል አዛዥ ኮሎኔል ማኩርጋ ፓናርድ፥ የኢትዮጵያና ኬንያ ሰላም አስከባሪ ሃይል በጋራ በአካባቢው ሰላም ለማስፈን እየሰሩ መሆኑን ገልጸዋል፡፡የክልሉ የፀጥታ ሃይል፣ ከፍተኛ የስራ አመራሮችና ህብረተሰቡም ከጎናቸው እንደሆነ አስታውቀዋል፡፡የ5ኛ ሞተራይዝድ ሻለቃ ዋና አዛዥ ኮሎኔል አሰፋ መኮንን በበኩላቸው፤ የቀጣናውን የሰላምና የፀጥታ ሁኔታ ለማጠናከር አልሸባብን በመዋጋት እንዲሁም የኬላ ፍተሻዎችን በማጠናከር የህብረተሰቡን ሰላምና ደህንነት ማረጋገጥ እንደሚገባ ጠቁመዋል፡፡አዲስ መን ታህሳስ 28/2013
https://www.press.et/Ama/?p=38959
178
0ሀገር አቀፍ ዜና
የማህበረሰባችን ሞራል የት ደረሰ?
መዝናኛ
November 21, 2019
44
በልጅነቴ ያስተዋልኩትን ሐቅ ልንገራችሁ። ነገሩ እንዲህ ነው። ሰዎች ተሰባስበው፣ እንዲቀናቸው ተመርቀው አደን ይሸኛሉ፡፡ኑሯቸውን በዱርና በገደል ያደርጋሉ፡፡በዚህ ሁኔታ ለወራት በመቆየት በለስ የቀናው አንበሳ በመግደል ጀግና ይሰኛል፡፡በለስ ያልቀናው በርሃብ ሲናውዝ ከርሞ ይመለሳል። ገዳዩም ጀግንነቱን በገበያ ያስመርቃል፤ ያውጃል፡፡የገደለውን የአንበሳ ቆዳ በትከሻው ላይ ይደርባል፤ ፀጉሩንም ቅቤ ይቀባል፡፡ከዚያም ሌሎች ጥቂት የሥጋ ዘመዶቹን አስከትሎ በገበያው መሐል እየተንጎማለለ ስለመፈጠሩ እንኳን በውል የማያውቁት በርካታ ሰዎችን በመንጋ ያስጨፍራል፤ ሲዘፍኑለት ይውላሉ፡፡እርሱም እንደሙሽራ ሲሳምና ሲሸለም የሞራል ግለቱ ጣራ ይነካል፡፡እግር የጣለው ሁሉ እያጨበጨበ አብሮ ይተማል፡፡የእንስሳት መብት ተሟጋች በማያውቃት አገራችን በቀደሙት ጊዜያት የአንበሳ ነፍስ ማጥፋት በመንጋ ያስከብርና በመንጋ ያዘፍን ነበር፡፡አሁን ላይ ይባስ ብሎ የሰው ልጅ ሕይወትን በመንጋ ማጥፋት እና በመንጋ አስክሬን መጎተት በመንጋ ያስከብር ይዟል፡፡በመንጋም ሲያስጨፍር አስተውለናል፡፡ እርግጥ ነው በዚህ የመንጋ እንቅስቃሴ ውስጥ የሀብት ጥሪት የመቋጠር ዕድል ያጋጠማቸው እንዳሉም ሹክሹክታ ይሰማል፡፡በመንጋው በአባልነት ተቀላቅለው የዘመቱ በቀን እስከ 500 ብር ሲቋደሱ፤ በመንጋው ዘመቻ በርካታ ሰው በመውረር ‹‹አራስ ነብር›› ሆነው ለዋሉ ደግሞ እንደዘመቻ አውዱ በበቃኝ ሳንቲም እንዲዘግኑ ይደረጋል መባሉን ከመከራ ቀማሿ ድሬ ሹክ ብለውናል፡፡አጃኢብ ያሰኛል፤ ጆሮ አይሰማው የለ፡፡ይሄ ገንዘብ የሚበቅልበትን ዛፍ አምላክ ይወቀው፡፡ተሠርቶ ያልተገኘ በጂኒ የሚመጣ ገንዘብ ሕዝቡን በመንጋ የጂኒ አመል እንዲኖረው አደረገ፡፡ለመልካም ተግባር ሲሆን የመሰባሰቡና የመደመሩ ጉዳይ ዳገት ይሆንብናል፡፡የእኛ ትውልድ እንዲህ ነው፡፡ቅን መሪዎችን ሳይሆን ቅንቅኖችን የሚሻ፡፡ከአብዮች ሳይሆን ከአባዮች የሚወዳጅ፣ ከሚወዱት ሳይሆን ከሚንቁት ጉልበት ሥር የሚወሸቅ፤ ተራማጅ አስተሳሰብን ያልፀነሰ ጮርቃ ሆኗል፡፡ ቢቆነጠጥና አደብ ቢይዝ አይሻልም ትላላችሁ? ‹‹አገር ሲያረጅ ጃርት ያፈራል›› ነበር ብሂሉ፡፡ታዲያ አገሬ ተባይ ማፍራቷ አርጅታ ይሆን እንዴ? እንጃ አይመስለኝም፡፡ትውልዳችንን ልንፈትሽና ልንመረምር ይገባል፡፡ወቅቱን ጠንቅቆ የሚረዳ ብልጥ ትውልድ ያስፈልግ ይመስለኛል፡፡ዋሽቶ ማስታረቅ እንጂ ዋሽቶ ማጋደል በክብር ሲያስጠራ ከታሪካችን አልሰማንም፤ አልተማርንም፤ ለማንም አይበጅም፡፡ዘመኑን የተነጠቀና ቀልቡ የተገፈፈ ባካኝ በአንዳንዶች አጠራር ‹‹የተረገመ›› ትውልድ እንዲበቅል ቆላ ከደጋ እየባከኑ ደም ሲያራጩ መዋልን ሥራዬ ብለው የተያያዙት በርክተዋል፡፡አዎ አገሪቱ እንዲህ አይነት አዳዲስ የሥራ መስኮች የሚፈጥሩ ሰዎች እንዳሻቸው የሚኖሩባት አገር ሆናለች፡፡የተራ ዜጋውም ጉዳይ ‹‹በሬ ካራጁ ….›› አይነት ሆኗል ወዳጄ፡፡‹‹ከደሙ ንፁህ ነን›› ባይ አፈቀላጤዎችም ወንድም ወንድሙን መግደልና ሲያሸብሩ መዋል እንደ ሥራ ስለመቆጠሩ እየነገሩን ነው፡፡እንደው ማን ይሙት በእኔ ልጅ ደም የእሱን ልጅ እንጀራ የሚያበስል የዋህ ኢትዮጵያዊ ስለመፈጠሩ እንደመስማት የሚያንገሸግሽ ሕመም ምን አለ?፡፡ በእምነት ቅንብብ አጥር ውስጥ በቅሎ እዚህ የደረሰ ኢትዮጵያዊ ‹‹ያልዘራውን የሚያጭድ›› አለመኖሩን መረዳት አያዳግተውም፡፡ የሰው ልጅ በሥራው ልክ ተመዝኖ የሚከፈለው በአንድ ወቅት በዓለም ላይ የበቀለ አረም ተደርጎ ሊታይ ይገባል፡፡ራሱን ዘላለማዊ በማስመሰል የአልማዝ፣ የወርቅና የብር ደረጃዎች እየሰጡ እያንዳንዱን ነገር ‹‹ለእኔ›› እያሉ መስገብገብ የኢትዮጵያውያን ስብዕናም አይደለም፡፡የሰው ልጅ ሕይወት መጥፋት የሚያስጨፍረው አካል መታየት ሲጀምር መላ ሊበጅለት ይገባል፤ ሕመም መለከፉን መረዳት ያስፈልጋል። ነገ ራሱ ተራ ጠባቂ ሟችነቱን ረስቶታል ማለት ነው፡፡‹‹ሆሆይ›› ለካ ነገረ ሥራው ከተቀየረ ዋል አደር ብሏል። የምኑ እንዳትሉኝ፤ ከመኖሪያ ቀያችሁ እስከ ፌስቡክ ሰፈራችሁ የምታዩትንና የምትሰሙትን ወሬና ድርጊት አብጠርጥራችሁ ፈትሹ፡፡‹‹ከሞኝ ደጃፍ ሞፈር…›› ነው ነገሩ፡፡ከእነ እንትና ሰፈር ዕሳት እየጫሩ በእነ እንትና ሰፈር በ‹‹ቪ ኤይት›› ቄንጠኛ መኪና መንፈላሰስ ዋ! ካላስባለ፣ ነገ ጨዋ ልጅ ከሰፈርህ ቀርቶ ከአብራክህ ሊወጣ አይችልም፡፡የሰውነት ሚዛናችን እያነሰ የእንስሳነት አመላችን እየጎለመሰ ይሄድ ይዟል፡፡ እኔ ለአቅመ ማስተዋል ከደረስኩበት ጊዜ አንስቶ ያስተዋልኩት የሰው ልጅ ሞራል የማጣት ልክ እንደዚህ ጊዜ ሲዘቅጥ አስተውዬ አላውቅም፡፡ምን አልባት የእኔ የማስተዋል ልክ ከሆነ አላውቅም፡፡ኧረ እንደውም ባደግንበት ወግና ባህልማ የሰው ልጅ በሕይወት ሲኖር ከሚያገኘው ክብር የላቀ አስክሬኑ ይከበር ነበር፡፡አብሮን ባደገው የመበቃቀል ክፉ ልማዳችንም ውስጥ ቢሆን እንጥፍጣፊ መከባበር ነበረበት፡፡እንኳንስ ሰውን ያህል ነገር ቀርቶ የእንስሳትም ቢሆን አስክሬን የተመለከተ ሰው ያዝናል፤ ባስ ሲልም በዓይኑ በብረቱ የሰው አስክሬን ወድቆ በድንገት የተመለከተ ሰው ራሱን ለከፍተኛ ፀፀት ይዳርጋል፡፡ምን የሠራሁት ሐጢያት (ክፉ ሥራ ) ቢኖር ይሆን ፈጣሪ ይሄን ያሳየኝ፤ በሚል ነፍሱን እሱ ያጠፋ ያህል ፈጣሪውን በፀፀት ይለምናል፡፡ነፍሱ በፈጣሪው ፊት ትጠየቅ እስከሚመስለው ድረስ ይፀፀታል፡፡‹‹ማረኝ›› ይላል፡፡አሁን አሁን የሚስተዋለው ድርጊት ግን ለየቅል ሆኗል፡፡እመኑኝ ታሪክ ዋሽቷል ወይም ትውልዱ ላሽቋል የሚያሰኝ ደረጃ ላይ እንገኛለን፡፡በመንጋ ተነስቶ በመዝመት የሰው ልጅ ሕይወትን ማጥፋት በየትኛውም እምነት የተወገዘ ብቻ ሳይሆን አውሬነት ተደርጎ የሚቆጠር ተግባር ነው፡፡እንዲህ አይነት የአውሬነት ተግባር የመፈፀም ድፍረት እንዲሁ በአጭር ጊዜ የሚለመድ ባህሪ አይምሰላችሁ፡፡ይህ ትውልድ ጤንነቱ ሊፈተሽ የሚገባ ይመስለኛል፡፡በማንኛውም መመዘኛ ሊያሳምን የሚችል አመክንዮ የሚቀርብበት ጉዳይ አይደለም፡፡አዲስ ዘመን ኅዳር 11/2012 ሙሐመድ ሁሴን
https://www.press.et/Ama/?p=22886
576
1መዝናኛ
መገናኛ ብዙሃን የአገር ሰላምንና አብሮነትን በማጎልበት ረገድ የሚጠበቅባቸውን እየተወጡ እንዳልሆነ ተገለጸ
ሀገር አቀፍ ዜና
January 6, 2021
11
 አዲስ አበባ (ኢዜአ)፦ መገናኛ ብዙሃን የአገር ሰላምና የህዝቦችን አብሮነትን በማጎልበት ረገድ የሚጠበቅባቸውን ሚና እየተወጡ እንዳልሆነ ተገለጸ። የኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባዔና የኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለስልጣን ትናንት በጋራ ባዘጋጁት የውይይት መድረክ ላይ የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ዋና ጸሃፊ ቀሲስ ታጋይ ታደለ እንዳስታወቁት፤ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ መገናኛ ብዙሃን እውነተኛ መረጃን ከማሰራጨት ይልቅ የህዝቦችን አብሮነት የሚሸረሽሩ ዘገባዎችን እያቀረቡ ነው። መገናኛ ብዙሃን የሚያሰራጯቸው መረጃዎች በዜጎች ደህንነት ላይ የሚፈጥሩትን አደጋ ሊገነዘቡ እንደሚገባም ያመለከቱት ቀሲስ ታጋይ፤ ‘እኛና እነሱ’ በሚል አስተሳሰብ የሚሰራጩ የተሳሳቱ ዘገባዎች በርካታ ንጹሃን ላይ ጉዳት እንዲደርስ ምክንያት መሆኑን አስታውቀዋል።የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጋዜጠኝነትና ተግባቦት ትምህርት ክፍል መምህር ዶክተር ሙላቱ አለማየሁ በበኩላቸው፤ በተለይ የፖለቲካ ሰዎችና አክቲቪስቶች በሚዲያ ቀርበው በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የጥላቻ ንግግሮችን ሲያስተላልፉ እንደሚስተዋል ተናግረዋል።“አብዛኞቹ የጥላቻ ንግግሮችም በዜና መልክ ለህዝቡ የሚቀርቡ ናቸው” ብለዋል።በርካታ የመገናኛ ብዙሃን ለሰላም ግንባታ ያላቸው ሚና በአግባቡ ከመወጣት ይልቅ ግጭቶች ላይ ትኩረት አድርገው እየሰሩ መሆኑንም አስታውቀዋል።በቅርቡ 15 ያህል መገናኛ ብዙሃን ላይ በተደረገ ጥናት 28 በመቶ የሚሆኑት ፖለቲካዊ ጉዳዮች ላይ ትኩረት አድርገው የሚሰሩ መሆናቸውንም ጠቁመዋል።18 በመቶው የሚሆነው ሽፋናቸው ደግሞ በግጭቶችና ከዚያ ጋር ተያይዞ በሚከሰቱ ሰብዓዊ ቀውሶች ላይ ትኩረት ያደረጉ መሆናቸውን ገልጸዋል።ጥናቱ መገናኛ ብዙሃን ለሰላም መስፈን ያበረከቱት አስተዋጽኦ ዝቅተኛ መሆኑን ያመላከተ እንደሆነም አስታውቀዋል።“የመገናኛ ብዙሃን አሰራር በሚፈለገው ልክ አለመዘመን ተልዕኳቸውን በአግባቡ እንዳይወጡ አድርጓል” ያሉት ደግሞ የኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ወንድወሰን አንዷለም ናቸው።የሚዲያ ስነ-ምግባር ከየትኛውም ሃይማኖት አስተምህሮ ጋር የሚጣጣም በመሆኑ በተለይ የህብረተሰቡን መልካም እሴቶች አጉልቶ በማውጣት ረገድ ከፍተኛ ኃላፊነት እንዳለባቸውም ገልጸዋል።የመገናኛ ብዙሃኑም ህግና ስርዓትን አክብረው ለአገሪቷ ሰላምና መረጋጋት የድርሻቸውን እንዲወጡ የአቅም ግንባታ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑንም ተናግረዋል።የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባዔ የበላይ ጠባቂ አባቶችም መገናኛ ብዙሃን ለአገሪቷ ሰላምና ለህዝቦች አንድነት የተጣለባቸውን ኃላፊነት እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል።አዲስ መን ታህሳስ 28/2013
https://www.press.et/Ama/?p=38960
251
0ሀገር አቀፍ ዜና
ኮሚሽኑ ለመተከል ተፈናቃዮች ዘላቂ ድጋፍ እንደሚያደርግ አስታወቀ
ሀገር አቀፍ ዜና
January 6, 2021
5
አሶሳ፡- በተባበሩት መንግስታት የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽን የመተከል ተፈናቃዮችን መልሶ ለማቋቋም የሚደገውን ጥረት በዘላቂነት እንደ ሚደግፍ አስታወቀ፡፡ በኮሚሽኑ የአሶሳ ንዑስ ቢሮ ኃላፊ ሚስ ጆላንዳ ቫን ለኢዜአ እንዳስታወቁት ፣ ኮሚሽኑ የመተከል ተፈናቃዮችን ለመደገፍ ከክልሉ መንግስት ጋር በቅንጅት እየሠራ ነው፡፡በክልሉ የተለያዩ የተባበሩት መንግስታት ረጂ ድርጅቶች እንዳሉ የጠቀሱት ኃላፊዋ፤ ድጋፉን ለማጠናከር ቅንጅታዊ አሰራር ፈጥረን እየተንቀሳቀስን ነው ብለዋል፡፡ካለፈው ሐምሌ ወር ጀምሮ ለዞኑ ተፈናቃዮች ምግብ ነክ ያልሆኑ የቁሳቁስ ድጋፎች ሲደረጉ መቆየታቸውን አመልክተዋል፡፡የመተከል ተፈናቃዮችን መልሶ ለማቋቋም መንግስት የሚያደርገውን ጥረት ኮሚሽኑ በቀጣይም በዘላቂነት እንደሚደግፍ አስታው ቀዋል፡፡ ከኮሚሽኑ ጋር በመቀናጀት ለመተከል ተፈና ቃዮች ድጋፍ እያደረጉ ከሚገኙ ተቋማት መካከል አክሽን ፎረ ዘ ኒዲ የተባለ ረጂ ድርጅት የአሶሳ ቅርንጫፍ አንዱ ነው፡፡ የቅርንጫፉ ኃላፊ አቶ መላኩ ገዛኸኝ እንዳሉት፤ ድርጅቱ ሰሞኑን ለመተከል ተፈናቃዮች ባደረገው የመጀመሪያ ዙር እገዛ የተለያዩ ቁሳቁሶችን በድጋፍ አቅርቧል፡፡ከቁሳቁሶች መካከል የምግብ ማብሰያ እና መመገቢያ ቁሳቁሶች፣ አልባሳት፣ ፍራሽ፣ የአልጋ አጎበር እና ሌሎችም ለክልሉ አደጋ ስጋት እና ስራ አመራር ኮሚሽን ማስረከቡን ጠቅሰው፤ ድጋፉ ቀጣይነት እንደሚኖረው አስታውቀዋል፡፡የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል አደጋ ስጋት እና ስራ አመራር ኮሚሽነር አቶ ታረቀኝ ተሲሳ በበኩላቸው ፣በክልሉ የመተከል ተፈናቃዮችን መልሶ ማቋቋም መንግስት ብቻውን የሚወጣው ባለመሆኑ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችን የማሳተፍ ስራ እየተካሄደ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡ ድርጅቶቹ ለቀረበላቸው ጥያቄ ተግባራዊ ምላሽ እየሰጡ ነው ብለዋል፡፡ድጋፉን እያደረጉ ከሚገኙ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች መካከል የተባበሩት መንግስታት የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽን እና አብረው የሚሰሩት ድርጅቶች ዋነኞቹ እንደሆኑ ገልጸዋል፡፡ ድጋፉን በክላስተር በመለየት ለማሰባሰብ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ጠቁመው፤ ድጋፉን ወደ መተከል በቀጥታ ማድረስ የማይችሉ ድርጅቶች በአሶሳ እና አካባቢው እንዲያስረክቡ እየተደረገ ነው ብለዋል፡፡ እስካሁን በርካታ ምግብ እና ቁሳቁሶች በድጋፍ መሰብሰባቸውን ጠቁመዋል፡፡በቅርቡ የተሰባሰበው ድጋፍ ወደ መተከል ቡለን እና ድባጤ ለማድረስ እየተሠራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በተባበሩት መንግስታት የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽን ቀደም ሲልም ለመተከል ተፈናቃዮች ከ30 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመቱ ቁሳቁሶች ድጋፍ ማድረጉ በወቅቱ ተገልጿል።አዲስ መን ታህሳስ 28/2013
https://www.press.et/Ama/?p=38973
261
0ሀገር አቀፍ ዜና
ከባድ ፈተናን ተሻግሮ የሚወለድ ስኬት
ስፖርት
May 31, 2020
35
ማንኛውም ሰው በሕይወት ዘመኑ ፈተና ይገጥመዋል፡፡ ፈተናው ከባድም ቀላልም ሊሆን ይችላል፡፡ ቁምነገሩ ፈተናውን አልፎ ወደሚታሰብ ስኬት መድረስና ለዚህም ተስፋ ሳይቆርጡ የሚቻለውን ብቻ ሳይሆን የማይቻለውን ነገር ለመሞከር ጥረት ማድረግ ነው፡፡ የስፖርቱ ዓለም ሰዎች ወደ ታላቅ ስኬት ከመሸጋገራቸው በፊት የተለያዩ ከባድ ፈተናዎችን የመጋፈጥ አጋጣሚዎች በሕይወት ዘመናቸው ሲከሰቱ ማየት የተለመደ ነው፡፡ የስፖርቱ ዓለም በርካታ ከዋክብቶች ከሞላ ጎደል በዚህ ዓይነት የሕይወት ውጣ ውረድ ማለፋቸውን የስኬታቸው ጫፍ ላይ ሆነው ሌሎችን ለማስተማርና ለማነሳሳት ብሎም በሕይወት ዘመናቸው የቱንም ያህል ከባድ ፈተና ቢገጥማቸው ውስጣቸውን በተስፋ ለመሙላት ሲናገሩት ይደመጣል፡፡ ዓለማችን በጤና ቀውስ ውስጥ ባለችበት በዚህም ወቅት የተለያዩ የስፖርቱ ዓለም ወጣትና ተስፈኛ ትውልዶች በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ ችግሮች ሊደቀኑባቸው እንደሚችሉ እርግጥ ነው፡፡ በተለይም እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ታዳጊ አገራት ውስጥ ነገን በትልቅ ተስፋ የሚጠባበቁ ወጣት ስፖርተኞች የአገራችንም ይሁን የዓለም ስፖርት መድረኮች ሽባ በሆኑበት በዚህ ወቅት በምጣኔ ሀብትና በሌሎች ፈተናዎች ሊወጠሩ እንደሚችሉ ግልፅ ነው፡፡ ይህን ፈተና በፅናት ለማለፍ የሥነልቦና ጥንካሬና ተስፋ አለመቁረጥ በባለሙያዎችም ይመከራል፡፡ ከዚህም በዘለለ አሁን ላይ በስኬት ማማ ላይ የተቀመጡ ከዋክብቶች ካለፉባቸው የሕይወት ውጣ ውረዶች በመማር ራሳቸውን በተስፋ መሙላት ይጠበቅባቸዋል፡፡ ለዚህም የሼን ደፊ ፈተናና የኋላ ስኬት ታሪክ አንዱ ምሳሌ ሊሆን ይችላል፡፡ እ.አ.አ በ2010 ሰኔ ወር ሼን ደፊ መልዕክት ደረሰው። ለአየርላንድ ብሔራዊ ቡድን ለመጀመሪያ ጊዜ መጠራቱን የሚያበስር መልዕክት ነበር። ገና በአስራ ስምንት ዓመቱ ለብሔራዊ ቡድን መጠራቱ ታላቅ ተስፈኛነቱን ያረጋገጠለት ስለነበር ደስታው ወደር አልነበረውም። ደፊ ዘለግ ያለ፣ ደንደን ያለ የፈርጣማ ሰውነት ባለቤት ነው። ሃያ ዓመት ሳይሞላው ዘጠና ኪሎ ግራም ይመዝናል። ቁመቱ ደግሞ 1ነጥብ 93 ሜትር ይረዝማል። እ.አ.አ በ2010 በኤቨርተን ጥቂት ጨዋታዎች ላይ እንደተሰለፈ ጆቫኒ ትራፓቶኒ ለአየርላንድ ብሔራዊ ቡድን የጠሩት ለመሐል ተከላካይነት ስፍራ ያስፈልጋል የሚሉት ተክለ ሰውነት ስላለውም ጭምር ነበር።አየርላንድ ከፓራጓይ ላለባት ግጥሚያ ቡድኑ ዝግጅት ጀመረ። በልምምድ ማዕከሉ የልምምድ ጨዋታ ሲያደርግ ደፊ በተከላካይነት ሚናው ተጫወተ። በጨዋታው እንቅስቃሴ መሐል ከክንፍ በኩል ኳስ ተሻማ። ደፊና የተከላካይ መስመር አጋሮቹ የሚያጠቃው ቡድን ተሻጋሪዋን ኳስ እንዳያገኛት ለማገድ ተረባርበው ታገሉ። ደፊም ተሻማ። ግን ግጭት ደርሶበት ወደቀ። አጋጣሚው ወትሮ ከሚያጋጥም የ«ጎል ላስቆጥር፣ አታስቆጥርም» ፍልሚያ የተለየ አልነበረም። ጉዳቱም ከተለመደ ጉዳት ይለያል ብሎ መገመት አይቻልም። ግን ግዙፉ ጎረምሳ ከወደቀበት መነሳት አቃተው። የተቧጨረ፣ የደማ፣ የተሰበረ የውጪያዊ ሰውነት ክፍል አይታይበትም። ሆኖም ደፊ ጣር ያዘው። ተሰቃየ። የሲቃ ድምፁን አሰማ። የአየርላንድ ቡድን የሕክምና ቡድን አባላት ህመም የሚሰማው የትኛው የሰውነቱ ክፍሉ ላይ እንደሆነ ሲጠይቁት በጎድን አጥንቱ ስር ያሳያቸዋል። ስቃዩን አይተው የገጠመው ጉዳት ቀላል እንዳልሆነ በመረዳታቸው በአስቸኳይ በአምቡላንስ ወደ ሆስፒታል ወሰዱት።በደብሊን በሚገኘው ማተር ሆስፒታል ሲደርስ አስቸኳይ ቀዶ ጥገና ታዘዘለት። ግብ ክልል ውስጥ የነበረው ፍትጊያና ግጭት ውጪያዊ ሳይሆን ውስጣዊ አካሉ ላይ ከባድ ጉዳት አድርሶበታል። በቢላዋ የሸረከቱት ይመስል ጉበቱ ተቀደደ። 3ነጥብ6 ሊትር ደም በመፍሰሱ ሆዱ ተነፋ። ከሰውነቱ የደም መጠን ሁለት ሦስተኛ የሚሆነው ሆድ ዕቃውን ሞላው። እሱንም ለማስቀረት የቀዶ ጥገና ርብርቡ ቀጠለ። በዚያች ክፉ ማክሰኞ አደጋው ደርሶበት ሆስፒታል ከገባ በኋላ እስከ ሐሙስ ድረስ ራሱን ስቶ ቆየ። ከዚያም እስከ እሁድ ድረስ በከፍተኛ የሕክምና ክትትል መስጫ ክፍል ውስጥ ከረመ። በሆስፒታል ኮሪደር ላይ በጭንቅ ወዲያ ወዲህ የሚሉት ወላጆቹ ከከፍተኛ የሕክምና ባለሙያዎቹ ቁርጡ ተነገራቸው። «ልጃችሁ የመትረፍ ዕድሉ ጠባብ ነው» ተባሉ። የልጃቸውን የሞት ዜና መጠባበቅ ጀመሩ።የደፊ ጉበት ደም ስሮች በመተርተራቸው ደሙ ውስጡ ተንዠቅዥቋል። ብዙ ደም ከመደበኛ ሥራው ውጪ ሆኗል። የተጫዋቹን ሕይወት ለመታደግ ብዙ ደም ወደ ሰውነቱ መጨመር አስፈለገ። ልቡና አእምሮው ደም ማጣት የለባቸውምና። በእግር ኳስ ሜዳ ላይ እንዲህ ዓይነት ጉዳት የተለመደ አይደለም። ጉዳቱ በከባድ የመኪና አደጋ ጊዜ ሊያጋጥም የሚችል እንደሆነ ዶክተሮቹ ይናገራሉ። ይሁን እንጂ ሕክምናው ስኬታማ ነበር። አቅሉን ከሳተበት ሲመለስ ምን ዓይነት አደጋ እንደደረሰበት ተነገረው። እርሱም «በቃ አበቃልኝ» በማለት ተስፋ ቆረጠ። ሐኪሞቹ ግን ጥረታቸውን ቀጠሉ። ደፊ ከጉዳቱ ሙሉ ለሙሉ ለማገገም ስድስት ሳምንታት አስፈለጉት። ለማገገም ብዙ ለፍቶ ከስድስት ወራት በኋላ ልምምድ ጀመረ። ዘጠና ኪሎ ግራም ይመዝን የነበረው ተከላካይ አስራ ስምንት ኪሎ ግራም ቀንሶ ወደ ሰባ ሁለት ኪሎ ግራም ወረደ። አቅሙን ሁሉ ለመመለስ ሁለት ዓመት ገደማ ፈጀበት። ደፊ ከዚህ ሁሉ ፈታኝ ውጣ ውረድ በኋላ ወደ ጨዋታ ሲመለስ ግን ኤቨርተን ቀድሞ የሚያውቀውን ብቃቱን ማግኘት አልቻለም። ስለዚህ እ.አ.አ ከ2011 እስከ 2016 ድረስ በበርንሊ፣ ስካንትሮፕ ዩናይትድና ዩኦቪል ታውን በውሰት ተዘዋውሮ ለመጫወት ተገደደ። ከ2014 – 2016 ደግሞ በብላክበርን ሮቨርስ ቆየ። ከአሰቃቂው ጉዳት ስድስት ዓመታት በኋላ በሁለተኛው ዲቪዚዮን የሚወዳደረው ብራይተን ኤንድ ሆቭ አልቢዮን አስፈረመው። ያኔ የመከራውና የጭለማው ዘመን አልፎ የንጋቱ ወጋገን ደምቆ ታየው። «ሳቢሳዎቹ» ወደ ፕሪሚየር ሊግ ሲያድጉ ደፊ ከቁልፍ ተጫዋቾቻቸው አንዱ ለመሆን በቃ። እ.አ.አ በሰኔ 2017 የአየርላንድ ብሔራዊ ቡድን ይህን ከሞት የተረፈ ተጫዋች በድጋሚ ጥሪ አደረገለት፡፡ እንደ አጋጣሚም ሆኖ ይሁን የዕጣ ፈንታ ጉዳይ ደፊ ለብሔራዊ ቡድን ጥሪ ሲደረግለት ዳግም ጣጣ አላጣውም፡፡ ከሊድሱ ተጫዋች ዩናይ ኦካኒ ጋር ከትውልድ ከተማው ዴሪ ወደ ብሔራዊ ቡድኑ ካምፕ በመጓዝ ላይ ሳሉ የመኪና አደጋ ደረሰባቸው። ሆኖም አደጋው ጉዳት ሳያደርስባቸው አለፈ። የመኪና አደጋ ሳይሆን እግር ኳስ ጨዋታ የመኪና አደጋ ያህል የጎዳው ሼን ደፊ ዛሬ ላይ ዕድሜው ሃያ ስምንት ደርሷል። የመከራው ጊዜ አልፎለት በየሳምንቱ መጨረሻ ለፕሪሚየር ሊጉ ብራይተን ተሰልፎ ለመጫወትም በቅቷል፡፡ ፅናቱም በተሻለው ደረጃ ላይ አስቀምጦታል። ከዚያ ሁሉ መከራና የጭንቅ ጊዜ አልፎም ከአጥቂዎች ጋር በግብ ክልል ውስጥ ሲታገል ታይቷል፣ ሲከላከልም ሆነ ሲያጠቃ የ2010ሩ አሰቃቂ የሕይወት አጋጣሚው አይታወሰውም። ቦጋለ አበበ
https://www.press.et/Ama/?p=33455
738
2ስፖርት
የውድድሮች መመለስ ስጋትና ጥቅሙ ሚዛን ላይ ሲቀመጥ
ስፖርት
June 1, 2020
23
በኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ 19) ስጋት ምክንያት ተቋርጠው የቆዩ እንቅስቃሴዎች አሁን ወደ ነበሩበት እየተመለሱ ነው። የአውሮፓ ሊጎችም የውድድር ዓመቱን ካቆመበት በመቀጠል ሂደት ላይ ናቸው። የጀርመን ቡንደስ ሊጋ ከሁሉም ቀድሞ ወደ ውድድር የተመለሰ ሲሆን፤ የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ፣ የስፔን ላሊጋ እና የጣሊያን ሴሪ ኤም ከተያዘው የፈረንጆቹ ወር ጥቂት ቀናት በኋላ ካቆሙበት ለመቀጠል ክለቦች ልምምድ ጀምረዋል። የዓለም አትሌቲክስም የዳይመንድ ሊግ ውድድሮችን ለማስጀመር ቀን መቁረጡ ታውቋል። በዚህ ወቅት ሃገራት ከቫይረሱ ቀውስ መጠነኛ ማገገም እንጂ ጥናትና ምርምሩ ያልተጠናቀቀውን ወረርሽኝ ጨርሰው ተቆጣጥረውታል ለማለት አዳጋች እንደሆነባቸው ግልጽ ነው። ዓለም በዚህ ጭንቀት ውስጥ ባለችበት ወቅት ስፖርት ወደነበረበት መመለሱ በጤና ነው? የሚሉ አስተያየቶች ከተለያዩ አቅጣጫዎች እንዲነሱ አድርጓል። እርግጥ ነው ክለቦች እንደ ቀድሞው የተጫዋ ቾቻቸውን ሙሉ ደመወዝ መክፈል በማይችሉበት ደረጃ ተቸግረዋል። አትሌቶችም በውድድሮች መሰረዝና መራዘም ምክንያት ገቢ ማግኘት አልቻሉም። በአጠቃላይ በስፖርቱ ዘርፍ የሚሰሩ አካላት በቢሊዮን ለሚቆጠር የገንዘብ ኪሳራ ተዳርገዋል። አሁን ካሉበት በጥቂቱም ቢሆን ለማገገም ደግሞ ውድድሮችን ማካሄድ ይኖርባቸው ይሆናል። ለተመልካች ዝግ የሆኑ ስታዲየሞችና የስፖርት ሜዳዎችም አማራጭ በመሆናቸው ላይ ሁሉም የሊግ አመራሮች ተስማምተዋል። እንዲያም ሆኖ ግን የጤና ባለሙያዎች ዓለም ራስ ምታት ከሆነባት ወረርሽኝ ሳታገግም ወደ ውድድሮች በመመለሳቸው ስጋታቸው ማየሉን አልሸሸጉም። በመድሃኒቶች ላይ የማማከር ስራ የሚሰሩት ዶክተር ማሶድ ኤጋ ‹‹ይህ ወቅት አሁንም መገለል የሚያስፈልግበት እንጂ ውድድሮች የሚጀመሩበት ነው ለማለት ያስቸግራል›› ሲሉ ቲአቲ ወርልድ ለተባለ ድረ ገፅ ስጋታቸውን ገልጸዋል። አሁን በጨዋታ ላይ የሚገኘው ቡንደስ ሊጋ ከመንግስት ፈቃድ ያገኘው እያንዳንዱ ክለብ ንጽህናውን በሚገባ እንዲጠብቅ በማሳሰብ ጭምር ነው። ከዚህ ቀደም በእግር ኳስ ማህበሩ ሁለት ዲቪዚዮን ውስጥ የሚጫወቱ 1ሺ724 ተጫዋቾች ላይ በተደረገው ምርመራ 10 የቫይረሱ ተጠቂዎች መገኘታቸውን ዘገባው አስታውሷል። በመሆኑም ንጽህናን ከመጠበቅ ባሻገር እያንዳንዱ ተጫዋች በየዕለቱ መመርመር እንዳለበት ዶክተር ማሶስ ያሳስባሉ። ይህ ካልሆነ ግን ቫይረሱ ድምጹን አጥፍቶ ከአንዱ ተጫዋች ወደሌላው ከዚያም ወደ ክለቦች በመዛመት ለመቆጣጠር አደገኛ ሊሆን እንደሚችልም ይጠቁማሉ። አሁንም ከተመልካች ውጪ ጨዋታን ማካሄድ አቻ የሌለው አማራጭ መሆኑ በስፖርት ቤተሰቦች ዘንድ ታምኗል። የጤና ባለሙያዎች በአንጻሩ ተመልካቾች ባይኖሩም በስታዲየም አካባቢ ከ100 የሚልቁ ሰዎች መገኘታቸው ከስጋት እንደማያድን ነው የሚያስገነዝቡት። ሊጎች እንዲሁም ክለቦች በበኩላቸው ከገቡበት የኢኮኖሚ ጫና ለመውጣት ባላቸው ብርቱ ፍላጎት ምክንያት የባለሙያዎችን ምክር ችላ እንዳሉ ቀጥለዋል። ተወዳጁ የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ ቀሪዎቹን 92 ጨዋታዎች በማካሄድ የውድድር ዓመቱን ካላጠናቀቀ የ1ነጥብ25 ቢሊዮን ዶላር ኪሳራ የሚያጋጥመው ይሆናል። በመሆኑም በተመረጡ ስታዲየሞች ከደጋፊ ውጪ ጨዋታዎቹን ለማካሄድ ቀናት ብቻ ቀርተዋል፤ ክለቦችም የልምምድ ሜዳዎቻቸውን ከፍተዋል። የጤና ባለሙያዎች በበኩላቸው ጨዋታዎቹን የግድ መቀጠል ቢገባ እንኳን ክለቦች ተጫዋቾቻቸውና ቤተሰቦቻቸው ላይ ሞት ሊከተል እንደሚችል፣ የሚገጥማቸውን ኪሳራ እንዲሁም ካሳን ታሳቢ ማድረግ እንዳለባቸው ያሳስባሉ። ሌላው የባለሙያዎች ስጋት የወረርሽኙ ፈጣን ስርጭት ሲሆን፤ በላብ እንዲሁም በግብ ጠባቂዎች ጓንት አማካኝነት የመዛመት እድሉ ሰፊ መሆኑንም ነው ያመላከቱት። ለዚህ ስጋት ምክንያት የሆነው ደግሞ ባለሙያዎቹ ለሚሰጡት ምክር የየክለቡ የጤና ባለሙያዎች ትኩረት እየሰጡ አለመሆናቸውን ነው። ከዚህ ባሻገር ተጫዋቾች በሚገባ በየዕለቱ ምርመራ እያደረጉ እንኳን፤ ደጋፊዎቻቸው ደግሞ ጨዋታን በቴሌቪዥን ለመከታተል አካላዊ ርቀታቸውን ሳይጠብቁ ይሰባሰቡ ይሆናል የሚል መሆኑን ዶክተር ማሶድ ያሰምሩበታል። የቡድን ስፖርቶች በባህሪያቸው ለአካላዊ ርቀት የማይመቹ በመሆናቸው እንደየስፖርት ዓይነቱ ውድድሮች ቢቀጥሉ የሚል ምክረ ሃሳብ የሚያቀርቡት ደግሞ በአሜሪካ የኮቪድ 19 ግብረ ኃይል አማካሪ እንዲሁም የብሄራዊ የኢንፌክሽን በሽታዎች ምርምር ማዕከል ዳይሬክተር የሆኑት ዶክተር አንቶኒ ፉሲ ናቸው። መታሰብ ያለበት ወረርሽኙ እንዴት በቀላሉ ከአፍንጫ ወደ እጅ ከዚያም ወደ ልብስ በመጨረሻም ወደ ሌላ ሰው እንደሚተላለፍ ነው። በመሆኑም ቀጣዩ የስጋት አቅጣጫ ጨዋታዎችና ግጥሚያዎች እንዳይሆኑ መጠንቀቅ አስፈላጊ ነው። የዓለምን እግር ኳስ የሚመራው ፊፋ የሕክምና ኮሚቴ ሊቀመንበርና የፊፋ ስራ አስፈጻሚ የሆኑት ዶክተር ሚካኤል ባሮን ሆግ በበኩላቸው ‹‹ዓለም ለእግር ኳስ ውድድሮች ዝግጁ አይደለችም›› ይላሉ። ቤልጂየማዊው ዶክተር ዘ ሰን ከተባለው ድረ ገጽ ጋር በነበራቸው ቆይታ፤ ዓለም ለጤና እና ለመድሃኒት ቅድሚያ መስጠት ያለበት ወቅት ላይ መሆኗን ይገልጻሉ። አደጋውን ሲያመለክቱም ‹‹በዚህ ድራማዊ በሆነ ክስተት ውስጥ ኃላፊነት መውሰድ ከባድ ነው። ተጫዋቾች በትክክል ሁለት ሜትሮችን ተራርቀው አይጫወቱም፤ የፊት ጭምብል ማድረግም አይችሉም። በሜዳ እና በመልበሻ ቤትም አብረው ናቸው። በዝግ ስታዲየም ይጫወቱ ቢባልም በሆነ አጋጣሚ ቡድናቸውን ለመደገፍ የገቡ ደጋፊዎች ይገኛሉ። ምርመራውን በየወቅቱ ማድረግ አስፈላጊ ቢሆንም፤ አንድ ሰው በቫይረሱ ተያዘ ማለት ግን ቡድኑን በሙሉ ወደ ለይቶ ማቆያ ማስገባት የግድ ይሆናል። ስለዚህ እግር ኳሱ መታገስ እና የጤና ባለሙያዎችን ምክር መስማት አለበት›› በማለት ያስረዳሉ። አዲስ ዘመን ግንቦት 24/2012ብርሃን ፈይሳ
https://www.press.et/Ama/?p=33507
598
2ስፖርት
ለአፍሪካ እግር ኳስ ፈተና ድጎማ ዘላቂ መፍትሄ ያመጣ ይሆን?
ስፖርት
June 2, 2020
19
በመላው ዓለም ከ210 ሀገራት በላይ የተዛመተው የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ የዓለምን የስፖርት እንቅስቃሴ በከፍተኛ ቀውስ ውስጥ ከቶታል። በወረርሽኙ ሳቢያ ትልልቅ የስፖርት ውድድሮች በመራዘማቸው፣ በመሰረዛቸው እና በመስተጓጐላቸው ኢንዱስትሪውን ከፍተኛ ገቢ እንደሚያሳጣው የተለያዩ ትንበያዎች አመልክተዋል። የስፖርት ኢንዱስትሪውን በስፖንሰርሺፕ የሚደግፉ ትልልቅ ዓለም አቀፍ ኩባንያዎች የበጀት ቀውስ ውስጥ መግባታቸው፣ ከትኬት ሽያጭ ከማርኬቲንግና ከተለያዩ ንግዶች የሚገኙ ገቢዎች መቆማቸው ሁሉንም ስፖርት ጎድቷቸዋል፡፡ በተለይ የእግር ኳስ ስፖርት ከፍተኛ ድርሻ የሚይዝ መሆኑ እየተነገረ ይገኛል። በዚህ ዓመት የእግር ኳሱ ገቢ በከፍተኛ ሁኔታ ይጨምራል ተብሎ ሲጠበቅ ከተላላፊው ቫይረስ ጋር በተያያዘ ገቢው በእጅጉ እያሽቆለቆለ ይገኛል። የአብዛኛዎቹ የእግር ኳስ ክለቦች ዋነኛ ገቢያቸውን የሚያገኙት ከሶስት ምንጮች ሲሆን፤ ይኸውም ከመገናኛ ብዙሃን የስርጭት መብት፣ ከስፖንሰርና ማስታወቂያዎች እንዲሁም በጨዋታ ወቅት ከስታዲየም የትኬት ሽያጭ እንደሆነ የወርልድ ኢኮኖሚ ፎረም መረጃዎች ያመላክታሉ።10 በሚደርሱ ሊጎች ያለው ቁጥራዊ መረጃ እንደሚያሳየው ከሆነም ክለቦቹ ከሚዲያ መብት ብቻ ከ50 ቢሊዮን ዶላር በላይ ያገኛሉ። ይህም ከአጠቃላይ ገቢያቸው 60 ከመቶ ይሸፍናል። በወረርሽኙ ምክንያት የውድድሮች መቋረጥን ተከትሎ ክለቦች ከእነዚህ ምንጮች የሚያስገቡት ገቢ በከፍተኛ ሁኔታ ማሽቆልቆሉን ያመላክታል። ዴይሊሜይል በዚሁ ዙሪያ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግን እንደማሳያ በመጥቀስ ያወጣው ይሄንኑ ያጠናክራል። የዓለማችን እጅግ ተወዳጅ ከሆኑ ሊጎች በግንባር ቀደምነት የሚጠቀሰው የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ በወረርሽኙ ምክንያት በከፍተኛ ሁኔታ መጎዳቱን በዘገባው ጠቅሷል። ፕሪምየር ሊጉ ባለፈው ዓመት አዲስ በገባው (ለሶስት ዓመታት) ኮንትራት 12 ቢሊዮን ዶላር ከሚዲያ መብት ብቻ ለመሰብሰብ አቅዶ ነበር። እግር ኳሱ አሁን ካለው ቁመና አኳያ እቅዱን ማሳካት የሚቻል አይሆንም ሲል ዘገባው አትቷል። ውድድሩ ሁለት ወራትን እንኳን ሳያስቆጥር ክለቦቹ ከ60 እስከ 150 ሚሊዮን ዶላር ኪሳራ ማስተናገዳቸውን እያስታወቁ ይገኛሉ። በመሆኑም ከቴሌቪዥን መብት ከሚገኝ ገቢ ብቻ እያንዳንዱ የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ ክለብ 750 ሚሊዮን ፓውንድ ያጣል። ስለዚህ ፕሪሚየር ሊጉ በዚህ ምስቅል ቅል ውስጥ ሆኖ ለማግኘት ያቀደውን ገቢ ማሳካት እንደማይችል በመግለጽ ፤ የኮቪድ -19 ወረርሽኝ የእግር ኳሱን ኢንዱስትሪ ለከፍተኛ የፋይናንስ ቀውስ የዳረገው መሆኑን በዘገባው አትቷል። የእግር ኳስ ጨዋታዎችና መሰል እንቅስቃሴዎች እንዲቆሙ መደረጉን ተከትሎ እንደ እንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ሁሉ በሁሉም ሀገራት የሊግ ውድድሮች ላይ መጠኑ ይለያይ እንጂ በፋይናንስ ቀውሱ የተጎበኙ መሆናቸው መረጃዎች እየወጡ ይገኛሉ። በተለይ በአህጉር አፍሪካ የሚገኙት ክለቦችና ብሄራዊ ፌዴሬሽኖችን በከፍተኛ ደረጃ እንዳቃወሳቸው ተነግሯል። የአፍሪካ ሀገራት ወረርሽኙን ለመከላከል የእንቅስቃሴ እግዳ መጣላቸውን ተከትሎ ኢኮኖሚያዊ መቃወስ ውስጥ አስገብቷቸዋል። የኢኮኖሚው መቃወስ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የክለቦች ቀጣይ ህልውና አስጊ ደረጃ የሚያደርስ ይሆናል። በዓለም አቀፍ ደረጃ አንቱ የተባሉ የእግር ኳስ ተንታኞች «የኮቪድ -19 ወረርሽኝ የዓለም እግር ኳስን በተለይ የአፍሪካ እግር ኳስን ከባድ ፈተና ይገጥመዋል» የሚሉ መላምቶችን እያስቀመጡ ይገኛሉ። የአህጉሪቱ እግር ኳስ በተለያዩ ችግሮች ተተብትቦ «የእድገት ውስንነት በሽታ» ሰለባ መሆኑን ያነሳሉ። የዓለም ፈተና የሆነው ኮቪድ-19 የወለዳቸው ችግሮች ተደምረውበታል። ይህም «በእንቅርት ላይ ጆሮ… » ያደርግበታል ። መጪው ጊዜ በተለይ ለአህጉር አፍሪካ እግር ኳስ ህልውና እጅጉን ፈታኝ እንደሚሆን መላምቶች እየተሰጡ ይገኛሉ። ለዓለም እግር ኳስ እድገትና ድምቀት እርሾ የሆነችውን አፍሪካ የእግር ኳኳ ህልውና ከገባበት አጣብቂኝ እንዲወጣ ድጎማ ማድረግ እንደሚገባ ምክረ ሃሳቦች ቀርበዋል። የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) የቀረቡትን ምክረ ሃሳቦች መሰረት ያደረገ ተግባር ሊፈጽም መሆኑ በሳምንቱ መጨረሻ ይፋ አድርጓል። ካፍ ዓለምን በአንድ የጭንቀት ቀረጢት ውስጥ የከተተው የኮቪድ -19 ወረርሽኝ በእግር ኳሱ ላይ ያሳደረውን ጫና ከፍትኛ መሆኑን በመረዳት የበኩሉን ድጋፍ ለማድረግ ውጥን መያዙን አስታውቋል። ኢትዮጵያን ጨምሮ በርካታ የአፍሪካ አገሮች ዓመታዊ የእግር ኳስ መርሐ ግብሮቻቸውን በዓለም አቀፉ ኮቪድ 19 ወረርሽን ምክንያት በሰረዙበት በዚህ ወቅት፣ የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) ለአባል አገሮቹ የገንዘብ ድጎማ ሊያደርግ መሆኑ ታወቀ፡፡ ኮንፌዴሬሽኑ ለእያንዳንዱ አገር 200 ሺሕ ዶላር ሊሰጥ ማቀዱ ነው ያስታወቀው ፡፡የ54 አገሮች ብሔራዊ ፌዴሬሽኖችን የሚያስተዳድረው ካፍ፣ በየዓመቱ በመደበኛነት ከሚያከናውናቸው ውድድሮች መካከል የአፍሪካ ክለቦች ሻምፒዮንስ ሊግና የአፍሪካ ክለቦች ኮንፌዴሬሽን ዋንጫ በዋናነት ይጠቀሳሉ፡፡ ይሁንና ሁሉም በወረርሽኙ ምክንያት ውድድሮቹ እንዲሰረዙ አድርጓል፣ የወደፊት ዕጣ ፈንታቸውን በሚመለከት አሁን ላይ ምንም ያለው ነገር የለም፡፡ የዘንድሮን የውድድር ዕጣ ፈንታ በሚመለከት ብዙዎቹ የአፍሪካ አገሮች ይህ ዘገባ እስከተጠናቀረበት ድረስ ስለመደረጉ ወይም ስለመሰረዙ ውሳኔ ላይ ባይደርሱም፣ 16 አገሮች መደበኛ ውድድሮቻቸውን መሰረዛቸውን ይፋ አድርገዋል፡፡ ኢትዮጵያ የዓመቱን ውድድር ከመሰረዟም በላይ በሚቀጥለው ዓመት በአፍሪካ የክለቦች ሻምፒዮንስ ሊግና የክለቦች ኮንፌዴሬሽን ዋንጫ ውክልና እንደማይኖራት ለጊዜውም ቢሆን ይፋ አድርጋለች፡፡ የተቀሩት 15 አገሮች ደግሞ በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ምክንያት ውድድሩ እስከተቋረጠበት ድረስ በደረጃ ሰንጠረዡ በተቀመጠላቸው ውጤት መሠረት የሚያሳትፏቸውን ክለቦች በማሳወቅ ውድድሮቻቸውን መሰረዛቸው ማረጋገጫ ሰጥተዋል፡፡ እነዚህም ቡርኪና ፋሶ፣ ጋምቢያ፣ ደቡብ ሱዳን፣ ሞሪሸስ፣ አንጎላ፣ ኬቨርዴ፣ ጊኒ፣ ቶጎ፣ ዴሞክራቲክ ኮንጎ፣ ኬንያ፣ ካሜሮን፣ ሩዋንዳ፣ ኒጀር፣ ኮንጎ ብራዛቪልና ላይቤሪያ ናቸው፡፡ በአጠቃላይ አህጉራዊው ተቋም እንደ አውሮፓና መሰል አህጉሮች በእሱ ሥር የሚያስተዳድረውን እግር ኳስ ወደ ገንዘብ በመለወጡ ረገድ ክፍተኛ ክፍተት ያለበት መሆኑ ተጠቅሷል ፡፡ ይሁንና ካፍ በየዓመቱ ለአባል አገሮቹ የሚሰጠውን የገንዘብ ድጎማ ሳያቋርጥ ለመስጠት ማረጋገጫ መስጠቱን የተለያዩ መገናኛ ብዙሃን የካፍን ድረ ገጽ ዋቢ በማድረግ ዘግበዋል፡፡ የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) ለአባል ሀገራቱ የ200 ሺህ ዶላር ድጋፍ እንደሚያደርገው ሁሉ፤ የዓለም አቀፍ እግር ኳስ ማኅበር (ፊፋ) የ150 ሺህ ዶላር ድጋፍ አደርጋለው ማለቱን ይታወሳል። ከዓለም እግር ኳስ ራስ የሆነው ተቋም ድጋፍ የሚያደርግ መሆኑ፤ ከሰሞኑ ደግሞ የአህጉሪቱ እግር ኳስ የበላይ ጠባቂ ካፍ ለአባል ሀገራቱ ድጋፍ እንደሚያደርግ አስታውቋል። የአፍሪካ እግር ኳስ በኮቪድ -19 ወረርሽኝ ምክንያት መጪው ጊዜ ፈታኝ እንደመሆኑ፤ ፈተናውን በድጎማ ይታለፍ ይሆን? አዲስ ዘመን ግንቦት 25/2012ዳንኤል ዘነበ
https://www.press.et/Ama/?p=33579
733
2ስፖርት
የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ለብሄራዊ ፌዴሬሽኖች ቃል የገባውን ገንዘብ ዛሬ ያስረክባል
ስፖርት
June 2, 2020
12
የዓለም ህዝብን በአንድ የጭንቀት ቋጥ ውስጥ ባስገባው የኮቪድ -19 ወረርሽኝ ምክንያት በስፖርቱ ዘርፍ ላይ ትልቅ ተጽዕኖ ማሳደሩ ይነገራል። የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ በሀገሪቱ የኮሮና ወረርሽኝ በስፖርቱ ላይ እያሳደረ ያለውን ጫና የሚዳስስ ውይይት ከሀገር አቀፍ ፌዴሬሽኖች ጋር አድርጎ ነበር። የሁሉም ብሔራዊ ፌዴሬሽኖች ውቅር የሆነው የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ከሀገር አቀፍ ፌዴሬሽኖች ጋር ካደረገው ውይይት መነሻነት እንዲሁም ፌዴሬሽኖቹም በሰጡት ጥናት መሰረት አንድ ውሳኔ አስተላልፏል። «ብሔራዊ ፌዴሬሽኖችን የገንዘብ ድጋፍ ይደረግላቸው ። ከዚህ በተጓዳኝ የገንዘብ አቅም የሌላቸው ስፖርቶችና ስፖርተኞች ወቅታዊ ብቃታቸው እንዳይወርድ ዕገዛ ይደረግላቸው» ሲል ነበር። የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ትናንት በመደበኛ የፌስቡክ ገጹ ፤« የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ለብሔራዊ ፌዴሬሽኖች ድጋፍ ለማድረግ ቃል የገባውን የገንዘብ ድጎማ ማክሰኞ ግንቦት 25 ቀን 2012 ዓ.ም እንደሚያስረክብ አስታወቋል። በኢትዮጵያ የተለያዩ ስፖርቶችን ለማሳደግና ለማስፋፋት የተቋቋሙ ከ26 በላይ ብሔራዊ ፌዴሬሽኖች ዓለም አቀፉ የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ከተከሰተ ጀምሮ ከማናቸውም ዓይነት ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች ተቆጥበዋል፡፡ በኅብረተሰቡ ዘንድ በስፋት የሚዘወተሩት ስፖርቶች ከሚመሩ ፌዴሬሽኖች በቀር ብዙዎቹ በወረርሽኙ ምክንያት ከቢሮ ይልቅ ቤት ውስጥ መዋል ከጀመሩ ሰነባብተዋል፡፡ ኦሎምፒክ ኮሚቴው የብሄራዊ ፌዴሬሽኖችን ምክረ ሐሳብን መነሻ በማድረግ ቃል የተገባውን ገንዘብ የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነሩ እና ምክትል ኮሚሽነሩ በተገኙበት ርክክቡ የሚደረግ ይሆናል ብሏል። ኦሎምፒክ ኮሚቴው ሥነ ሥርዓቱን መገናኛ ብዙሃን በስፍራው ተገኝተው መረጃውን በመከታተል ለህዝብ ተደራሽ ያደርጉለት ዘንድ ጥሪውን በመደበኛ ማህበራዊ ፌስቡክ ገጹ አስፍሯል። ሕጋዊ ሰውነት አግኝተው በአገሪቱ በመንቀሳቀስ ላይ ከሚገኙ ብሔራዊ ፈዴሬሽኖች የኢትዮጵያ አትሌቲክስና የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽኖች ካልሆኑ ሌሎቹ በአጠቃላይ ከመንግሥት ቋት በሚለቀቅላቸው አነስተኛ በጀት የሚንቀሳቀሱ ናቸው፡፡ መንግሥት ከሚመደብላቸው በጀት ይልቅ ከስፖርት ኮሚሽንና ከኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ የተሻለ የገንዘብ ድጎማ እንደሚደረግላቸው የሚናገሩት ብሔራዊ ፌዴሬሽኖቹ፣ ስፖርት በቂ ፋይናንስ ታክሎበት ካልሆነ በስተቀር ብሔራዊ በሚለው ስያሜ ብቻ ትርጉም ያለው እንቅስቃሴና ውጤት ማስመዝገብ እንደማይችል ጭምር ያምናሉ፡፡ የፌዴሬሽኖቹ አመራሮችም የዓለም አቀፍ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ለወትሮ በዓመት አንድ ጊዜ እንደ አስፈላጊነቱ ይሰጥ የነበረው የሙያ ማሻሻያ ኦሊምፒክ ሶሊዳሪቲ በወረርሽኙ ምክንያት ስለመቋረጡ ጭምር ይናገራሉ፡፡ አዲስ ዘመን ግንቦት 25/2012ዳንኤል ዘነበ
https://www.press.et/Ama/?p=33574
276
2ስፖርት
የዘረኝነት ተቃውሞ በስፖርቱ ዓለም ከዋክብት
ስፖርት
June 3, 2020
18
ዘመናዊው ኦሊምፒክ በተመሰረተበት ወቅት ከጸደቁ ድንጋጌዎች መካከል በግምባር ቀደምትነት የሰፈረው ሃሳብ ‹‹ስፖርት ለሰው ልጆች ሰላምና ሁለንተናዊ ስብዕና መዳበር እንዲውል ማድረግ›› ይላል፡፡ ይህንንም ከምስረታው (እ.አ.አ 1896) ጀምሮ በውድድር ሜዳዎች ሳይወሰን መልካም ያልሆኑ አሠራሮችን በመቃወምና የህብረተሰቡ ትግል አጋር በመሆን ማረጋገጡን የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ባሳተመው መጽሔት ላይ ሰፍሯል፡፡ ለአብነት ያህልም እ.አ.አ 1964 ኮሚቴው አፓርታይድን በመቃወሙ ደቡብ አፍሪካን ከቶኪዮ ኦሊምፒክ ተሳትፎ ማገዱን ማስታወስ ይቻላል:: ከዚህም ባለፈ የራሱን ቡድን በማቋቋምም ደቡብ አፍሪካዊያኑ በአፓርታይድ ምክንያት ከሚደርስባቸው ጭቆና እስኪላቀቁ ድረስ መታገሉም ተጠቃሽ ነው፡፡ የስፖርት ውድድሮች ሁሉ ራስ የሆነው ኦሊምፒክ ተሳትፎ ዓላማና ግብ ይህም ብቻ አይደለም፡፡ ይልቁንም በተለያዩ ጊዜያት በዓለም ላይ የታዩ ኢ ሰብዓዊ የሆኑ ክስተቶችን በመቃወም፤ የስፖርት መነሻና መድረሻው ሰብዓዊነት መሆኑን አስመስክሯል፡፡ በማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እንዲሁም ፖለቲካዊ ሁነቶች ጎን በመቆም ዘመናት የተሻገረው ስፖርት አሁንም የአጋርነት ሚናውን እየተወጣ መሆኑን የሰሞኑ ክስተት አንዱ ማሳያ ነው፡፡ ዓለም በስልጣኔ እንደመራቀቋ የሰው ልጅም በአስተሳሰቡ እንደመምጠቁ የቆዳ ቀለምን መሰረት ያደረገ የዘረኝነት ጥቃት ሊገፋ ያልቻለ ቋጥኝ ሆኗል፡፡ የቆዳ ቀለምን ዒላማ ያደረጉ ጥቃቶችና አስነዋሪ ድርጊት ለዓመታት በስፖርት ሜዳዎችም ጭምር ተንሰራፍተው ታይተዋል፡፡ ሰሞኑን መነሻውን በአንድ ጥቁር ግለሰብ ግድያ ላይ ያደረገውና አሜሪካንን እየናጠ ባለው ተቃውሞም ስፖርት እንደ ትላንቱ ሁሉ ዛሬም ፀያፉን ተግባር በመቃወም ግንባር ቀደም ሆኗል፡፡ ከስፖርቱ ሰዎች መካከል አንዱ የሆነው የቀድሞ ቦክሰኛ ፍሎይድ ሜይዌዘር በሚኒያፖሊስ በጭካኔ የተገደለውን የ46 ዓመቱን አፍሪካ አሜሪካዊ ጆርጅ ፍሎይድን የቀብር ስነ-ስርዓት ወጪ እንደሚሸፍን አስታውቋል፡፡ የከባድ ሚዛን ዓለም ቻምፒዮናው ሜይዌዘር በቲውተር ገጹ ላይ ይህንኑ እንዳሰፈረም ነው ዘ ኢንዲፔንደንት በዘገባው ያመላከተው፡፡ የጎልፍ ተጫዋቹ ታይገር ውድስም በተመሳሳይ በሁኔታው ማዘኑን እንዲሁም የሟች ፍሎይድ ቤተሰቦች እንዲበረቱ በትዊተር ገጹ መልዕክት አስፍሯል፡፡ የፖሊሱንም ተግባር ‹‹ያለ ቦታው ኃይልን የተጠቀመና ዕርምጃውም መስመር ያለፈ›› ብሎታል፡፡ አሜሪካዊው የቅርጫት ኳስ ኮከብ ሚካኤል ጆርዳን በበኩሉ በአሜሪካ ያለው ዘረኝነት ስር የሰደደ መሆኑን አስምሮበታል፡፡ ሌሎች የአሜሪካ ቅርጫት ኳስ ተጫዋቾችና ስፖርተኞችም በገንዘብና በሃሳብ ከተጎጂው ቤተሰቦች ጋር መሆናቸውን ከመግለጽ ባለፈ አስነዋሪውን ተግባር በመቃወም አጋርነታቸውን እያሳዩ ይገኛሉ፡፡ የአሜሪካንን ድንበር ያቋረጠውና ወንዝ የተሻገረው ተቃውሞና ለጥቁሮች ወንድማዊ ስሜትን የማሳየቱ ሂደትም በመላው ዓለም እንደቀጠለ ነው፡፡ በአውሮፓ የሚገኙ በርካታ የእግር ኳስ ተጫዋቾች በጨዋታ እንዲሁም በልምምድ ሜዳዎች ላይ በግልና በቡድን በድርጊቱ የተቃውሞ እንዲሁም ከጥቁሮች ጋር የአብሮነት ስሜታቸውን አንጸባርቀዋል፡፡ በኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት የተቋረጠውን የእግር ኳስ ውድድር ከሌሎች ቀድሞ በጀመረው የጀርመን ቡንደስሊጋም ይኸው እንቅስቃሴ ተስተውሏል፡፡ የቦሩሲያ ዶርትመንዱ ተጫዋች ጃደን ሳንቾ ‹‹ፍትህ ለጆርጅ ፍሎይድ›› የሚል ካኒቴራ ከማሊያው ስር በመልበስ ያሳየ ሲሆን፤ ሌሎችም በጉልበታቸው በመንበርከክ ኀዘናቸውን መግለጻቸውን ስካይ ስፖርት ዘግቧል፡፡ የተቋረጠውን ሊግ ለመቀጠል በልምምድ ላይ የሚገኙት የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ ተጫዋቾችም በተመሳሳይ ሁኔታ አብሮነታቸውን አሳይተዋል፡፡ 29 የሚሆኑ የሊቨርፑል ተጫዋቾች በሜዳቸው አንፊልድ ከጉልበታቸው በመንበርከክ መልዕክት አስተላልፈዋል፡ ፡ የማንቺስተር ዩናይትድ ተጫዋቾቹ ፓውል ፖግባ እና ማርከስ ራሽፎርድም ድምፃቸውን ካሰሙ ተጫዋቾች መካከል ይገኙበታል፡፡ ፖግባ ከቢቢሲ ጋር በነበረው ቆይታ ‹‹ለፍሎይድና ለመላው ጥቁር ማህበረሰብ የንዴት፣ የኀዘን እና የመከፋት ስሜት ተሰምቶኛል፡፡ ጥቁሮች በእግር ኳስ፣ በትምህርት ቤት፣ በሥራና ሁሉም ስፍራ ይህንን ስሜት በየዕለቱ ያስተናግዳሉ፡፡ በመሆኑም ይህ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ መቆም አለበት፤ ዛሬውኑ›› ሲል አስተያየቱን ሰጥቷል፡፡ እንግሊዛዊቷ የአጭር ርቀት አትሌት ዲና አሸር ስሚዝ፣ የሜዳ ቴኒስ ኮከቧ ሴሪና ዊሊያምስ፣ የፎርሙላ ዋን ሞተር ስፖርት ተወዳዳሪዎች እንዲሁም ሌሎች የስፖርቱ ሰዎችም በሁኔታው መከፋታቸውን በመግለጽ ተቃውሟቸውን የገለጹም የስፖርቱ ዓለም ከዋክብት ናቸው፡፡ አዲስ ዘመን ግንቦት 26/2012ብርሃን ፈይሳ
https://www.press.et/Ama/?p=33634
462
2ስፖርት
ኮሚቴው ለፌዴሬሽኖችና የቀድሞ አትሌቶች ድጋፍ አደረገ
ስፖርት
June 3, 2020
12
የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ለብሔራዊ ፌዴሬሽኖችና ለቀድሞ አትሌቶች የገንዘብ ድጋፍ አድርጓል፡፡ ‹‹የኮቪድ 19 መሰራጨት የዓለምን ስፖርት ቢያጠቃም፣ እንደ ስፖርት እኛም ክፉኛ ብንጎዳም በሥራችን ያሉ ፌዴሬሽኖችን ማገዝ አለብን በሚል ፅኑ አቋም ድጋፉን አድርገናል›› በማለት ትናት መግለጫ የሰጡት የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ፕሬዚዳንት ዶክተር አሸብር ወልደጊዮርጊስ ናቸው፡፡ በዚህም መሰረት ለየፌዴሬሽኖቹ በነፍስ ወከፍ ሃምሳ ሃምሳ ሺ ብር የተሰጠ ሲሆን፤ ለቀድሞ አትሌቶች 200 ሺ ብር እንዲሰጥ መወሰኑን ፕሬዚዳንቱ አስረድተዋል፡፡ ብሔራዊ ኦሊምፒክ ኮሚቴው በስሩ ሃያ አራት ፌዴሬሽኖችና አራት የስፖርት ማህበራት ያሉት ለድጋፉ ከአንድ ነጥብ አራት ሚሊየን ብር በላይ ወጪ ማድረጉ ታውቋል፡፡ በኦሊምፒክ ኮሚቴው ጽሕፈት ቤት በተካሄደው መግለጫ ላይ የፌዴራል ስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነር ኤሊያስ ሽኩርና ምክትል ኮሚሽነሩ አቶ ዱቤ ጅሎ ተገኝተው ንግግር አድርገዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል ባለፈው መጋቢት ወር የሦስት ሚሊዮን ብር ድጋፍ ማድረጉ አይዘነጋም፡፡ አዲስ ዘመን ግንቦት 26/2012
https://www.press.et/Ama/?p=33641
124
2ስፖርት
አበረታች ቅመም የተጠቀመው አትሌት ቅጣት ተጣለበት
ስፖርት
June 7, 2020
14
የኢፌዴሪ ብሄራዊ የጸረ አበረታች ቅመሞች ጽህፈት ቤት የተከለከለ ንጥረ ነገር መጠቀሙ በተረጋገጠበት አትሌት ላይ ውሳኔ አሳለፈ፡፡ የሌሎች ሁለት አትሌቶች ጉዳይም እየተጣራ መሆኑን ጽህፈት ቤቱ አስታውቋል፡፡ የስፖርት አበረታች ንጥረ ነገር በመጠቀም በውድድር ላይ መሳተፉ በተደረገበት ማጣራት የታወቀው አትሌት የአራት ዓመታት እገዳ ተጥሎበታል፡፡ የቅጣት ውሳኔው የተላለፈበት አትሌት ወንደሰን ከተማ የሚባል ሲሆን፤ እአአ ታህሳስ 01/2019 በቻይና በተካሄደውና ዓለም አቀፍ ደረጃ ባለው ሻንዛቢ ማራቶን በግሉ ተሳትፎ ነበር፡፡ በውድድሩ ወቅት በተወሰደው የደምና የሽንት ናሙና በመጠርጠሩ ምክንያት ላለፉት አምስት ወራት የአበረታች ቅመም መጠቀም አለመጠቀሙን ለማወቅ ማጣራት ሲደረግበት መቆየቱን ጽህፈት ቤቱ የላከው መግለጫ ያሳያል፡፡ አትሌቱ በተደረገበት ተጨማሪ የማጣራት ተግባተርም (Cahinone) የተባለና በስፖርት የተከለከለውን አበረታች ቅመም መጠቀሙ ተረጋግጧል፡፡ በዚህም የኢፌዴሪ ብሄራዊ የጸረ አበረታች ቅመሞች ጽህፈት ቤት በአትሌቱ ላይ አስተማሪ የሆነ እርምጃ ወስዷል፡፡ በቅጣቱም የአትሌቱ ጥፋት የመጀመሪያ ደረጃ መሆኑን ከግምት በማስገባት እአአ ከየካቲት 01/2020-የካቲት 01/2024 ድረስ በየትኛውም ሃገር አቀፍ እና ዓለም አቀፍ ውድድሮች ላይ ተሳታፊ እንዳይሆን የሚያደርገውን እገዳ ጥሎበታል፡፡ ከእገዳው ባሻገር በቻይናው ውድድር ያስመዘገበው ውጤት እንዲሁም ሽልማቱ እንዲሰረዝም ውሳኔ የተላለፈበት መሆኑ ታውቋል፡፡ ጽህፈት ቤቱ ሌሎች ሁለት አትሌቶች ላይም ማጣራት እየተደረገ መሆኑን ጠቁሟል፡፡ አትሌቶቹ በተለያዩ ዓለም አቀፍ ውድድሮች ላይ በግላቸው ተሳትፎ ያላቸው ሲሆን፤ የተከለከሉ የስፖርት አበረታች ንጥረ ነገር መውሰዳቸው ከጥርጣሬ ገብቷል፡፡ በመሆኑም ጉዳዩ ተጣርቶ ተጠቃሚነታቸው ከተደረሰበት የስም ዝርዝራቸውንና የቅጣት ውሳኔያቸው ለህዝብ ይፋ እንደሚሆን ይጠበቃል፡፡ ከዚህ ጋር በተያያዘ አትሌቶች ራሳቸውን ከኮሮና ወረርሽኝ እንዲሁም ከአበረታች ንጥረ ነገር እንዲጠብቁም ጽህፈት ቤቱ መልእክቱን አስተላልፏል፡፡ ወቅቱ የዓለም ህዝብ ከወረርሽኙ ጋር ግብ ግብ የገጠመበት እንደመሆኑ ውድድሮች መቋረጣቸው ይታወቃል፡፡ ነገር ግን በሃገሪቷ በየደረጃው የሚደረገው የስፖርት አበረታች ቅመሞች ክትትልና ቁጥጥር ተጠናክሮ ይቀጥላል፡፡ አበረታች ቅመሞቹን መጠቀሙ የተረጋገጠበትም ይሁን በተለየ መልኩ የህግ ጥሰት በሚፈጽሙ አትሌቶችና ከጀርባ በመሆን በሂደቱ በሚሳተፉ ግለሰቦች ላይ ጽህፈት ቤቱ የእርምት እርምጃ መውሰዱን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ጠቁሟል፡፡ አዲስ ዘመን ግንቦት 30/2012ብርሃን ፈይሳ
https://www.press.et/Ama/?p=33864
264
2ስፖርት
ኮቪድ-19 በስፖርት ላይ የሚያሳድረውን ተፅዕኖ የሚያጠና ኮሚቴ ተቋቋመ
ስፖርት
June 4, 2020
21
የዓለምን ኢኮኖሚያዊ፣ማህበራዊና ፖለቲካዊ ነባራዊ ሁኔታ ወደተለየ አቅጣጫ ያዞረው የኮሮና ቫይረስ ስርጭት በስፖርቱ ዓለም ያሳደረው አሉታዊ ተፅዕኖ ተዘርዝሮ የሚልቅ አይደለም። አንዳች ውድድር በዓለም ላይ እንዳይኖር ከማስገደድ ባለፈ የስፖርቱን ዓለም ሽባ አድርጎታል። ብዙ ታቅዶባቸው፣ብዙም ተለፍቶባቸው ለዓመታት በዝግጅት ላይ የነበሩ ዓለም አቀፍ ውድድሮች በትልቅ ኪሳራ የሚካሄዱበት ጊዜ እንዲራዘም ግድ ብላል። የኮሮና ቫይረስ ስርጭት በዓለም ዙሪያ ከተንሰራፋ ወዲህ በግለሰብ ደረጃ ካልሆነ በስተቀር የትኛውም የስፖርት እንቅስቃሴ ተገድቦ እንደቆየ ይታወቃል። የቫይረሱ ስርጭት በዓለም ዙሪያ እያሻቀበ መሄዱን ተከትሎም ታላላቅ ስፖርታዊ ውድድሮች በቅርቡ ወደ መደበኛ እንቅስቃሴያቸው ይመለሳሉ የሚል ተስፋ የለም። ይሁን እንጂ የዓለማችን ታላላቅ የእግር ኳስ ሊጎች በዝግ ስታድየምም ቢሆን የውድድር ዓመቱን ቀሪ መርሐግብሮች ለማጠናቀቅ በቅርቡ ወደ ውድድር እንደሚመለሱ ተስፋ መስጠታቸው አልቀረም። የዓለም ጤና ድርጅት የሕክምና ባለሙያዎች ግን ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች በትልቅ ደረጃ ወደ መደበኛ እንቅስቃሴያቸው እንዳይመለሱ ምክራቸውን ለግሰዋል። በዓለማችን ብሎም በአገራችን በፍጥነት እየተስፋፋ የመጣውን የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ 19) ስርጭትን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር በሚደረገው ጥረት የስፖርት ቤተሰቡ መደበኛ እንቅስቃሴውን ገቶ የበኩሉን አስተዋፅኦ ማድረግ ከጀመረ ሰነባብቷ። የስፖርት ቤተሰቡ ወረርሽኙን ለመከላከል ግንዛቤ ከመፍጠር እስከ ደም ልገሳ፤ ከቁሳቁስ እስከ ገንዘብ ድጋፍ በማድረግ አጋርነቱን አሳይቷል ፤ በማሳየት ላይም ይገኛል። ወረርሽኙ በዓለም ላይ ከተከሰተና ከተስፋፋ ወዲህ የስፖርቱን ዘርፍ ክፉኛ የጎዳው ሲሆን የአገራችንን ጨምሮ በዓለም ላይ በርካታ ታላላቅ ውድድሮች እንዲቆሙ አስገድዷቸዋል። በተለይም ወረርሽኙን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር በተወሰዱ እርምጃዎች ስልጠናዎች፣ ውድድሮች ቁመዋል ፤ ስፖርተኛው እና የስፖርት ቤተሰቡ ከፍተኛ የሆነ የስነ ልቦና እና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ አጋጥሟቸዋል ። በርካታ የስፖርት ክለቦች የመፍረስ አዳጋ ተደቅኖባ ቸዋል፤ አንዳንዶቹም ለስፖርተኞች ወርሃዊ ደመወዝ እስከ መከልከል ደርሰዋል። በመሆኑም የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን ከባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር ጋር በመተባበር በወረርሽኙ ወቅት እና ከወረርሽኙ በኋላ ስፖርቱ እንዴት ወደ ነበረበት መመለስ ያስችላል የሚለውን የሚያጠና እና ለመንግሥት የሚያቀርብ ጠንካራ ኮሚቴ መቋቋሙን የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር አቶ ዱቤ ጅሎ መናገራቸውን የተቋሙ ይፋዊ የፌስ ቡክ ገፅ ላይ ተዘግቧል። የተቋቋመው ኮሚቴ አብይ እና ቴክኒካል ኮሚቴ ያለው ሲሆን አብይ ኮሚቴው በባህልና ቱሪዝም ሚኒስትሯ ዶክተር ሂሩት ጣሰው የሚመራ ይሆና። ቴክኒካል ኮሚቴው ደግሞ በአቶ ዱቤ ጅሎ እንደሚመራ ታውቋል። ኮሚቴው አጠቃላይ የኮሮና ወረርሽኝ በአገራችን ስፖርት ላይ እያሳደረ ያለውን ጫና እና መፍትሔዎችን በማጥናት ሰነዱን ለመንግሥት የሚያቀርብ ይሆናል። በጥናቱም የሌሎች አገራት ተሞክሮ ምን እንደሚመስል ተካቶ እንደሚቀርብ አቶ ዱቤ አብራርተዋል። ጥናቱን መሠረት በማድረግ መንግሥት ስፖርቱ ለአገራችን ማህበራዊ ፣ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ፋይዳ ግምት ውስጥ በማስገባት አስፈላጊውን ድጋፍ ያደርጋል ተብሎ እንደሚጠበቅ ምክትል ኮሚሽነሩ ገልፀዋል ።አዲስ ዘመን ግንቦት 27/2012ቦጋለ አበበ
https://www.press.et/Ama/?p=33697
349
2ስፖርት
በአንድነት ፓርክ፤ ትናንትንም ዛሬንምይመልከቱ
መዝናኛ
November 7, 2019
51
 ሳልፍና ሳገድም፤ አሻግሬ ከማየት ባለፈ ዥንጉርጉሩን የደንብ ልብስ ለብሰው፣ መለዮአቸውን አድርገው፣ መሳሪያቸውን አንግበው በበሩ ላይ ሆነው ሌት ተቀን ከሚጠብቁት ጠባቂዎች አልፌ ከቅጥር ግቢው እገባለሁ ብዬ ላስብ ቀርቶ ተመኝቸው እንኳን አላውቅም፤ ብሔራዊ ቤተ መንግስት። እነሆ ዛሬ በወጣት አስተናጋጆች በአክብሮት በግቢው ዘልቄ ከግር እስከራሱ ለመጎበኘት በቃሁ። ጊዜ ለኩሉ ይል የለ። ፍተሻውን አልፈው ወደ ግቢው ከገቡ በኋላ በቅደም ተከተል የሚጎበኟቸውን እና የማረፊያ ቦታዎችን ሙሉ መረጃ የያዘ መግለጫ (ማፕ) ይሰጥዎታል። አንድሺ ብር ከፍለው ከገቡ በአስጎብኚ (በአስረጅ) ይታገዛሉ። የከፈሉት ሁለት መቶ ብር ከሆነ ግን የተሰጥዎትን አቅጣጫ ጠቋሚ በመጠቀም ይመራሉ። በመግቢያ ላይ በአማርኛና በእንግሊዝኛ በትላልቅ ፊደላት ‹ኢትዮጵያ› ተብሎ ተጽፏል። ፅሁፉ እንደ ሰንደቅ ዓላማ ከፍ ብሎ ተሰቅሎ በራሱ ‹‹እባክዎን ወደ ውስጥ ዝለቁ›› የሚል ያህል ይጋብዛል። ጽሁፉን ሲያነቡትም ልብ ይሞላል። እድሜ ጠገብ ከሆኑት ሀገር በቀል ዛፎች የሚነፍሰው ንጹህ አየርም ጎብኚዎችን ለመቀበል ተባባሪ የሆነ ይመስላል። ምድረ ግቢው፣ በውስጡ የተገነቡት የቤቶች የስነ ህንፃ ውበትና ጥበብ፣ ኢትዮጵያ ታላላቅ ተብለው ከሚጠሩ ሀገራት ጋር ስለነበራት ግንኙነት፣ በታሪክ ተሰንዶ የሚታየው ሁሉ ከአዕምሮ በላይ ነው። በቃላት ብቻም የሚታለፍ አይደለም። ታሪክ ይናገራል። የት እንዳለሁ ትገምታላችሁ በሚል። ብዙ አወራሁ፤ ‹አንድነት ፓርክ› ውስጥ ነኝ! በሉ ተከተሉኝ። የፓርኩን የውስጥ ለውስጥ መንገድ፣ ለንግድ ለማረፊያና ለተለያየ አገልግሎቶች የሚውሉ ግንባታዎች፣ የአትክልትና የአበባ ሥፍራዎችን በማዘጋጀት፣ ብቻ በፓርኩ ውስጥ ያስፈልጋሉ የተባሉ ነገሮችን ለማሟላት የሚከናወኑ ተግባራትንም እግረ መንገድ እየተመለከትኩ፣ በሥራው በመሳተፍ ላይ ያሉት የዛሬ ወጣቶች የነገ የዕድሜ ባለጸጋ የታሪክ ተቋዳሽ መሆናቸው ደግሞ ሌላው ድንቅ ታሪክ ነው። የአንድነት ፓርክ በውስጡ ስድስት የቱሪዝም ዋና ዋና መዳረሻዎች ያሉት ሲሆን፣ እያንዳንዱም ሰፊ ታሪክ ያለው በመሆኑ አለፍ አለፍ እያልኩ የተደመምኩበትንና የታዘብኩትን ብቻ ነው በምናብ በመውሰድ እየሳልኩ የማስተዋውቃችሁ። ወደ ሰው ሰራሽ የጥቁር አንበሳ ዋሻ አመራሁ። ዋሻው ከአለት ድንጋይ ተፈልፍሎ የወጣ እንጂ የእጅ ጥበብ አይመስልም። የዱር እንስሳት መኖሪያ በስፍራው ስለሚገኝ ብቻዬን በዋሻው ውስጥ ለማለፍ አልደፈርኩም። በአጋጣሚ በኤሌክትሪክ ሙያ የተሰማሩ ወጣቶች ለሥራ በውስጡ ሲያልፉ ተከተልኳቸው። በዋሻው መግቢያ ላይ አራት አናብስት አየሁ። ደነገጥኩ። እንደማይደርሱብኝ ስላረጋገጥኩ ፍርሃቴ አልቆየም። እንኳን በአካል በድምጹ ከሚያስፈራው አንበሳ ጋር ከመስተዋት ማዶና ወዲህ በቅርበት ተያየን። ‹‹ማን ይባሉ ይሆን?›› በፓርኩ የሚሰሩት ወጣቶች ወንዱን ቀነኒሳ፣ ሴቶቹን ደግሞ በጥሩነሽና በገንዘቤ ሰየሙልኝ፤ በስያሜው ተሳስቀን ተለያየን፡፡ ዋሻውን አልፌ ወደ ሌላው የታሪክ ሥፍራ ሳመራ በባህላዊ የመድኃኒት ተክል የተሞላ አካባቢ ደረስኩ። ለምች መድኃኒት የሚወሰደው ዳማከሴ፣ ጤና አዳም፣ ጠጅ ሳር፣ ሮዝመሪኖ ሌሎችም እይታን በሚስብ ቦታ ተተክለዋል። ተክሎቹን እንዳለፍኩ ካየኋቸው የነገሥታትና የመሪዎች ፎቶግራፎች መካከል የንግሥት ዘውዲቱን ፎቶግራፍ ማየቴ ለጾታዬ እንዳደላ አድርጎኛል። የስምንተኛው መሪ የዶክተር ዐብይ አህመድ ፎቶ ግራፍ ግን አልተካተተም። የትናንቱን ብቻ እንድናስታውስ ታስቦ ይሆን? አለፍኩት። በጉብኝቴ ውስጥ ‹ላንቺያ› የተባለችው የአፄ ኃይለ ሥላሴ መኪናም ትኩረትን በሚስብ እይታ ቦታ ነበረች። ገና ከፋብሪካ የወጣች እንጂ እድሜ ጠገብ አትመስልም። ባለ8 ማዕዘኑ እና የእንቁላል ቅርጽ ጉልላት ባለው የዳግማዊ ሚኒልክ ቤተመንግሥት ውስጥ ትኩረቴን የሳበው በግድግዳው ውስጥ የተቀበረው ከብረት የተሰራው የድምጽ ማስተላለፊያ ቱቦ ነበር። ምድርና ፎቅ ሆነው በድምጽ መልዕክት የሚለዋወጡበት መሳሪያ መሆኑ ባስጎብኝዋ ሄለን በቀለ ገለፃ ባይደረግልን ኑሮ የውሃ መውረጃ የሚመስለን ጥቂት አንሆንም ነበር። አፄ ሚኒልክና ባለቤታቸው እቴጌ ጣይቱ የተለያየ መኝታ ክፍል እንዳላቸው በአስጎብኝዋ ገለጻ ሲደረግልን ቀልደኛ ጎብኚ ደንገጥ ብሎ ‹ለየብቻ ነው የሚተኙት› በማለት ጠየቀ። መልስ ባይገኝም ሳቅ ፈጥሯል። የመጀመሪያው የስልክ ቤትም በዚሁ የሚኒልክ ቤተመንግሥት ውስጥ ይገኛል። ስምንት ሺ ኪሎ ሜትር ይረዝማል ተብሎ በሚገመተው ጠፍር ጣሪያው የተሰራው፣ ሰባት መስኮቶችና 12 በሮች ያሉት፣ እስከ ሶስት ሺ እንግዶች የሚያስተናግደው የግብር አዳራሽ ልዩ ድባብ አለው። ሥራውን ለኪነ ህንጻ ጠቢባን ትቸዋለሁ። በዚህ ክፍል ውስጥ ከዛሬ አምስት አስርት ዓመት በፊት በቀድሞ ተግባረዕድ በአሁኑ እንጦጦ ቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ ተብሎ በሚጠራው ትምህርት ቤት ሲማሩ በትምህርታቸው የላቀ ውጤት በማምጣታቸው ተጋብዘው ከአፄ ኃይለሥላሴ ዲፕሎማና ሽልማት የወሰዱት አቶ ነጋሽ ገብሬ የታሪክ አጋጣሚው ያኔ ለሽልማት አሁን ደግሞ ‹አንድነት ፓርክ› ተብሎ ተሰይሞ ለጉብኝት አብረን ታድመናል። ለአቶ ነጋሽ መታደማቸው ልዩ ስሜት ነበር ያሳደረባቸው። በጉብኝታቸው የተደመሙበትንና በተንቀሳቃሽ ስልካቸው የቀረጿቸውን ወደ ሚኖሩበት አሜሪካን ሜሪላንድ ሲመለሱ ለወዳጆቻቸው ለማሳየት ቸኩለዋል። የማስተዋወቅ ኃላፊነትም እንዳለባቸው አጫውተውኛል። የሌሎች ጎብኚዎችን ስሜትም እየተጋራሁ ስለነበር ‹‹ለካ እንዲህ ነው እንዴ ያረጁ ቤቶችን ነበር የጠበኩት›፣ ‹ጉብኝቱ በግማሽ ሰዓት የሚያልቅ ነበር የመሰለኝ›፣ ‹እድሜ ሰጥቶን ይሄን ማየታችን ዶክተር ዐብይ እግዚአብሄር ይስጠው› የሚሉ በደስታ የሚገለጹ ስሜቶችን ነበር የሰማሁት፤ ከገጽታቸው ያነበብኩት ይህንኑ ነው። በምስል፣ በድምጽና በጽሁፍ ተቀነባብሮ አፈታሪክ በተባለው ክፍል ውስጥ የሚጎበኘው ደግሞ በጽሁፍ ከምገልጽላችሁ በላይ ነው። በአንድነት ፓርክ ውስጥ ከበጎ እስከ ክፋት የተፈጸሙ ነገሮች ቢቀርብልዎትም ታሪክ ነውና ያለፈውን በትዝታ የወደፊቱን ደግሞ በአንድነት ሆነው እንዲቀጥሉ የሚያስተሳስሩ የብሄር፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ባህልና ወግ የሚያንጸባርቁ እሴቶችም ይገኛሉ፤ አበቃሁ።አዲስ ዘመን ጥቅምት27/2012 ለምለም መንግሥቱ
https://www.press.et/Ama/?p=22108
644
1መዝናኛ
ነፃ ጠረጴዛ ፈልጉ!
