headline
stringlengths
2
1.42k
category
stringclasses
6 values
date
stringlengths
9
35
views
stringlengths
1
7
article
stringlengths
63
36.2k
link
stringlengths
28
740
word_len
int64
16
6.74k
label
class label
6 classes
በክልሉ በዘንድሮው መኸር ወቅት ለመሰብሰብ ከደረሰው ሰብል 94 በመቶው መሰብሰቡ ተገለጸ
ሀገር አቀፍ ዜና
December 24, 2020
8
ሞገስ ጸጋዬአዲስ አበባ፡- በዘንድሮው የመኸር ወቅት ከተዘሩ የተለያዩ የሰብል አይነቶች መካከል ለመሰብሰብ ከደረሰው ሰብል ውስጥ 94 በመቶ የሚሆነውን መሰብሰብ መቻሉን የኦሮሚያ ግብርናና ተፈጥሮ ሃብት ቢሮ አስታወቀ።የቢሮው ምክትል ኃላፊ የሆኑት አቶ ጌቱ ገመቹ በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደገለጹት፤ የመኽር ሰብል ስብሰባን በተመለከተ አስፈላጊው ዝግጅት ተደርጎ ወደ ስራ ተገብቷል። በዚህም ወደፊት የሚደርሱ የጥራጥሬ ሰብሎች፣ እንዲሁም በአንዳንድ አከባቢዎች ዘግይተው ከሚደርሱ ሰብሎች ባለፈ፤ አሁን ለመሰብሰብ ከደረስው ሰብል መካከል 94 በመቶ የሚሆነውን መሰብሰብ ተችሏል።እንደ አቶ ጌቱ ማብራሪያ፤ አሁን ላይ የተሰበሰበው ሰብል በወቅቱ በሰብል ከተሸፈነው ከ6 ነጥብ 3 ሚሊዮን ሄክታር ውስጥ አምስት ሚሊዮን ሄክታር የሚሸፍን ሲሆን፤ ቀሪውን የጥራጥሬ እህልና ገና ወደ ፊት የሚደርሱ ሰብሎችን ለመሰብሰብ አስፈላጊው ዝግጅት ተደርጓል።በመጀመሪያ በክልሉ ከ6 ነጥብ 1 ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬትን በሰብል ለመሸፈን ታቅዶ የነበረ መሆኑን የጠቆሙት አቶ ጌቱ፤ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በሰጡት አቅጣጫ መሰረት ጾም የሚያድር ባዶ ቦታ እንዳይኖር ታስቦ በመሰራቱ በአርሶ አደሮች፣ በኢንቨስተሮች እና መንግስታዊና መንግስታዊ ባልሆኑ ድርጅቶች ስር ያሉ መሬቶች እንዲታረሱ በማድረግ ወደ 6 ነጥብ 3 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በማዘጋጀት በተለያዩ ሰብሎች መሸፈን መቻሉን ተናግረዋል። ከዚህም ውስጥ 191 ሚሊዮን ኩንታል እህል ለመሰብሰብ ታቅዶ አሁን ባለው የመሬት ሽፋን መሰረት ግቡን ማሳካት እንደ ተቻለ ገልጸዋል። እንደ አቶ ጌቱ ገለጻ፤ አርሶ አደሩ ልጆቹን ቤተሰቦቹን በሙሉ ይዞ እንዲሰበስብ ከክልል እስከ አርሶ አደሩ ድረስ የሚደርስ ኮሚቴ በማቋቋም አቅጣጫ ወርዶ መስራት በመቻሉ የደረሱ ሰብሎች ወቅታቸውን ጠብቀው እንዲሰበሰቡ ተደርጓል። በፍጥነትና የእህል ብክነት ሳይኖር ለመሰብሰብ ዘመናዊ ኮምባይነሮች ጥቅም ላይ ውለዋል። በተለይ የስንዴና ገብስ አምራች በሆኑ ቦታዎች በባሌ፣ በአርሲና በምዕራብ አርሲ አካባቢ በሰፊው መካናይዝድ በሆነ መንገድ እየተነሳ ነው። ይህንን ልምድ ወደ ሌላው አካባቢ በማስፋትም የደረሱ ሰብሎችን ሳይባክን ለመሰብሰብ እየሰራ ነው።