መዝናኛ
November 8, 2019
43
በጠዋት ነው ቢሮ የገባሁት፤ በወሩ የመጨረሻ ቀናት ላይ ነኝና የሚደርሰኝን ገቢዬን ከወጪዬ ጋር እያሰላሁ ነው:: የቤት ኪራይ፤ የምግብ፤ የትራንስፖርትና ሌሎች ለመኖር አስፈላጊ የሚባሉ ወጪዎችን አሰላለሁ። ደመወዜንም አሰብኩት:: ኦ! አምላኬ ለካስ ደመወዜ ስንት እንደሆነ አላውቅም:: ማሰቡ ስለከበደኝ ተውኩት:: ወጪና ገቢዬን ሳመዛዝን ስላስጨነቀኝ ማሰቡን ለመርሳት ሞከርኩ:: የምር ግን ደመወዛችሁ ስንት እንደሆነ ታውቃላችሁ ወዳጆቼ? እኔ ግን ደመወዜ ስንት እደሆነ አላውቅም:: ”እንዴት?” ካላችሁኝ ምክንያት አለኝ:: ቆዩማ፤ እንዴት ላውቀው እችላለው እኔ ዘንድ ደርሶ አያውቅማ፤ ያልቀረበን ነገር ማወቅ ይከብድ የለ? ከእጄ ሳይደርስ እኮ ነው ተከፋፍሎ የሚያልቀው፤ ሳሳዝን! ሰርቼ፤ ጥሬ ግሬ የማስረክባቸው ብዙ ጠባቂዎች አሉኝ::እኔ ምለው!? እኔ ወጪና ገቢዬን እያሰብኩ ከምጨነቅና ግራ ከምጋባ ሰዎችን ላስቸግር መሰለኝ:: እስኪ አስታውሱኝ ስንት ነበር? የቤት አከራዬ፤ የመስሪያ ቤቴ ሻይ ክበብ፤ የምመላለስባችሁ ታክሲዎች፤ እኔ ሰፈር ያለኸው ባለ ሱቅ፤ የምትቀፍሉኝ ጓደኞቼ፤ እስኪ አንዴ ሰብሰብ በሉና ወርሐዊ ወጪዬን ንገሩኝ:: እኔ ምንም ገቢ የለኝማ:: የተቀበልኩትን መስጠት፤ የተሰጠኝን ለእናንተ ማድረስ ስለሆነ ገቢዬን አላውቅም:: እናንተ ከእኔ የምታገኙት ገቢ ምን ያህል እንደሆነ ደመር.. ደመር አድርጉና ንገሩኝ:: ከወጪ ይልቅ ገቢ መደመር ደስ ይል የለ? አዎን!በሳምንቱ መጀመሪያ ቀን ሰኞ ላይ የሥራ “ሙዴ” ቶሎ አይቆሰቆስም:: ልምድ ይሁን እንጃ ብቻ ሰኞ ዕለት ብሰራም የሰራሁት ለእኔም አያጠግበኝም:: በጠዋት ቢሮዬ ገብቼ ኮምፒዩተሬን መነካካት፤ መረጃዎችን ማየት ቀጠልኩ። በሳምንቱ ውስጥ በምሰራቸው ተግባራት ምንነት ላይ በወጉ እያሰብኩ ቆዬቼ፤ ሥራ ከመጀመሬ በፊት ቡና ጠጥቼ ነቃ ለማለት ወደ ሻይ ክበብ ሄድኩ:: ዛሬ ቀኔን ብሩህ ላደርገው አስቤያለሁ:: ደስ የሚል ቀን ማሳለፍ ፈልጌያለሁ:: ሰላም መናፈሻ ውስጥ የተመለከትኳቸውን ባልደረቦቼን ተቀላቀልኳቸው:: ሙግት ይዘዋል። አንዱ የሌላውን ሐሳብ ይነቅፋል፤ የራሱን ደግሞ ያስከትላል:: የሚከራከሩበት ርዕሰ ጉዳዩ አንድ፤ አተያያቸው ግን ለየቅል ሆኖ ላለመግባባት በሚመስል ሁኔታ በቃላት ይፋለጣሉ:: ጉዳዩ የሰለቸኝ የፖለቲካ ጉዳይ ነው:: መከራከሪያው ወቅታዊ ርዕሰ ጉዳይ ነው:: ይሄ ክርክር ተደጋገመና በየሄድኩበት የሚወራው እሱ ሆነና ሰለቸኝ:: ከሊቅ እስከ ደቂቅ የሚያነሳና የሚጥለው ፖለቲካዊ ጉዳይ ላይ ሆነና አሰለቸኝ:: ወሬው ሁሉ ፖለቲካ የተቀላቀለበት ሆነና እረፍት ፈለኩ:: ቦታዬን የቀየርኩት በምክንያት ነው። ክርክሩን ለመራቅ፤ ተሳካልኝና በቀየርኩት ጠረጴዛ ላይ ሌላ ርዕሰ ጉዳይ ተይዟል:: “ኡፉፉ…ግልግል”፤ እዚህ በሚወራው ሌላ ርዕሰ ጉዳይ ደስ ተሰኘሁ:: ሰሞኑን በወጣ መጽሐፍ ላይ ነው ውይይቱ፤ አጋጣሚ እኔም መጽሐፉን አንብቤው ስለነበር አፍታም ሳልቆይ ሐሳቡ ሲገባኝ መሳተፍ ጀመርኩ:: ትንሽ ሐሳብ እንደተለዋወጥን በመጽሐፉ ላይ ያለ አንድ ርዕሰ ጉዳይ “የሆነ ወገን የሚነካ ነው” መባሉ ከዚያው ከተወያዮች መካከል ተነሳ:: ይሄኔ ጠረጴዛው ላይ ያለው ውይይት መልኩ ሊቀይር እንደሆነ ገባኝና ተከፋሁ:: በተቻለኝ መጠን ርዕሰ ጉዳዩን ልቀይረው ፈለግሁ። አልተሳካልኝም:: ጭራሽ ጉዳዩ ከርሮ የተናገረውን ልጅ ትርጓሜ ተቃራኒ የሆነ ሐሳብ ያለው ነበረና “እነሱ ድሮም…” ማለት ሲጀምር ያዘዝኩትን ቡና ሳልጨርስ ከመቀመጫዬ ተነስቼ መዝናኛ ክበቡን ለቅቄ ወደ ቢሮዬ አመራሁ:: ቢሮዬ ገብቼ ሥራ ከመጀመሬ በፊት የዓለምን አዳር ለማየት ማህበራዊ ገፆችን ከፈትኩ:: ማየት ከሰለቸኝ ርዕሰ ጉዳይ ውጭ የተጻፈ ጽሑፍ፣ ማየት ከመረረኝ ዜና ውጭ ብዙም አዲስ ነገር አጣሁ:: ከፖለቲካ ነፃ የሆነ ምንም ባይኖርም ነፃ የሆነ ሐሳብ ግን ሞልቷል:: የት ሄዶብን ይሆን ነፃ የሆነው ሃሳባችን እንዲህ የሌሎች ሃሳብና አተያይ ጥገኛ ሆነን የቀረነው ጎበዝ!? እንዴት ነፃ መውጣትና በራሳችን መልካም እሳቤ መጓዝ፤ እኛው በምናምንበት በጎ አመለካከት መዝለቅ አቃተን? በጣም ናፈቀኝ፤ የናፈኩት ግን ከአይኔ የራቀ፤ የጠፋብኝ ዘመዴ ወይም ወዳጄ አይደለም:: በጣም አሰኘኝ፤ ያሰኘኝ የምበላው ምግብ ወይም የምጎነጨው ጣፋጭ መጠጥ ግን አይደለም:: የናፈቀኝ ነፃ ጠረጴዛ ነው። መደማመጥ ያለበት፤ ፍሬ ያለው ሐሳብ የሚለዋወጡበት፤ ከፖለቲካዊ ክርክር ነፃ የሆነ ጠረጴዛ፤ ሰዎች ሁሉ የራሳቸውን ሥራ እርግፍ አድርገው መደበኛ “ሥራዬ ፖለቲከኛነት ነው፤ ወሬዬም ከዚያ የማይሻገር” ብለው ከያዙት አሰልቺ ንትርክ ነፃ የሆነ ጠረጴዛ ናፈቀኝ፤አሁን ላይ እኮ ብሶብናል ወገን፤ እንዴት ሁላችንም ፖለቲከኛ ሆነን እንችለዋለን? ግዴለም የምግብና የመጠጥ ማጀቢያችን፤ የጉዞና የአብሮነት ቆይታችን ማጣፈጫ ሌላ መሆኑን ትተን ይሄው ጉዳይ ይሁን፤ ግን እንዴት መሰማማት ተሳነን? ምንም አይነት መደማመጥ በሌለበት የቃላት ልውውጡ ድንበር አልፎ ለጠብ የሚዳርግ እየሆነ ነው:: ታዲያ ይሄ አይሰለችም ወገን? ሃሳብ በመሞገት ማሸነፍ ሳይሆን፤ የራስን ስሜት ብቻ የሚከተሉበትን፤ መግባባት የራቀውን ክርክር ጠላሁ::ነፃ የሆነ ሰው ታውቃላችሁ? ነፃነትን ተጎናጽፎ ንፅት፤ ፅድት ብሎ ህይወቱን የሚመራ ሰው የምታውቁ ከሆነ አገናኙኝ:: አመላክቱኝና ይሄ ሰው ነፃ መሆንን እንዲያጋባብኝ ልወዳጀው፤ እንዴት ይሆን የሚኖረው? ምን አይነት ሐሴት ተጎናፅፎ፤ ምንኛ ከፍ ያለ የመንፈስ እርካታ በውስጡ ናኝቶ? የቱስ አይነት ሐሴት በውስጡ ሰርፆ፤ ሰላም አስገኝቶ ይሆን? ሲያስቀና! እንዲህ ያለ ሰው የማግኘት ህልም አለኝ:: ወዳጆቼ ምሩኝና ላግኘው እባካችሁ! ነገሮችን ሚዛናዊ ሆኖ የሚያይ፤ በስሜት ከመፍረድና ከመወሰን ይልቅ አስልቶ የሚጓዝ ሰው ፈልጉልኝማ፤ ነፃነቱን ተጎናፅፎ ሐሳቡን የሚያራምድ ሰው ተወደደ አይደል? ታዲያ ወዳጆቼ እንዲህ ያለ ሰው መናፈቅ ይነሰኝ? ነፃ የሆነ ባጣ፤ ሁሉም በራሱ ነፃነቱን አጥቶ፤ አርነቱን አስነጥቆ በተገኘበት ዘመን ነፃ የሆነ ሰው መፈለጌ ትክክል አይደለሁ?ነፃ መሆን ውስጣዊ ሰላም ይሰጣል:: ነፃነት ውድ ቢሆንም ሊጎናፀፉት ግድ የሚል የሐሴት መድረክ ነው:: ነፃነት የደስታ ጥግ ላይ የሚያደርስ ብቸኛ መንገድ ነው:: ግን ደግሞ አብዛኞቻችን ነፃነታችንን የምናጣው በኛው በግል ተግባራችን ነው:: ውዶቼ የምናስበውን ነፃነት ነፃ ሆነን ካላሰብነው ነፃነቱ በራሱ ባርነት ነው:: አርነት ውስጥ የማይጎናፀፉት ድል የለም:: አቦ! ከአድልኦ፤ ከበደል፤ ከምቀኝነት ነፃ ያውጣን! አበቃሁ:: ቸር ያሰማን! አዲስ ዘመን ጥቅምት28/2012 ተገኝ ብሩ
https://www.press.et/Ama/?p=22165
707
1መዝናኛ
‘‘ነፃነት… ነፃነት…. ነፃነቴን ስጡኝ”
መዝናኛ
November 10, 2019
50
 አሁን ባለው የኢትዮጵያ ሁኔታ በአዕምሮዬ ሁለት ሐሳቦች ይመላለሳሉ፤ ነፃነት እና ባርነት። ይህንኑ አወርዳለሁ አወጣለው ፤ ታዲያ በመሐል አንድ ሐሳብ ብልጭ አለልኝ። ከማን ነው ነፃነት የሚመጣው? ባሪያ ያደረገኝ ማን ነው ? ሌላ የሐሳብ መንገድ… ሌላ መልስ ፍለጋ… ለነገሩ አዕምሮ አታስብ አይባል። በዚህ መሐል ነው በአንድ ወቅት ከቡክ ወርልድ ድረ ገጽ ያነበብኩት ታሪክ ትዝ ያለኝ።በድሮ ጊዜ አንድ ታላቅ የነፃነት ታጋይ በተራራማው የሀገሪቱ ክፍል እየተጓዘ በአንድ ማደርያ ቦታ ለተወሰነ ጊዜ ለማሳለፍና ለማረፍ ወሰኖ ጎራ አለ። በዚያ ቤት ውስጥ አንድ የሚያምር ተናጋሪ ወፍ (ፓሮት) በወርቅማ የወፍ ቤት ውስጥ ተቀምጦ “ነፃነት፣ ነፃነት፣ ነፃነት” እያለ ይጮሐል። ድምፁንም ጋራ ሸንተረሩ እያስተጋባው ተመልሶ “ነፃነት … ነፃነት …” በሚል ድምፅ አካባቢው ይሞላል።የነፃነት አርበኛው እንዲህ ሲል አሰበ” በህይወቴ በዚህ ዓለም ስዞር ብዙ የፓሮት ወፎችን በፍርግርግ ብረት ውስጥ ተቆልፎባቸው ሲኖሩ አይቻለሁ። እንደዚህ ወፍ ግን የነፃነት ናፍቆት ያለው በየደቂቃው ነፃነቴን እያለ የሚጮህ አይቼ አላውቅም !” ቀኑን በዚህ ወፍ እየተገረመ ውሎ መምሸት አልቀረም መሸ። የቤቱ ባለቤት በጊዜ እንቅልፍ ወስዶት ቤቱ ጭር እንዳለ ቀኑን በወፉ ሲገረም የዋለው በተፈጥሮው ለነፃነት ታላቅ ክብር የሚሰጠው ሰው አንድ ሐሳብ ብልጭ አለለትና ተነስቶ ወደ ወፉ ቤት በመሄድ የብረት ቤቱን በር ከፈተለት። ወፉ ግን ወደተከፈተለት በር በመቅረብ ፋንታ ወደኋላ እየሸሸ “ነፃነት፣ ነፃነት፣ ነፃነት… “ ሲል ጮኸ፤ አርበኛውም “አሁን በሩ ተከፍቶልሐል፣ ና ውጣ በሰማዩ እንደፈለክ ብረር የነፃነትን አየር ተንፍስ ሁሉም ተኝተዋልና የሚይዝህ የለም፤ አምልጥ አለው” ተናገሪዋ ወፍ ግን ይበልጥ ከመውጫ በሩ እየሸሸ በፍርግርግ ብረቶቹ መታከኩን ቀጠለ ግራ የተጋባው ሰው እጁን ወደወፉ ቤት ሰዶ ሊይዘውና እንዲወጣ ሊረዳው ሞከረ ወፉም ባለ በሌለ ሃይሉ እጁን ቧጨረው ነከሰው እንደዛም ሆኖ ጎትቶ አውጥቶ እንዲበር ለቀቀው እና ክፉኛ የተነከሰው እጁ ህመሙ ቢሰማውም በሠራው መልካም ተግባር ግን ልቡ ረክቶ ተኛ በጠዋት ሲነሳ የተቀበለው የፓሮት ወፉ ድምፅ ነበር “ነፃነት ነፃነት ነፃነት” ይላል አርበኛውም አንድ አለት ላይ ወይም ዛፍ ላይ ተቀምጦ እንደልማዱ እየጮኸ ነው ብሎ እያሰበ ከመኝታው ተነስቶ ወደ ወፉ ቤት ሲመለከት ባየው ነገር ደነገጠ ወፉ በሩ በተከፈተው እስር ቤቱ (ጎጆው) ውስጥ ሆኖ “ነፃነት ነፃነት ነፃነቴን ስጡኝ” ብሎ እየጮኸ ነው።አሁን ባለችው ኢትዮጵያ እየሆነ ያለው ይኸው ነው፤ በተከፈተ በር በሚረዳ እና በሚያግዝ መሪ የመጣውን ሰላም ማጣጣም አቅቶን የምንባክነው። ልክ ከላይ እንዳለችው ፓሮት ከነበርነበት ፍርግርግ ወይ ከእርዳታ አልወጣን፣ አሊያም በራሳችን ጉልበት እንዲያው ፍርግርግ ውስጥ ሆነን በመጋጨት አካላችን ጎዳን እንዲሁም ለነፃነታችን ዋጋ የከፈሉ ሊረዱን የተዘረጉ እጆችን አደማን፤ ጎዳን። እስቲ ወደ ልቦናችን እንመለስ የምንፍልገው ምንድነው? ጭራስ የሌለን ነው? ወይስ የጎደለን? ለሁሉም እንደ ፓሮቷ ከመጮሐችን በፊት እንዲህ ያሉ ጥያቄዎችን እያነሳን እንጠይቅ፤ ታላቁ መጽሐፍ “የጻድቅ አይኖች ወደራሱ ናቸው” ይላል። ይህም ማለት ራስን በመግዛት ራስን ማየት ብዙውን ጥያቄና የምንፈልገውን ሰላም ይመልስልናል።ስለዚህም ለምንጠይቀው ጥያቄ መልሱ ያለው እኛው ጋር መሆኑን መረዳት ይኖርብናል፤ ወዳጆቼ እንደሚታወቀው ነፃነት አንፃራዊና ከእንቅስቃሴ ጋር የተዛመደ ነው። የሰው ልጅ ሲፈጠርም ሆነ ሲኖር ነፃ አይደለም። እድገቱና አኗኗሩ በተፈጥሮና ሰው ሰራሽ አጥሮች የተከበበ ነው። ያሻውን፣ የፈለገውን ማድረግ አይችልም። ውስንነት አለበት። አንድም በባህልና በሃይማኖት ሌላው ደግሞ በሰው ሰራሽ ሕግጋት ተጽዕኖ ሥር ነው።በሌሎች ላይ በደል ያደረሰ ሰው ፈፅሞ በነፃነት መኖር አይቻልም። የመኖር መለኪያ ደግሞ ነፃነት ነው። የመሥራት፣ የማደግ ዋልታ ደግሞ ስምምነት ነው። ምድር የሁሉም ቤት ናት። ሰውም ምድርን በጊዜያዊነት ይገለገልበታል። አርሶ፣ ዘርቶ፣ አጭዶ፣ ወቅቶ ይጠቀምበታል። አምርቶ፣ ፈብርኮ፣ ለብሶ፣ አጊጦ ይታይባታል። ተወልዶ፣ አድጎ፣ አግብቶ፣ ወልዶ ተዛምዶ ይኖርባታል። ግን በነፃነት አይኖርም። ምክንያቱም ነፃነት በተፈጥሮ ሳይሆን በፍለጋ የሚገኝ በመሆኑ ነው። ነፃነት ያለ ተጠቃሚነት ባርነት ነው። በድህነት ሥር የሚዳዳ ሰው ነፃ ይሁን አይሁን ትርጉም አይሰጠውም። ለምን የቅድሚያ ቅድሚያ ተጠቃሚ አይደለምና። የነፃነት መለኪያ በስምምነት ላይ የተተከለ ተጨባጭነቱ የተረጋገጠ የተጠቃሚነት ውህደት ድምር ውጤት ነው። ሰው በተፈጥሮና በሰው አዕምራዊ ውጤት የሚገኝ ጥቅም ተጠቃሚ ካልሆነ ነፃነት አልባ ከመሆኑም በላይ የዲሞክራሲ ሥርዓት የለውም። ተጠቃሚነት ባልስፈነበት ዲሞክራሲ ይጎረብጣል። ዲሞክራሲ ከፍላጎት ጋር ካልተጣጣመ ጉዳት ነው። ምክንያቱም ዲሞክራሲ የነፃነት ጥቅም ማስከበሪያ መሣሪያ በመሆኑ ከማህበረሰብ ፍላጎት ጋር መጣጣም ይኖርበታል። ፍትሐዊ ጥቅምና ለውጥ ያለፍትሐዊ ነፃነት ዋጋ ቢስ ከመሆነም በላይ የጋርዮሽ ስምምነት መርሆች ያፈርሳል። በጋራ ለመኖርና ለመበልፀግ የጋራ መርሆ ያስፈልጋል። የመርሆች ተፈፃሚነት ማሳያ አንዱ ሰብአዊ ብልፅግና ነው።ሁሉም የተሰጠውን በአግባቡ ቢጠቀም፤ የጎደለ ካለ ከራሱ ለራሱ እየሞላ ምክንያቱም አገር ማለት ጠያቂው (ግለሰብ፣ ማህበረሰብ)፣ ተጠያቂው (መንግሥት)፣ መሬቱ፣ ጋራው፣ ሸንተረሩ… ስለሆነ…. የኮንትራት ህይወቱ እስክታልቅ በነፃነት በሰላም ለሰላም እየኖሩ ማለፍ….. ትውልድ ይመጣል …ትውልድ ያልፋል። መልካም ዕለተ ሰንበት !!አዲስ ዘመን ጥቅም30/2012 አብርሃም ተወልደ
https://www.press.et/Ama/?p=22254
622
1መዝናኛ
ከፅዳት ሠራተኝነት እስከ አብራሪነት
መዝናኛ
November 11, 2019
48
ህይወት በብዙ ውጣ ውረዶች የተፈተነች ናት። ገሚሶቹ ዛሬን ተቸግረው ነገን በተስፋ ሲያልሙ የተቀሩት ደግሞ በአቋራጭ ለመክበር ድንጋዮችን ሲፈነቅሉ ይስተዋላል። ተስፋን የሰነቁ ሁሉ በመንገዳቸው የሚገጥማቸውን እንቅፋት ገሸሽ በማድረግ የነገ መንገዳቸውን ያመቻቻሉ። ችግር ከጉዟቸው እንዳያደናቅፋቸው ከወዲሁ የሰነቁትን የሞራል ስንቅ በመከላከያነት ይጠቀማሉ። ውጣ ውረዶችን እንዲሁም ከፍታና ዝቅታን የህይወት አንድ አካል አድርጎ በመቁጠር በተስፋ ወደፊት መገስገስን የሚለማመዱት እነዚህ የነገ አላሚዎች መነፅራቸው ስኬትን እንጂ ውድቀትን አይመለከትም።ሁሌም የሚያስቡትና የሚያልሙት ትናንትናቸው አስተማሪ፣ ዛሬያቸው ተስፋ እና ነጋቸው ብሩህ መሆኑን ብቻ ነው። ከፍታ የሚጀመረው ዝቅ ብሎ ከተቀመጠው መወጣጫ መሆኑን ጠንቅቀው የሚያውቁት እነዚህ ግለሰቦች ከግባቸው ለመድረስ ለአፍታም ሲያመነቱ አይስተዋልም። እሾሁን ለቅመው፣ ጠጠሩን ጠርገው፣ አቧራውን አራግፈውና የችግር አጥርን ጥሰው ከፍ ብለው መታየት ቀጣዩ የህይወት ጉዞ መሆኑን በመረዳት ለዚህ ጉዞ ወገባቸውን ጠበቅ አድርገው ይታጠቃሉ። በሀገራችንም ሆነ በአለማችን በተለያዩ ጊዜያት እጅግ ዝቅ ካለ የኑሮ ደረጃ ተነስተው አለምን የሚቀይር ሃሳብ፣ እውቀትና ገንዘብ ያካበቱ በርካታ ግለሰቦችን ታሪክ አይተንም ሰምተንም እናውቃለን።ከራሳቸው አልፈው ለሌሎች የጠቀሙና አንቱታን ያተረፉ ግለሰቦች የስኬት መንገዳቸው ሲመረመር የአንዳንዶቹ ለማመን ሲከብድ ይስተዋ ላል። የስኬታማ ግለሰቦች የራስ ጥረትና ትጋት ተጨምሮበት በሩጫቸው ውሃ ያቀበሏቸው አጋሮ ችም የስኬት መሰላልን የሚያስጨብጡ ተምሳሌቶች ናቸው።ዛሬ ከወደ ናይጄሪያ የተሰማ የአንድ ስኬ ታማ ግለሰብን ታሪክ ልናስነብባችሁ ወደናል። ኢንተለጀንስ ዶት ኮም እንዳስነበበው ግለሰቡ አብራሪ የመሆን ህልሙን የጀመረው ከአውሮፕላን የፅዳት ሰራተኝነት ተነስቶ ሲሆን አሁን ላይ የንግድ አውሮፕላን አብራሪ ለመሆን በቅቷል። የዚህ ስኬታማ ሰው አጭር የስኬት ታሪክ እንደሚከተለው ነው።ናይጀሪያዊው መሀመድ አቡበከር ከዛሬ 24 አመታት በፊት የአውሮፕላን ፅዳት ሰራተኛ ሆኖ ነበር ካቡ ኤር በተባለ ኩባንያ የተቀጠረው። በካዱና ፖሊ ቴክኒክ ለመማር አመልክቶ የትምህርት ማስረጃዎቹን በጊዜው ባለማስገባቱ ተቀባይነት ሳያገኝ የቀረው መሀመድ ምንም እንኳን የስራ ምርጫው ባይሆንም ለረጅም ጊዜ ያለስራ መቀመጥን ባለመምረጥ ነበር በካቡ ኤር ውስጥ ለመቀጠር የወሰነውና በአውሮፕላን የፅዳት ሰራተኝነት ስራ የጀመረው።የመሀመድ ደመወዝ እጅግ ዝቅተኛ ማለትም በቀን 200 የናይጀሪያ ናይራ ወይም 0.5 የአሜሪካን ዶላር በመሆኑ ማንም ሰው በስራው ላይ ይቆያል ብሎ አልገመተም ነበር፤ ነገር ግን ይህ ባለሩቅ ተስፋ ሀልመኛ ወጣት በስራው በመግፋት ብቻም ሳይሆን ውጤታማ ሰራተኛ በመሆን ከጊዜ ቆይታ በኋላ በሜዱግሪ ኤር በግራውንድ ስታፍነት ተቀጠረ።ራሱን በዲሲፕሊን የታነፀና ውጤታማ ሰራተኛ ያደረገው መሀመድ በአቪየሽን ዘርፍ በርካታ እውቀቶችን እንዲያካብት አስቻለው። በቀጣይም መሀመድ በካቦ ኤር የበረራ አባልነት ላይ የማመልከት እድል አግኝቶ ስራውን መስራት ጀመረ። በዚህ ስራም ስምንት አመታትን በወር 17 ሺህ ናይራ ወይም 47 የአሜሪካን ዶላር እየተከፈለው ሰራ። ከዚህ በኋላም በበረራ ተቆጣጣሪነት ወደ ኤሮ ኮንትራክተርስ ተዛወረ።የስራ ታታሪነቱና ፈጣን አዕምሮው በድርጅቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ትኩረትን መሳብ የቻለው መሀመድ ወርሀዊ ደመወዙ በወር ወደ 170 ሺህ ናይራ ወይም 469 የአሜሪካን ዶላር ከፍ አለ። ይህንን ማመን ያቃተው መሀመድ የመጀመሪያ የደመወዝ ክፍያ ቼኩን ሲቀበል ገንዘቡን ለመመለስ ሞክሮ እንደነበር ተገልጿል።የሚያገኘውን ደመወዝ በዋዛ ፈዛዛ ማጥፋት ያልፈለገው መሀመድ ቁጠባ በመጀመር አብራሪ የመሆን ህልሙን እውን ለማድረግ ጉዳዩን ለዋና ዳይሬክተሩ አስረዳ፤ ዳይሬክተሩም የመሀመድን ሃሳብ በመደገፍ ድጋፍ ተደርጎለት በካናዳ የግል አብራሪነት ፈቃድ ለማግኘት ትምህርቱን ጀምሮ በስኬት አጠናቀቀ።መሀመድ ወደ ናይጀሪያ ከተመለሰ በኋላ የንግድ አብራሪነት ፈቃድ መያዝ ቢፈልግም በቂ ገንዘብ ስላልነበረው ይህንን ማሳካት አልቻለም፤ ይሁን እንጂ ችግሩ ይህንን ህልሙን እና ጠንካራ መንፈሱን ሳይጎትተው ወደ ፊት በመገስገስ የድርጅቱን ም/ዋና ዳይሬክተር ድጋፍ በመጠየቅ ታማኝነቱና ስራ ወዳድነቱ በኩባንያው ተጨማሪ ድጋፍ እንዲደረግለት ረዳው።ለሁለተኛ ጊዜ ወደ ካናዳ በመሄድ የንግድ አውሮፕላን አብራሪነት ስልጠናውን አጠናቆ ወደ ትውልድ ሀገሩ ናይጀሪያ ተመለሰ። ከ24 አመታት ጠንካራና ውጤታማ የስራ ጊዜያት በኋላ መሀመድ በአዝማን ኤር ውስጥ የአውሮፕላን አብራሪ ሆኖ በመቀጠር ህልሙን እውን አደረገ። አሁን መሀመድ በዚህ አየር መንገድ ውስጥ በአብራሪነት ስራውን እየሰራ ይገኛል፡አዲስ ዘመን ኅዳር 1 / 2012 በድልነሳ ምንውየለት
https://www.press.et/Ama/?p=22304
503
1መዝናኛ
ተዝናኖታዊ ንባብ ለተሟላ ሰብዕና
መዝናኛ
November 11, 2019
46
የሰው ልጅ የጋራ ባህርያትና ተግባራት ከሆኑት መካከል አንዱ መዝናናት ሲሆን የጋራ ያልሆነው ደግሞ የሚያዝናናው ነገር፣ የሚዝናናበት ፍሬ ነገርና ይዘት ጉዳይና ለዚህም የሚሄድበት ርቀት ነው። ያንዱ መዝናኛ ስፖርታዊ እንቅስቃሴ (ዋና፣ ብስክሌት መንዳት . . .) ሲሆን ለሌላው ጉብኝት ሊሆን ይችላል። ለአንዱ ምግብ ማብሰል ሲሆን ለሌላው ልብስ ማጠብ፤ ለአንዱ ሰብሰብ ብሎ ማውራት (ካፌም ቢሆን) ሲሆን ለሌላው ሽር ሽር ቢሆን አይገርምም። አሁን አሁን ደግሞ ይህ ቀረህ በማይባል ደረጃ ጥፋት እያደረሰ ባለው ማህበራዊ ሚዲያ (በተለይ ፌስቡክ) ሱስ የተጠመዱ ሰዎች ጉዳይ እያሳሰበ ከመሆኑም በላይ ለተከታዮቹ መዝናኛቸው ሁሉ እሱ እየሆነ መምጣቱ በየጊዜው በሚወጡ ጥናቶች እየገለፁ ነው።ቴዎድሮስ ታደሰ “ሰው በወደደው/ባፈቀረው ይገድፋል” እንዳለው፤ ጉዳዩ የግል ምርጫ ሲሆን፤ እዚህ ልንጨዋወት የፈለግነው ግን ምርጫቸው ንባብ/ማንበብ ስለሆነው ተዝናኞት ነው።“ማንበብ ሙሉ ሰው ያደርጋል!!”፤ “ማንበብ ማበብ ነው።” የሚሉትም ሆኑ ሌሎች እንዳሉ ሆነው የንባብን ማዝናናት ሚና ማውሳት ተገቢ ነው። በእርግጥ ከሥነፅሁፍ አላማዎች አንዱ ማዝናናት ነው። ይሁን እንጂ ይህን የተረዱ ቢኖሩ ጥቂቶች ናቸው። ንባብ ባህል በሆነባቸው አገራት አንድ ሰው በአማካይ በቀን ውስጥ 16 በመቶ ያህል ጊዜውን የሚያሳልፈው በንባብ መሆኑን የሚያወሱ በርካታ ጥናቶች ለአደባባይ ከበቁ ሰንብተዋል። የማቀበያ ክሂል የሆነው ንባብ መረጃ ከሚሰበሰብባቸው አበይት ምንጮች አንዱ ሲሆን ዛሬ ዛሬ ከመረጃ አቀባይነቱ በዘለለ አዝናኝነቱ እየተነገረለት፤ መፃህፍትን ለተዝናኖት የሚያነቡ ሰዎች ቁጥርም በእጅጉ እየላቀ ይገኛል።በተለይ በህፃናት በኩል እየተለመደ የመጣውና ወደ ፊትም ባህል ይሆናል ተብሎ የሚጠበቀው ተዝናኖታዊ ንባብ በአንዳንድ አገራት ይሁነኝ ተብሎ ጊዜ፣ በጀትና የሰው ሀይል ተመድቦለት ልምዱን የማጎልበት ስራዎች ሲሰሩ ይታያል። ሌሎችም ልምዱን እየወሰዱ ይገኛሉ። ይህን ጉዳዬ ብሉ እየሰራበት ካለው ኦፕን ዩኒቨርሲቲ ድረ-ገፅ “READING FOR PLEASURE” አምድ የበለጠ መረዳት ይቻላል።ተዝናኖታዊ ንባብን ከሌሎች የንባብ አይነቶች ለየት የሚያደርጉት በርካታ ሁኔታዎች ያሉ ሲሆን ዋና ዋናዎቹ ምንም አይነት ቦታና ጊዜን አለመምረጡ፣ በተገኘው አጋጣሚ ሁሉ ሊከናወን መቻሉ፣ ቀስ በቀስ የህይወት አካል እየሆነ መሄዱ፣ ወደ ሂሳዊና ምርምራዊ የንባብ ሂደቶች ማደጉ፣ ከማዝናናት በተጨማሪ በተለያዩ ዘርፎች ሰፊ እውቀትን ማስጨበጡ፣ ከበርካታ የመዝናኛ አይነቶች የተሻለ ሆኖ መገኘቱ፣ አለማችንን የበለጠ ለማወቅና ትስስራችንን ማጥበቁ፣ ወጪ ቆጣቢነቱ፣ ለማህበራዊ ህይወትና መስተጋብር መጠናከርና መጎልበት ያለው ፋይዳ ከፍተኛ መሆኑ፣ ሌሎችን ለመረዳትና ለመግባባት በከፍተኛ ደረጃ መጥቀሙ፣ አንባቢው ስለሙያው የተሻለ እውቀትና ግንዛቤን ማግኘት መቻሉ እና የመሳሰሉት ናቸው። ይሁን እንጂ እንደ አንዳንድ አጥኚዎች ግኝት ደግሞ የተዝናኖት ንባብ አዞታሪ ከሁሉም በላይ የሚያገኘው ጠቀሜታ ቢኖር በተሟላ ደረጃ ጤነኛ የመሆኑ ጉዳይ ነው። በጉዳዩ ላይ ያጠኑት እንደሚናገሩት ተዝናኖታዊ ንባብ ለጤና መጠበቅ እጅግ አስፈላጊ ከመሆኑም በላይ ያጋጠመ የጤና እክል እንኳን ቢኖር በመፍትሄነት የማገልገሉ ጉዳይ የተረጋገጠ ነው። አቢጌል ፒኔው “WHAT ARE THE BENEFITS OF READING FOR PLEASURE?” በሚል ርእስ ያቀረቡት ጥናት እንደሚያሳየው ተዝናኖታዊ ንባብ ከጭንቀት ይገላግላል፣ አንድ ሰው ጭንቀት ካለበትም በከፍተኛ ደረጃ ይቀንስለታል፣ በእለት ተእለት ህይወታችን የሚያጋጥሙንን ችግሮች እንድንረሳቸውና በእነሱ ከመብሰልሰል እንድናመልጥ ይረዳናል፤ ደረጃ በደራጃ የበሰሉ የሥነጽሁፍ ስራዎችን ወደ ማንበብና መረዳት እንድንሄድ፣ አምስቱን የስሜት ህዋሳቶቻችንን በአግባቡ እንድንጠቀም ያደርገናል፣ ትክክለኛ፣ ውስጣዊ ሰላም ያለውና ነፃ ደስተኛነት (inner peace and tranquility)ን ያስገኛል፤ ስለራሳችን – ማንነታችንንና ከየት እንደመጣን በውል እንድንገነዘብ ያደርገናል፤ አንባቢ ማህበረሰብና አንባቢ ትውልድ ለመፍጠር ያግዛል፤ እየተደረገ ያለው ጥረት ካለ ያፋጥናል፤ ሃሳብ መቀበልና ሃሳብ መስጠት ላይ ያሉ እንቅፋቶችን ያስወግዳል፤ ወደ ዳበረ የፅሁፍ/መፃፍ ክሂል እንድናመራ ያደርገናል፤ እውቀትን ያበለፅጋል (ከጠቅላላ እውቀት ጀምሮ)፤ በማንኛውም ዘርፍ ያሸጋግረናል፤ በስራ ቦታ የሆነም እንደሆን በስራ ባልደረቦችም ሆነ አለቆች ዘንድ ተወዳጅ፣ ተደማጭና ተከባሪ ያደርጋል፤ የማስታወስ አቅማችንን ይጨምራል፤ የአእምሮ መነቃቃትን ይፈጥራል፤ ብቸኝነት ጥንቡሳሱን ይዞ ገደል ይገባ ዘንድ ያግዛል፤ የተንታኝነት፣ መርማሪነት፣ ሃያሲነት ወዘተ ፍላጎት፣ አቅምና ብቃት እንዲኖረን ያደርጋል፤ ወቅታዊ ያደርጋል፤ በአንድ ጉዳይ ላይ አተኩረን የመስራት ችሎታችንን ያዳብርልናል፤ በራስ መተማመን እንደልብ ነው። እንደ ተመራማሪዋ ግኝት ተዝናኖታዊ ንባብ ሌሎችም በርካታ ፋይዳዎች ያሉት ሲሆን ባጭሩ ሱስ ነው። ከትምህርት ቤት ውጪ ለተዝናኖት ሲሉ መፃህፍትን የሚያነቡ የ16 አመት ልጆች በአብዛኛው የወደፊት ሙያዊ የመሪነት መንበራቸውን ከወዲሁ የሚያረጋግጡ ናቸው። (16-year-olds who choose to read books for pleasure outside of school are more likely to secure managerial or professional jobs in later life.) የሚለውን የእንግሊዝ አገር ጥናት ስንመለከት ደግሞ የተዝናኖት ንባብን የጠቀሜታ ጥጉ የት ድረስ እንደሆነ ጥርት አድርገን እንገነዘባለን።የአሜሪካው “The U.S. National Reading Panel” እንደሚለን ከሆነ ጥሩ አንባቢያን በተዝናኖት ንባብ ውስጥ ያለማቋረጥ እንደሚሳተፉ የሚያሳዩ በርካታ ጥናቶች አሉ። በጥናቶቹም 80 በመቶዎቹም መዝናኛቸው ንባብ እንደሆነም ተመልክቷል።እዚህ ላይ በተደጋጋሚ የሚነሳውና እንደ የተዝናኖት ንባብ ተግዳሮት ተደርጎ የሚወሰደው የአገልግሎትና አቅርቦት ጉዳይ ነው። ተዝናኖታዊ ንባብ የመንግስታትን፣ ተቋማትን፣ ባለሀብቶችን እና የሌሎችን ቀና ትብብር ሁሉ ይፈልጋል። ለምን ቢሉ በተለያዩ መንገዶች በተለያዩ ስፍራዎች የሚነበቡ መፃህፍት ይገኙ ዘንድ የግድ ነውና ነው። ቤተመፃህፍት በብዛት ያስፈልጋሉ፤ የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር አይነት አሰራር – የሚነበቡ መፃህፍት አቅርቦት ያስፈልጋል፤ በየሆቴሎች፣ ካፌዎች. . . ሁሉ ንባብን የሚያበረታቱ፣ ስለንባብ የቆሙ ጉዳዮች ሊኖሩ ይገባል። የተዝናኖታዊ ንባብ ሱሰኛው በሄደበት ሁሉ የሚያነበው ነገር የሚፈልግ በመሆኑ እጥረትን አይፈልግም። ለዚህም ነው እነ ፊንላንድ (“The Most Literary Nation in The World” የተባለላት)፣ አሜሪካ፣ እንግሊዝን የመሳሰሉ አገራት በተዝናኖታዊ ንባብ በኩል ምንም አይነት ክፍተት እንዳይፈጠር እየሰሩ የሚገኙት። ትኩረት ለተዝናኖታዊ ንባብ!አዲስ ዘመን ኅዳር 1 / 2012  ግርማ መንግሥቴ
https://www.press.et/Ama/?p=22315
707
1መዝናኛ
ሙስና በሀገር ህልውና ከደቀነው አደጋ አንጻር መገናኛ ብዙሀን ትኩረት ሰጥተው ሊሰሩበት እንደሚገባ ተጠቆመ
ሀገር አቀፍ ዜና
January 5, 2021
3
 በጋዜጣው ሪፖርተርአዳማ፦ መገናኛ ብዙሀን ሙስና በሀገር ህልውና ላይ ፈጥሮት ከነበረው አደጋ አንጻር ትኩረት ሰጥተው ሊሰሩበት እንደሚገባ የፌደራል የስነ ምግባር እና ጸረ ሙስና ኮሚሽን አስታወቀ። የኮሚሽኑ ኮሚሽነር አቶ ጸጋ አራጌ “ ስነ ምግባርን በመገንባትና ሙስናን በመከላከል ረገድ የሚዲያ ተቋማት ሚና” በሚል መሪ ሃሳብ በአዳማ ከተማ ትናንት በተዘጋጀው የውይይት መድረክ ላይ እንዳስታወቁት፤ በሀገሪቱ የተንሰራፋው የሙስና ችግር የሀገሪቱ ዕጣ ፈንታ ላይ ከፍተኛ ተግዳሮት ሆኗል። በቅርቡ ሀገሪቱ የገጠማትና ከፍተኛ ዋጋ ያስከፈላት ችግር ከሙስና ጋር የተያያዘ መሆኑን የጠቆሙት አቶ ጸጋ፤ ችግሩ በሙስና የተዘፈቀ ስርአትን ለማስቀጠል፣ በሙስና የተሰበሰበን ሀብት ያለ ችግር ለመጠቀም ካለ ከፍ ያለ መፈለግ ጋር የተያያዘ ነው ብለዋል። ይህ ችግር ለአንድ ተቋም ወይም ለተወሰኑ የመገናኛ ብዙሀን የሚተውት ሳይሆን የሁሉንም የመገናኛ ብዙሀን ንቁ ተሳትፎ የሚጠይቅ መሆኑን ጠቁመው፤ ሁሉም ችግሩ ሊያስከትል ከሚችለውና አስከትሎት ከነበረው አደጋ አንጻር ሊመለከቱት ይገባል ብለዋል።ከጋዜጠኝነት ሙያ አንጻር የሙስና ጉዳይ ወቅታዊ መሆኑን ያመለከቱት አቶ ጸጋ፤ ጉዳዩን አጀንዳ በማድረግ መገናኛ ብዙሀን በስፋትና በጥልቀት ሊሄዱበት እንደሚገባ አስታውቀዋል። ወቅታዊነቱም የችግሩ ስፋት እስኪቀንስ ሊቀጥል የሚችል እንደሆነ አመልክተዋል። ኮሚሽኑ ከ2008 ዓ.ም በፊት የማስተማር ፣የመከላከል ፣የመመርመርና የመክሰስ ተቋማዊ ኃላፊነትና ህጋዊ ስልጣን እንደነበረው አመልክተው፤ በአሁኑ ወቅት ተልእኮው በማስተማርና በመከላከል ላይ እንዲያተኩር መደረጉን አስታውቀዋል። የመመርመርና የመክሰስ ስልጣንና ኃላፊነት ለፖሊስና ለአቃቤ ህግ መሰጠቱንም ጠቁመዋል። በሀገሪቱ በተቋሞች መካከል ካለው በአግባቡ ያለመናበብ ባህል አንጻር ለጸረ-ሙስና ትግሉ ስኬት ኮሚሽኑ ስራዎችን በራሱ ተቋማዊ አቅም “ከመነሻ እስከ መጨረሻ” የሚሄድበት ስልጣንና ኃላፊነት ቢሰጠው የተሻለ እንደሚሆን አስታውቀዋል። በአሁኑ ወቅት ኮሚሽኑ ከተሰጠው ተልእኮ አንጻር በአብዛኛው ከምርመራና ከክስ ጉዳዮች ጋር በተያያዘ ስሙ እንደሚነሳ አመልክተው፤ ከምርመራና ከክስ ጋር የተያያዙ ጉዳዮች ከፖሊስና ከአቃቤ ህግ ጋር የተያያዙ ስለመሆናቸው አመልክተዋል። ኮሚሽኑ ቀደም ባሉት ጊዜያት በአብዛኛው ስኬታማ አለመሆኑ የሚነገረው እንደ ተቋም የተሰጠውን ተልእኮ የመወጣት ችግር ስለነበረበት ሳይሆን ከነበረው ሰፊ ጣልቃ ገብነት የተነሳ እንደነበር ገልጸው፤ በተቋሙ ላይ የነበረው ጣልቃ ገብነት ግላዊ ፍላጎትን እስከማስፈጸምና መበቃቀያ እስከመሆን የደረሰ እንደነበር አስታውቀዋል።የመገናኛ ብዙሀን የምርመራ ዘገባዎችን በስፋት በመስራት በጸረ ሙስና ትግሉ ውስጥ ጉልህ አስተዋጽኦ ማበርከት እንደሚችሉ ያስታወቁት ኮሚሽኑ፤ መገናኛ ብዙሀን ይህን ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል። ለዚህም ኮሚሽኑ የሙያ ክህሎት ስልጠናዎችን ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆኑ ለመስጠት ፈቃደኝ መሆኑን አስታውቀዋል። የምርመራ ጋዜጠኝነት ሙስናን ለመከላከል የሚደረገውን ትግል በማቅለል ከፍ ያለ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው አመልክተው፤ የምርመራ ጋዜጠኝነት የኮሚሽኑን ፣ የፖሊስና የአቃቤ ህግን ስራዎች በማቅለል የሚኖረው አዎንታዊ ጠቀሜታ የጎላ ነው ብለዋል። ኮሚሽኑ ከመገናኛ ብዙሀን ጋር በቅንጅት ለመስራት ዝግጁ መሆኑን ያስታወቁት ኮሚሽነሩ፤ መገናኛ ብዙሀን የሙስና ጉዳይ ችግሩ ለተወሰነ አካል የሚተው አለመሆኑን በአግባቡ ተገንዝበው አብረውት እንዲሰሩ ጠይቀዋል። በውይይት መድረኩ ላይ” ሙስናን ለመዋጋት የመገናኛ ብዙሀን ሚና “በሚል ጥናታዊ ጽሁፍ ያቀረቡት የኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ጌታቸው ድንቄ በበኩላቸው፤ መገናኛ ብዙሀን ሙስናን በመከላከል ሂደት ውስጥ ከፍ ያለ ሙያዊ ኃላፊነት እንዳለባቸው ጠቁመዋል። በቀደሙት ጊዜያት መገናኛ ብዙሀን በብዙ ተግዳሮቶች ውስጥ ማለፋቸውን ያመለከቱት ዋና ዳሬክተሩ፤ በከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት ሳይቀር በአደባባይ የምርመራ ጋዜጠኝነት ለሀገሪቱ እንደማያስፈልግ ለመናገር የተደፈረበት እውነታ እንደነበር አስታውሰዋል። ይህም ጋዜጠኞች ላይ የነበረው ጫና የቱን ያህል ከባድ እንደነበር ማሳያ ነው ብለዋል።የምርመራ ጋዜጠኝነት ከፍ ካለ ኃላፊነት የሚመነጭ ቁርጠኝነት የሚጠይቅ፣ በሙያው ትልቅ ስፍራ የሚሰጠው መሆኑን የጠቆሙት ዶክተር ጌታቸው፤ በስራው የሚሰማራው ጋዜጠኛም ከሚያነሳቸው ጉዳዮች ክብደት አንጻር ለአደጋ የሚያጋልጡ እንደሆኑ አመልክተዋል።ይህም ሆኖ ግን ልንገነባው ካለነው የዴሞክራሲ ስርአት አንጻር የምርመራ ጋዜጠኝነት ከፍተኛ ትኩረት የሚፈልግ በመሆኑ መገናኛ ብዙሀን ትኩረት ሰጥተው ሊሰሩበት እንደሚገባ አመልክተዋል።መገናኛ ብዙሀን እስካሁን በመጡበት ሂደት ከምርመራ ጋዜጠኝነት አንጻር የጀመሯቸው ስራዎች መኖራቸውን አመልክተው፤ ስራዎች በህዝብ በሰፊው ተቀባይነት እንደነበራቸው አስታውቀዋል። እነዚህን ጅማሮች አጠናክሮ በመቀጠል ያለባቸውን ሙያዊ ኃላፊነት መወጣት የሚያስችል የተሻለ ዝግጁነት መፍጠር እንደሚጠበቅባቸው አሳስበዋል። በውይይት መድረኩ ላይ የተለያዩ የመገናኛ ብዙኃን ከፍተኛ ባለሙያዎች እና አመራሮች ተሳትፈዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 27/2013
https://www.press.et/Ama/?p=38879
518
0ሀገር አቀፍ ዜና
የበቆሎ ምርት በሄክታር ከ42 ኩንታል በላይ መድረሱ ተገለጸ
ሀገር አቀፍ ዜና
January 5, 2021
9
ሰላማዊት ውቤአዳማ፦ በአሁኑ ወቅት ከሦስት ዋና ዋና የግብርናው ዘርፍ መርሐ ግብሮች አንዱ በሆነው የድህነት ቅነሳ የበቆሎ ምርትን በሄክታር 42 ኩንታል ማድረስ መቻሉ ዓለም የደረሰበት ደረጃ ለመድረስ ጥሩ ሂደት ላይ መሆናችንን እንደሚያሳይ ተገለጸ። የግብርና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ማንደፍሮ ንጉሴ ከትናንት በስቲያ በአዳማ ከተማ ለግማሽ ቀን በተካሄደና አጠቃላይ ግብርናው ያለበትን ሁኔታ የዳሰሰ ፓናል ውይይት ላይ እንዳስታወቁት፤ ባለፉት 20 ዓመታት የበቆሎ ምርት ከፍተኛ ዕድገት አሳይቷል።ዕድገቱ በአንደኛውና በሁለተኛው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዘመን ጭምር የተገኘ ነው ያሉት ዶክተር ማንደፍሮ፤ እስከ አምና ድረስ በሄክታር የተገኘው 42 ነጥብ 4 ኩንታል መሆኑንም ጠቅሰው፤ በዚህ ዓመት ሲጨመር ደግሞ በሄክታር የሚገኘው የበቆሎ ምርት ከዚህ ከፍ ሊል እንደሚችልም ጠቁመዋል።የምርት ዕድገቱ ምን ያህል ለድህነት ቅነሳ ትኩረት ሰጥቶ እየተሰራ እንደሆነ የሚያመለክት መሆኑን የጠቆሙት ሚኒስትር ዴኤታው በዓለም ላይ በሄክታር በአማካኝ ያለው የበቆሎ ምርት ዕደገት 58 ኩንታል መሆኑንም ተናግረዋል።እንደ ሀገር በሄክታር የደረስንበት 42 ነጥብ 4 ኩንታል ከዓለም ጋር የሚቀራረብና ዓለም የደረሰበት ደረጃ ለመድረስ በዚህ ሰብል ጥሩ ሂደት ላይ ነን ማለት የሚያስችል መሆኑን ዶክተር ማደፍሮ ጠቁመው፤ የስንዴ ምርትም ባለፉት አስር አመታት በከፍተኛ ሁኔታ ማደጉንና አሁን ላይ ከራሳችን አልፈን ወደ ውጪ ለመላክ በዘመቻ መርሐ ግብር መልክ እየሰራን ነው ብለዋል። ‹‹የአሁን ምርትና ምርታማነትን የማሳደግ መርሐ ግብር የድህነት ቅነሳን ብቻ ሳይሆን ሁሉንም አመጣጥኖ የሚሄድ ነው›› ያሉት ሚኒስትር ዴኤታው፤ ግብርና ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ትልቅ ፋይዳ ያለው በመሆኑ የተጀመረውን ድህነት ቅነሳ ፕሮግራም ተግባራዊ ለማድረግ ትልቅ ፋይዳ እንዳለውም ጠቁመዋል።የድህነት ቅነሳ መተግበር ሲጀምር የነበረው አጠቃላይ አገራዊ የምርት መጠን 69 ሚሊዮን ኩንታል ብቻ ሲሆን በሁለተኛው 181 ሚሊዮን ኩንታል፣ በሦስተኛው ደግሞ 270 ሚሊዮን ኩንታል መድረሱን የጠቆሙት ሚኒስትር ዴኤታው፤ ዘንድሮ ደግሞ 414 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ይገኛል ተብሎ እንደሚታሰብና ይህም የምርት አሰባሰብ ሂደቱ በየጊዜው በከፍተኛ ሁኔታ እያደገ መሄዱን ማሳያ ነው ብለዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 27/2013
https://www.press.et/Ama/?p=38881
256
0ሀገር አቀፍ ዜና
አጫጭር ዜናዎች
ስፖርት
May 19, 2020
20
የደብረ ብርሃን አትሌቲክስ ማሰልጠኛ ማዕከል በርካታ ምርጥ አትሌቶችን የማፍራት ጉዞ የደብረ ብርሃን አትሌቲክስ ማሰልጠኛ ማዕከል በአማራ ክልል ከሚገኙ ዞኖች የመመልመያ መስፈርቱን አሟልተው የተገኙ አትሌቶችን ወደ ማዕከሉ በማስገባት ማሰልጠን የጀመረው በ2002 ዓ.ም። ማዕከሉ እስከአሁንም ከ360 በላይ አትሌቶችን አሰልጥኖ አብቅቷል። የማዕከሉ ዋና ዓላማ በክልሉ የተሻሉና ወደ ፊትም የተደራጀና ሳይንሳዊ ስልጠና ቢያገኙ ውጤትማ ሊሆኑ ይችላሉ ተብሎ የሚታመንባቸውንና የማዕከሉን የመምረጫ መስፈርት አሟልተው የተገኙ ወጣቶችን እያሰለጠነ ክልሉን እና ሀገርን የሚወክሉ አትሌቶችን ማፍራት ነው። ይህንንም መሰረት በማድረግ ማዕከሉ ስልጠና መስጠት ከጀመረበት ከ2002 ዓ.ም ጀምሮ ለአስር ተከታታይ ዓመታታ በተሰጠ ስልጠና በርካታ ምርጥ አትሌቶችን ማፍራት መቻሉ ተነግሯል። በማዕከሉ 360 አትሌቶች ስልጠናውን መውሰዳቸው የተገለጸ ሲሆን ከዚህ ውስጥም 117 አትሌቶች ወደ ከፍተኛ ክለቦች ገብተዋል፤ 49 አትሌቶች ወደ ብሄራዊ ቡድኑ መግባት ችለዋል፤ 16 አትሌቶች ሀገራቸውን በመወከል በተለያዩ ዓለም አቀፍ ውድድሮች ላይ በመሳተፍ ከፍተኛ ውጤት አስመዝግበዋል ተብሏል። የአውሮፓ ቡድኖች እስከ 4 ነጥብ 2 ቢሊየን ዶላር ኪሳራ ሊያጋጥማቸው ይችላል ተባለ የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ በአውሮፓ ታላላቅ ሊጎች የሚጫወቱ የእግር ኳስ ቡድኖችን እስከ 4 ነጥብ 2 ቢሊየን ዶላር ድረስ ሊያሳጣቸው እንደሚችል ተገምቷል። ነገሮችን ለቡድኖቹ ይበልጥ አሳሳቢ የሚያደርገው ደግሞ ሊጎቹ እንደምንም ተብሎ ቢጠናቀቁ እንኳ ይህን ኪሳራ ማስቀረት አለመቻላቸው ነው። ሊጎቹ በታሰበላቸው ጊዜ መጠናቀቅ የማይችሉ ከሆነ ደግሞ ኪሳራው እስከ 7 ነጥብ 5 ቢሊየን ዶላር ከፍ ሊልም ይችላል። የጀርመን ቡንደስሊጋ ትናንት የተጀመረ ሲሆን የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ ደግሞ በሚቀጥለው ወር አጋማሽ አካባቢ እንደሚጀመር ይጠበቃል። ፈረንሳይ ደግሞ ሊጓን ያቋረጠች ሲሆን የደረጃ ሰንጠረዡን ሲመራ የነበረው ፓሪስ ሴይንት ጀርሜይን አሸናፊ ተብሎ ዋንጫውን አንስቷል። በመላው አውሮፓ የሚገኙ ሊጎችም ይህን ያክል ገንዘብ ላለማጣት ሲሉ ሊጎቻቸውን በተቻለ መጠን ለማስጀመር እየተሯሯጡ ይገኛሉ። ነገር ግን በዚህ መሀል የተጫዋቾች ደህንነት እንዳይረሳ የሚያሳስቡም አልጠፉም።አዲስ ዘመን ግንቦት 11/2012
https://www.press.et/Ama/?p=32684
247
2ስፖርት
የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን የ20 ሚሊዮን ብር የሕዳሴ ግድብ ቦንድ ገዛየፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን የ20 ሚሊዮን ብር የሕዳሴ ግድብ ቦንድ ገዛ
ሀገር አቀፍ ዜና
January 5, 2021
9
– ለግድቡ በአምስት ወራት ከ888  ሚሊዮን ብር በላይ ተሰብስቧልበጋዜጣው ሪፖርተር አዲስ አበባ፡- የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታን ለማገዝ የ20 ሚሊዮን ብር የቦንድ ግዥ ፈፀመ። የቦንድ ግዢው የግድቡን ግንባታ ለማጠናቀቅ የኅብረተሰቡ ተሳትፎ እንዲያድግ መንግሥት ያደረገውን ጥሪ ተከትሎ የተደረገ መሆኑን ትናንት በተደረገው የርክክብ ሥነ ሥርዓት ላይ ተገልጿል። የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽንን በመወከል ቼኩን ለታላቁ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ሕዝባዊ ተሳትፎ አስተባባሪ ምክር ቤት ያስረከቡት ዋና ሥራ አስፈጻሚው አቶ ረሻድ ከማል ናቸው። የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ረሻድ ከማል በርክክቡ ወቅት እንደገለጹት፤ የፌደራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ለተለያዩ ሀገራዊ ልማት ፕሮጀክቶች ድጋፍ እያደረገ መሆኑን አስታውሰው፤ ለኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ የሚያደርገውን ድጋፍ በልዩ ሁኔታ በመመልከት ሰፊ ተሳትፎ እያደረገ መሆኑን ጠቁመው፤ ይህንንም አጠናክሮ እንደሚቀጥል የኢትዮጵያ ህዝብ ሀብት የሆነው የህዳሴው ግድብ እስኪጠናቀቅ ድረስ ኮርፖሬሽኑ ታሪካዊ አሻራውን ማኖሩን አበክሮ ይቀጥላል።ኮርፖሬሽኑ ከዚህ ቀደም ባደረጋቸው የገንዘብ አስተዋጽኦዎች ለገበታ-ለሀገር ፕሮጀክት 20ሚሊዮን ብር፣ ለመቄዶኒያ የአረጋዊያን መኖሪያ ግንባታ 5 ሚሊዮን ብር፣ የ COVID-19 ስርጭትን ለመከላከል እየተደረገ ላለው ሀገራዊ ርብርብ 10 ሚሊዮን ብር፣ ባለፉት 6 ወራት የኮርፖሬሽኑ ተከራይ ደንበኞች 50% የቤት ኪራይ ክፍያ እንዲቀነስላቸው በማድረግ 400 ሚሊዮን ብር ድጋፍ የተደረገ ሲሆን፤ ለገበታ-ለሃገር የተሰጠውን 20 ሚሊዮን ብር ጨምሮ በድምሩ 455 ሚለዮን ብር ገደማ ወጪ በማድረግ ኮርፖሬሽኑ ማህበራዊ ኃላፊነቱን በመወጣት ላይ እንደሚገኝም አቶ ረሻድ ጠቁመዋል።የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ሕዝባዊ ተሳትፎ አስተባባሪ ብሔራዊ ምክር ቤት ጽ/ቤት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አረጋዊ በርሔ በበኩላቸው፤ የሕዳሴ ግድብ ለሀገሪቱ ሁለንተናዊ ለውጥ ወሳኝ ነው ብለዋል። ኮርፖሬሽኑ ያደረገው ድጋፍ ለሌሎች ተቋማት አርአያ የሚሆን ተግባር እንደሆነ የጠቆሙት ዶክተር አረጋዊ፤ ሁሉም ተቋማትና ዜጎች ተሳትፎአቸውን በማሳደግ ግድቡን ለማጠናቀቅ የሚደረገውን ርብርብ እንዲደግፉም ጥሪ አቅርበዋል።ባለፉት አምስት ወራት ብቻ መላ ኢትዮጵያውያን በአገር ውስጥና በውጪ ከ790 ሚሊዮን ብር በላይ የቦንድ ግዥ ድጋፍ ማደረጋቸውንና በ8100 የገቢ ማስገኛ ፕሮግራምም ከ98 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ መገኘቱን የግድቡ ግንባታ ህዝባዊ ተሳትፎ ማስተባበሪያ ምክር ቤት ጽ/ቤት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ፍቅርተ ታምር ገልጸው፤ ይህም በግድቡ ግንባታ ታሪክ ከፍተኛ አስተዋጽኦ መሆኑን አስታውቀዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 27/2013
https://www.press.et/Ama/?p=38880
289
0ሀገር አቀፍ ዜና
የብሔራዊ ኦሊምፒክ ኮሚቴዎች ማህበር ጠቅላላ ጉባዔ ተራዘመ
ስፖርት
May 20, 2020
21
በመጪው ጥቅምት ወር በደቡብ ኮሪያ ሴኡል ከተማ ሊካሄድ የነበረው የብሔራዊ ኦሊምፒክ ኮሚቴዎች ማህበር ጠቅላላ ጉባዔ በኮሮና ቫይረስ ስጋት መራዘሙ ታውቋል። የሁሉም አገራት ብሔራዊ ኦሊምፒክ ኮሚቴዎች የሚሳተፉበት ወሳኝ ጠቅላላ ጉባዔ በመጪው ጥቅምት አጋማሽ ለሁለት ቀናት እንደሚካሄድ ቀጠሮ ተይዞለት ነበር። የብሔራዊ ኦሊምፒክ ኮሚቴዎቹ እንዲሁም ጠቅላላ ጉባዔውን የምታዘጋጀው ደቡብ ኮሪያ የስፖርትና ኦሊምፒክ ኮሚቴ በጋራ በሰጡት መግለጫ ጠቅላላ ጉባዔው የተራዘመው በሁሉም ባለድርሻ አካላት ፍላጎት መሆኑ ታውቋል። እኤአ የ1988 ኦሊምፒክ የሆነችው ሴኡል ከተማ ይህን ታላቅ ጠቅላላ ጉባዔ በመጪው 2021 የፈረንጆች ዓመት እንደምታስተናግድ ይገለፅ እንጂ መቼ እንደሆነ ቁርጥ ያለው ቀን አልተነገረም። ጠቅላላ ጉባዔው የሚካሄድበት እርግጠኛው ቀን ወደ ፊት እንደሚገለፅም ተጠቁሟል። ብሔራዊ ኦሊምፒክ ኮሚቴዎቹ ወሳኝ በሆነው ጠቅላላ ጉባዔ ሃሳባቸውን እንዲያቀርቡ በማህበሩ በኩል ሪፖርቶችና አጀንዳዎች ቀደም ብሎ ተሰጥቷቸው ነበር።‹‹ጠቅላላ ጉባዔው በተያዘለት ጊዜ ባለመካሄዱ ቅር ተሰኝተናል፣ ይሁን እንጂ ዓለም አሁን ካለችበት ወቅታዊ ችግር አኳያ ጠቅላላ ጉባዔውን ማራዘማችን ትክክለኛ ውሳኔ ነው›› በማለት የማህበሩ ፕሬዚዳንት ተወካይ ሮቢን ሚሼል ለዓለም መገናኛ ብዙሃን በተሰራጨው መግለጫ ሃሳባቸውን አስቀምጠዋል። የፕሬዚዳንቱ ተወካይ አክለውም፣ ጠቅላላ ጉባዔውን ለማስተናገድ በዝግጅት ላይ የነበሩት የደቡብ ኮሪያ ስፖርትና ኦሊምፒክ ኮሚቴ የሥራ ኃላፊዎች ስብሰባውን በታቀደለት ጊዜ ለማስተናገድ ያደረጉትን ጥረትና ስብሰባው ይራዘም ሲባል ሃሳቡን ለመቀበል ላሳዩት ቅንነት ምስጋና አቅርበዋል። በቀጣይም ጠቅላላ ጉባዔው እዚያው ሴኡል ከተማ እንዲካሄድ ከአገሪቱ የስፖርት ኃላፊዎች ጋር ተቀራርበው እንደሚሰሩ ቃል ገብተዋል። በኮሮና ቫይረስ ፈጣን ስርጭት የተነሳ በርካቶቹ የዓለማችን አገራት የዜጎቻቸውን እንቅስቃሴ ከመግታት ጀምሮ ዓለም አቀፍ ጉዞዎች ላይ እገዳ እንደጣሉ ይታወቃል። የደቡብ ኮሪያ ስፖርትና ኦሊምፒክ ኮሚቴ ፕሬዚዳንት ሊ ኪ ሁንግ በጠቅላላ ጉባዔው የሚሳተፉ የተለያዩ አገራት የስፖርት ልዑካን ቡድን አባላት የጤናና ደህንነት ሁኔታን ከግምት በማስገባት ሁሉም ባለድርሻ አካላት በተስማሙት መሰረት ስብሰባው እንዲራዘም መደረጉን ገልፀዋል። ጠቅላላ ጉባዔውን በተራዘመው መርሐግብር መሰረት ለማስተናገድም አገራቸው ፍቃደኛ መሆኗን ተናግረዋል። ‹‹ዓለም አሁን የገጠማት ችግር የኦሊምፒክ እንቅስቃሴን ያስቆማል የሚል እምነት የለንም›› ያሉት ፕሬዚዳንቱ በቀጣይ የዓለማችን ስፖርት እጣፋንታ ላይ የሚወስኑ የሁለት መቶ ስድስት አገራት ብሔራዊ ኦሊምፒክ ኮሚቴዎችን ልዑካ ቡድን አባላት ለመቀበልና የተሳካ ጠቅላላ ጉባዔ ለማድረግ እንደሚዘጋጁም ቃል ገብተዋል። ከዚህ ቀደም የብሔራዊ ኦሊምፒክ ኮሚቴዎች ማህበር ጠቅላላ ጉባዔ የሚካሄደው በማህበሩ ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት መካከል እንዲሁም በማህበሩ የሥራ ባልደረቦች መካከል ነበር። በዚህ ጠቅላላ ጉባዔ እኤአ ከ2014 ወዲህ ማህበሩ ጠቅላላ ጉባዔውን በሚያካሂድበት ከተማም ትልቅ ዓመታዊ የሽልማት ሥነሥርዓት እንደሚያደርግ ይታወቃል። የዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ፕሬዚዳንቶች በዚህ ጠቅላላ ጉባዔ ተገኝተው ንግግር የሚያደርጉም ሲሆን በዓለማችን ስፖርቶች እንዲሁም ታላላቅ ዓለም አቀፍ ውድድሮች ዙሪያ ምክክር ይደረግበታል። ማህበሩ ባለፈው ዓመት ኳታር ዶሃ ላይ ባደረገው ጠቅላላ ጉባዔ የማህበሩ ፕሬዚዳንት ሼክ አሕመድ አል ሳባህ የፍርድ ሂደት መቋጫ እስኪያገኝ ድረስ ሮቢን ሚሼል የማህበሩ ፕሬዚዳንት ተወካይ ሆነው እንዲያገለግሉ መወሰኑ ይታወቃል። ባለፈው ወር ለሁለተኛ ጊዜ የሚካሄደው የብሔራዊ ኦሊምፒክ ኮሚቴዎች የባህር ዳርቻ የስፖርት ውድድሮች በኮሮና ቫይረስ ስጋት እኤአ እስከ 2023 እንዲራዘም መወሰኑ አይዘነጋም። የዓለምን ኢኮኖሚያዊ፣ማህበራዊና ፖለቲካዊ ነባራዊ ሁኔታ ወደተለየ አቅጣጫ ያዞረው የኮሮና ቫይረስ ስርጭት በስፖርቱ ዓለም ያሳደረው አሉታዊ ተፅዕኖ ተዘርዝሮ የሚያልቅ አይደለም። አንዳች ውድድር በዓለም ላይ እንዳይኖር ከማስገደድ ባለፈ የስፖርቱን ዓለም ሽባ አድርጎታል። ብዙ ታቅዶባቸው፣ብዙም ተለፍቶባቸው ለዓመታት በዝግጅት ላይ የነበሩ ዓለም አቀፍ ውድድሮች በትልቅ ኪሳራ የሚካሄዱበት ጊዜ እንዲራዘም ግድ ብሏል። ጃፓን ካለፉት ሰባት ዓመታት በላይ ከፍተኛ ዝግጅት ስታደርግበት የቆየችው የቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ በትልቅ ኪሳራ ለአስራ ስድስት ወራት የተራዘመና በጉጉት ሲጠበቅ የነበረ ታላቅ የስፖርት መድረክ ነው። ይህን ታላቅ የስፖርት መድረክ ዓለም አቀፉ የኦሊምፒክ ኮሚቴ እየተናነቀውም ቢሆን ለ2021 ለማራዘም ተገዷል። ኦሊምፒኩን ጨምሮ በርካቶቹ ዓለም አቀፍ የስፖርት ውድድሮችና ጉባዔዎች ወደ ቀጣይ ዓመት የተሸጋገሩት የኮሮና ቫይረስ ስርጭት በቁጥጥር ስር ይውላል በሚል ተስፋ ነው። ይሁን እንጂ በዓለም ላይ አሁን ያለው ነባራዊ ሁኔታ ከተስፋ በስተቀር የቫይረሱ ስርጭት በጊዜ የሚገታ ወይም ፈውስና ክትባት በዚህ ጊዜ እውን ይሆናል የሚያስብል እንዳልሆነ መታዘብ ይቻላል። ይህንን ከግምት ያስገቡት የቶኪዮ ኦሊምፒክ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ቶሺሮ ሙቶ ኦሊምፒኩ የቫይረሱን ስጋት ለማምለጥ በአሥራ ስድስት ወራት ቢራዘምም ከቫይረሱ ተፅዕኖ ሊያመልጥ እንደማይችል ሰሞኑን በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ማመልከታቸው ይታወሳል።አዲስ ዘመን ግንቦት 12/2012
https://www.press.et/Ama/?p=32747
559
2ስፖርት
ከአካላዊ ውድድር የተነጠለው ስፖርት በቴክኖሎጂ ተጠናክሯል