ቀደም ሲል በኢንቨስተሮች እጅ የነበሩና በተያዘው አመት ብቻ ወደ ሰማኒያ የሚደርሱ ኮምባይነሮችን ለአርሶ አደሮች በማሰራጨት በጥቅሉ ከስድስት መቶ በላይ የሚሆኑ ኮምባይነሮችን ወደ ስራ በማስገባት ጥሩ ስራ ተሰርቷል። የኮምባይነሮችን ኪራይ በተመለከተም ከዚህ በፊት አንድ ኩንታል በመቶ ሃያ ብር ይሰበሰብ የነበረ ሲሆን፤ በዚህ አመት ግን በግማሽ ቀንሷል። አርሶ አደሮችም አሁን የሰብል መሰብሰብ አቅማቸው እና ዝግጁነታቸው ጥሩ እንደመሆኑ ይህን አጠናክረው መቀጠል ይኖርባቸዋል። ሰብል በሚሰበሰብበት ጊዜ በርካታ ነፍሳትና ሌሎች ፀረ ሰብል ተባዮች መኖራቸውን የሚናገሩት አቶ ጌቱ፤ አርሶ አደሩ የእህል ብክነት እንዳይኖር በጥንቃቄ መስራት እንዳለበት አሳስበዋል። በሐረርጌ አካባቢ ሁለተኛ ዙር የአንበጣ መንጋ ተከስቶ ከባድ ስጋትን እየፈጠረ መሆኑን በመጠቆምም፤ በባሌም እህል ገና ባልደረሰበት ሁኔታ አስፈሪ የሆነ የአንበጣ መንጋ ከሱማሌ እየገባ በመሆኑ ትልቅ ስጋት መፍጠሩን ተናግረዋል። አዲስ ዘመን ታህሳስ 15/2013
https://www.press.et/Ama/?p=37993
356
0ሀገር አቀፍ ዜና
አትክልት ተራው ወደ ኃይሌ ጋርመንት መዛወሩ ለግብይትም ሆነ ለሕግ ማስከበር ስራ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩ ተገለጸ
ሀገር አቀፍ ዜና
December 24, 2020
22
ሞገስ ተስፋአዲስ አበባ፡-መንግስት ማግኘት የሚገባውን ገቢ ለማግኘት፣ የግብይት ሁኔታ ምቹ ለማድረግ እንዲሁም ውጤታማ የገቢ ሕግ የማስከበር ሥራ ለማከናወን የአትክልት ተራው ወደ ኃይሌ ጋርመንት መዛወር ጠቃሚ እንደሆነ የአዲስ አበባ ከተማ ገቢዎች ቢሮ አስታወቀ።የከተማ አስተዳደሩ ገቢዎች ቢሮ የሕግ ማስከበር ዘርፍ ኃላፊ ኮማንደር አህመድ መሃመድ በተለይም ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደገለፁት በከተማ አስተዳደሩ ጥላ ሥር የከተማዋ፣ የክልልና የፌደራል ነጋዴዎች ተሰባጥረው የሚሰሩ በመሆኑ በሕገ ወጥ ነጋዴዎች ላይ የሚደረገውን ቁጥጥር አዳጋች አድርጎታል።እንደ ኮማንደር አህመድ ገለጻ፤ አንድ የአዲስ አበባ ገቢዎች የሕግ አስከባሪ አካል የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ነጋዴ ነው ብሎ ሕግ ሲያስከበር ከጎኑ ያለው ነጋዴ በፌደራል ሥር ከሆነ በዝምታ የሚያልፍበት ሁኔታ ይታያል። በተመሳሳይም የፌደራል ነጋዴውም ሕገ ወጥ ስራ እየሰራ አንተ የአዲስ አበባ ነህ፣ አንተ የኦሮሚያ ነህ አይመለከትህም የሚል አስተሳሰብ ስለነበረ ችግሩ ውስብስብ ነው ያሉት ኮማንደር አህመድ፤ ሕግ የማስከበር ተግባር በአንድ ቢሮ ብቻ የሚፈታ ስላልሆነ የበርካታ አካላትን ተሳትፎና ቅንጅት የሚጠይቅ ነው ብለዋል።