ስፖርት
May 25, 2020
16
ስፖርት የማይካተትበት ዘርፍ የለም፤ ቴክኖሎጂም እንዲሁ።ሁለቱም ዘርፎች በማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊ እንዲሁም ሌሎች ጉዳዮች ጋር በመቆራኘት ህይወትን በማቅለል ለዘመናዊው ዓለም የጎላ ሚና በመጫወት ላይ ይገኛሉ።ከዚህ ባለፈ አንዱ ለሌላኛው ቁልፍ ጉዳይ መከወኑም አልቀረም።በልምድ ይካሄድ የነበረው ስፖርት በሳይንስና ቴክኖሎጂ በመደገፉ፤ ዘመናዊውን ስፖርት ከሳይንስና ቴክኖሎጂ ለይቶ ማሰብ በዚህ ወቅት አዳጋች ሆኗል።በቴክኖሎጂ የታገዙ ፈጠራዎች መበራከትም የስፖርተኞችን ብቃት በማሳደግ እንዲሁም የስልጠና ሂደቱን በማቃለልም ዘርፉን ትርፋማ ማድረግ ችሏል።የዘመኑ ስትንፋስ የሆነው ቴክኖሎጂ በ19ኛው ክፍለ ዘመን ስፖርትን ተቀላቅሎ በቁጥር የማይተመኑ ለውጦችን አስገኝቷል።በስፖርት ትጥቅና የስልጠና ቁሳቁስ፣ ውድድሮችን በቀጥታ ለደጋፊዎች በማስመልከት፣ በውድድር ሜዳዎች ተገኝቶ ለመመልከት ትኬት የመቁረጫ አማራጭ፣ የስፖርት ሜዳዎች ሁለገብና ዘመናዊ እንዲሆኑ፣ ከውድድር አጨራረስ እንዲሁም ዳኝነት፣ የስፖርተኞችን መረጃና ውጤትን በመመዝገብ፣ ከዚህ ቀደም የነበረን ውድድርና ብቃት ለመገምገም፣ ስለ ስፖርቱ የሚወጡ አዳዲስ መረጃዎችን ለመከታተል፣ ስፖርተኞችን ከደጋፊዎቻቸው በማገናኘት፣ ንጹህ ስፖርትን ለማካሄድና በስፖርት የሚፈጸሙ የረቀቁ ወንጀሎችን ለማጣራት (ከአበረታች ቅመሞች ጋር በተያያዘ)፣ ከጉዳት ለማገገም (ስፖርት ህክምና)፣ በትልልቅ ጨዋታዎችና ውድድሮች ከአየር ሁኔታ ጋር በተያያዘ ችግር እንዳይገጥም እንዲሁም ዘርፈ ብዙ ግኝቶችንም አበርክቷል። በዋናነት እነዚህ ተጠቀሱ እንጂ ቴክኖሎጂ በእያንዳንዱ ስፖርት ለእያንዳንዱ ሂደት እየተወጣ ያለው አስተዋጽኦ ይዘርዘር ቢባል አዳጋች ነው የሚሆነው።ለአብነት ያህል ግን ባለፈው የፈረንጆቹ ዓመት በጉልህ ከታዩ የቴክኖሎጂ ውጤቶች መካከል በሁለት ተወዳጅ ስፖርቶች የታዩትና የስፖርት ቤተሰቡን ቀልብ የሳቡትን ማንሳት ይቻላል።በአትሌቲክስ ስፖርት በመሮጫ ጫማ ላይ የነበረው የቴክኖሎጂ እገዛ የሰው ልጅ በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ ማራቶንን ከሁለት ሰዓት በታች በመሮጥ አዲስ ታሪክ እንዲያስመዘግብ አድርጓል።በቪዲዮ የታገዘ ዳኝነት በእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ መተግበሩም እስካሁን በእግር ኳሱ ነጥረው ያልወጡ ጉዳዮች እንዲስተዋሉ ያደረጉ ሆነዋል። የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ 19) ዓለምን በእጅጉ እያስጨነቀ ባለበት በዚህ ወቅት ደግሞ ቴክኖሎጂ ለስፖርቱ እጅጉን አስፈላጊ መሆኑ በተግባር እየታየ ይገኛል።በተለይ ከስፖርታዊ ውድድሮች መሰረዝና ‹‹ከቤት አትውጡ›› ትዕዛዝ ጋር በተያያዘ ስፖርተኞች እንዲሁም ስፖርት ወዳዶች ቴክኖሎጂን እንደ አማራጭ ይዘውታል።የስፖርት መገናኛ ብዙሃን እንዲሁም ድረ ገጾችም የውድድሮች አለመኖርን ተከትሎ ከዚህ ቀደም የተካሄዱ ውድድሮችን በድጋሚ በማስታወስ ላይ ይገኛሉ።ስፖርተኞች በበኩላቸው በግላቸው የሚያደርጓቸውን እንቅስቃሴዎች በተለያዩ ድረ-ገጾች ለሌላው ህዝብ በማጋራት ላይ ናቸው።አሰልጣኞችም ስፖርተኞች በቤታቸው ሲቆዩ እንዳይዘናጉ በተለያዩ ቴክኖሎጂ አፈራሽ መንገዶች ስልጠናቸውን ቀጥለዋል።የውድድር አዘጋጅ አካላት ደግሞ በአካል ስፖርተኞችን ማፎካከር ባይችሉም በስልኮች ላይ በሚጫን መተግበሪያ ውድድሮችን እያካሄዱ ይገኛሉ።የ ‹‹በቤት ቆዩ›› ቻሌንጆችም በዓለም ላይ እየተበራከቱ መሆኑ በግልጽ የሚታይ ነው። ይህ ሁኔታ በኢትዮጵያም እየተለመደ ያለ ሲሆን፤ ስፖርተኞች፣ ባለሙያዎች፣ የስፖርት ማህበራት እንዲሁም ስፖርቱን የሚመሩ አካላት የብዙሃን መገናኛዎችንና ድረገጾችን በመጠቀም ህዝቡን ተደራሽ እያደረጉ ናቸው።አሰልጣኞችም በማህበራዊ ድረ-ገጾች ከሰልጣኞቻቸው ጋር ግንኙነት ያደርጋሉ። የስፖርትና የስልጠና ባለሙያዎችም የአካል ብቃት እንቅስቃሴ እንዴት እንደሚከወን ህብረተሰቡን ግንዛቤ እያስጨበጡና እያነቁም ይገኛሉ።የኢትዮጵያን ስም ከገነኑ አትሌቶች እኩል የሚያስነሳው ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያም በተንቀሳቃሽ ስልክ መተግበሪያ አማካኝነት የሩጫ ውድድር እያካሄደ ይገኛል።‹‹ቨርቹዋል ሬይስ›› የሚሰኘው ይህ የውድድር ዓይነት እየተለመደ ያለና በርካቶች ተሳታፊ እየሆኑበትም ይገኛሉ፡፡በወቅታዊው ሁኔታ ስፖርት ለጊዜውም ቢሆን ከአካላዊ እንቅስቃሴ ጋር መለያየቱን ተከትሎም ከስፖርት ቴክኖሎጂ ጋር በተያያዘ የሚሰሩ ድርጅቶች ገበያቸው እየደራ መሆኑም ተስተውሏል።ፎርብስ በዚህ ጉዳይ ላይ የሰራው ዘገባ፤ ስፖርተኞች በቤት ውስጥ ከመቆየታቸው ጋር በተያያዘ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ መከወኛ መሳሪያዎች ፍላጎትና ግዢ ጭማሪ አሳይቷል።በእንግሊዝ የሚገኝ አንድ የስፖርት ቁሳቁስ አምራች ከድረ-ገጹ ጋር በነበረው ቆይታ፤ ባለፉት ሁለት አስርት ዓመታት ባልታየ መልኩ የፈረንጆቹ 2020 ከገባ በኋላ ጥያቄው መበርታቱን ጠቁሟል።በተለይ የኦሊምፒክ ተሳታፊ አትሌቶች፣ ቡድኖች እና ታዋቂ አትሌቶች ደግሞ ቀዳሚ ፈላጊዎች መሆናቸው ታውቋል። ዘ ኢኮኖሚክስ ደግሞ የዓለም ስፖርት በኮሮና ቫይረስ ምክንያት በወራት ውስጥ ከአካላዊ እንቅስቃሴ ወደ ዲጂታል (በቴክኖሎጂ የታገዘ) መቀየሩን አመላክቷል።ይህ ‹‹ኢ-ስፖርት›› የተሰኘው ውድድር በኮምፒዩተር የሚካሄድ ሲሆን፤ ከፍተኛ መጠን ያለው ገንዘብ የሚያሸልም ነው።በዚህም ምክንያት የተሳታፊዎቹ ቁጥር በእጥፍ እያደገ መሆኑ ተረጋግጧል።ቁጥራዊ መረጃዎች እንደሚያሳዩት ከሆነም፤ እአአ በ2019 የተሳታፊዎች ቁጥር 443 ሚሊዮን የደረሰ ሲሆን፤ ይህም ከ2018 ጋር ሲነጻጸር በ12 ከመቶ ጭማሪ ያሳየ ነው።በዚህ ዓመት ደግሞ በዚህ ጨዋታ ተሳታፊ ከሆኑ ሰዎች አንድ ቢሊዮን ዶላር ገቢ መገኘቱም ታውቋል።አዲስ ዘመን ግንቦት 17/2012 ብርሃን ፈይሳ አጫጭር ዜናአትሌቷ እርዳታ አድርጋለች ኢትዮጵያን በኦሊምፒክ፣ በዓለም ቻምፒዮና፣ በዳይመንድ ሊግ እንዲሁም በሌሎች ውድድሮች በ5 እና 10 ሺ ሜትሮች የሜዳሊያ ባለቤት ያደረገችው አትሌት አልማዝ አያና እርዳታ አድርጋለች።አትሌቷ ከባለቤትዋ ጋር በመሆን ከአሁን በፊት የጀመረችውንና ከ30 በላይ የሚሆኑ አቅመ ደካማ አዛውንቶችን ለሁለተኛ ጊዜ የለገሰች ሲሆን፤ ከ50 ለማያንሱ ገቢያቸው አነስተኛ ለሆነና ወደፊት ሀገራቸውን ሊያስጠሩ ለሚጥሩ አትሌቶችም እርዳታውን ማበርከቷን የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በድረ ገጹ አስነብቧል።ተረጂዎች እያንዳንዳቸው እንዳንድ ካርቶን ፓስታ፣ 5 ሊትር ዘይት እና 50 ኪሎ ዱቄት አግኝተዋል።ከዚህ ባሻገር የኮሮና ወረርሽኝን (ኮቪድ 19) ለመዋጋት በሚደረገው ጥረት የሚውል 150 ሺህ ብር ለድጋፍ አስተባባሪው አምባሳደር ምስጋኑ አረጋ አስረክበዋል።አትሌቷ በጥቅሉ 267ሺ ብር እርዳታ ነው ያደረገችው።ሁለተኛ ዙር የምገባ መርሃ ግብር ተጀመረ የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን፣ ከኢትዮጵያ አትሌቲክስና እግር ኳስ ፌዴሬሽኖች እንዲሁም ቢጂአይ ጋር በመሆን ለአንድ ወር የሚቆይ የምገባ መርሃ ግብር ማካሄዳቸው የሚታወስ ነው።አሁን ደግሞ ለአንድ ወር የሚቆይና በአዲስ አበባ ስቴድዮም ዙሪያ የሚገኙ ችግረኞችን የሚያቅፍ ሁለተኛ ዙር የምገባ መርሃ ግብር በይፋ ተጀምሯል።ምገባውን የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን፣ ከኢትዮጵያ አትሌቲክስና እግር ኳስ ፌዴሬሽኖች፣ ከኢትዮጵያ ጸረ አበረታች ቅመሞች ጽህፈት ቤት፣ ከወጋገን ባንክ፣ ከቢጂአይ ኢትዮጵያ እና ከአቶ አብነት ገብረመስቀል ጋር በመተባበጀር የሚካሄድ መሆኑም ታውቋል። የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ በቀጣዩ ወር ይመለሳል በኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት የተቋረጡ የሊግ ውድድሮች እየተመለሱ መሆኑ ይታወቃል።ከእነዚህ መካከል አንዱ የሆነው ተወዳጁ የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግም በቀጣዩ ወር የሚቀጥል መሆኑን ቢቢሲ አስነብቧል።ባሳለፍነው ሳምንት መጀመሪያ ልምምድ የጀመሩት ክለቦቹ ከ17 ቀናት በኋላ ውድድር የሚጀምሩ መሆኑን የፕሪምየር ሊጉ ዋና ስራ አስፈጻሚ ሪቻርድ ማስተር አረጋግጠዋል።በሊጉ ከሚሳተፉ 20 ክለቦች ውስጥ ባሉ ተጫዋቾች በተደረገው የኮቪድ 19 ምርመራ በሶስት ክለቦች ውስጥ የሚገኙ ስድስት ተጫዋቾች ላይ መገኘቱም የሚታወስ ነው።አዲስ ዘመን ግንቦት 17/2012
https://www.press.et/Ama/?p=33056
768
2ስፖርት
የሦስት አስርት ዓመታት የቁልቁለት ጉዞ
ስፖርት
May 24, 2020
30
ኢትዮጵያ በዘመናዊ ስፖርቶች በዓለም መድረኮች መታየት ከጀመረች ከግማሽ ምዕተ ዓመት በላይ ተቆጥሯል። በእነዚህ ዓመት አገሪቱን ሦስት የተለያዩ መንግሥታት መርተዋታል። አንድ መንግሥት የሚከተለው ርዮተ ዓለም በአንድ አገር ላይ ፖለቲካዊና ማህበራዊ ተጽዕኖ የማሳደሩን ያህል በአንድ አገር ስፖርት ላይም የራሱ የሆነ አሉታዊና አዎንታዊ ተጽዕኖዎችን ማሳረፉ የግድ ነው። አንድ የፖለቲካ ስርዓት በስፖርቱ ላይ ብቻም ሳይሆን የስፖርቱ ዋና ተዋናይ የሆነው ግለሰብ ላይም ተመሳሳይ ተፅዕኖ እንደሚያሳርፍ እርግጥ ነው። የአንድ አገር የፖለቲካ ስርዓት በዲፕሎማሲ፤ በኢኮኖሚ፤ ልማትና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ያለው ነባራዊ ሁኔታ በቀጥታና በተዘዋዋሪ ስፖርቱንና ስፖርተኛውን መንካቱ አይቀሬ ነው። ባለፉት ሦስት አስርት ዓመታት ገደማ አገራችን የምትከተለው የፖለቲካ ስርዓት በአገሪቱ ስፖርት ላይ የተለያዩ አዎንታዊና አሉታዊ ጎኖችን ማሳደሩ አልቀረም። ባለፉት ሦስት አስርት ዓመታት የነበረው የፖለቲካ ስርዓት ለአገራችን ስፖርት ካበረከታቸው አዎንታዊ ጎኖች አንዱ ከዲፕሎማሲ እውነታዎች አኳያ ይቀኛል። አገራችን ባለፉት ሦስት አስርት ዓመታት ከሌሎች አገሮች ጋር ያላትን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት በላቀ መልኩ ማሻሻሏ የሚካድ አይደለም። ይህም በዓለም አቀፍ የስፖርት መድረኮች በተለይም መል ካም ስም ባላት የአትሌቲክስ ስፖርት ኦሊምፒክንና የዓለም ቻምፒዮናን በመሳሰሉ ታላላቅ መድረኮች የነቃ ተሳትፎ እንዲኖራት የራሱን የሆነ አስተዋፅኦ አበርክቷል። ኢትዮጵያ እኤአ ከ1956 ከሜልቦርን ኦሊምፒክ ጀምሮ በኦሊምፒክ መድረኮች ተሳታፊ መሆን ችላለች። ከእዚህ ጊዜ አንስቶ አስራ ሰባት ያህል ኦሊምፒኮች ቢካሄዱም ኢትዮጵያ በሁለቱ ተካፋይ መሆን አልቻለችም ነበር። እኤአ በ1984 አሜሪካ ሎሳንጀለስ ባስተናገደችው የኦሊምፒክ ጨዋታ ኢትዮጵያ በወቅቱ የሶሻሊዝም ርዮተ ዓለም ተከታይ ከመሆኗ ጋር ተያይዞ በእዚህ ታላቅ መድረክ መካፈል አልቻለችም ነበር። ከአራት ዓመት በኋላም 1988 ላይ የአፓርታይድ ስርዓትን በመቃወም በሲዎል ኦሊምፒክ ላይ አልተገኘችም። ኦሊምፒክን በመሳሰሉ ታላላቅ የስፖርት መድረኮች በፖለቲካ ርዮተ ዓለም ልዩነት የተነሳ መካፈል አለመቻል አንድን አገር ከሜዳሊያ በዘለለ በርካታ ነገሮች እንደሚያሳጣ አያከራክርም። ባለፉት ሦስት አስርት ዓመታት ኢትዮጵያ በሁሉም የኦሊምፒክና የዓለም ቻምፒዮናዎች ላይ ቀርታ አታውቅም። በእነዚህ ታላላቅ የስፖርት መድረኮች ሜዳሊያ ከመሰብሰብ ባሻገር መድረኩን ተጠቅማ ገፅታዋን ለመገንባትና ራሷን ለማስተዋወቅ ጠቅሟታልም። በእነዚህ መድረኮች የዘወትር ተሳታፊ መሆኗም የአገሪቱን ስፖርት እንዲነቃቃና ስፖርተኛው ተጠቃሚ እንዲሆን አስችሏል። አንድ ስፖርተኛ ራሱን በኦሊምፒክ መድረክ በማሳየት ዓለም አቀፍ ተጠቃሚነትን እንዲያገኝ ከሌሎች አገራት ጋር ያለን መልካም የሆነ የዲፕሎማሲ ግንኙነት እዚህ ጋር ቁልፍ ሚና እንዳለው መገንዘብ ይቻላል። ስፖርተኞቻችን የግል ውድድራቸውን በሌሎች አገሮች ለማድረግ ወደ አንድ አገር በቀላሉ ለመግባት መልካም የዲፕሎማሲ ግንኙነት የሚኖረው አስተዋፅኦ ግልፅ ነው። ይህም ስፖርተኞች በተለይም አትሌቶቻችን በተለያዩ ዓለማት ተዟዙረው በስፖርቱ ያላቸውን ተሰጥኦ ተጠቅመው ከራሳቸው አልፈው ለሌሎች ወገኖችና ለአገር ሲተርፉ እንድንመለከት አድርጓል። እዚህ ላይ የአገራችን አቪዬሽን ዘርፉ መዘመንና በበርካታ አገሮች ተደራሽ መሆን ለአትሌቶቻችን እንደ ልብ የፈለጉት አገር በረው የትራንስፖርት ጉዳይ ሳያሳስባቸው ጊዜና ገንዘባቸው ሳይባክን ውድድሮች ላይ እንዲገኙ ማስቻሉ መንግሥት በትራንስፖርት ልማቱ ያከናወነውን ተግባር ዋጋ እንድንሰጠው እንገደዳለን። ስፖርት በዘመናችን ከፍተኛ የገቢ ምንጭ በሆነበት በእዚህ ወቅት አትሌቶቻችን በሌሎች አገሮች ላባቸውን አፍሰው ያመጡትን ገንዘብ አገራቸው ላይ ሠርተው እንዲለወጡበት መንግሥት ቅድሚያ ሰጥቷቸው ሁኔታዎችን በማመቻቸት ወደ ኢንቨስትመንቱ እንዲገቡ አድርጓል። በእዚህም በርካታ አትሌቶቻችን በሆቴልና ሪዞርት እንዲሁም በሌሎች የኢንቨስትመንት ዘርፎች ግንባር ቀደም ተዋናይ ሆነው እናገኛቸዋለን። ይህም ሁኔታ ስፖርተኞቻችን ወደ አደጉት አገራት ለውድድር ወጥተው ከመቅረት ይልቅ ያገኙትን ይዘው ተመልሰው ከራሳቸው አልፈው ለበርካታ ዜጎት እንጀራ ሲከፍቱ እንድንመለከት አድርጓል። ስፖርታዊ እንቅስቃሴ ማድረግ የአንድ ህብረተሰብን አካላዊ እና ስነ ልቦናዊ ጤንነትን በመጠበቅ ረገድ ምርታማነትን የሚያጎለብት፥ ለማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እድገት ቁልፍ ሚና ያለው የዜጎች መሰረታዊ መብት እየሆነ መጥቷል። ይህን ልብ ያለው የ1990 ዓ.ም የተቀረፀው የኢትዮጵያ ብሔራዊ የስፖርት ፖሊሲ በየደረጃው መላውን ህብረተሰብ በስፖርት በማሳተፍ ተተኪ ስፖርተኞችን ማፍራት ቀዳሚ ዓላማው አድርጎታል። ለዚህም መላው ህብረተሰብ በሚኖርበት፥ በሚሠራበት እና በሚማርበት አካባቢ በስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች ተሳታፊና ተጠቃሚ እንዲሆን ለማስቻል በየደረጃው ምቹ ሁኔታዎችን የመፍጠር ግልፅ አቅጣጫ አስቀምጧል። የዚህን ፖሊሲ አቅጣጫ ስኬታማ በሆነ መልኩ ተፈፃሚ ለማድረግ የመላ ኢትዮጵያ ጨዋታዎች ፅንሰ ሃሳብ ለመጀመሪያ ጊዜ በ1996 ዓ.ም በወቅቱ በነበረው የኢፌዴሪ ስፖርት፤ ባህል እና ቱሪዝም ሚኒስቴር ነበር የተጠነሰሰው። የኦሊምፒክና የመላ አፍሪካ ጨዋታዎችን መርህ መነሻ በማድረግ ህብረተሰቡን በስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች በስፋት በማሳተፍ እና ተጠቃሚነቱን በማጎልበት የበርካታ ባህልና ትውፊቶች ባለቤት የሆኑ ብሔሮችና ብሔረሰቦች በአንድ መድረክ ተገናኝተው የባህል እና ልምድ ልውውጥ እንዲያደርጉ ታስቦ ፖሊሲው እንደተቀረፀ የመጀመሪያው የጥናት ሰነድ ላይ ተቀምጧል። ይህም አገራችን በምትከተለው የፌዴራሊዝም ስርዓት ህዝቦች የእርስ በእርስ ግንኙነታቸውን በማጠናከር በጋራ መግባባት ላይ የተመሰረተ መተሳሰብ እና መቀራረብ አዲሲቷን ኢትዮጵያ ለመገንባት ዘርፈ ብዙ ጥቅም እንዳለው ታምኖበታል። በዚህም የአገራችን ስፖርት ዜጎችን ተጠቃሚ ከማድረግ አኳያ ተስፋ ሰጪ ምልክቶችን ማየት ተችሏል። ዘመናዊና ግዙፍ ስቴድየሞች በየክልሉ መገንባታቸው፤ አገር አቀፍ የታዳጊ ወጣቶች የስፖርት አካዳሚና በተለያዩ ስፖርቶች የወጣት ፕሮጀክቶች መጀመራቸው የአገራችን ስፖርት ባለፉት ሃያ ስድስት ዓመታት የተጓዘባቸው መንገዶች ናቸው። የመላ ኢትዮጵያ ጨዋታዎች ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ለአገሪቱ ትልልቅ መሠረተ ልማቶችን አስገ ኝቷል፡፡ ለውድድሩ ሲባልም ትልልቅ ስታዲየሞች በክልሎች ተገንብተዋል፡፡ በመገንባት ላይም የሚገኙ በርካታ ናቸው፡፡ በባህር ዳር፣ ሐዋሳና መቐለ የተገነቡት ዘመናዊ ስታዲየሞች ከመላ ኢትዮጵያ ጨዋታዎች አልፈው ዓለም አቀፍ ውድድሮችን የሚያስተናግዱ ሆነዋል፡፡ አልፎ ተርፎም ኢትዮጵያ የአፍሪካን ሁለተኛውን ትልቅ የእግር ኳስ ዋንጫ የ2020 አፍሪካን ኔሽን ቻምፒዮን ሺፕ(ቻን) አዘጋጅነት ዕድል እንድታገኝ እነዚህ ስቴድየሞች ካፍን ማሳመን የቻሉበት አጋጣሚ ነበር(ባይሳካም)። ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች በየሁለት ዓመቱ የሚካሄዱትን መላ ኢትዮጵያ ጨዋታዎች ላይ እያሳዩ ያለው ፉክክር ወደ መጋጋል ደረጃ ለመምጣቱ አንዱ ማሳያ፣ ውድድሮችን ለማዘጋጀትና መሠረተ ልማቶችን አሟልቶ ለመገኘት የሚያደርጉት ሽር ጉድ ለዚህ ተጠቃሽ ነው፡፡ በእነዚህ ስቴድየሞች ግንባታ ሂደትም በሺዎች ለሚቆጠሩ ዜጎች የሥራ ዕድል ከመፈጠሩ ባሻገር በግንታው ዘርፍ በቢሊየን የሚቆጠር ገንዘብ ሊንቀሳቀስ ችሏል። በዚህም የአገራችን ተቋራጮችን አቅም ከማሳደጉ በተጨማሪ በዘርፉ ትልቅ የእውቀት ሽግግር ሊደረግ ችሏል። ይሁን እንጂ በእነዚህ ስቴድየሞች ግንባታ በብዙ መልኩ የሚነሱ እንከኖች የሉም ማለት አይደለም፡፡ መላ ኢትዮጵያ ጨዋታም ቢሆን ባለፉት ጥቂት ዓመታት የታለመለትን ዓላማ ስቶ ወዳልተፈለገ እኩይ ተግባር መቀየሩና የፖለቲካ መጠቀሚያ መሆኑ የሚካድ አይደለም፡፡ በእነዚህ ዓመታት በአገራችን ስፖርት ከታዩ አንኳር የሆኑ አሉታዊ ጎኖች ዋነኛው ከአትሌቲክስ ስፖርት ውጪ ሌሎቹ ስፖርቶች መዳከማቸውና እድገት አለማሳየታቸው ይጠቀሳል። ለእዚህም በርካታ ምክኒያቶች ይቀመጣሉ። ቀደም ሲል አንድ ክለብ ሲቋቋም ያደገ ወይንም ተከታይ ያለው ስፖርት ብቻ ይዞ መቋቋም አይችልም። ይህ ማለት አንድ እግር ኳስ ክለብ ለማቋቋም ሌሎች ከአምስት ያላነሱ ስፖርቶችን ማቀፍ የሚያስገድድ ሁኔታ ነበር። ይህም አንድ ስፖርት ብቻ ተነጥሎ እንዳያድግና ሌሎች ያላደጉ ስፖርቶች ተያይዘው እንዲያድጉ የሚያስችል ነበር። አሁን ላይ ይህ ዓይነቱ አካሄድ በመቅረቱ በርካታ ክለቦች የፈለጉትን ስፖርት ብቻ ይዘው በመጓዛቸው በርካታ ስፖርቶች ሲወድቁ እንመለከታለን። ቀደም ሲል ኢትዮጵያ ከአትሌቲክስና እግር ኳስ በተጨማሪ ቮሊቦል፤ ቅርጫት ኳስ፤ እጅ ኳስና ሌሎች ስፖርቶች ከሌሎች አገሮች ጋር ተፎካካሪ ነበረች። አሁን ላይ ይህ ገፅታ ተቀይሮ ከእግር ኳስና አትሌቲክስ ውጪ ባሉት ስፖርቶች እንኳን ወደ ውጭ አገር ሄደን ጠንካራ ተፎካካሪ ልንሆን በአገር ውስጥም ጠንካራ እንቅስቃሴ ሲደረግባቸው ለማየት ተቸግረናል። በስፖርት መሰረተ ልማቶች ትላልቅ ፕሮጀክቶች ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ተግባራዊ እየሆኑ ቢመጡም በአገራችን ስፖርት መሰረት የሆኑ የተለያዩ ማዘውተሪያ ስፍራዎች ሕንፃና ቤት ተሠርቶባቸው እናገኛለን። ይህም በምንታወቅባቸው በተለይም በእግር ኳስ ከተለያዩ አካባቢዎች የሚወጡ ተጫዋቾችን እንድናጣ ማድረጉ በርካታ የስፖርት ቤተሰቦች የሚስማሙበት ነው። በሌላ በኩል የሚታየው አሉታዊ ጎን ከአገሪቱ የኢኮኖሚ አቅም ጋር ተያይዞ የሚነሳ ቢሆንም ወደ ፊት ትኩረት ተደርጎ ሊሠራበት የሚገባ አብይ ጉዳይ ነው። ለበርካታ ስፖርቶች መዳከም ዋነኛ ምክኒያት የፌዴሬሽኖች የገንዘብ አቅም ማነስ ነው። መንግሥት ለስፖርት ኮሚሽን ከሚበጅተው ገንዘብ ተመፅዋች ሆነው እንደልብ መራመድ የከበዳቸው አገር አቀፍ ፌዴሬሽኖች ጥቂት አይደሉም። እነዚህ ፌዴሬሽኖች ውድድሮችን ለማካሄድ ስፖርቱን ለማሳደግ አንድና አንድ ችግራቸው የገንዘብ አቅም ነው። እነዚህ ፌዴሬሽኖች የመንግሥት እጅ ከመጠበቅ ይልቅ በራሳቸው የገንዘብ አቅማቸውን ለማጠናከር መሥራት እንዳለባቸው ብዙ ጊዜ ምላሽ ይሰጣል። ይሁን እንጂ እነዚህ ፌዴሬሽኖች ራሳቸውን በገንዘብ የሚያጠናክሩበት አቅም እስኪፈጥሩ ድረስ መንግሥት አሁን ከሚበጅትላቸው ገንዘብ በዘለለ ወጥ የሆነ አደረጃጀት ፈጥሮላቸው ዘላቂ የሆነ መስመር በመዘርጋት በኩል ክፍተቶች አሉ። መንግሥት ለፌዴሬሽኖች ዓሣ ከመስጠት ይልቅ ዓሣ የሚያጠምዱበትን ዘዴ ሊያስተምራቸውና መንገዱን ሊያሳያቸው ይገባል። እስከዚያው ድረስም አሁን የተሠሩት መሰረተ ልማቶች ከጋሪው ፈረሱ የቀደመ እንዳይሆኑ ዓመታዊ በጀታቸው ቢያንስ በርካታ ውድድሮችን በዓመት ውስጥ ማስተናገድ የሚያስችላቸውና በኋላ መሰረተ ልማቱ ተሟልቶ ስፖርቱ ኋላ እንዳይቀር በአንድ ላይ መጓዝ የሚያስችል መላ አልተፈጠረም፡፡ የአገራችን ስፖርት ባለፉት ሦስት አስርት ዓመታት ገደማ በእንዲህ ዓይነት የቁልቁለት ጉዞ በመራመድ ዛሬ ላይ ደርሷል። ካለፈው መጋቢት 2010 ወዲህ አገሪቱ በአዲስ የፖለቲካ ርዕዮተ ዓለም ባሆንም የለውጥ መንገድ ላይ መሆኗ አይካድም፡፡ ይህ የለውጥ ማዕበል በፖለቲካ ውጥረት ውስጥ ገብቶ አገር በማረጋጋት የተጠመደ ከመሆኑም ጋር ተያይዞ ሊሆን ይችላል የስፖርቱን ዘርፍ ትኩረት ሰጥቶ ሲመለከተው አይስተዋልም፡፡ ሁሉም ነገር ወደ መደበኛው እንቅስቃሴ ሲመለስና የፖለቲካ ውጥረቱ ሲረግብ ግን የስፖርቱን የቁልቁለት ጉዞ ሽቅብ እንዲጓዝ የማድረግ ትልቅ የቤት ሥራ እንደሚጠብቀው ከወዲሁ ማስታወስ ግድ ነው፡፡አዲስ ዘመን ግንቦት 16/2012ቦጋለ አበበ
https://www.press.et/Ama/?p=32985
1,172
2ስፖርት
ስፖርት የአብሮነትና አጋርነት መገለጫ ነው !!
ስፖርት
May 26, 2020
23
ስፖርት ከአካላዊ እንቅስቃሴና ከመዝናኛነት ባለፈ ማህበራዊ ግዴታን በመወጣት ረገድ ትልቅ ፋይዳ እንዳለው በተለያዩ አጋጣሚዎች ታይቷል፡፡ በተለይም ዓለም በኮሮና ቫይረስ(ኮቪድ 19) ምክኒያት ጭንቅ ውስጥ በገባችበት በዚህ ወቅት ስፖርትና የስፖርቱ ማህበረሰብ ማህበራዊ ግዴታን በመወጣት ረገድ ትልቅ ስራ እየሰራ ይገኛል።ስፖርት የአብሮነትና አጋርነት መገለጫ የመሆኑን “ሃቂቃ” ባለፉት አምስት ወራት በዘርፉ የተከናወኑ ሰብዓዊ ድጋፎች በቂ ማስረጃ ተደርገውም ይነሳሉ። በሀገራችንም በተመሳሳይ በስፖርቱ ዘርፍ ማህበራዊ ኃላፊነቱን ከመወጣት አኳያ ሰፊ እንቅስቃሴ እንደሚደረግ መናገር ይቻላል። በዘመነ ኮሮና በስፖርቱ ዘርፍ በኩል ማህበራዊ ኃላፊነትን ለመወጣት ሲደረግ የነበረውን ርብርብ ዘወር ብሎ መመልከቱ ለዚህ እማኝ ይሆናል።በሀገራችን ኮሮናን ለመከላከል ሲደረግና እየተደረገ ባለው ርብርብ የስፖርት ዘርፍም በዚህ እንቅስቃሴ ቀዳሚ ተሰላፊ ነበር። የስፖርት አመራሮች፣ የስፖርት ማህበራት፣ ስፖርተኞች፣ አሰልጣኞች እንዲሁም ደጋፊዎቻቸው፤ መልእክት በማስተላለፍ፣ በየቤታቸው ላሉ ዜጎች የአካል ብቃት እንቅስቃሴ በማሰራት፣ የገንዘብ ድጋፍ በማድረግ፣ የምግብና ሌሎች መገልገያዎችን በመለገስ እንዲሁም በሌሎች ተግባራት ላይ እየተንቀሳቀሱ ነው። ዘርፉን የሚመራው የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽንም ይህን እንቅስቃሴ በማስተባበር እንዲሁም እንደ አንድ ባለድርሻ አካል በሚጠበቅበት ሁሉ የራሱን ድርሻ በመወጣት ረገድ የነበረው ሚና ደግሞ ግዙፍ ነበር። ኮሚሽኑ ወገናዊነቱን ለመወጣት እየሄደ ያለባቸው ርቀቶች ደግሞ የበለጠ እንዲመሰገንና እንዲደነቅ ያደረገ መሆኑ የተለያዩ አካላት እያነሱ ይገኛሉ። በጠቅላይ ሚኒስቴር ዶክተር አብይ አህመድን በመጋቢት መጨረሻ “ማዕድ ማጋራት” ሲሉ በሰየሙት የድጋፍ መርሃ ግብር የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ስፖርት ኮሚሽን ከተለያዩ አካላት ጋር በመቀናጀት የጀመረው ተግባር በግንባር ቀደምነት ይጠቀሳል። በስፖርት ኮሚሽኑ አስተባባሪነት ሚያዝያ 17 ቀን 2012 ዓ.ም በአዲስ አበባ ስታዲየም በይፋ የተጀመረው “ማዕድ ማጋራት” መርሃ ግብሩ ስፖርት የአብሮነትና የአጋርነት መገለጫ መሆኑን በተጨባጭ ያሳየ ተግባር እንደሆነ ብዙዎች መስክረውለታል።የስፖርቱን ዘርፍ ወገናዊነት የሚንፀባረቅበት ማህበራዊ ኡደት እንደሆነ በመርሃ ግብሩ 300 የጎዳና ተዳዳሪዎችን ለአንድ ወር ያህል በመመገብ ባከናወነው ተግባር አስመስክሯል።ስፖርት ኮሚሽኑ የተለያዩ የስፖርት ተቋማቱና አጋር ድርጅቶችን አስተባብሮ ለአንድ ወር ያህል ሲያከናውነው የነበረው የምገባ መርሃ ግብር ባሳለፍነው እሁድ ተጠናቋል።የስፖርቱ ማኅበረሰብ በዘመነ ኮሮና ህዝባዊነቱን በተጠናከረ መልኩ ያሳየ መሆኑን የመጀመሪያው ዙር የተጠናቀቀው የምገባ መርሃ ግብር አስረጂ ይሆናል። የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ስፖርት ኮሚሽን ግን «ስፖርት የአብሮነትና የአጋርነት መገለጫ እንደመሆኑ ማህበራዊ ኃላፊነት የመወጣቱ ተልዕኮ የሚቋጭ ሳይሆን በአዲስ ምዕራፍ የሚጀመር ነው »ሲል ሁለተኛውን ዙር የምገባ መርሃ ግብር መጀመሩን አስታውቋል። በስፖርት ኮሚሽን ፊት አውራሪነት፣ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን፣ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ከቢጂ አይ ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር 300 ጎዳና ተዳዳሪዎችን ለአንድ ወር ያህል በምገባ መርሃ ግብሩ ተጠቃሚ ማድረጉን አስታውሷል።የስፖርት ቤተሰቡ ወገናዊነት በተግባር የሚያሳየውን መርሃ ግብር በመሆኑ ኮሚሽኑ ሁለተኛ ወር ለማስቀጠል ሌሎች አጋዥ አካላትን በማስተባበር እንዲሁም ድጋፎችን ማሰባሰብ በመቻሉ መርሃ ግብሩ ለቀጣይ አንድ ወርም ተጠናክሮ ሊቀጥል መቻሉ ተነግሯል። በስፖርት ኮሚሽኑ ፊት አውራሪነት ተግባራዊ የተደረገው የምገባ መርሃ ግብር በሁለተኛ ዙር ላይ የኢትዮጵያ ፀረ አበረታች ቅመሞች ጽ/ቤት፣ ወጋገን ባንክ እንዱሁም አቶ አብነት ገብረ መስቀል አጋርነታቸውን ያሳዩበት ሆኗል። ግንቦት 15 ቀን 2012 ዓ.ም አቶ ኤሊያስ ሽኩር የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነር፣ የብሔራዊ ድጋፍ አሰባሳቢ ንዑስ ኮሚቴ ሰብሳቢ አምባሳደር ምስጋው አረጋ እና ሌሎች እንግዶች በተገኙበት በአዲስ አበባ ስታዲየም ተጀምሯል። ኮሚሽነር አቶ ኤሊያስ ሽኩር መርሃ ግብሩን ሲያስጀምሩ፤«የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር በተወሰዱ እርምጃዎች ስፖርተኛው እና የስፖርት ቤተሰቡ ከፍተኛ የሆነ የስነ ልቦና እና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ አጋጥሟቸዋል ።ችግሮች ቢያጋጥሙም ስፖርተኛው እና የስፖርቱ ቤተሰብ በአንድ በኩል ከአለው ላይ በመቀነስ ለሌሎች በመደገፍ፤ በሌላ በኩል ሌሎች አካላትን በማስተባበር ወረርሽኙ ሊያስከትለው የሚችለውን ማህበራዊ እና ሰብዓዊ ቀውስ ለመከላከል ከፍተኛ አስተዋጽኦ በማድረግ ላይ ይገኛሉ »ሲሉ ዓለም በኮሮና ቫይረስ(ኮቪድ 19) ምክኒያት ጭንቅ ውስጥ በገባችበት በዚህ ወቅት ስፖርትና የስፖርቱ ማህበረሰብ ማህበራዊ ግዴታን በመወጣት በኩል እያበረከተ መሆኑን ነው ያስገነዘቡት። አቶ ኤልያስ በሌላ በኩል «በመዲናችን ኗሪ ለሆኑ 300 ጎዳና ተዳዳሪዎች ለአንድ ወር ያህል በምገባ መርሃ ግብሩ ተጠቃሚ ሲደረግ የነበረበት ሁኔታ መቋረጥ እንደሌለበት በማመን ሁለተኛውን ዙር እንዲጀመር ተደርጓል። በመሆኑም ሁለተኛው ዙር የምገባ ፕሮግራም መንግስት የጎዳና ተዳዳሪዎች በዘላቂነት ህይወታቸውን እንዲመሩ እሲኪያመቻች ድረስ በእኛ ደረጃ ለአንድ ወር የምገባ ፕሮግራሙን ለማራዘም ነው »ያሉት። አምባሳደር ምስጋናው አረጋ በበኩላቸው፤ ወረረሽኙን ለመከላከል ከጅምሩ ጀምሮ ቀጣይነት ባለው የስፖርት ቤተሰቦች እያደረጋችሁት ላለው ድጋፍ ምስጋና ይገባችኋል ብለዋል። በስፖርቱ መስክ የሚገኙ አካላት ለህዝብ ያላቸውን ወገንተኝነት እና ታማኝነት አርዓያነት ያለው ተግባር መሆኑን አመልክተዋል። «ህዝብ ሲኖር ስለሆነ ስፖርት የሚኖረው። ስለዚህ ሁላችንም በአንድ ላይ መቆም የምንችልበት የበለጠ የምንተባበርበት ወቅት በመሆኑ የተጀመሩ ድጋፎች ተጠናክረው ሊቀጥሉ ይገባል» ሲሉ ነበር መልዕክታቸውን ያስተላለፉት። በአጠቃላይ በሀገራችን ኮሮናን ለመከላከል ሲደረግና እየተደረገ ባለው ርብርብ የስፖርት ዘርፍ ከፍተኛ እንቅስቃሴ በማድረግ ረገድ በግንባር ቀደምነት ይጠቀሳል።የስፖርት አመራሮች፣ የስፖርት ማህበራት፣ ስፖርተኞች፣ አሰልጣኞች እንዲሁም ደጋፊዎቻቸው፤ መልእክት በማስተላለፍ፣ በየቤታቸው ላሉ ዜጎች የአካል ብቃት እንቅስቃሴ በማሰራት፣ የገንዘብ ድጋፍ በማድረግ፣ የምግብና ሌሎች መገልገያዎችን በመለገስ እንዲሁም በሌሎች ተግባራት ላይ ሲደረጉ የነበሩ እንቅስቃሴዎች ይሄንኑ ይመሰክራሉ።ዘርፉን የሚመራው የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽንም ይህን እንቅስቃሴ በማስተባበር እንዲሁም እንደ አንድ ባለድርሻ አካል በሚጠበቅበት ሁሉ የራሱን ድርሻ በመወጣት ላይ ይገኛል።ኮሚሽኑ በእርሱ አውራሪነት ተግባራዊ ያደረገው የምገባ መርሃ ግብር ደግሞ ማህበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት እያደረገ ያለውን አስደማሚ ጥረት መስካሪ ተግባር ነው። በመርሃ ግብሩ 300 የጎዳና ተዳዳሪዎችን ለአንድ ወር በመመገብ የፈፀመውን ሰብዓዊ ተግባር ቀጣይነት ይኖረው ዘንድ፤ ግንቦት 15 ቀን 2012 ዓ.ም ሁለተኛው ዙር መርሃ ግብር እንዲጀመር በማድረግ «ስፖርት የአብሮነትና አጋርነት መገለጫ ነው !!»የሚለውን አባባል በተጨባጭ፣ በተግባር……እንዲታይ አድርጓልና ሌሎችም ከዚህ ሊማሩ ይገባል ባይነን።አዲስ ዘመን ግንቦት 18/2012ዳንኤል ዘነበ
https://www.press.et/Ama/?p=33113
724
2ስፖርት
የእንቁላል ጨዋታ
መዝናኛ
October 27, 2019
31
 ከሦስት ዓመት በፊት ይሆናል። ወደ ሀዋሳ ለሥራ ጉዳይ ከባልደረቦቼ ጋር ተጉዘን በውቧ የደቡብብሔር ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ዋና ከተማ መሽገናል። ከተማዋ እንደዛሬው ጭር ሳትል፤ ፍርሀት ሳይነግስባት፤ የአገር ውስጥም ሆነ የውጭ አገር ጎብኚዎች የሚጎርፉባት፤ ሁሉም የነፃነት ክንፉን ዘርግቶ የሚንሳፈፍባት ነበረች:: ነዋሪዎቿም ቢሆኑ ኢትዮጵያን የሚመስሉ ውብ ድብልቅ ናቸው። አሁንም ጭርሱኑ እንቅስቃሴ የለም ብዬ ባልታበልም። መንፈሷ መታወኩን ሳልናገር ማለፍ ግን ይከብደኛል። ከያዛት ቆፈን ለመውጣት ዳር ዳር የምትል ይመስለኛል። ነገሩ ግን ወዲህ ነው ንትርኩን ሳላበዛ ወደ ጉዳዬ ልግባ መሰለኝ።በወቅቱ በደቡባዊቷ ፈርጥ የከተምኩት በአትሌት ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ ባለቤትነት የሚዘጋጀውን «የታላቁ ሩጫ በሀዋሳ» የ10 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ውድድርን ለመዘገብ ነበር። ታዲያ በዚያን ጊዜ ነው ለዓመታት ከአእምሮዬ ሊወጣ ያልቻለ አስተማሪ ነገር ያጋጠመኝ። በጊዜው ማረፊያችንን ያደረግነው በከተማዋ በሚገኘው በኃይሌ ሪዞርት ነበር። ኃይሌ ሮጦ ብቻ ሳይሆን አልምቶ አንጀት የሚያርስ መሆኑን ያወኩትም ያኔ ሳይሆን አይቀርም። ገጠመኜም ከዚሁ ጀግና ጋር የሚያያዝ ነው። ቀኑ ቅዳሜ ነው። የጎዳና ላይ ሩጫው የሚካሄደው ደግሞ እሁድ ጠዋት ነበር። ቅዳሜ ምሽት ደግሞ ኢትዮጵያውያንንና የውጭ አገር ዜጎችን ያሳተፈ ከፓስታ ብቻ የሚዘጋጅ ጣፋጭ ምግቦች የሚወራረዱበት ‹‹ፓስታ ፓርቲ›› የመክፈቻ መዝናኛ ዝግጅት ነበር። በምሽቱ ከጣፋጭ ምግቦቹ ውጪ ታዳሚዎች የሚሳተፉበት የተለያዩ ጨዋታዎች ነበሩ:: ከዚህ መካከል የኢትዮጵያ ጀግና ኃይሌ ገብረሥላሴ ተመልካችን እንዲያዝናና ከሌሎች ተሳታፊዎች ጋር ውድድር ማድረግ ነበረበት።ጨዋታው እንዲህ ነው። የተወዳዳሪዎቹን ቁጥር የሚስተካከል እንቁላል እና ማንኪያ ተዘጋጅቷል:: ኃይሌን ጨምሮ ተፎካካሪዎቹ ይሄን እንቁላል በማንኪያው ላይ አድርገው በአፋቸው ይይዛሉ። መነሻው እና መድረሻው በተዘጋጀው ስፍራ እንቁላሉን በማንኪያው ይዘው ቀድመው መድረስ ይኖርባቸዋል:: ኃይሌ እንቁላሉን ይዞ ቀድሞ ገብቶ ውድድሩን አሸንፎ ይሆን? የሚለው የእናንተ ጥያቄ እንደሚሆን አልጠራጠርም። ነገሩ ግን ወዲህ ነው።ኃይሌ ውድድሩ ምን እንደሆነ ሲነገረው። ተሳታፊ እንደማይሆን ተናግሮ የተወዳዳሪዎቹንና የታዳሚውን ወሽመጥ ቆረጠው። ለምን አትሉኝም። የሱ መልስ እጅግ በጣም ቀላል ነበር። ‹‹አንድ ጊዜ በልቶ የማያድር ሕዝብ ባለበት መሀል ተፈጥሬ በእንቁላል አልጫወትም›› በማለት በምግብ መጫወት የኑሮውም፣ የባህሉም ሆነ የእምነቱም ሁኔታ እንደማይፈቅድለት ተናግሮ ታዳሚውንም እጅግ አስደንቆና አስተምሮ ከመድረክ ወረደ።በወቅቱ የተከሰተው ሁኔታ አብዛኛዎቻችንን ያስገረመ ነበር። ከድህነት ውስጥ በበቂ ሁኔታ ባንወጣም፤ የኛን ባህል በማያውቁ የውጭ አገር ዜጎች መሀል በመከበባችን እና ፓስታ ፓርቲ ላይ በመሆናችን አዘጋጆቹም እኛን ሊያዝናኑ፤ እኛም በእንቁላል ልንዝናና ቃንጥቶን ፍፁም አቅላችንን ስተን ነበር። በገጠሩ አካባቢ አድጎ የገጠሯን እናት ልፋት፤ የአርሶ አደሩን አባት ድካም የሚያውቀው ብርቱው ጀግናችን ግን ያለው ሀብት እና ዝና ሳያስተው፤ ብልፅግና ልቡን ሳይሰውረው አሁን ደረቱን ነፍቶ ‹‹እኔ በእንቁላል አልጫወትም›› ሲል አዲስ መንገድ አሳየን።ይሄ ክስተት ላለፉት ሦስት ዓመታት የተለያዩ አጋጣሚዎች በተፈጠሩ ቁጥር በህሊናዬ ሲመላለስ ቆይቷል። ዛሬ ደግሞ በምን አጋጣሚ አስታወስከው ካላችሁ ሌላ አንድ ልብ የሚሰብር አሳዛኝ አጋጣሚን እነግራችኋለሁ። ከሦስት ዓመት በፊት ይህ እውቅ እና አስተዋይ ሰው በእንቁላል መጫወት ትክክል አለመሆኑን በአስገራሚ እይታው እና አንደበቱ ቢነግረኝም ይበልጥ እንዳከብረው ያደረገኝ ገፊ ምክንያት ሰሞኑን ያጋጠመኝ ጉዳይ ነው። ነገሩ እንዲህ ነው…የሥራ ባህሪዬ ሆነና በሁሉም የአገሪቷ ክፍል (ከገጠር እስከ ከተማ) የመዘዋወር እና ከሰዎች ጋር የመገናኘት አጋጣሚዬ ሰፊ ነው። ባሳለፍነው ሳምንትም ወደ ሰሜን ሸዋ ምድር የመጓዝ ዕድሉን አግኝቼ ነበር:: ሸዋ ከሥርዓተ መንግሥት ምስረታ ገድሏ ባሻገር በአሁኑ ወቅት እስከ ሦስተኛ ዲግሪ መመረቂያ ጽሑፍ ለማቅረብ የሚጠቅሙ የምርምር የታሪክ እና ሥነ ጽሑፍ ለኢትዮጵያ፣ ለአፍሪካ እንዲሁም ለዓለም የተረፉ የጥበብና የሥልጣኔ ፊትአውራሪ ሰዎች የፈለቁባት ነች። በተለይ ከግእዝ ወደ አማርኛ በርካታ መጽሐፍትን በመተርጎም፤ ከፊደል ገበታ እስከ ታላላቅ መጽሐፍት በመድረስ ለኢትዮጵያውያን ያበረከቱት ተስፋ ገብረሥላሴ፣ንጉስ ሳህለሥላሴ፣አፄ ምኒልክ እና የታሪክ ተመራማሪው እና ምሁሩ ተክለፃዲቅ መኩሪያ የሚጠቀሱ ናቸው።ታዲያ በሸዋ ምድር ቆይታዬ ለማየት ከቻልኳቸው ቦታዎች መካከል የምኒልክ እና የበርካታ ነገስታት መቀመጫ የነበረው የሚገኝበትን ‹‹አንኮበር ቤተ መንግሥት›› አንዱ ነበር። ግዘፍ እንደነሳው ታሪኩ እና ባለውለታነቱ የተረሳ እና እጅግ የሚያሳዝን ማህበረሰብ ያለበት መሆኑን በስፍራው የተገኘ ብቻ ነው የሚረዳው። ሕዝቡንና አካባቢውን አይቶ አይን ባያነባ እንኳን ልብ ማልቀሱ አይቀሬ ነው። ይህን ጉዳይ የሚያስረዳልኝ ደግሞ ቅዳሜ ቀን ገበያ ወጥታ ያገኘኋት የምስኪኗ እናት መከራ ነበር።ይህቺን እናት በገበያ ውስጥ ስዘዋወር ነው ያገኘኋት። የሥራ ባልደረቦቼ አብረውኝ ነበሩ። ግርግር በበዛበት ስፍራ ከፊት ለፊቷ ብጫቂ ጨርቅ ዘርግታ ከአንዲት ትንሽ ድንጋይ ላይ ቁጢጥ አለች:: ነገረ ሥራዋ ትኩረታችንን ስለሳበው ድርጊቷን መከታተል ጀመርን:: ልትለምን አልነበረም። ከያዘችው ቀረጢት ውስጥ በጥንቃቄ ሁለት ትናንሽ ነገሮችን አውጥታ ከዘረጋችው ጨርቅ ላይ አስቀመጠቻቸው። እንቁላሎች ነበሩ። ሁለት እንቁላሎች። ለዚያውም የሚሸጡ እንቁላሎች:: ይቺ እናት አይኗን ወደ ገበያተኛው እያማተረች ገዢዎችን እየተጠባበቀች ነው።ጠጋ ብዬ ስለሁኔታው አነጋገርኳት። የሚያስ ገርመው ደግሞ እዚህ የገበያ ቦታ ለመድረስ ከ10 ኪሎ ሜትር በላይ ተጉዛለች። ሁለት እንቁላል ለመሸጥ!! በምታገኘው ገንዘብ ደግሞ ጨው ገዝታ ወደ ልጆቿ ትበራለች። ሌላ አስር ኪሎ ሜትር ተጨማሪ:: ትራንስፖርት የማይታሰብ ነው። ጉዞ በእግር ነው። አዛኙ ጓደኛዬ ኪሱ ያለውን አውጥቶ እጁን ዘረጋላት:: ፊቷ በብርሃን ፈካ። ቢያንስ ለሦስት ሳምንት ገበያ መውጣት አይጠበቅባትም። ኑሮዋ እጅጉን ያሳዝናላ።እኔ ደግሞ በሀሳብ ነጎድኩ። ወደ ሃዋሳ። ኃይሌ ሪዞርት። ኃይሌ እንዲህ ይላል ‹‹እኔ በእንቁላል አልጫወትም!!››      አዲስ ዘመን ጥቅምት 16/2012 ዳግም ከበደ
https://www.press.et/Ama/?p=21513
676
1መዝናኛ
«እኛ» በ «እኔ» ተተክቶ ይሆን?
መዝናኛ
October 28, 2019
37
 ሰው እራሱን ታዝቦ ያውቃል? መቼም እራሴን ታዝቤያለሁ የሚል ሰው ካለ ቀን በቀን ሰውነቱን የሚታጠብ ሰው መሆን አለበት። ምክንያቱም ቀን በቀን ሰውነቱን ሲታጠብ መወፈሩን፣ መቅጠኑን፣ መቅላቱንና መጠቆሩን ስለሚመለከት ይመስለኛል። ነገር ግን ሰዎች እራቸውን ማለቴ ውስጣቸው ታዝበውት ያውቁ ይሆን? ብዬ አስባለሁ….. ምነው እራስህን ታዝበህ ታውቃለህ? ካላችሁ….አላውቅም ነው መልሴ….ለምን ብትሉ…..እራስን መታዘብ እኮ እራስ ማስጠፋት የሚያደርስ ወቀሳ አለዋ!!መቼም ሰው ስንባል ትዝብት…..ምናምን በጣም ይመቸናል። በተለይ ደግሰን፣ ታመንና በሌሎች ማህበራዊ ጉዳዮች ሰዎች ሲቀሩ «ታዝቤሀለሁ» እንላለን። ሕዝብ መሪውን ሲመርጥ ወይም ተወካዩን ሲመርጥ ታዛቢ ያስቀምጣል… (ታዛቢ ሲባል ቁጭ ብሎ ድምፅ ሲሰጥና ሲቆጠር የሚያይ ነው)። በሌላም መንገድ ስናጠፋ…ወይ ጥሩ ስንሰራ የሚታዘበን ሰው አናጣም አይደል…።እስቲ አንዳንድ ሁኔታዎችን እንታዘብ….:: መቼም ርዕሱን አይታችሁ ምን ላወራ እንዳሰብኩ ገምታችኋል? በአሁኑ ወቅት የሚያወራና የሚታዘብ ሰው ከመብዛቱ «እኛነት» ጠፍቶ «እኔ» የሚለው አባባል በአንቀፅ ለብቻው ተከልሎ የመገንጠል ጥያቄ አንስቷል። በአገሪቱ የሞላነው ሰዎች የማናውቀውን የምንነቅፍ፣ በድህነት ውስጥ ሆነን እኔ እበልጥ የምንባባልና ስብሰባና መንገድ መዝጋት ሥራችን ከሆነ ሰነባብቷል።ሰላም ያስጠብቃሉ ተብሎ የተመደቡ ፖሊሶች ቀኑን ሙሉ ስብሰባ እየተቀመጡ በተገላቢጦሽ ሕዝቡ ነው የሚጠብቃቸው አሉ…«አሉ» ነው….። ድንበር ጠባቂ ወታደሮቹም ከድንበር ይልቅ የውስጥ የውስጥ ችግሮችን ሲፈቱ መዋል ዋነኛ ሥራቸው የሆነ ይመስላል፤ ከአገር ግለሰብ ይበልጣል ብለው ሊሆን ይችላል….። እኛ ደግሞ ጥቅም በሌላቸው ሀሳቦች ተከፋፍለንና ተቧድነን መደባደብ ይዘናል….ከየት እንዳመጣነው የማናውቀውን መሬት የኔ ነው…..ውጣ…ውጡ…..ማለት ደመወዝ የሌለው ሥራችን ከሆነ ዓመታት ተቆጥረዋል። ድህነት እና ድርቅ ተጋብተው አገሪቱን መውጫና መግቢያ አሳጥተዋት ባለበት ወቅት እኛ ደግሞ በየመንገዱ መኪና እያስቆምን መዝረፍ፣ እህል ማፍሰስ እና እንዳይንቀሳቀሱ ማድረግ ጀብደኝነት ሆኖ ያሸላልመናል። የአንዱ ጉዳት ለሌላኛችን ደስታ ከመሆን አልፎ ርዕዮት ዓለም ሆኖም እያወዛገበም መጥቷል……። እኛ ባለፈ ታሪክ አሁንም ድረስ የምንናቆር ጉዶች ሆነናል… እኮ።በመንግሥት መስሪያ ቤቶች ውስጥ የሚገኙ ሠራተኞች አገልግሎት ከመስጠት ይልቅ ቁጭ ብለው በማህበራዊ ሚድያ በመቧደናቸው ዋና ሥራቸው የሆነውን ሕዝብን ማገልገል አቁመዋል። በተለይ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ቢሮዎች የፖለቲካ መድረክ ከመሆን አልፈው የአንድ ግለሰብ ሃሳብ ወደ ማራመጃነት አድገዋል። ‹‹ለመንግሥት ሥራ አትልፋ ግን ከወንበርህ አትጥፋ» የምትለዋን አባባል ሙሉ ለሙሉ የሚያሟሉ ሠራተኞችም በየዓመቱ ምርጥ ፈፃሚ እየተባሉ ይሸለማሉ..።(ፈፃሚዎቹ «ከእኛ» አስተሳሰብ ወደ «እኔ» ልጠቀም አስተሳሰብ በመሻገራቸው መሸለማቸውን ልብ በሉ)። ወጣቱ በአገር ጉዳይ ከመከራከርና ከመግባባት ይልቅ በውጭ እግር ኳስ መደባደብን አማራጭ አድርጎ መያዙ በአገር ጉዳይ አያገባኝም መንፈስ ውስጥ ከቶታል..። ይህም ብቻ አይደለም፤ አያድርገውና አገሪቱ በጠላት ብትወረር እንደድሮው ዘምቶ የሚዋጋ ያለ አይመስለኝም… ለምን ብትሉ አሁን ያለነው ሰዎች እኮ «እኔ» ጋር ካልደረሰ ምን አገባኝ ብለን ጥቅልል ብለን የምንተኛ ነን…..ምን እሱ ብቻ አንዳንዶቻችንማ ለጠላት አግዘን ሳንዋጋም እንቀራለን?….። ይህ ዓመት ከገባ ሁለተኛው ወር እየተገባደደም አይደል…. በነዚህ ወራት ውስጥ ብዙ ሁነቶች ተከናውነዋል….በተለይ የድጋፍ፣ የበዓልና የመንገድ መዝጋት ሰልፎች መቼም አይዘነጉም..። የመንገድ መዝጋትን ስናነሳ ያለፈው ሳምንት መንገድ የመዝጋት አባዜያችን ምን ላይ እንደደረሰ ማሳያ ነው። በተለያዩ ከተሞች መንገዶችን በድንጋይ በመዝጋት የአገሪቱን እቅስቃሴዎች ለማገድ የተደረገው ሙከራ ዛሬም ከዚህ በሽታ አለመውጣታችንን የሚያሳይ ነው። ሌላው ደግሞ በመንግሥት ድጋፍ ሰልፎች ላይ የተፎካካሪ ፓርቲ አርማዎች ማየት እየተለመደ መምጣቱ ነው። በተገላቢጦሽ የመንግሥት አርማዎችና የአገሪቱን ሰንደቅ አላማ መያዝ የሚያስደበድብ ወንጀል ሆኗል። መጨረሻውን ያሳምረው እንጂ ወደፊትማ አንድ ግለሰብ ሲደብረው ወይ ሲደሰት በአገር አቀፍ ደረጃ ይከበር ሳይባል አይቀርም..። ሕዝባችን ለምን ወደ ኋላ ተመልሶ ማሰብ ፈለገ ብዬ ወዳጄን ስጠይቀው ምን አለኝ መሰላችሁ «ካለፈው ተምሮ የወደፊቱን ከማስተካከል ይልቅ….ከወደፊቱ በመማር የኋላውን ለማስተካከል እየጣረ ስለሆነ ነው» ብሎ መለሰልኝ….ሳስበው ትክክል ነው..። ለምን ካላችሁ በመገናኛ ብዙኃን ይሁን በግለሰቦች እየተወራ የሚገኘውን ያለፈ ታሪክ ከመማርያነት ይልቅ ታሪኩን ለማስተካከል እየተደረገ ያለውን ትግል ካየሁ በኋላ ነው። ታድያ መቼ ነው የምንለወጠው? መቼ ነው የሰለጠነ ማህበረሰብ የምንፈጥረው? መቼ ነው ያደገ አገር የምንሆነው? ቢባል ….መቼም ይሆናል መልሱ። ምክንያቱም «እኛ»ን አስወግደን «እኔ»ን በመምረጣችን ነዋ።                                                                                                              አዲስ ዘመን ጥቅምት 17/2012 መርድ ክፍሉ
https://www.press.et/Ama/?p=21524
518
1መዝናኛ
ፍርሃትን ለጉብኝት
መዝናኛ
October 29, 2019
32
 በርካታ ሀገራት ከቱሪዝም ዘርፍ ዳጎስ ያለ ገቢ ለማግኘት ያላቸውን የተፈጥሮና ሰው ሰራሽ ቅርሶች ለጎብኚዎች ክፍት ያደርጋሉ። የጎብኚዎቻቸውን ቁጥር ለመጨመርም ለቱሪስቶች አስፈላጊ ናቸው ብለው ያመኑባቸውን ነገሮች ሁሉ ያሟላሉ። በአሁኑ ወቅት ደግሞ የተፈጥሮና ሰው ሰራሽ ቅርሶች የሌላቸው ሀገራት ስማርት ከተሞችን በመገንባትና ለልዩ ልዩ ኮንፍረንሶች በማዋል የቱሪስቶችን ቀልብ በመሳብ ከፍ ያለ ገቢ ማግኘት ጀምረዋል። በየሃገራቱ ያሉ የግል ባለሀብቶችም ተፈጥሯዊ ይዘት ያላቸውን ሪዞርቶችና ቅንጡ ሆቴሎች በመገንባት ከቱሪዝም የሚገኘውን ገቢ እያሳደጉት ይገኛሉ። ቱሪስቶች ወደነዚህ ሪዞርቶችና ቅንጡ ሆቴሎች የሚመጡት ለመዝናናትና ለእረፍት ካልሆነ በስተቀር ለመሳቀቅ አልያም ለመፍራት አይሆንም። ኦዲቲ ሴንትራል ከሰሞኑ ይዞት ብቅ ያለው መረጃ ግን ከዚህ የተለየ ነው። ሰዎች ለመፍራትና ለመሳቀቅ ፍላጎቱ ካላቸው ከኪሳቸው ሰባራ ሳንቲም ሳያወጡ ይልቁንም ተከፍሏቸው ሊጎበኟቸው የሚችሉ አስፈሪ ቤቶች መፈጠራቸውን ጠቁሟል። በሰዎች ላይ የፍርሃት ስሜት የሚፈጥሩ ቤቶች በአንዳንድ ሀገራት ውስጥ ለጉብኝት የሚውሉ መሆናቸው የሚታወቅ ቢሆንም፣ መኬሚ ማኖር የተሰኘው አሜሪካዊ ከሰሞኑ ገንብቶ ለጎብኚዎች ክፍት ያደረገው ቤት በጎብኚዎች ላይ ፍርሃት በመልቀቅ ወደር አልተገኘለትም። ቤቱ በሚፈለገው ልክ በጎብኚዎች እየተዘወተረ ባለመሆኑም በቤቱ ውስጥ የነገሰውን የፍርሃት ድባብ ለአስር ሰዓታት ተቋቁመው ለሚወጡ ሰዎች መኬሚ ማኖር የ20 ሺ የአሜሪካ ዶላር ሽልማት መመደቡ ታውቋል። ለጉብኝት የሚመጣ እያንዳንዱ እንግዳ የመጨረሻው ሰዓት ላይ እስኪደርስና ቤቱን ለቆ እስኪወጣ የአእምሮና የአካል ፈተና የሚገጥመው ሲሆን፣ በቤቱ ውስጥ በሚኖረው የአስር ሰዓታት ቆይታ ከእርሱ ጋር አካላዊ ንክኪ ያላቸው ይሁንና ለንክኪው ምላሽ የማይሰጡ አስፈሪ ተዋንያን መመደባቸው ተገልጿል። ይህንኑ አስፈሪ ቤት በመጎብኘት ለሽልማት የተዘጋጀውን 20 ሺ የአሜሪካ ዶላር ለማፈስ የፈለጉ ተሳታፊዎችም እድሜያቸው ከ21 ዓመት በላይ መሆን እንዳለበት በመረጃው ተጠቁሟል። ቤቱን መጎብኘት የሚፈልጉ የህክምና ኢንሹራንስ ማስረጃ የሚያቀርቡ፣ ስፖርታዊ ቅርፅ ያላቸውና በዚህ ቤት ለመቆየት መስማማታቸውን የሚገልፀውን ባለ አርባ ገፅ ቅፅ ለመፈረም ዝግጁ መሆን ይኖርባቸዋል። ይህንን ቅድመ ሁኔታ ያሟሉ ሰዎች በቅድሚያ ጉብኝቱን በተመለከተ አስተማሪ ቪዲዮ እንዲመለከቱ እንደሚደረግም ተነግ ሯል። በዚህ አስፈሪ ቤት ውስጥ ጎብኚዎች ከገቡ በኋላ 20 ሺ የአሜሪካ ዶላር ለማግኘት ያላቸውን ተስፋና ጉጉት በፍፁም ማሳየት እንደሌለባቸው መኬሚ ይመክራል። ይህን ማድረግ በፍፁም የተከለከለና ከቤቱ ውስጥ የሚያስወጣ መሆኑንም ገልጿል። የተለያዩ ቁልፎች የሚገኙባቸውን አቅጣ ጫዎችና አቅጣጫዎቹ ወዴት እንደሚያመሩ አስፈላጊዎቹ መረጃዎች ሁሉ ለጎብኚዎች የሚገለጹ ሲሆን፣ ጎብኚዎቹ አንድ ጊዜ ቤቱ ውስጥ ከገቡ በኋላ እያንዳንዱን ነገር ማስታወስ የእነሱ ሃላፊነት መሆኑንም አብራርቷል። ‹‹ያዘጋጀሁትን 20 ሺ ዶላር ሽልማት አታሸንፉም›› ሲልም መኬሚ አስጠንቅቋል። የማስፈራሪያ ቤቶች በአብዛኛው በአስፈሪ ድምጾች የታጀቡና በመጠኑ የፍርሃት ስሜት ውስጥ የሚከቱና አንዳንዴም ከጨለማ ጥግ ድንገት የሚዘሉ አክተሮች የሚታዩባቸው ቢሆኑም፣ መኬሚ ማኖር ሸረሪቶችና በረሮዎችን በደም ውስጥ በመንከርና በጎብኚዎች ፊት ላይ እንዲያርፉ በማድረግ እንዲሁም ሌሎችንም ዘግናኝ ድርጊቶችን በመጨመር ነገሮችን አዲስ ለማድረግና የበለጠ አስፈሪ ድባብ ለመፍጠር ጥረት አድርጓል ተብሏል። ይህንኑ ቤት ለማስተዋወቅ የተለቀቀው ቪዲዮም ወደዚህ ቤት የሚመጣን ማንኛውንም ሰው የሚያስጠነቅቅ እንደሆነም ተነግሯል።አዲስ ዘመን ጥቅምት 18/2012 አስናቀ ፀጋዬ
https://www.press.et/Ama/?p=21576
387
1መዝናኛ
ሌጣዎችን ብቻ የሚያስተናግደው ቡና ቤት
መዝናኛ
October 29, 2019
44