ኮማንደር አህመድ እንደገለጹት የሁሉም የሕግ አስከባሪ ስራ አላማ ሕገ ወጥ ንግድን መግታት ቢሆንም በጋራና በመናበብ የመስራት ልምድ ባለመዳበሩ ክፍተቶች ይታያሉ። ክፍተቶቹ የተፈጠሩት ከክፋት ሳይሆን ከአሰራር ክፍተት ነው። ለምሳሌ የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ ተግባሩ ተፅፎ ሲሰጠው “እነዚህን ጉዳዮች ትሰራለህ፣ ሕግ ታስከብራለህ፣ ገቢ ትሰበስባለህ” ተብሎ ስለሆ ከተሰጠው ሕግ የማስከበር ስራ ውጪ ሌሎች ነጋዴዎችን የሚከታተልበት አግባብ አይኖርም። ስለዚህ ሁሉም የራሱን ግብር ከፋዮች እየለየ ይሰራል። ይህ ሁኔታ ለሕግ ማስከበሩ ፈታኝ በመሆኑ የጋራ ህብረት ፈጥሮ በትብብር መስራት ይገባል።እንደ ኮማንደሩ ገለጻ በከተማ አስተዳደሩ በነበረው የአትክልት መሸጫ ቦታ ሕጋዊ ሆኖ የመሸጥ ሁኔታው ብዙም አልነበረም። በዚህ ሁኔታ ደግሞ ከገቢ አንፃር ሲታይ ነጋዴው ሲሸጥ ደረሰኝ እየቆረጠ መንግስት ማግኘት የሚገባውን ገቢ እያስገኘ ነበር ማለት ያስቸግራል። ምክንያቱም ቦታው አንዱ ሸጦ የሚሄድበት፣ ሌላው ተቀምጦ የሚሸጥበት፣ ከፊሉ ደግሞ ቆሞ የሚስተናገድበት የተዘበራረቀ ሁኔታ በመኖሩ ለመቆጣጠር አመቺ አልነበረም። በዚህ ሁናቴ የሕግ አካላት ንግድ ፈቃድ ያለውና የሌለውን ለመለየት የሚቸገሩበት ሁኔታ በመኖሩ አሰራሩን ዘመናዊ ማድረግ የግድ እንደሆነ ኮማንደር አህመድ ተናግረዋል።ይህንን ታሳቢ በማድረግም የአትክልት ተራው ኃይሌ ጋርመንት አካባቢ በዘመናዊ መንገድ ወደ ተደራጀው ቦታ በመዛወሩ ለቁጥጥርና ለክትትል አመቺ ሁኔታ መፈጠሩንና እያንዳንዱ ነጋዴም ቁጥር ተሰጥቶት የንግድ ፈቃዱን ማሳየት በሚችልበት አግባብ ተደራጅቶ እንቅስቃሴውን መለየት በሚያስችል መንገድ መሰራቱን ኮማንደሩ ገልፀዋል።በመጨረሻም የንግዱ ማህበረሰብ የትም ሆኖ ይሰራ የትም ንግድ ፈቃድ ኖሮት ሕጋዊ ሆኖ እንዲሰራ ማድረግ የገቢዎች ህግ የማስከበር ተግባር ነው የሚሉት ኮማንደር አህመድ፤ ማንኛውም ነጋዴ ህጋዊ ሆኖ ለሚሸጠው ነገር ደረሰኝ እየቆረጠ የሚጠበቅበትን ግዴታ መወጣት እንዳለበት አሳስበዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 15/2013
https://www.press.et/Ama/?p=38005
348
0ሀገር አቀፍ ዜና
ችግሩን ለመፍታት በተለያየ መልኩ የተደረገው ጥረት ባለመሳካቱ መንግሥት ችግሩን ከመሠረቱ ለመፍታት አስፈላጊውን የተቀናጀ ኃይል እንዲሠማራ ማድረጉን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገለጹ
ሀገር አቀፍ ዜና
December 25, 2020
10
በጋዜጣው ሪፖርተርአዲስ አበባ፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ መተከል ዞን በተደጋጋሚ የሚፈጸመውን ጥቃት ከማስቆም እና ችግሩን ከመፍታት አንጻር በተለያየ መልኩ የተደረገው ጥረት ባለመሳካቱ መንግስት ችግሩን ከመሰረቱ ለመፍታት አስፈላጊውን የተቀናጀ ኃይል እንዲሰማራ ማድረጉን ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ገለጹ።ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ በቤኒሻንጉል ክልል መተከል ውስጥ በዜጎች ላይ እየተፈጸመ ያለውን ጭፍጨፋ አስመልክተው ባስተላለፉት መልዕክት፤ በአከባቢው ያለውን ችግር ከመፍታት አኳያ በተለያየ መልኩ የተደረገው ጥረት ባለመሳካቱ መንግሥት ችግሩን ከመሠረቱ ለመፍታት አስፈላጊውን የተቀናጀ ኃይል እንዲሠማራ ማድረጉን ተናግረዋል።ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመልዕክታቸው፣ “በቤኒሻንጉል ክልል መተከል ውስጥ በዜጎች ላይ እየተፈጸመ ያለው ጭፍጨፋ እጅግ አሳዛኝ ሆኗል፤ በወገኖቻችን ላይ በተፈጸመው ኢ-ሰብዓዊ ተግባር በእጅጉ አዝኛለሁ፤ ብለዋል።ችግሩን በተለያየ መንገድ ለመፍታት ያደረግነው ጥረት የሚፈለገውን ውጤት አለማምጣቱን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ “የጠላቶቻችን ዓላማ በጁንታው ላይ የሠነዘርነውን ብርቱ ኃይል ለመበተን ነው፤ ይህ የሚሳካ አይደለም፣” ብለዋል።መንግሥትም ችግሩን ከመሠረቱ ለመፍታት አስፈላጊውን የተቀናጀ ኃይል እንዲሠማራ ማድረጉን በመግለጽም፤ “የምንፈልገውን ውጤት ለማግኘት ሁላችንም እንደ ከዚህ ቀደሙ በትኩረትና በኅብረት እንድንሠራ ጥሪ አቀርባለሁ” ብለዋል።ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከሁለት ቀን በፊት በመተከል ዞን ተገኝተው ከክልሉ አመራሮች፣ ከአካባቢው ነዋሪዎች እንዲሁም የአገር ሽማግሌዎች ጋር በመወያየት የተለያዩ የመፍትሄ አቅጣጫን በማስቀመጥ ለአካባቢው ሰላም ሁሉም የሚጠበቅበትን ሊወጣ እንደሚገባ ማሳሰባቸው የሚታወስ ነው።አዲስ ዘመን ታህሳስ 16/2013
https://www.press.et/Ama/?p=38054
171
0ሀገር አቀፍ ዜና
የጋዜጠኛ እና አርቲስት ኢብራሂም ሀጂ አሊ ስርአተ ቀብር ተፈጸመ
ሀገር አቀፍ ዜና
December 24, 2020
12
 በጋዜጣው ሪፖርተርአዲስ አበባ፡- በኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ስር የሚታተመው በሪሳ ጋዜጣ በ1968 ዓ.ም ስራ ሲጀምር ከነበሩት ጋዜጠኞች መካከል አንዱ የነበሩት ጋዜጠኛ፣ አርቲስት እና በአፋን ኦሮሞ ቋንቋ ዕድገት ውስጥ ትልቅ አስተዋፅኦ ያበረከተው ኢብራሂም ሀጂ አሊ ስርዓተ ቀብር ተፈጸመ።ኢብራሂም ሀጂ አሊ ካለፈው ክረምት ጀምሮ ባጋጠመው የጤና እክል ሳቢያ የህክምና ክትትል ሲደረግለት ቆይቶ ትናንት ሌሊት ከዚህ ዓለም በሞት መለየቱ ይታወሳል። የቀብር ስነስርዓቱም ትናንት 9፡00 ሰዓት ላይ ቤተሰቦቹ፣ የስራ ባልደረቦቹ የሙያ አጋሮቹ እንዲሁም አድናቂዎቹ በተገኙበት በኮልፌ የሙስሊም መቃብር ተፈጽሟል።