 ሰዎች መዝናናት ሲፈልጉ ሰብሰብ ማለትን ይመርጣሉ።ሰብሰብ ማለት የተለያዩ ጨዋታዎችን ማምጣት የሚያስችል ሳይሆን ወጪንም ሊቆጥብ ይችላል።ለእዚህም ነው ጉዞ እና የመሳሰሉትን በቡድን የሚደረጉት፤ ድንኳን እየተጣለም ዳንኪራ የሚረገጠው።ጓደኞሞች ተጠራርተው ተቀጣጥረው ተያይዘው መጠጥ ቤት፣ ካፌ ቤት ወዘተ የሚገናኙት በጋራ የሚያደርጉት ጨዋታ ሁሌም የማይገኝ በመሆኑም ጭምር ነው። ኦዲቲ ሴንትራል የተሰኘው ደረ- ገጽ ሰሞኑን ያስነበበን ግን ከዚህ የተለየ ነው።በጃፓን ቶኪዮ የሚገኝ አንድ አነስተኛ ቡና ቤት ሌጣውን የሚመጣን ሰው ብቻ ማስተናገድን ምርጫው አድርጓል።ሂይቶሪ የተሰኘው ይህ ቡና ቤት በሌሎች ቡና ቤቶች የማይመረጥ የራሱን ደንበኞች የሚያስተናግድበት መንገድ አለው፡፡ መረጃው እንዳመለከተው፤ ብቻውን እስከ ሆነ ድረስ የትኛውም ግለሰብ ቡና ቤቱን መገልገል ይችላል።ወደ ቡና ቤቱ በቡድን ሆኖ መግባት ክልክል ነው።ፈቃዱም ሆነ ክልከላው በቡና ቤቱ መግቢያ በር እና በሌሎች ስፍራዎች ላይ በግልጽ ተልጥፏል፡፡ ‹‹ሰብስብ ብላችሁ ዘና ማለት የምትፈልጉ ከሆነ ይህ ቡና ቤት ለእናንተ ዝግጁ አይደለም፡፡›› ያለው መረጃው፣ ይህ ማለት ግን ቡና ቤቷ የብቸኞች ወይም የሌጣዎች ወይም ማህበረሰቡ ያገለላቸው ሰዎች መሰብሰቢያ ነው ማለት አይደለም ይላል፡፡ ቡና ቤቱ ለተገልጋዮቹ ያልተለመደ የተባለ ፖሊሲ ማውጣቱን የሰማችው አንድ የሶራ ኒውስ 24 መገናኛ ብዙሃን ሪፖርተር ማሪኮ በቅርቡ ቡና ቤቱን ጎብኝታለች።ጋዜጠኛዋ ቡና ቤቱ ከምትጠበቀው በላይ አካታች ሆኖ እንዳገኘችውም ተናግራለች።ወደ ቡና ቤቱ እንደገባችም ከስድስት የማያንሱ ተገልጋዮችን ማየቷን ጠቅሳ፣ ሰዎቹ ብቻቸውን እንደገቡ ሰዎች ሆነው እንዳለገኘቻቸው ተናግራለች።ለየብቻቸው ከመሆን ይልቅ ተሰብሰብው ሲጨዋወቱም ተመልክታለች።በአስተናጋጁ አማካይነት ቀረበቻቸውናም አጠገባቸው ተቀመ ጠች። ተገልጋዮቹ ለየብቻቸው ቢመጡም ብዙ ጊዜ አብረው እንደኖሩ ጓደኛሞች እርስ በእርስ ሲያወሩ ትመለከታለች።ማሪኮ መጠጥ አዘዘች፤ ይሁንና ቀጥሎ ምን ማድረግ እንዳለበት አላወቀችም።አስተናገጁ ምን እንደተሰማት ተረድቷል፤ ወደ ቡና ቤቱ የመጣሽው ለመጀመሪያ ጊዜ ነው ሲልም ጠየቃት፡፡ ጋዜጠኛዋ ለቀረባላት ጥያቄ ምላሽ ስትሰጥ ሌሎቹ ደንበኞች ጭምር መሳተፍ ጀመሩ፤ ወደ ቡና ቤቱ ለመጀመሪያ ጊዜ እንዴት ሊመጡ እንደቻሉ ሀሳብ ተለዋወጡ።ማሪኮም በውይይቱ ውስጥ መሳተፍ ቀጠለች።ወደ ቡና ቤቱ የሚመጡ ሁሉ በዚህ አይነት መልኩ እየተቀላቀሉ ተደስተው እንደሚመለሱም ተነገራት።የቡና ቤቱ ባለቤትም ይህን አስቦ ቡና ቤቱን መክፈቱን መረጃው ይጠቁማል። ‹‹ ሰዎች ቡና ቤት መሆን አለበት ብለው በሚያስቡት አይነት ቡና ቤት እኔ እምነቱ የለኝም›› ሲል ለሪፖርተሯ የተናገረው የቡና ቤቱ ባለቤት፣ ቡና ቤቴን እንዴት ባደርገው ከቡና ቤቶች ሁሉ የተለየ ሊሆን ይችላል እያለ ሲያስብ መቆየቱንም ይገልጻል።ቡና ቤቱ አዳዲስ ሰዎች እየመጡ የሚገናኛኙበትና የሚደሰቱባት እንዲሆን ይፈልግ እንደነበርም ይናገራል። ‹‹ቡና ቤቱ እንደገባህ ራስህን ብቸኛ ያረገህ ይመስልሃል፤ በሌሎች የተገለልክም ይመስልሃል፤ በእርግጥም ይመስላል፤ ከዚያም በቡና ቤቱ ከሚገኙት በርካታ ሰዎች ጋር ማውራት ውስጥ ተገባለህ›› ሲል አንዱ ተገልጋይ ይናገራል።ሌላው ተገልጋይ በበኩሉ ‹‹በሌሎች ቡና ቤቶች የማላውቃትን ሴት ለማውራት ብሞክር ሌሎች ድብደባ የሚፈጸምብኝ እየመሰላቸው ይበሳጩብኛል፤ እዚህ ግን ሁላችንም የመሰለንን እንጨዋወታለን፤ ነገሮች ቀለል ያሉ በመሆናቸውም እንደሰታለን›› ሲል የቡና ቤቷን ምቹነት ገልጿል። የሂቶሪ ቡና ቤት የመስተንግዶ ፖሊሲ ማህበራዊነትን የሚጻረር ቢመስልም አዳዲስ ሰዎች ማግኘት የሚቻልበትን ከባቢ ለመፍጠር የራሱን አስተዋጽኦ ያበረክታል።በዚህም ምንም አይነት ግፊት በሌለበት ሁኔታ ሰዎች በራሳቸው ፍላጎት መግባባት የሚችሉበትን መድረክ ለመፍጠር ምቹ ስፍራ ነው ሲል መረጃው ያመለክታል።ይህ ሁኔታ ሲታይ ቡና ቤቱ ከተቀሩት ቡና ቤቶች አንጻር ሲታይ የበለጠ አካታች ነው ሲል መረጃው ያመለክታል፡፡አዲስ ዘመን ጥቅምት 18/2012 ዘካርያስ
https://www.press.et/Ama/?p=21578
423
1መዝናኛ
የፌዴሬሽኑ አማራጭ እቅዶችን የመጠቀም እንቅስቃሴ
ስፖርት
May 27, 2020
18
ይህ ዓመት እንደ ከዚህ ቀደሞቹ ቢሆን፤ በስፖርቱ ዓለም በተለይ በዚህ ወቅት በርካታ ውድድሮች፣ ጉባኤዎችና ሥልጠናዎች ሊካሄዱ ይችሉ ነበር። ነገር ግን ሳይታሰብ ተከስቶ ዓለምን ባዳረሰው የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ19) ወረርሽኝ ምክንያት ውድድሮች ብቻም ሳይሆኑ በርካታ ጉዳዮች በታቀደላቸው ሁኔታ እንዳይካሄዱ ማድረጉ ግልጽ ነው። ታዲያ የስፖርት ማህበራትና ሌሎች ተቋማት እቅዶቻቸው በዚህ መልኩ አቅጣጫቸውን ሲስቱ ምን ዓይነት አማራጮችን ተጠቀሙ? ከዓመት እስከ ዓመት በሩጫ ላይ ከሆኑና በሥራ ከሚወጠሩ ፌዴሬሽኖች መካከል አንዱ የሆነው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ነው። የፌዴሬሽኑ የሥልጠና ጥናትና ምርምር ዳይሬክተሩ አቶ ሳሙኤል ብርሃኑ የሚናገሩት አላቸው። የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ቻምፒዮናን ጨምሮ የሻምበል አበበ ቢቂላ ማራቶን፣ የወጣቶች ቻምፒዮና እንዲሁም ሌሎች ውድድሮች ፌዴሬሽኑ በዚህ ዓመት ያላካሄዳቸው የውድድር ዘርፍ እቅዶች ናቸው። በሥልጠና ጥናትና ምርምር ዘርፍ ደግሞ የዚህ ዓመት ዋነኛ እቅድ የነበረው ባለሙያዎችን ማብቃትና መመዘን መሆኑን ዳይሬክተሩ ይገልጻሉ። ዳኞችና አሰልጣኞች ዓለም አቀፍ ሥልጠናዎችን አግኝተው ደረጃቸውን እንዲያሳድጉ ለማድረግ እንቅስቃሴዎች እየተደረጉ ባለበት ወቅት ግን የዓለም ትኩሳት የሆነው ጉዳይ በመከሰቱ እንደታሰበው ማስኬድ አልተቻለም ይላሉ። በተለይ ከሚያዝያ እስከ ሰኔ ወር ድረስ የሥራ ክፍሉ በዚህ ለማሳለፍ ያስቀመጠው እቅድ ወደ መሬት ሳይወርድ ቀርቷል። በዓመቱ ኦሊምፒክና ሌሎች ዓለም አቀፍ ውድድሮች ላይ መሳተፍና ብሔራዊ ቡድንን የማዘጋጀት እቅድም ተመሳሳይ ዕጣፈንታ ገጥሞታል። ለብሔራዊ ቡድን የተጠሩ አትሌቶችም ተበትነው ወደየ ቤታቸው ሄደዋል። ይህ ሁሉ ሲሆን ፌዴሬሽኑ ግን ሥራውን ከማቋረጥ ይልቅ ሌሎች አማራጮችን መጠቀምን መርጧል። ዋናው የአትሌቶች ጤንነትና በብቃት መቆየት በመሆኑም የተሻለ ያለውን ተግባር ሲከውን እንደቆየ ዳይሬክተሩ ያስረዳሉ። ፌዴሬሽኑ ከቫይረሱ ጋር በተያያዘ ስፖርታዊ ክዋኔዎችን ማካሄድ አዳጋች መሆኑን በመገንዘቡ ቀደም ብሎ ወደ ዝግጅት መግባቱን ይጠቁማሉ። አትሌቶች ሥልጠና ማቋረጣቸውን ተከትሎ ከስፖርቱ እንዳይርቁ እንዲሁም አሰልጣኞችም ከአትሌቶቻቸው በጋራ ያላቸው ግንኙነት እንዳይቋረጥ ምን ማድረግ ይገባል? የሚለውን በማሰብም ነው በቴሌቪዥን ስርጭት በትምህርትና በሌሎች ጉዳዮች ላይ የሚያጠነጥኑ ፕሮግራሞች እንዲተላለፉ የተደረገው። በዚህም የስፖርቱ ባለሙያዎችን በማካተት በሦስት የቴሌቪዥን ጣቢያዎች ለስድስት ሳምንታት ለአትሌቶች ጠቃሚ የሆኑ መርሃ ግብሮች ሲተላለፉ ቆይቷል። የመርሃ ግብሩ ይዘትም ሥነ-ልቦና፣ ሥነ-ምግብ፣ ሕክምና፣ ማህበራዊ ግንኙነት፣ የተምሳሌት አትሌቶች መልዕክት፣ የአሰልጣኞች ምክረ ሃሳብ እንዲሁም አትሌቶች በአጠቃላይ ምን ማድረግ ይገባቸዋል የሚለውን ያጠቃለለ ነበር። ከቴሌቪዥን ስርጭቱ ባሻገር በፌዴሬሽኑ ይፋዊ ማህበራዊ ገጽ (ፌስ ቡክ) እንዲሁም በድረገጹ አማካኝነትም አትሌቶችን ተደራሽ ሲያደርግ ቆይቷል። በዚህ ሂደትም ፌዴሬሽኑ ማድረግ የሚገባውን መልካም ተግባር ማከናወኑን ለመታዘብ ተችሏል። አትሌቶችና ሌሎች ባለሙያዎችም ለዚህ የሚሰጡት ግብረ መልስ ጥሩ ሥራ መሰራቱን የሚያሳይ ነው። አትሌቶች ቤታቸው በሚሆኑበት ወቅት ምን መስራት እንዳለባቸው ግራ ተጋብተው ነበር የሚሉት ዳይሬክተሩ፣ አሰልጣኞች በሚሰጧቸው አቅጣጫ ተጠቃሚ ሆነዋል። በተለያዩ ክልሎች ለሚገኙና እነዚህን አማራጮች የማያገኙ አትሌቶችን ደግሞ አሰልጣኞች በስልክና በሌሎች መንገዶች በተመሳሳይ እየረዷቸው ይገኛሉ። አሁን ካለው ሁኔታ አንጻር ጥናት መስራትና አትሌቶችን ማግኘት ባይቻልም በተለያዩ መንገዶች ምስጋናቸውን ያደርሳሉ። በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ምክር የሚጠይቁ አትሌቶች ቁጥር መበራከትም ይህንኑ የሚያመላክት ነው። አሰልጣኞች በበኩላቸው ወትሮ ከነበረው ሁኔታ በተሻለ መልኩ ከፌዴሬሽኑ ጋር ያላቸውን ግንኙነት ያጠናከሩ ሲሆን፤ ግብረመልስ በመስጠትም አጋርነታቸውን እያሳዩ ነው። ከዚህ በኋላም ፌዴሬሽኑ ማህበራዊ ኃላፊነቱን ከመወጣት ጎን ለጎን መርሃ ግብሩን በአዲስ መልክ የሚያስቀጥልም ይሆናል። የሀገርን ስም በዓለም አቀፍ ደረጃ ያስጠራው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ወረርሽኙን ለመቆጣጠር በሚደረገው ርብርብ ቅድሚያ ተሰላፊ መሆኑን በተግባር በማሳየት ላይ እንደሚገኝ ይታወቃል። ከዚህ ቀደም በግሉ፣ ከሌሎች ተቋማት ጋር እንዲሁም በአትሌቶቹ አማካኝነት በገንዘብ እንዲሁም በቁሳቁስ የድርሻውን በማድረግ ላይ ይገኛል። አመራሩና ሌሎች ታዋቂ አትሌቶችም ለሕዝቡ መልዕክት በማስተላለፍ ላይ ናቸው። አሁንም ከዚህ በላቀ መልኩ ለመስራት የሚያስችል ተነሳሽነት አለ። እንደሚታወቀው በዚህ ወቅት ውድድሮችና ሌሎች የሥልጠና መርሃ ግብሮች ተቋርጠዋል። በዚህ ምክንያት ፌዴሬሽኑ ቀድሞ የያዛቸውን እቅዶች በመቀየር የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሃ ግብሮች ላይ ለማተኮር ማቀዱን ዳይሬክተሩ ይጠቁማሉ። በዚህም ከፌዴሬሽኑ ስፖንሰር ማልታ ጊነስ ጋር በመሆን በቴሌቪዥን የሚተላለፉ መርሃ ግብሮችን በመስራት ላይ ነው። በአንድ ወር ውስጥ ለ16 ቀናት ያህል የሚተላለፈው መርሃ ግብሩ እንደ ቀድሞ በምክረ ሃሳብ ላይ ሳይሆን በተግባር ላይ የተመሰረተ እንደሚሆንም ታውቋል። በአትሌቶች ዘንድ ተምሳሌት የሆኑና ዝነኛ አትሌቶች እንዲሁም ባለሙያዎች የሚሳተፉበት ሲሆን፤ ተከታታይነት ያላቸው እንቅስቃሴዎች በምን መልኩ እንደሚሰሩ የሚያሳይም ይሆናል። እንቅስቃሴው ከአትሌቶች ጋር ብቻ ሳይሆን ሌላውን ኅብረተሰብም የሚጠቅምም ነው የሚሆነው። ለዚህ የሚሆነው ዝግጅት በመጠናቀቁ በቅርቡ አየር ላይ የሚውልም ይሆናል። በዚህ ወቅት አብዛኛው ኅብረተሰብ ትኩረቱ የመገናኛ ብዙኃን ላይ በመሆኑ፤ ትብብራቸውን እንዳያቋርጡ ይጠይቃሉ። ከቴሌቪዥን ባሻገር በርካቶችን ተደራሽ የሚያደርጉ የመገናኛ ብዙኃን አብሮነታቸውን እንዲያሳ ዩም ጠይቀዋል።አዲስ ዘመን ግንቦት 19/2012 ብርሃን ፈይሳ
https://www.press.et/Ama/?p=33175
592
2ስፖርት
እነ አፋጀሽኝ…
መዝናኛ
October 31, 2019
38
 ‹‹እንዲህ አይነት ጭንቅ ጥብብ ያለ የአፋጀሽኝ ዘመን በእድሜዬ አላየሁም›› አሉ ሼሁ። የተዘባረቀ፤ የተጭበረበረ፤ የተወናገረ፤ የተወሳለተ ዘመን። ‹‹አላህ አላህ›› አሉ መለሱና። ሼሁ የእድሜ ባለጸጋ የተከበሩ አንቱ የተባሉ አባት ናቸው። መካሪ ዘካሪ አስታራቂ በመንደሩ በሰፈሩ በሀገሩም የተከበሩ። ሼሁ መኖሪያ አቅራቢያ አብረው ረዥም ዘመን የኖሩ ጎረቤታቸው ቄስ አሉ። መምሬ ደምሌ። ሁለቱም የብዙ ልጆች አባት ልጅና የልጅ ልጅ ያዩ ናቸው። ቃላቸው እንደ ፈጣሪ ቃል ይከበራል። ደግሞም ይፈራል። ሁለቱም ወደ የቤተ እምነታቸው ሲሄዱ ቦታው ቢለያይም አብረው እያወጉ እየተማከሩ እየተወያዩ ነው የሚሄዱት። አይለያዩም። የሀገር አድባሮች። ለሼሆቹም ለቄሶቹም እድሜና ጤና አብዝቶ ይስጥልን፡፡ ‹‹ቄስ፤ መነኮሳት ሼሆችን የሚያርድ ፤ መስጊድና ቤተክርስቲያን የሚያነድ የሚያጋይ የሚያቃጥል ነፍሰ በላ አውሬ ሕዝቡን ሲጨርሰው በሀገር ሲዘምት ፈጣሪ እንዴት አይቆጣ›› አሉ መምሬ ደምሌ በስጨት ብለው። ሼሁ በረዥሙ የተንዠረገገውን ጺማቸውን በሀሳብ ተውጠው እያልመዘመዙ በሚሰሙት በሚያዩት በሚነገራቸው የሰላም እጦት፤ የዜጎች መገደል፤ የእናቶችና የሕጻናት እንክርት፤ ስደት፤ መጠለያ ማጣት ሁሉ ‹‹አቤቱ በደላችንን ይቅር በለን፤ አላህ›› እያሉ ተንሰቅስቀው ያለቅሳሉ። ያዝናሉ። ‹‹ኧረ ይህች ሀገር እንዲህ አልነበረችም ምን መጣብን›› ይላሉ። አብዝተው ይጨነቃሉ። ይጠበባሉ። ያዝናሉ። ሼሁ የጥንቱ የወሎ ሼሆች ዝየራ ትዝ አላቸውና በለሆሳስ ማንጎራጎር ጀመሩ። በእንዲህ አይነት ዘመን… አይተኙም ይነቋል…፤ መሳሪያውን ስሎ በየጎራው ዘልቋል፤ አሉ። ክፉ ዘመንን የሚያስታውሳቸው ነበር። ለጠቁና ፈጣሪ ለሀገራችን ለሕዝቧ ምህረቱን አብዝቶ ያውርድልን አሉ። ዱአቸውን ቀጠሉ ሼሁ። መለስ ብለው ልመና ዱአ ነው ደጉ የጠፋውን የሚያለማው፤ ጠማማውን የሚያቀናው፤ ክፉውን የሚያገራው፤ ዱአ (ጸሎት) ነው። ሁሉም እንደ የእምነቱ ወደ የፈጣሪው መጸለይ ነው የሚበጀው አሉ ሼህዬ። ‹‹ሌላማ ምን ይባላል መቸስ›› አሉ በቁጨት እየተብሰለሰሉ። መምሬ ደምሌ ከሼሁ ቀበል አድርገው፤ ‹‹ጦቢያ የምትባል ሀገር እንደሁ የሰው ዘር መነሻ፤ እስላም ክርስቲያኑ በአንድ ተፈትሎ፤ በአንድ ተገምዶ፤ በአንድ ተሰድሮ፤ ከጥንት እስከ አሁን የኖረባት ወደፊትም የሚኖርባት እግዚአብሔር የባረካት ሀገርና ምድር ናት። ልጆቿ እሾህና አሜከላ እየሆኑ ሲጥሏት ሲያነሷት ይኖራሉ። ግን ግን አትወድቅም። አትጠፋም። ጠላቶቿ ግን ይጠፋሉ›› አሉና ፊታቸውን ወ ደ ሼሁ አዞሩ መምሬ። በሰርግ በደስታ በፌሽታ በሀዘኑ በበዓሉ አብረን ሁነን፤ አብረን በልተን ጠጥተን ተጫውተን፣ ድረን፣ ኩለን ኖረናል። ዘመናትን ገፍተናል። የወደፊቱን እሱ ያውቃል። እንግዲህ መቸም ተፈርቶ አይሞት፤ ዱአ የበዛ ዱአ ማድረግ ያስፈልጋል መምሬ ሰሙኝ አሉ ሼሁ በተራቸው። መምሬ ቀጠሉ፡፡ ‹‹እንዲህ አይነት መላቅጡ የጠፋ ወንድም ወንድሙን የሚገድልበት ግዜ በሀገራችን አይተን ሰምተንም አናውቅም። በብርቱ አዝነናል። ፈጣሪ ሀዘናችንን አይቶ ምላሽ ይሰጣል። ሀገር መበጥበጥ፤ ሰላሟን ማናጋት ሕዝቡን ሰላም መንሳት፤ መንገድ መዝጋት፤ ቤተ እምነት ማቃጠል ዘር ለይቶ ማጥቃት፤ በሰይጣኖች የተቀነባበረ ሴራ መሆኑን ሕዝበ ሙስሊሙም ሕዝበ ክርስቲያኑም ጠንቅቆ ያውቃል። እንግዲህ እንደየ እምነታችን በእነአፋጀሽኝ ላይ እርግማን አውርደናል›› አሉ መምሬ ደምሌ። ሕዝብን ለመለያየት ደም ለማቃባት እርስ በእርሱ ለማባላት ያሴሩት ሴራ ሁሉ ተበትኖ ይጠፋሉ። ሴራቸው እንደ ጉም እንደ ጠዋት ጤዛ ይበናል። የተመኙትን ወንበር አይቀመጡበትም። የሰበሰቡትን ሀብት አይበሉትም። የተከበረ የሰውኛ ቀብር እንኳን አያገኙም። ኢትዮጵያን እናጠፋለን ብለው ሲነሱ ጸባቸው ከሕዝቧ ጋር ብቻ አይደለም። ጠብቆ አጽንቶ ከፈተናዎች ሁሉ እያወጣ ካኖራት ታላቅ አምላኳ ጋር ነው። ይጠፋሉ። ድህነትን መከራን ከትውልድ ትውልድ ይወርሳሉ። ጉልበታቸውና ሴራቸው ይሰበራል። ዝንተ ዓለም በድህነት በስደት በረሀብ በመከራ እየተገረፉ ተንከራተው ይኖራሉ። መሳሪያ ዎቻቸው ይደነብሻሉ። አይተኩሱም። አይመቱም። ቀኑ ጨለማ ይሆንባቸዋል። ኢትዮጵያ ግን ሴራቸውን ሁሉ እንደጉም አብንና አጥፍታ ተመልሳ ታላቅ የተከበረች ሀገር ትሆናለች። የሚሻለው ባይነኳት ነበር። አምላኳ እጅግ ኃይለኛ ብርቱ የማይንበረከክ የማይተኛ ከነኩት የማይለቅ በቀለኛም ነው። እነአፋጀሽኝ የሼሆቹንና የቄሶቹን እምባና ሀዘን ልኩን አላወቁትም። የአባቶች እምባስ የት ያደርስ ይሆን? አህዛብ ወዮልህ ማለት ይሄኔ ነው። የሚሆነው ይሆን ዘንድ ግድ ነው። ዘመንና ወቅት ይፈራረቃል። ቀንና ሌሊትም እንዲሁ። ኢትዮጵያም ፈተናዎችን ሁሉ አልፋ ታፍራና ተከብራ ለዘለአለም ትኖራለች፡፡አዲስ ዘመን ጥቅምት20/2012 ወንድወሰን መኮንን
https://www.press.et/Ama/?p=21738
500
1መዝናኛ
ኢትዮጵያ 50 ዓመታት የተጠቀመችበትን የንግድ ህግልትቀይር ነው
ሀገር አቀፍ ዜና
January 3, 2021
24
 ክፍለዮሐንስ አንበርብርአዲስ አበባ፡- ኢትዮጵያ ለግማሽ ክፍለ ዘመን ስትጠቀምበት የነበረውን የንግድ ህግ ከዘመነ ቴክኖሎጂ ጋር የተናበበና ነባራዊ ሁኔታዎችን ባገናዘበ አዲስ ህግ ልትቀይረው መሆኑን ተገለጸ። አገሪቷ ከምትጠቀምባቸው መድሃኒቶች ውስጥ 80 ከመቶ የሚሆነው በውጭ ምንዛሪ ተገዝቶ ወደ አገር ውስጥ የሚገባ መሆኑም ተገለጸ።የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስትር ድኤታ አቶ ምስጋኑ አረጋ በተለይ ለአዲስ ዘመን እንዳስታወቁት ፤ ኢትዮጵያ ግማሽ ክፍለ ዘመን ስትጠቀምበት የነበረው የንግድ ህግ ከዘመነ ቴክኖሎጂ ጋር የተናበበና ነባራዊ ሁኔታዎችን ባገናዘበ መልኩ በአዲስ ህግ ልትተካ ነው።አገሪቷ እያካሄደች ያለው የምጣኔ ሀብት ማሻሻያ መርህ በዋናነት በማክሮ ኢኮኖሚ፣ መዋቅራዊ እና የዘርፍ ማሻሻያ ላይ ትኩረት ያደረገ መሆኑን ጠቁመው ፣ በዚህም በአሁኑ ወቅት ሁለንተናዊ ለውጦችን ለማምጣት ከመቼውም በላይ እየተንቀሳቀሰች መሆኑን አብራርተዋል። እንደ ሚኒስትር ድኤታው ገለፃ፤ እየተደረጉ ካሉ ማሻሻያዎች መካከል 50 ዓመታትን በሥራ ላይ የነበረው የንግድ ህግ ዘመኑ የደረሰበትን የዕድገት ደረጃ ባገናዘበ መልኩ የማሻሻል እና ህግ ሆኖ የማውጣት ሂደቱ ከጫፍ መድረሱን አብራርተዋል። በአሁኑ ወቅትም የተረቀቀው ህግም ለተወካዮች ምክር ቤት መላኩን ጠቁመው ። ውይይት ከተደረገበትና የተወካዮች ምክር ቤት ይሁንታን ካገኘ በኋላ ወደ ሥራ እንደሚገባ ጠቁመዋል። ይህም አገሪቱ የጀመረችውን ዕድገት ለማፋጠን እና አቅም በፈቀደ መጠን የንግዱን ማህበረሰብ ጥያቄ ለመመለስ አጋዥ እንደሚሆን አመልክተዋል። የዓለም ማህበረሰብ በአሁኑ ወቅት በቴክኖሎጂ በመታገዝ ከፍተኛ ግብይት እያካሄደ ይገኛል ያሉት ሚኒስትር ድኤታው፤ የመጠቁ አገራት የንግድ ፈቃዳቸውን ጨምሮ ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮችንና መረጃዎችን በቴክኖሎጂ በመታገዝ በኦንላይን እያስተናገዱ ይገኛል ብለዋል። ይሁንና ኢትዮጵያ ከዚህ አኳያ እጅጉን ወደ ኋላ የቀረች በመሆኑ እነዚህንና መሰል ጉዳዮችን ታሳቢ ያደረጉ ማሻሻያዎች እየተደረጉ መሆኑን አስታውቀዋል።የኢትዮጵያ የንግድ አካሄድ ሚዛን ያልጠበቀ መሆኑን የጠቆሙት አቶ ምስጋኑ ፣ በቀጣይ እነዚህን ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ ይሠራል ብለዋል። ለአብነትም አገሪቱ ከምትጠቀምባቸው መድሀኒቶች ውስጥ 80 ከመቶ የሚሆነው በውጭ ምንዛሪ ተገዝቶ ወደ አገር ውስጥ እንደሚገቡ አመልክተዋል። በዘርፉ ሀገር ውስጥ ያሉ አምራቾችን አቅም በማጎልበትና በቁጥር እንዲበዙ በማድረግ ከሀገር ውስጥ ፍጆታ በተጨማሪ ለውጭ ገበያ እንዲያቀርቡ ለማድረግ መንግሥት ከአምራቾች ጋር በቅርበት የሚሠራ መሆኑን ሚኒስትር ድኤታው አረጋግጠዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 25/2013
https://www.press.et/Ama/?p=38749
276
0ሀገር አቀፍ ዜና
ኮሚሽኑ የኮቪድ- 19 ወረርሽኝ ለመዋጋት ጠንካራ ሥራዎችን መስራቱን ገለጸ
ስፖርት
May 12, 2020
19
የአዲስ አበባ ስፖርት ኮሚሽን የኮቪድ- 19 ወረርሽኝ ለመዋጋት የስፖርት ቤተሰቡንና ባለድርሻ አካላት በማሳተፍና በማስተባበር ጠንካራ ሥራዎችን መስራቱ ተገለጸ። በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስፖርት ኮሚሽን በበጀት ዓመቱ የታቀዱ ዕቅዶችና ከተከሰተው የኮቪድ- 19 ወረርሽኝ አንፃር የተከናወኑ አበይት ተግባራት ትናንት ለማህበራዊ ዘርፍ ተቋማት ሱፐር ቪዥን ቀርበው ግምገማ ተደርጎባቸዋል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዮናስ አረጋይ በዕለቱ እንደተናገሩት፤ በ2012 ዓ.ም በጀት ዓመት ባለፉት ዘጠኝ ወራት ቁልፍና አበይት ዕቅዶችን አውጥቶ በታዳጊ ወጣቶች ስልጠና መርሀ ግብር፣ በማስ ስፖርት (በማህበረሰብ አቀፍ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ) በስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች ልማት፣ በውድድርና ተሳትፎ፣ እና በተቋማዊ ለውጥ ሥራ በሽታው ከመከሰቱ በፊት በርካታ ሥራዎች ማከናወን ተችሏል። አቶ ዮናስ አክለው «ዓለም አቀፍ ስጋት የሆነው ኮቪድ-19 ወረርሽኝ መከሰቱን ተከትሎ ከመደበኛ ሥራው ትይዩ ቫይረሱ ከተከሰተ ጀምሮ በከተማ አቀፍ ደረጃ ወረርሽኙን ለመዋጋት እንቅስቃሴዎች ሲደረጉ ነበር። የአዲስ አበባ ስፖርት ኮሚሽን በበጀት ዓመቱ የኮቪድ- 19 ወረርሽኝ ለመዋጋት የስፖርት ቤተሰቡንና ባለድርሻ አካላት በማሳተፍና በማስተባበር ጠንካራ ሥራዎቹን አከናውኗል ሲሉ ገልጸዋል። ኮሚሽኑ የኮቪድ- 19 ወረርሽኝ ለመዋጋት በከተማ ደረጃ በአብይ ኮሚቴ ውስጥ በመሳተፍ እነዚህን ሥራዎች ሲያከናውን እንደነበር ገልፀው፤ የስፖርት ቤተሰቡንና ባለድርሻ አካላት በማሳተፍና በማስተባበር በገንዘብና የቁሳቁስ ድጋፍ ለከተማ አስተዳደሩ ማስረከባቸው፣ ለታማሚ የሚሆን የቅድመ ቦታ መለየትና ማዘጋጀት፣ ለወገን ወገን በመሆኑ የደም ልገሳ መመደረጉ፣ የኮሮና ቫይረስ ቅድመ መከላከል የግንዛቤ ማስጨበጫ ሰፊ ሥራዎች መሠራታቸው እና በተለይ በቤታቸው ቫይረሱን ለመከላከል የሚኖሩ የጋራ መኖሪያ ኮንዶሚኒየም ነዋሪዎች ቤታቸው አካላዊ ርቀትን ጠብቆ የተሰሩ የአካል ብቃት እንቅስቃሴዎችን ከብዙ በጥቂቱ ናቸው። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የማህበራዊ ዘርፍ ተቋማት ዋና አስተባባሪ አቶ ሀይለሰማዕት መርሀጥበብ በበኩላቸው፤ ኮሚሽኑ በበጀት ዓመቱ ያከናወናቸው ተግባራት እጅግ የሚያስደስቱና የሚበረታቱ እንደሆኑ አመልክተዋል።ኮሚሽኑ በቀጣይ የስራ አቅጣጫ ላይ ያሉበትን ክፍተቶች በመሙላት የበለጠ ለውጤት መብቃት እንደሚገባው አስገንዝበዋል። አዲስ ዘመን ግንቦት 4/2012 ዳንኤል ዘነበ
https://www.press.et/Ama/?p=32176
253
2ስፖርት
የ12ኛ ክፍል ሃገር አቀፍ ፈተናን ለመውሰድ 311 ሺህ 421 ተማሪዎች ተመዝግበዋል
ሀገር አቀፍ ዜና
January 3, 2021
53
 ዳንኤል ዘነበ አዳማ፦ በሀገር አቀፍ ደረጃ የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ የብቃት መመዘኛ ፈተና ለመውሰድ እስከ አሁን 311 ሺህ 421 ተማሪዎች መመዝገባቸውን የሀገር አቀፍ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጀንሲ አስታወቀ። በሀገሪቱ ለመጀመሪያ ጊዜ በኦንላይን ለሚደረገው የ12ኛ ክፍል ሃገር አቀፍ ፈተና 500 ሺ ታብሌቶች ተዘጋጅተዋል። በሀገር አቀፍ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጀንሲ የተፈታኞች ምዝገባና ውጤት ጥንቅር ዳይሬክተር አቶ ዩሴፍ አበራ በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደገለጹት፤ የአጠቃላይ ሀገር አቀፍ የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ብቃት መመዘኛ ፈተና ከጥር 30 ቀን 2013 ዓ.ም በኋላ ለመስጠት መርሐግብር ተይዟል። በዚህ መሰረት የተማሪዎች ምዝገባ መደረጉን ገልጸው፤ በሀገር አቀፍ ደረጃ የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ብቃት መመዘኛ ፈተና ለመውሰድ እስከ አሁን 311 ሺህ 421 ተማሪዎች መመዝገባቸውን አስታውቀዋል። ምዝገባው ከትግራይ ክልል እና ከቤንሻንጉል ጉምዝ መተከል ዞን በስተቀር በሁሉ የሀገሪቱ ክፍሎች በሚገኙ ትምህርት ቤቶች መካሄዱን የገለጹት ኃላፊው፣ በትግራይ ክልልና በመተከል ዞን ካጋጠመው የጸጥታ ችግር ጋር በተያያዘ ተማሪዎችን ለመመዝገብ እንዳልተቻለ አመልክተዋል። በትግራይ ክልልና በመተከል ዞን ቀደም ሲል ምዝገባ የተጀምረ ቢሆንም ከጸጥታ ችግር ጋር ተያይዞ መቋረጡን አስታውሰው፤ በእነዚህ አካባቢዎች የሚገኙ ተማሪዎችን ለመመዝገብ የሚያስችል ሁኔታ ለመፍጠር እየተሠራ ይገኛልም ብለዋል። በትግራይ ክልል 80 ያህል ትምህርት ቤቶች እንዲሁም በመተከል ደግሞ እስከ 14 ትምህርት ቤቶች አሉ ተብሎ ይገመታል፣ በእነዚህ ትምህርት ቤቶች የሚገኙ ተማሪዎች ምዝገባ ከተደረገ ቁጥሩ ይጨምራል ተብሎ እንደሚጠበቅ አስታውቀዋል። ሀገር አቀፍ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ዲላሞ ኦቶሬ በበኩላቸው፤ መንግሥት በወሰደው ቁርጠኛ አቋም ትምህርት ሚኒስቴር እና ኤጀንሲው በመቀናጀት የሁለተኛ ደረጃ መልቀቂያ የ12ኛ ክፍል ፈተናን በኦንላይን ለመፈተን መደረግ የሚገባቸው ቅድመ ዝግጅቶች እያጠናቀቁ መሆኑን ገልጸዋል። በሀገራችን ለመጀመሪያ ጊዜ በኦንላይን ለሚደረገው የ12ኛ ክፍል ፈተና 500 ሺ ታብሌቶች መዘጋጀታቸውን አስታውቀዋል። በክልሎች ደረጃ የሚገኙ የፈተና ጣቢያዎች ከወዲሁ ለሂደቱ አስፈላጊ የሆኑ መሰረተ ልማቶችን አሟልተው እንዲገኙ ከፌዴራል በወረደላቸው አቅጣጫ መሰረት እየተንቀሳቀሱ እንደሚገኙ አመልክተዋል። በዘንድሮ አዲስ ቴክኖሎጂ ይዘን ወደ ተማሪዎቻችን የምንቀርብ ከመሆኑ አንጻር ከመቼውም ጊዜ በበለጠ ከኤጀንሲው ባለድርሻ አካላት ድጋፍ ያስፈልገናል ብለዋል። ባለድርሻ አካላትም አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል። በትምህርት ሚኒስቴር የአጠቃላይ ትምህርት ጥራት ማረጋገጥ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ወይዘሮ ሑሪያ አሊ በበኩላቸው፤ የብሔራዊ ፈተናዎች አሰጣጥ ባህላዊነት ጋር ተያይዞ ከፍተኛ ወጪ፣ ውስብስብ አሠራር፣ ስርቆትና ኩረጃ፣ አድካሚ የሥራ ሂደትና ሌሎች ዘርፈ ብዙ ተግዳሮቶች አሉበት ብለዋል። ኮምፒውተርን መሰረት ያደረገ የፈተና ሠርዓት መዘርጋት ችግሩን ለመቅረፍ፣ አሊያም ለመቀነስ አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ እንደሆነም አብራርተዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 25/2013
https://www.press.et/Ama/?p=38751
333
0ሀገር አቀፍ ዜና
መገናኛ ብዙሃን በቅርበት አብረውት እንዲሠሩ የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ ጥሪ አቅረበ
ሀገር አቀፍ ዜና
January 3, 2021
14
 በኃይሉ አበራአዲስ አበባ፦ መገናኛ ብዙሃን በቅርበት አብረውት እንዲሠሩ የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ ጥሪ አቀረበ። ተቋማቱ የሚያሰራጯቸው መረጃዎች ተአማኒነት በአግባቡ ሊፈተሸ እንደሚገባ አሳሰበ።የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ በሀገራችን በተለያዩ ጊዜያት በሰው ሕይወትና በንብረት ላይ እየደረሰ ያለውን ውድመት አስመልክቶ ትናንት በፅሕፈትቤቱ በሰጠው መግለጫ፣ የአካዳሚ ፕሬዚዳንት ፕሮፌሰር ፅጌ ገብረማርያም እንዳስታወቁት፣ ሀገራችን ለዓለም የሚተርፍ ሀብት ባለቤት ብትሆንም በታሪካችን ሂደት ባስተናገድናቸው የእርስበርስ ጦርነቶችና ግጭቶች የተነሳ ሳንጠቀምበት ቀርተናል ብለዋል።አካዳሚው በተለያዩ ሙያዎች ከፍተኛ ልምድ ያካበቱ፤ ያካበቱትን እውቀትና ተሞክሮ መሰረት በማድረግ ለሀገርና ለህዝብ የሚጠቅሙ ምክረ ሃሳቦች ሊሰጡ የሚችሉ ምሁራን የሚገኙበት መሆኑን ጠቁመው፣ መገናኛ ብዙሃን ይህንን ሀገራዊ አቅም ለመጠቀም ከተቋሙ ጋር በቅርበት እንዲሠሩ ጥሪ አቅርበዋል።ማንም ዜጋ የመኖር መብት ያለው ቢሆንም፣ በሀገራችን የመኖር መብት ጥያቄ ውስጥ እየገባ መሆኑን አመልክተዋል። ይህ መብት በማንም መወሰድ እንደሌለበትም አሳስበዋል።አካዳሚው በተለይም ከሁለት ዓመታት በፊት በሀገሪቱ ተከስተው የነበሩ አለመረጋጋቶችን ለመቅረፍ የሚያስችሉ የፖሊሲ ግብአቶች እና በመርህ ላይ የተመሰረቱ የተለያዩ ሃሳቦች ሲያቀርብ መቆየቱን አስታውሰዋል። አካዳሚው በመርህ ደረጃ ጥናትን መሰረት ያደረጉ መረጃዎችን ለሀገራዊ፣ አህጉራዊ እና ዓለም አቀፋዊ ተቋማት እየሰጠ እንደሚገኝ አመልክተዋል። የአካዳሚው የቦርድ አባል ዶክተር ፀደቀ አባተ በበኩላቸው፣ ከጥላቻ፣ ከግል ጥቅም እና የመሳሰሉ አፍራሽ ሁኔታዎችን ከማስወገድ አንጻር የመገናኛ ብዙሃን ሰፊ ሚና ሊጫወቱ ይገባል ብለዋል።በእለቱ በጽሑፍ በተነበበው የአካዳሚው የአቋም መግለጫ ፣ መንግሥት በሀገራችን የህግ የበላይነት ለማስፈን የሚወስደውን እርምጃ አካዳሚው እንደሚደግፍ ገልጸው ፣ እርምጃውም በሁሉም አካባቢ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ፤ ከቤት ንብረታቸው ለተፈናቀሉ ዜጎችም ሰብዓዊ ድጋፍ እንዲደረግላቸውም ጠይቀዋል።በሶሪያ እና በሊቢያ እና በየመን እንደታየው ሁሉ በሀገራችንም መሰል ቀውስ እንዳይፈጠር ዜጎች ልዩነቶቻቸውን በውይይት ብቻ እንዲፈቱም መልእክት አስተላፈዋል።አካዳሚው ከ177 በላይ አባላት ያሉት መሆኑም በወቅቱ ተገልጿል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 25/2013
https://www.press.et/Ama/?p=38753
230
0ሀገር አቀፍ ዜና
የጅት ኩንዶው ማዕከል ምስጉን የረድዔት ተግባር
ስፖርት
May 14, 2020
22
ስፖርት ከአካላዊ እንቅስቃሴና ከመዝናኛነት ባለፈ ማህበራዊ ግዴታን በመወጣት ረገድ ትልቅ ፋይዳ እንዳለው በተለያዩ አጋጣሚዎች ታይቷል። በተለይም ዓለም በኮሮና ቫይረስ(ኮቪድ 19) ምክኒያት ጭንቅ ውስጥ በገባችበት በዚህ ወቅት ስፖርትና የስፖርቱ ማህበረሰብ ማህበራዊ ግዴታን በመወጣት በኩል እያበረከተ የሚገኘው አስተዋፅኦ እዚሁ አገራችንም ትልቅ ቦታ እንዳለው መታዘብ ይቻላል። ኤርሚያስ ገሰሰ ጂምና ማርሻል አርት ማዕከል ወጣቶችን በጅት ኩን ዶ እንቅስቃሴ ከማብቃት ጎንለጎን የበጎ አድራጎት ስራዎች ላይ ንቁ ተሳትፎ በማድረግ ይታወቃል። የበጎ አድራጎት ስራ ከማርሻል አርት ስፖርት ጋር አብሮ እንደሚሄድ የሚናገረው ማስተር ኤርሚያስ ወጣቶች ማርሻል አርትን ሲማሩ የስነምግባር ትምህርትም አብሮ እንደሚሰጣቸው ያብራራል። ይህ የስነ ምግባር ትምህርት መገለጫው ደግሞ በጎ ተግባር ነው። 1995 ዓ.ም አካባቢ የተማሪ ቤተሰቦች፣በጎ ፍቃደኞችና ሌሎችም በጋራ ሆነው የስፖርቱን እንቅስቃሴ ሲጀምሩ ገንዘብ በማዋጣት ጎዳና ላይ ያሉ ወገኖችን በምግብ፣ በአልባሳት ድጋፍ ከማድረግ ባሻገር በዘላቂነት በማቋቋም መደበኛ ትምህርታቸውን እንዲከታተሉ እያደረገም ይገኛል። የበጎ አድራጎት ስራውን ከስፖርቱ ባሻገር ለማስፋት በቅርቡ ‹‹ዿጉሜ 5 የበጎ አድራጎት ድርጅት›› በሚል ስያሜ በማሳደግ እውቅና አግኝቶ እየተንቀሳቀሰም ነው። በየዓመቱም የትንሳዔን በዓል ምክኒያት በማድረግ በጎዳና ላይ ያሉ ወገኖችን የመመገብ፣አልባሳትንና ገንዘብ የመስጠት መርሃግብሮችን ያካሂዳል። መማር የሚችሉ እንዲማሩ፣መስራት የሚችሉ እንዲሰሩ ማድረግም አንዱ ተግባሩ ነው። በዚህም የበርካታ ወጣቶችን ሕይወት መለወጥ ተችሏል። ይህ ምስጉን የረድዔት ተግባር በየጊዜው እያደገ ሄዶም ኤርሚያስ ገሰሰ ጂምና ማርሻል አርት ማዕከል ከ‹‹ዿጉሜ 5 የበጎ አድራጎት ድርጅት›› ጋር በመተባበር ባለፈው እሁድ ሃያ ሁለት የጎዳና ልጆችን በማንሳት ማዕድ ከማጋራት ባሻገር መስራት የሚችሉ ወደ ስራ እንዲገቡ፣ ወደ ቤተሰብ የመመለስ ፍላጎት ያላቸው አስፈላጊው ነገር ተሟልቶላቸው እንዲመለሱና በዘላቂነት እንዲቋቋሙ እስከ ማድረግ የደረሰ የረድዔት ተግባር አከናውኗል። በስፖርቱ የሚሳተፉ ወደ በጎ አድራጎት ድርጅቱ አባልነት እንዲካተቱ በማድረግ ችግርተኛ ወጣቶች ላይ ትኩረት አድርጎ እየተሰራ መሆኑን የሚናገረው ማስተር ኤርሚያስ አምስት መቶ ያህል አባላት ያሉት የበጎ አድራጎት ድርጅት ከዚህም በላይ የረድኤት ስራዎችን የማከናወን ፍላጎት ቢኖረውም ከጎዳና ላይ የሚያነሳቸውን ልጆች ማሳደሪያ ወይም ማረፊያ ቦታ ትልቁ ችግር እንደሆነ ያስረዳል። ተረጂዎቹ ወጣቶች ቢታመሙም የሕክምና ጉዳይ አሳሳቢ እንደሆነባቸው ገልጿል። በዚህ ረገድ ማንኛውም አካል ቢደግፋቸው ሌሎቹን አስፈላጊ ግብዓቶች ለማሟላት እንደማይከብድም ይናገራል። በተለይም እነዚህ ከበጎ አድራጎት ድርጅቱ አቅም በላይ የሆኑ ችግሮች ከኮሮና ቫይረስ ስርጭት ጋር በተያያዘ አሁን ያለንበት አስቸጋሪ ጊዜ እስኪያልፍ ማንኛውም አካል ትብብር እንዲያደርግ ጥሪውን አቅርቧል። ይህም ልጆቹን ከቫይረሱ ተጋላጭነት ከመጠበቅ ባለፈ የቫይረሱን ስርጭት ለመቆጣጠር በሚደረገው ርብርብ ትልቅ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው ያለውን እምነት ተናግሯል። በቀጣይም ሌሎች ወጣቶችን ከጎዳና ለማንሳት ጥረት እንደሚደረግ ቃል ገብቷል። ባለፈው እሁድ ማዕድ የማጋራት መርሃግብሩ ሲከናወን በስፍራው የተገኙት የቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ አስራ አራት ዋና አስፈፃሚ ወይዘሮ ወይንሸት አስናቀ፣ የስፖርት ማዕከሉና የእርዳታ ድርጅቱ ከወረዳው አስተዳደር ጋር በመሆን መሰል ስራዎችን ከዚህ ቀደምም ሲያከናውን መቆቱን ተናግረዋል። በተለይም በኮሮና ቫይረስ ስጋት የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ ኢንጂነር ታከለ ኡማ ማዕድ የማጋራት መርሃግብርን ይፋ ካደረጉ ወዲህ የስፖርት ማዕከሉና የእርዳታ ድርጅቱ በጋራ በመሆን ጎዳና ላይ ያሉ ወጣቶችን ትኩረት አድርጎ እየሰራ እንደሚገኝ መስክረዋል። ‹‹በወረዳችን በርካታ ጎዳና ላይ ያሉ ወጣቶች አሉ›› ያሉት ዋና ስራ አስፈፃሚዋ እነዚህን ወጣቶች ማዕድ ከማጋራት ባለፈ ወደ ስራ እንዲሰማሩና እንዲቆጥቡ በማድረግ፣ ወደ ትምህርት እንዲመለሱ አስፈላጊውን ድጋፍ በማድረግ እንዲሁም ወደ ቤተሰባቸው መመለስ የሚፈልጉትን በመመለስ በርካታ ተግባራት መፈፀማቸውን አስታውሰዋል። ሌሎችም ከዚህ ምስጉን ተግባር በመማር ተመሳሳይ የረድዔት ስራዎችን እንዲሰሩ በማድረግ የስፖርትን ማህበራዊ ኃላፊነት በተግባር ማሳየት እንደሚያስፈልግ ጠቁመዋል። ወረዳው የስፖርት ማዕከሉና የረድዔት ተቋሙ የሚያደርጉትን በጎ ተግባር ለመደገፍም ማደሪን የመሳሰሉ ችግሮችን ለመቅረፍ ጥረት እንደሚያደርግ ቃል ገብተዋል። አዲስ ዘመን ግንቦት 6/2012ቦጋለ አበበ
https://www.press.et/Ama/?p=32321
483
2ስፖርት
አጫጭር ዜናዎች
ስፖርት
May 15, 2020
22
አትሌት ፶ አለቃ ታደሰ በቾ አዳሙ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ አትሌት ፶ አለቃ ታደሰ በቾ አዳሙ በተወለዱ በ55 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ። አትሌቱ ከ1984 ዓ. ም ጀምሮ በሀገር ውስጥ፣ በአህጉርና በዓለም አቀፍ ደረጃ የረጅም ርቀት ሩጫ ውድድሮች ላይ በመካፈል ክለባቸውን አየር ኃይልንና ኢትዮጵያን ወክለው በመሰለፍ በድል ማስጠራት የቻሉ ውጤታማ አትሌት ነበሩ። አትሌት ፶ አለቃ ታደሰ ባጋጠማቸው የጤና እክል ምክንያት በህክምና ሲረዱ ቆይተው ግንቦት 5ቀን 2012 ዓ. ም. ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩ ሲሆን፤ የቀብር ሥነ ሥርዓታቸው በአዲስ አበባ ቀራንዮ ቅዱስ መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን ተፈጽሟል። አትሌት ፶ አለቃ ታደሰ ባለትዳር ሲሆኑ ከትዳር አጋራቸው የአንድ ወንድ እና የሦስት ሴት ልጆች አባትም ነበሩ። የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽንም በአትሌቱ ሞት ለቤተሰቦቻቸው፣ ለወዳጅ ዘመዶቻቸውና ለአድናቂዎቻቸው በሙሉ መጽናናትን ተመኝቷል። በኢትዮጵያ ዶፒንግን ለመቆጣጠር የተሰራው ሥራ ውጤታማ መሆኑ ተነገረ በኢትዮጵያ ባለፉት ሦስት ዓመታት የስፖርት አበረታች ቅመሞችን ወይም ዶፒንግን ለመከላከልና ለመቆጣጠር ተቋማዊ አደረጃጀቱን ማጠናከርን ጨምሮ የተካሄደው እንቅስቃሴ ውጤታማ መሆኑን የዓለም አቀፉ የፀረ-ዶፒንግ ኤጀንሲ አስታወቀ። በዓለም አቀፍ ሕጎችና ስታንዳርዶች መሠረት በየደረጃው ጠንካራና ቀጣይነት ያለው የፀረ-ዶፒንግ ሥርዓት ለመዘርጋት የኢትዮጵያ ብሔራዊ የፀረ-አበረታች ቅመሞች ጽሕፈት ቤት ከዓለም አቀፉ የፀረ-ዶፒንግ ኤጀንሲ እና ከደቡብ አፍሪካ የፀረ-ዶፒንግ ተቋም ጋር የሦስትዮሽ የፓርትነርሽፕ ፕሮግራም በመቅረፅ ተግባራዊ ሲደረግ ቆይቷል። በዚህም የሚፈለገውን ስኬት ማስመዝገብ መቻሉን አፈፃፀሙ በተገመገመበት ወቅት ተጠቁሟል። ይህ ውጤት በአፍሪካ ደረጃም ንፁህ ስፖርት ለማስፋፋት ከፍተኛ ፋይዳ እንዳለው ኤጀንሲው በድረ- ገፁ ላይ ባወጣው መግለጫ አመላክቷል። አዲስ ዘመን ግንቦት 7/2012
https://www.press.et/Ama/?p=32392
208
2ስፖርት
የአፍሪካ አትሌቲክስ ቻምፒዮና ከኦሊምፒክ ቀድሞ ይካሄዳል
ስፖርት
May 16, 2020
29
የአፍሪካ አትሌቲክስ ቻምፒዮና ከኦሊምፒክ ቀድሞ ይካሄዳል የኮሮና ቫይረስ(ኮቪድ 19) በዓለም ላይ በከፍተኛ ፍጥነት መሰራጨቱን ተከትሎ የሁሉም ዓለም አቀፍ የስፖርት መርሃግብሮች ዝብርቅርቅ መውጣቱ ይታወቃል፡፡ ይህንንም ተከትሎ በርካታ ታላላቅ የስፖርት መርሃግብሮችን ዳግም መከለስ አስፈላጊ ሆኗል፡፡ በዚህም መሰረት ክለሳ የተደረገባቸው የተለያዩ መርሃግብሮች ውዝግብ ሲያስነሱ ማየት እየተለመደ መጥቷል፡፡ ከተያዘለት መርሃግብር እንዲራዘም የተደረገው የአፍሪካ አትሌቲክስ ቻምፒዮና በ2021 እንዲካሄድ ከተራዘመው የቶኪዮ ኦሊምፒክ አስቀድሞ እንዲካሄድ የአፍሪካ አትሌቲክስ ኮንፌዴሬሽን ውሳኔ ላይ መድረሱን ከሁለት ቀናት በፊት አሳውቋል፡፡ የኮንፌዴሬሽኑ ፕሬዚዳንት ሐማድ ካልካባ በአልጄሪያ የሚካሄደው የአፍሪካ አትሌቲክስ ቻምፒዮና ከቶኪዮ ኦሊምፒክ ከአንድ ወር ቀደም ብሎ እንደሚካሄድ ማረጋገጫ ሰጥተዋል፡፡ የዓለም አትሌቲክስ ምክትል ፕሬዚዳንት የሆኑት ካልካባ የውድድሩ አዘጋጅ አገርም አዲሱን መርሃግብር የመቀበል ግዴታ እንዳለባት ገልፀዋል፡፡ ካልካባ ቻምፒዮናው ከተራዘመው ኦሊምፒክ በፊት መካሄዱ ለአትሌቶች ጥቅም እንደሚኖረው የገለፁ ሲሆን ውድድሩ በተከለሰው የኦሊምፒክ ማጣሪያ መርሃግብር ውስጥ እንደሚካተት ጠቁመዋል፡፡ ‹‹ውድድሩ የኦሊምፒክ ማጣሪያ(ሚኒማ) ለሚፈልጉ አትሌቶች ጠቃሚ ይሆናል›› ያሉት ካልካባ የዓለም አትሌቲክስ የኦሊምፒክ ማጣሪያ መርሃግብር እስከ ቀጣዩ ዓመት ሰኔ ወር እንዲራዘም ግፊት ማድረጉን አስታውሰዋል፡፡ በኮሮና ቫይረስ ስጋት የተነሳ የአትሌቲክስ ስፖርት የኦሊምፒክ ማጣሪያ ውድድሮች እስከ መጪው ታህሳስ ወር ድረስ እንዳይካሄዱ የዓለም አትሌቲክስ ውሳኔ ማሳለፉን ተከትሎ እስከ ተጠቀሰው ጊዜ የሚካሄዱ ማንኛቸውም ውድድሮችና ውጤቶች የኦሊምፒክ ማጣሪያም ይሁን እውቅና እንደማያገኙ ማስጠንቀቁ ይታወሳል፡፡ ይህ የዓለም አትሌቲክስ ውሳኔ በበርካታ ታላላቅ የዓለማችን አትሌቶች የሰላ ትችት ሲሰነዘርበት እንደሰነበተ ይታወቃል፡፡ በኮሮና ቫይረስ ስርጭት ምክንያት የስፖርቱ ዓለም ካለፉት ሁለት ወራት በላይ እንቅስቃሴው ተገድቦ ቢቆይም ከቅርብ ቀናት ወዲህ የተለያዩ ዓለም አቀፍ ውድድሮች ወደ መደበኛ እንቅስቃሴያቸው ለመመለስ ሲፍጨረጨሩ እየተስተዋለ ነው፡፡ ታላላቆቹን አውሮፓ እግር ኳስ ሊጎች ጨምሮ አንዳንድ አገራትም ስፖርታዊ ውድድሮቻቸውን ለማስጀመር ከቫይረሱ ስጋት ነፃ ሳይሆኑ ጥረት እያደረጉ ሲሆን አብዛኞቹ ውድድሮችን በዝግ ስቴድየሞች በማድረግ የውድድር ዓመቱ ከመጠናቀቁ በፊት መርሃግብሮቻቸውን ስለመፈፀም እየተጨነቁ ይገኛሉ፡፡ በርካቶቹ የዓለም አቀፍ ውድድሮች ግን ቀደም ሲል ቫይረሱ በቀጣዩ ዓመት ይጠፋል ወይም በቁጥጥር ስር ይውላል በሚል ተስፋ ወደ ቀጣይ ዓመት እንዲዞሩ መወሰናቸው ይታወሳል፡፡ ከነዚህ መካከል በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው የቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ ዘግይቶም ቢሆን በቫይረሱ ስርጭት ስጋት የተነሳ ታላቁን የስፖርት መድረክ ለአስራ ስድስት ወራት እንዲራዘም ማድረጉ ይታወሳል፡፡ ይህም እንደሌሎቹ ውድድሮች ሁሉ ቫይረሱ በቀጣዩ ዓመት በቁጥጥር ስር ይውላል ከሚል ተስፋ እንጂ በተጨባጭ መረጃና ማስረጃ አልነበረም፡፡ በርካቶቹ ይህን ተስፋ የሙጥኝ ብለው እያንዳንዱ ቀን እንደ ዓመት እየረዘመባቸውም ቢሆን ቀጣዩን ዓመት በጉጉት እየተጠባበቁ ይገኛሉ፡፡ የቫይረሱ ስርጭት ግን በተቃራኒው እየቀነሰ ከመሄድ ይልቅ በአስደንጋጭ ፍጥነት እየተስፋፋ ይገኛል፡፡ ይህንን ያስተዋሉ የጤና ባለሙያዎችም ለአስራ ስድስት ወራት የተራዘመው የቶኪዮ ኦሊምፒክ በቀጣዩ ዓመት ላይካሄድ እንደሚችል ከወዲሁ እየተናገሩ ይገኛሉ፡፡ የኦሊምፒኩ አዘጋጅ የሆነችው ጃፓን የተላላፊ በሽታዎች ፕሮፌሰር የሆኑት ኬንታሮ ዋታ የቫይረሱ ስርጭት ኦሊምፒኩ በተራዘመበት ወቅት በቁጥጥር ስር ስለመዋሉ አጠራጣሪ በመሆኑ ውድድሩ ላይካሄድ እንደሚችል ስጋታቸውን ለመገናኛ ብዙሃን መግለፃቸው ይታወሳል፡፡ በዓለም ላይ አሁን ያለው ነባራዊ ሁኔታ ከተስፋ በስተቀር የቫይረሱ ስርጭት በጊዜ የሚገታ ወይም ፈውስና ክትባት በዚህ ጊዜ እውን ይሆናል የሚያስብል እንዳልሆነ መታዘብ ይቻላል፡፡ ይህንን ከግምት ያስገቡት የቶኪዮ ኦሊምፒክ ዋና ስራ አስፈፃሚ ቶሺሮ ሙቶ ኦሊምፒኩ የቫይረሱን ስጋት ለማምለጥ በአስራ ስድስት ወራት ቢራዘምም ከቫይረሱ ተፅዕኖ ሊያመልጥ እንደማይችል ሰሞኑን በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ማመልከታቸውን አሶሼትድ ፕሬስ ማስነበቡ ይታወሳል፡፡ የአፍሪካ አትሌቲክስ ቻምፒዮናም ከዚህ የተለየ እድል እንደማይገጥመው ማንም እርግጠኛ አይደለም፡፡አዲስ ዘመን ግንቦት 8/2012ቦጋለ አበበ
https://www.press.et/Ama/?p=32480
451
2ስፖርት
ግንቦት አምስት- የጥቁር ተጫዋቾች የነፃነት ቀን
ስፖርት
May 17, 2020
34
ግንቦት አምስት ቀን ባለፈው ረቡዕ ነበር። ጥቁር ተጫዋቾች በዓለም ነፃ እንዲወጡ በኢትዮጵያ ውስጥ ታሪክ የተጠነሰሰበትና ታሪካዊው የእግር ኳስ ግጥሚያው የተደረገበት ቀን ነው። ሀሳቡን ያመነጩት፤ ተግባራዊ ያደረጉት ፤ከኢትዮጵያ አልፎ በአፍሪካ አቋርጦ በዓለም አደባባይ እንዲደርስ ጥረት ያደረጉት የጥንቱ የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብ ማህበረሰቦች ናቸው። ይሄ ነገር ለረጅም ጊዜ ክለቡ አካባቢም አይነሳም ነበር። የኢትዮጵያ ስፖርት ታሪክ ነጋሪና ጋዜጠኛ ገነነ መኩሪያ(ሊብሮ) በአንድ ወቅት ‹‹ከመሳለሚያ እስከ ፍራንክፈርት- የ32 ዓመት ፈታኝ ጉዞ›› በሚል ካሰፈረው የጥቁር ተጫዋቾች የነፃነት መሰረት ድንጋይ የተጣለበትን የታሪክ አጋጣሚ የሚዳስስ የታሪክ ማስታወሻ የተወሰደውን ፅሁፍ በዛሬው የስፖርት ማህደር አምዳችን ቀንጭበን ለንባብ ለማብቃት ወደድን። ቅዱስ ጊዮርጊስ የመጀመሪያውን ጨዋታ ከነጮች ጋር ያደረገው(ከውጭ ሀገር ሰዎች ጋር እንደመጀመሪያ ኢንተርናሽናል ጨዋታ ከተቆጠረ) አራራት ከተባለ የአርመኖች ቡድን ጋር ነው። ጊዜውም በየካቲት 28 ቀን 1928 ዓ.ም ነበር።(በተመሰረተ በሁለት ወሩ)ለሁለተኛ ጊዜ ከነጮች ጋር የተደረገው ግጥሚያ ደግሞ በግንቦት 5 ቀን 1934 ዓ.ም ነው። ይሄ ጨዋታ ከግጥሚያዎች ሁሉ ትልቅ ትርጉም ያለውና በዓለም ያሉ ጥቁር ተጨዋቾችን ነፃ ለማውጣት መሰረት የተጣለበት ቀን ነው። ዛሬ ላይ በርካታ ጥቁር ተጫዋቾች በበርካታ ታላላቅ ክለቦች ተቆጥሮ የማያልቅ ገንዘብ እየተከፈላቸው ለመጫወታቸው መሰረት የሆነችው ይህች ቀን ነች። ጊዮርጊሶች ታሪካዊውን ጨዋታ የተጫወቱት ከጣሊያኑ ፎርቲቲዲዮ ጋር ነበር። ጨዋታውን ለማድረግ ድርድሩ አንድ ዓመት ያህል ፈጅቷል። ጦርነቱ ካለቀ ገና ጥቂት ወር ውስጥ ነው ድርድር የተጀመረው። በአንድ በኩል የሀገሬው ሰው ‹‹እንዴት ሲገድሉን ከነበሩት ጣሊያኖች ጋር እርቅ አድረጋችሁ ኳስ ትጫወታላችሁ?››በሚል ቅሬታና ተቃውሞ ሲደርስ ፤በጣሊያኖች በኩል በኳስ አሳበው አደጋ ቢያደርሱብንስ በሚል ላለመጫወት ብዙ መጓተት ታይቷል። የያኔው ኳስ ጨዋታ ለእርግጫ በጣም የቀረበ መሆኑ ለዚህ ጥርጣሬ መነሻ ነበር። ሁለቱ ቡድኖች ፋሽስቱ ያወጣውን ህግ አፍርሰው ‹‹ጥቁርና ነጭ አንድ ነው›› በሚል ተስማምተው ከብዙ ውጣ ውረድ በኋላ ተፈራርመው ተጫወቱ። ይሄ ፊርማ መጨረሻ ላይ ፊፋ ውስጥ ኢትዮጵያ አቅርባው ሁሉም ተስማምቶ የፈረመበት የመጀመሪያው መሰረት ነው። ይሄ ፊርማ በእግር ኳስ ሜዳ ልዩነትን የሚያጠፋ ወንድማማችነትን የሚያሰፍን ነው። የዓለም እግር ኳስ ዛሬ ላይ ለደረሰበት ሁለንተናዊ እድገትም ትልቅ ድርሻ አለው። የዚህ ሀሳብ መነሻ ደግሞ የጊዮርጊስ መስራች የሆኑት አየለ አትናሽና ጆርጅ ዱካስ ናቸው። ሁለቱ በቆዳ ነጭና ጥቁር ናቸው። በኢትዮጵያ ውስጥ ጣሊያን ህጉን ሲያወጣ መጀመሪያ እንዲለያዩ ማስጠንቀቂያ የሰጠው ለእነርሱ ነበር።ሁለቱ ጀምረው ሌሎች የጊዮርጊስ ሰዎች አቀጣጥለውና ህግ አውጥተው ህጉ በአፍሪካ አልፎ በዓለም አቀፍ ደረጃ ደንብ ሆኖ ሲወጣ በመጀመሪያ የተደሰቱትም ሁለቱ መስራቾች ነበሩ። ይህ ዓለም አቀፍ ደንብ ዛሬ ላይ ሆነን ስንመለከተው በቀላሉ እውን የሆነ ሊመስል ይችላል። ይሁን እንጂ ረጅም ጊዜ የፈጀ፣ ብዙ ውጣውረድና ትግል የተደረገበት ነው። በወቅቱ ፊፋ ውስጥ ያሉ እንግሊዞችና ደቡብ አፍሪካ ያሉ አመራሮች ይሄ ጉዳይ በካፍና በፊፋ ላይ እንዳይነሳ አቅምና ተሰሚነታቸውን ተጠቅመው በገንዘብም ጭምር ለመደለል ቢጥሩም ኢትዮጵያ በቀላሉ ጉዳዩን ችላ የምትል አልሆነችም። ጉዳዩን ሲያጣሩ ኢትዮጵያ ውስጥ ነገሩን አጥብቀው የያዙት የጊዮርጊስ ማህበረሰብ እንደሆኑ ታወቀ። በዚህ የተነሳም ‹‹የጊዮርጊስ ሰዎች ናቸው ያስቸገሩት›› በሚል ጥርስ ተነክሶባቸው ነበር። በርግጥም በየስብሰባው ታላቁ ይድነቃቸው ተሰማ ጉዳዩን በጥብቅ ስለሚያነሱት ግምታቸው ትክክል ነበር። የደቡብ አፍሪካ ነጮች ኬንያ ባለው ‹‹ሚስር አሌክሳንደር›› በተባለ የናይሮቢ ከንቲባ በኩል ክለቡን ለማፍረስ ብዙ መጣራቸውም እዚህ ጋር ሳይነሳ አይታለፍም። ያም ሆኖ ኢትዮጵያኑ በመጨረሻም አሸንፈው ህጉ ጸድቋል። የዚህ ሀሳብ መነሻው ጊዮርጊስ ክለብ ይሁን እንጂ ነገሩ የሀገርን ስም ከፍ የሚያደርግ በዓለም ከክለቦች አንስቶ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የተሳተፈበት ታሪካዊ ድል ነው። (ፊፋ ላይ ያቀረበው ፌዴሬሽኑ በመሆኑ)። ጊዮርጊሶች በሀገራቸው ተገልለው የተጫወቱት መሳለሚያ በሚገኘው ኳስ ሜዳ ነው። ለዓለም ጥቁሮች ነጻ መውጣት እና የደቡብ አፍሪካ አፓርታይድ ከስፖርት እንዲገለል ህጉ የጸደቀው ፍራንክፈርት ላይ በተደረገው የፊፋ ስብሰባ ነው። ያቀረበችው ኢትዮጵያ ስትሆን ተከራካሪው ይድነቃቸው ተሰማ ነበሩ። ይድነቃቸው ከመሳለሚያ እስከ ፈራንክፈርት ባለው ጉዞ ተሳታፊ ናቸው። ለ32 ፈታኝ ዓመታት ትግል ከተደረገ በኋላ ህጉ ጸድቆ ጥቁር ተጫዋቾች ያለምንም ገደብ በየትኛውም የዓለም ክልል እንዲጫወቱ ሆኗል። አዲስ ዘመን ግንቦት 9/2012 ቦጋለ አበበ
https://www.press.et/Ama/?p=32528
531
2ስፖርት
«ተምዘግዛጊው ሚሳኤል» አረፈ!