በ1968 ዓ.ም በሪሳ ጋዜጣ ስራ ሲጀምሩ ኢብራሂም ሀጂ አሊ አንደኛው ጋዜጠኛ ነበረው ጋዜጠኛ፣ አርቲስት እና የቋንቋ ተመራማሪው በሙዚቃ ህይወቱ በርካታ ነጠላ ዜማዎችን ያበረከተ ሲሆን፣ አራት ዓይነት የሙዚቃ መሳሪያዎችን መጫወት ይችል ነበር። ኢብራሂም ሀጂ አሊ ሙዚቃን የጀመረው ተወልዶ ባደገበት በድሬዳዋ ሲሆን በ1967/68 የአርፈን ቀሎ ባንድ 2ኛ ትውልድ በመባል በሚጠራው ከአዱ ቢራ ባንድ መስራቾች ከሚባሉት የክብር ዶክተር አርቲስት አሊ ቢራ፣ ሂሜ የሱፍ፣ አብዱ ሸኩር፣ መሀመድ ጠዊል ጋር በመሆን አንደኛው መስራች ነበረ።ከዚያን ጊዜ በኋላ የጋዜጠኝነት ህይወትን እስከሚቀላቀል የአፋን ኦሮሞ ሙዚቃን በኢትዮጵያ በሁሉም አካባቢዎች ለማስተዋወቅ እድል አግኝቶ ተጠቅሞበታል። ኢብራሂም የግጥም እና ዜማ ደራሲ እንደነበረም በቅርብ የሚያውቁት እና የእርሱን ስራዎች የተጫወቱ ይመሰክሩለታል።በ1987 ዓ.ም ሬዲዮ ፋና ሲመሰረት ፋናን ከተቀላቀሉ አንጋፋ ጋዜጠኞች መካከልም አንደኛው ሲሆን፤ ተወዳጅ የሆነውን ፋና አፋን ኦሮሞ ፕሮግራምን አዘጋጅቶ በማቅረብም ይታወቃል። ኢብራሂም በፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እስከ ኤዲተርነት ያገለገለ ሲሆን ህይወቱ እስከሚያልፍ ድረስም የስፖርት ጋዜጠኛ ነበር። አፋን ኦሮሞ በጥናት ላይ ተመስርቶ እንዲያድግም ጥረት ካደረጉ ታላላቅ ሰዎች መካከል አንደኛው እንደሆነ የዘገበው ፋና ብሮድካስት ኮርፖሬት ነው።አዲስ ዘመን ታህሳስ 15/2013
https://www.press.et/Ama/?p=38008
225
0ሀገር አቀፍ ዜና
በቀድሞ የደርግ ባለሥልጣናት ላይ የተሰጠው ውሳኔ የሕግ ጥሰት እንደሌለበት ተገለጸ
ሀገር አቀፍ ዜና
December 25, 2020
29
አዲሱ ገረመው አዲስ አበባ፡- ከፍተኛው ፍርድ ቤት በትላንትናው ዕለት በቀድሞ የደርግ ባለሥልጣናትን በአመክሮ እንዲለቀቁ ያሳለፈው ውሳኔ የትኛውንም ወገን እንደማይጎዳና የህግ ጥሰት እንደሌለበት ተገለጸ። የጊዜያዊ ወታደራዊ መንግስት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የነበሩት ኮሎኔል ብርሃኑ ባዬ እና ኤታማዦር ሹም የነበሩት ሌፍተናንት ጄኔራል አዲስ ተድላ ላይ የተሰጠው ውሳኔ ለኢትዮጵያ ቀጣይ ጉዞ የሚኖራቸው አንድምታ ከፍተኛ መሆኑም ተጠቁሟል። የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዶክተር ዳንኤል በቀለ በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደተናገሩት፤ በሰብዓዊ መብት መርኅ አስተሳሰብ የሞት ቅጣት በጣም ከፍተኛ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ስለሚያስከትል ወደ እድሜ ልክ እሥራት መቀየሩ ተገቢና ፍትሐዊ እርምጃ ነው። በቀድሞ የደርግ ባለሥልጣናት ላይ የተወሰነው ፍርድም ሕጉን ተከትሎ የተፈጸመ ሂደት ነው። እድሜ ልክ ቅጣት የሚፈረድበት ሰው 20 ዓመታት ከታሰረ በኋላ በአመክሮ ሊለቀቅ እንደሚችል የሚደነግግ ሥርዓት በመኖሩ ውሳኔው ማንንም የማይጎዳና የሕግ ጥሰትም የሌለበት ነው።