ስፖርት
May 15, 2020
50
ከአዲስ አበባ በ110 ኪ.ሜ ርቀት ላይ የምትገኘው ወንጂ ከተማ በእግር ኳሱ በርካታ ተጫዋቾችን ማፍራቷ ይነገርላታል። ይህም ከተማዋ ከምትታወቅበት ጣፋጭ የሸንኮራ አገዳ አምራችነቷ፣ የስኳር ፋብሪካ ማዕከልነቷ ትይዩ የእግር ኳስ ተጫዋቾች መፍለቂያ አሰኝቷታል። የወንጂን ከተማ በእግር ኳሱ ካስተዋወቁት ተጫዋቾች መካከል ደግሞ አንጋፋው ተጫዋች ተስፋዬ ኡርጌቾ ይጠቀሳል። በወንጂ ከተማ ተወልዶ ያደረገው ተስፋዬ፤ በእግር ኳሱ ትልቅ ቦታ መድረስን የልጅነት ህልሙ አድርጎ የተነሳ መሆኑን የቅርብ ወዳጆቹ ይናገሩለታል። ከልጅነቱ ጀምሮ ለእግር ኳስ ልዩ ፍቅር በመያዝ መነሻው ከሰፈር ሜዳ ነበር። በኳሱ የመጓዝ ህልሙ ሩቅ የሆነው የትናንቱ ታዳጊ ተስፋዬ፤ በስፖርቱ የሚያደርገውን እንቅስቃሴ በማጎልበቱ ወደ ክለብ እንዲያድግ አጋጣሚን አገኘ። ከከተማዋ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ መሠረት አንዱ የሆነው የወንጂ ስኳር ፋብሪካ ያቋቋመውን «የወንጂ ስኳር እግር ኳስ ክለብ» ነበር የተቀላቀለው። ተስፋዬ የወንጂ ስኳርን መቀላቀሉ በኳሱ ለሚያልመው ህልሙ፣ ለሰነቀው ተስፋ እውን መሆን መንደርደሪያውን የትውልድ ከተማው ሆነለት። ከክለቡ ጋር የተወሰኑ ጊዜያትን ቆይታ ካደረገ በኋላ የሕይወቱ አቅጣጫ ወደ ሌላ ምዕራፍ ተሸጋገረ። በወንጂ ስኳር እግር ኳስ ክለብ በፈጣንና ጥበብ የተሞላበት እንቅስቃሴ ባለቤትነቱ በአየር ኃይል እግር ኳስ ቡድን እይታ ውስጥ አስገባው። በወቅቱ የአየር ኃይል አሰልጣኝ የነበረው አንጋፋው አሰልጣኝ ሀጎስ ደስታ ልብ በማሸነፍ አሰልጣኙ አየር ኃይልን እንዲቀላቀል አስቻለው። በእግር ኳሱ ትልቅ ደረጃ የመድረስ ተስፋ በልቡ ሰንቆ ወደሜዳ ለሚመጣው ታዳጊ ትልቅ ዕድል ነበር። በአየር ኃይል ቤት ተስፋዬ ምኞቱን መኖር ለመጀመሩ መንደርደሪያው ነበር። በቡድኑ ውስጥ ያሳየው እንቅስቃሴ ክለቡ እንዲደሰትበት ከማድረግ አልፎ፤ ለብሔራዊ ቡድን እንዲጫወት ሀገራዊ ጥሪ እንዲቀርብለት አድርጎታል። በ1983 ዓ.ም ለኢትዮጵያ ወጣት ብሔራዊ ቡድን በመመረጥ በግብጽ አዘጋጅነት በተካሄደው 7ኛው የአፍሪካ ወጣቶች ዋንጫ ላይ ለመሳተፍ ችሏል። የወንጂው ፍሬው ተስፋዬ የስኬት ጀንበርን በአጭር ጊዜ ውስጥ መመልከት የቻለ ሲሆን፤ በሜዳ ላይ የሚያሳየው ብቃትና የተላበሰው መልካም ስብዕናው ተደምረው ጉዞው ያማረ እንዲሆን አደረጉት። የወጣት ብሔራዊ ቡድኑ በሻምፒዮናው ላይ ከተሳትፎ መልስ የተስፋዬ የክለብ መዳረሻ ከአየር ኃይል ተወርውሮ ወደ አንጋፋው ቅዱስጊዮርጊስ ላይ አረፈ። በ1983 ዓ.ም በኢትዮጵያ እግር ኳስ ታሪክ ውስጥ አንፀባራቂ ታሪክ ባላቸው በኢንስትራክተር መንግሥቱ ወርቁ አማካኝነት ክለቡን ተቀላቀለ። የእግር ኳሱ ጥበበኛ ተስፋዬ ፈረሰኞቹን መቀላቀሉ በኳሱ የስኬትን ቁንጮ ለመቆናጠጥ ትልቅ ዕድል ፈጥሮለታል። በአማካይና የተመላላሽ ቦታዎች ላይ በመጫወት ክለቡን ለስኬት ማብቃት በመቻሉ የክለቡ ደጋፊዎች ዛሬም ድረስ ትልቅ ቦታ እንዲኖራቸው አድርጓል። ከ1983 ዓ.ም እስከ 1992 ዓ.ም ፈረሰኞቹን ማገልገል የቻለው አመለሸጋው ተስፋዬ፤ በቆይታው ከፍተኛ ዝናና ተወዳጅነት አትርፏል። በፈረሰኞቹ ቤት በቆየባቸው የሰባት ዓመታት ቆይታ ውስጥ በ1986 ዓ.ም የአዲስ አበባ ሻምፒዮን ኮከብ ተጫዋችነትን ክብር አግኝቷል። ክለቡ ቅዱስጊዮርጊስ ከ1986 እስከ 88 ዓ.ም የአዲስ አበባ ሻምፒዮናነትን ክብር ሲቀዳጅ ግብ አስቆጣሪ ከሆኑት ተጫዋቾች ጀርባ የእርሱ ሚና ግዙፍ እንደነበር በወቅቱ የነበሩ ተጫዋቾች መስክረውለታል። ከክለቡ ስኬት ተሻግሮም ለሚወዳት ሀገሩ በብሔራዊ ቡድን ደረጃ ተመርጦ በርካታ ጨዋታዎችን ተጫውቶ አሳልፏል። በ1985 ዓ.ም በአዲስ አበባ ስታዲየም ላይ ለአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ኢትዮጵያ ናይጄሪያን 1ለ 0 ስታሸንፍ ብቸኛዋን ግብ በማስቆጠር ሀገሩን ለድል ያበቃበት አጋጣሚ በአብዛኛው የስፖርት ቤተሰብ ዘንድ ይታወሳል። በብሔራዊ ቡድን ብሎም በክለብ ደረጃ የነበረው እንቅስቃሴ ከክለቡ ተሻግሮ በስፖርት አፍቃሪው ዘንድ ከፍተኛ ተደናቂነት ማትረፍ የቻለ ተጫዋች ነበር። በሀገር ውስጥ የክለብ ፍልሚያዎች በፈረሰኞቹ ቤት በ4 ቁጥር ማሊያ መንገስ ችሏል። በሜዳ ላይ ፈጣንና ድንቅ እንቅስቃሴ የሚያሳይ መሆኑን ተከትሎ «ተምዘግዛጊው ሚሳኤል» የሚል ቅጽል ስም የተሰጠው ተስፋዬ፤ ከሀገር አልፎ ወደ አውሮፓም አምርቶ በፊንላንድ ሊግ መጫወት ችሏል። በኢትዮጵያውያን ተጫዋቾች ዛሬም ድረስ እንደ ብርቅ በሚታየው የአውሮፓ ሊግ የኳስ ጥበበኛው ተስፋዬ ባህር ተሻግሮ። እግር ኳስን በተጫወተባቸው ዓመታቶች በመሀል ሜዳ የጨዋታ ብቃቱ የብዙዎቹን የእግር ኳስ አፍቃሪዎች እና የቅዱስ ጊዮርጊስ ደጋፊዎችን ቀልብ ይስብ የነበረው፤ ተስፋዬ የተጫዋችነት ዘመኑን ቢያበቃም ከኳሱ አልተለየም ነበር። ከተጫዋችነት ወደ አሰልጣኝነት የሕይወቱ አቅጣጫ ተሸጋገረ። በአሰልጣኝነትም ሕይወት በመሰማራት የጌታ ዘሩን የታዳጊ ፕሮጀክት እና የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲንም ክለብን በመያዝ አሰልጥኗል። የሕይወቱን ፍጻሜ ከኳስና ከእናት ሀገሩ ለመነጠል ፍላጎት ያልነበረው ተስፋዬ፤ መኖር ግድ ነበርና በአሜሪካ በስደት በርካታ ዓመታትን አሳልፏል። «ተምዘግዛጊው ሚሳኤል» በገጠመው ህመም ከሚኖርበት አሜሪካ የመጣ ሲሆን፤ በሚወዳት ሀገሩ በሕክምና ሲረዳ ቆይቶ ግንቦት 05 ቀን 2012 ዓ.ም በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ሕይወቱ አርፏል። በኢትዮጵያ የእግር ኳስ ታሪክ ውስጥ የራሱን አሻራ ማሳረፍ የቻለው ተስፋዬ የቀብር ሥርዓቱ በትውልድ ከተማው ወንጂ ሸዋ ኪዳነ ምህረት ከትናንት በስቲያ ተፈጽሟል። የተስፋዬ ሞት ብዙዎቹን ያሳዘነም ሲሆን የዝግጅት ክፍላችን በተስፋዬ ሞት የተሰማውን ጥልቅ ኀዘን እየገለፀ ለቤተሰቦቹ ለወንድሙ ተከተል ኦርጌቾና ለመላው ስፖርት አፍቃሪ እና ለቅዱስ ጊዮርጊስ ደጋፊዎች መፅናናትን ይመኛል። አዲስ ዘመን ግንቦት 7/2012ዳንኤል ዘነበ
https://www.press.et/Ama/?p=32391
610
2ስፖርት
የኢትዮጵያ ቨርቸዋል ሩጫ ተካሄደ
ስፖርት
May 19, 2020
30
ኮቪድ 19 ወረርሽኝ ያሳደረውን ተፅዕኖ መቀነስና መቀየር ይቻል ዘንድ በኢንተርኔት የታገዘ በመላው ዓለም የሚገኙ ኢትዮጵያውያን የተሳተፉበት የቨርቿል ሩጫ ተካሄደ። በኢንተርኔት የታገዘ የቀጥታ ቪዲዮ «ቨርቿል ሩጫ» መርሐ ግብር በተሳካ ሁኔታ ከትናንት በስቲያ መካሄዱን የሩጫ አዘጋጁ የታላቁ ሩጫ በዋሽንግተን ዲሲ አስታውቋል። በቨርቹዋል ሩጫ መርሐ ግብሩ ላይ አትሌት ደራርቱ ቱሉ፣ ቀነኒሳ በቀለ፣ ጥሩነሽ ዲባባ፣ ገንዘቤ ዲባባ፣ ስለሺ ስህን፣ ፋጡማ ሮባ፣ ሚሊዮን ወልዴ እና እጅጋየሁ ዲባባ መሳተፋቸው ታውቋል። በውድድሩ አንድ ሺህ የሚሆኑ ኢትዮጵያዊያን ከመላው ዓለም ሆነው ዙም በተሰኘ መተግበሪያ ላይ በኢንተርኔት በቀጥታ እየተያዩ በቤታቸው እና ግቢያቸው ውስጥ ሆነው በመሮጥ እና ሶምሶማ በማድረግ ተሳትፈውበታል ተብሏል። የኢትዮጵያ ቨርቹዋል ሩጫ ዋና አዘጋጅ ዶክተር ጋሻው አብዛ ለመገናኛ ብዙሃን እንደተናገሩት ፤ የኮቪድ-19 በሽታ በዓለም ዙሪያ ከፈጠረዉ የጤና ፈተና ጎን ለጎን፣ በተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች ላይ ኢኮኖሚያዊና ስነ ልቦናዊ ጫና አስከትሏል። በመላው ዓለም የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ይህ ዓለም አቀፍ ወረርሽኝ ከተከሰተ ጀምሮ ረዘም ላለ ጊዜ ቤት ውስጥ ለመቀመጥ ተገደዋል። በመሆኑም የወገኖቻችንን ችግር በተወሰነ መልኩ ማቃለል ይቻል ዘንድ በኢንተርኔት የታገዘ ቨርቿል ሩጫ ማዘጋጀት አስፈልጓል ብለዋል፡፡ በአገር ውስጥም ሆነ በውጭው ዓለም ያሉ ኢትዮጵያዊያን በተለይ ደግሞ ወረርሽኙ በበረታባቸው አሜሪካና አውሮፓ የሚገኙ ኢትዮያዊያን ከተለመደው የአኗኗር ዘይቤ በወጣ ሁኔታ ረዘም ላለ ጊዜ ቤት ውስጥ ለመቀመጥ በመገደዳቸው ሥራን እንደ ወትሮው ወጥቶና ነፃ ሆኖ መሥራት አልተቻለም። ስለዚህ በበርካቶች ላይ ስጋትና የአዕምሮ ጭንቀት በመፍጠር ላይ እንደሚገኝ የገለጹት ዶክተር ጋሻው፤ ጫናውን በተወሰነ ደረጃ ለመቀነስ የሚያግዝ በኢንተርኔት በቤትና ግቢ ውስጥ ሆነው የሚሮጡት የቨርቹዋል ሩጫ ተዘጋጅቶ በስኬት መከናወኑን አብራርተዋል። በኢትዮጵያ ቨርቹዋል ሩጫ ላይ አንጋፋና ብርቅዬ አትሌቶች የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ለማበርከት በመላው ዓለም የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን መሳተፍ የቻሉ መሆኑን የተናገሩት ዶክተር ጋሻው ፤ከዝግጅቱ የተገኘው ገቢ በኮቪድ-19 ዙሪያ ኢትዮጵያ ውስጥ ለሚሠሩ ሁለት መንግሥታዊ ያልሆኑና በኢትዮጵያዊያን ለሚመሩ አነስተኛ ድርጅቶች የሚበረከት መሆኑንም ተናግረዋል። በሩጫው ላይ አትሌቶች በያሉበት ቦታ ሆነው በቪዲዮ ተራ በተራ እየሮጡ ለውድድሩ በተዘጋጀ መተግበሪያ ላይ በቀጥታ በማህበራዊ ሚዲያ ከተሳታፊዎች ጋር ሩጫውን አካሄደዋል። ተሳታፊዎችም በቤትና ግቢ ውስጥ እንዲሁም የመሮጫ ማሽን ላይ በመሆን እየሮጡ በስልካቸው፣ በኮምፒዩተርና በሌሎች የቴክኖሎጂ መሳሪያዎች በመታገዝ አትሌቶችን እየተከተሉ ሮጠዋል። በፌስቡክ እና ዩቲዩብ ላይቭ ላይ ከተለያዩ የዓለም ክፍል የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን በተመሳሳይ ሰዓት በአንድ ላይ ሆነው በኢንተኔት በታገዘው ሩጫ ላይ ካሉበት ሆነው መሳተፋቸው ታውቋል። ቨርቹዋል ሩጫ (Virtual Race) የሚባለው ከየትኛውም ቦታ እና አካባቢ በመሆን የሚከናወን ሩጫ ወይንም ፈጠን ያለ የዕርምጃ ውድድር እንደማለት ነው።አዲስ ዘመን ግንቦት 11/2012ዳንኤል ዘነበ
https://www.press.et/Ama/?p=32673
340
2ስፖርት
በመተከል ዞን እየተወሰደ ባለው የህግ ማስከበር ዕርምጃ የታጠቁ ኃይሎች እጃቸውን እየሰጡ ነው
ሀገር አቀፍ ዜና
January 2, 2021
2
በጋዜጣው ሪፖርተር አዲስ አበባ(ኢዜአ):- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን እየተወሰደ ባለው የህግ ማስከበር ዕርምጃ በርካታ የታጠቁ ኃይሎች እጃቸውን ለጸጥታ ኃይሉ እየሰጡ መሆኑን በጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ የተቋቋመው የተቀናጀ ግብረ ኃይል አስታወቀ።የህግ ማስከበርና የፀጥታውን ዘርፍ በበላይነት የሚመሩት ሌተናል ጀኔራል አስራት ዴኔሮ፤ የጥፋት ቡድኑ በመተከል ዞን በተለይም ቡለንና በቆጂ ወረዳዎች ዜጎችን በመግደል፣ ንብረት የመዝረፍና የማቃጠል አረመኔያዊ ተግባር መፈፀሙን አስታውሰዋል።የተጠናከረ ዘመቻ በማካሄድ በአካባቢው ህግ በማስከበር ሰላምን ለማረጋገጥ በተደረገው ጥረት በርካታ የታጠቁ ኃይሎች እጃቸውን እየሰጡ መሆኑን ጠቅሰዋል።ታጣቂ ቡድኑ ቀደም ሲል የፈፀመውን ጥቃት ተከትሎ ስጋት አድሮባቸው መኖሪያቸውን ለቀው የነበሩ ዜጎችም ወደ ቀያቸው እየተመለሱ መሆኑን ሌተናል ጀኔራል አስራት ገልጸዋል።ግብረ ኃይሉ አካባቢውን ከተረከበ በኋላ በተለይ ስጋት ተፈጥሮባቸው የነበሩ አካባቢዎችን በማረጋጋት ወደ ተሻለ ሰላማዊ እንቅስቃሴ እንዲመለሱ መደረጉን ተናግረዋል።በሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማዕከል አስተባባሪና የኮማንድ ፖስቱ የፖለቲካና ህዝባዊ ውይይቶች መሪ አቶ ተስፋዬ በልጅጌ በዜጎች ላይ ጥቃት የፈፀመውን ታጣቂ ቡድን የማደን ሥራ መቀጠሉን ገልጸዋል።የተፈፀመውን ጥቃት በመምራትና በማስተ ባበር የተጠረጠሩና ጥቃቱን መከላከል ሲገባቸው ኃላፊነታቸውን ያልተወጡ አመራሮች ላይ ህጋዊና ፖለቲካዊ ዕርምጃ እየተወሰደ መሆኑን ተናግረዋል።የጥፋት ቡድኑን ዓላማ ያልተቀበሉ የጉሙዝ ማህበረሰቦችን ጨምሮ በተለያዩ የማህበረሰብ አካላት ላይ በአሰቃቂ ሁኔታ ህይወት ማጥፋት፣ አካል ማጉደልና ንብረት ማውደም መፈፀሙን አቶ ተስፋዬ ገልጸዋል።ችግሩ እኩይ ዓላማ ያላቸው ኃይሎችን ብቻ የሚመለከት መሆኑን ጠቅሰው፤ “በዘላቂነትመፍትሔ ለማበጀት ግብረ ኃይሉ ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር በቅንጅት እየሠራ ነው” ብለዋል።ለተፈናቀሉ ዜጎች ሰብአዊ ድጋፍ የማድረስና ወደ ቀዬአቸው መልሶ የማቋቋም ስራ ተጠናክሮ መቀጠሉንም አቶ ተስፋዬ ገልፀዋል።በሂደቱ የሰላምና የህግ የበላይነትን ለማረጋገጥ የሚያግዙ ህዝባዊ ውይይቶች እንደሚካሂዱም አስታውቀዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 24/2013
https://www.press.et/Ama/?p=38672
220
0ሀገር አቀፍ ዜና
የበርሊን ማራቶን ላይካሄድ ይችላል
ስፖርት
May 17, 2020
19
በርካታ የማራቶን የዓለም ክብረወሰኖች የሚሻሻሉበት የበርሊን ማራቶን በዚህ ዓመት የመሰረዝ ወይም የመራዘም እድል ያልገጠመው ብቸኛው ውድድር ነው ማለት ይቻላል። ይህ ታላቅ የማራቶን ውድድር የኮሮና ቫይረስ በዓለም ላይ ከመከሰቱና ከመስፋፋቱ አስቀድሞ መስከረም ወር ላይ በመካሄዱ የሌሎቹ ታላቅ ውድድሮች እጣ ፋንታ ሳይገጥመው ቀርቷል። ያም ሆኖ የኮሮና ቫይረስ ስርጭት እስካሁን የሚያቆመው ባለመኖሩና ወደ ፊትም መፍትሄ ማግኘቱ አጠራጣሪ እየሆነ በመምጣቱ በቀጣዩ መስከረም የበርሊን ማታሪን የመካሄዱ ጉዳይ አጠራጣሪ ሆኗል። የውድድሩ አዘጋጆች ሰሞኑን እንደጠቆሙትም ውድድሩን በተለመደው ወቅት ለማካሄድ እስካሁን ውሳኔ ላይ መድረስ አልቻሉም። ውድድሩን ለማካሄድ ወይም ለማራዘም ውይይት እየተደረገ ሲሆን ውሳኔ ላይ ለመድረስ ጊዜ እንደሚያስፈልጋቸው አሳውቀዋል። የጀርመን መንግስት በኮሮና ቫይረስ ስጋት እስከ መጪው ጥቅምት ወር መጨረሻ ከአምስት ሺ ሰው በላይ የሚሰበሰብባቸው ማንኛቸውም መርሃግብሮች ማገዱን ተከትሎ የውድድሩ አዘጋጆች ውሳኔ ላይ ለመድረስ እንደተቸገሩ ጠቁመዋል። እንደ በርሊን ማራቶን ሁሉ ዋነኞቹ የዓለማችን የማራቶን ውድድሮች የሆኑት የቦስተንና የለንደን ማራቶን ውድድሮችም በተመሳሳይ ምክንያት መካሄድ ከነበረባቸው ወቅት የመራዘም እድል እንደገጠማቸው ይታወሳል። የበርሊን ማራቶን አዘጋጆች ውድድሩ ካለው ስፋትና ከሚያሳትፈው የሰው ብዛት አኳያ የሚካሄድበት እድል መኖር አለመኖሩን በማጥናት ላይ የሚገኙ ሲሆን ውሳኔ ላይ ለመድረስም የተወሰነ ጊዜ እንደሚያስፈልጋቸው አሳውቀዋል። ለዚህም የውድድሩ አዘጋጆች አሁን ላይ በቫይረሱ ስጋት የተነሳ በሙሉ ሃይላቸው ተገናኝተው መስራት አለመቻላቸው አንዱ እንቅፋት መሆኑን ገልፀዋል። በርካታ የዓለም ክብረወሰኖች የሚመዘገቡበት የበርሊን ማራቶን 2018 ላይ ኬንያዊው ኢሉድ ኪፕቾጌ 2፡1፡39 የሆነ አዲስ የዓለም ክብረወሰን በርቀቱ እንዳስመዘገበበት ይታወሳል። ባለፈው መስከረም ደግሞ ቀነኒሳ በቀለ ይህን ክብረወሰን ለማሻሻል በሁለት ሰከንድ የዘገየ ሰዓት ማስመዝገቡ አይዘነጋም። ከቀናት በፊት የወጡ ሪፖርቶች እንደሚያሳዩት በጀርመን ከ172 ሺ በላይ ሰዎች በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሲሆን ከ7600 በላይ የሚሆኑ ሕይወታቸው ማለፉ ታውቋል። ይህም የ2020 በርሊን ማራቶን ላይ ትልቅ ተፅዕኖ ከማሳደሩ ባለፈ እንዲሰረዝ ወይም እንዲራዘም ሊያደርገው እንደሚችል ስጋት ፈጥሯል። አዲስ ዘመን ግንቦት 9/2012 ቦጋለ አበበ
https://www.press.et/Ama/?p=32529
255
2ስፖርት
የአበረታች ቅመሞች ቁጥጥር ከጥንቃቄ ጋር ይቀጥላል
ስፖርት
May 18, 2020
21
የወቅቱ የዓለም ራስ ምታት በሆነው የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች አንቀላፍተው ቢቆዩም ከሰሞኑ የአውሮፓ ሊጎች ወደ ልምምድ መመለስን ተከትሎ የስፖርቱ ኢንዱስትሪ መነቃቃት ጀምሯል። አሁንም የኮሮና ወረርሽኝ (ኮቪድ 19) ስጋት እንዳለ ቢሆንም ጥንቃቄን በተላበሰ መልኩ ወደ ቀድሞው መደበኛ ሁኔታ ለመመለስ ጥረቶች እየታዩ ነው። በዚሁ ምክንያት ተቀዛቅዞ የቆየው አበረታች ቅመሞችን መከላከልና የመቆጣጠር ሥራ ነው። ይህ ስፖርትን በተፈጥሯዊው መንገድ ብቻ እንዲካሄድ የማድረግ ጥረት ሊቀዛቀዝ የቻለው በዓለም አቀፍ ደረጃ ውድድሮች መቋረጣቸውን ተከትሎ ነው። ይሁን እንጂ ከዓላማው አንጻር ረጅም ጊዜ መውሰዱና መዘናጋቱ ዋጋ ሊያስከፍል ይችላል። በመሆኑም ዓለም አቀፉ የጸረ አበረታች ቅመሞች ተቆጣጣሪ ኤጀንሲ በስሩ ለሚገኙት ብሔራዊ ጽሕፈት ቤቶች መመሪያ ማዘጋጀቱን ከሰሞኑ በድረገጹ አስነብቧል። ይህም በየሀገራቱ የሚገኙ የጸረ አበረታች ቅመሞች ተቆጣጣሪ ጽሕፈት ቤቶች ወደ ቀደመ ሥራቸው እንዲመለሱ የሚያስችል ርምጃ ነው። ኤጀንሲው በወረርሽኙ ምክንያት በዓለም ዙሪያ ሲሰሩ የቆዩት ናሙና የመውሰድና ምርመራ የማድረግ ሂደቶችን የቀነሰና አንዳንድ ሥራዎችንም በጊዜያዊነት ማቋረጡን በዘገባው ተጠቁሟል። ነገር ግን አሁን ወደ ሥራ ለመመለስ እንቅስቃሴ መደረግ እንዳለበት የኤጀንሲው ፕሬዚዳንት ዊቶልድ ባንካ ይገልጻሉ። በኤጀንሲው ስር ካሉ ተቋማት ጋር ከወቅታዊው ጉዳይ ጋር በተያያዘ በቅርበት ሲሰሩና ድጋፍ ሲያደርጉ ቆይተዋል። አሁን ግን ሥራው እንደቀድሞው መቀጠል ያለበት በመሆኑ፤ በቴክኖሎጂ በታገዘና የናሙና አወሳሰዱን በአዲስ መንገድ ማካሄድ ተገቢ መሆኑን ያመላክታሉ። ለዚህ ደግሞ በጸረ አበረታች መድኃኒት ቁጥጥር ላይ የሚሰሩ አካላት አዲስ ነገር ለመፍጠር ርብርብ ላይ ይገኛሉ። የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር ኦሊቨር ኒግሊ በበኩላቸው፣ በዚህ ወቅት ናሙናዎችን ከአትሌቶች ለመውሰድ አዳጋች መሆኑን ነው የሚጠቁሙት። ምርመራው መቀጠል የሚገባው አስፈላጊው የጤናና ንጽህና ሁኔታ የተስተካከለ ሲሆን ብቻ ነው። የአትሌቶችና በዙሪያቸው ያሉ አካላት ጤናም ኤጀንሲው ትኩረት የሚሰጠው ቀዳሚ ጉዳይ ነው። ተቋሙ የአትሌቶችን ናሙና በመውሰድ አበረታች መድኃኒት ተጠቃሚነታቸውን በምርመራ መለየት ብቻም ሳይሆን የጤና ግለ ታሪካቸውንም መመዝገብ ሌላው ተግባሩ ነው። ንጹህ ስፖርት ለመፍጠር በሚደረገው ጥረት ግንዛቤ ማስጨበጥም እንዲሁ። በመሆኑም በቀጣይ ሳምንታት ከብሔራዊ ተቋማቱ ጋር በመሆን ሥራው በምን መልኩ መቀጠል ይገባዋል በሚለው ላይ መፍትሄ በማፈላለግ ወደ ሥራ የሚመለስ እንደሆነ አብራርተዋል። የሯጮቹ ሀገር ኢትዮጵያም የኤጀንሲው አባል ሀገር በመሆን ንጹህ ስፖርት እንዲካሄድ ሚናቸውን ከሚወጡት መካከል ትጠቀሳለች። ተሞክሮውን ለሌላው ዓለምም ማጋራት የቻለና በሥራው ምስጉን የሆነ ጽሕፈት ቤትም በአጭር ጊዜ ለማቋቋም መቻሉ ይታወቃል። በመላው ዓለም ባጠላው በዚህ የወረርሽኝ ወቅት የኢትዮጵያ ብሔራዊ የጸረ አበረታች ቅመሞች ተቆጣጣሪ ጽሕፈት ቤት እንቅስቃሴውን በምን መልኩ እያከናወነ ይገኛል? የሚለውን የጽሕፈት ቤቱ ዳይሬክተር አቶ መኮንን ይደርሳል ያስረዳሉ። የተቋሙን ውስጣዊና ውጫዊ እንቅስቃሴ በሁለት የሚከፍሉት ዳይሬክተሩ፤ የኮሮናን ቫይረስ በመከላከል ረገድ ሠራተኞችን የመቀነስና የንጽህና ቁሳቁስን የማዘጋጀት ሥራዎች መከናወናቸውን ይጠቁማሉ። ሁለተኛውና ከተቋሙ ውጪ ከአትሌቶች ጋር በመገናኘት የሚከናወነው ደግሞ ከአበረታች መድኃኒት ቁጥጥር ጋር የተያያዘው ሥራ ነው። ይሁን እንጂ ከአትሌቶች ናሙና መውሰድ በእጅጉ ለንክኪ የሚያጋልጥ በመሆኑ አትሌቶችንም ሆነ በምርመራው ተሳታፊ የሆኑ ባለሙያዎችን ለቫይረሱ ተጋላጭ እንዳይሆኑ በማሰብ ለጊዜው ገታ ተደርጓል። ነገር ግን ሥራውን ሙሉ ለሙሉ ማቆም የማይቻል በመሆኑ ለቫይረሱ አጋላጭ ይሆናሉ የሚል ስጋት ያሳደሩ ሥራዎችን ፎርማት ለመቀየር መሞከሩን ዳይሬክተሩ ይገልጻሉ። በዚህም መሠረት አበረታች ንጥረ ነገር ተጠቃሚ የሆኑ አትሌቶችን የማጋለጥ፣ አትሌቶች ባዮሎጂካል ፓስፖርት ፕሮግራም ሥራን የማጠናከር እንዲሁም ሌሎች ሥራዎች እየተከናወኑ ነው። በዚህ ጊዜ ውድድሮች የተቋረጡ ቢሆንም ስፖርተኞች ግን በየግላቸው በቤታቸው ውስጥ እንቅስቃሴ ማድረጋቸውን አላቆሙም። ይህንን ተከትሎም ከውድድር ውጪ የሚወሰዱ አበረታች ንጥረ ነገሮችን ከመውሰድ እንዲቆጠቡም ያሳስባሉ። በጥቅሉ በጊዜያዊነት ንክኪ ካለባቸው ሥራዎች በቀር ሌሎች ሥራዎች እንደቀጠሉ ሲሆን፤ የአድራሻ ምዝገባቸውን በመደበኛ መልኩ የሚያደርጉ በመሆኑ በዚህ ላይም መዘናጋት አይገባም። ዓለም አቀፉ የጸረ አበረታች መድኃኒቶች ተቆጣጣሪ ኤጀንሲ በመግለጫው ባመላከተው መሠረት፤ ጽሕፈት ቤቱም እንደቀደመው የአትሌቶችን ናሙና ወደመውሰድና መመርመር ሥራው ለመመለስ የሚያስችለውን ሁኔታ እያጠና ይገኛል። እንደ ዳይሬክተሩ ገለጻ ከሆነም ስፖርተኞች ከባለሙያዎች ጋር የሚኖራቸውን ንክኪ በሚቀንስና ለበሽታው አጋላጭ በማይሆን መልኩ መፍትሄ እንደተገኘ በቀጥታ ምርመራው የሚጀመር ይሆናል። በብሔራዊ ቡድን፣ በክለብ እና በማሰልጠኛ ተቋማት የተያዙ አትሌቶች እንዲሁም በቡድን ሆነው የሚሰሩ ሰልጣኞች በዚህ ወቅት ልምምድ አቋርጠው በቤታቸው ይገኛሉ። ምንም ዓይነት የቡድን እንቅስቃሴ የማይፈቀድ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ አትሌቶች በያሉበት አነስተኛ ልምምድ ብቻ የሚያደርጉ ይሁን እንጂ አሁንም እንደ ተቋም አስጊ ሁኔታዎች መኖራቸው አልቀረም። ይህም ወቅታዊውን ሁኔታ ሽፋን በማድረግ የተከለከሉ ንጥረነገሮችን የመጠቀም አዝማሚያ ሊኖር ይችላል የሚል ስጋት ነው። እስካሁን በተጨባጭ የተገኘ መረጃ ባይኖርም በዓለም አቀፍ ደረጃም ሆነ እንደ ተቋም ስጋቱ አለ። ከአትሌቶች ባሻገር ከጀርባ በመሆን አጋላጭ የሆኑ አካላት አበረታች ቅመሞችን እንዲጠቀሙ በመገፋፋትና በማሳመን የሕግ ጥሰት የመፈጸም አዝማሚያ ሊኖር ይችላል የሚል ግምት አለ። በመሆኑም ስጋቱን ለመቅረፍ የሚያስችሉ ሥራዎች በመከናወን ላይ ነው የሚገኙት። በስፖርተኞች በኩል ስለ ጉዳዩ ያለውን ግንዛቤ ለማስፋትም በመገናኛ ብዙኃን በመታገዝ መልዕክቶች በመተላለፍ ላይ ይገኛሉ። በተመረጡ መገናኛ ብዙኃን ላይም የማስታወቂያ እንዲሁም የማንቂያ ሥራዎች እየተካሄዱ መሆኑን የሚጠቁሙት ዳይሬክተሩ በጽሕፈት ቤቱ ድረገጽም መረጃዎችን እያስተላለፉ ይገኛል። ይህም አትሌቱ በሚመቸው መንገድ መረጃ እንዲያገኝ ያስችለዋል። በቀጣይም በመደበኛነት ማስታወቂያዎቹ የሚተላለፉባቸውን የመገናኛ ብዙኃን ቁጥር ለመጨመር ታቅዷል። ሌላው ጽሕፈት ቤቱ በትኩረት እየሄደበት ያለው የሕግ ማዕቀፍ የማሻሻል ሥራ ነው። ኤጀንሲው የጸረ አበረታች ቅመሞች ሕግን ጨምሮ ሌሎች ዓለም አቀፍ ስታንዳርዶችን አሻሽሏል፤ በመሆኑም በጽሕፈት ቤቱ በኩል እአአ በ2021 ተግባራዊ የሚሆኑ የተለያዩ የሕግ ማዕቀፎችን ለመከለስ በእንቅስቃሴ ላይ ይገኛል። በመጨረሻም ዳይሬክተሩ ስፖርተኞችም ሆኑ ሌሎች የሀገሪቷ ዜጎች የሕክምና ባለሙያዎችን ምክር በመተግበር በዓለም ላይ ከተከሰተው ወረርሽኝ ራሳቸውን እንዲጠብቁ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል። ስፖርተኞች፣ የስፖርት ባለሙያዎች፣ የስፖርት አመራሮች እንዲሁም ሁሉም ባለድርሻ አካላት በበኩላቸው በአበረታች ንጥረ ነገር መከላከልና መቆጣጠር ሥራው ለአፍታ የቆመ ባለመሆኑ መዘናጋት እንዳይኖር ዳይሬክተሩ ያሳስባሉ። ዓለም አቀፉ ኤጀንሲም ሆነ የዓለም አትሌቲክስ ይህ ጊዜ ሲያልፍ ስፖርቱ አደጋ ላይ እንዳይወድቅ በጥንቃቄ እየተመለከቱት ነው። በዚህ መሠረት የሚመለከታቸው አካላት ጥንቃቄ ማድረግ አለባቸው። ተጠቃሚነታቸው ከተረጋገጠም ጽሕፈት ቤቱ አስፈላጊውን አስተዳደራዊ እንዲሁም የወንጀል እርምጃ ከመውሰድ ወደኋላ የማይል በመሆኑ ስፖርተኛው በመደበኛ ጥንቃቄው መቀጠል እንዳለበት ዳይሬክተሩ አስቀምጠዋል።አዲስ ዘመን ግንቦት 10/2012ብርሃን ፈይሳ
https://www.press.et/Ama/?p=32614
790
2ስፖርት
ኢትዮጵያ በተባበሩት መንግሥታት የፀረ-ሙስና ኮንቬንሽን አንቀጽ 44 ላይ የነበራትን ተዓቅቦ አነሳች
ሀገር አቀፍ ዜና
January 2, 2021
7
በጋዜጣው ሪፖርተር አዲስ አበባ፦ ኢትዮጵያ ወንጀለኞችን አሳልፎ መስጠት (Extradition) የሚደነግገው የተባበሩት መንግሥታት የፀረ-ሙስና ኮንቬንሽን አንቀጽ 44 ላይ የነበራትን ተዓቅቦ አነሳች። የፌዴራል ሥነ-ምግባርና የፀረ ሙስና ኮሚሽን ለዝግጅት ክፍሉ በላከው መግለጫ ኢትዮጵያ በተባበሩት መንግሥታት የፀረ-ሙስና ኮንቬንሽን አንቀጽ 44 ላይ ያላትን ተዓቅቦ አንስታለች ብሏል።ኢትዮጵያ የኮንቬንሽኑን አንቀጽ 44 አስመልክቶ ተዓቅቦ (reservation) እንዳላት የኮንቬንሽኑ ምዕራፍ ሦስት ውስጥ የተመለከተውን የሙስና ወንጀልን ወንጀል አድርጎ መደንገግና ምዕራፍ አራት ዓለም አቀፍ ትብብርን አስመልክቶ እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር ከ2010 አስከ 2015 ባለው ጊዜ የነበራትን አፈጻጸም ለገምጋሚ አገራት አቅርባ ማስገምገሟን ገልጿል። የአፈጻጸም ግምገማን ተከትሎ ኢትዮጵያ እንድታስተካክል ተሰጥተዋት ከነበሩ ምክረ ሃሳቦች አንዱ ከላይ በተጠቀሰው የኮንቬንሽኑ አንቀጽ ላይ ያላት ተዓቅቦ እንደነበር በመግለጫው ተመልክቷል።በዚህ ግምገማ መሠረት ኢትዮጵያ አንቀጽ 44 ላይ የነበራትን ተዓቅቦ ያነሳች ሲሆን፤ የፕሮቶኮሉን ድንጋጌዎች በሙሉ በማክበር ግዴታዎቿን እንደምትወጣ አረጋግጣለች። አንቀጽ 44 ላይ ያላት ተዓቅቦ መነሳቱን መቀመጫውን ኦስትሪያ ቬና ላደረገው የተባበሩት መንግሥታት የአደገኛ ዕፅ እና ወንጀል መቆጣጠሪያ ጽህፈት ቤት (UNODC) እንዳስታወቀችም የኮሚሽኑ መግለጫ አመልክቷል። ኢትዮጵያ የተባበሩት መንግሥታት የፀረ-ሙስና ኮንቬንሽን አባል አገር በመሆን በኮንቬንሽኑ የተቀመጡ ድንጋጌዎችን ለመተግበር በመስማማት በፊርማዋ አጽድቃ በሕግ አውጪ ፓርላማዋ በአዋጅ ቁጥር 544/1999 ኮንቬንሽኑን በማጽደቅና የሀገሪቱ የሕግ አካል በማድረግ ኮንቬንሽኑን ከሚተገብሩ አገራት መካከል ትጠቀሳለች፡፡ አዲስ ዘመን ታህሳስ 24/2013
https://www.press.et/Ama/?p=38673
176
0ሀገር አቀፍ ዜና
የት ሄዱ?
መዝናኛ
October 11, 2019
36
ሁሌም ጠዋት ጠዋት ቁርሴን እየበላሁ ትስስራቸው ጠብቆ ፍቅራቸው ሞቆ አብሮነታቸው ጎልቶ የሚታዩኝ ጥንዶች ዘወትር አገኛቸው ከነበረበት ቦታ አጣኋቸውና ብዙ ጠየቅሁ። በነገራችን ላይ እኛ ግቢ የሰው አይን ማረፊያ መሆናቸውን፤ በሁሉም ዘንድ እውቅና የተሰጣቸው ጥንዶች መሆናቸው ጥያቄ የጠየኩት ሁሉ ስለነሱ ሳነሳ በሚመለሰው መልስ አወቅሁ። አዎን! እንደኔ ሌሎችም መድረሻቸው አሳስቦታል። “የት ሄደው ይሆን?” ብዙ መላ ምቶች አሰብኩ። “ተጣልተው ይሆን?” የዘንድሮ ፍቅር የኢንዶሚን አይነት ነው ቶሎ ሞቆ ቶሎ ደርሶ ተፋፍሞ ወዲያው ጣፍጦ በፍጥነት የሚያልቅ። የእርስ በርስ ቁርኝታችን ላልቶ ማህበራዊ ግንኙነታችን ሻክሮ እንደው ምን ነካን? የሚያስብል ደረጃ ላይ ደርሰናልና መፋቀር፣ ፍቅር ስናይ መገረም፤ መዋደድን ስናስተውል መመሰጥ ተላምደናል። በፍቅር መተሳሰሩ፤ በመውደድ መጣመሩ የሚሰጠውን ልዩ ጣዕም የሚያሳጡን ጉዳዮች በዝተዋልና ደጋግመን ምሬት፤ መስማት መነጣጠል ማየት አዘውትረናል። ፍቅር መገኛው የት ይሆን? ተፋቀሪዎችስ የት ገቡ? ማለታችን በዝቷል። ምን እናድርግ ሰው ከፍቅር ይልቅ ጠብ ቀሎታል። ከአንድነት ይልቅ መነጠል ብቸኝነት ውስጡ ሆኗል።“ሲሄዱም አንድ ላይ ሲጠጡም አንድ ላይ ለየብቻ እንዳላይ..” ያለው ዘፋኝ፤ ማለቴ የስንኙ ባለቤት እነዚህን ጥንዶች አይቶ ይሆን እንዴ? እንጃ ይመስላል፤ ለየብቻ መሆን ፈፅሞ የማይሆንላቸው እነዚያ ጥንዶች ብቻውን የሆነ ሰው ሲያዩ ምን ይሉ ይሆን? አሁን ላይ ብቸኝነት በርክቷልና ተላምደውት እያለፉን ይሆናል እንጂ አስቁመው ለምን ብለው ሁላ የሚጠይቁን ይመስለኛል። በዚህ ፍቅር የኑሮን ያህል በተወደደበት ዘመን ላይ ተገኝተን የእርስ በርስ ግንኙነታችንን አለዘብነው። ከአብሮነት ይልቅ ብቻነት ቀለለን። ሁኔታችን የሎሬት ፀጋዬ ገብረ መድህንን ግጥም “ፈራን ፍቅርን ፈራን” ደጋግሞ ያስነበንባል። አዎን ፈርተናል። መተሳሰርን አብሮነትን ንቀናል። እኔ ምለው? ለብቻ መሆንን የመረጥነው በአብሮነት መኖሩ ሰልችቶን ይሆን እንዴ? በእርግጥ መቀራረባችን አንድ ላይ መሆናችን እኮ አሁንም አለ። ችግሩ ውስጣዊ ጥምረት ነው ከኛ የነጠፈው። እንጂማ “ውዴ፣ ማሬ፣ ከረሜላዬ” መባባሉን በጣም ተክነንበታል። ማፍቀር ቢያቅተን እንዴት የፍቅር ተጓዦችን ማድነቅ ያቅተናል። ፍቅረኞችን ማየት ናፍቃችሁ ታውቃላችሁ? እውነተኛ ጥምረት ማርኳችሁስ ያውቃል? በበጎ ነገር መማረክ በጎነትን ያላምዳል። ፍቅርን መናፈቅ ወደ ፍቅር ጉዞ ሚያደርጉትን መንገድ ያሰምራል። እኔ ግን በእነዚህ ጥንዶች ተጠልፌያለው። አብሮነታቸው ሰምሮ፤ አንድነታቸው ቀጥሎ፤ መተሳሰራቸው ጎልብቶ ማየት ተመኘሁ። “ፍቅር ግን አለ?” ብለው ለሚጠይቁ ሰዎች “አዎን በደንብ ነዋ!” የሚያስብሉ የመውደድና የፍቅር ጥግ የሚያስኮመኩሙ፤ ፍቅርን ከማሳየት በላይ የሚኖሩት አሉ። “ይሄው እዚህ ዘንድ ተመልከቱ!” የሚያስብሉ አንዳንድ የፍቅር መልዕክተኞች አልፎ አልፎ ይገጥሙናል። እኔም አንድ መዝናኛ ውስጥ የሱስ ያህል አብሬ ካላየኋቸው ቅር የሚለኝ፤ ጥምረትና አንድነታቸው የሚያስገርመኝ ፍቅረኛሞች ገጥመውኛል። እንዲያው ጥብቅብቅ ብለው ሲበሉ፤ ሲያወሩ፤ ሲጓዙ አዎን ፍቅር ያስውባል፤ ያሳምራል የሚያሰኙ ጥንዶች ከእይታዬ ሳጣቸው ናፈቁኝ። የመዝናኛው ተጠቃሚ መነጋገሪያ፤ የቤቱ ደንበኛ ሁሉ አይን ማሪፊያ የነበሩት ጥንዶች የት ሄዱ? ስለናፈቁኝ ፍቅረኛሞች፤ ከአይኔ ስለራቁት ጥንዶች ደጋግሜ ማሰቤ ብሎም መጠየቄን አጠናከርኩ። በእርግጥ የጠፉበትን ምክንያት ባውቅም ጥፉ የተባሉበት መንገድ ቅር አሰኘኝ።ትናንት ከአንዱ ባልደረባዬ ጋር ስናወጋ ማዕቀብ ተጥሎባቸው ከቤቱ መጥፋታቸው ተነገረኝ። እርግጥ ነው አንዳንዴ ይሳሳሙ ነበር። መሳሳማቸው ግን በፍቅር ስለሆነ በጠብ ከምንናከሰው ከብዙዎቻችን የነርሱ የተሻለ ነው። እርግጥ ነው አብረው የሆኑ ሳይሆን አንድ የሆኑ ያህል ይጠባበቁ ነበር። ግን ከኛ መገፋፋት የነእርሱ መጣበቅ ይሻላል። እርግጥ ነው በተቀመጡበት ሁሉ በፍቅር አፍ ላፍ ገጥመው ያወሩ ነበር። ግን ከኛ ተደብቆ ከመተማማት እሱ ይልቃል። በማውራታቸው መሀል ከተራ ግንኙነት ያለፈ ጥምረት የሚፈጥር መግነጢሳዊ ሃይል አለ። ሲያወሩ፣ ሲሳሳሙም ሰው አያዩም። ምክንያቱም ፍቅር እውነት እንጂ ሌላ አይታየውም። ፍቅር አይፈራም። በእርግጥ ጨዋነት በሚያጎድል መልኩ፣ ባህልን በማያፋልስ መልኩ ቢያደርጉት መልካም ነበር። ሲሳሳሙ ግን ሁሉም አፍጥጦ ያይ፣ ይመለከታቸው ነበር። መሳሳማቸውን እየተቃወመም ቢሆን እንዳያቋርጡት ይመኝ ነበር። እነሱም ባስተሳሰራቸው ፍቅር ተጠልለው ሌላውን አያዩትም ነበር። ፍቅር እኮ መሸሸጊያ፤ መከለያ ነው። እሱ ውስጥ ተሁኖ ሌላ አይታይም። ፍቅር ያሉበትን አስረሳቸው። እና እነዚህ ጥንዶች ሁሌ ከሚቀመጡበት ቦታ ሳጣቸው ጠየቅሁ። ሁሌም ከሚጓዙበት መንገድ ሳጣቸው የትነታቸውን ለማወቅ ወተወትኩ። “አትምጡ!” ተብለው እንደሆነ ስሰማ ተገረምኩ።“መፋቀራችሁ፣ መጣመራችሁ፣ መዋሃዳችሁ ትክክል ነው። አንዳንዴ ሳታውቁት የምትሳሳሙትን ቢያንስ አቁሙ” ማለት ሲገባ፤ “እዚህ ቤት መሳሳማችሁ ያስከፋቸው ሰዎች ስላሉ ወደዚህ ድርሽ ባትሉ መልካም ነው” መባሉ ግን ተገቢ አይደለም። እናም ተፋቃሪዎቹን ያባረረው መዝናኛ ጠበኞችን ሰብስቦ ሊያውል ማሰቡ ይሆን እንዴ? የት ይሆኑ ግን? ያያቸው አለ? አበቃሁ! ቸር ይግጠመን።አዲስ ዘመን መስከረም 30/2012
https://www.press.et/Ama/?p=20466
559
1መዝናኛ
«ቀዝቃዛ ቮልካኖ»
መዝናኛ
October 13, 2019
44
መቼም ጆሮ ሰጥቶ ላደመጠ ፣ አይኑን ከፍቶ ለተመለከተ፣ተስፋ ሰንቆ ራዕይ አስቀምጦ ለተጓዘ፣ ቅን ልቦና ያለው ሁሉ፣… በዚህ ዘመን ብዙ ነገሮችን ያስተውላል። ያያል፣ ያደምጣል፤ አእምሮ ያለው ሰው ከሆነ ደግሞ ቁም ነገሮችን ይጨብጣል። የተሳሳተውን ያርማል። አዳዲስ ነገሮች ይማራል ፤ ይሰንቃል። ይሄ ልብ ላለው ነው፤ ለሌለውስ ? ብሎ ለሚጠይቅ ምላሹ ለሁሉም የሚል ይሆናል። ልብ ላጣ ልብ መመለሻ ጊዜ ነው። ነገር ግን ልባችንን ተስፋ ሳይሆን ጥቀርሻ ሸፍነን፤ በብርሀን ሳይሆን በሀምሌ ዳመና ጋርደን ፤ አይናችንን ከፍተን ሳይሆን ጨፍነን አላየንም ፣አልሰማንም፣ አንሰማም ብለን ብቻ ክፋትን የምናስብ ከሆነ እርግጠኛ ሆኖ ለመናገር ነጩ ጥቁር ነው። ያውም ጭግግ ያለ የክረምት ሌሊት። የተስፋ ብርሀን እያየ በብርሀን ውስጥ እየተመላለሰ መሆኑን ለተረዳ ደግሞ ማለዳ የፈነጠቀ ጸሀይ ከፊት ለፊቱ ይታየዋል። ተስፋውም በዚያው ልክ ቦግ ቦግ ይላል። እንግዲህ ጆሮውን ሰጥቶ፣ አእምሮውን ከፍቶ ላደመጠ ብዙ ጣፋጭ ምግቦች አሉ እያልኩ ነው። ካጣጣምኩት አንዱን ጣፋጭ ተቋደሱ ብልስ ታዲያ። እንደእውነቱ ከሆነ መልካም ነገርን ያቋደሰ እንዳውም ይመሰገናል፤ ይመረቃል እና እኔም ይሄው ምርቃት እንደማይነፈገኝ እርግጠኛ ነኝ። ተመርቆ ደስ የማይለው ሊኖር ይችል ይሆን? ብቻ መራቂ አያሳጣን ማለት መልካም ነው። እንዳው የእኔ ነገር ከተነሳሁበት ጉዳይ ጭልጥ ብዬ ወጣሁ እንዴ ልመለስ። ያንን ያደመጥኩትን መልካም ነገር ወደ መንገሩ፤ አልማዝ ከስም በላይ ነው ልል አሰብኩና እውነት ነው አልማዝ ማዕድን ነው። ያውም የከበረ ማዕድን በጥቂቶች እጅ ላይ የሚገኝ ውድ፣ አንፀባራቂ፣ አጓጊ ብቻ አልማዝ ን የሚያውቀው ያውቀዋል ብዬ ባቆምስ። እኔ ከማውቀው በላይ እናንተ የአልማዝን ክብር ፣ ዋጋ ፣ እሱን ለማግኘት የሚደረገውን ልፋት ፤ ልፋት ብቻም ሳይሆን ተፈጥሮም አግዛና ተጋግዛ እኮ ነው አንድን አገር አልማዝ በአልማዝ የምታደርገው። ሀብታም ሀገሮች ናቸው እነ እገሌ የሚባሉት በሌላ አይደለም ከምድር ውስጥ በሚያገኙት ማዕድን አይደል?አንድ ምሁር በተለይ ለእኔ ትልቅ ምሁር ካልኩት ሰው አንደበት የወጣውን ነው።ምሁር መቼም አስተዋይ፣ አርቆ አሳቢ፣ ቅን፣ ሀገርና ወገኑን የሚወድ፣ የሚያከብር፣ ለሀገሩ የቆመ አዋቂ ነው ። ለእኔ እንደዛ ነው የሚሰማኝ። ታዲያ ይሄ ሰው አልማዝ እንዴት ተሰራ የሚለውን በአንድ መድረክ ላይ ቆሞ ያብራራል። እኔም በተመስጦ እያዳመጥኩ ነው። አልማዝ የሚለውን የከበረ ዋጋው እጅግ በጣም ውድ ነገር በሽበሽ ብሎ የማይገኝ በመሆኑ መቼም ማናችንም ብንሆን ለአልማዝ የምንሰጠው ዋጋ ስም እንደማውጣት የቀለለ አይደለም። ስም አውጪዎቹ ቦታ ያለው ክብር ግን ልጆቻቸው እንደዛ የከበረ ማዕድን ተወዳጅ፣ ተፈላጊ፣ አጓጊ እንዲሆኑላቸው በመመኘት ነው። መልከ ጥፉን በስም ይደግፉ እንደሚባለው አባባል እንደማይሆን አምናለሁ። መልካም መልካሙን ተመኝተው ስም ላወጡት እንዳው ክብር ይገባቸዋል ብልስ ምክንያቱም ዛሬ እኮ ስም የሚወጣው በትርጉም፣ መልካም በመመኘት ሳይሆን አፍ ላይ በቀለለ ሳይሆን ቀረ ብላችሁ ነው? እነ ቲቲ፣ ቡቹ ፣ቶሚ… መጠሪያ ሆነው እነ የውብ ዳር፣ ቆንጅት፣ ሞገስ፣ ነዋይ… አይነቶቹ ሀገር በቀል ስሞች ዳይ ወደ ጓዳ ተብለዋል። ድሮ ድሮ ልጅ ነበር ወደ ጓዳ የሚባለው ያውም እንግዳ ሲመጣ። ልጅስ ምን ሊያደርግ ማን ፈቅዶለት ሳሎን ወጥቶ። ለማንኛውም የዛሬው ጉዳዬ ስም ላይ አይደለምና እናሳድረው።እና እንዲህ ይላል ያ ሰው አልማዝ እንዴት እንደሚገኝ ታውቃላችሁ? ይጠይቃል ደግሞ ማብራሪያውን ሲሰጥ “ አልማዝ በጣም ርቀት ባለው ጥልቅ መሬት ውስጥ ፣እጅግ በጣም ከፍተኛ ሙቀት እንዲሁም እጅግ በጣም ከባድ ግፊት ባለበት ፣ በጣም ረጅም ዘመን ኖሮ የሚወጣ ማዕድን ነው። ይህን ማዕድን እንዴት ማውጣት ይቻላል ከተባለ አልማዝ የሚወጣው ከባድ እሳተገሞራ (ቮልካኖ) ሲፈጠር ያንጊዜ ገንፍሎ ይፈሳል። ያንን አብረቅራቂ ነገር ከቆሻሻው በመለየት ሞርዶና አስተካክሎ በማሳመር ማዕድኑ ይወጣል። ከፈለጋችሁ ከሰልም አልማዝ መሆን ይችላል። እንዴት ካላችሁ አሁን አልማዝ እንዴት እንደሚገኝ ባየነው መንገድ ተጉዞ ። ይሄንን ወደ አገር እንውሰደው ኢትዮጵያም እንደ አልማዝ ናት ።በከፍተኛ ችግር ለረጅም ዓመታት በስቃይ በየዘመኑ በሚፈጠር ውጥረት ስትታመስ ኖራለች። ከባድ ድርቅ ፣ጦርነት፣ መፈናቀል፣ ረሀብ… በመሳሰሉት ተወጥራ ረጅም ዘመናትን አሳልፋለች። አሁን ቀዝቃዛ ቮልካኖ ( እሳተ ጎሞራ) በመውጣቱ ምክንያት መጠነኛ ለውጥ ታይቷል። ይሄ የእሳተ ገሞራው ውጤት ነው።”ይላል። ንግግሩ መሳጭ ነው። አንደበተ ርዕቱና ትሁት ሰው መሆኑን ከአንደበቱ የሚንቆረቆረው ጆሮ ግቡ ንግግሩ ይመሰክራል። ንግግሩን አላበቃም። ቀጠለ “አሁን ያንን አልማዝ መሳይ ለውጥ በመሞረድ ለማስተካከል ጥረት ማድረግ ከሁሉም ይጠበቃል። በደንብ መስራት ከተቻለ አልማዝ ውድ ዋጋ እንደሚያወጣ ሁሉ ለውጡም እጅግ በጣም ውድ የሆነውን የምንናፍቀውን የምናልመውን ብልጽግናን ያመጣል። ይሄ የሚሆነው ታዲያ በአልማዙ መጠቀም ለቻለ ብቻ ነው።” እንግዲህ ይሄን ሀሳብ ከአደመጥኩት ላይ የወሰድኩት በመሆኑ ቃል በቃል አላሳረፍኩትም። ምን አልባት ያጎደልኩት ፣ ያሰፋሁት ካለ እንደክፋት ሳይቆጠርብኝ ይቅርታ ልጠይቅ። በይቅርታና በምህረት ዘመን ጥፋትን ማመን፣ ይቅርታ መጠየቅ ሁለተኛ ላለማጥፋት ግማሽ መንገድ እንደመሄድ ነውና። እንዲህ ከሆነ ቶሎ ቶሎ ስህተቶቻንን እያረምን፣ ጥፋታችንን እያስተካከልንና ከጥፋታችን እየተማማርን የበለጸገች አገር እንገነባለን ። መቼም ብልጽግና የሚለውን ቃል መጥራት በራሱ መበልጸግ ይመስለኛል። ምክንያቱም ብዙ ጊዜ የምናወራቸው፣ የምናደምጣቸው ፣ በየድረ ገጹ የምናነባቸው ተስፋ የሚያስቆርጡ አይነት ነገር ናቸውና። እንዲህ አይነቱ ታዲያ ለመስራትም፣ ለመለወጥም፣ ለመማርም፣ የተሻለ ለማሰብም እድል አይሰጥም። ስለዚህ ስለተስፋና ብልጽግና እናልም።ሰላም!አዲስ ዘመን ጥቅምት 2/2012 አልማዝ አያሌው
https://www.press.et/Ama/?p=20668
664
1መዝናኛ
የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ክለቦች ሊጉን ለማጠናቀቅ ቆርጠው ተነስተዋል
ስፖርት
May 5, 2020
27
ዓለምን በአንድነት እያስጨነቀ የሚገኘው ወቅታዊ ጉዳይ የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ19) ወረርሽኝ መሆኑ ይታወቃል። የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ለመግታት ያስቻለ ፈውስ በዓለም ሳይንቲስቶች፣ የህክምና ጠቢባንም ይሁን በሃያላን አገራት አቅም ማምጣት አልተቻለም። ይህም የዓለምን ነባራዊ ሁኔታ ከመለወጥ አንስቶ በተለያዩ ዘርፎች ላይ በርካታ አሉታዊ ተፅዕኖው እንዲያርፍ አድርጓል። የስፖርቱ ዓለም በቫይረሱ ስጋት ሳቢያ ብዙ ተጽዕኖ እያስተናገደ ከመሆኑ ባሻገር፤ ለከፍተኛ ኪሳራ መዳረጉን መረጃዎች ያመላክታሉ። በወረርሽኙ ሳቢያ ትልልቅ የስፖርት ውድድሮች በመራዘማቸው፣ በመሰረዛቸው እና በመስተጓጐላቸው ኢንዱስትሪውን ከፍተኛ ገቢ እንደሚያሳጣው የተለያዩ ትንበያዎች አመልክተዋል። የስፖርት ኢንዱስትሪውን በስፖንሰ ርሺፕ የሚደግፉ ትልልቅ ዓለም አቀፍ ኩባንያዎች የበጀት ቀውስ ውስጥ መግባታቸው፣ ከትኬት ሽያጭ ከማርኬቲንግና ከተለያዩ ንግዶች የሚገኙ ገቢዎች መቆማቸው ሁሉንም ስፖርት ጎድቷቸዋል፡፡ በተለይ የእግር ኳስ ስፖርት ከፍተኛ ድርሻ የሚይዝ መሆኑ እየተነገረ ይገኛል። በዚህ ዓመት የእግር ኳሱ ገቢ በከፍተኛ ሁኔታ ይጨምራል ተብሎ ሲጠበቅ ከተላላፊው ቫይረስ ጋር በተያያዘ ገቢው በእጅጉ እያሽቆለቆለ ይገኛል። የስፖርት እንቅስቃሴን ጨምሮ ሌሎች መደበኛ እንቅስቃሴዎችን በቅርብ ጊዜ ማድረግ የሚቻልበት ሁኔታ ተስፋ ሰጪ ምልክቶች እየታዩ አለመሆኑ፤ በኢንደስትሪው ላይ የሚደርሰው ቀውስ እንዲያሻቅብ እንደሚያደርገው ተነግሯል። የቫይረሱ ስርጭት በዓለም ዙሪያ እያሻቀበ በመሆኑ ታላላቅ ስፖርታዊ ውድድሮች በቅርቡ ወደ መደበኛ እንቅስቃሴያቸው የሚመለሱበት ሁኔታ ጠባብ መሆኑ እየተነገረ ባለበት ወቅት ቢቢሲ ከቀናት በፊት ይዞት የወጣው መረጃ ተስፋ ሰጪ ሆኗል። ቢቢሲ ፤ የዓለማችን ታላላቅ የእግር ኳስ ሊጎች በዝግ ስታድየምም ቢሆን የውድድር ዓመቱን ቀሪ መርሃግብሮች ለማጠናቀቅ በቅርቡ ወደ ውድድር ሊመለሱ መሆኑን ጽፏል። ከዚህ ውስጥ ደግሞ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ግንባር ቀደም ሊሆን እንደሚችል አስነብቧል። የውድድር ዓመቱን ቀሪ መርሃግብሮች ለማጠናቀቅ ማሳባቸውን ጠቅሶ፤ በተለይ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ክለቦች ሊጉን ለማጠናቀቅ ቆርጠው ተነስተዋል ሲል አስነብቧል። የዓለም ጤና ድርጅት የሕክምና ባለሙያዎች ግን ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች በትልቅ ደረጃ ወደ መደበኛ እንቅስቃሴያቸው እንዳይመለሱ ምክራቸውን መለገሳቸውን ዘገባው አመልክቷል፡፡ የዓለማችን ታላላቅ የእግር ኳስ ሊጎች በዝግ ስታድየምም ቢሆን የውድድር ዓመቱን ቀሪ መርሃግብሮች ለማጠናቀቅ የተለያዩ ሀገራት ሊጎች እንደ አማራጭ እየቀረበ ይገኛል። በዝግ ስታዲየም ውድድሮችን አማራጭን ወደ ተግባር ለመቀየር የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ክለቦች ቆርጠው መነሳታቸውን አስነብቧል። የ2020 የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ በኮሮና ወረርሽኝ ምክንያት መጋቢት ወር መግቢያ ላይ ነበር የተቋረጠው። ሊጉ የውድድር ዘመኑ ሊጠናቀቅ 92 ጨዋታዎች ይቀሩታል። የቫይረሱ ስርጭት በዓለም ዙሪያ እያሻቀበ መሄዱን ተከትሎም የውድድር ዘመኑን በመደበኛው መልኩ ለማካሄድ ለመመለስ የሚያስችል ተስፋ የለም። የ2020 ውድድር ዘመን 92 ጨዋታዎችን እንዴት እናጠናቅ በሚለው ዙሪያ የሊጉ ክለቦች የቪድዮ ስብሰባ አድርገዋል። በስብሰባው ላይ እንደ ሕክምና ባለሙያዎች ያሉ ያገባቸዋል የተባሉ ሰዎችም ተገኝተው ነበር። ክለቦች ሊጉ በቀላሉ ወደ ውድድር እንደማይመለስ መግባባት ላይ ደርሰዋል። የውድድር ዓመቱን ለማጠናቀቅ የተቀሩትን ውድድሮች በዝግ ስታዲየም ለማድረግ ከስምምነት መድረሳቸውን ቢቢሲ አስነብቧል። በቪዲዮ ስብሰባ ወቅት «የሊጉ ክለቦች ይህን ለማድረግ ደግሞ ቢያንስ 10 ገለልተኛ ሜዳዎች ያስፈልጋሉ ። ገለልተኛ ሜዳዎችን መጠቀም ያስፈለገው ደጋፊዎች ከሜዳ ውጪም ቢሆን እንዳይሰበሰቡ በማሰብ ነው። አልፎም የሚመረጡት ሜዳዎች ከፖሊስና የስፖርት ሜዳዎችን ደህንነት ከሚመረምር አካል ይሁንታ ያገኙ መሆን አለባቸው» መባሉን በዘገባው አስፍሯል። በተጨማሪም ተጫዋቾች በሳምንት ሁለት ጊዜ የኮሮናቫይረስ ምርመራ ይደርግላቸዋል። በየቀኑ ደግሞ የበሽታው ምልክት ታየባቸው አልታየባቸው የሚለው ይለካል። አልፎም ሜዳዎች በየጊዜው ንፅህናቸው ይጣራል ተብሏል። ተጫዋቾች ከጨዋታ ውጪ ባሉት ጊዜያት ሁሉ የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ጭምብል ማድረግ አለባቸው። በውድድር ስፍራዎች ውስጥም ምግብ መብላትም ሆነ ገላን መታጠብ እንዳይችሉ የሚደረግ መሆኑን አመልክቷል። የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ክለቦች ሊጉን ለማ ጠናቀቅ በገለልተኛ ሜዳ ውድድሮችን ለማድረግ ከስምምነት መድረስ ቢችሉም ከሀገሪቱ መንግስት በኩል የሚኖረውን ተቀባይነት ምን ሊሆን ይችላል ? የሚለው ምላሽ የሚያሻ መሆኑን ዘገባው አንስቷል። የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግን መጋቢት ወር መግቢያ ላይ ነበር በኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት እንዲቆም የተደረገው። የፕሪሚየር ሊጉ አስተዳዳሪ አካል መንግሥት ይሁንታ ሲሰጥ ብቻ ወደ ሜዳ የሚመለስ መሆኑን ዘገባው አመልክቷል። የውድድር አመቱ የቀሩትን 92 ጨዋታዎች ለመጫወት ከስምምነት ቢደርሱም የሀገሪቱ መንግስት ውሳኔ ምን ሊሆን እንደሚችል የተባለ ነገር አለመኖሩን ዘገባው ጠቅሷል። የዚህ ዓመት ወድድር ይቋረጥ የሚል ሐሳብ ከየትኛውም ክለብ አልመጣም ነበር። በመሆኑም በሁሉም የሊጉ ክለቦች በኩል የተወሰነው ውሳኔ ከመንግስት ድጋፍ የሚያገኝ ከሆነ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መቋጫው በቅርብ ጊዜያት ውስጥ ሊሆን እንደሚችል ግምቱን አስፍሯል። የእንግሊዝ መንግሥት እንቅስቃሴዎች ቀስ በቀስ ወደነበሩበት እንዲመለሱ ካደረገ በኋላ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ በዝግ ሜዳ ወደ ውድድር እንደሚመለስ ይጠበቃል።አዲስ ዘመን ሚያዝያ 27/2012ዳንኤል ዘነበ
https://www.press.et/Ama/?p=31713
577
2ስፖርት
ኦሊምፒክ ኮሚቴ አትሌቶችን እደግፋለሁ አለ
ስፖርት
May 5, 2020
18
የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ምክንያት ከውድድር ውጪ ለሆኑ ብሔራዊ አትሌቶች አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ አስታወቀ፡፡ የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ተጠሪነቱ ምንም እንኳ ለሁሉም ብሔራዊ ፌዴሬሽኖች ቢሆንም፣ ብሔራዊ አትሌቶችን በሒደት ከገንዘብ ድጎማ ጀምሮ የተለያዩ ድጋፎችን ለማድረግ እየሠራ መሆኑ ፕሬዚዳንቱ ዶክተር አሸብር ወልደ ጊዮርጊስ አስታውቀዋል፡፡ ከድጋፉ ባሻገር የዓለም አቀፍ ኦሊምፒክ ኮሚቴ (አይኦሲ) የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ከመከሰቱ በፊት ለአገሮች በሰጠው ነፃ የትምህርት ዕድል ኮታ መሠረት ኤሊት አትሌቶች ዕድሉን እንዲጠቀሙ ለማድረግ ሥራዎችን እየሠራ እንደሚገኝም ገልጸዋል፡፡ ብሔራዊ ተቋማት ችግሩ በአትሌቶች ላይ ሥነ ልቦናዊና ኢኮኖሚያዊ ጫና እንዳያሳድር የሚችሉትን እያደረጉ ይገኛሉ። ቀደም ሲል የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ከ15 ሚሊዮን ብር በላይ በማውጣት አትሌቶችንና መሰል ሙያተኞችን መደጎሙ አይዘነጋም፡፡ አዲስ ዘመን ሚያዝያ 27/2012
https://www.press.et/Ama/?p=31712
101
2ስፖርት
ካፍ ለአፍሪካ እግር ኳስ አባል አገሮች የሰጠው ቀነ ገደብ ዛሬ ይጠናቀቃል
ስፖርት
May 5, 2020
23
አፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን ካፍ አባል ሀገራት የተቀመጠላቸው ቀነ ቀደብ ዛሬ ይጠናቀቃል። የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) በኮቪድ 19 ወረርሽኝ ምክንያት የተቋረጠው የየአገሮቹ የውስጥ ሊግ ለማስቀጠልም ሆነ ለማቋረጥ መደረግ ስለሚገባው የጋራ አቋም አገሮች ከየራሳቸው የሊግ አደረጃጀትና ሁኔታ በመነሳት የሚኖራቸውን ሐሳብ በሚያዝያ 19 ቀን 2012 ዓ.ም መጠየቁ ይታወሳል። ለአፍሪካ እግር ኳስ አባል አገሮች በጻፈው ደብዳቤ በኮቪድ 19 ወረርሽኝ ምክንያት ተቋርጦ የቆየው የየአገሮቹ የውስጥ ሊግ ካለው ነባራዊ ሁኔታ በመነሳት መቀጠልም ሆነ መቋረጥ ካለበት አገሮቹ የየራሳቸውን ሐሳብና ዕቅዳችሁን አሳውቁኝ ነበር ያለው፡፡በዕቅዱ መካተት ይኖርባቸዋል ብሎ የጠቀሳቸው ነጥቦች፣ ሊጉ የተጀመረበትና የሚጠናቀቅበት ጊዜ እንዲሁም ሊጉ የሚቀረው የጨዋታ መርሐ ግብርና የቡድኖች የደረጃ ሰንጠረዥ፣ ሊጉ የተቋረጠበት ወር፣ የሚቀረው የጨዋታ ብዛት፣ ቀሪውን ውድድር እናጠናቅቃለን ለሚሉ ሊከተሉት ስላሰቡት የጨዋታ ሥርዓትና ሁኔታ፣ ማስቀጠል አንችልም የሚሉ ካሉም እንዲሁ በዝርዝር ተብራርቶላቸዋል፡፡ ጥቅሙን በሚመለከት ተቋሙ ወደፊት ውድድሮችን ከመምራት ጀምሮ የሚያከናውናቸው ዕቅዶች ከአባል አገሮች ዕቅዶች ጋር እንዳይጋጩ የመፍትሔ አቅጣጫ ማስቀመጥ ይችል ዘንድ መረጃ ለማሰባሰብ እንደሆነ አስገንዝቧል፡፡ የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) ደብዳቤውን ከመላክ ባሻገር አባል ሀገራቱ ውሳኔያቸውን እስከ ሚያዚያ 27 ቀን 2012 ዓ.ም ድረስ እንዲያሳውቁት ነበር ያሳሰበው። ካፍ ሀገራቱ በውስጥ ውድድራቸውን በተመለከተ ውሳኔ የሚያስተላልፍበት ቀን በዛሬው እለት የሚጠናቀቅ ይሆናል። አዲስ ዘመን ሚያዝያ 27/2012
https://www.press.et/Ama/?p=31720
178
2ስፖርት
የተራዘመው ኦሊምፒክና የዓለም አቀፍ ፌዴሬሽኖች የገንዘብ ጥያቄ
ስፖርት
May 7, 2020
22
የቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ ለአስራ ስድስት ወራት ከመራዘሙ አስቀድሞ የተፈራው ሊደርስ የሚችለው የፋይናንስ ቀውስና ትልቅ የገንዘብ ኪሳራ መሆኑ ይታወቃል።ኦሊምፒኩ እንደተራዘመ ይፋ ከተደረገም በኋላ የአዘጋጇ አገር ጃፓን መንግስትና የዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ በሚደርሰው ኪሳራና ተጨማሪ ወጪ ዙሪያ ውዝግብ ውስጥ መግባታቸው አልቀረም።ዓለም አቀፍ ኮሚቴው ገና ከጅምሩ ኪሳራውን ለማካካስ ሁሉም ባለድርሻ አካላት እንደሚጋሩት ተስፋ አድርጎ የነበረ ቢሆንም አሁን አጣብቂኝ ውስጥ እየገባ መሆኑን የሚጠቁሙ መረጃዎች እየወጡ ይገኛል። የዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ትልቅ ባለድርሻ አካል የሆነው የዓለም አትሌቲክስ ከተራዘመው ኦሊምፒክ ገቢ ጋር በተያያዘ ድርድር መጀመሩን አሳውቋል።የዓለም አትሌቲክስ ፕሬዚዳንቱ ሴባስቲያን ኮ በዚህ ጉዳይ ላይ ከዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ጋር ንግግር መጀመራቸውን ከትናንት በስቲያ ይፋ አድርገዋል። የኢንሳይድ ዘ ጌምስ ሃተታ እንደሚያመለክተውም በርካታ ዓለም አቀፍ የስፖርት ፌዴሬሽኖች ከተራዘመው ኦሊምፒክ ሊያገኙት የነበረውን ገንዘብ መጠየቅ እንደሚጀምሩ ተረጋግጧል።የዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ውድድሩ በመራዘሙ ምክንያት ብቻ ከፍተኛ የገንዘብ ኪሳራ ውስጥ ገብቶ በሚዳክርበት በዚህ ወቅት ባለድርሻው የሆኑት ታላላቅ ዓለም አቀፍ የስፖርት ፌዴሬሽኖች ድርሻቸውን ለመጠየቅ ወደ ኋላ አለማለታቸው አስደንጋጭ ዜና ሆኗል። አሁን ድርሻውን የጠየቀው የዓለም አትሌቲክስ ትልቁ ባለድርሻ ሲሆን የዓለም ውሃ ዋና እና የዓለም ጅምናስቲክ ፌዴሬሽኖች በተከታይነት ትልቅ ድርሻ አላቸው።እነዚህ ፌዴሬሽኖች ብቻ ኦሊምፒኩ በመራዘሙ ቢያንስ እያንዳንዳቸው አርባ ሚሊዮን ዶላር ድርሻ እንዲሰጣቸው መጠየቃቸው እንደማይቀር ታውቋል።ይህም ኦሊምፒክ በመራዘሙ ብቻ በርካታ ውስብስብ ፈተናዎች ውስጥ ለገባው የዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ ሆኖበታል። ‹‹እንደ አብዛኞቹ የኦሊምፒክ ስፖርቶች የዓለም አትሌቲክስም ከኦሊምፒክ የቴሌቪዥን ስርጭት በሚያገኘው ገቢ ላይ ጥገኛ ነው›› ያሉት ሴባስቲያን ኮ ባለፉት አራት ዓመታት ይህን ገቢ ለማግኘት ሲሰራ መቆየቱን ጠቁመው ይህን ገንዘብ ማግኘት የግድ መሆኑን አብራርተዋል፡፡ የዓለም አቀፉ ብስክሌት ፌዴሬሽን ከኦሊምፒኩ የሚያገኘው ገቢ ለጊዜው ቢራዘምም እስከ 2020 አጋማሽ ገቢ ሊደረግ እንደሚገባ ከወር በፊት ማሳወቁ ይታወሳል።የዓለም አቀፉ እጅ ኳስ ፌዴሬሽንም ተመሳሳይ ሃሳብ ያንፀባረቀ ሲሆን ሌሎችም በቀላሉ ሃሳብ እንደማይቀይሩ ይጠበቃል።በተለይም የዓለም አትሌቲክስ ኦሊምፒኩ በመራዘሙ በ2021 በአሜሪካ ዩጂን የሚያካሂደው የዓለም ቻምፒዮና ላይ ተፅዕኖ በመፍጠሩና ጥያቄውን በቀላሉ ወደ ኋላ እንደማይመልሰው ተገምቷል።የ2021 ዩጂን የዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮና ከተራዘመው ኦሊምፒክ ጋር የሚካሄድበት ወቅት የሚጋጭ በመሆኑ ወደ 2022 እንዲራዘም መደረጉ ይታወሳል። ላለፉት ሰባት ዓመታት የበለጠ ዝግጅት ሲደረግበት የቆየው የኦሊምፒክ ውድድር መራዘሙ ከፍተኛ የገንዘብ ኪሳራ ማስከተሉ የአዘጋጆቹ ራስ ምታት እንደሚሆን ቀድሞም የታወቀ ነው።ይህ ከፍተኛ የገንዘብ ኪሳራ የጃፓን መንግስትንም ይሁን ዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴን በእጅጉ ሊፈትን እንደሚችል በባለሙያዎች አስተያየት ሲሰጥበት የቆየ ሲሆን ሁለቱ አካላት ኪሳራውን ለማካካስ እንደሚደጋገፉና ሌሎች ባለድርሻ አካላትም ለዚህ እንዲዘጋጁ ጥሪ ሲያቀርቡ ቆይተዋል። የዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ እንዲህ አይነት ችግሮች ሲገጥሙት ትልቅ ተቋም እንደመሆኑ የመድህን ዋስትና እንዳለው ይታወቃል።አሁን የገጠመው ግን ካለው የመድህን ዋስትና አቅም በላይ በመሆኑ ነው እዚህ ችግር ውስጥ የተዘፈቀው።ስለዚህ የመድህን ዋስትናው በህጉ መሰረት የሚሸፍነው ኪሳራ እንዳለ ሆኖ ተጨማሪ ኪሳራውን የሚያካክስበት አንድ ነገር መፈጠሩ የግድ ይሆናል።ይህንን ተጨማሪ ኪሳራ የጃፓን መንግስት እንደሚሸፍን ጠቅላይ ሚኒስትር ሺንዞ አቤ ቀደም ሲል በተለያዩ አጋጣሚዎች መስማማታቸው ቢገለፅም አሁን የሃሳብ ለውጥ እንዳደረጉ የሚጠቁሙ መረጃዎች መውጣታቸውን ተከትሎ ውዝግቦች መነሳታቸው ይታወሳል።አዲስ ዘመን ሚያዝያ 29/2012ቦጋለ አበበ
https://www.press.et/Ama/?p=31846
421
2ስፖርት
ቡንደስሊጋው በባዶ ስታዲያም ከ10 ቀናት በኋላ ይጀመራል
ስፖርት
May 8, 2020
23
የኮቪድ 19 ወረርሽኝ የዓለምን ሕዝብ በአንድ ልብ የጭንቀት ቋት ውስጥ በመክተት የተጽእኖ በትሩን ማሳረፍ ከጀመረ አራት ወራት አለፉት። በወቅቱ በሀገረ ቻይና ውሃን ከተማ የወረርሽኙ መከሰት ሲሰማ ጉዳዩ እንደዋዛ፣ እንደዘበት ነበር የዓለም ሕዝብ ያደመጠው። ኮቪድ 19 መነሻውን በአንድ ሀገር ያድርግ እንጂ የስርጭቱን አድማስ በፍጥነት በመጨመር ዓለምን አዳርሷል። የቫይረሱ መከሰት ዜና ይፋ ሲደረግ ጉዳዬ ያላለውን የዓለም ሕዝብ በአንድ ልብ ትኩረቱና ስጋቱ ኮሮና ከሆነ አራት ወራት አልፈውታል። በዓለም አቀፍ ደረጃ ሩብ ሚሊዮን ሰዎችን እንደቅጠል ያረገፈው ወረርሽኙን ለመቆጣጠር ጥረቶች ቢደረጉም ዛሬም መፍትሄ ማግኘት አልተገኘም። በዓለም ሳይንቲስቶች፣ የህክምና ጠቢባንም ይሁን በኃያላን አገራት አቅም ማምጣት አለመቻሉ ደግሞ የተጽእኖውን በትር እንዲበረታ አድርጎታል። ኮቪድ-19 ከሰው ልጆች ሕይወት ባሻገር በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ጉዳት ያልዳሰሰው ምድራዊ ኃይል የለም። ወረርሽኝ በእጅጉ ከጎዳቸው ዘርፎች መካከል ስፖርቱ በዋናነት ይጠቀሳል። የስፖርት ኢንዱስትሪውን በስፖንሰር ሺፕ የሚደግፉ ትልልቅ ዓለም አቀፍ ኩባንያዎች የበጀት ቀውስ ውስጥ መግባታቸው፣ ከትኬት ሽያጭ ከማርኬቲንግና ከተለያዩ ንግዶች የሚገኙ ገቢዎች መቆማቸው ሁሉንም ስፖርት ጎድቷቸዋል። በተለይ የእግር ኳስ ስፖርት ከፍተኛ ድርሻ የሚይዝ መሆኑ እየተነገረ ይገኛል። በዚህ ዓመት የእግር ኳሱ ገቢ በከፍተኛ ሁኔታ ይጨምራል ተብሎ ሲጠበቅ ከተላላፊው ቫይረስ ጋር በተያያዘ ገቢው በእጅጉ እያሽቆለቆለ ይገኛል። የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ19) ወረርሽኝ በአጭር ጊዜ ውስጥ ለመቆጣጠር የሚቻል እንዳልሆነ እየወጡ የሚገኙት መረጃዎች የስፖርት እንቅስቃሴን በቅርብ ጊዜ ውስጥ ማድረግ ይጀመራል የሚል ተስፋ እንዳይጣል አድርጓል። ወረርሽኙ በታላላቆቹ የአውሮፓ ክለቦችን ጨምሮ ሁሉም የስፖርት ዘርፍ ላይ እያሳደረ ያለውን የፋይናነስ ቀውስን እንዲያሻቅብ ያደርገዋል ተብሏል። ከሰሞኑ እየወጡ የሚገኙት መረጃዎች ግን ይሄንን የሚሽሩ መሆኑን ቢቢሲ አስነብቧል። በአንዳንድ ሀገራት ላይ ወረርሽኙን መቆጣጠር እየተቻለ መሆኑን ተከትሎ፤ ስፖርታዊ ውድድሮች ሊያደረጉ መሆኑ አስነብቧል። መራሂተ መንግሥት አንጌላ መርኪል በሀገሪቱ የኮሮና ወረርሽኝ እያሳደረ ያለው ተጽእኖ በተመለከተ ከፌዴራል መንግሥቱ ሹማምንቶች ጋር ትናነት በቪዲዮ ኮንፍረንስ ውይይት አድርገዋል። የጀርመን ቦንደንስሊጋው ከአስር ቀን አልያም ከአስራ አምስት ቀናት በኋላ ለማስጀመር የሚያስችለው የስምምነት ሰነድ በውይይቱ ላይ መቅረቡን አመልክቷል። በሀገሪቱ 16ቱም ግዛቶች ከፌዴራል መንግሥቱ ጋር በመጣመር የቫይረሱን ስርጭት ለመቆጣጠር አመርቂ ውጤት ማምጣታቸው ተከትሎ መንግሥት ጥሏቸው የነበሩ ገደቦችን እንዲነሱ ውሳኔ ሊያስተላልፍ መቻላቸውን ዘገባው አትቷል። መራሄተ መንግሥት አንጌላ መርክል እንደተናገሩት «ጀርመን የቫይረሱን የስርጭት ፍጥነት ለመቀነስ የወጠነችው ግብ በመሳካቱ የንግድ ቦታዎች እንዲከፈቱና ደንበኞቻቸውን ማስተናገድ ይችላሉ። ከዚህም በተጨማሪ ቡንደስሊጋውም እንዲጀመር ተወስኗል» ማለታቸውን ጠቅሶ፤ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ መከሰቱን ተከትሎ ከተቋረጡ የሊግ ውድድሮች ውስጥ አንዱ የሆነው የጀርመን ቡንደስሊጋ በቅርቡ ወደ ውድድር የሚመለስ ይሆናልም ብሏል። ጀርመን እንዲህ ዓይነቱ መረጃ ከተሰሙባቸው ጥቂት ሀገራት ግንባር ቀደም መሆን ያስችላታል የሚለው ዘገባው፤ የጀርመን እግር ኳስ ሊግ ቡንደስሊጋው የፊታችን ግንቦት 1 ወደ ውድድር በመመለስ ያለ ተመልካች ውድድሮቹን አድርጎ ለማጠናቀቅ ዝግጁ እንደሆነ ሲገልጽ መቆየቱን አስታውሷል። ቡንደስሊጋውን እና የሁለተኛ ዲቪዥን ጨዋታዎችን የሚያስተዳደረው የጀርመን እግር ኳስ ሊግ ከ36 ፕሮፌሽናል ክለቦች ጋር ከሳምንት በፊት በነበረው ውይይት የዘንድሮውን የውድድር ዓመት ያለተመልካች የመጨረስ ፍላጎት እንዳለው ከስምምነት ተደርሶ ነበር። የጀርመን እግር ኳስ ሊግ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ክርስቲያን ሲፈርት ቦንደንስሊጋው ከአስራ ቀናት በኋላ እንዲጀመር በተላለፈውን ውሳኔ በእጅጉ ደስተኛ መሆናቸውን ተናግረዋል። በውድድሩ ተሳታፊ ክለቦች መካከል ውድድሩን መስመር በያዘ መልኩ ለማካሄድ ቀደም ሲል የስምምነት ሰነድ መዘጋጀቱን ሥራ አስፈጻሚው ገልጸው፤ «ግጥሚያዎቹ ከመጀመራቸው በፊት ለሁለት ሳምንታት በለይቶ ማቆያ፤ ምናልባትም በስልጠና ካምፖች ውስጥ እንዲሆኑ ይጠይቃል። በመጀመሪያውና በሁለተኛው ዲቪዚዮን 36 ቡድኖች ውድድራቸውን እንዲጀምሩ የሚደረግ መሆኑ በሰነዱ ተካቷል። ክለቦች የሚደርስባቸውን የምጣኔ ሀብቱን ጉዳት መቀነስ እንዲቻል ከግንዛቤ በማስገባት ነው» ሲሉ አስተያየታቸውን መስጠታቸውን ዘገባው አስፍሯል። ቢቢሲ በዚሁ ዘገባው ቫይረስ ወረርሽኝ መከሰቱን ተከትሎ ከተቋረጡ የሊግ ውድድሮች ውስጥ አንዱ የሆነው የጀርመን ቡንደስሊጋ ወደ ውድድር እንዲመለስ መደረጉን ትልቅ ተስፋ ይሰጣል መባሉን የገለጸው ዘገባው፤ የጀርመን ቦንደንስሊጋ በቅርቡ መጀመሩ ስጋትና ቅሬታ ያስነሳ መሆኑንም አያይዞ አመልክቷል። በጀርመን ከሚገኙ ክለቦች አንዱ በሆነው ኮሎኝ ክለብ ተጫዋች የሆኑ ሦስት ተጫዋቾች በኮሮና ተሐዋሲ ተጠቅተዋል። በገለልተኛ ቤተ-ሙከራ ውስጥ ጠቅላላ የቡድኑ አባላት በተደረገላቸው ምርመራ ከሦስቱ በስተቀር ነጻ ተብለዋል። የጀርመን ቡንደስሊጋ የእግር ኳስ ውድድር ለመጀመር ፍቃድ ማግኘቱ አደገኛ ሊሆን እንደሚችል ቅሬታ መነሳቱን ዘግቧል። የጀርመን ቡንደንስሊጋ በቅርቡ በመመለሱ ቅሬታን ከፈጠረባቸው አካላት መካከል የተለያዩ ክለብ ተጫዋቾች መሆናቸው አያይዞ አንስቷል። ተጫዋቾቹ «ውድድሩ የሚጀምርበት ጊዜ ተፋጠነ» ሲሉ ቅሬታ አቅርበዋል። ዓለም አቀፍ ስጋት ለሆነው የኮሮና ወረርሽኝ ክትባት አልያም መድሃኒት አልተገኘም። የኮሎኝ እግር ኳስ ክለብ ተጫዋቾች በቫይረሱ መጠቃታቸው በታወቀበት ሁኔታ ወደ ውድድር በቅርቡ መመለስ አደጋው ከፍተኛ ይሆናል። ከዚሁ ትይዩ ደግሞ በሀገሪቱ የሰዎች እንቅስቃሴ ሙሉ ለሙሉ ባልተፈቀደበት በዚህ ወቅት የጀርመን እግር ኳስ ሊግ አስተዳዳሪዎች ፍቃድ ማግኘታቸው ግርምትን መፍጠሩን አትቷል።አዲስ ዘመን ሚያዝያ 30/2012 ዳንኤል ዘነበ
https://www.press.et/Ama/?p=31911
624
2ስፖርት
የአትሌቲክስ አሰልጣኞች የፈታኙ ወቅት ተሞክሮ
ስፖርት
May 6, 2020
19
የዓለማችን ኮከብ አትሌቶች በዚህ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ (ኮቪድ 19) በተስፋፋበት ወቅት በምን ሁኔታ ቀናቸውን እያሳለፉ እንደሚገኙ የስፖርቱን ዓለም ሰዎችና ሌላውን ማህበረሰብ ከማስተማር አኳያ በተለያዩ ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን ሰፊ ሽፋን እያገኘ መሆኑ ይስተዋላል፡፡ ከዚህ ጎን ለጎን የአትሌቲክስ የጀርባ አጥንት የሆኑትና አትሌቶችን ላሉበት ደረጃ ትልቅ ሚና የሚጫወቱት አሰልጣኞች ሥራቸውን በምን መልኩ እያከናወኑ እንደሚገኙ ከሥራቸውና ከቫይረሱ ባህሪ አኳያ ብዙዎች ጥያቄ ሲያነሱ ይስተዋላል፡፡ የዓለም አትሌቲክስም በድረ ገጹ በተለያዩ ዓለማት ቻምፒዮኖችን ያፈሩ አሰልጣኞች በዚህ ወቅት ሥራቸውን በምን መልኩ እየከወኑ እንደሚገኙ የተለያዩ ቅኝቶችን በማቅረብ ሌሎች እንዲማሩበት ጥረት እያደረገ ይገኛል፡፡ በዓለም አትሌቲክስ ተሞክሯቸውን እንዲያጋሩ ከተመረጡት አሰልጣኞች መካከል አንዱ ደግሞ የዓለም ሁለተኛው የማራቶን ፈጣን ሰዓት ባለቤቱ ቀነኒሳ በቀለ አሰልጣኝ መርሻ አስራት ናቸው፡፡ አትሌቱ በሦስት ኦሊምፒኮች ተሳትፎው ወርቃማ ታሪክ እንዲጽፍ ከጀርባ በመሆን ከፍተኛውን ድርሻ የተጫወቱት አሰልጣኝ፣ በዚህ የውድድር ዓመት ኮከቡ አትሌት በለንደን ማራቶን የርቀቱን ክብረወሰን እንዲሁም በጃፓኗ ቶኪዮ ለማካሄድ በታሰበው ኦሊምፒክ በማራቶን አራተኛውን ድል ለማስመዝገብ ትልቅ ዝግጅት አድርገው ነበር፡፡ የኦሊምፒኩንና የተጠባቂውን ለንደን ማራቶን መራዘም ተከትሎም ቀነኒሳ ከምንጊዜም ተቀናቃኙና የወቅቱ የማራቶን የዓለም ባለ ክብረወሰን ከሆነው ኬንያዊው ኢሉድ ኪፕቾጌ ጋር በተንቀሳሳሽ ምስል የታገዘ ውይይት ማድረጋቸውን ኤንኤን ትሬኒንግ የተባለው ድረገጽ አስመልክቷል፡፡ በዚህም አትሌቶቹ ከቤተሰቦቻቸው ጋር በቤታቸው በመሆን የግል እንቅስቃሴ እያደረጉ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ አሰልጣኞች ዓለም ውጥረት ውስጥ በገባበት በዚህ ወቅት ሥራቸውን በምን መልኩ ይከውናሉ፣ ቀናቸውንስ እንዴት ያሳልፉታል፣ አትሌቶች ከልምምድ እንዳይርቁና ብቃታቸውን ጠብቀው እንዲቆዩ የአሰልጣኞቹ ሚና በምን መልኩ አትሌቶች ጋር እየደረሰ ይገኛል? ለሚለው የአምስትና አስር ሺ ሜትርን ክብረወሰን ለረጅም ዓመት ሳያስደፍር ይዞ የቆየው አትሌት ቀነኒሳ አሰልጣኝ ተሞክሯቸውን ያጋራሉ፡፡ አሰልጣኝ መርሻ የመጀመሪያው ቁም ነገር ዓለም የገጠማትን ይህንን ወጀብ በምን መልኩ ማለፍ ይቻላል? የሚለውን ማሰብ ቀዳሚ እንደሆነ እምነታቸው ነው፡፡ ወረርሽኙ በውድድሮች ላይ እንዲሁም በቡድን በሚሰጡ ስልጠናዎች ላይ የራሱን አሉታዊ አስተዋፅዖ እንዳሳደረ ይናገራሉ፡፡ ነገር ግን ጊዜውን በጥንካሬ ማሳለፍ የግድ ነው ይላሉ፡፡ ሰልጣኞቻቸውም በዚህ መልክ መቆየት እንዳለባቸው ይጠቁማሉ፡፡ በንግግራቸውም ‹‹ሁሉም አትሌቶቼ ጠንካራና በባህሪያቸውም ለሌሎች ምሳሌ መሆን ይገባቸዋል፤ እንደ አሰልጣኝ የምነግራቸውም ይህ ጊዜ ያልፋል ብዬ ነው›› ብለዋል፡፡ ምንም እንኳን በዚህ ወቅት ሁሉም ውድድሮች ከተያዘላቸው መርሐ ግብር ሽግሽግ እንዲደረግባቸውና ሌሎቹም የተሰረዙ ቢሆንም አትሌቶች ልምምዳቸውን ማቆም እንደማይገባቸው አሰልጣኝ መርሻ ይመክራሉ፡፡ አትሌቶች የሚሠሩት እንቅስቃሴም ለጥንካሬ እና አቅምን ለማዳበር የሚረዱ መሆን እንዳለበት ገልጸዋል፡፡ ይህንንም ሲያብራሩ ‹‹ለተወሰኑ ጊዜያት ውድድሮች ስለሌሉ ጠንክሮ መሥራት ተገቢ የሆነበት ወቅት ነው፡፡ በመሆኑም በእኔ ስር ለሚሰለጥኑ ሁሉም አትሌቶቼ መሥራት የሚገባቸውን እየጠቆምኳቸው ነው፡፡ ወቅቱ ጥንካሬን የሚያዳብሩበት ነው፤ በደንብ እንዲሠሩም ዕድል ይሰጣቸዋል›› ብለዋል፡፡ ከዓለም አትሌቲክስ ጋር ቆይታ ያደረጉት ሌሎች አሰልጣኞችም በተመሳሳይ ለአትሌቶቻቸው መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡ የማራቶንና ግማሽ ማራቶን የዓለም ክብረወሰን ባለቤቶቹ ኬንያዊን ኢሉድ ኪፕቾጌ እና ጆፈሪ ካምዎረር አሰልጣኝ ፓትሪክ ሳንግም ተሞክሯቸውን አጋርተዋል፡፡ በርካታ አትሌቶች በቡድን የሚያሰለጥኑት አትሌቱ ቡድናቸውን የበተኑት ከወር በፊትም ነበር፡፡ በተለያዩ የማህበራዊ መገናኛ ዘዴዎች ታግዘው አትሌቶቻቸውን ቢያገኙም ለውጣቸውን የመመልከት ዕድል አለማግኘታቸው ፈተና እንደሆነባቸው ጠቁመዋል፡፡ ብራዚላዊው አሰልጣኝ ሞራ ኮት አትሌቶች ቀድሞ በነበራቸው መነቃቃት ማቆየት አዳጋች መሆኑን ይገልጻሉ፡፡ አሰልጣኞችና አትሌቶች መልካም መግባባት ያላቸው ከሆነም በሚያወጧቸው እቅድ መሰረት ባሉበት ሆነው በእንቅስቃሴ ላይ መቆየት ይችላሉ፡፡ ቢሆንም ይህ ጊዜ ሲያልፍ ምን ሊከሰት እንደሚችል ለመገመት አዳጋች መሆኑን አልሸሸጉም፡፡ ‹‹አዲስ ልምድ እንደምናገኝና ይህ ሁኔታ ለበጎ እንደሚሆንም ተስፋ አለኝ›› ይላሉ፡፡ የኒውዝላንድን አትሌቶች ሲያዘጋጁ የቆዩት አሰልጣኝ ዳሌ ስቴቨንሰን በበኩላቸው አትሌቶቻቸውን በስነልቦና እያገዙ እንደሚገኙና በቅርቡ ወደነበሩበት እንደሚመለሱ እየነገሯቸው መሆንኑን ገልጸዋል፡፡ ወቅቱ ወደኋላ የሚመለሱበት ሳይሆን በጥሩ ሞራል እንደ ሙሉ ጊዜ አትሌት ጊዜያቸውን መጠቀም እንዳለባቸውም ምክረሃሳብ ሰጥተዋል፡፡ አሰልጣኞችም አትሌቶቻቸው በምን መልኩ እንቅስቃሴ ማድረግ እንዳለባቸው ማሳየት ተገቢ ነው የሚሉት አሰልጣኙ፤ በአንዳንድ አትሌቶቻቸው መደነቃቸውንም ይናገራሉ፡፡ አትሌቶች በአካባቢያቸው በሚያገኟቸው ቁሳቁስ ስልጠናቸውን እያደረጉ እንደሚገኙና በዚህም እንዲቀጥሉ አሳስበዋል:: ሌላኛው አሰልጣኝ ብራም ሶም አትሌቶች ከሁኔታዎች ጋር ራሳቸውን በማስማማት በዝግጅት ላይ መቆየት እንዳለባቸውም ጠቁመዋል፡፡ ከአትሌቶች ጋር ፊት ለፊት በመተያየት ብቃታቸውን መገምገም ባይቻልም አዲስ ተሞክሮ እንዳስገኘላቸውም አክለዋል፡፡ አዲስ ዘመን ሚያዝያ 28/2012ብርሃን ፈይሳ
https://www.press.et/Ama/?p=31772
542
2ስፖርት
የሊግ ካምፓኒው የሳተው መስመር
ስፖርት
May 9, 2020
28
የኮሮና ቫይረስ(ኮቪድ 19) ወረርሽኝ እንደሌሎቹ ማህበራዊ፣ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ኩነቶች ሁሉ የዓለምን ስፖርት ውጥንቅጡን አውጥቶታል። ታላላቅ የዓለማችን ሊጎች የሚያዙትን የሚጨብጡትን አጥተዋል። በተለይም ወትሮውንም ችግር የማያጣት አፍሪካ የዚህ ገፈት ቀማሽ መሆኗ ነገሩን በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ እንደሚያደርግባት ቀድሞም የተገመተ ነው። በእንደዚህ አይነት አስቸጋሪ ወቅት በሁሉም ረገድ ነገሮችን በብልሃት የሚያልፍ የበሰለ አመራር ሰጪነት ወሳኝ ነው። ለዚህም ሩቅ ሳንሄድ እዚሁ አፍሪካ ውስጥ የቡርኪናፋሶ እግር ኳስ ተሞክሮን መመልከት አንዱ ማሳያ ነው። ቡርኪናፋሶ እንደሌሎቹ የዓለማችንም ይሁን የአፍሪካ አገራት ሰሞንኛ ማህበራዊ ሁኔታዋ ጤነኛ አልነበረም ። አፍሪካ ውስጥ በከፍተኛ ሁኔታ የኮሮና ቫይረስ ያጠቃቸው ፖለቲከኞች ተመዝግበውባታል። የቡርኪናፋሶ መንግስት ይህ ቫይረስ ተስፋፍቶባቸዋል ብሎ ካወጀባቸው ቦታዎች መካከል የስፖርት ማዘውተሪያ ቦታዎች ይገኙበታል። ጅምናዚየም ፣ የኳስ መጫወቻ ሜዳዎች ለዚህ ተጠቃሽ ከሚባሉት ቦታዎች ውስጥ ይገኛሉ። ስለዚህ ይህንን አደጋ ለመቀነስ እና ለማህበረሰቡ ዋስትና ለመስጠት ሊጉን ሰርዞ የተለያዩ ውሳኔዎችን በዚህ ሳምንት አሳልፏል። የዘንድሮው የውድድር ዓመት እንደማይጠናቀቅ እና በዚሁ ውጤት እንደሚያልቅ፣ ሁሉም ክለቦች በውል ውስጥ የሚገኙ ተጫዋቾቻቸውን ውል እንዲያከብሩላቸው እና እስከውል ማለቂያው ድረስ ደመወዝ እንዲከፍሉ፣ ማንኛውም ክለብ ያለምንም በቂ ምክንያት ምንም አይነት የክለብ አባላት ቅነሳ እንዳያደርግ፣ የትኛውም ተጫዋች ተበደልኩ ቢል ለፌዴሬሽኑ ፅህፈት ቤት እንዲያመለክት፣ ከሁሉም በላይ በዘንድሮ 2019 የውድድር ዘመን በኢንተርናሽናል መድረክ አገሪቱን የወከሉት ቡድኖች ማለትም (ራሂሞ ኤፍ ሲ) እና (ሳሊታስ) የተባለው ክለብ በክለቦች ኮንፌዴሬሽን ጨዋታ በሚመጣው ዓመት አገሪቱን እንዲወክሉ አድርጓል። ይህንን ያደረገውም የዘንድሮ ልፋታቸው ሽልማት እንኳን ቢሆን ብሎ በማሰብ ነው ። አሱማ ሲሪማ የቡርኪናፋሶ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ናቸው። ይህንን ውሳኔ ሲወስኑ ሁሉንም እንደሚያስማማ በማሰብ መሆኑን ተናግረዋል። ቡርኪናፋሶን የወከሏት ቡድኖች የተገኙት አምና ባስመዘገቡት ውጤት ነው ። ይህ አንዳንዴ የተቀመጠን ህግ እና አሰራር ወቅቱ በሚፈቅደው ነገር እንደሚጠመዘዝ ማሳያ ነው ። የኢትዮጵያ ሊግ ካምፓኒ ምንም አይነት ቡድን ኢትዮጵያን በኢንተርናሽናል ውድድር አይወክልም የሚል ውሳኔ ከቀናት በፊት አስተላልፏል። ይህ እንደ አገር በድጋሚ ሊጤን የሚገባው ውሳኔ እንደሆነ በርካቶች አስተያየት ሰጥተውበታል። በኢንተርናሽናል ውድድሮች ኢትዮጵያን ወክለው የሚሳተፉት ቡድኖች ከየትም ወገን ይምጡ የሚወክሉት ሊጉን ነው ። ሊጉ ደግሞ በድግግሞሽ በየዓመቱ ኢትዮጵያን በጥራት የሚወክሉ ቡድኖችን ይፈልጋል። ይህንን ጥራት ለማምጣት ደግሞ የቡድኖችን የኢንተርናሽናል ተሳትፎ መንገድ መቁረጥ ሌላ ፈተና ይዞ እንደሚመጣ ሳይታለም የተፈታ ነው። ይህን መቁረጥ በአንድ ዓመት የኢንተርናሽናል ልምድ በጥሩ ብቃት ላይ የሚገኝ ተጫዋች ራሱን የማሳየት ተስፋ ማጨለሙ አይቀርም። የክለቦችን የአስተዳደራዊ ዝግጅት ደረጃ ከፍ የማድረግ ልምድ ማ ሳነስም ሌላኛው ኪሳራ ነው። ለምሳሌ ሊጉን እየመራ የሚገኘው ፋሲል ከነማ ዘንድሮ ጥሩ የውድድር ዘመን አሳልፏል። ይህ ማለት ቡድኑ ሊጉ እስከተቋረጠበት ጊዜ ራሱን በሚገባ እያዘጋጀ እንደነበር ማሳያ ነው ። ተከታዮቹ መቐለ 70 እንደርታ እና ቅዱስ ጊዮርጊስም ወደ ውድድሩ የገቡት በተጠና እና የዝግጅታቸውን አቅም ፣ ጥልቀት በሚያሳይ ጥራት ነበር። ከእነዚህ ቡድኖች ውስጥ ወደ ኢንተርናሽናል ውድድር ለመቅረብ ቡድኖች ቢመረጡ እና እንዲወከሉ ቢደረግ ለቡድኖቹ ረዥም የሜዳ ተግባር እና የገንዘብ አቅም ቅድመ ዝግጅት ያገኙ ነበር ። የሊግ ኮሚቴው ውሳኔውን ክለቦች ተስማምተውበት እንዳሳለፈ ቢያሳውቅም ራሱን በሚገባ ሳያዘጋጅ የቀረበ እና የሊግ ካምፓኒው ሊጉ በአጠቃላይ ማግኘት የሚገባውን ጥቅም እንዳያገኝ አድርጎታል። ጉዳዮ ቻምፒዮን የመሆን እና ያለመሆን ጥያቄ አይደለም። በኢንተርናሽናል መድረክ ሊጋችንን የመወከል እና ያለመወከል ጥያቄ ነው። በድግግሞሽ ውስጥ መማር የሚገባው ሊግ ሊማርበት የሚገባውን አንዱን ነጥብ እንደሳተ ብዙዎች ይስማማሉ። እግር ኳሱ ላይ አብዛኛውን ጊዜ የሚወሰኑ ውሳኔዎች የሚሰጡት ጥቅም በአገራዊ መነፀር መታየት ይኖርባቸዋል ተብሎ ይታመናል። ለዚህ ደግሞ ክለቦች ጊዜ ወስደው እንዳያስቡና ፣ ጥናት ያለማድረግ ፣ ማንን ላስደስት የሚለውን አመለካከት አውልቆ አለመጣል ዋነኛው ምክንያት እንደሆነ ይታመናል። የቡርኪናፋሶ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አምና በኢንተርናሽናል መድረክ የተወከሉትን ቡድኖች ዘንድሮም ‹‹እነሱ ናቸው የሚወክሉኝ›› ብሎ ሲወስን ክለቦችን ጊዜ ሰጥቶ በሚገባ አናግሯል። ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናትንም በቴሌ ኮንፈረንስ ገንቢ ሐሳብ እንዲሰጡበት አድርጓል። ኘሬዚደንቱ ‹‹እኛ የሚያስጨንቀን የሚመጣው ዓመት የሚሰጠንን ኮታ እንዳናጣው ነው ፣ ምክንያቱም ክለቦቻችን ልምድ እና ተሞክሮ ያስፈልጋቸዋል›› ነበር ያሉት ። ሁለቱ ቡድኖች ዘንድሮ አገሪቱን በኢንተርናሽናል መድረክ ሲወክሉ ፣ ራሂሞ የተባለው ቡድን በቅድመ ማጣሪያ 5ለ1 ተረቶ ነበር ። ከዚህ ሽንፈት በኋላም ሌላ ልምድ እናግኝ ብለው እንደገና ተነጋግረው ፣ ተግባብተው ወካያቸው አድርገውታል። የሊግ ካምፓኒው ውሳኔውን ካሳለፈ በኋላም ቢሆን ስህተቱን አምኗል። ማመን ብቻ ግን በቂ አይደለም። ካለመሳተፍ መሳተፍ ልዩ ዋጋ እንዳለው ተገንዝቦ የተሳሳተውን ውሳኔ የሚያርምበት ቀዳዳ መፈለግ ይኖርበታል።አዲስ ዘመን ግንቦት 1/2012 ቦጋለ አበበ
https://www.press.et/Ama/?p=31988
593
2ስፖርት
ብሔራዊ ፌዴሬሽኑ ለአትሌቲክስ ብሔራዊ ቡድን አባላቱ ቃል የገባውን ገንዘብ ማስረከብ ጀመረ
ስፖርት
May 12, 2020
18
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ለብሔራዊ ቡድን አባላት ቃል የገባውን የአራት ሚሊዮን ብር ድጋፍ ማስረከብ መጀመሩን አስታወቀ። የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ሥራ አመራር ቦርድ በኮሮና ቫይረስ ምክንያት ዓለም አቀፍ ውድድሮች በመሰረዛቸው ምክንያት ጥቅማ ጥቅም ለሚያጡ ብሔራዊ አትሌቶች አራት ሚሊዮን ብር ለመደጎም ከሳምንታት በፊት ውሳኔ መተላለፉን አስታውሷል። የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በወቅቱ በገባው ቃል መሠረት ከሰኞ ግንቦት 3 ቀን 2012 ዓ.ም ማለዳ ጀምሮ ለብሔራዊ አትሌቲክስ ቡድን አባላት ማስረከብ መጀመሩን አስታውቋል። ብሔራዊ ፌዴሬሽኑ የሥራ አመራር ቦርዱ ለ267 ብሔራዊ አትሌቶችና አሠልጣኞች በተናጠል የሚደረጉትን ልምምድና ዝግጅት አጠናክረው መቀጠል ይችሉ ዘንድ፣ ለእያንዳንዳቸው 15 ሺህ ብር የገንዘብ ድጋፍ ለማድረግ ከስምምነት ተደርሶ ነበር። በብሔራዊ ቡድን የሚገኙ አትሌቶቹና አሰልጣኞቹ እያንዳንዳቸው ቃል በተገባላቸው መሠረት 15 ሺህ ብር እንዲሁም ሙሉ የስፖርት ትጥቅ ከነመለማመጃው በተዘጋጀው መርሃ ግብር መሠረት እየተረከቡ ይገኛሉ ብሏል። ብሔራዊ ፌዴሬሽኑ የገንዘብ ድጋፉን ለማድረግ ውሳኔ ባስተላለፈበት ወቅት እንደተናገረው ከውሳኔ፤ በዓለም አቀፍና አኅጉር አቀፍ ደረጃ የአትሌቲክስ ውድድሮችና በቡድን የሚካሄዱ ልምምዶች በኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት እንዲቋረጡ ተደርጓል፡፡ በተለይም በብሔራዊ ቡድን ደረጃ በተለያዩ የውድድር ዓይነቶች ማለትም የሜዳ ተግባራትን ጨምሮ ከአጭር ርቀት እስከ ማራቶን 211 አትሌቶችንና 56 ብሔራዊ አሠልጣኞች በድምሩ 267 የአትሌቲክስ ቤተሰቦች ሥነ ልቦናቸው ተጠብቆ ልምምዳቸውን እንዲቀጥሉ ማድረግ አስፈላጊ እንደሆነ ፌዴሬሽኑ አምኖበታል፡፡ ሌላው የውጭ የአትሌቲክስ ውድድሮች በመቋረጣቸው በተለይ የአጭር ርቀትና የሜዳ ተግባራት አትሌቶችና አሠልጣኞቻቸው ያገኟቸው የነበሩ ጥቅማ ጥቅሞች በማነሳቸውና በመቀነሳቸው ተቋሙ ከጎናቸው መሆኑን እንዲያረጋግጡ የሞራል ስንቅ ከመሆኑ ባሻገር፣ ለቀጣዩ ኦሊምፒክ ከወዲሁ ተገቢውን ዝግጅትና ተያያዥ ሥራዎችን እንዲያከናውኑ ያለመ ስለመሆኑ ጭምር ነው፡፡ በዚሁ መሠረት ለቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ ለቅድመ ማጣሪያው ከ800 ሜትር እስከ ማራቶን ባሉት ርቀቶች ለተመረጡ 91 ብሔራዊ አትሌቶች እንዲሁም ለኦሊምፒክ ዝግጅት አትሌቶችን ላስመረጡ 27 አሠልጣኞች፣ ለ63 የአጭር ርቀትና የሜዳ ተግባራት አትሌቶችና ለ16 አሠልጣኞች፣ ለ57 ተተኪና ወጣት አትሌቶች እንዲሁም ለ13 ተተኪ ወጣት አትሌቶች አሠልጣኞች በገንዘብ ድጋፉ የተካተቱ ሲሆን ብሔራዊ ፌዴሬሽኑ ባወጣው መርሃ ግብር መሠረት ድጋፍ ለማድረግ ቃል የተገባውን ገንዘብና ትጥቅ የሚረከቡ ይሆናል ተብሏል። የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ሥራ አመራር ቦርድ በኮሮና ቫይረስ ምክንያት ዓለም አቀፍ ውድድሮች መቋረጣቸውን ተከትሎ ለአትሌቶች እያደረገው እንዳለው ድጋፍ ሁሉ ፤ የዓለም አትሌቲክስና ዓለም አቀፍ አትሌቲክስ ፋውንዴንሽን በወረርሽኝ ለተጎዱ አትሌቶች የ5 መቶ ሺህ ዶላር ድጋፍ ሊያደርግ መሆኑን ከሳምንት በፊት ማሳወቁ ይታወሳል። የዓለም አትሌቲከስ ፕሬዚዳንት ሰባስቲያን ኮ እንደተናገሩት ድጋፉን የሚያገኙት በወረርሽኙ ምክንያት ባለፉት ወራት ውድድሮች ባለማድረጋቸው ገቢ ያጡ ፕሮፌሽናል አትሌቶች ነው። ድርጅቱ ድጋፉን የሚያደርገው እኤአ በ2020 እና በ2021 በጀቱ በመቀነስ መሆኑ ነበር ያሳወቀው። አዲስ ዘመን ግንቦት 4/2012 ዳንኤል ዘነበ
https://www.press.et/Ama/?p=32181
352
2ስፖርት
ዶፒንግ ቅሌት በምን ይዳኝ?
ስፖርት
May 11, 2020
15
ጀግናው አትሌት ሃይሌ ገብረስላሴ እኤአ በ2016 መባቻ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ሆኖ መመረጡን ተከትሎ አበረታች መድሃኒት ተጠቅመው የተገኙ አትሌቶች በስፖርት ህግ ሳይሆን በወንጀል መቅጫ ህግ እንዲጠየቁና ለእስር እንዲዳረጉ መበረታታት እንዳለበት ሲሞግት ነበር። የኢትዮጵያ መንግስትም በዚህ ወንጀል የተሳተፉ አትሌቶች በወንጀል መቅጫ ህግ እንዲጠየቁና ለእስር እስከሚዳርግ ቅጣት እንዲጣልባቸው ማድረጉን ተከትሎ በዓለም ዙሪያ ብዙ ክርክሮች ተነስተው እንደነበር አይዘነጋም። ይህ አከራካሪ ጉዳይ አሁንም መቋጫ አላገኘም። በተለይም ሃይሌ ከቀናት በፊት ከዓለም አቀፉ የስፖርት ጋዜጠኞች ማህበር ወጣት ሪፖርተሮች ጋር በነበረው የልምድ ልውውጥ በዚህ አቋሙ እንደፀና መግለፁን ተከትሎ በጉዳዩ ላይ የሚነሱ ክርክሮች በርትተው ታይተዋል። በተለያዩ መገናኛ ብዙሃንም ሰፊ ሽፋን እየተሰጠው ይገኛል። በእርግጥ የስፖርቱን ቤተሰብ ለሁለት የከፈለው ‹አበረታች መድሃኒት የተጠቀሙ አትሌቶች በስፖርት ወይንም በወንጀለኛ መቅጫ ህግ ይዳኙ?› የሚለው ሃሳብ አከራካሪ መሆኑ የግድ ነው። የዓለም አቀፉ ፀረ አበረታች መድሃኒቶች ኤጀንሲ(ዋዳ) አበረታች ንጥረ ነገሮችን በሚጠቀሙ አትሌቶች ላይ ምንም አይነት ምህረት እንደሌለውና እንደማይታገስ ቢታወቅም አትሌቶች በወንጀል መቅጫ ህግ እንዲጠየቁና ለእስር እንዲዳረጉ አይደግፍም። ይሁን እንጂ ኤጀንሲው በራሱ ህግ መሰረት አበረታች መድሃኒት ተጠቅመው የተገኙ አትሌቶችን በቅድሚያ ለአራት ዓመት ከየትኛውም ውድድር በማገድ ያገኙትን ክብር ሁሉ ይነጥቃል። ለሁለተኛ ጊዜ ጥፋተኛ ሆኖ የተገኘ አትሌትም ለስምንት ዓመታት ተመሳሳይ ቅጣት ይጣልበታል። ከዚህ ካለፈም ለእድሜ ልክ ከስፖርቱ ይታገዳል። ይህም በቂ ቅጣት ነው ብሎ ያምናል። ሃይሌ ግን ይህ ቅጣት ብቻውን በቂ እንዳልሆነ ያምናል። አበረታች መድሃኒት ተጠቅመው የተገኙ አትሌቶች በስፖርቱ ህግ ብቻ ሳይሆን በወንጀል መቅጫ ሕግ እስከ እስር የሚደርስ ቅጣት ሊጣልባቸው እንደሚገባ ይሞግታል። ለዚህም የተለያዩ ሞጋች ምክንያቶችን ይደረድራል። ‹‹አበረታች መድሃኒት መጠቀም ውድድሮችን ለማሸነፍ ብቻ በማሰብ የተፈፀሙ ተደርጎ መታሰብ የለበትም፣ ሰዎች ቀለል አድርገው ይመለከቱታል›› የሚለው ሃይሌ ወንጀሉ ከስፖርታዊ ኩነትም የበለጠ ትርጉም እንዳለው ያምናል። እንደ ሃይሌ እምነት አንድ አትሌት በአንድ ውድድር ሲያሸንፍ ሁለት ወይም ሦስት መቶ ሺ ዶላር ሽልማት ያገኛል። ይህን ሽልማት በማሰብ አበረታች መድሃኒትም ይጠቀማል፣ ከዚያም ተይዞ ለአራት ዓመት ከውድድር ይታገዳል። አትሌቱ ሽልማቱን እስካገኘ ድረስ ከውድድር መታገዱ ምንም ላይመስለው ይችላል፣ እገዳውን ሲጨርስ ዳግም ተመሳሳይ ጥፋት ይፈፅማል። በሌላው ህብረተሰብ ዘንድም ወንጀል እንደሰራ ላይታሰብ ይችላል። ይሁን እንጂ ይህን ድርጊት የፈፀም አትሌት በወንጀል ቢጠየቅና ለእስር ቢዳረግ በሌላው ማህበረሰብ ዘንድም እንደ‹ሌባ› ሊቆጠርና ሊወገዝ ይችላል። ዳግምም በዚህ ድርጊት ተሳታፊ እንዳይሆን በእርስ ቅጣቱ ሊማር ይችላል። የሃይሌን ሃሳብ ከሚቃወሙት የስፖርቱ ቤተሰቦች መካከል የዓለም አቀፉ ፀረ አበረታች መድሃኒት ኤጀንሲ(ዋዳ) የቀድሞ ፕሬዚዳንት ሰር ክሬግ ሬዲ አንዱ ናቸው። አበረታች መድሃኒት እንደ አጋጣሚ ተጠቅመው ለሚገኙ አትሌቶች ስፖርታዊ ቅጣቶቹ በቂ መሆናቸውን ያምናሉ። በእርግጥ ሰር ክሬግ አገራት በአትሌቶች ላይ ሳይሆን አበረታች መድሃኒቶችን በማምረት፣ በማሰራጨትና አትሌቶች እንዲጠቀሙ በማድረግ ተሳታፊ የሆኑ ማንኛቸውም ግለሰቦችና ተቋማት በወንጀል ህግ እንዲጠየቁ ዋዳ እንደሚያበረታታም አልዘነጉም። ሃይሌ የአበረታች መድሃኒት ተጠቃሚነት ጉዳይ የኢትዮጵያን አትሌቲክስና የአገሪቱን ባህል ከመጣስ አኳያ ትልቅ ክብደት የሚሰጠው ጉዳይ እንደሆነ ይናገራል። ኢትዮጵያ የምትወስደውን እርምጃ ሌሎች አገራት የግድ ይተግብሩት የሚል አቋም ግን የለውም። በዓለም አቀፍ ደረጃ ያለው ቅጣትም መጥፎ ነው ብሎ አያምንም። እያንዳንዱ አገርም በራሱ መንገድ ነገሮችን እንደሚመለከት ይናገራል። ሰር ክሬግ በበኩላቸው እያንዳንዱ አገር የየራሱ የወንጀል መቅጫ ህግ ያለው እንደመሆኑ መጠን ተመሳሳይ ጥፋት ያጠፉ አትሌቶች በየአገራቱ የወንጀል መቅጫ ህግ ይዳኙ ከተባለ ሚዛናዊነት ገደል ይገባል። ይህ ማለት እንደየ አገራቱ የወንጀል መቅጫ ህግ ልዩነት ኢትዮጵያ ውስጥ ወንጀሉን የፈፀመ አትሌት ሌሎች አገራት ላይ ተመሳሳይ ወንጀል ከፈፀመ አትሌቱ እኩል ቅጣት ሊገጥመውም ላይገጥመውም ይችላል።አዲስ ዘመን ግንቦት 3/2012
https://www.press.et/Ama/?p=32125
470
2ስፖርት
መምህርነት በህፃንነት
መዝናኛ
October 1, 2019
44
የሰው ልጅ የፊት ገፅታ እንደ እድሜውና እንደ ኑሮው ደረጃ ብሎም እንደጤናው ሁኔታ ይለያያል። ሰው ኑሮውን ይመስላል እንዲሉ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ያሉ ሰዎች በአብዛኛው ጎስቆል ያለ የፊት ገፅታን ሲላበሱ በጥሩ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ ሰዎች ደግሞ ከዚህ በተቃራኒ በፊታቸው ላይ ምቾት ይነበባል። የሰው ልጅ መልኩ ሆዱ ውስጥ ነው የሚባለውም ለዚሁ አይደል። የሰዎች የፊት ገፅታም ቢሆን እንደየእደሜ ደረጃቸው የሚታይ ቢሆንም አልፎ አልፎ ግን ከጤና ችግርና ከተፈጥሮ ጋር በተያያዘ አንዳንድ ሰዎች በአፍላ የወጣትነት እድሜያቸው ላይ ሆነው የሽምግልና ገፅታ፤ በሽምግልና እድሜ ላይ ሆነው ደግሞ የወጣትነት የፊት ገፅታን ይላበሳሉ። በየሃያ ሁለት ዓመቱ ፊሊፒንሳዊ ወጣት ላይ የታየውም እውነት ይሄው ነው ሲል ኦዲቲ ሴንትራል ከሰሞኑ ዘግቧል።እንደዘገባው ከሆነ በፊሊፒንስ ቡልካን ፕሮቪንስ በሳን ሆዜ ዴል ሞንቴ መዋእለ ህፃናት መምህር የሆነው ኢያን ፍራንሲስ እድሜው 22 ዓመት ቢሆንም ፣ልክ እንደ እድሜ አቻዎቹ የጉርምስናን የፊት ገፅታ ሊላበስ አልቻለም። አቻዎቹ በአገጫቸውና ባላይኛው ከንፈራቸው ላይ ፂም ሲያበቅሉ እርሱ ግን ለዚህ አልታደለም። ከዚህ ይልቅ በመካከለኛ የክፍል ደረጃ እንዳሉ የታዳጊዎች የፊት ገፅታን ሊይዝ ችሏል። ወጣቱ በጉርምስና እድሜው የልጅ ፊት ገፅታ ቢላበስም ከእድሜ እኩዮቹ ሆነ ከሚያስተምራቸው ህፃናት ደግሞ ሽርደዳ አልገጠመውም። ምን አልባት ከጤና ጋር የተያያዘ ችግር ይሆናል በሚልም የሃኪም ቤት ደጅንም አልረገጠም። ስታንዳርድ ትሩዝ የተሰኘው የሃገሪቱ ሚዲያ እንደዘገበው ከሆነ ፤እድገቱ ሊዘገይና የልጅ ፊት ገፅታን ሊላበስ የቻለው ምን አልባት በህፃንነቱ በተደጋጋሚ በህመም ሲጠቃ ስለነበር እንደሆነ ኢያን አምኗል ብሏል። የመዋለ ህፃናት የመመህርነት መግቢያ ፈተናውንም ያለፈው ከገጠመው የጤና ችግር ጋር ተጋፍጦ እንደሆነ ገልጸዋል። በአሁኑ ወቅትም በመዋእለ ህጻናት ትምህርት ቤቱ የሁለተኛ ክፍል ተማሪዎችን የሚያስተምር ሲሆን ትምህርት ቤቱም ለክፍል ደረጃው የሚመጥን መሆኑና በተማሪዎች ዘንድም የሚወደድ መሆኑን አረጋግጧል። ኢያን ማግና በበኩሉ ብዙዎቹ የእርሱ ተማሪዎች እርሱን እንደ ታላቅ ወንድማቸው የሚቆጥሩት እንደሆነ ተናግሯል። ይሁንና የህፃንነት ገፅታን የሚያሳየው ፊቱን ለማስረሳትና ራሱን ልክ እንደ መምህር ለመቁጠር ብዙ ጥረቶችን ማድረጉን ይገልፃል። በትክክለኛው የእድሜ ደረጃ ላይ የሚገኝ ወጣት ለመምሰልም ሰፋፊ የትልቅ ሰው ልብሶችንና ሹል የቆዳ ጫማዎችን እንደሚያደርግም ተናግሯል። ‹‹ምንም እንኳን የህጻን ፊት ቢኖረኝም እንደ መመህር አርያ ሆኜ መገኘት ይኖርብኛል›› ሲል ኢያን ለዚሁ ሚዲያ ገልጧል። ‹‹ሳስተምር ኮስተር እላለሁ በዚህ ጊዜ ተማሪዎች ኮስታራ መሆኔን ይረዳሉ›› ሲልም ጨምሮ ተናግሯል። ኢያን ካለው የህፃን ፊት ገፅታ በተጨማሪ ድምፁም የህፃን ልጅ ይመስላል። ቁመቱም 1፡62 ብቻ የሚረዝም ነው። እርሱ እንደሚለው የትምህርት ቤት ጓደኞቹ በእርሱ ላይ የሚቀልዱ ባይሆንም የእርሱ የህፃንነት ቁመና ግን አንዳንድ ጊዜ ከጫካኝ ቀልደኞች ኢላማ ሊያስመልጠው አልቻለም። አዲስ ዘመን መስከረም 20/2012አስናቀ ፀጋዬ
https://www.press.et/Ama/?p=19810
348
1መዝናኛ
የእግር ኳሱ ዓለም ‹‹ፍቅር እስከ መቃብር››
ስፖርት
May 10, 2020
40
የፍቅር ጉዳይ ሲነሳ በዓለማችን የተለያዩ ጥንዶች በተለያዩ ዘመናት የነበራቸው የሚያስቀና ፍቅር በብዙ ታሪኮች ሲጠቀስ ይታያል፡፡ በአገራችንም ተሰምተው የማይጠገቡ፣ ለበርካቶች ትምህርት የሆኑ ዘመን ተሻጋሪ የፍቅር ታሪኮች አሉ፡፡ ብዙ ጊዜ የልብ ወለድ እንጂ በገሃዱ ዓለም ያሉ ወይም ተከስተው የነበሩ የማይመስሉ የተለያዩ የፍቅር ታሪኮችን ቢያንስ አንድ የሚያውቅ አለ ተብሎ አይታሰብም፡፡ ዘመን አይሽሬው የአገራችን ልብ ወለድ ‹‹ፍቅር እስከ መቃብር›› የሁለት ጥንዶችን የፍቅር ጥግ በማሳየት በብዙዎች ዘንድ የሚረሳ አይደለም፡፡ ከዚያም የተነሳ በውጣ ውረድ የተሞላ፣ ፈተናዎች የበዙበት የፍቅር ሕይወትና ፅናት ‹‹ፍቅር እስከ መቃብር›› የሚል ስያሜ ሲቸረው ማየት የተለመደ ነው፡፡ በስፖርቱ ዓለምም በተለይም በእግር ኳሱ አንድ የፍቅር ታሪክ በርካቶችን ሲያነጋግር ኖሯል፣ እያነጋገረም ይኖራል፡፡ የዚህ ፅኑ ፍቅር ታሪክም በዛሬው የስፖርት ማህደር አምዳችን እንዲህ ይነበባል፡፡ የዚህ ፍቅር ታሪክ መሪ ተዋናይ ቤርናዴት አዳምስ ትባላለች፡፡ ቤርናዴት ዘወትር ማልዳ ትነሳለች። አንድ ሰዓት እንኳን ሳይሞላ ቀኗ ይጀመራል። ቁርሷን ትበላለች፣ ባለቤቷን ለመንከባከብ ራሷን ታዘጋጃለች። ልብስ ትቀይርለታለች። ምግብ ታበስልለታለች። ወደ መፀዳጃ ቤት ትወስደዋለች። ቆሻሻውን ሁሉ ታፀዳለታለች። ጡንቻውን ታፍታታለታለች። ይህ የአንድ ቀን ብቻ ልማዷ አይደለም። ላለፉት ሰላሳ ስምንት ዓመታት አድርጋዋለች። በየዕለቱ ደጋግማዋለች። እስከ መጨረሻው ላታቋርጥም ለራሷ ቃል ገብታለች… ዘመኑ በ1960ዎቹ ፈረንሳይ በጄኔራል ሻርል ደጎል አመራር ሥር ሳለች፣ የመንግሥት ወግ አጥባቂ አስተዳደር እያደር የህዝብ ቅሬታ ሲያስነሳ ነበር። ጥቁሮች ከነጭ ፈረንሳዊያን ጋር በጋብቻ ከተጣመሩ ጉድ የሚባልበት ያ የዘረኝነት ዘመን…። ጥቁሩ ዣን ፒዬር አዳምስ ግን ከነጯ ቤርናዴት ጋር በፍቅር ወደቀ። ወደደችው፣ ወደዳት። አገር ጉድ ይበል ብለው ፍቅራቸውን እስከ ጋብቻ አደረሱት። ገና አማተር ተጫዋች ሳለ ነበር የተዋወቁት። በ1969 አዲስ ዘመን እሁድ ግንቦት 2 ቀን 2012 ዓ.ም ከጋብቻ በኋላ፣ ከፍተኛ ዲቪዚዮን የነበረው ኒም ፕሮፌሽናል ኮንትራት አቀረበለት። ተቀበለው። ዣን-ፒየር እና ቤርናዴት ኑሯቸውን ወደ ኒም ከተማ አዛወሩ። በፍቅር ሲኖሩም ወንድ ልጅ ወለዱ። 1970ዎቹ ለጥንዶቹ አስደሳች ዘመናት ነበሩ። አዳምስ ከፈረንሳይ ብሔራዊ ቡድን የመጀመሪያ ጥቁር ተጫዋቾች መካከል አንዱ ነው። ዝና፣ ገንዘብ፣ መሽቀርቀር፣ መደሰት የአዳምስ የዕለት ተዕለት ልማድ ነበር። ቀልድ ያውቃል። ፈገግታ ከፊቱ አይጠፋም። ዝና ሲጨመርበት ደግሞ… አለ አይደል… አብሮ የሚስቅም አይጠፋም። ገና የ10 ዓመት ብላቴና ሳለ አያቱ በመንፈሳዊ ጉዞ ሰበብ ይዘውት ከመጡ በኋላ የሴኔጋሉ ልጅ ፈረንሳይን ቤቴ ብሏል። ፓሪ ሰን ዠርመ እና ኒስን ጨምሮ እስከ 1981 ድረስ በዲቪዚዮኑ ለእውቅ ክለቦች ተጫወተ። 34 ዓመቱ ላይ ጫማውን ሰቅሎ፣ ለቀሪው ህይወቱ ህፃናትን ለማሰልጠን ለትምህርትና ልምምድ ወደ ዲዦ ከተማ አቀና። እዚያም በልምምድ ላይ ሳለ በጉልበቱ ላይ ጉዳት ደረሰበት። የሊጋሜንቱን ህመም ለመገላገል በሊዮን ከተማ በሚገኘው ኤድዋርድ ሄሪዮ ሆስፒታል ምርመራ አደረገ። ጉዳቱ ቀዶ ህክምና እንደሚያስፈልገው በማረጋገጡ ለቀዶ ጥገናው ቀን ተቀጠረ። የቀን ጎዶሎ፣ እ.ኤ.አ መጋቢት 17 ቀን 1982። አዳምስ ቀጠሮውን ጠብቆ ቢመጣም በአገሪቱ የጤና ባለሙያዎች የሥራ ማቆም አድማ አድርገዋል። ህሙማን ብዙ ቢሆኑም ሐኪሞች ጥቂት ነበሩ። የአዳምስ ቀዶ ጥገና አስቸኳይ ባለመሆኑ እንደገና ሊቀጠር ይችል ነበር። ሆኖም ባሉት ባለሙያዎች ጉልበቱ ሊከፈትና ሊጠገን ተወሰነ። አንድ የማደንዘዣ ባለሙያ ብቻ ሥራ ላይ ነበረች። ተለማማጅ ተማሪዎችም አሉ። ህሙማን እንደ ቦኖ ውሃ በየተራ ማደንዘዣ ተሰጣቸው። አዳምስ ተራው ደርሶ አሸለበ። ግን እንደተጠበቀው አልሆነም። ጉልበት ላድን ያለው ህክምና እጅና እግሩን ጨምሮ መላው አካላቱን ከጥቅም ውጭ አደረጋቸው። ከዓይኖቹ ሽፋሽፍት በስተቀር ቢጠሩት እንኳን ፊቱን ዞር ማድረግ ተሳነው። አንደበቱ ተዘጋ፣ በድጋሚ መናገር አልቻለም። የማደንዘዣው ሂደት የህክምና ስህተት ነበረው። ተለማማጆቹ ወደ ሰውነቱ ያስገቧቸው ትቦዎች እንኳን በቅጡ አልተሰኩም። ወደ ሳንባው የተላከው ትቦ የአሰካክ ስህተት ስለነበረው ሳምባዎቹ በቂ ኦክስጅን ባለማግኘታቸው የልቡ ሥራ ተስተጓጎለ። አንጎሉ በቂ ኦክስጂን ባለማግኘቱ ለአደጋ ተጋለጠ። ያ ፈርጣማ ተከላካይ ሰውነቱ ከዳው። መላወስ አቃተው። በዚያች እርጉም ቀን ያለ ድጋፍ ወደ ሆስፒታል ቢገባም፣ በራሱ አቅም ወደ ቤቱ መመለስ አልቻለም። ቤርናዴት ለአምስት ቀን በሆስፒታል እየዋለች፣ እያደረች ጠበቀችው። ፍቅሯ፣ የልጇ አባት፣ የህይወቷ ጓድ ከተኛበት ሳይነሳ ቀረ። ከእንግዲህ በሰው ድጋፍ እንጂ በራሱ አቅም መንቀሳቀስ እንደማይችል ቁርጡን ነገሯት። የህክምና ኃላፊዎች ለአረጋዊያን መንከባከቢያ ማዕከል እንድትሰጠው መከሯት። ለቤርናዴት ይህ የሰነፎች ምክር ነበር። አልተቀ በ ቻቸውም። <<ወደ ቤታችን እወስደ ዋለሁ፣ እዚያም እስከመጨረሻው እንከባከበዋለሁ>> ብላ ወሰነች። በደግ ዘመን ፍቅርን ወዳዩበት ቤታቸው አመጣችው። 2018…፣ ዣን ፒየር አሁንም በህይወት አለ። ዕድሜው ሰባዎቹን አልፏል፡፡ ቤርናዴትም አልሰለቸችም። ዕድሜ ተጭኗት ቆዳዋ ተሽብሽቧል። የዚያ ዘመን ውበቷ ረግፏል። እርጅና ቤት እየሰራባት ነው። ግን እጅ አልሰጠችም። ባሏን መንከባከብ የዕለት ተዕለት ሥራዋ ከሆነ 38ኛ ዓመቷን ልትደፍን ተቃርባለች። ዘመናት ቢያልፉም ታማኟ ሴት ግን ሰው ሥራሽ ስህተት አልጋ ላይ የጣለውን ሸበላ አይኗ እያየ ልትጥለው አልፈቀደችም። የመጀመሪያ ፕሮፌሽናል ክለቡ ከሚገኝበት ኒም ከተማ አቅራቢያ ዣን ፒየር አዳምስ አሁንም ተኝቷል። ዛሬም ቤርናዴት ከጎኑ አለች። ከአደጋው በኋላ በእያንዳንዷ ቀን እንዳደረገችው ሁሉ ዛሬም ማልዳ ትነሳለች። ታጥበዋለች፣ ታለብሰዋለች፣ ትመግበዋለች፣ ከመተኛት ብዛት ጎኑ እንዳይላላጥ ታገላብጠዋለች። አልታከተችም፣ አልሰለቸችም። መልስ ባይሰጣትም ታወራዋለች፣ እ.ኤ.አ በ1969ና 1976 የወለዷቸው ልጆች ላውረንትና ፍሬድሪክ እንደወለዱና ሃያት እንደሆነም አብስራዋለች፡፡ አንድ ቀንም ይነቃል የሚል ተስፋዋ አብሯት አለ፡፡አዲስ ዘመን ግንቦት 2/2012ቦጋለ አበበ
https://www.press.et/Ama/?p=32041
670
2ስፖርት
ዩኒቨርሲቲዎቻችን እንደስማቸው
መዝናኛ
October 6, 2019
39
ውብ ጸጉር ያለው ታዳጊ ነው። ለጸጉሩ ያለው ፍቅር ከሴቶችም በላይ ነው። በእንክብካቤ ይይዘዋል። ቢነካካው፣ ቢታጠበው፣ ቢያበጥረው፣ ቢዳስሰው አይጠግብም ።በክረምት ደግሞ አሳድጎ እሱ የሚጨምርበት ንቅናቄ እንዳለ ሆኖ ነፋስ ሽው ሲያደርገው እንደደረሰ የጤፍ ቡቃያ ይዘናፈላል። ሀርነቱ፣ ዞማነቱ ብቻ እንደ እኔ ጸጉር የሚወድን ሰው ብቻ ሳይሆን ጸጉር ለሴት እንጂ እስከሚለው ሰው ድረስ አይን ይስባል። ያማልላል። ይሄ የምላችሁ ልጅ ጸጉር ታዲያ መስከረም ሲጠባ ያው እንደተለመደው የትምህርት ቤት ህግ አለና ይቆረጣል። ባይወድም ግድ ነውና መቼ ይሆን ዩኒቨርሲቲ ገብቼ እንደፍላጎቴ የማደርገው ብሎ እየተነጫነጨም ቢሆን ብቻ የትምህርት ቤቱ ህግ ነው ይታጨዳል ።ለአስር ወራት የትምህርት ጊዜውን ተስተካክሎ ወጣት ወንድ ተማሪ የሚያስመስለውን ጸጉሩን ታጥቦ ከመውጣት በስተቀር ሌላ ምርጫ የለውም ። እንዳው ይሄንን ስል መመስገን የሚገባቸውን የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን ላመስግን። ሁሉም ባይሆኑም ብዙዎች የግል ትምህርት ቤቶች የተማሪዎቻቸውን ጸጉር ፣ ዩኒፎርም እና የሚያደርጉትን ጫማ ጭምር ከስርዓት የወጣ እንዳይሆን ይቆጣጠራሉ።ወንዶቹ ሱሪያቸውን በስርዓት እንዲታጠቁ ያስገድዳሉ።እንዳውም አንድ የትምህርት ቤት ባለቤት በትምህርት ዘመኑ መጀመሪያ ቀን ተማሪዎችን አሰልፎ “እያንዳንዳችሁ ወንዶች ቀበቶ መታጠቅ አለባችሁ ። ሱሪዬን ዝቅ አደርጋለሁ ብትሉ አትገቡም። ወላጆቼ ቀበቶ አልገዙልኝም፣ የለኝም የምትሉ ካላችሁ ሱሪያችሁን በቃጫ ድብን አድርጋችሁ ታስራላችሁ” እንዳላቸው የነገሩኝን አልረሳውም። በእነሱ አባባል ሙድ ቢጤ ቢይዙበትም ለእኔ ግን ትልቅ መልዕክት ትቷል። እንዲህ አይነት ልጆችን ከልጅነታቸው ጀምሮ ስነስርዓት ይዘው እንዲያድጉ የሚያደርጉትን ታዲያ ማመስገን አለብን በሚለው ሁሉም ይስማማል ብዬ አስባለሁ። ነገር ግን ሱሪያቸውን እንደ እጀጠባብ አጣብቀው ከወገባቸው ዝቅ አድርገው ጸጉራቸውን አንጨባረው፣ አንጨፋረውና ቆጣጥረው ወደ ትምህርት ቤት የሚሄዱትን ደግሞ ዝም ብለው የሚቀበሉ ትምህርት ቤቶች እና መምህራን መኖራቸው አይዘንጋ። በቀለም አባትነት የሚቀርፁትን ተማሪ በምንቸገረኝነት የሚመለከቱ ታዲያ መምህራን ናቸው ብሎ መናገር መዳፈር አይሆን ይሆን? እንደ እኔ መምህራን ናቸው ። ተማሪ እየቀረፁ ነው ማለቱ ከበድ አለኝ። ታዲያ ይሄ የስነምግባር ችግር የሚታየው በግል ትምህርት ቤቶች ላይ ብቻ እንዳይመስላችሁ። ምንቸገረኝነቱ በመንግስት ትምህርት ቤቶችም ጎልህ ነው። በነገራችን ላይ የትምህርት ቤት ስነምግባር ተጓደለ ስል ይሄ በተማሪው ብቻ እንዳልሆነ ይያዝልኝ።”ስርዓት አልበኛ” ከምንላቸው ተማሪዎች ባልተናነሰም ስርዓት አልበኛ መምህራንም ብዙ ናቸውና። ተማሪ ከትምህርት እንጂ ከእኔ ስነምግባር ምንአለው እስከሚሉት ድረስ ማለቴ ነው። ከሚያስተምሩት ተማሪ ጋር በጫት ቤት፣ በመጠጥ ቤት የሚጎዳኙ መምህራን መኖራቸው አይዘንጋ። አሁንም እላለሁ ሁሉም መምህራን አይደሉም። በሙያቸው በምግባራቸው አንቱ የተሰኙ፣ የእውነቱ የቀለም አባቶች አሉን። የማንረሳቸው ክፉ አይንካችሁ የምንላቸው፣ ከወላጅ አባት የማይለዩ ብዙ ምስጉን መምህራን አሉን። መቼም የማይረሱ ውለታቸውን እንዴት ልመልስ የሚያሰኙትን መምህራን ኢትዮጵያ አፍርታለችና። አሁንም መምህርነትን እያከበሩና እያስከበሩ ያሉት እነሱ ናቸው። አሁንም እላለሁ እናንተም በራሳችሁ ለራሳችሁ ብቻም ሳይሆን ሌላውንም ከመስመር ወጣ የሚለውን መምህር ጭምር ሃይ በሉ። አበው በአንድ እጅ አይጨበጨብም እንዲሉ በጥቂት ብቁና ሙሉ መምህራን ብቻ ብልሹ መምህራንንና ተማሪን ማረቅ ከበድ ይላል።እዚህ ላይ መምህራኖች ተዳፍሬና ቀዩን መስመር አልፌ ከሆነ ሁሌም ስሳሳትና ሳጠፋ እንደምለው ይቅርታ ይደረግልኝ። ይሁንና ያየሁትን አይቼና የሰማሁትን ሰምቼ እንጂ ልቦለድ እያወራሁ እንዳልሆነ ግን እናንተንም ምስክሮቼ ብዬ እቆጥራለሁ። አነጋጋሪው የስነምግባር ጉዳይ ከተማሪ ወደ መምህራን ሙልጭ አድርጎ ወሰደኝ አይደል፣ ልመለስ ስለተነሳሁበት ወጣት ሀሳብ ።ይሄ ጸጉራማ ወጣት ታዲያ ዘንድሮ ወደ ዩኒቨርሲቲ ሊገባ ነውና ጸጉሩን እንደ ጉድ አሳድጓል።ዘንድሮ ክረምቱም ያማረ እንደነበረው ዝናብ የጠገበ ለምለም ቡቃያ መስሏል የእሱም ጸጉር ። ክረምቱ ጸጉርም ያሳምራል ልበል? አይቼ በውስጤ ያሰበኩት ነው። አሁንም እንደለመድኩት ጥያቄ ማንሳቴን ግን አልተውኩም። ” ይሄ ጸጉር መፍትሄ የለውም እንዴ?” ስል አነሳሁ ። በሳቅ የታጀበ መልስ ነበር አጸፋው።” ዘንድሮ ጉዞ ወደ ዩኒቨርሲቲ ነው። ተስተካከል ፣ ይሄን ልበስ ፣ያን አትልበስ፣ ደህና እደሪ” ነበር መልሱ። በልጁ አላዘንኩም መለስ ብዬ ያስታወስኳቸው ዩኒቨርሲቲዎቻችንን ነበር። ልጁ ያለው እውነት እኮ ነው አልኩ። የት ነህ? ማንነህ? ምንድነህ?… የሚል ከሌለ ዩኒቨርሲቲዎቻችን እውቀት መገብያ መሆናቸው ይቀርና ልክ የሰማነውን የምናየውን ይሆናሉ። እዚህ ላይ አንድ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ከፍተኛ ባለስልጣን ያሉኝን ላስታውስ። “ዩኒቨርሲቲዎቻችን ቡና የማይጠጡ ልጆችን ተቀብለው ጫት ቃሚ አድርገው ነው የሚያስረክቡት “ብለዋል ። ታዲያ ይሄንን እየሰማና እያየ ያደገ ተማሪ ዩኒቨርሲቲ እንደፈለግኩ የምሆንበት ቦታ ነው ብሎ ቢያስብ ይፈረድበታልን? የልጁን ፍላጎት አስቤ በተለይ ደግሞ የትምህርት ዘመኑ አልቆ ስንገናኝ ይሄ ጸጉር የት ሊደርስ እንደሚችል ዝም ብዬ ስስለው እንደሴቶቹ ወደኋላ ተኝቶ በፖኒተል አስሮ እንደምንገናኘ ሳላሸልብ አለምኩ። ደግሞም ይሆናል ምክንያቱም ሀይባይ የለማ። ይሄ የሚሆነው እስከ አለፈው ዓመት ብቻ ይመስለኛል። ምክንያቱም ቢዘገይም እንኳን ዘንድሮ ላይ ዩኒቨርሲቲዎቻችን ኮስተር ለማለት ማቀዳቸውን ሰምተናልና። ስርዓት አልበኛ ተማሪ አናፈራም፣ ሱሪ ዝቅ፣ ቡጭቅጭቅ …ለተማሪዎቻችን አይመጥንም እያሉ መሆናቸውን ጭምጭምታው ደርሶናል። እኛም ያድርገው እንላለን።ኧረ እንዳውም ደህና ነገር ሲሰማ አይቀይርብን ተብሎ ጸሎትና ዱአ ሁሉ ይደረጋል። የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የዩኒቨርሲቲ ተማሪ ሆነው እንዲገኙ እኛም ይሄንኑ እናደርጋለን ። ይሄንን መነሻዬ አደረግኩት እንጂ ብዙ ኧረ በጣም ብዙ ዩኒቨርሲቲ ገብተን ፀጉራችንን ቆጣጥረን፣ አሳድገን፣ አፍሮ አበጥረን… ብለው የሚያልሙ እንዳሉ አንዘንጋ ። ሁሉም ይሄንን የሚያልሙት ታዲያ ከምን ተነስተው ነው ብለን ብናስብ መልሱ ቀላል ነው። ቀደም ሲል ከገቡ ተማሪዎች ያዩትን ለመድገም ፣ የዕድገት ወይም የዩኒቨርሲቲ ተማሪ የመሆን መለያ አድርገው በማሰብ ይመስለኛል ብል ተሳሳትኩ እንዴ? ከሆነም ይቅርታ። የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ሪዛቸውና ጸጉራቸው የሚያድገው ለመስተካከል ጊዜ እያጡ የጥናት ሰዓት ይሻማብናል ብለው ይሆናል ብዬ አስባለሁ። በዚህ ሀሳቤ ዙሪያ አንድ የጤና ተማሪ ግን ምን አለኝ” ጸጉር መስተካከል እንዳውም የጥናት ጊዜ ያስገኛል ። ጸጉር መንከባከብ ነው ጊዜ የሚወስደው” አለኝ ።እንዴት? የእኔ ጥያቄ ነበር። በቃ አንድ ልጅ ጸጉሩን ካሳጠረ ጠዋት ፊቱን ሲታጠብ ጸጉሩንም ታጥቦ ንጹህ ይሆናል። ጸጉር ያለው ተማሪ ግን ያንን ጸጉሩን መንከባከብ ይጠበቅበታል ።መስታወት እያየ ማበጠርና ማስተካከል ሁሉ ይኖራል። ይሄ ደግሞ ጊዜውን ይሻማል ። ነገር ግን የጤና ተማሪዎች ከሶስተኛ ዓመት በላይ ሲሆኑ ፀጉር ማሳደግ አይፈቀድላቸውም። አለባበሳቸውም ሆነ ጸጉር አቆራረጣቸው ስርዓት ያለው መሆን አለበት ። ይሄ ግዴታ ነው። የሚያክሙትን ህመምተኛና የሚጎበኙት ታካሚ እምነት ሊጥልበት የሚችል ስርዓት የተከተሉ መሆን አለባቸው ተብሎ ይታመናል” ሲል አስረዳኝ። ይሄ በጣም ጠቃሚና ይበል የሚያሰኝ ሀሳብ ነው። ታዲያ ሌላው ሙያ ላይ እምነት የሚጣልበትና ለሚሰማራበት ሙያ አስፈላጊውን ስነምግባር የተላበሰ ማድረጉ ምነው ከፋን። ስለዚህ ሁሉም ተማሪ ስነስርዓት ያለው አለባበስና የጸጉር አቆራረጥ ይኑረው ነው ሀሳቤ። ይሄ በጣም ጥሩ ነገር ነው በሌላው ዘርፍስ በህብረተሰቡ ዘንድ ተመራጭ ተመስጋኝ ቢሆን የሚያገለግለው ደንበኛ የሚደሰትበት ቢሆን ኧረ እንዳውም ሱሪውን ከፍ አድርጎ ወገቡ ላይ የታጠቀ ወላጆቻችን እንደሚሉት ቆፍጣና ወንድ ቢሆን ምን አለ ። እንዳው ምነው ወንዶቹ ላይ በረታሽ አትበሉኝ። የሴቱም ለዛሬም ባይሆን ብዙ ይባልበታልና በዚሁ ይያዝ። ዘንድሮ ግን ዩኒቨርሲቲዎቻችን የመጥፎ ምሳሌ አንሆንም! እምቢ አሻፈረኝ! ለማለት መዘጋጀታቸውን ወሬ አይደበቅ አይደል ሀሜቱ ሽው ብሎኛል። ቀድሜ ካመሰገንኩ በኋላ ለመውቀስ አይሁን ብዬ እንጂ እውነት ያሰቡትን ከተገበሩት ቀደም ብለን ምስጋና ይድረሳችሁ ማለት ይገባል። ዩኒቨርሲቲዎች ሌላው አሳዳጊዎች ናቸው። ተማሪዎችን በእውቀት አጎልብተው፣ በአእምሮ አደርጅተው፣ ለሀገር ለወገን አሳቢ፣ ሀገር ወዳድ ዜጋ አድርገው ማውጫ ቦታ ናቸው። ታዲያ በተማሪ አያያዛቸው እንደስማቸው ቢሆኑስ? ሰላም!አዲስ ዘመን መስከረም 25/2012አልማዝ አያሌው
https://www.press.et/Ama/?p=20092
933
1መዝናኛ
አራት ሺህ ሜትሩ “ቁርጥ”
መዝናኛ
October 4, 2019
26
 ወዳጄ ነገ ከቻልክ እንቅልፍ እንዳወስድህ። የሀገርህን ውብ ገፅታ፤ የህዝብህን ድንቅ ባህል ወጥተህ ታደም።ወዳጄ የቁርስ ጉዳይ አያሳስብህ የምትታደመው “እንካ ብላልኝ፤ በሞቴ ይህቺን ደህሞ ተረጎንጭልኝ” የሚል ህዝብ በደገሰው ድንቅ ባህል ነው። በባህሉ ባለሙያዎች በልዩ መልኩ የተዘጋጀ ቁርጥ ተዘጋጅቶልሀል።የኦሮሞ ጭኮ ማለት ንፁህ ቅቤ እየቆረጥክ መላፍ በለው።ይሄ ድንቅ የሆነ ማህበረሰብ “ናልኝ በሞቴ ብላ፤ ይህቺን ድገም” ብሎ ሊያጎርስህ ተዘጋጅቷል።“ቁርጡን” እየቆረጥክ በአይኖችህ አይጠገቤ የሆኑ የባህል ትርኢቶች፣ መዋደድን የሚሰብኩ ልዩ ልዩ ሁነቶችን አይተህ ትደመማለህ።አዎን ወዳጄ ነገ ሸገር ላይ የሚከበረውን ድንቅ ባህል፤ አዲስ ላይ የሚጥለቀለቀውን ማራኪ ውበት፤ ፊንፉኔ ላይ የሚታየውን ፍቅር ተቋደስ።ኢሬቻን በመታደም በብዙ ተጠቀም! ቀጣዩን አመት በጉጉት እንድትጠብቅ የሚያደርግህ የበዛ መደመም ይገጥምሀል።አብሮህ የሚኖረውን ማህበረሰብ ድንቅ እሴት፤ የእርስ በዕርስ መዋደድና ፍቅር ትመለከታለህ።እስርህ ሆኖ ያማታውቀውን አስደናቂ ማንነት፤ አብሮህ ሆኖ ያልተላመድከውን ልዩ ክስተት ኢሬቻ ላይ ታገኘዋለህ። የሀገርህን ድንቅ ውበት፤ የህዝብህን የማይነጥፍ ድንቅ ባህል፤ የወገንህን የ አብሮነት ጥምረት ትኮመኩማለህ። ወዳጄ ይሄን ጥሩ ገጠመኝ እንዳታልፍ፤ አብረህ ተቀላቅለህ የባህሉና የበዓሉ ባለቤት ሆነህ ፍቅርን ተላመድ።ድንቁን የሀገሬን ሰው በባህል ልብሱ አጌጦ፤ ለአምላኩ ምስጋናውን ሲያደርስ ተመልከት።ደግነቱን፣ ቀናነቱን፣ የአብሮ መኖር ጥልቅ ፍቅሩንና ህብረቱን የሚገልፅበትን ልዩ እሴቱን ታደም።በአመት አንዴ ኦሮሞ በሚያከብረውን ታላቅ የባህል መድረክ ላይ ተገኝተህ ከታላቅ ህዝብ ጋር ዋል። አይንህ በተመለከተው ነገር ላይ ሁሉ ይደመማል።የባህል አልባሳቱን አይቶ ያደንቃል፤ የማህበረሰቡን ልዩ ልዩ ትስስራዊ መገለጫዎችን አይቶ ይደመማል።አንተ ብቻ እዚያ ቦታ ተገኝተህ ወገንህን ለማየት ያብቃህ እንጂ የምትናፍቀው ልዩ ገጠመኝ ይጠብቅሀል።“ቁርጥ” ስልህ የአገሬ ሰው ጥርስህን የሚያደክም በትግል የምታኝከው አይደለም። እየሰለቀጥህ የምታሻምደው የቅቤ ልውስ እንጂ፤ ጣዕሙ ስታስበው ምራቅ የሚያስውጥ ቁርጥ ነው። ኢትዮጵያ ድንቅ ሀገር ናት። ህዝቦችዋም የተዋቡ፤ የዚህችን ውብ ሀገር አስደናቂ ባህሎችና ማራኪ ገፅታ አይኑን ገልጦ ላስተዋለው ልቡን ከፍቶ ላሰበ ያ’ጅባል። ከራስ አስከ እግሯ፤ ከፊት እስከ ጀርባዋ ላስተዋለ ይደመማል። ተነግሮ የማያልቅ ተዳስሶ የማይደረስ ባህልና ትውፊት ባለቤት ናት ሀገሬ፤ ኢሬቻም ከእነዚህ ሀገራዊ ድንቅ ባህላዊመገለጫዎች አንዱ ክብረ በዓል ነው።በጋው መሬቱን በፀሀዩ ሰነጣጥቆ አፈሩን እንደ ዱቄት ሊበትነው ሲቃረብ፤ ክረምቱ ደርሶ የተራበውን መሬት በዝናብ አርሶ፤ የደረቀውን መሬት ድጋሚ ህይወት ይዘራ ዘንድ፤ ድጋሚ ምድሩ ይለመልም ዘንድ ወቅቱን ይረከባል።ክረምት የህይወት መቀጠያ፤ የመኖር ዋስትና ውሀ መፍለቂያና የዝናም ምንጭ ነውና በብርቱ ይናፈቃል። በዚህ ወቅት ኦሮሞ ልዩ ባህል አለው።የክረምቱን መምጣት ተከትሎ የሚያከብረው አምላኩን በክረትም ከሚገኝ መልካም ነገር እነዲያጎናፅፈው የሚለምንበት በክረምት ከመጣ ክፋት እንዲጠብቀው የሚማፀንበት፤ ኢሬቻ ተፈጥሮን ገርቶ፣ ምድርን አለምልሞ፣ ጤናን ጠብቆ ሀገርን አንፆ ላቆመ አምላክ ምስጋና የሚቀርብበት ድንቅ የኦሮሞ ትውፊታዊ በዓል ነው።የኢሬቻ ፍልስፍናው የሰዎችን አንድነትና መጠናከር የሚሰብክ፤ ፍቅር፤ ሰላም የሚያፀና፤ አብሮ መኖርንና መተጋገዝን የሚነግር መሆኑ ተናፋቂ በዓል ያርገዋል።ነገ ይህንን ክብረ በዓል መዲናችን ልታስተናግድ ወገብዋን አስራ ለበዐሉ ስርዐት በመትጋት ላይ ትገኛለች።በዚህ ክብረ በዓል ላይ በመገኘት አንተነትህን ከፍ አድርግ፤ በዚህ የሚሊዮኖች ስበስብ ላይ ታድመህ ባህል የፋፋቴ ያህል ሻኣ…ብሎ ሲወርድ ሁሉንም ሲያረሰርስ ተመልከት። ባህል በራሱ የሚያንፀው የሚያቀናው ብዙ ጉዳይ አለ። ባህል የሚያወርሰው የበዛ ትርፍ መቋደስ የሚሰጠው ትልቅ ችሮታ ነው። የሌላ ’ምትለው አንድም ነገር የለም።መልካም ነገርን ሲመለከት የራስን ማድረግ መልካምነት ነው።“የአንተ ነው” ተብሎ የተሰጠህን ነገር “የእኔ አይደለም” ብሎ መግፋት ደግሞ ከባድ ጉዳይ፤ ነው፡፡ ኢሬቻ የሀገርህ ትሩፋት ከመሆን አልፎ የተባባሩት መንግስታት ደርጅት በዓለም ቅርስነት ሊመዘግበው ከጫፍ ላይ ደርሷል። አንተ የኔ አይደለም ብትል ይከብደብሀል። የአንዱን ባህል በሌላው መከበሩ፤ የአንዱ በጎ ነገር ሌላው ዘንድ ደርሶ በጎነት ማላበሱ፤ ፍቅርን መጨመሩ እጅጉን የሚወደድ ጉዳይ ነው።እኛ ኢትዮጵያዊያን ብዙነታችንን አክብርን፤ የእርስ በእርስ ትስስራችን አጠንክርን መሄድ ወደፊት መጓዝ እንዳለብን ስያንፅ ያቆየን ባህላችን አይደል? የሚያስውበን የሚያስተሳስረን ድንቅ እሴታችን አይደል? ድንቅ ባህላችንን ከፍ አድርገን በጋራ ከፍታ ላይ እንድንደርስ መንገድ ሊሆነን የሚችል ብዙ ትሩፋት አለን።በዚያ ማትረፍን እንጂ መጉደልን እንዴት ልናስበው እንች ላለን? ባህል በማህበረሰብ የረጅም ጊዜ ልምድ የሚዳብር የማህበረሰቡ መገለጫ ነው።ያንን ባህል ተወልዶ፤ በዚያው ተኮትኩቶ አድጎ የፈጠረውን በጎ ተፅዕኖ ለሌላው የሚተርፍ አገር አቅኚ ከሆነ ያ ባህል መልካምነቱ አይካድም።የሚሰጠው ጥቅምና የበዛ ትርፍ ባትራፊው የኔ ነው ባይነት ላይ ይወሰናል።በጎ ነገርን የጋራ ማድረግ ከጋራ የከበደ ብልጠት፤ ከመውደድ ከፍ ያለ መጋመድ ይፈጥራል። አዎን፤ የሀገሬ ልጆች! እኛ ኢትዮጵያውያን የችግሮቻችን መፍትሄ ያለው በእኛው እጅ ላይ ነው። ተቀራርበን እንነጋገር፣ እንግባባ እንደራደር።የሚለያየን ነገር ይቀረፋል፤ ልዩነታችን የሰፋ ቢሆን እንኳን ተቀብለን አንደኛችን የሌላውን አክብረን በልዩነት ውስጥ በፍቅር እናድራለን። አንድ አመለካከት ሀገርን ቀይሮ አያውቅም።አንድነት ፍቅርና ህብረት እንጂ፤ የኢሬቻን የአንድነት ጥሪ አብሮ የመቆምን ባህል አብረን በማክበር አብረን በማስዋብ እናፅናው።ያ ነው ኢትዮጵያዊነት! የተሟላ፤ እርስ በርስ የሚያስተሳስር ሙሉ የሆነ ውብ ባህል አለን።የጎደለው የሚሞላው ያለውን በማጉደል አይደለም። ሀገር የሚለወጠው በሰፊ ሀሳብ ነው። ሀገር ማለት የክብርህ መጎናፀፈያ፤ የችግርህ መከለያ ጥላ ናት። ለራሳችን ብለን ሀገራችንን እንውደድ! ለሀገራችን በጎ እንመኝ።የህዝቦችዋን መቀራረብ የሚያጠናክር መንገድ መፈለግ የሚያለያይ ከመፈለግ እጅጉን ይቀላል ወዳጄ።በህብረት ውስጥ የምታገኘው በጎ ተግባር ውጤቱ የጭኮ ያህል ይጥ ማል።በአብሮነት ከቆምን፤ የእርስ በርስ ፍቅራችን ከደረጀ እመነኝ ያኔ ከፍታ ላይ እንገኛለን። ከፍታ ላይ የሚያደርሰው ደግሞ ፍቅር ብቻ ነው። አብሮነታችን በአብሮነት የታነፀ ውብ ጉዳይ ነው።“የእነሱ” የምንለው ምንም ነገር የለም። የኛ፤ የጋራችን፤ የሁላችን የምንለው የበዛ ነገር አስተሳስሮናል።የእጆችህን ጣቶች እያቸው ወዳጄ የተለያየ ቅርፅ፤ የራሳቸው ቁመትና ተግባር አላቸው። አንድ ላይ ሆነው ግን የተቃና ተግባር ይከውኑልሀል።ይሄ ትልቅ ሚስጥር ነው ወዳጄ፤ በጥልቀት ከተረዳኸው ብዙ የሚነግር፤ ባህሏን በመጠበቅ የእርስ በርስ ግንኙነታችንን በማጠናከር “ሀገሬ ክብሬ” የምንላትን ሀገር እንገንባ። ትውልድን ፍቅር በማስተማር በባህሉ የታነፀ፤ የሀገር ፍቅር የገባው፤ የህዝብ ጥቅም የሚያስቀድም ቀና እናድርግ። ለትውልዱ ሳናቋርጥ ፍቅርን መስበክ እንልመድ።በፍቅር የታነፀ ሀገሩን የሚወድ ትውልድ መግሪያው ይህ መንገድ ብቻ ነውና፤ በፍቅር ጥላ ስር ተቻችሎ ማደርና ተባብሮ ማደግ ደስታና ሀሴት ለሁሉም ይዳረሳል። በፍቅር የተጋሩት የከፋ ነገር እንኳን የለዘበ ክፉ ነው እንጂ ፅልመት የለውም። ታደም ያልኩህ የኢሬቻ በዓል የተዋበ ባህሉን ከየአቅጣጫው አቅርቦ የሚያስኮመኩምህ ደጉ ወገኔ ውበቱንና ፍቅሩን እንድታይበት ነው።በፍቅር ደግፎ የዛሬ መገኛህ ላይ ያደረሰንህ ውብ ባህል እድትመለከት አብረህም እንደትቋደስ መፈለጌ ነው ውትወታዬ፤ የሀገርህን ውብ ባህል አውቀህ ለሌላው መተረክ ትችል ዘንድ የማህበረሰብህን ባህል፤ የወገንህ ክብረ በዓል በማስጌጥ አብረህ ዋል። የበዛ ክብረ በዓልና ባህል የታደለች ሀገር ላይ መፈጠር በራሱ ትልቅ እድል ነው ያልኩህም በዚሁ ምክንያት ነው።የተዋበ ነገር ለመዋዋስ፤ የተጓደለን ለመሙላት በብዙ ልዩነት ውስጥ በተጋመደ አንድነት ማለፍ ትልቅ ጥቅም አለው።የራቀን ነገር እኳን አቅርቦ የኔነት ስሜት መፍጠር መልመድ በጎ ነው። ይሄ ግን የቅርብ ቅርብህ ነው። የራስህ፤ አንድነት ላይ ቆሞ ስለ አንድ ሀገር ማሰብ የላቀ ምጥቀት ነው።ቀለመ ብዙ፤ ባህለ ስብጥር መሆን መልካም ነው። የዚህችን ሀገር ተዓምራዊነት ለመረዳት ተዓምረኛ ወይም የመጠቅህ መሆን አይጠበቅብህም ወዳጄ፤ ውበት ሞልቶ የሚፈስባት፤ የተዋበ ባህል ያለት ለመሆኑ በጓዳህ ያሉትን፤ በስርህ ያሉትን ባህልና እሴቶችዋን ተመልከት።የሀገሪቱ ውበት መገለጫ የሆኑ ልጆችዋ የየራሳቸው ልዩ ባህል ስያንፀባርቁ ተመልክተህ ብዙ ትማራለህ። በህብረት የቆሙት ልጆቿ የየራሳቸው መልካም እሴት ተላብሰው፤ ባህልና ማንነታቸውን በተለየየ መልኩ በመግለፅና በአንድነት ቆመው የሚያስጌጧ ውብ ሀገር መሆኗን ለመስከር ባህላዊ ክብረ በዓላቸውን መታደም በቂ ነው። እዚህች ሀገር ላይ መፈጠርህን በራሱ ትልቅ አድል ነው ያልኩህ የሚገባህ ሀገሪቱ ውስጥ ያለውን ድንቅ ነገር ስትረዳ ነው።ተዟዙረህ የምታየው በረከት የተትረፈረፈ ሆኖ ታገኘዋለህ።እርግጥ ሀገሪቱ ያላት የበዛ በረከት ልጆች ተረድተው መጠቀሙ ላይ ገና ብዙ ቢቀራቸውም፤ የበዛው ሀብትቷ ግን ሳይነኩትም ብዙ መሆኑ ያስታውቃል።የሰጡትን አጥፎ የሚመልሰው፤ የዘሩበት አለምልሞ የሚያበቅለው ለሙ መሬት ጠረኑ ይናፍቃል። ይሄንን የምትረዳው ስትርቅ ነው ወዳጄ፡፤ የሀገር ፍቅር እና ክብር ማጣጣም የሚቻለው ከጉያዋ ሲርቁ ነው።ሀገር ጥላ ነው፤ የክፉ ቀን መሸሸጊያ፤ ባህል ደግሞ የማህበረሰብ መገለጫ፤ ባህላችንን በበጎ ተጠቅምን የጋራ መቆሚያ አውድ ማድረጉ የእኛ የምንለው ነገር እንዲበዛ ያደርግልናል።ቸር ይግጠመን!አዲስ ዘመን መስከረም 23/2012ተገኝ ብሩ
https://www.press.et/Ama/?p=19977
1,025
1መዝናኛ
አጫጭር ዜናዎች
ስፖርት
April 24, 2020
16
የበርሊንና ለንደን ማራቶን በተያዘላቸው ጊዜ አይካሄዱም በዓለማችን ከሚካሄዱ ስድስት ታላላቅ የስፖርት ውድድሮች መካከል የሆኑት የበርሊንና የለንደን ማራቶን በተያዘላቸው ጊዜ እንደማይካሄዱ ታወቀ። የበርሊን ማራቶን በጎርጎሮሳውያኑ አቆጣጠር ሴፕቴምበር 27 ቀን 2020 ይካሄዳል ተብሎ የታቀደ ቢሆንም ጀርመን የእንቅስቃሴ ገደቧን እስከ ጥቅምት ወር መጨረሻ ድረስ በማራዘሟ የተነሳ እንደማይካሄድ ታውቋል። የውድድሩ አዘጋጆች በመግለጫቸው በታቀደለት ጊዜ «አይካሄድም» ከማለት ውጪ ለሌላ ጊዜ ይተላለፍ አይተላለፍ የገለፁት ነገር የለም። ቀጣዩን እርምጃ እንደሚያስተባብሩም ጨምረው ገልፀዋል። የበርሊኑ ውድድር ሊካሄድ ታቅዶ የነበረው ከለንደኑ ማራቶን በፊት አንድ ሳምንት ቀደም ብሎ ሲሆን በኋላ ላይ ግን የለንደኑ ማራቶን እኤአ ወደ ኦክቶበር 4 ተገፍቷል። የለንደኑ ማራቶን በመጀመሪያ እቅዱ መሰረት በዚህ ሳምንት መጨረሻ ለመካሄድ እቅድ ተይዞ የነበረ ሲሆን በኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት ነው ወደ ሌላ ጊዜ የተላለፈው። የበርሊን ማራቶን አዘጋጆች በቅርብ ጊዜ እንዲካሄድ የሚወስኑ ከሆነ በሕዳር ወር አጋማሽ ሊሆን ይችላል የተባለ ሲሆን በዚያ ወቅትም ግን የኒውዮርኩ ማራቶን እንደሚካሄድ የወጣው የጊዜ ሰሌዳ ያሳያል። በናይጄሪያ 30 የእግር ኳስ ተጫዋቾች በቁጥጥር ስር ዋሉ የናይጄሪያ ፖሊስ በካኑ ግዛት 30 እግር ኳስ ተጫዋቾችን በቁጥጥር ስር ማዋሉ ተገለፀ። እነዚህ የእግር ኳስ ፍቅር ያሳበዳቸው ወጣቶች በአገሪቱ የተጣለውን የመንቀሳቀስ ገደብ ቸል ብለው ጨዋታዎችን አዘጋጅተዋል፤ ተጫውተዋልም ተብሏል። የናይጄሪያ ዜና ኤጀንሲ (ናን) እንደዘገበው እግር ኳስ ተጫዋቾቹ በግዛቲቱ የተለያዩ አካባቢዎች በመዘዋወር የተጫወቱ ሲሆን ደጋፊዎቻቸውም ተሰብስበው ሲመለከቷቸው ነበር። ተጫዋቾቹ በማህበራዊ መገናኛ ብዙኃን ይህንኑ የሚያሳይ ተንቀሳቃሽ ምስል አጋርተዋል። የካኖ ግዛት ፖሊስ ኃላፊ የሆኑት አብዱላሂ ሃሩና እንዳሉት ተጫዋቾቹ የተያዙት ግጥሚያ ካደረጉ በኋላ ነው። እንደ ዜና ኤጀንሲው ዘገባ ከሆነ የተጣለውን የእንቅስቃሴ ገደብ በመተላለፍ ይከሰሳሉ። የኮሮና ሕግን የጣሱት ሁለቱ ተጫዋቾች ይቅርታ ጠየቁ የቶተንሃም እግር ኳስ ተጫዋቾች ሰርጅ ኦሪየር እና ሞሳ ሲሶኮ ኮሮና ቫይረስን ተከትሎ የተጣለውን ገደብ በመጣሳቸው ይቅርታ ጠየቁ። ተጫዋቾቹ ይቅርታ ያሉት አብረው ልምምድ ሲያደርጉ የሚያሳይ ፎቶ በማህበራዊ ሚዲያ ከለቀቁ በኋላ ነበር። ኦሪየር በማህበራዊ ሚዲያ ላይ የተለቀቀውና በኋላ ያጠፋው ቪዲዮ የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ (ማስክ) አድርጎ ከሲሶኮ ጋር ጎን ለጎን ሲሮጡ ያሳያል። የዩናይትድ ኪንግደም መንግሥት በኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት አካላዊ እንቅስቃሴ ለማድረግ ለብቻ አሊያም አብረዋችሁ ከሚኖሩ ሰዎች ጋር ብቻ ይሁን ሲል ውሳኔ አሳልፏል። ተጫዋቾቹ ይቅርታቸውንም ለመግለፅ ለብሔራዊ የጤና አገልግሎት ድጋፍ እንደሚያደርጉ ተናግረዋል።አዲስ ዘመን ሚያዝያ 16/2012
https://www.press.et/Ama/?p=31026
311
2ስፖርት
የታክስ ውስጥ ጥቅሶች
መዝናኛ
October 4, 2019
89
በተለምዶ ጥቅስ ሲባል፤ በመደበኛ አጠቃቀም ከመጻሕፍት (ቅዱሳን መጻሕፍት፣ የምርምር እና የሣይንስ መጻሕፍት፣ የታሪክ ድርሳናት እና የልብ ወለድ ድርሰቶች) የሚታወቁ እና ለምንናገርበት ወይም ለምንጽፈው ጉዳይ ማጠናከሪያ ሆነው የሚጠቀሱ እና ባለቤት ያላቸውን ነው፡፡ ነገር ግን ጥቅስ ተናጋሪው ወይም ጸሐፊው ሳይታወቅ ሀሳብን በተቃውሞ ወይም በድጋፍ የማኅበረሰቡን ሥሜት ሲገልፁ ይስተዋላል፡፡ለዚህ ተግባር ከሚጠቀሱት ደግሞ የመፀዳጃ ቤቶች /በተለይ በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት/ እና የታክሲ ውስጥ ጥቅሶች በዋናነት ይነሳሉ፡፡ እነዚህ ጥቅሶች በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የጥናት እና ምርምር ርዕሰ ጉዳይ በመሆን በርካታ ጥናቶች ተካሂዶባቸዋል፡፡ ከቅርብ ጊዜ ጀምሮ ደግም በማኅበራዊ ሚዲያዎች የመወያያ ሀሳብ እየሆኑ መቅረብ ጀምረዋል፡፡ እኛም በዚህኛው አውድ የተወሰኑትን ጀባ ብለናል፡፡ ከታክሲ ሥራ ጋር የተያያዙ ጥቅሶች ዘመን መፂሄት መስከረም 2012 አባይ ፈለቀ
https://www.press.et/Ama/?p=19999
103
1መዝናኛ
የእግር ኳሱ ዓለም ‹‹ፍቅር እስከ መቃብር››
ስፖርት
April 27, 2020
38
የፍቅር ጉዳይ ሲነሳ በዓለማችን የተለያዩ ጥንዶች በተለያዩ ዘመናት የነበራቸው የሚያስቀና ፍቅር በብዙ ታሪኮች ሲጠቀስ ይታያል፡፡ በአገራችንም ተሰምተው የማይጠገቡ፣ ለበርካቶች ትምህርት የሆኑ ዘመን ተሻጋሪ የፍቅር ታሪኮች አሉ፡፡ ብዙ ጊዜ የልብ ወለድ እንጂ በገሃዱ ዓለም ያሉ ወይም ተከስተው የነበሩ የማይመስሉ የተለያዩ የፍቅር ታሪኮችን ቢያንስ አንድ የሚያውቅ አለ ተብሎ አይታሰብም፡፡ ዘመን አይሽሬው የአገራችን ልብ ወለድ ‹‹ፍቅር እስከ መቃብር›› የሁለት ጥንዶችን የፍቅር ጥግ በማሳየት በብዙዎች ዘንድ የሚረሳ አይደለም፡፡ ከዚያም የተነሳ በውጣ ውረድ የተሞላ፣ ፈተናዎች የበዙበት የፍቅር ሕይወትና ፅናት ‹‹ፍቅር እስከ መቃብር›› የሚል ስያሜ ሲቸረው ማየት የተለመደ ነው፡፡ በስፖርቱ ዓለምም በተለይም በእግር ኳሱ አንድ የፍቅር ታሪክ በርካቶችን ሲያነጋግር ኖሯል፣ እያነጋገረም ይኖራል፡፡ የዚህ ፅኑ ፍቅር ታሪክም በዛሬው የስፖርት ማህደር አምዳችን እንዲህ ይነበባል፡፡ የዚህ ፍቅር ታሪክ መሪ ተዋናይ ቤርናዴት አዳምስ ትባላለች፡፡ ቤርናዴት ዘወትር ማልዳ ትነሳለች። አንድ ሰዓት እንኳን ሳይሞላ ቀኗ ይጀመራል። ቁርሷን ትበላለች፣ ባለቤቷን ለመንከባከብ ራሷን ታዘጋጃለች። ልብስ ትቀይርለታለች። ምግብ ታበስልለታለች። ወደ መፀዳጃ ቤት ትወስደዋለች። ቆሻሻውን ሁሉ ታፀዳለታለች። ጡንቻውን ታፍታታለታለች። ይህ የአንድ ቀን ብቻ ልማዷ አይደለም። ላለፉት ሰላሳ ስምንት ዓመታት አድርጋዋለች። በየዕለቱ ደጋግማዋለች። እስከ መጨረሻው ላታቋርጥም ለራሷ ቃል ገብታለች… ዘመኑ በ1960ዎቹ ፈረንሳይ በጄኔራል ሻርል ደጎል አመራር ስር ሳለች፣ የመንግስት ወግ አጥባቂ አስተዳደር እያደር የህዝብ ቅሬታ ሲያስነሳ ነበር። ጥቁሮች ከነጭ ፈረንሳውያን ጋር በጋብቻ ከተጣመሩ ጉድ የሚባልበት ያ የዘረኝነት ዘመን…። ጥቁሩ ዣን ፒዬር አዳምስ ግን ከነጯ ቤርናዴት ጋር በፍቅር ወደቀ። ወደደችው፣ ወደዳት። አገር ጉድ ይበል ብለው ፍቅራቸውን እስከ ጋብቻ አደረሱት።ገና አማተር ተጫዋች ሳለ ነበር የተዋወቁት። በ1969 ከጋብቻ በኋላ፣ ከፍተኛ ዲቪዚዮን የነበረው ኒም ፕሮፌሽናል ኮንትራት አቀረበለት። ተቀበለው። ዣን-ፒየር እና ቤርናዴት ኑሯቸውን ወደ ኒም ከተማ አዛወሩ። በፍቅር ሲኖሩም ወንድ ልጅ ወለዱ። 1970ዎቹ ለጥንዶቹ አስደሳች ዘመናት ነበሩ። አዳምስ ከፈረንሳይ ብሔራዊ ቡድን የመጀመሪያ ጥቁር ተጫዋቾች መካከል አንዱ ነው። ዝና፣ ገንዘብ፣ መሽቀርቀር፣ መደሰት የአዳምስ የዕለት ተዕለት ልማድ ነበር። ቀልድ ያውቃል። ፈገግታ ከፊቱ አይጠፋም። ዝና ሲጨመርበት ደግሞ… አለ አይደል… አብሮ የሚስቅም አይጠፋም። ገና የ10 ዓመት ብላቴና ሳለ አያቱ በመንፈሳዊ ጉዞ ሰበብ ይዘውት ከመጡ በኋላ የሴኔጋሉ ልጅ ፈረንሳይን ቤቴ ብሏል። ፓሪ ሰን ዠርመ እና ኒስን ጨምሮ እስከ 1981 ድረስ በዲቪዚዮኑ ለእውቅ ክለቦች ተጫወተ። 34 ዓመቱ ላይ ጫማውን ሰቅሎ፣ ለቀሪው ህይወቱ ህፃናትን ለማሰልጠን ለትምህርትና ልምምድ ወደ ዲዦ ከተማ አቀና። እዚያም በልምምድ ላይ ሳለ በጉልበቱ ላይ ጉዳት ደረሰበት። የሊጋሜንቱን ህመምለመገላገል በሊዮን ከተማ በሚገኘው ኤድዋርድ ሄሪዮ ሆስፒታል ምርመራ አደረገ። ጉዳቱ ቀዶ ህክምና እንደሚያስፈልገው በማረጋገጡ ለቀዶ ጥገናው ቀን ተቀጠረ። የቀን ጎዶሎ፣ እኤአ መጋቢት 17 ቀን 1982። አዳምስ ቀጠሮውን ጠብቆ ቢመጣም በአገሪቱ የጤና ባለሙያዎች የስራ ማቆም አድማ አድርገዋል። ህሙማን ብዙ ቢሆኑም ሃኪሞች ጥቂት ነበሩ። የአዳምስ ቀዶ ጥገና አስቸኳይ ባለመሆኑ እንደገና ሊቀጠር ይችል ነበር። ሆኖም ባሉት ባለሙያዎች ጉልበቱ ሊከፈትና ሊጠገን ተወሰነ። አንድ የማደንዘዣ ባለሙያ ብቻ ስራ ላይ ነበረች። ተለማማጅ ተማሪዎችም አሉ። ህሙማን እንደ ቦኖ ውሃ በየተራ ማደንዘዣ ተሰጣቸው። አዳምስ ተራው ደርሶ አሸለበ። ግን እንደተጠበቀው አልሆነም። ጉልበት ላድን ያለው ህክምና እጅና እግሩን ጨምሮ መላው አካላቱን ከጥቅም ውጭ አደረጋቸው። ከአይኖቹ ሽፋሽፍት በስተቀር ቢጠሩት እንኳን ፊቱን ዞር ማድረግ ተሳነው። አንደበቱ ተዘጋ፣ በድጋሚ መናገር አልቻለም። የማደንዘዣው ሂደት የህክምና ስህተት ነበረው። ተለማማጆቹ ወደ ሰውነቱ ያስገቧቸው ትቦዎች እንኳንበቅጡ አልተሰኩም። ወደ ሳንባው የተላከው ትቦ የአሰካክ ስህተት ስለነበረው ሳምባዎቹ በቂ ኦክስጅን ባለማግኘታቸው የልቡ ስራ ተስተጓጎለ። አንጎሉ በቂ ኦክስጂን ባለማግኘቱ ለአደጋ ተጋለጠ። ያ ፈርጣማ ተከላካይ ሰውነቱ ከዳው። መላወስ አቃተው። በዚያች እርጉም ቀን ያለ ድጋፍ ወደ ሆስፒታል ቢገባም፣ በራሱ አቅም ወደ ቤቱ መመለስ አልቻለም። ቤርናዴት ለአምስት ቀን በሆስፒታል እየዋለች፣ እያደረች ጠበቀችው። ፍቅሯ፣ የልጇ አባት፣ የህይወቷ ጓድ ከተኛበት ሳይነሳ ቀረ። ከእንግዲህ በሰው ድጋፍ እንጂ በራሱ አቅም መንቀሳቀስ እንደማይችል ቁርጡን ነገሯት። የህክምና ኃላፊዎች ለአረጋውያን መንከባከቢያ ማዕከል እንድትሰጠው መከሯት። ለቤርናዴት ይህ የሰነፎች ምክር ነበር። አልተቀበለቻቸውም። ‹‹ወደ ቤታችን እወስደዋለሁ፣ እዚያም እስከመጨረሻው እንከባከበዋለሁ›› ብላ ወሰነች። በደግ ዘመን ፍቅርን ወዳዩበት ቤታቸው አመጣችው። 2018…፣ ዣን ፒየር አሁንም በህይወት አለ። ዕድሜው ሰባዎቹን አልፏል፡፡ ቤርናዴትም አልሰለቸችም። ዕድሜ ተጭኗት ቆዳዋ ተሽብሽቧል። የዚያ ዘመን ውበቷ ረግፏል። እርጅና ቤት እየሰራባት ነው። ግን እጅ አልሰጠችም። ባሏን መንከባከብ የዕለት ተዕለት ስራዋ ከሆነ 38ኛ ዓመቷን ልትደፍን ተቃርባለች። ዘመናት ቢያልፉም ታማኟ ሴት ግን ሰው ሰራሽ ስህተት አልጋ ላይ የጣለውን ሸበላ አይኗ እያየ ልትጥለው አልፈቀደችም። የመጀመሪያ ፕሮፌሽናል ክለቡ ከሚገኝበት ኒም ከተማ አቅራቢያ ዣን ፒየር አዳምስ አሁንም ተኝቷል። ዛሬም ቤርናዴት ከጎኑ አለች። ከአደጋው በኋላ በእያንዳንዷ ቀን እንዳደረገችው ሁሉ ዛሬም ማልዳ ትነሳለች። ታጥበዋለች፣ ታለብሰዋለች፣ ትመግበዋለች፣ ከመተኛት ብዛት ጎኑ እንዳይላላጥ ታገላብጠዋለች። አልታከተችም፣ አልሰለቸችም። መልስ ባይሰጣትም ታወራዋለች፣ እኤአ በ1969ና 1976 የወለዷቸው ልጆች ላውረንትና ፍሬድሪክ እንደወለዱና አያት እንደሆነም አብስራዋለች፡፡ አንድ ቀንም ይነቃል የሚል ተስፋዋ አብሯት አለ፡፡ አዲስ ዘመን ሚያዝያ 19/2012 ቦጋለ አበበ
https://www.press.et/Ama/?p=31210
658
2ስፖርት
ኮሚሽኑ ኮቪድ 19ን ለመከላከል የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ ይቀጥላል
ስፖርት
April 30, 2020
14
የዓለም ህዝብ ስጋት የሆነውን የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ 19) የሚያስከትለውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ ለመቋቋምና ለመከላከል መተጋገዝ አስፈላጊ መሆኑ ተደጋግሞ ይነገራል። በዚህም ምክንያት የተለያዩ አካላት በዓይነት፣ በገንዘብ እንዲሁም ባለሙያዎችም በጉልበታቸው ጭምር ርብርብ በማድረግ ላይ ይገኛሉ። የስፖርት ዘርፍም በዚህ እንቅስቃሴ ቀዳሚ ተሰላፊ መሆኑ ታይቷል። የስፖርት አመራሮች፣ የስፖርት ማህበራት፣ ስፖርተኞች፣ አሰልጣኞች እንዲሁም ደጋፊዎቻቸው፤ መልእክት በማስተላለፍ፣ በየቤታቸው ላሉ ዜጎች የአካል ብቃት እንቅስቃሴ በማሰራት፣ የገንዘብ ድጋፍ በማድረግ፣ የምግብና ሌሎች መገልገያዎችን በመለገስ እንዲሁም በሌሎች ተግባራት ላይ እየተንቀሳቀሱ ነው። ዘርፉን የሚመራው የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽንም ይህን እንቅስቃሴ በማስተባበር እንዲሁም እንደ አንድ ባለድርሻ አካል በሚጠበቅበት ሁሉ የራሱን ድርሻ በመወጣት ላይ ይገኛል። ቫይረሱ ወደ ኢትዮጵያ መግባቱ ከተሰማበት ጊዜ አንስቶ የመንግስትን አቅጣጫ በመከተል የተለያዩ እርምጃዎችንም ወስዷል። በቅድሚያም ህዝቡን በብዛት በማሳተፍ ቫይረሱን በማሰራጨት ረገድ ከፍተኛ ሚና ሊጫወቱ እንደሚችል ስጋት የሚያሳድሩ የእግር ኳስና ሌሎች ስፖርታዊ ውድድሮችን ማቋረጥ ነው። በቀጣይም በየክለቦቹ እንዲሁም በማሰልጠኛ ተቋማት ያሉ ሰልጣኞች ወደ የአካባቢያቸው በመሄድ ራሳቸውን በየቤታቸው እንዲያቅቡ ማድረግ ነው። በቀጣይም የቶኪዮ ኦሊምፒክ ብሄራዊ ቡድኑን አባላት መበተንን ጨምሮ የተለያዩ የቡድን እንቅስቃሴዎች በስፖርቱ ዘንድ እንዳይካሄዱ ማገድ ነው። ከዚህ በኋላም ስፖርተኞችና ማህበራት በግላቸውና በቡድን ከሚያደርጉት እገዛ ባሻገር በስሩ ያሉትን አካላት በማስተባበርና በማቀድ እየሰራ ይገኛል። ኮሚሽኑ በዋናነትም አራት ተግባራትን በመለየት ኃላፊነቱን እየተወጣ እንዳለም ኮሚሽነር ኤሊያስ ሽኩር ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ ገልጸዋል። ይኸውም የገንዘብ ድጎማ፣ በስፖርት ቤተሰቡ የግንዛቤ ማስጨበጥ፣ የአካል ብቃት እንቅስቃሴዎችን በመገናኛ ብዙሀን ማስተላለፍ እንዲሁም የማሰልጠኛ ተቋማት ቫይረሱን ለመዋጋት በሚደረገው እንቅስቃሴ አንድ አካል እንዲሆን የማድረግ ትብብር ነው። የገንዘብ ድጎማውን ተከትሎም የስፖርት ማህበራት በግላቸው ከፍተኛ እንቅስቃሴ በማድረግ ላይ ይገኛሉ። በኮሚሽኑ አስተባባሪነት ከአገር አቀፍ ስፖርት ማህበራትና የአትሌቶች ማህበር ጋር በመሆን የተደረገውን የሶስት ሚሊየን ብር ድጋፍ ጨምሮ፣ የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ፣ የኢትዮጵያ አትሌቲክስና እግር ኳስ ፌዴሬሽን፣ የፕሮፌሽናል ፉትቦለርስ አሶሴሽን፣ የወጣቶች ስፖርት ማሰልጠኛ ማዕከላት፣ በጥቅሉ ወደ 15 ሚሊዮን የሚሆን ብር ለብሄራዊ ድጋፍ አሰባሳቢ ኮሚቴ አስረክቧል። አቅም ለሌላቸው ዜጎች የሚውሉ የምግብና የንጽህና ቁሳቁሶችንም በተመሳሳይ ገቢ ማድረግ ተችሏል። ለህብረተሰቡ እንዲሁም ለስፖርት ቤተሰቡ ግንዛቤ በማስጨበጥ ረገድም የተለያዩ ስራዎች ተከናውነዋል። ታዋቂና ተጽእኖ ፈጣሪ የስፖርት ሰዎችን በመጠቀም ተደራሽነታቸው ሰፊ በሆኑ የመገናኛ ብዙሃን ትምህርታዊ ማስታወቂያዎች እየተላለፉም ይገኛል። ሌሎች ስፖርተኞችም በተመሳሳይ በግላቸውና በቡድን በመሆን ግንዛቤ በማስጨበጥ ላይ ይገኛሉ። ከዚህ በተጓዳኝ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ቫይረሱን በመከላከል ረገድ ከፍተኛ ሚና የሚጫወት በመሆኑ ኮሚሽኑ በመገናኛ ብዙሃን ለማስተላለፍ እየተንቀሳቀሰ ይገኛል። የአትሌቲክስ ፌዴሬሽን ለአትሌቶች የሚሰጠው ምክርና አቅጣጫም ለዚህ ተጠቃሽ ነው። የኢትዮጵያ ወጣቶች ስፖርት አካዳሚንና የጥሩነሽ ዲባባ አትሌቲክስ ማሰልጠኛ ማዕከልን ጨምሮ በተለያዩ ክልሎች የሚገኙ የስልጠና ማዕከላትን ከቫይረሱ ጋር በሚደረገው ጦርነት በተፈለጉ ጊዜ እንዲያገለግሉ ዝግጁም ተደርጓል። ሌላው ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ይፋ የተደረገው የምገባ መርሃ ግብር ነው። በዚህም 300 ለሚሆኑ በአዲስ አበባ ስታዲየም ዙሪያና ሌሎች አካባቢዎች ለሚገኙ ጎዳና ተዳዳሪዎች ለአንድ ወር የሚቆይ የምገባ መርሃግብር ነው። በቀጣይም ኮሚሽኑ በምን መልኩ መደገፍ እንዳለበት ከስፖርት ማህበራትና ተጠሪ ከሆኑት ተቋማት ጋር ውይይት በማድረግ ጉድለት ያለባቸው ቦታዎችን በመለየት ድጋፉን የሚቀጥል መሆኑን ኮሚሽነሩ አረጋግጠዋል። አዲስ ዘመን ሚያዝያ 22/2012ብርሃን ፈይሳ
https://www.press.et/Ama/?p=31441
418
2ስፖርት
የጃፓን መንግሥትና የዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ውዝግብ
ስፖርት
April 25, 2020
14
የቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ ለአስራ ስድስት ወራት በመራዘሙ ምክንያት የአዘጋጅ አገሯ ጃፓን መንግሥትና የዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ገና ከጅምሩ በርካታ ውስብስብ ችግሮች ውስጥ መዘፈቃቸው ሲነገር ቆይቷል። የኦሊምፒክ ውድድሩ በዓለም ላይ ከፍተኛ ስጋት በፈጠረው የኮሮና ቫይረስ ስርጭት ጋር ተያይዞ ወደ ቀጣዩ ዓመት መራዘሙ ግድ መሆኑ ከታመነበት ወቅት አንስቶ አዘጋጆቹ በርካታ ፈተናዎችን መጋፈጣቸው የማይቀር ሆኗል። በተለይም ላለፉት ሰባት ዓመታት የበለጠ ዝግጅት ሲደረግበት የቆየው የኦሊምፒክ ውድድር መራዘሙ ከፍተኛ የገንዘብ ኪሳራ ማስከተሉ የአዘጋጆቹ ራስ ምታት እንደሚሆን ቀድሞም የታወቀ ነው። ይህ ከፍተኛ የገንዘብ ኪሳራ የጃፓን መንግሥትንም ይሁን ዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴን በእጅጉ ሊፈትን እንደሚችል በባለሙያዎች አስተያየት ሲሰጥበት የቆየ ሲሆን ሁለቱ አካላት ኪሳራውን ለማካካስ እንደሚደጋገፉና ሌሎች ባለድርሻ አካላትም ለዚህ እንዲዘጋጁ ጥሪ ሲያቀርቡ ቆይተዋል። የዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ እንዲህ ዓይነት ችግሮች ሲገጥሙት ትልቅ ተቋም እንደመሆኑ የመድህን ዋስትና እንዳለው ይታወቃል። አሁን የገጠመው ግን ካለው የመድህን ዋስትና አቅም በላይ በመሆኑ ነው እዚህ ችግር ውስጥ የተዘፈቀው። ስለዚህ የመድህን ዋስትናው በሕጉ መሠረት የሚሸፍነው ኪሳራ እንዳለ ሆኖ ተጨማሪ ኪሳራውን የሚያካክስበት አንድ ነገር መፈጠሩ የግድ ይሆናል። ይህንን ተጨማሪ ኪሳራ የጃፓን መንግሥት እንደሚሸፍን ጠቅላይ ሚኒስትር ሺንዞ አቤ ቀደም ሲል በተለያዩ አጋጣሚዎች መስማማታቸው ቢገለፅም አሁን የሃሳብ ለውጥ እንዳደረጉ የሚጠቁሙ መረጃዎች መውጣታቸውን ተከትሎ ውዝግቦች ተነስተዋል። የዓለም አቀፍ ኮሚቴው ፕሬዚዳንት ቶማስ ባኽ ሰሞኑን ከአንድ የጀርመን ጋዜጣ ጋር በነበራቸው ቃለምልልስ እንደጠቆሙት፣ ዓለም አቀፍ ኮሚቴው ከጃፓን መንግሥት ጋር በተስማማው መሠረት ለሚደርሰው በመቶ ሚሊዮን ዶላሮች የሚገመተውን ኪሳራ ለመሸፈን የራሱ ድርሻ አለው። ተጨማሪ የተባለውን ኪሳራ የመሸፈን ግዴታ ያለበት ደግሞ የጃፓን መንግሥት ነው። ይህን ስምምነት ሁለቱ አካላት እአአ 2013 ላይ እንዳደረጉ ቢገለፅም የጃፓን ካቢኔ አባላት ዋና ፀሐፊው ዮሺሂዴ ሱጋ ስምምነቱ እንዳልተደረገ አስተባብለዋል። ይህንንም ተከትሎ በሁለቱ አካላት መካከል ውዝግብ የተፈጠረ ሲሆን ተጨማሪ የተባለው ኪሳራ እስከ ሦስት ቢሊዮን ዶላር ሊደርስ እንደሚችል የጃፓኑ ክዮዶ ኒውስ ዘግቧል። የቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ አዘጋጅ ቃል አቀባይ ማሳ ታካያ በበኩላቸው የጃፓን መንግሥት፣ የኦሊምፒኩ አዘጋጅ ኮሚቴና ዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ውድድሩ በመራዘሙ ሊገጥሙ የሚችሉ እንቅፋቶችን በጋራ እንደሚወያዩና መፍትሄ እንደሚያስቀምጡ ተናግረዋል። ኦሊምፒኩ በመራዘሙ ብቻ የጃፓን መንግሥትን ጨምሮ በርካታ ባለድርሻ አካላት ከፍተኛ የገንዘብ ኪሳራ ውስጥ እንደሚገቡ ቀደም ሲል ተዘግቧል። የጃፓኑ ኦሊምፒክ አዘጋጅ ኮሚቴም ገና ከመጀመሪያው ከፍተኛ ኪሳራ ሊገጥም እንደሚችል መናገሩ ይታወሳል። ዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ለዚህ ኪሳራ ስጋት ሰላሳ ሦስቱንም ዓለም አቀፍ ፌዴሬሽኖች የሚመለከት መድህን የገባ ቢሆንም በቂ እንደማይሆን ታምኖበታል። ፕሬዚዳንቱ ቶማስ ባኽም ኦሊምፒኩ መራዘሙን በገለፁበት ወቅት ከባድ ኪሳራ እንደሚኖር በማመን ሁሉም ባለድርሻ አካላት መስዋዕትነት መክፈል እንደሚጠበቅባቸው ለመጠቆም ሞክረዋል። ከባዱን መስዋዕትነት ማን እንደሚከፍልና ጫናው በየትኛው ወገን ትከሻ ላይ ሊወድቅ እንደሚችል ግን ከመጀመሪያውም ግልፅ አልነበረም። አሁን ላይ ገና ኦሊምፒኩ አስራ አምስት ወራት ገደማ እየቀሩትም ሁለቱ አካላት ውድድሩ በመራዘሙ የገጠማቸውን ውስብስብ ችግሮች ከመፍታት ይልቅ ከገንዘብ ጋር በተያያዘ ባለው ጉዳይ ላይ መነታረ ክ ጀምረዋል። የተለያዩ ተንታኞች እንደሚናገሩት ከሆነ የኮሮና ቫይረስ ስርጭት በዓለም ላይ ሙሉ ለሙሉ እስከ ቀጣዩ ዓመት በቁጥጥር ስር ካልዋለ ኦሊምፒኩ በተራዘመበት 2021ም ላይካሄድ ይችላል። ከዚህም በዘለለ የመሰረዝ ዕድል ሊገጥመው ይችላል። ኦሊምፒኩ በመራዘሙ ብቻ በሚገጥመው ኪሳራ ትልቅ ውዝግብ የሚነሳ ከሆነ ከነጭራሹ ከተሰረዘ የሚገጥመው ኪሳራም በቀላሉ የሚሰላ እንደማይሆን ይታመናል። አዲስ ዘመን ሚያዝያ 17 / 2012 ቦጋለ አበበ
https://www.press.et/Ama/?p=31115
450
2ስፖርት
የአውሮፓ አትሌቲክስ ቻምፒዮናና ዳይመንድ ሊግ
ስፖርት
April 26, 2020
37
በርካታ ዓለም አቀፍ ውድድሮች በተሰረዙበትና በተራዘሙበት በዚህ ወቅት እንደሚካሄድ ተስፋ ተጥሎበት የነበረው የአውሮፓ አትሌቲክስ ቻምፒዮና ከመሰረዝ እንዳልዳነ ታውቋል፡፡ በፈረንሳይ መዲና ፓሪስ እኤአ ከሐምሌ 25 እስከ 30 በቻርሌቲ ስቴድየም ሊካሄድ ታስቦ የነበረው ቻምፒዮና በኮሮና ቫይረስ ስጋት እንደተሰረዘ አዘጋጆቹ ባሳለፍነው ሳምንት መጨረሻ አሳውቀዋል፡፡ ውድድሩን በተያዘለት ጊዜ ለማካሄድ የተቻለው ሁሉ ጥረት ቢደረግም በአሁኑ ወቅት ከኮሮና ቫይረስ ስርጭት ጋር በተያያዘ በፈረንሳይ መሰብሰብ የተከለከለ በመሆኑ የውድድር አዘጋጅ ኮሚቴው፣ የአውሮፓ አትሌቲክስ ማህበርና የፈረንሳይ አትሌቲክስ ባለስልጣናት ውድድሩን ለመሰረዝ እንደተገደዱ አሳውቀዋል:: እዚህ ውሳኔ ላይ ለመድረስም የፈረንሳይ የጤና ኮሚሽን በአትሌቶችና በተመልካቾች ላይ ሊደርስ የሚችለውን አደጋ ከግምት ያስገባ ጥናት ማድረጋቸው ታውቋል:: የውድድሩ አዘጋጅ ኮሚቴ ፕሬዚዳንት ጂን ጋርሺያ ለመገናኛ ብዙኃን እንደገለፁት፣ ውድድሩን ለማካሄድ እስከ መጨረሻው ሰዓት ድረስ ጥረት የተደረገ ቢሆንም ሳይሳካ ቀርቷል:: «በርካታ ውድድሮች በተሰረዙበት ሰዓት ለአትሌቶች በውድድር ዓመቱ መጨረሻ ሰዓት አንድ የሚያስደስት ነገር ለማድረግ አስበን ነበር» ያሉት ፕሬዚዳንቱ ውድድሩን ከቫይረሱ ስጋት ነፃ ለማድረግ የስቴድየሞች ተመልካች የመያዝ አቅም በግማሽ እንዲያንስ ለማድረግ ጥረት መደረጉን አብራርተዋል፡፡ ውድድሩን ከመሰረዝ ይልቅ ወደ ቀጣዩ ዓመት እንደ አማራጭ ታስቦ እንደነበረ የተናገሩት ግራሺያ የቫይረሱ ስጭት ምናልባት እስከ ቀጣይ ዓመትም ካልተገታ ማራዘሙ አማራጭ እንደማይሆን ታምኖበት ውሳኔ ላይ እንደደረሰ ገልፀዋል፡፡ ለውድድሩ ከአስራ ስምንት ሚሊዮን ዶላር በላይ በጀት የተያዘ ሲሆን ሊገጥም የሚችለውን ኪሳራ ለማዳን የአገሪቱ መንግሥት ዋስትና እንደሚሰጥ ታውቋል:: የአውሮፓ አትሌቲክስ ማህበር ሥራ አስፈፃሚ ቦርድ ከወር በፊት ውድድሩ በተያዘለት ጊዜ መካሄድ የሚችልበትን መንገድ ማጥናት እንደሚገባ የጠቆመ ሲሆን ውድድሩ በተያዘለት ጊዜ ካልተካሄደ የሚራዘምበት ዕድል እንዲፈጠር ፍላጎት ነበረው፡፡ ያም ሆኖ አዘጋጆቹ ከማራዘም ይልቅ ለመሰረዝ ተገደዋል፡፡ በዚሁ በአውሮፓ በርካታ ከተሞች ይካሄዱ የነበሩ የዳይመንድ ሊግ ውድድሮች በተያዘላቸው መርሃግብር መሠረት እንደማይካሄዱ የተገለጸ ሲሆን የሚካሄዱበት አዲስ መርሃግብር ከዓለም አትሌቲክስ ጋር በመወያየት እንደሚገለፅ ተጠቁሟል፡፡ ከግንቦት መጨረሻ አንስቶ በአስራ አራት የተለያዩ የዓለማችን ከተሞች የሚካሄዱት የዳይመንድ ሊግ ውድድሮች የፓሪስና የዩጂን ዳይመንድ ሊጎችን ጨምሮ በርካቶቹ መራዘማቸው ታውቋል፡፡ በዚህ ሁኔታ ውስጥ በኖርዌይ ኦስሎ የሚካሄደው የዳይመንድ ሊግ ውድድር ቢራዘምም አዘጋጆቹ በምትኩ አዲስ የውድድር አማራጭ ማቅረባቸው አነጋጋሪ ሆኗል፡፡ «የማይቻል» የተባለው ውድድር በኦስሎ አዘጋጆች ሲታቀድ በኤግዚቢሽን መልኩ በዝግ ስቴድየም እንደሚሆን ተገልጿል፡፡ ውድድሩን ማህበራዊ ርቀትን በመጠበቅና የኮሮና ቫይረስ የሚፈልገውን ጥንቃቄ ተግባራዊ በሚያደርግ መልኩ ለማካሄድ የታሰበ ሲሆን በኖርዌያን የሜዳ ተግባራት አትሌቶች መካከል የዓለም ክብረወሰን የሚሻሻልበት ይሆናል ተብሏል፡፡ በተለይም ኖርዌያዊው የርዝመት ዘላይ ካርልስተን ዋርሆልም እንዲሁም የምርኩዝ ዘላዮቹ ሞንዶ ዱፕሌንቲስና ሪናውድ ላቪሌኒ የሚያደርጉት ፉክክር ተጠባቂ እንደሚሆን ተገምቷል፡፡ ለአንድ ሰዓት ያህል የሚካሄደው ውድድር በኖርዌይ የሕዝብ ቴሌቪዥን ጣቢያ በቀጥታ እንደሚተላለፍ ተጠቁሟል፡፡ ይህ የኖርዌይ ውሳኔ ከኮሮና ቫይረስ ስጋት ጋር ተያይዞ ለብዙዎች የማይመስል ቢሆንም የዓለም አትሌቲክስ ፕሬዚዳንት ሴባስቲያን ኮ ጭምር አድናቆታቸውን ገልጸውለታል፡፡ አዲስ ዘመን ሚያዝያ 18/2012ቦጋለ አበበ
https://www.press.et/Ama/?p=31149
374
2ስፖርት
ማዕድ የማጋራት ብሄራዊ ጥሪና የስፖርቱ ማኅበረሰቡ ምላሽ
ስፖርት
April 28, 2020
22
ኃያላኑን አገሮች ጨምሮ የዓለም ሳይንቲስቶች ከሁሉም በፊት ትኩረታቸውን በአንድ ነገር ካደረጉ አራት ወራት አለፈ።በቻይና ውኃን ግዛት በፈረንጆቹ አዲስ ዓመት መባቻ ለተከሰተውና በምህፃረ ቃሉ ኮቪዲ 19 የሚል መጠሪያ ላገኘው ኮሮና ቫይረስ።ወረርሽኙ ዘር፣ ቀለም፣ ትንሽና ትልቅ ሳይለይ ሁሉንም በማጥቃት የአለም ህዝብ በፍርሃት አቁማዳ ውስጥ እንዲገባ ካደረገ አራት ወራቶች አልፈዋል። በእነዚህ ወራት የወረርሽኙን ስርጭት ለመግታት የቻለ ምድራዊ ኃይል አልተገኘም። የአለም ሀያላን አገራት ከምድር ተሻግረን ጨረቃ ላይ እንወጣለን ሲሉ እንዳልተመፃደቁ፤ የኮሮና ወረርሽኝ ከቤታቸው ራሱ እንዳይወጡ አደረጋቸው። ሀገራቱ የወረርሽኙን ስርጭት በቶሎ የመቆጣጠር አቅም በማጣታቸው በአራት ወራት ብቻ ከሁለት መቶ ሺህ ሰዎች በላይ ህይወት ተቀጠፈ። የአለም ህዝብን እንደ ቅጠል ከማርገፍ በተጨማሪ በተለያዩ የንግድ ተቋማት ላይ ይህ ቀረሽ የማይባል ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ቀውስ አስከትሏል። የኮቪድ 19 ስርጭት በማይታመን ፍጥነት ከመጨመር በተጓዳኝ መድሃኒት አልባ በመሆኑ ሀገራት ትኩረታቸውን ሁሉ ቅድመ መከላከል ላይ መስራትን መርጠዋል። ኢትዮጵያም የአለም ሀገራትን በአንድ ልብ እያስጨነቀ ካለውን ጠላት ህዝቦቿን ለመታደግ በብሄራዊ ደረጃ መከላከልና መቆጣጠር የሚያስችሉ ሥርዓቶችን በመዘርጋት እየተንቀሳቀሰች ትገኛለች። መንግስት የወረርሽኙ ባህሪ ከሀገሪቱ የኢኮኖሚ፣ ማህበራዊ አቋም አኳያ ስርጭቱ ከፍተኛ ሊሆን እንደሚቸል በመገንዘብ ለህዝቡ ጥሪ በማድረግ የጋራ ተሳትፎን ያማከለ እንቅስቃሴ ሲደረግ ቆይቷል። በዚህ ተግባር ላይ የተለያዩ አካላት ተሳትፏቸውን ባሳዩበት ተግባር ላይ በስፖርቱ ዘርፍ ባሉ አካላት በኩል አፋጣኝ ምላሽ በመስጠት የነበራቸው ተሳትፎ ትልቅ እንደነበር ለመታዘብ ተችሏል። የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ መከሰት ከታወቀበት ከመጋቢት መጀመሪያ ሳምንት ጀምሮ በቡድንም ሆነ በተናጠል ለወረርሽኙ መከላከያ የሚውል የገንዘብ ድጋፍ በማሰባሰብ ነበር ይሄንኑ ያስመሰከሩት። የስፖርቱን ተቋማት ከሚመሩት አካላት ጀምሮ በየደረጃው የሚገኙ መንግሥታዊና መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ከወራት በፊት መንግስት ላቀረበው ጥሪ አፋጣኝ ምላሽ በመስጠት ያሳዩት ተሳትፎ ዳግም ማሳየተቻው ተነግሯል። የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን በጋራ ለማሸነፍ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ጠቅላይ ሚኒስቴር ዶክተር አብይ አህመድ ከሳምንታት በፊት የማዕድ ማጋራት ብሔራዊ ጥሪን አድርገው ነበር። የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ስፖርት ኮሚሽን ከኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን፣ ከኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን እና ከቢ. ጂ አይ ኢትዮጵያ በጋራ በመሆን በሳምንቱ መጨረሻ ላይ አንድ መርሃ ግብር ይፋ አድርገዋል። የስፖርቱ ተቋማት በኩል ይፋ የተደረገው መርሃ ግብር ጠቅላይ ሚኒስቴር አብይ አህመድ ያቀረቡትን «የማዕድ ማጋራት ብሄራዊ ጥሪ»ን እውን ያደርጋል ተብሏል። መጋቢት መጨረሻ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ “ማዕድ ማጋራት” ሲሉ በሰየሙት መንገድ መንግስት የኮሮና ወረርሽኝ የከፋ ጉዳት ቢያደርስ በየቤቱ ምግብ ለማድረስ አቅሙም ሆነ መንገዱ ስለማይኖረው፤ ሰዎች በምግብ እጦት እንዳይጎዱ አንድ ቤተሰብ በቀን አንድ ምግብ ሌላ ቤተሰብ ለማቅረብ ዝግጅት እንዲደረግ እና እንደቤተሰብ ምክክር እንዲደረግ ሲሉ ነበር ያሳሰቡት። የጠቅላይ ሚኒስቴሩን ጥሪ ተከትሎ በርካቶቸ ምላሽ ሰጥተዋል። የስፖርት ተቋማቱ ከአጋር ድርጅቶች ጋር በመቀናጀት ሰሞኑን ይፋ ያደረጉት የምገባ መርሃ ግብር ይሄንኑ መሰረት አድርጓል። በዚህ መርሃ ግብር 300 የጎዳና ተዳዳሪዎችን ለአንድ ወር ያህል እንደሚመግብ ተነግሯል። የስፖርቱ ን ማኅበረሰብ ህዝባዊነት የሚያረጋግጥ መሆኑ የተነገረለት መርሃ ግበር ሚያዝያ 17 ቀን 2012 ዓ.ም በአዲስ አበባ ስታዲየም ሲጀመር የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ኤሊያስ ሽኩር እንደተናገሩት፤ የኮሮና ቫይረስ ወደ ሀገራችን ከገባ ጀምሮ ወረርሽኙን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የስፖርቱ መንግስታዊ እና ህዝባዊ አደረጃጀቶች፣ ታዋቂ አትሌቶች፣ የደጋፊ ማህበራት፣ በአጠቃላይ የስፖርት ቤተሰቡ ህብረተሰቡን በማንቃት እና ኢኮኖሚያዊ ጫናውን ለመቋቋም የሚያግዝ የገንዘብ ድጋፍ በማድረግ ማህበራዊ ኃላፊነታቸውን መወጣታቸውን አስታውሰዋል። የስፖርቱ ማኅበረሰብ ድጋፍ ተጠናክሮ የሚቀጥልና የምገባ መርሃ ግብሩ መጀመር ለዚሁ ማሳያ ይሆናል ብለዋል። የጎዳና ላይ የሚገኙ ወገኖቻችንን በተወሰነ መልኩ ለማገዝ አንድ ወር የሚቆይ የምገባ መርሃ ግብሩ ይሄንኑ ሚና መሰረት ባደረገ መልኩ መጀመሩን የተናገሩት አቶ ኤልያስ፤ በስታዲየም ዙሪያ መርሃ ግብሩ እንዲደረግ የተመረጠበትን ምክንያት መኖሩን አመልክተዋል።« በወቅታዊ የኮሮና ወረርሽኝ ምክንያት ስርጭቱን ለመቆጣጠር ሲባል በተለይ ስታዲየም ዙሪያ የሚገኙ ባር እና ሬስቶራንቶች መዘጋታቸው እና በአካባቢው ያለው እንቅስቃሴ መቆሙ ይታወቃል። ሬስቶራንቶች መዘጋታቸውን ተከትሎ ከሬስቶራንቶች ተመላሽ የሚሆኑ ምግቦችን ይጠቀሙ የነበሩ የጎዳና ተዳዳሪዎችም ሆነ በስታዲየም አካባቢ የተለያዩ ነገሮችን በመሸጥ ይተዳደሩ የነበሩ የህብረተሰብ ክፍሎች ለከፋ ችግር ተጋልጠዋል። በመሆኑም ጊዜው የከፋ ችግር ላጋጠማቸው የህብረተሰብ ክፍሎች እጃችን የምንዘረጋበት፤ የጋራ መከራችንን በመተጋገዝ የምናልፍበት መሆኑን በማመን እና ማህበራዊ ኃላፊነታቸውን ለመወጣት ነው »ሲሉ አብራርተዋል። አቶ ኤልያስ በመጨረሻ የተጀመረው ተግባር የሚቋረጡ ሳይሆን በቀጣይም እነዚህ ወገኖቻችን በዘላቂነት ህይወታቸውን ሊመሩበት በሚችሉ ጉዳዮች ላይ የስፖርት ቤተሰቡ በሙሉ አቅሙ የሚደግፍ መሆኑን አመልክተዋል። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን፣ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን እና የቢጂ አይ ኢትዮጵያ አመራሮች በጋራ በመሆን ባስተላለፉት መልዕክት ደግሞ፤ የምገባ መርሃ ግብሩ በቀጣይ ተጠናክሮ እንዲቀጥል አስፈላጊውን ሁሉ እንደሚያደርጉ አስታውቀዋል። «በአሁኑ ሰዓት የገጠመንን ፈተና ለማሸነፍ ለመንግስት ብቻ የሚተው ባለመሆኑ ሁሉም በአቅሙ ማህበራዊ ኃላፊነቱን ሊወጣ ይገባል »ያሉት ደግሞ፤ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ የሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ክብርት ዶክተር ኤርጎጌ ተስፋዬ ናቸው። ሚኒስትሯ በሀገር አቀፍ ደረጃ የተጀመረው የምገባ ፕሮግራም ለሌሎች ድርጅቶች እና ባለሀብቶች አርዓያነት ያለው ተግባር መሆኑም ገልጸዋል። በተለይም ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ያቀረቡትን የማዕድ ማጋራት ብሔራዊ ጥሪ ተከትሎ የስፖርት ቤተሰቡ እና አመራሩ በዚህ በጎ ተግባር መሳተፉ ሊያስመሰግነው እንደሚገባ አመልክተዋል። የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ስፖርት ኮሚሽን ከኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን፣ ከኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን እና ከቢ. ጂ አይ ኢትዮጵያ በጋራ በመሆን ሚያዚያ 17 ቀን 2012 ዓ.ም በአዲስ አበባ ስታዲየም ይፋ ያደረጉት መርሃ ግብር ለአንድ ወር ያህል የሚዘልቅ ይሆናል። በመርሃ ግብሩ 300 ሰዎች ተጠቃሚ የሚሆኒ ሲሆን ተመጋቢዎቹ በቀን 2 ጊዜ እንዲመገቡ ይደረጋል። የተጠቃሚዎች ዝርዝር በቂርቆስ ክፍለ ከተማ የወረዳ 7 የሠራተኛ እና ማህበራዊ ጉዳይ ጽህፈት ቤት አማካኝነት ተለይተው እንዲቀርቡ የተደረጉ ናቸው። ለምገባ ፕሮግራሙ ከ800 ሺ ብር በላይ ወጪ የሚደረግ መሆኑ ታውቋል።አዲስ ዘመን ሚያዝያ 20/2012 ዳንኤል ዘነበ
https://www.press.et/Ama/?p=31281
743
2ስፖርት
የመሬትና የብድር አጠቃቀም ችግር በወጣቶች የስራ ዕድል ፈጠራ ላይ ጫና ማሳደሩ ተገለጸ
ሀገር አቀፍ ዜና
December 31, 2020
17
ዋቅሹም ፍቃዱአዲስ አበባ፡- የመሬትና የብድር አጠቃቀም ችግር በወጣቶች የስራ ዕድል ፈጠራ ላይ ጫና ማሳደሩን የአሶሳ ከተማ ከንቲባ አስታወቁ። በበጀት ዓመቱ ለ1ሺህ 117 ወጣቶች የስራ ዕድል ለመፍጠር አቅዶ በሩብ ዓመቱ 543 ወጣቶች የስራ ዕድል መፍጠሩን ገለጹ ።የከተማው ከንቲባ አቶ ዑመር መሀመድ በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንዳስታወቁት ፣ አሶሳ ከተማ ከሁሉም የአገሪቱ ክፍል የሚመጡ የብሔር ብሔረሰቦች መናኸሪያ በመሆኗ በርካታ ወጣቶች ስራ ፍለጋ ወደ ከተማይቱ ይመጣሉ። የከተማ መስተዳድርም ያለምንም አድሎ አቅም በፈቀደ መጠን የስራ ዕድል ተጠቃሚ እያደረገ ይገኛል። ለወጣቶቹ የብድር አቅርቦት ሲመቻች አንዳንድ ወጣቶች ሰርተው ከመለወጥ ይልቅ ያገኙትን ገንዘብ ይዘው የመሰወር እንዲሁም የመጥፋት ሁኔታ ያሳያሉ ያሉት ከንቲባው ፣ በተመሳሳይ መልኩ አንዳንዶቹም ምንም እንኳ እንደሌሎቹ ገንዘብ ይዘው ባይጠፉም በአግባቡ ሰርተው ከተለወጡ በኋላ የተበደሩትን ገንዘብ ሳይመልሱ ተጨማሪ ብር የመጠየቅ ሁኔታዎች አሉ ብለዋል ። ይህ ደግሞ ሌሎች አዳዲስ ስራ ፈላጊዎች በአግባቡ እንዳይስተናገዱ አሉታዊ ተጽዕኖ እያደረገ መሆኑን አመልክተዋል። ከተማ መስተዳድሩ ለበርካታ ወጣቶች የስራ ዕድል ለመፍጠር ላይ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ቢሆንም ፣በከተማው የስራ ቦታ እጥረት መኖሩን አመልክተዋል ። ያለውም ቢሆን ለህገ ወጥ ወረራ የተጋለጠ በመሆኑ ችግሩን ለማቃለል እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል ። የብድር አቅርቦትም ቢሆን ምናልባት ከአገራችን ነባራዊ ሁኔታ ጋር ተያይዘው እጥረት እንዳለም የጠቆሙት ከንቲባው ፣ በቀጣዩ ከፌዴራልም ሆነ ከክልሉ ለከተማይቱ ወጣቶች የሚመደበው በጀት በአግባቡ ስራ ላይ እንዲውል ልዩ ድጋፍና ክትትል እንደሚደረግም አስረድተዋል። በከተማው የመሬት ወረራ ትልቁ ራስ ምታት እንደሆነ ጠቁመው ፣ ወጣቶች የተሰጣቸውን የስራ ቦታ በአግባቡ ሰርተውበት ከተለወጡ በኋላ ለቀጣዩ ስራ ፈላጊ ከመልቀቅ ይልቅ አንዳንድ ወጣቶች የወሰዱትን መሬት ለሌሎች አሳልፈው እንደሚሸጡና የተሸጠው መሬትም ለስራ አጥ ወጣቶች የስራ ዕድል ከመፍጠር ይልቅ ለህገ ወጥ መኖሪያ ቤት ግንባታ እንደሚውል ከተማ መስተዳድሩ ባደረገው ክትትልና ግምገማ እንደ ደረሰበት ከንቲባው አክለው ገልጸዋል። እንደ እርሳቸው ገለጻ አሶሳ ከተማ ለስራም ሆነ ለኑሮ ምቹ በመሆኗ በተለይ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በርካታ አዳዲስ ፊቶችን፣ በተለይ ወጣቶችን በከተማይቱ ማየት እየበዛ መጥቷል። ወደ ከተማው የሚመጡ ሰዎች አሶሳ አገራቸው እንደሆነች በማመንና በመተማመን ስለሚመጡ የከተማ አስተዳደሩም እነዚህ ወጣቶች የስራ ዕድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ አቅዶ እየሰራ ይገኛል። እስካሁንም የስራ እድል ከተፈጠረላቸው ወጣቶች መካከልም ግማሾቹ ከሌሎች አከባቢ የመጡ ናቸዉ። አቶ ዑመር ከብድር አጠቃቀም ጋር የተስተዋሉ ችግሮችን ለመፍታት ለስራ ቁርጠኛ የሆኑና ሰርተው ለመለወጥ ጽኑ ዓላማ ያላቸውን ወጣቶች በጥንቃቄ እንዲመለመሉ በማድረግ በዋስ ተጠቃሚ ለማድረግ እንዲሰሩ ጠቁመው፣ በመሬት አጠቃቀም ዙሪያም ጠንካራ የአሰራር ስርዓት መዘርጋት ችግሩን ለመፍታት እየተንቀሳቀሱ መሆኑን አመልክተዋል ። አዲስ ዘመን ታህሳስ 22/2013
https://www.press.et/Ama/?p=38531
345
0ሀገር አቀፍ ዜና
በኦሊምፒክ መራዘም የ3ሺ ሜትር መሰናክል አትሌቶች ምን አሉ?
ስፖርት
April 27, 2020
18
የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ 19) የዓለም ስጋት ከመሆኑ አስቀድሞ በስፖርቱ ዓለም ተጠባቂ ከሆኑ ጉዳዮች መካከል አንዱ ኦሊምፒክ ነበር። ነገር ግን ሊካሄድ ወራት ብቻ በቀሩትና ሀገራትም ብሔራዊ ቡድናቸውን ማዘጋጀት በጀመሩበት ወቅት መራዘሙ ተሰማ። አጋጣሚውም በተለያዩ አትሌቶች ዘንድ ሁለት ዓይነት ስሜት የፈጠረ ሆኗል። የመጀመሪያዎቹ አትሌቶች የጊዜውን መርዘም ተጠቅመው በ2021ዱ ኦሊምፒክ በተሻለ ብቃት ለመገኘት ዕድል ያላቸው ሲሆኑ፣ ሁለተኛዎቹ ደግሞ በጥሩ አቋም ላይ የሚገኙና ምናልባትም መራዘሙ እክል ሊያስከትልባቸው የሚችሉ ናቸው። ኢትዮጵያም የአትሌቲክስ ቡድኗን መርጣ ልምምድ ለመጀመር ዝግጅት በማጠናቀቅ ላይ በነበረችበት ወቅት ነው የቶኪዮ ኦሊምፒክ በመራዘሙ አትሌቶች እንዲበተኑ የተደረገው። ከተበተነው ብሔራዊ ቡድን አባላት መካከል የ3ሺ ሜትር መሰናክል አንዱ ሲሆን፤ ይህ ቡድን በዓለም የቤት ውስጥ ቻምፒዮና ውጤታማነቱን ያስመሰከረ ነበር። በኦሊምፒኩ ለአሸናፊነት የሚጠበቀውና ከፍተኛ ግምት ያገኘው ቡድኑና አባላቱ ምን ዓይነት ዝግጅት ሲያደርጉ ቆዩ፣ መራዘሙ ምን አስከተለባቸው እንዲሁም በዚህ ወቅት በምን ሁኔታ ላይ ይገኛሉ በሚለው ጉዳይ ላይ የቡድኑ አባላት የሚናገሩት አላቸው። ለቡድኑ ከተመረጡትና ባለፈው የፈረንጆቹ ዓመት በምርጥ አቋም ላይ ከነበሩአትሌቶች መካከል አንዱ የዳይመንድ ሊግ አሸናፊው ጌትነት ዋለ ይጠቀሳል። አትሌቱ ኦሊምፒክን ጨምሮ በግሉ ይሳተፍባቸው ለነበሩ ውድድሮች ከአሰልጣኙ ጋር በመሆን ጠንካራ ቅድመ ዝግጅት ሲያደርግ መቆየቱን ይገልጻል። በዚህ ሁኔታ ላይ እያለ ኦሊምፒኩ መራዘሙ ከጥቅሙ ይልቅ ጉዳቱ ጎልቶ የሚታየው ጌትነት፤ «አትሌት ባለበት አቋም መጠቀም የሚገባው በወቅቱ ነው» የሚል አመለካከት አለው። የየትኛውም አትሌት አላማ የሆነውን በኦሊምፒክ ሀገርን ወክሎ ድል ማስመዝገብ ካለመቻሉም በላይ ከሚወዱት ሥራቸውም መነጠል ያስከፋል። ነገር ግን ቫይረሱ በመላው ዓለም ሕዝብ ላይ ስጋትና አደጋ በመሆኑ፤ ወቅቱ ይለፍ እንጂ በርትቶ በመስራት ብቃትን መመለስ እንደሚቻል ያምናል። አቋሙ ባለበት እንዲቀጥልም በቤቱ ውስጥ ከቀደመው ጊዜ ያነሰ ልምምድ እየሰራ ጊዜውን በማሳለፍ ላይ ይገኛል። እንደ አጋጣሚ ሆኖ አሰልጣኙ እርሱ በሚኖርበት አቅራቢያ የሚኖር በመሆኑ አልፎ አልፎ በርቀት እየተገናኙ መመሪያዎችን የሚቀበልና በስልክም መረጃ እንደሚለዋወጡ ይጠቁማል። ከዚህ ባለፈ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በመገናኛ ብዙኃን ታግዞ በባለሙያዎች የሚሰጠውን መረጃም ይከታተላል። ሌሎች አትሌቶችም በዚህ መልኩ ከቤታቸው ሳይርቁና ሰዎች በብዛት ባሉባቸው ስፍራዎች ባለመገኘት በአቋማቸው ለመቀጠል እንቅስቃሴ እንዲያደርጉም ጥሪውን ያቀርባል። ኦሊምፒክ በጉጉት ይጠብቀው የነበረውድድርና ከአሰልጣኙም ጋር ልዩ ዝግጅት ሲያደርግ የቆየ መሆኑን የሚያስታውሰው ደግሞ በቅርቡ ከኢትዮጵያ ወጣቶች ስፖርት አካዳሚ ሥልጠናውን ያጠናቀቀውና ሌላኛው የ3ሺ ሜትር መሰናክል ወጣት አትሌት አብረሃም ስሜ ነው። በዚህ ሁኔታ ላይ ሳሉ ይህ ቫይረስ መከሰቱ ቢያሳዝንም በዓለም የመጣ ነገር በመሆኑ የግድ ራስን ከቡድን ልምምድ ማራቅ ተገቢ ነው። የኦሊምፒክ መራዘም አማራጭ የሌለው ጉዳይ ቢሆንም እርሱን በመሰሉና በመልካም አቋም ላይ ለነበሩ አትሌቶች ጉዳት አለው። ይህ ቫይረስ እስኪያልፍ ድረስም ጊዜውን እንደ ማገገሚያ በመጠቀም በአቋሙ ለመቆየት በቤቱ እንቅስቃሴ ማድረግ አላቋረጠም። እንደ ቡድን አጋሩ ጌትነት አብርሃምም የሚኖረው ከአሰልጣኙ ጋር በቅርብ ርቀት አካባቢ በመሆኑ በስልክ ከመገናኘት ባለፈ በአካል ተገናኝቶ ለመወያየትም ዕድል ሰጥቶታል። በአሰልጣኞች እንዲሁም በጤና ባለሙያዎች የሚሰጠውን መመሪያ በጥንቃቄ በመተግበርም እንቅስቃሴውን ቀጥሏል። በየማዕከላቱ የሚሰለጥኑ ታዳጊዎችን ጨምሮ በየክለቡ ያሉ አትሌቶች ተበትነው በየክልሉ ተመልሰዋል። በመሆኑም ጊዜው እስኪያልፍ ድረስ ከእንቅስቃሴ ሳይርቁ እንዲቆዩ መልዕክቱን ያስተላልፋል። በብሔራዊ ቡድን የ3ሺ ሜትር መሰናክል ዋና አሰልጣኙ ተሾመ ከበደ በብሔራዊ ቡድን ከተካተቱ አትሌቶች አብዛኛዎቹ ከእርሱ ጋር የነበሩ በመሆኑ ወጥ የሆነ ልምምድ ላይ እንደነበሩ ያስታውሳል። ከአትሌቶቹ ጋር በመሆን በቤት ውስጥ ቻምፒዮና ዝግጅት ሲያደርጉ ቆይተው ለዓመታዊው ዳይመንድ ሊግ ውድድር እንቅስቃሴ ሲያደርጉ የቆዩ ሲሆን፤ የኦሊምፒክ ሚኒማ ለማሟላት ሲሰሩም ነበር። ነገር ግን የኦሊምፒክ መራዘምን ተከትሎ ቡድኑ በመበተኑ አትሌቶች ተፈጥሯዊ የበሽታ መከላከል አቅማቸውን ሊያጎለብት የሚችል ቀላል እንቅስቃሴዎችን እየሰሩ እንዲቆዩ ተደርጓል። ቀድሞ ለአምስት ቀናት ያደርጉ የነበረውን መደበኛ ስልጠና እና ጫና በመቀነስም ክብደት እንዳይጨምሩ ቀላል እንቅስቃሴዎችን በየቤታቸው ይሰራሉ። አሰልጣኞችም በስልክና በሌሎች መንገዶች ከአትሌቶቻቸው ጋር በመገናኘት መስራት ያለባቸውን እየነገሯቸው መሆኑንም ይጠቁማል። የኦሊምፒኩ መራዘም እንደ ሀገር የሚያስከትለው ጉዳት መኖሩን የሚያነሳው አሰልጣኙ፤ እርሱ በሚያሰለጥንበት ርቀት ደግሞ አትሌቶች በጥሩ አቋም ላይ በመቆየታቸው ለኦሊምፒኩም የማሸነፍ ዕድል ነበራቸው። በአንጻሩ መራዘሙ የሚጠቅመው በጉዳት ላይ የቆዩና በወቅቱ በጥሩ አቋም ላይ ያልነበሩ አትሌቶችን ነው። ሁኔታውን ተጠቅመው አቅማቸውን አጎልብተው በመመለስ ብርቱ ተፎካካሪ የመሆን ዕድል ያላቸው በርካቶች እንደመሆናቸው ይህ ጊዜ ሲያልፍ ጠንካራ ሥራ ከአትሌቶች የሚጠበቅ መሆኑንም አሰልጣኙ ያመላክታል። በመጨረሻም አሰልጣኙ አትሌቶች ራሳቸውን ከዚህ ቫይረስ እንዲጠብቁ መልዕክቱን አስተላልፏል። ራሳቸውን ከበሽታ ሊከላከል የሚችልና ያሉበትን አቋም የሚጠብቅ እንቅስቃሴ ከማድረግ በዘለለ ራሳቸውን በጤና መጠበቅ እንዳለባቸውም ምክሩን ይለግሳል። አዲስ ዘመን ሚያዝያ 19/2012
https://www.press.et/Ama/?p=31209
588
2ስፖርት
የሞዴል ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ኤግዚቢሽንና ባዛር የ4 ሚሊዮን ብር ሽያጭና የገበያ ትስስር እንደሚፈጠር ተገለጸ
ሀገር አቀፍ ዜና
December 31, 2020
12
አዲሱ ገረመው አዲስ አበባ፡- የ2013 በጀት ዓመት የ4 ሚሊዮን ብር ሽያጭና የገበያ ትስስር እንደሚፈጥር የፌዴራል የከተሞች የስራ ዕድል ፈጠራና የምግብ ዋስትና ኤጀንሲ አስታወቀ። ከተሳታፊዎች ውስጥ 50 በመቶዎቹ ሴቶች መሆናቸው ተጠቆመ ። ኤጀንሲው ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው፤ በ2013 በጀት አመት አንደኛው ዙር የሞዴል ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ሀገር አቀፍ ኤግዚቢሽንና ባዛር ‹‹ዘላቂነት ያለው የገበያ ትስስር ለስራ ዕድል ፈጠራና ለኢንተርፕራይዞች ልማት መሰረት ነው ›› በሚል መሪ ቃል ከታህሳስ 22 እስከ ታህሳስ 28 ቀን 2013 ዓ.ም በጀሞ አንድ አደባባይ ትራፊክ መብራት ፊትለፊት ለሰባት ተከታታይ ቀናት የሚካሄድ ይሆናል። የ4 ሚሊዮን ብር ሽያጭና የገበያ ትስስር እንዲሚፈጥርም ይጠበቃል። በኤግዚቢሽንና ባዛሩ ላይ ከሁሉም ክልሎችና ከተሞች የተውጣጡ 202 የጥቃቅን እና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች 10 አነስተኛና መካከለኛ ኢንዱስትሪዎች የሚሳተፉ ሲሆን፤ ሴቶች 50 በመቶ እና አካል ጉዳተኛ ሦስት በመቶ በማሳተፍ ምርትና አገልግሎታቸው ከ20ሺ በላይ በሚሆን ተጠቃሚ የህብረተሰብ ክፍል እንዲጎበኝ ይደረጋል ብሏል ። ባዛሩ ከተለያዩ ክልሎችና አካባቢዎች የተሰባሰቡና በልዩ ልዩ ዘርፎች የተሰማሩ ብቁና ተወዳዳሪ ኢንተርፕራይዞችንና አንቀሳቃሾችን የሚያሳትፍ ሲሆን፤ በአንድ ማዕከል በማገናኘት በሚፈጠረው ትውውቅና የልምድ ልውውጥ በመካከላቸው ጤናማ የውድድር ስሜት ለማቀጣጠል እንደሚያስችልም “ኤጀንሲው አመልክቷል ። ባህላዊና ዘመናዊ የጨርቃጨርቅና አልባሳት ምርት ውጤቶች፣ ባህላዊና ዘመናዊ የቆዳ አልባሳትና የቆዳ ምርት ውጤቶች፣ ባህላዊ የዕደ-ጥበባትና ቅርጻ-ቅርጽ ሥራዎችና ውጤቶች፣ የብረታብረት፣ የእንጨት ሥራና የኢንጅነሪንግ ስራዎችና ውጤቶች፣ የአግሮ-ፕሮሰሲንግ ምርቶች እና የከተማ ግብርና ውጤቶች፣ የቴክኖሎጂ ውጤቶችና የፈጠራ ስራዎች፣ ፈሳሽ ሳሙና፣አልኮል፣ሳኒታይዘር፣ የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ጭንብል/ማስኮች/፣ እና ሌሎችም ምርቶች በኤግዚቢሽንና ባዛሩ እንደሚቀርቡ አስታውቋል። የአዲስ አበባ ነጋዴ ሴቶች ማህበር፣ የሴቶች ኢንተርፕርነርሺፕ ልማት ፕሮግራም፣ ኢንተርፕርነርሺፕ ልማት ማዕከል፣ ፋሽን ዲዛይን አሶሴሽን፣ የሴቶች ራስ አገዝ ድርጅት፣ የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር በዕደ ጥበብ ዘርፍ የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞችና ሌሎችም ተሳታፊ ኢንተርፕራይዞች እንደሚሆኑ ጠቁሟል። ሁነቱ የተሞክሮ ልውውጥና የንግድ ልማት ግንዛቤ ከማዳበሩም ባሻገር፤ ኢንተርፕራይዞች ከተጠቃሚው ህብረተሰብ ጋር በሚያደርጉት ግንኙነት ዘላቂ የገበያ ትስስር ለመፍጠር የሚያስችል ምቹ አጋጣሚ ይሆንላቸዋል። ምርቶቻቸውንና አገልግሎታቸውን ለተጠቃሚዎች በቀጥታ በመሸጥም ተጠቃሚ እንደሚሆኑም እጀንሲው አስታውቋል ።አዲስ ዘመን ታህሳስ 22/2013
https://www.press.et/Ama/?p=38532
277
0ሀገር አቀፍ ዜና
የመቀሌ ከተማ በአስተማማኝ ሰላምና መረጋጋት ላይ እንደምትገኝ ተገለጸ
ሀገር አቀፍ ዜና
December 31, 2020
20
እፀገነት አክሊሉአዲስ አበባ፦ የመቀሌ ከተማ በአስተማማኝ ሰላምና መረጋጋት ላይ እንደምትገኝ የከተማው ኮሙኒኬሽን ጽህፈት ቤት አስታወቀ ። በህብረተሰቡ የንግድ እንቅስቃሴ ላይ ተጽዕኖ ያሳደረው የገንዘብ ቅያሪም ባንኮች ሥራ ከጀመሩበት ቀን ጀምሮ ቅዳሜና እሁድን ጨምሮ በ14 ቀናት ውስጥ እንዲፈጸም ብሔራዊ ባንክ አስታወቀ።ከከተማዋ ኮሙኒክሽን ጽህፈት ቤቱ ያገኘነው መረጃ እንደሚያመለክተው በከተማዋ በቤተ እምነቶችና በሌሎች ቦታዎች ላይ ተሰብስቦ የተገኘ ሰው ይገደላል፣ ታፍሶ ወደበረሃ ይወሰዳል እየተባለ ከፍተኛ ውዥንብር ይነዛ ነበረ፤ ሆኖም በትናንትናው እለት የማርያምን ወርሃዊ በዓል ለማክበር ህዝቡ በመቀሌ ከተማ እነዳማርያም ቤተክርስቲያን በብዛት በመገኘት በተረጋጋ ሁኔታ ለአሉባልታዎች ጆሮ ባለመስጠት ሃይማኖታዊ ሥርዓቱን ፈጽሟል። በከተማዋ የገበያ ስፍራዎች፣ የትራንስፖርት አገልግሎት እንዲሁም ሌሎች ማህበራዊ አገልግሎት መስጫ ተቋማት ወደቀድሞ ስራቸው እየተመለሱ ነው፤ ህዝቡም ምንም ሳይሸበር በሰላማዊ መንገድ ወጥቶ የፈለገውን ጉዳዩን ፈጽሞ ተገበያይቶ ቤቱ እንዲገባ የማድረጉም ስራ እየተሰራና ውጤትም እየታየበት ይገኛል። በከተማዋ ክፍለ ከተሞችንና ወረዳዎችን የማደራጀት ስራዎች እየተከናወኑ ነው ያለው መረጃው፣ እስከ አሁን ለስድስቱም ክፍለ ከተሞች አመራር የመምረጥ ስራ ተጠናቋል። በእነዚህ ክፍለ ከተሞች ውስጥ ላሉ ቀበሌዎች ደግሞ 20 አባላት ያሏቸው ካቢኔዎች ተደራጅተዋል፤ እነሱም የወረዳ አመራሮችን የመረጡ ሲሆን በትናንትናው እለት የአይደር ክፍለ ከተማ አመራር ተመርጧል። ከዚህ ቀደም 88 በመቶ የሚሆነው የመንግስት ሰራተኛ ወደ ስራው ለመመለስ ሪፖርት አድርጎ የነበረ ሲሆን አሁን ላይ ሪፖርት ካደረጉት ውስጥ ምን ያህሉ በስራ ገበታቸው ላይ ተገኙ የሚለውን ለማጣራት የታህሳስ ወርን የስራ አፈጻጸም በመሰራት ላይ መሆኑን የገለጸው መረጃው ፤ ስራው እንደተጠናቀቀም ውጤት እንደሚገለጽ ተብራርቷል። በሌላ በኩልም የመቀሌ ከተማ ንግድ ምክር ቤት እንደ አዲስ ተቋቁሞ የንግዱ ማህበረሰብ ህዝቡን ለማገልገል ስራዎች ወደነበነሩበት እንዲመለሱ የራሳቸውን ጥረት እያደረጉ ሲሆን በተለይም ከወልድያ መቀሌ ያለው መንገድ ክፍት መደረጉ በከተማዋ ያለው የንግድ እንቅስቃሴ ሞቅ እንዲል ብሎም ከዚህ ቀደም እጅግ ዋጋቸው ንሮ የነበሩ የእህል ምርቶች ዋጋ እንዲቀንሱ ማስቻሉን መረጃው ያመለክታል። “ባለፈው አንድ ወር ከተማው ትርምስምሱ ወጥቶ ፤ የታክሲ ታሪፍ ፣ መጫኛና ማውረጃ ቦታዎች በውል እስካለመታወቅ ደርሰው ነበር ፤ አሁን ላይ ግን እነዚህ ሁሉ ነገሮች በሚገባ ተስተካክልውና ወደቦታቸው ተመልሰዋል፤ የትራፊክ ፖሊሶችም ወደመደበኛ ስራቸው ገብተው ህግ እያስከበሩ ነው” ብላል። በሌላ በኩልም የትራፊክ ፍሰቱን አውኮ የነበረው የጸጥታ ሁኔታ እንዲሁም የነዳጅ እጥረት በአሁኑ ወቅት መፈታት ስለቻለ ከባጃጅ ጀምሮ ታክሲና ሌሎች የትራንስፖርት አማራጮች ወደስራ ገብተዋል ያለው መረጃው፣ ህብረተሰቡም ይህንን በመገንዘብ ከአላስፈላጊ ውዥንብሮች ራሱን ጠብቆ ሊንቀሳቀስ እንደሚገባም አመልክቷል። የከተማዋ ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎትም ከተማዋ ላይ በብዛት ተቆልሎ የሚገኘውን ቆሻሻ በማንሳትና የጽዳት ስራዎችን የመንገድ ዳር የማስዋብ ተግባራትን እያከናወነ ከተማዋን ለነዋሪዎቿ ምቹ እንድትሆን የራሱን ሚና እየተጫወተ መሆኑ መረጃው አመልክቷል። የጁንታው ቡድን ከወህኒ ቤት ፈትቶ የለቀቃቸው የህግ ታራሚዎች በከተማዋ ላይ ከፍተኛ የሆነ የጸጥታ ስጋት ጋርጠው እንደነበር ያስታወሰው መረጃው ፣ አሁን የክልሉ ፖሊስና መከላከያ ሰራዊት በተቀናጀ ሁኔታ በሰሩት የህግ ማስከበር ስራ ከተማዋ ከእለት እለት መረጋጋት እያሳየች ትገኛለች። “ መንግስት ይሄዳል መንግስት ይመጣል ይህ ደግሞ ምንም አዲስ ነገር የለውም፤ ትግራይ ክልል ላይም የተከሰተው ይኸው ነው፤ አንዳንዶች ግን ለውጡን ለመቀበል ተቸግረዋል፤ አብዛኛው ህዝብ ግን የተቀየረውን መንግስት ደግፎ ሰላሙ ተረጋግጦ በሰላም ወጥቶ እንዲገባ እየጠየቀ ነው፤ በዚህ መካከል ግን ህወሓት ተመልሶ ክልሉን ያስተዳድራል በማለት በህዝቡ ላይ ጥርጣሬን የሚነዙ አሉ ህብረተሰቡ ይህንን ተረድቶ ወደ ኋላ ሳይሆን ወደፊት እየሄደ ልማቱን ማስቀጠል እንደሚኖርበት አሳስቧል። በተያያዘ ዜና ተቋርጦ የነበረውን የአሮጌ ብር ኖት ቅያሬ ከታህሳስ 21/2013 ዓ.ም ጀምሮ ለ14 ቀናት እንዲከናወን ብህራዊ ባንክ መወሰኑ ተገልጿል።የገንዘብ ኖቶ ቅየራው ቅዳሜና እሁድን ጨምሮ እንደሚከናወን ያስታወቀው ባንኩ በብር መቀየሩ ሂደት የነበሩ መመሪያዎችና አሠራሮች እንደተጠበቁ መሆናቸውንም አስታውቋል።ከባንክ በጥሬ ገንዘብ የሚወጣው የገንዘብ መጠን ላይ በተሻሻለው መመሪያ ላይ በተቀመጠው መሠረት ተፈፃሚ የሚሆን ሲሆን ከ100 ሺ እስከ 1ነጥብ 5 ሚሊዮን አሮጌ ብር ያላቸው የመቀየሪያው የጊዜ ገደብ የህግ ማስከበሩ ዘመቻ ከመጀመሩ በፊት የተጠናቀቀ በመሆኑ ብር መቀየር የሚችሉት ከ100ሺህ ብር በታች ያላቸው መሆናቸውን ባንኩ ጠቁሟል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 22/2013
https://www.press.et/Ama/?p=38541
529
0ሀገር አቀፍ ዜና
እግር እንይ
መዝናኛ
September 23, 2019
47
እግር እንይ አርቀን ማስተዋል ማለት፤ የኛን ስልጣኔ ድልድይ እግር ማየት ነው ብለዋል፤ እስቲ እንግዲህ እግር እንይ! ያባቶችህ ያይን ድንበር፤ ከተረከዝ ሎሚ ሳያልፍ አንተ ግን ጆቢራው – ዘራፍ ጠረፍ አይወስንህ ጉብል ጥሎህ በዘመንህ ዕድል ዓይንህ ባት አልፎ እንዲዋልል፤ ቴህ ወዲያ ጀግንነት የለ፥ ተዚህ የዘረረ ግዳጅ ባደባባይ የዱር ገደል፥ ስትናደፍ የእግር አዋጅ ለሊቱን በየሌት- ‘ግለብ’ ቀኑን ጭምር በጠራራ ሲነጋ እንደ ጠዋት ጆቢራ በከተማህ ስታቅራራ በዕድሜህ መንከራተት ስራ፥ ካንዱ ቢሮ ሌላው ቢሮ፥ አቦል በረካውን ብለህ ያገሩን ወሬ ተንትነህ ተጨቃጭቀህ ተለፋልፈህ አመሳጥረህ፥ የዚያን ጉዳይ ከዚህ ጉዳይ ዘጋግነህ በቡና ምገህ፥ አምጥተህ ደክመህ ስትለያይ፥ በዚህ ብቻ ሳታስቀረው፥ ደግሞ አዲሱን የአገር ጠባይ ከልማድህ የቡና ሱስ ጋር፥ የዘመኑን ሳትለያይ እስቲ ደግሞ አራዳ ወጥተህ፥ በከተማው አደባባይ ያንዷን ካንዷ ዳሌና ባት፥ እግሯን ከእግር ጋር አስተያየው ደርቶልህ ያገር ልጅ ቅልጥም ዳሌው ባቷ እስኪፈረጥም እየናረ እስኪያስገመግም አንተ አድፍጠህ ከኃላዋ፥ በአይንህ ሳግ ስታነፈንፍ ያቺን ልክፍ ያቺን ንድፍ እያረክ ስታሾል፣ አንዷ ፈርታህ አንዷ ስታፈጥ ተጠግታ ባቷ ሲያገምጥ «ዘራፍ» ቀርቶ ቀልብህም «ውይ!» እያለ ወኔህ እግር ይይ! «በሰየጠኑትማ ዘንድ አንዱን የባላንጣ ዘዴ፣ የባዕዳን ስውር መንገድ ዘመናይ ጦር መሳሪያ ነው፣ ታዳጊ ሃገር ለማንጋደድ እምነቱን ለማወናበድ ያንድን ትውልድ የህልም አቅጣጫ ወደፊት ሳይሆን ወደታች፣ አመንምኖ ማቀጨጫ!» ቢልህ ፈጥጦ በግልምጫ ለህሊናህ ማጋለጫ ናቀው እርግፍ አድርገህ ተወው፣ ቴህ ብጤው ጋር አትንጫጫ። ሰልጥነን ንቀን አልፈነው፣ የይሉኝታን መቀጣጫ የኛ ዓይን የእግር ነው እንጂ፣ በቅቶት ህሊና መግለጫ። አርቀን ማስተዋል ማለት፣ የኛን ስልጣኔ ድልድይ እግር ማየት ነው ብለናል፣ አሜን በቃን እግር እንይ! ምንጭ :- ፀጋዬ ገ/መድህንአዲስ ዘመን  መስከረም 12/2012 እግር እንይእግር እንይ አርቀን ማስተዋል ማለት፤ የኛን ስልጣኔ ድልድይ እግር ማየት ነው ብለዋል፤ እስቲ እንግዲህ እግር እንይ! ያባቶችህ ያይን ድንበር፤ ከተረከዝ ሎሚ ሳያልፍ አንተ ግን ጆቢራው – ዘራፍ ጠረፍ አይወስንህ ጉብል ጥሎህ በዘመንህ ዕድል ዓይንህ ባት አልፎ እንዲዋልል፤ ቴህ ወዲያ ጀግንነት የለ፥ ተዚህ የዘረረ ግዳጅ ባደባባይ የዱር ገደል፥ ስትናደፍ የእግር አዋጅ ለሊቱን በየሌት- ‘ግለብ’ ቀኑን ጭምር በጠራራ ሲነጋ እንደ ጠዋት ጆቢራ በከተማህ ስታቅራራ በዕድሜህ መንከራተት ስራ፥ ካንዱ ቢሮ ሌላው ቢሮ፥ አቦል በረካውን ብለህ ያገሩን ወሬ ተንትነህ ተጨቃጭቀህ ተለፋልፈህ አመሳጥረህ፥ የዚያን ጉዳይ ከዚህ ጉዳይ ዘጋግነህ በቡና ምገህ፥ አምጥተህ ደክመህ ስትለያይ፥ በዚህ ብቻ ሳታስቀረው፥ ደግሞ አዲሱን የአገር ጠባይ ከልማድህ የቡና ሱስ ጋር፥ የዘመኑን ሳትለያይ እስቲ ደግሞ አራዳ ወጥተህ፥ በከተማው አደባባይ ያንዷን ካንዷ ዳሌና ባት፥ እግሯን ከእግር ጋር አስተያየው ደርቶልህ ያገር ልጅ ቅልጥም ዳሌው ባቷ እስኪፈረጥም እየናረ እስኪያስገመግም አንተ አድፍጠህ ከኃላዋ፥ በአይንህ ሳግ ስታነፈንፍ ያቺን ልክፍ ያቺን ንድፍ እያረክ ስታሾል፣ አንዷ ፈርታህ አንዷ ስታፈጥ ተጠግታ ባቷ ሲያገምጥ «ዘራፍ» ቀርቶ ቀልብህም «ውይ!» እያለ ወኔህ እግር ይይ! «በሰየጠኑትማ ዘንድ አንዱን የባላንጣ ዘዴ፣ የባዕዳን ስውር መንገድ ዘመናይ ጦር መሳሪያ ነው፣ ታዳጊ ሃገር ለማንጋደድ እምነቱን ለማወናበድ ያንድን ትውልድ የህልም አቅጣጫ ወደፊት ሳይሆን ወደታች፣ አመንምኖ ማቀጨጫ!» ቢልህ ፈጥጦ በግልምጫ ለህሊናህ ማጋለጫ ናቀው እርግፍ አድርገህ ተወው፣ ቴህ ብጤው ጋር አትንጫጫ። ሰልጥነን ንቀን አልፈነው፣ የይሉኝታን መቀጣጫ የኛ ዓይን የእግር ነው እንጂ፣ በቅቶት ህሊና መግለጫ። አርቀን ማስተዋል ማለት፣ የኛን ስልጣኔ ድልድይ እግር ማየት ነው ብለናል፣ አሜን በቃን እግር እንይ! ምንጭ :- ፀጋዬ ገ/መድህንአዲስ ዘመን  መስከረም 12/2012
https://www.press.et/Ama/?p=18824
449
1መዝናኛ
በሬሳ ሳጥን ውስጥ መቆየት ያሸልማል
መዝናኛ
September 24, 2019
126
ጎበዝ የሬሳ ሳጥን ስትመለከቱ ምን ይሰማችኋል። አንዳንዶች ሟች ዘመድ ወዳጆቻቸውን ሊያስቡ ይችላሉ። አንዳንዶች ደግሞ ሞት አጠገባቸው የደረሰ ይመስላቸውም ይሆናል። አይደለም የሬሳ ሳጥን የሬሳ መኪና ሊፍት ሊሰጣቸው ሲቆም የሚሸሹም አጋጥመውኛል። የሚሪላንዱ ቲም ፓርክ ግን ጥንዶች በሬሳ ሳጥን ውስጥ ለበርካታ ሰአታት ሊቆዩ የሚችሉበትን ውድድር እያዘጋጀ ነው። በውድድሩ እንዲሳተፉ የሚጠበቁት ጥንዶች በሬሳ ሳጥን ውስጥ ለ30 ሰአታት እንዲቆዩ ይደረጋል። ውድድሩ የሚካሄድበት ስፍራም በጣም ያልተለመደ ነው። የሬሳ ሳጥኖቹ ስድስት ሰንደቅ አላማዎች የሚደረጉባቸው ሲሆን ፣ፍቅረኞች ፣ ጓደኛሞች፣ የቤተሰብ አባላት፣ወዘተ የሆኑ ስድስት ጥንዶች እንዲሳተፉ የሚደረግበት መሆኑን ዩፒአይ ሰሞኑን የለቀቀው መረጃ ያመለክታል። ጥንዶቹ በቀን ለሰላሳ ሰአት ከፈረንጆቹ መስከረም 27 ቀን ከጠዋቱ 4 ሰአት አንስቶ እስከ መስከረም 28 ቀን 10 ሰአት ድረስ በሬሳ ሳጥኑ ውስጥ መቆየት ይኖርባቸዋል። ጥንዶቹ በቆይታቸው ፓርኩ ስራ ላይ በሚሆንባቸው ሰአቶች በፓርኩ አቅራቢያ ጓደኛ ሊጠብቃቸው ይችላል።ፓርኩ ከተዘጋ በኋላ ግን ብቻቸውን እንዲሆኑ ይደረጋል።ይህ የሆነበት ምክንያት የጨለማው ወቅት አስፈሪ ከመሆኑ ጋር በተያያዘ የሚኖራቸውን ስሜት ለመፈተን ተፈልጎ ይመስላል። ተወዳዳሪዎቹ በውድድሩ ወቅት ስማርት ስልኮችን እንዲይዙ አይፈቀድላቸውም። ይህ ብቻም አይደለም ሌሎች የኤሌክትሮኒክስ ቁሳቁስንም መያዝ አይኖርባቸውም። እነዚህ ቁሳቀስ መያዝ የሚችሉት በተፈቀደላቸው የእረፍት ጊዜ ብቻ ይሆናል። ‹‹ መጸዳጃ ቤት ለመጠቀምና ምግብ ለመብላት ከተፈቀደው ጊዜ ውጪ በተለያየ ምክንያት ከሬሳ ሳጥኑ የወጣ ተወዳዳሪ ከውድድሩ ውጪ እንደሚደረግ ፓርኩ አስጠንቅቋል። ተወዳዳሪዎቹ ሰው ሰራሽ ጭጋግና መብረቅ እንደሚለቀቅባቸውም ተጠቁሟል። የፎቶግራፍ ፍላሾችና ከባድ የአየር ሁኔታ እንዲሚጠብቃቸውም ታውቋል። ይህን ሁሉ ፈተና አልፈው ለውድድሩ ከተያዘው 30 ሰአት በኋላ የሚገኙ ጥንዶች እያንዳንዳቸው 600 ዶላር የሚሸለሙ ይሆናል። አዲስ ዘመን  መስከረም 13/2012 ዘካርያስ
https://www.press.et/Ama/?p=19038
218
1መዝናኛ
የኮሮና ቫይረስ የፈጠረው የእግር ኳሱ ዓለም ፈተና
ስፖርት
April 18, 2020
19
በቢሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ የሚያንቀሳቅሰው የስፖርት ዓለም ላይ በመጣው ፈተና ምክንያት በእጅጉ እየተጎዱ ካሉት ዘርፎች መካከል እግር ኳስ አንዱ ሆኗል።በርካቶችን በአንድነት በማሰባሰብና በአንድ ስፍራ ላይ በሺዎች የሚቆጠሩ ተመልካቾች ከሚገኙባቸው መዝናኛዎች መካከል አንዱ የሆነው ስፖርት ለቫይረሱ እጅግ አጋላጭ ሁኔታን እንደሚፈጥር ታምኖበታል።በመሆኑም ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች በቅድሚያ ያለ ደጋፊ እንዲካሄድ ቀጥሎም ሙሉ ለሙሉ ሊቋረጥ ችሏል።ይህ ደግሞ እንደሌላው የኢኮኖሚ ዘርፍ ሁሉ ኪሳራን እንዲያስተናግድ አስገድዶታል። እአአ በ2018 የስፖርቱ ዘርፍ 471 ቢሊዮን ዶላር ነበር ያስመዘገበው፤ ይህም እአአ ከ2011 ጋር ሲነጻጸር በ45 በመቶ ጭማሪ አሳይቶ ነበር።አሁን ግን የስፖርቱ ሰንሰለት በኮቪድ 19 ምክንያት ተቋርጧል፤ ስፖርተኞች፣ ክለቦች፣ ሊጎች፣ ጨዋታዎችንና ውድድሮችን የሚያሰራጩ መገናኛ ብዙሃን እንዲሁም ሌሎች የስፖርቱ አካላት እንደ ድሮ መንቀሳቀስ አልቻሉም።ከዚህ ውስጥ ከፍተኛውን ድርሻ የሚይዘው ደግሞ ተወዳጁ የእግር ኳስ ስፖርት ቢሆንም፤ በዚህ ዓመት ገቢው ይጨምራል በሚል ቢጠበቅም ከተላላፊው ቫይረስ ጋር በተያያዘ ውድድሮች በመቋረጣቸው ገቢው በእጅጉ እያሽቆለቆለ ይገኛል። በዚህ ስፖርት እያንዳንዶቹ ክለቦች የየራሳቸው የሆነ መለያና አሰራር ቢኖራቸውም ዋነኛ ገቢያቸውን የሚያገኙት ከሶስት ምንጮች ነው።ይኸውም ከመገናኛ ብዙሃን የስርጭት መብት፣ ከስፖንሰርና ማስታወቂያዎች እንዲሁም በጨዋታ ወቅት ከስታዲየም የትኬት ሽያጭ ከሚገኝ ገቢ ነው።10 በሚደርሱ ሊጎች ያለው ቁጥራዊ መረጃ እንደሚያሳየው ከሆነም ክለቦቹ ከሚዲያ መብት ብቻ ከ50 ቢሊዮን ዶላር በላይ ያገኛሉ።ይህም ከአጠቃላይ ገቢያቸው 60 ከመቶ የሚሸፍን መሆኑን ወርልድ ኢኮኖሚክ ፎረም በዘገባው ያመላክታል። ተወዳጁና በዓለም ላይ ከፍተኛ ተመልካች ያለው የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ ባለፈው ዓመት አዲስ በገባው (ለሶስት ዓመታት) ኮንትራት 12 ቢሊየን ዶላር ከሚዲያ መብት ብቻ ለመሰብሰብ አቅዶ ነበር።ነገር ግን አሁን ባለው ሁኔታ ይህንን ማሳካት የሚቻል አይመስልም፤ ምክንያቱም ከተቋረጠ ሁለት ወራትን እንኳን ሳያስቆጥር ክለቦቹ ከ60 እስከ 150 ሚሊየን ዶላር ኪሳራ ማስተናገዳቸውን እያስታወቁ ነው። እንደ ዴይሊሜይል ዘገባ ከሆነም ከቴሌቪዝን መብት ከሚገኝ ገቢ ብቻ እያንዳንዱ የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ ክለብ 750 ሚሊየን ፓውንድ ያጣል። በዚህም ምክንያት ክለቦቹ ከተጫዋችና አሰልጣኞች ቡድን ባሻገር የሚገኙ ሰራተኞቻቸውን በጊዜያዊነት እያሰናበቱ ነው።የተጫዋቾቻቸውን ደመወዝ ለመክፈል በመቸገራቸውም አንዳንዶች ግማሽ ክፍያ ሌሎች ደግሞ የተወሰነ ቅናሽ በማድረግ እንደሚከፍሉ እያሳወቁ ነው።በተያዘው ወር መጀመሪያ ላይም ሊጉ ሃያዎቹ ክለቦች ከተጫዋቾች ደመወዝ 30 በመቶ ለመቀነስ የተጫዋቾቻቸውን ስምምነት እንዲጠይቁ ማሳወቁን ጎል ዶት ኮም አስነብቧል።በስምምነቱ ማንቸስተር ዩናይትድ የመጀመሪያው ክለብ ሲሆን ተቀናሽ የሚሆነው ገንዘብ ቫይረሱን ለመከላከል ለሚደረገው ትግል ገቢ እንዲደረግም ወስነዋል። የፕሮፌሽናል ተጫዋቾች ማህበር በበኩሉ ክለቦች አቅሙ ካላቸው ሙሉ ክፍያ ለተጫዋቾች እንዲሰጡ፤ ካልቻሉ ግን የክለቦቻቸውን የፋይናንስ ኪሳራ እንዲጋሩ ለአባላቱ ጥሪውን አቅርቧል። ይህ በዓለም የመጣው አስቸጋሪ ሁኔታ በኢትዮጵያም መስተናገዱ አይቀርም።በተለይ የሊጉ ክለቦች በአብዛኛው በመንግስት የሚደጎሙ እንደመሆኑ ጠንካራ ፋይናንስ ያላቸው ክለቦች ያቃታቸውን ይወጡታል ማለት አስቸጋሪ ነው።በእንግሊዝና በሌሎች ሊጎች የታየው የደመወዝ ቅነሳም በኢትዮጵያ ክለቦችም እየታየ ይገኛል፡፡ የወልቂጤ ከተማ እግር ኳስ ክለብ ደግሞ በዚህ ረገድ ቀዳሚው ሆኗል።ፕሪምየር ሊጉን ዘንድሮ የተቀላቀለው ክለቡ በኮሮና ቫይረስ በተቋረጠው ሊግ ምክንያት ሊፈጠር የሚችለውን የፋይናንስ ጫና ለመቀነስ በማሰብ ተጫዋቾች የአንድ ወር ደመወዛቸውን ላለመውሰድ መወሰናቸውን ሶከር ኢትዮጵያ በዘገባው አስነብቧል። በቀጣይም የክለቦችና ተጫዋቾች ገቢ በምን ዓይነት ሁኔታ ይቀጥላል የሚለው የወቅቱ ፈተና እንደሚሆን ነው የሚጠበቀው፡፡አዲስ ዘመን ሚያዝያ 10/2012
https://www.press.et/Ama/?p=30594
414
2ስፖርት
የስፖርት ማኅብረተሰቡ- ማኅበራዊ ኃላፊነት የመወጣት ሰብዓዊው መንገድ
ስፖርት
April 18, 2020
17
የዓለም ሕዝብ ሁሉ ጭንቀትና ስጋት የሆነው የኮሮና ቫይረስ ስርጭት ከትንሽ እስከ ትልቅ፣ ከሀብታም እስከ ድሃ፣ ከሊቅ እስከ ደቂቅ ዋነኛ ትኩረቱ እንዲሆን ካስገደደ ስድስት ወራት ተቆጠሩ፡፡ የቫይረሱ ስርጭት በእነዚህ ወራት እንደ ሰደድ እሳት ያላዳረሰው የዓለም ክፍል ስለመኖሩ አጠራጣሪ ሆኗል፡፡ ሀገራት ዓለም በጋራ የገጠማት ጦርነት በድል ለመወጣት የሚያስችል መፍትሄ ለማበጀት ጥረት ማድረጉን ተያይዘውታል። የቫይረሱ ማንነትና፣ ምንነት ፈጣን መፍትሄ ማበጀት የሚያስችል አልሆነም። በእርግጥም የኮሮና ወረርሽኝ በዓለም ፖለቲካ፣ ኢኮኖሚና ማህበራዊ መስተጋብር ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ብቻ ነውን? በእኔ እሳቤ አዎንታዊ እንዳለው መካድ ንፍግነት ይሆናል! የኮሮና ቫይረስ ዓለምን እንደጎዳት ባለበት ደረጃ ባይሆንም በጎ መልኮችን ይዞ መምጣቱን በድፍረት መናገር ይገባል። ዓለም ከገባችበት የጋራ ማዕጥ ለመውጣት ከሚደረግ ጉዞ የሚቀዳው «ሰውነትን» ያስቀደሙ ደጋግ እጆችን፤ ኅብረተሰቡ ከተጋረጠበት አደጋ ለመታደግ ሰብአዊነትን አርግዘው የሚወለዱ ድጋፎችን በዘመነ ኮሮና ሊበረክቱ ችለዋል። በዓለም አራቱም አቅጣጫዎች ሰብአዊነትን ባስቀደመ መልኩ ሲደረጉና እየተደረጉ ያሉ ድጋፎችን ብሶባቸው ታዝበናል። በተለያዩ መስኮች እንፋሎቱ ሳይበርድ የቀጠለው ልግስና ከስፖርቱ መስክ ያለውን ሁኔታ መመልከቱ ይበጃል። ስፖርት ሰላም፣ ፍቅር፣ የአብሮነትና የአንድነት፣ የመተሳሰብ፣ የወንድማማችነት ልዩ መገለጫ ነው። ስፖርት ዘር፣ ሃይማኖት፣ ፆታና ቀለምን አይለይም። በየትኛውም ሁኔታ ውስጥ የስፖርታዊ እንቅስቃሴ አስኳል ሃሳብ ወዳጅነትና መተሳሰብ መሆኑ ይታወቃል። በታሪክ ገጾች እንደሰፈረውም በሰው ልጅ ታሪክ ባጋጠሙ በጎም ሆኑ መጥፎ ክስተቶች ስፖርት በአጋርነት ተሳትፏል። ስፖርታዊ ክንዋኔዎች ሰላምንና አንድነትን የሚሰብኩ እንደመሆናቸው በማህበራዊ፣ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች በመግባት ሚናቸውን ሲወጡም ኖረዋል። ስፖርት ሰብአዊነትን ያነገበ የልግስና ማዕድ መሆኑን ዘመነ ኮሮና በተጨባጭ አሳይቶናል። የቫይረሱ ስጋትነት በዓለም አቀፉ የጤና ተቋም ከተረጋገጠበት ጊዜ ጀምሮ፤ ውድድሮችን ከማቋረጥና ከመሰረዝ ባለፈ የስፖርቱ ተዋንያን በተናጥልም ሆነ በተቋማዊ ደረጃ አበርክቷቸውን እየተወጡ ይገኛሉ። በእግር ኳስ ጠቢብነታቸው ዓለም የመሰከረላቸው ተጫዋቾችና ስመ ጥር አሰልጣኞችም፤ ለደጋፊዎቻቸው መልእክት ከማስተላለፍና ገንዘብ ከመለገስ ባሻገር ሆቴሎቻቸውን ለህክምና አገልግሎት እንዲውሉም ጭምር መስጠታቸው ይታወሳል። በሀገራችን በተመሳሳይ የስፖርቱ ለጋስነትና ሰብአዊነት መገለጫ ያደረጉ ተግባራት ዛሬም እንደ ትናንቱ በዘመነ ኮሮና ከነበረው ብሶበት አለኝታነቱን እያሳየ ይገኛል። የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ መከሰት ከታወቀበት ከመጋቢት መጀመሪያ አንስቶ በስፖርቱ ማህበረሰብ ጠንካራ እንቅስቃሴ በማድረግ አጋርነቱን በፈጠነና በቀደመ መልኩ ያሳየው። በስፖርት ቤተሰቡ በቡድንም ሆነ በተናጠል ለወረርሽኙ መከላከያ የሚውል የገንዘብ ድጋፍ በማሰባሰብ ከመንግስት ጎን በመቆም ወገን ላይ የተደቀነውን አደጋ በአንድነት ለመመከት ህዝባዊነቱን ማሳየት ችሏል፡፡ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ኢንጂነር ታከለ ኡማ የድጋፍ መሠባሰብ ጥሪ ተከትሎ የስፖርቱ ማህበረሰብ ተሳትፎ በተጠናከረ መልኩ መቀጠሉን ለመታዘብ ችለናል። ከመከላከያ ስፖርት ክለብ አካባቢ የተሰማው ዜና ይሄንኑ ያስረዳል። የመከላከያ ስፖርት ክለብ አዋቂ ወንዶች እና ሴቶች እግር ኳስ ቡድን እና ኮቺንግ አባላቱ 211 ሺህ ብር ድጋፍ አድርጓል። የስፖርት ክለቡ ለኮረና ቫይረስ መከላከልና መቆጣጠር እንዲውል በከተማ አስተዳደሩ ለተቋቋመ ድጋፍ ማሰባሰቢያ ኮሚቴ ነበር ገንዘቡን ያስረከበው። «የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ባቀረበው የድጋፍ ጥሪ መሠረት የኮቪድ -19 ለመግታት በሚደረገው ርብርብ የበኩላችንን ለመወጣት ነው» ሲሉ ነበር የስፖርት ክለቡ አባላት በስፖርቱን ማህበረሰብ ዘንድ ሰብአዊነትን ባስቀደመ መልኩ ማህበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት እየተደረገ ያለውን ተሳትፎ ያመላከቱት። የሀገር ዳር ድንበር ህልውና ከሆነው የስፖርቱ ክለብ በተመሳሳይ፤ በስፖርቱ የሰብአዊነት ልግስናው ተጠናክሮ የመቀጠሉን ሁኔታ የጠዋት ጎህ አትሌቶች የልማት መረዳጃ ተግባርም ይነሳል። በተለያዩ ዓለም አቀፍ መድረኮች ድል በማድረግ የሀገራችንን ሰንደቅ አላማ በማወለብለብ ስሟና ዝናዋን ከፍ ባደረጉት አትሌቶች የተቋቋመው ዕድሩ 200 ሺህ ብር ድጋፍ በማድረግ አጋርነታቸውን አስመስክረዋል፡፡ የአትሌቶቹ የመረዳጃ ዕድር አባላት አስተባባሪዎች ኮማንደር አትሌት ጌጤ ዋሚ፣ አትሌት ተስፋዬ ቶላ፣ አሰልጣኝ ንጋቱ ወርቁ ፣ ዶክተር በዛብህ ወልዴ እና ወይዘሮ አይናዲስ ተስፋዬ ድጋፍ ለማድረግ የመሻታቸውን ሚስጥር በጋራ እንዲህ አጋርተዋል። «ዓለም ብሎም ሀገራችን በጭንቅ ተውጣለች። ህዝባችንም በሲቃ ተኮራምቷል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለኮረና ቫይረስ መከላከል ጥሪ ማቅረቡን ተከትሎ እኛም የዜግነት ግዴታችን ለመወጣት የገንዘብ ድጋፍ ልናደርግ ወደናል። ኢትዮጵያዊነታችን የሚደምቀው በዚህ በጭለማና በጭንቅ ወቅት ስንረዳዳና ስንተጋገዝ በመንፈስና በፀሎት አብረን ከማህበረሰባቸን ጎን ስንቆም ነው» የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጆች ከሆኑ አትሌቶች ልግስና ወረድ በማለት እንደ መቋጫ አንድ ክስተት ስንጠቅስ፤ በኢትዮጵያ የወንዶችና የሴቶች ብሔራዊ ቡድኖች አሠልጣኞች እንዲሁም የስፖርቱ ሙያተኞች የተደረገ ልግስና የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ለመከላከል ከስፖርቱ ቤተሰብ በኩል እየተደረገ ያለውን ልግስና የሚያሳየው ሁነት ነው። እነዚህ አካላት ህዝብን ለመታደግ በሚደረገው ርብርብ በየአቅጣጫው 120 ሺህ ብር መሰብሰብ ችለዋል። ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ለኢንጂነር ታከለ ኡማ አስረክበዋል፡፡ ይህ ተግባር በአጠቃላይ ከስፖርት ማኅብረተሰቡ ዘንድ የተንፀባረቁትን ወገናዊ ድጋፎችንና ችግርን በአንድነት ለመመከት እየተደረገ ካለው ጥረት በመነሳት የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ከፈጠረውና ካሳደረው አሉታዊ ተጽእኖ ጎን ለጎን የፈጠረው በጎ መልክ ስለመኖሩ የሚያስገነዝብ ይሆነናል። በስፖርት ማኅብረተሰቡ አካላዊ ርቀትን በጠበቀ መልኩ ማኅበራዊ ኃላፊነትን የመወጣት ጉዞ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል እሙን ነው።አዲስ ዘመን ሚያዝያ 9/2012 ዳንኤል ዘነበ
https://www.press.et/Ama/?p=30621
632
2ስፖርት
‹‹ፋሲል ከነማ›› – የትውልድ ቅብብሎሽ አርማ!
ስፖርት
April 20, 2020
21
 በአገራችን ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በእግር ኳሱ ትልቅ ተፅዕኖ እያሳደሩ ከመጡ ክለቦች አንዱ ፋሲል ከነማ ስለመሆኑ ማረጋገጫ አያስፈልግም። ክለቡ የፕሪሚየር ሊግ ተሳታፊ መሆኑን ካረጋገጠ ወዲህ በጥቂት ዓመታት ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ዋልታና ማገር የሆኑ በርካታ ተጫዋቾችን ከማበርከት ባለፈ በፕሪሚየር ሊጉ የዋንጫ ተፎካካሪ በመሆን በተደጋጋሚ ዓመታት ጥንካሬውን አሳይቷል። በቁጥርም በውበትም የእግር ኳሱን ቤተሰቦች ያስደመሙ ደጋፊዎችን በማበርከትም ካምቦሎጆን ካደመቁ ጥቂት ክለቦች መካከል አንዱ ሆኗል። የውብ ደጋፊዎች ባለቤት የሆነውን ፋሲል ከነማ እግር ኳስ ክለብ ከብዙ በጥቂቱ በዛሬው የስፖርት ማህደር አምዳችን እንደሚከተለው ለመመልከት ወደድን።1960 ዓ.ም ጎንደር ከተማ ላይ የያኔ ወጣቶች በአገሪቱ የነበሩ ትልልቆቹን የእግር ኳስ ቡድኖች (አሥመራ ቡድን፣ ሸዋ ቡድን፣ አየር ኃይል ቡድን፣…) እያሰቡ፤ አንድ ትንሽ የእግር ኳስ ቡድን በራሳቸው ጥረት መሰረቱ። በጨርቅ ኳስ የተጀመረው የእግር ኳስ ቡድን ስብስብ ብዙ የተለየ እንቅስቃሴ ሳያድርግ ስድስት ዓመታት ተቆጠሩ። ስብስቡ የሰፈር ጨዋታዎችን ከማካሄድ ሳይሻገር ኢትዮጵያ አዲስ የታሪክ ምዕራፍ አስተናገደች። ሕዝባዊ አብዮት። የ1966ቱ የኢትዮጵያ አብዮት የአገሪቱን ፖለቲካና ኢኮኖሚያዊ መዋቅሮች ብቻከገጽ 20 የዞረሳይሆን ማህበራዊ መዋቅሩንም ቀየረው። የለውጡ አካል የነበረችው ጎንደር፤ በሥር ነቀል ሂደቱ ውስጥ ስታልፍ በከተማው ውስጥ ከስድስት ዓመታት በፊት የተመሰረተው የእግር ኳስ ቡድን እንደዘመኑ መንፈስ አዲስ የቡድን ስያሜ ያዘ። ‹‹ትግል ፍሬ የእግር ኳስ ቡድን›› ተሰኘ። አሁን ጊዜው 1967 ዓ.ም ሆኗል።የትግል ፍሬ የእግር ኳስ ቡድን ተጫዋቾች በአብዛኛው የቀበሌ 16 በተለምዶ ‹‹ቸቸላ›› ተብሎ የሚጠራው ሰፈር ልጆች ናቸው። በጊዜ ሂደት ግን ከየአቅጣጫው ቡድኑን የተቀላቀሉት የከተማዋ ወጣቶች አልጠፉም። መካሻ፣ አባቡ፣ ሰጠኝ፣ አራጋው፣ … የትግል ፍሬ እግር ኳስ ቡድን ሞተር ነበሩ። በእግር ኳስ ያበደ ልባቸው በፖለቲካ ለመቅለጥ ጊዜ አልፈጀበትም። አብዛኛዎቹ የቡድኑ አባላት በኢህአፓ የፖለቲካ መስመር ተጠለፉ። እንደዘመኑ መንፈስ፤ ህብዑ ገቡ። ይህም ሆኖ ትግል ፍሬ የእግር ኳስ ቡድን ከአቻዎቹ ጋር የእግር ኳስ ግጥሚያ ከማካሄድ አልቆመም። የግጥሚያ ሜዳው በየጊዜው ይቀያየር ነበር። ጎንደር ሆስፒታል ግቢ ውስጥ በተለምዶ ‹‹ኳስ ሜዳ›› ተብሎ በሚጠራው ሜዳ፣ ፋሲለደስ መዋኛ ግቢ ፊት ለፊት (ዛሬ ላይ ፋሲለደስ ስታዲየም ተብሎ የተሰየመው)፣ ፋሲለደስ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ቅጥር ግቢ ውስጥ፣ … የእግር ኳስ ውድድሮች በተዘጋጁ ቁጥር ትግል ፍሬ የእግር ኳስ ቡድን ተሳታፊ ነበር።የደርግ ምህረት የለሽ ቅጣት በኢህአፓ ወጣቶች ላይ እየበረታ ሲመጣ፣ የመላኩ ተፈራ ፈርዖናዊ እብሪት በጎንደር አደባባዮች ላይ ናኘ። ከተማዋ በደም አበላ ታጠበች። ትግል ፍሬ የእግር ኳስ ቡድን ቅርቃር ውስጥ ገባ። የቡድኑ ቁልፍ ተጫዋቾች መመናመን ጀመሩ። ያም ሆኖ የቀይ ሽብር ዘመን አልፎ እንኳ ቡድኑ አልከሰመም። መደብዘዙ ግን አልቀረም።ትግል ፍሬ የእግር ኳስ ቡድን ‹‹ዓለም የለምም›› ሳይባል ዓመታት ነጐዱ። ደርግ በድራማዊ አጀብ እንደተከሰተው፤ በትራጄዲ ሁነት ተሰናበተ። ትግል ፍሬ እንደ አጀማመሩ ባይሆንም ቡድኑ በሥም ደረጃ ይንቀሳቀስ ነበር። ከደርግ ውድቀት በኋላ ግን ትግል ፍሬ በስምም ከሰመ። ለሁለት ዓመት ብቻ። 1985 ዓ.ም የትግል ፍሬ ተከታይ ትውልድ በአዲስ መንፈስ ‹‹ፋሲል›› በሚል ሥያሜ የእግር ኳስ ቡድን ተቋቋመ። ፋሲል ከነማ የሚለው ስያሜ የሽግግር መንግሥቱ ጊዜ ካበቃ በኋላ በተፈጠረው የከተሞች አደረጃጀት የመጣ ስያሜ መሆኑ እዚህ ላይ ይነሳል።1985 እና ከዛ በኋላ የነበሩ ዓመታት እንደ ቀዳሚዎች ዓመታት ከፖለቲካና ኢኮኖሚ እንቅስቃሴዎች አኳያ ለጐንደር ፈታኝ ጊዜያት ነበሩ። ማህበራዊ ቀውሶች በተጨማሪነት ቢስተዋሉም በእግር ኳስ ረገድ ግን ጥሩ መነቃቃት ነበር። ዛሬ ላይ ‹‹ታየ በላይ ሆቴል›› የተገነባበት ቦታ ‹‹ሜክሲኮ ሜዳ›› ይባል ነበር። በዚህ መለስተኛ ሜዳ በመሬት አርድ የእግር ኳስ ደጋፊዎች የታጀበ የእግር ኳስ ውድድር መርሃ ግብሮች ይካሄዱ ነበር። አራዳ፣ ውሃ ልማት፣ ፖሊ፣ ኳሊበር፣ ኒያላ፣ ኢዲዲሲ … የተሰኙ የእግር ኳስ ቡድኖች ቀንደኛ ተፋላሚዎች ነበሩ። ከእነዚህ ቡድኖች ውስጥ የተሻለ የመጫወት ጥበብ ያላቸው ተጫዋቾች ለፋሲል እግር ኳስ ቡድን መጋቢ በመሆን አገልግለዋል። የያኔው ፋሲል ከ‹‹ሜክሲኮ›› ጨዋታ ከፍ ባለ መልኩ ከወረዳ የእግር ኳስ ቡድኖች ጋር ይጫወት ነበር። ‹‹ፋሲል ከነማ የትውልዶች ቅብብል ውጤት ነው›› የሚባለውም ለዚህ ነው።የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አደረጃጀትና የአሰራር ዝግመታዊ ለውጥን ተከትሎ ፋሲል ከነማ ለዓመታት በከተማ ደረጃና በብሔራዊ ሊግ ደረጃ ሲጫወት ቆይቶ፤ በ2008 የውድድር ዘመን ብሄራዊ ሊጉን በበላይነት በማጠናቀቅ የኢትዮጵያ ፕሪሚሪ ሊግ ተሳታፊ ለመሆን በቃ። የትውልድ ቅብብሎሽ በታየበት በዚህ የታሪክ ሂደት መሰረት ክለቡ 50 ዓመታት በላይ ያስቆጠረ አንጋፋ ክለብ ነው።‹‹ፋሲል ከነማ በትውልዶች ቅብብል የቆመ የከተማችን እግር ኳስ ክለብ ነው›› የሚለው አቋም የክለቡ ደጋፊዎች የጋራ ምልከታ ነው። በተለይም ክለቡ በብሔራዊ ሊግ ቆይታው በነበረበት የገንዘብ እጥረት የተነሳ ፈታኝ ጊዜያትን አሳልፏል። በ2008 ዓ.ም የብሔራዊ ሊጉ የውድድር ዘመን ፋሲል ምድቡን በበላይነት እየመራ እንኳን ከተማ አስተዳደሩ ለክለቡ የበጀተው በጀት በዓመቱ አጋማሽ አልቆ ነበር። በክለቡ ስም የንግድ ትርዒት (ባዛር) እና የሙዚቃ ዝግጅት (ኮንሰርት) በማዘጋጀት ገቢ በማሰባሰብ፤ በጐንደር ዩኒቨርሲቲ ድጋፍ፤ በከተማው ወጣቶችና አጋር የስፖርቱ ቤተሰቦች ጥረት እንዲሁም ዳሽን ቢራ ፋብሪካ በሰጠው ገንዘብ ዓመቱን እንደምንም ቆይቶ ብሔራዊ ሊጉን በድል በማጠናቀቅ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግን ለመቀላቀል በቃ።ለብዙዎቹ የአገሪቱ እግር ኳስ ተከታታዮች ክስተት በሆነ መልኩ የፋሲል ከነማ ስኬታማ የሚባል ጉዞ ያለ ደጋፊው ማዕበል የሚታሰብ አልነበረም። የክለቡ ደጋፊዎች ፋሲል ከነማን እንደ አንድ የጎንደር የታሪክ አካል አድርገው ይመለከቱታል። ከዚህ ምልከታቸው በመነሳት ለክለቡ የሚያደርጉትን ድጋፍ ማቀጣጠያ ዘዴያቸውም ታሪክ ነው። ‹‹የጎንደር ክብሯ ታሪኳ ነው›› የሚሉት የክለቡ ደጋፊዎች፤ የፋሲል ከነማ ክለብ ዋና መለያ ‹‹አፄዎቹ›› ሆኗል። በፖለቲካ አፈና፣ በማህበራዊ ሕይወት ብክነትና በኢኮኖሚ መገፋት ተበታትነው የነበሩት የጎንደር ከተማና አካባቢዋ ወጣቶች ፋሲል ከነማ ምክንያት ሆኗቸው በአንድነት ጥላ ስር ተገናኝተዋል። በፋሲለደስ ስታዲየም፤ ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱና ጓዶቹ ስማቸው እየተነሳ ተዘምሮላቸዋል። አርበኛ ጐቤ መልኬ ታስቦበታል። ዛሬ ላይ ፋሲል ከነማ በአገሪቱ ቀዳሚ የደጋፊ ሃብታም ከሚባሉ ክለቦች አንዱ ብቻ ሳይሆን ጠንካራ ተፎካካሪም ሆኗል። የድጋፍ መሰረቱ የሰፋውን ያህል ግን የገቢ አቅሙን ማሳደግ አልቻለም። ትላንት፣ ዛሬም ሆነ ነገ ዘመናዊ አደረጃጀትና ዘላቂ የገቢ/ስፖንሰር ምንጭ ዕጥረት የክለቡ ፈተና ሆነው ይቀጥላሉ። ፋሲል ከነማ ካስቆጠረው ዕድሜና ከመጣበት የታሪክ ሂደት አኳያ በአደረጃጀት ተገቢ በሚባል ደረጃ ላይ ይገኛል ማለት ስህተት ይሆናል። በየዘመኑ ግን ህያው የሕዝብ ድምፅ በመሆን የትውልድ ቅብብሎሽ አርማ ሆኖ አገልግሏል። እያገለገለም ነው።አዲስ ዘመን ሚያዝያ 11 ቀን 2012 ዓ.ም ቦጋለ አበበ
https://www.press.et/Ama/?p=30665
814
2ስፖርት
ኦሊምፒክን በተመለከተ አማራጭ እቅድ አልተቀመጠም
ስፖርት
April 20, 2020
14
በአስከፊው የኮሮና ቫይረስ ስርጭት ምክንያት ለአስራ ስድስት ወራት የተራዘመው የቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ አሁንም ከአንድ ዓመት በላይ እየቀረው ከቫይረሱ ስጋት ነፃ መሆን አልቻለም። የቫይረሱ ስርጭት ከመሻሻል ይልቅ እየባሰበት መሄዱ ከአስራ ስድስት ወራት በኋላም የመቆሙ ነገር ጥርጣሬ ውስጥ እንዲገባ አድርጓል። ይህም የቀጣዩን ዓመት ኦሊምፒክ ስጋት እንዲኖርበት ከማድረግ ባሻገር በርካታ ጥያቄዎች እንዲነሱ ሆኗል። በተለይም ዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ከዚሁ ስጋት ጋር በተያያዘ ኦሊምፒኩን ዳግም የማራዘም ወይም ሌላ አማራጭ እቅድ መያዙን በርካቶች እየጠየቁ ይገኛሉ። ይሁን እንጂ የኦሊምፒኩ ቃል አቀባይ ማሳ ታካያ ዓለም አቀፍ ኮሚቴው ውድድሩን በቀጣዩ ዓመት ከማካሄድ ውጪ ሌላ አማራጭ እንዳላስቀመጠ ከጃፓን ጋዜጠኞች ጋር በነበራቸው መግለጫ ጠቁመዋል። ‹‹ኦሊምፒኩ በተራዘመበት ወቅት እንዲካሄድ እየሰራን ነው፣ በዚህ መሰረት ሁሉም ባለድርሻ አካላት እየተንቀሳቀሱ ይገኛሉ፣ አሁን ላይ መናገር የምችለው ይህን ብቻ ነው›› በማለትም ቃል አቀባዩ ኦሊምፒኩን ዳግም የማራዘምም ይሁን የመሰረዝ ሃሳብ እንደሌለ አስረድተዋል። ቃል አቀባዩ በጀርመኑ እለታዊ ጋዜጣ ዳይ ዌልት ኦሊምፒኩ የመሰረዝ ወይም የመራዘም እድል እንዳለው ተጠይቀው በቀጥታ ምላሽ አልሰጡም። ወዲያው ግን የኦሊምፒክ አዘጋጆቹና የጃፓኑ ጠቅላይ ሚኒስትር ሺንዞ አቤ ኦሊምፒኩን የመሰረዝም ይሁን የማራዘም ምንም አይነት ሃሳብ እንደሌለ ለመገናኛ ብዙሃን ለመጠቆም ሞክረዋል። ከተራዘመው የጉዞና የሆቴል ጉዳይ፣ የስቴድየም መግቢያ ትኬቶችና በአጠቃላይ ኦሊምፒኩ በመራዘሙ ሊገጥም የሚችለውን ኪሳራ በተመለከተ ጥያቄ ተነስቷል። ይህ ኪሳራ ከሁለት እስከ ስድስት ቢሊየን የጃፓን የን እንደሚሆን ግምቶች ቢሰጡም አሁንም ትልቁ ጥያቄ የኪሳራው መጠን ምን ያህል ነው? ማንስ ይከፍለዋል? የሚል ነው። የዓለም አቀፍ ኮሚቴው ፕሬዚዳንት ቶማስ ባኽ ተቋማቸው በመቶ ሚሊየን ዶላሮች ሊከስር እንደሚችል የጠቆሙ ሲሆን ጃፓንም አዘጋጅ አገር እንደመሆኗ ሊገጥማት የሚችለው ኪሳራ በቀላሉ የሚታይ አይሆንም። ቶኪዮ ኦሊምፒኩን ለማስተናገድ አስራ ሁለት ቢሊየን የን ማውጣቷን ትናገራለች። ባለፈው ዓመት የታተመው የአገሪቱ መንግስት ኦዲተር ሪፖርት እንደሚያመለክተው ግን ወጪው በሁለት እጥፍም ሊልቅ ይችላል። ከዚህ ገንዘብ ውስጥ ግን አምስት ነጥብ ስድስት ቢሊየን የሚሆነው በግል ባለሃብቶች ወጪ የተደረገ ሲሆን ቀሪው በአገሪቱ መንግስት ነው። የዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ውድድሩ ወደ 2021 እንዲዘዋወር ውሳኔ ላይ ከደረሰ ወዲህ በቫይረሱ ስጋት በአስተናጋጇ ጃፓን ቶኪዮን ጨምሮ በሰባት ከተሞች የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ታውጇል። ከቀናት በፊት የወጡ መረጃዎች እንደሚያመለክቱትም በኮሮና ቫይረስ በጃፓን ከስድስት ሺ በላይ ሕዝቦች ሲጠቁ ከመቶ በላይ የሚሆኑት ሕይወታቸውን አጥተዋል። ኦሊምፒኩ እስከሚካሄድ ገና አስራ ስድስት ወራት የቀሩት ቢሆንም የቫይረሱን ስርጭት በነዚህ ጊዜያት በቁጥጥር ስር ማዋል ካልተቻለ ኦሊምፒኩ አሁንም ከስጋት ውጪ ሊሆን እንደማይችል የቶኪዮ ኦሊምፒክ ዋና ስራ አስፈፃሚ ቶሺሮ ሙቶ መናገራቸው ይታወሳል። ‹‹በዚህ ወቅት ማንም በእርግጠኝነት ቫይረሱን በቁጥጥር ስር አውላለሁ የሚል እምነት የለውም፣ ስለዚህ የተራዘመው ኦሊምፒክ ከቫይረሱ ስጋት ነፃ ይሆናል ብለን ለመናገር ይቸግረናል›› በማለትም ሃሳባቸውን አጠናክረዋል። በቫይረሱ ስጋት ኦሊምፒኩን ከአንድ ዓመት በላይ ለማራዘም እንደተወሰነ ያስታወሱት ስራ አስፈፃሚው፣ ዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ በዚህ ወቅት ለተራዘመው ኦሊምፒክ ጠንክሮ ከመዘጋጀት ውጪ ሌላ ነገር ሊያደርግ እንደማይችል አስረድተዋል። ይሁን እንጂ የሰው ልጅ እስከዚያው ቫይረሱን በቁጥጥር ስር ያውላል የሚል ተስፋ እንዳላቸው ገልፀዋል። የተራዘመው ኦሊምፒክ ዘንድሮ ሊካሄድ በታቀደበት ተመሳሳይ ወቅት እንዲካሄድ ከመወሰኑ ውጪ በየትኛው ቀን እንደሚካሄድ ቁርጥ ያለ ቀን አልተቀመጠለትም። ይህንንም ለመወሰን ዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ የተለየ አማራጭ እስካሁን እንዳልተመለከተ አስረድተዋል። ከዚህ ይልቅ ኦሊምፒኩን ቀጣይ ዓመት ላይ በተሳካ ሁኔታ ለማካሄድ የተቻለውን ሁሉ ጥረት ማድረግ የሚቻልበትን አማራጭ ታሳቢ በማድረግ እንቅስቃሴ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ዓለምን እያስጨነቀ የሚገኘው የኮሮና ቫይረስ በቀጣዮቹ አስራ አምስት ወራት በቁጥጥር ስር እስካልዋለ ኦሊምፒኩ ቢካሄድም የደበዘዘ እንደሚሆን ከወዲሁ ግምታቸውን የሚያስቀምጡ ተበራክተዋል። በተለይም ውድድሮች በሚካሄዱባቸው ስቴድየሞች የሚታደሙ ተመልካቾች ጉዳይ በታላቁና ደማቁ የስፖርት መድረክ ላይ ቀዝቃዛ ውሃ እንዳይጨምር ያሰጋል። ለበርካታ ወራት በቫይረሱ ስርጭት ምክንያት የዓለም ሕዝቦች ራሳቸውን ለመጠበቅ የፊት ጭምብል የማድረግና ማህበራዊ ርቀትን የመጠበቅ ልም ምድ ውስጥ ገብተዋል። ታላቁን የስፖርት መድረክ በስቴ ድየም ተገኝቶ መመልከት የሚቻልበት እድል ቢኖር እንኳን ደጋፊዎች ከዚህ ረጅም ልማድ ሳይወጡ ውድድሮችን ለመመልከት እንደሚገደዱ ይጠበቃል። ይህም በስቴድየም ወንበሮች ተራርቆ ከመቀመጥ ጋር ተያይዞ የተመልካቾች ቁጥር በእጅጉ እንደሚቀንስ ይታመናል። ይህም በኪሳራ ላይ የሚገኙትን የውድድሩ አዘጋጆች ከትኬት ሽያጭ ጋር በተያያዘ ለሌላ ኪሳራ እንደሚዳርጋቸው ያሰጋል። ከደጋፊዎች ጋር በተያያዘ እንደቀድሞው የአገራቸውን ሰንደቅ አላማ አንግበው በስቴድየም በአንድ ላይ ተሰብስበው ማየት ብርቅ ሊሆን ይችላል። ደጋፊዎች የአገራቸው አትሌቶች ሲያሸንፉ እንደተለመደው በደስታ ተቃቅፈው የሚያነቡበት፣ አብረው ፎቶ ግራፍ የሚነሱበትና በጋራ ተሰብስበው ደስታቸውን የሚገልፁበት አጋጣሚ ብርቅ ሊሆን ይችላል። ይህ በአንድ አገር አትሌቶች መካከልም ይሁን በተለያዩ አገራት አትሌቶች መካከል የተለመደ የመጨባበጥ፣ ተቀራርቦ የመደናነቅና ‹‹ተቃቅፎ እንኳን ደስ ያለህ›› የመባባል የስፖርታዊ ጨዋነት መገለጫዎች ቅንጦት እንዳይሆኑም ያሰጋል። ይህ ሁሉ ስጋትና እንቅፋት የተደገነበት የቶኪዮ ኦሊምፒክን በተመለከተ በተራዘመበት ጊዜ ከማካሄድ ውጪ አዘጋጆቹ ሌላ አማራጭ እቅድ እስኪያጡ ድረስ ተጨንቀዋል። ይህም የዓለም አቀፉን ኦሊምፒክ ኮሚቴ ያህል ትልቅ ተቋም ከወዲሁ የሰላ ትችት እንዲሰነዘርበት እያደረገ ይገኛል። አዲስ ዘመን ሚያዝያ 12 /2012
https://www.press.et/Ama/?p=30712
653
2ስፖርት
የአውሮፓ እግር ኳስና ኮሮና ቫይረስ
ስፖርት
April 18, 2020
30
በአሁኑ ሰዓት ተቋርጦ የሚገኘው የአውሮፓ እግር ኳስ ከዚህ በኋላ በዝግ ስታዲየሞች እንዲደሚካሄድ ግልጽ ቢሆንም መቼ የሚለው ጥያቄ ግን ምላሽ እንዳላገኘ በአውሮፓ የሚገኙ ሊጎችን የሚወክለው ማህበር አስታወቀ። የማህበሩ ምክትል ኃላፊ አልቤርቶ ኮሎምቦ እንዳሉት በኮሮና ቫይረስ ምክንያት የተቋረጠው የአውሮፓ ሊግ ከፍተኛ ችግር ውስጥ ገብቷል። «አብዛኛዎቹ የማህበሩ አባል ሊጎች በተለይም የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ ጨዋታዎች እንዲጀመሩ ከፍተኛ ፍላጎት አላቸው። ነገር ግን እንደ ቤልጂየም ያሉ ጥቂት አገራት ከነጭራሹ የዘንድሮው ውድድር እንዲሰረዝ ሀሳብ አቅርበዋል» ብለዋል። የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ ዓርብ ዕለት የወደፊት እርምጃዎችን በተመለከተ ስብሰባ እንደሚያደርግ የሚጠበቅ ሲሆን ዘጠኝ ጨዋታዎች የሚቀሩት ሊግ መቼ ይቀጥል? የሚለው ዋና ርዕስ እንደሚሆን ይጠበቃል። ባለፈው ሳምንት አንዳንድ የጀርመን ክለቦች ወደ ስልጠና መመለሳቸውን ተከትሎ እግር ኳስ ማህበራትና የእግር ኳስ አፍቃሪዎች በተስፋ ተሞልተው ነበር። አልቤርቶ ኮሎምቦ ግን ዋናው ትኩረታችን መሆን ያለበት ሐምሌ እና ነሐሴ ላይ ጨዋታዎቹን እንዴት ማስቀጠል አለብን የሚለው ላይ ነው፤ ከዛ በፊት ያሉት ወራት ላይ ጨዋታዎችን ማካሄድ የማይታሰብ ሊሆን ይችላል ብለዋል። «በመጀመሪያ የተጫዋቾች ስልጠና መጀመር አለባቸው። በመቀጠል የጨዋታዎቹ አዘጋጆች የደህንነት ማረጋገጫ ስራዎችን ይሰራሉ። ጨዋታዎቹ በዝግ ስታዲየሞች መከናወናቸው የማይቀር ነገር ነው። እኛ ሀሳብ እናቀርባለን እንጂ የመጨረሻው ውሳኔ ያለው የአገራቱ መንግስት ላይ ነው። የተጣሉት እገዳዎች እንደተነሱ ጨዋታዎችን ከከፍተኛ ጥንቃቄ ጋር በዝግ ስታዲየም እናከናውናለን» ሲሉ ተናግረዋል። የጣልያን እግር ኳስ ፌደሬሽን እግር ኳስ ተጫዋቾች ሌላው ቢቀር ልምምዳቸውን መስራት እንዲጀምሩ በማሰብ ከመጪው ግንቦት ወር ጀምሮ ተጫዋቾቹ ላይ የኮሮና ቫይረስ ምርምራ ማድረግ እንደሚጀምር አስታውቋል። የአውሮፓ እግር ኳስ ማህበር በበኩሉ በኮሮና ቫይረስ ምክንያት የተከሰተውን የሊጎችና ውድድሮች መቋረጥን በተመለከተ በሚቀጥለው ሳምንት ስብሰባ ያደርጋል ሲል ቢቢሲ ዘግቧል።አዲስ ዘመን ሚያዝያ 9/2012
https://www.press.et/Ama/?p=30623
229
2ስፖርት
የተወዳጁ ስፖርት በመሰናክል የተዋጀው መንገድ
ስፖርት
April 21, 2020
20
በዓለም አቀፍ ደረጃ በስፋት ከሚዘወተሩ የስፖርት አይነቶቸ በግንባር ቀደምነት ይጠቀሳል ። በተለያዩ አገራት ከፍተኛ ተቀባይነትን ማግኘት የቻለው የዳርት ስፖርት መነሻው ጥንታዊቷ ግሪክ እንደሆነች የታሪክ ድርሳናት ይናገራሉ። በግሪክ ወታደራዊ ተቋማት ውስጥ የዳርት ስፖርት በተለየ ሁኔታ ይዘወተር ነበር። በአጭር ጊዜም በአገሪቱ የሚኖረው ሌላው ማህበረሰብ አውቆት በስፋት ወደ ማዘውተር መሸጋገሩ ይነገራል፤ የዳርት ስፖርት፡ በዓለም ዓቀፍ ደረጃ በስፋት ወደ መዘውተር ሊሸጋገር የቻለውም በዚህ ሂደት ውስጥ አልፎ ነው። ዳርት አካልንና አዕምሮን የሚያነቃቃ ባህሪ የተላበሰ ስፖርት ሲሆን፤ የማሰብ ችሎታን የማሳደግ አቅም ያለው መሆኑ ስፖርቱን ተወዳጅ እንዲሆን አድርጎታል። ስፖርቱ መነሻውን ግሪክ ያድርግ እንጂ በአሁኑ ወቅት አድማሱን በማስፋት በተለያዩ አገራት በመዘውተር ላይ ይገኛል። ኢትዮጵያ ስፖርቱ መዳረሻውን ካደረገባቸው አገራት መካከል አንዷ ናት። ስፖርቱ በአገሪቱ መዘውተር ከጀመረ ረጅም ጊዜ እንዳስቆጠረም መረጃዎች ያመላክታሉ። የስፖርቱ መዘውተር የጀመረበት ዓመታትን ያስቆጠረ ቢሆንም በሚፈለገው የዕድገት ደረጃ ላይ እንደማይገኝ ይስተዋላል። ስፖርቱ ዕድሜ፣ ጾታ፣ ሃይማኖት፣ የዘርና ቀለም ልዩነት ሣይገድበው ማንኛውም ሰው አካሉንና አዕምሮውን ለማዳበር፤ ጤናውን ለመጠበቅ፣ በመስኩም ተወዳዳሪ ለመሆን የሚሳተፍበት ስፖርት ቢሆንም፤ በሁሉም ክልሎችና ከተማ መስተዳድሮች እየተዝወተረ እንደማይገኝ ለስፖርቱ ቅርብ የሆኑ ሰዎች ወቀሳ ሲሰነዝሩ ይስተዋላል። ለዳርት ስፖርት እንደሌሎች የስፖርት አይነቶች ትኩረት አለመሰጠቱም ምክንያት ተደርጎ ይነሳል። የኢትዮጵያ ዳርት ፌዴሬሽን ጽፈት ቤት ሃላፊ አቶ ጥላሁን አላምረው፤ ስፖርቱ በሚፈለገው ደረጃ እንዳያድግ ከበጀት እጥረት ጋር ተያይዞ ያሉ ችግሮች ዋነኛ ምክንያት መሆናቸውን ይናገራሉ። ይህም ስፖርቱን በብዙ መልኩ ጎድቶታል። የኢትዮጵያ ዳርት ፌዴሬሽን የዓለም አቀፍ ዳርት ፌዴሬሽን (WDF) አባል መሆኑን ተከትሎ እ.ኤ.አ በ2017 በጃፓን በሚካሄደው ዓለም አቀፍ ውድድር ኢትዮጵያ የመሳተፍ ዕድሉን አግኝታ ነበር። ለአገራችን የዳርት ስፖርት ይህ አጋጣሚ ትልቅ ቢሆንም ፌዴሬሽኑ ባለበት የበጀት ውስንነት ምክንያት ብሔራዊ ቡድኑን በዚህ መድረክ ላይ ለማሳተፍ ሳይቻል መቅረቱን እንደ ማሳያ ያስቀምጣሉ። በአገሪቱ የዳርት ስፖርት በሚፈለገው ደረጃ እንዳይጓዝ የተለያዩ ፈተናዎች እንቅፋት ቢሆኑበትም፤ ፌዴሬሽኑ ኃላፊነቱን ለመወጣት እየሠራ መሆኑን አቶ ጥላሁን ያነሳሉ። ስፖርቱን ከማስተዋወቅ፣ ከማስፋፋት አኳያ በርካታ ሥራዎችን በተለየ መልኩ በማከናወን ውጤታማ መሆንም እንደሚቻልም ይጠቁማሉ። ለዚህም በአገር አቀፍ ደረጃ የውድድር መድረኮችን እንደ ትልቅ አጋጣሚ መጠቀም አማራጭ ተደርጎ እንደተወሰደም ያመለክታሉ። ለአብነትም በኢትዮጵያ ዳርት ፌዴሬሽን አማካኝነት የሚዘጋጀው አገር አቀፍ የዳርት ቻምፒዮና ስፖርቱ በህብረተሰቡ ዘንድ ተወዳጅና ተዘውታሪ እንዲሆን ባለፉት ዓመታት ትልቅ ሚና ተጫውቷል። በአገር አቀፍ ደረጃ፣ ክልሎችና ከተማ መስተዳድሮች የሚሳተፉበት ዓመታዊ የዳርት ቻምፒዮና ስፖርቱን ከማስተዋወቅ፣ ተወዳጅና ተዘወታሪ ከማድረግ ባሻገር ታዋቂ ስፖርተኞችን ከማፍራት አኳያ አበረታች ውጤትም ማግኘት መቻሉን አብራርተዋል። የውድድር መድረኩ ለስፖርቱ ውጤታማነት ያለውን አስተዋጽኦ ለመጨመር በዘንድሮው ዓመትም ቻምፒዮናው የሚቀጥል ይሆናል። የኢትዮጵያ ዳርት ቻምፒዮና ለ14ኛ ጊዜ በመጪው ሰኔ በትግራይ ክልል አክሱም ከተማ ለማካሄድ ዝግጅት ሲደረግ የቆየ ሲሆን፤ በዓለም ዓቀፍ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ መከሰቱን ተከትሎ ሻምፒዮናው ላልተወሰነ ጊዜ መራዘሙን ነው ያመላከቱት። ብሔራዊ ፌዴሬሽኑ የስፖርቱን እንቅስቃሴ ወደ ተሻለ ደረጃ ለማድረስ እንዲህ አይነት ውድድሮችን በማዘጋጀት የሚወሰን አለመሆኑን ያነሳሉ። በማንኛውም ደረጃ የሚካሄዱ የዳርት ውድድሮች፣ ግጥሚያዎችና ጨዋታዎች ወጥ በሆነ መንገድ የሚመሩት ሥራዓቶችን በማበጀት እየተሰራ ይገኛል። ስፖርቱን ትክክለኛውን መስመር እንዲይዝ የሚያደርገውን ማንዋሉ በዘርፉ ባለሙያዎች በተዘጋጀና ዓለም አቀፍ ድንጋጌዎችን ባካተተ መልኩ የተዘጋጀ መሆኑ ውጤቱ የተሻለ እንዲሆን ያደርገዋል ሲሉ አስገንዝበዋል። በኢትዮጵያ ስፖርቱ ተወዳጅ ቢሆንም፤ እየተኬደበት ያለው መንገድ መሰናክል የበዛበት መሆኑን በመጨረሻ ያነሱት፤ ኃላፊው፤ ብሔራዊ ፌዴሬሽኑም በቀጣይ የውድድር አማራጮችን መፍጠር ያስፈልጋል። በመሆኑም የዳርት ስፖርትን የበለጠ ተወዳጅና ተዘውታሪ ከማድረግ፣ ከማዘመን፣ ስፖርታዊ ጨዋነትን ከማስፈን፣ የመረጃ አያያዝ ሥርዓትን ከማቀላጠፍ፣ በክልል ፌዴሬሽኖች፣ ማህበራትና ሌሎች ክበባት መካከል የጋራ ግንዛቤን ከማዳበር አንፃር ሰፊ ሥራዎቸን ለመሥራት ዕቅድ መያዙን አስታውቀዋል። የዓለምን ህዝብ ሥጋት ውስጥ የከተተው የኮሮና ቫይረስን በመቆጣጠር በሀገራችን መደበኛ እንቅስቃሴ መጀመር ሲቻል ፌዴሬሽኑ እነዚህና መሰል ጉዳዮች ላይ ትኩረት አድርጎ እንደሚሠራ በማስገንዘብ ሐሳበቸውን ቋጭተዋል።አዲስ ዘመን ሚያዝያ 13/2012ዳንኤል ዘነበ
https://www.press.et/Ama/?p=30805
505
2ስፖርት
ኢትዮጵያዊቷ የ5 ሺህ ሜትር ሯጯ አትሌት መሰረት ደፋር
ስፖርት
April 21, 2020
19
በመንግሥት የኮሮና ቫይረስ ወረርሽን ለመከላከል እያደረገ ለሚገኘው ርብርብ እንዲጠቀምበት ህንፃዋን በጊዜያዊነት አበረከተች። አትሌቷ ህንፃውን የፌዴራል ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ የሆኑት ወ/ሮ አዳነች አበቤ፣ የሳይንስ እና ከፍተኛ ትምህርት ሚስትር ፕሮፌሰር ሂሩት ወልደማርያም፣ በኢትዮጵያ ጤና ኢንስቲቲዩት እንዲሁም የጤና ተቋማት ዝግጁነት እና ለይቶ ማቆያ ዋና አስተባባሪ የሆኑት አቶ ኢሳያስ አገኘሁ ጨምሮ የተለያዩ የመንግሥት ሹማምንቶች በተገኙበት አስረክባለች። አትሌት መሰረት ደፋር በወቅቱ እንደተናገረችው፤ ከዚህ ህብረተሰብ መሐል የተገኘሁ ሰው ነኝ። እኔም ሆንኩ የኢትዮጵያ ህዝብ ጤና ስንሆን ነው ሁላችንም አብረን በሰላም ሰርተን የምንኖረው። ይህን ህንፃ እኔ እና ባለቤቴ ቴዲ እንገንባው እንጂ የኛ ብቻ አይደለም። ከኛ ጋር በሃሳቡ አብሮ የሮጠ የጤና ችግር ሲገጥመኝ አብሮ የታመመ የተጨነቀልኝ፤ በስፖርቱ ዓለም ለነበረኝ ያማረ ጉዞ በሙሉ ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይል ከጎኔ ሆኖ ሁሉን የተካፈለኝ የሀገሬ፣ የወገኔ፣ የኢትዮጵያ ህዝብ ህንፃ ነው ብላለች። ህንፃው አገሬንና ወገኔን በእንዲህ አስቸጋሪውን ጊዜ ካላገለገለና ካልጠቀመ ዋጋ እንዳለው የሚቆጠር አለመሆኑን ገልፃለች አያደርግም። በመሆኑም የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል እየተደረገ በሚገኘው ተግባር እንዲውል ህንፃውን በጊዜያዊነት ማስረከቧን ተናገራለች። እኛ ኢትዮጵያኖች ደግሞ አኗኗራችን በመረዳዳት፣ በመደጋገፍ፣ አብሮ በመኖርና በመብላት፣ የተሳሰር ነው። በሽታው «ደግሞ እነዚህን የማይወድ ክፉ በመሆኑ እኛም የገጠመን እባካችሁ አብሮ የመኖር አብሮ ሁሉን የመጋራት ልምዳቸንን ገታ በማድረግ ከመንግሥት ጤና ተቋማት የሚሰጡንን መመሪያዎች በመተግበር አስቸጋሪውን፣ ክፉ ጊዜ መሻገር አለብን »ብላለቸ። የፌደራል ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ የሆኑት ወ/ሮ አዳነች አበቤ በበኩላቸው፤ በእውነት መሰረት እና ባለቤቷ አቶ ቴድሮስ ህንፃው ገና ሥራ ሳይጀምር ለእንዲህ አይነት የተቀደሰ አላማ እንዲውል መስጠታቸው የሚደነቅ ተግባር ነው። ለንግድ ሥራ ተገንብቶ ሥራውን “ሀ” ብሎ ሲጀምር ለበጎ ሥራ የዋለ ወይም በበጎ ሥራ የጀመረ የመጀመሪያው የአትሌት ህንፃ ይመስለኛል። ይህን ማድረግ መቻል ደግሞ ትልቅ መባረክና ለሌሎችም አርአያ ጭምር መሆኑን አመልክተዋል። የኢትዮጵያ ፕሮፌሽናል ተጫዋቾች ማህበር ከ6 ሚሊየን ብር በላይ ድጋፍ አደረጉ የኢትዮጵያ ፕሮፌሽናል ተጫዋቾች ማህበር ለኮሮና ቫይረስ መከላከያ ያሰባሰቡትን ከ6 ሚሊየን ብር በላይ ድጋፍ አደረጉ። በማህበሩ አባላት ለኮሮና ቫይረስ መከላከያ ይውል ዘንድ ከፕሪምየር ሊግ እና ከከፍተኛ ሊግ ቡድን ተጨዋቾች ያሰባሰቡትን ከ6 ሚሊየን ብር በላይ ዕርዳታ ከትናነት በስቲያ ለድጋፍ አሰባሳቢ ኮሚቴ ሰብሳቢ አስረክበዋል። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት የመስተዳድሩ እና የስፖርት ኮሚሽን ከፍተኛ ሃላፊዎች እንደዚሁም ደግሞ የየክለቡ ካፒቴኖች እና የኢትዮጵያ ፕሮፌሽናል ተጨዋቾች አመራሮች በአዲስ አበባ ስታድየም በተገኙበት በእዚህ የገንዘብ ርክክብ ፕሮግራም ላይ ማህበሩ ይሄን ለወገን ደራሽ ወገን ነው በሚል መርህ ኮረና ቫይረስን መነሻ አድርጎ ለሰራው ሥራ ከመስተዳደሩ ከስፖርት ኮሚሽንና ከኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ከፍተኛ ምስጋና ቀርቦለታል። የመልካም ቤተሰብ – ተምሳሌት በስዊዘርላንድ ብሔራዊ ቡድን እና በስዊዝ ዋናው ሱፕር ሊግ ስኬታማ ትውልደ ኢትዮጵያዊ ታዳጊ ተጫዋቾች ሲነሳ በጥሩ ምሳሌነት ማረን ሃይለሥላሴ እና ቅዱስ ሃይለሥላሴ ይጠቀሳሉ። ታዳጊዎቹ ከወላጆቻቸው ጋር በመሆን ባሳለፍነው ሳምንት በኢትዮጵያ በቋሚነት ለሚረዱት የከለላ እግርኳስ ክለብ ታዳጊዎች እና በኮሮና ቫይረስ ምክንያት ኑሮ ለከበዳቸው የምግብ ፍጆታ ድጋፍ አድርገዋል።አዲስ ዘመን ሚያዝያ 13/2012ዳንኤል ዘነበኢትዮጵያዊቷ የ5 ሺህ ሜትር ሯጯ አትሌት መሰረት ደፋር በመንግሥት የኮሮና ቫይረስ ወረርሽን ለመከላከል እያደረገ ለሚገኘው ርብርብ እንዲጠቀምበት ህንፃዋን በጊዜያዊነት አበረከተች። አትሌቷ ህንፃውን የፌዴራል ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ የሆኑት ወ/ሮ አዳነች አበቤ፣ የሳይንስ እና ከፍተኛ ትምህርት ሚስትር ፕሮፌሰር ሂሩት ወልደማርያም፣ በኢትዮጵያ ጤና ኢንስቲቲዩት እንዲሁም የጤና ተቋማት ዝግጁነት እና ለይቶ ማቆያ ዋና አስተባባሪ የሆኑት አቶ ኢሳያስ አገኘሁ ጨምሮ የተለያዩ የመንግሥት ሹማምንቶች በተገኙበት አስረክባለች። አትሌት መሰረት ደፋር በወቅቱ እንደተናገረችው፤ ከዚህ ህብረተሰብ መሐል የተገኘሁ ሰው ነኝ። እኔም ሆንኩ የኢትዮጵያ ህዝብ ጤና ስንሆን ነው ሁላችንም አብረን በሰላም ሰርተን የምንኖረው። ይህን ህንፃ እኔ እና ባለቤቴ ቴዲ እንገንባው እንጂ የኛ ብቻ አይደለም። ከኛ ጋር በሃሳቡ አብሮ የሮጠ የጤና ችግር ሲገጥመኝ አብሮ የታመመ የተጨነቀልኝ፤ በስፖርቱ ዓለም ለነበረኝ ያማረ ጉዞ በሙሉ ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይል ከጎኔ ሆኖ ሁሉን የተካፈለኝ የሀገሬ፣ የወገኔ፣ የኢትዮጵያ ህዝብ ህንፃ ነው ብላለች። ህንፃው አገሬንና ወገኔን በእንዲህ አስቸጋሪውን ጊዜ ካላገለገለና ካልጠቀመ ዋጋ እንዳለው የሚቆጠር አለመሆኑን ገልፃለች አያደርግም። በመሆኑም የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል እየተደረገ በሚገኘው ተግባር እንዲውል ህንፃውን በጊዜያዊነት ማስረከቧን ተናገራለች። እኛ ኢትዮጵያኖች ደግሞ አኗኗራችን በመረዳዳት፣ በመደጋገፍ፣ አብሮ በመኖርና በመብላት፣ የተሳሰር ነው። በሽታው «ደግሞ እነዚህን የማይወድ ክፉ በመሆኑ እኛም የገጠመን እባካችሁ አብሮ የመኖር አብሮ ሁሉን የመጋራት ልምዳቸንን ገታ በማድረግ ከመንግሥት ጤና ተቋማት የሚሰጡንን መመሪያዎች በመተግበር አስቸጋሪውን፣ ክፉ ጊዜ መሻገር አለብን »ብላለቸ። የፌደራል ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ የሆኑት ወ/ሮ አዳነች አበቤ በበኩላቸው፤ በእውነት መሰረት እና ባለቤቷ አቶ ቴድሮስ ህንፃው ገና ሥራ ሳይጀምር ለእንዲህ አይነት የተቀደሰ አላማ እንዲውል መስጠታቸው የሚደነቅ ተግባር ነው። ለንግድ ሥራ ተገንብቶ ሥራውን “ሀ” ብሎ ሲጀምር ለበጎ ሥራ የዋለ ወይም በበጎ ሥራ የጀመረ የመጀመሪያው የአትሌት ህንፃ ይመስለኛል። ይህን ማድረግ መቻል ደግሞ ትልቅ መባረክና ለሌሎችም አርአያ ጭምር መሆኑን አመልክተዋል። የኢትዮጵያ ፕሮፌሽናል ተጫዋቾች ማህበር ከ6 ሚሊየን ብር በላይ ድጋፍ አደረጉ የኢትዮጵያ ፕሮፌሽናል ተጫዋቾች ማህበር ለኮሮና ቫይረስ መከላከያ ያሰባሰቡትን ከ6 ሚሊየን ብር በላይ ድጋፍ አደረጉ። በማህበሩ አባላት ለኮሮና ቫይረስ መከላከያ ይውል ዘንድ ከፕሪምየር ሊግ እና ከከፍተኛ ሊግ ቡድን ተጨዋቾች ያሰባሰቡትን ከ6 ሚሊየን ብር በላይ ዕርዳታ ከትናነት በስቲያ ለድጋፍ አሰባሳቢ ኮሚቴ ሰብሳቢ አስረክበዋል። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት የመስተዳድሩ እና የስፖርት ኮሚሽን ከፍተኛ ሃላፊዎች እንደዚሁም ደግሞ የየክለቡ ካፒቴኖች እና የኢትዮጵያ ፕሮፌሽናል ተጨዋቾች አመራሮች በአዲስ አበባ ስታድየም በተገኙበት በእዚህ የገንዘብ ርክክብ ፕሮግራም ላይ ማህበሩ ይሄን ለወገን ደራሽ ወገን ነው በሚል መርህ ኮረና ቫይረስን መነሻ አድርጎ ለሰራው ሥራ ከመስተዳደሩ ከስፖርት ኮሚሽንና ከኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ከፍተኛ ምስጋና ቀርቦለታል። የመልካም ቤተሰብ – ተምሳሌት በስዊዘርላንድ ብሔራዊ ቡድን እና በስዊዝ ዋናው ሱፕር ሊግ ስኬታማ ትውልደ ኢትዮጵያዊ ታዳጊ ተጫዋቾች ሲነሳ በጥሩ ምሳሌነት ማረን ሃይለሥላሴ እና ቅዱስ ሃይለሥላሴ ይጠቀሳሉ። ታዳጊዎቹ ከወላጆቻቸው ጋር በመሆን ባሳለፍነው ሳምንት በኢትዮጵያ በቋሚነት ለሚረዱት የከለላ እግርኳስ ክለብ ታዳጊዎች እና በኮሮና ቫይረስ ምክንያት ኑሮ ለከበዳቸው የምግብ ፍጆታ ድጋፍ አድርገዋል።አዲስ ዘመን ሚያዝያ 13/2012
https://www.press.et/Ama/?p=30808
800
2ስፖርት
ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች ቫይረስን ከመዋጋት አኳያ
ስፖርት
April 22, 2020
50
ዓለምን በአንድነት እያስጨነቀ የሚገኘው ወቅታዊ ጉዳይ የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ 19) ወረርሽኝ መሆኑ ይታወቃል። ታዲያ በዚህ ቫይረስ ላለመጠቃት አሊያም በቶሎ ለማገገም ከሚረዱ ጉዳዮች መካከል አንዱና ዋነኛው ስፖርታዊ እንቅስቃሴ ነው። በየዕለቱ አካላዊ እንቅስቃሴዎችን ማዘውተር አዕምሮን ከጭንቀት ነፃ ከማድረጉም በላይ አካላዊ ጤንነትን ለመጠበቅና በሽታ የመቋቋም አቅምን ለመገንባት እንዲሁም በቶሎ ከጉዳት ለማገገም ያለው ጠቀሜታ በቁጥር የሚተመን አይደለም። ይህንንም ጥናቶችና የዘርፉ ባለሙያዎች ይስማሙበታል። ሃርቫርድ ዩኒቨርሲቲ በህክምና ትምህርት ቤቱ በኩል በሚያዘጋጀው ህትመት የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል መደረግ ካለባቸው ነገሮች መካከል አንዱ በሽታን የመከላከል አቅምን ማጎልበት መሆኑን ይጠቁማል። ሰውነት በሽታን የመከላከል አቅሙን እንዲያሳድግ ከሚያደርጉ ዋነኛ መንገዶች አንዱ ደግሞ አካላዊ እንቅስቃሴ ማዘውተር ነው። የአካል ብቃት እንቅስቃሴን በመደበኛነት ማካሄድ ከልብ፣ ከደም ግፊት፣ ከሰውነት ክብደት መጨመር እንዲሁም በርካታ በሽታዎች ሊከላከል ይችላል። በተፈጥሯዊ መንገድ በሽታ የመከላከል ችሎታን የመጨመርና በጤናማ ሁኔታ እንዲቆይ ያስችላል፤ በመሆኑም እንደ ወቅታዊው ወረርሽኝ ላሉ በሽታዎች መፍትሔ መሆኑን ይመክራል ጽሑፉ። በየቀኑ ለግማሽ ሰዓት ያህል የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ማካሄድ በቫይረስ ከሚመጡና ገዳይ ከሆኑ በሽታዎች የሚታደግ መሆኑን የሚያረጋግጡት ደግሞ የጥናትና ምርምር ዩኒቨርሲቲ በሆነው (UIUC) ተመራማሪ የሆኑት ፕሮፌሰር ጄፍሪ ዉድስ ናቸው። ተመራማሪው የስፖርትና ጤና ሳይንስ ከሆነ ጆርናል ጋር ባደረጉት ቆይታ እአአ በ2000 ያደረጉትን ጥናት ዋቢ በማድረግ አካላዊ እንቅስቃሴ በሽታ የመከላከል አቅምን እንደሚያሳድግ በእንስሳት ላይ ማረጋገጣቸውን ያስረዳሉ። በኮሮና ቫይረስ ላይ እስከአሁን የተረጋገጠ ጥናት ባለመኖሩና አዲስ እንደመሆኑ እርግጥ የሆነ ነገር መናገር ባይቻልም፤ አካላዊ እንቅስቃሴን በጥንቃቄና የጤና ባለሙያዎች የሚመክሯቸውን የመከላከያ መንገዶች እየተገበሩ መሥራት ግን እጅግ ጠቃሚ መሆኑንም ያስገነዝባሉ። በቨርጂኒያ ዩኒቨርሲቲ የህክምና ትምህርት ቤት ዳይሬክተር የሆኑት ዶክተር ዢን ያን በበኩላቸው የአካል ብቃት እንቅስቃሴን ማድረግ በሳንባ ውስጥ የሚከሰቱ ህመሞችን አስቀድሞ መከላከልና መቀነስ እንደሚያስችል በጥናት መረጋገጡን ያስረዳሉ። እያንዳንዷ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ የበሽታ መከላከል አቅምን በማሳደግ በኮሮና ቫይረስ መጠቃትን ለመቀነስ የሚችልበት ሚና እንዳለው በቁጥራዊ መረጃ አስደግፈው ለኒውሮ ሳይንስ ድረገጽ ገልጸዋል። ስፖርት ከበሽታ የመከላከል አቅምን ከመፍጠሩ ጎን ለጎን ‹‹በቤት ቆዩ›› ለሚለው መመሪያም ደጋፊ ሊሆን የሚችል ቁልፍ ጉዳይ ነው። ይኸውም አብዛኛው ሰው ከቤቱ ሳይወጣ እንዲሁም ከአካባቢው ሳይርቅ እንዲቆይ የሚያደርገው የእንቅስቃሴ ገደብ ስነ-ልቦናዊና አካላዊ ተጽእኖ ማድረሱ አይቀሬ ነው። ታዲያ በዚህ ሁኔታ አካላዊ ክብደት ከመጨመር ባሻገር ጭንቀትን ተከትሎ የሚከሰቱና ድምፅ አልባ ለሆኑ በሽታዎች አጋላጭ ነው። በመሆኑም ስፖርተኞች ብቻም ሳይሆኑ ማንኛውም ሰው በቤቱም ሆነ ባለበት ስፍራ በተቻለው አቅም ሰውነትን ማንቀሳቀስና ማፍታታት አስፈላጊ ነው። በመሆኑም በሌሎች ዓለማት ባለሙያዎችና ተቋማት በስፋት በቤት ውስጥ መሠራት የሚችሉ የእንቅስቃሴ ዓይነቶችን ያፈራሉ። ዘርፈ ብዙ የሆነውን የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ጠቀሜታ ከግንዛቤ ያስገቡ አካላት በኢትዮጵያም እየሠሩ ይገኛሉ። በእርግጥ እንቅስቃሴው በጅማሬ ላይ ያለ ቢሆንም፤ አበረታች ነገር ግን ስፖርታዊ ማህበራትና ሌሎች አካላትን ጨምሮ የበርካቶች ኃላፊነት እንደመሆኑ ሁሉም የበኩሉን ርብርብ ሊያደርግ እንደሚገባ ጠቋሚ ነው። በህዝባዊ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ረገድ ፈርቀዳጅ በመሆን የሚጠቀሰው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስፖርት ኮሚሽን በዚህ ወቅትም አበተታች ሥራ እያከናወነ ነው። ኮሚሽኑ በተለይ በጋራ መኖሪያ አካባቢ በመገኘት በባለሙያዎቹ አማካኝነት አካላዊ እንቅስቃሴ አካሂዷል። ነዋሪውም በእንቅስቃሴው ተካፋይ ከመሆኑ ባለፈ በቀጣይም በምን መልኩ ከቤቱ ሳይወጣ እንቅስቃሴ እንደሚያደርግ ግንዛቤ ያገኘበት ነው። ሌላው ኢትዮጵያን ለዘመናት እያስጠራ ከዚህ የደረሰው የአትሌቲክስ ስፖርት ነው። ፌዴሬሽኑ በሃገሪቷ ከፍተኛ ሽፋን ባላቸውና ተደራሽም በሆኑ የመገናኛ ብዙሃን ታግዞ በሺዎች ለሚቆጠሩ አትሌቶቹ በቤት ውስጥ ምን ማከናወን እንደሚገባ እያስገነዘበ ይገኛል። ይህም ጠቃሚ መልዕክቶችንና ሳይንሳዊ ትንታኔዎችን ያቀፈ በመሆኑ ከአትሌቶች ባሻገር ህዝቡም ጠቃሚ መረጃ ሊያገኝበት ያስችላል። በአፍሪካ ቀዳሚና በዓለምም ስመ ጥር ከሆኑ የጎዳና ላይ ሩጫዎች መካከል ተጠቃሽ የሆነው ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያም በተመሳሳይ በዚህ ወቅትም ህዝቡ ከስፖርት መራቅ እንደሌለበት ትምህርት በመስጠት ላይ ይገኛል። ተቋሙ በዩቲዩብ ገጹ መርሐ ግብሮችን በማዘጋጀት ለግማሽ ሰዓት የሚቆይ እንቅስቃሴ በምን መልኩ እንደሚካሄድ በባለሙያዎች እያሳየ ይገኛል። ይህ ይበል የሚያሰኝ ሥራም ከስፖርታዊ አካላት ባለፈ ሁሉም ተሳታፊ ሊሆንበት የሚገባ መሆኑን በማስገንዘብ በኩልም ዘርፈ ብዙ ሥራዎች መከናወን ይኖርባቸዋል።አዲስ ዘመን ሚያዝያ 14/2012ብርሃን ፈይሳ
https://www.press.et/Ama/?p=30882
532
2ስፖርት
በቀዳማዊት እመቤት ጽሕፈት ቤት የተገነቡ ስምንት ትምህርት ቤቶች ለርክክብ ዝግጁ መሆናቸው ተገለጸ
ሀገር አቀፍ ዜና
December 30, 2020
14
 መሀመድ ሁሴንአዲስ አበባ፡- በቀዳማዊት እመቤት ጽሕፈት ቤት አማካኝነት በመገንባት ላይ የሚገኙ ግንባታቸው ከዚህ ቀደም ተጠናቆ ለአገልግሎት ከበቁ ትምህርት ቤቶች ተጨማሪ የስምንት ትምህርት ቤቶች ግንባታ ተጠናቆ ለርክክብና ለአገልግሎት ዝግጁ መሆናቸውን ጽሕፈት ቤቱ አስታወቀ። የቀዳማዊት እመቤት ጽሕፈት ዳይሬክተር አቶ ሙሉቀን ፋንታ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ የቀዳማዊት እመቤት ጽሕፈት ቤት የሚያስገነባቸው የትምህርት ተቋማት ፕሮጀክቶች በአብዛኛው በመጠናቀቅ ላይ ናቸው። ከዚህ ቀደም ግንባታቸው ተጠናቀው ስራ ከጀመሩት በተጨማሪ የስምንት ትምህርት ቤቶች ግንባታ ተጠናቆ ለርክክብና ለአገልግሎት ዝግጁ ሆነዋል። ግንባታቸው ተጠናቆ ርክክብ የሚፈጸምባቸው ትምህርት ቤቶች በአፋር ክልል ዱብቲ፣ በጋምቤላ አኝዋክ ዞን፣ በቤኒሻንጉል ክልል አሶሳ እና መተከል ዞን ፣ በሶማሌ ክልል ጅግጅጋ ዞን 02 እና 06 ቀበሌዎች፣ በአማራ ክልል ሰሜን ጎንደር ደባርቅ ከተማ እና ዋግኸምራ ዞን ሳህላ ሰለምት ወረዳ የተገነቡ መሆናቸውን አመልክተዋል።ግንባታቸው ቀድመው የተጠናቀቁና ርክክባቸው ተፈጽሞ ስራ የጀመሩት አምስት ትምህርት ቤቶች መኖራቸውን ያስታወሱት ዳይሬክተሩ፤ በአማራ ክልል ጎንደር ሎዛ ቀበሌ፣ ደቡብ ወሎ ጦሳ ፈላና ቀበሌ (አልብኮ ወረዳ)፣ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን ሊበን ጭቋላ ቀበለ (ቢሾፍቱ አካባቢ)፣ ምዕራብ ጉጂ ዞን እና ሰሜን ሸዋ ዞን ውጫሌ ወረዳ ጃቴ ቀበሌ (ሙከጡሪ አካባቢ) የሚገኙት መሆናቸውንና አሁን ላይ ተማሪዎችን ተቀብለው በማስተናገድ ላይ እንደሆኑ ገልጸዋል። በተጨማሪም ግንባታቸው እስከ ታህሳስ 30/2013 ባለው ጊዜ ውስጥ የሚጠናቀቁ አራት ትምህርት ቤቶች መኖራቸውን የጠቀሱት ዳይሬክተሩ፤ ትምህርት ቤቶቹም በደቡብ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል ሸካ ዞን፣ ጌዲኦ ዞን፣ ደቡብ ኦሞ እና በኦሮሚያ ክልል ሐዊ ጉዲና ወረዳ ሐሮ ቢሊቃ ቀበሌም እንደሚገኙ አስታውቀዋል። በአዲስ አበባ የተሰራው የሕጻናት ማሳደጊያ፣ በሰበታ ከተማ የሚገኘውን ማየት የተሳናቸው ትምህርት ቤት እና በተለያዩ ክልሎች የተገነቡትን ክፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ገንብቶ ለማጠናቀቅ ጽህፈት ቤቱ እስካሁን 760 ሚሊዮን ብር ወጪ ማድረጉንአስታውቀዋል። ገንዘቡም ከተለያዩ የውጭ አገራት ረጂ ድርጅቶች የተገኘ መሆኑን ጠቁመዋል። በዚህ ዓመትም 10 ትምህርት ቤቶችን ለመገንባት እቅድ ተይዞ የአምስቱ የግንባታ ቦታ መለየቱን የጠቀሱት አቶ ሙሉቀን፤ የእነዚህ ፕሮጀክቶች ወጪ የሚሸፈነውም የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ ከመደመር መጽሀፍ ሽያጭ ያገኙትንና ለጽህፈት ቤቱ ባበረከቱት ገንዘብ መሆኑን አስታውቀዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 21/2013
https://www.press.et/Ama/?p=38455
287
0ሀገር አቀፍ ዜና
ህብረተሰቡ የአፍ እና የአፍንጫ መሸፈኛ ጭምብሎችን በመጠቀም የጤና ባለሙያዎችን እንዲያግዝ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጥሪ አቀረቡ
ሀገር አቀፍ ዜና
December 30, 2020
5
አዲስ አበባ ፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ ህብረተሰቡ የአፍ እና የአፍንጫ መሸፈኛ ጭምብሎችን በአግባቡ በመጠቀም የጤና ባለሙያዎችን እንዲያግዝ ጥሪ አቀረቡ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በፌስ ቡክ ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት የኮቪድ-19 ታማሚዎች ቁጥር በማሻቀብ ላይ መሆኑን አስታውቀዋል።በአሁኑ ወቅት የጽኑ ሕሙማን ክፍል ያለውን ዐቅም ሁሉ አሟጦ እየሠራ እንደሚገኝ ጠቁመው ፥ በዚህ ወቅት የጥንቃቄ እርምጃዎችን ቸል ማለት እንደማይገባም አሳስበዋል። ህብረተሰቡ የራሱን ሕይወት እንዲታደግ የሌሎችንም ሕይወት እንዲያተርፍም ጥሪ አቅርበዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 21/2013
https://www.press.et/Ama/?p=38454
67
0ሀገር አቀፍ ዜና