እንደ ዶክተር ዳንኤል ገለጻ፤ የቀድሞ መንግስት ባለ ሥልጣናት የነበሩ ሰዎች በፍርድ ቤት ጥፋተኛነትና የቅጣት ውሳኔ ከተወሰነባቸው በኋላ የሞት ቅጣት ወደ እድሜ ልክ እስራት ሲቀየር የመጀመሪያው አይደለም። ከዚህ በፊትም የእስር ዘመናቸውን ጨርሰው የተለቀቁ ብዙ ታሳሪዎች የሞት ቅጣቱ ወደ እድሜ ልክ እስራት ተቀይሮላቸው ነው የእስር ዘመናቸውን ያጠናቀቁትና ከእስር የወጡት።በሰብዓዊ መብት መርኅ ደግሞ የሞት ቅጣት ወደ እድሜ ልክ እሥራት መቀየሩ ተገቢ እርምጃ እንደሆነ ይታመናል። ምክንያቱም የሞት ቅጣት በጣም ከፍተኛ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ስለሚያስከትል በተለይ ረጅም ጊዜ ለታሰሩ ሰዎች ወደ እስር መቀየሩ ተገቢና ፍትሐዊ እርምጃ ነው። ስለዚህ እርምጃው ሕጉን ተከትሎ የተፈጸመ ሂደት ነው።ዶክተር ዳንኤል እንደሚሉት፤ በውሳኔ አሰጣጥ ሂደቱ ላይ የሀሳብ ልዩነት ቢኖር አያስገርምም። ምክንያቱም ሁልጊዜም ቢሆን በዳኝነት ላይ ሦስት ዳኞች ሲሰየሙ ዳኞች የተለያየ አተረጓጎም ሊኖራቸው ስለሚችል ካልተስማሙ በአብላጫ ድምጽ ይወሰናል። እናም የአብላጫ ድምጽ ውሳኔው የሞት ቅጣቱ ወደ እድሜ ልክ እስራት እንዲቀየር መደረጉ፤ እድሜ ልክ ቅጣት የሚፈረድበት ሰው 20 ዓመት ከታሰረ በኋላ በአመክሮ ሊለቀቅ እንደሚችል የሚደነግግ ሥርዓት አለ። ከዚህ በፊት የተለቀቁት ብዙ የደርግ ባለሥልጣኖችም በዚሁ አይነት ሁኔታ ነው የተለቀቁት። ስለዚህ ይሄም ብዙ የተለየ አይሆንም።ምናልባት ይሄን ከዚህ በፊት ከነበሩት ለየት የሚያደርገው አሁን ጉዳዩ የሚመለከታቸው ሰዎች መንግስት እስር ቤት ውስጥ ሳይሆን ይሄንን 20 ዓመት ያሳለፉት ኤምባሲ ቅጥር ጊቢ ውስጥ መሆኑ ነው። ነገር ግን ፍርድ ቤቱ የነበሩበት ሁኔታ ከእስር ጋር የሚመሳሰል መሆኑን መሠረት አድርጎ ነው ውሳኔውን ያሳለፈው።ይሁን እንጂ ከዚህ በፊት እንደተለቀቁት የደርግ ባለስልጣናት በተለቀቁበት ወቅት ጥያቄ አስነስቶ ነበር። ከተጎጂ ቤተሰቦች አንጻር የዚህ አይነት ጥያቄ በተወሰነ መጠን ሊነሳ እንደሚችል ይገመታል። ነገር ግን ሁሉም የተጎጂ ቤተሰቦች አንድ ዓይነት ስሜትና አስተያየት አላቸው ማለት አይደለም። አንዳንድ የተጎጂ ቤተሰቦች ይሄን ያህል እስር ከተፈጸመ በቂና ተመጣጣኝ ቅጣት ነው፤ ከዚህ የበለጠ እስር ቤት መታሰር የለበትም የሚል አስተያየት ያላቸው ሰዎች ይኖራሉ። አንዳንድ የተለያየ አስተያየት ያላቸው ሰዎች ደግሞ ሊኖሩ ይችላል። ሁሉንም ሰው በእኩል ደረጃ ያስደስታል ተብሎ ባይታሰብም፤ በአብዛኛው አስተሳሰብ አንድ ሰው በጥፋቱ 20 ዓመት ያህል ከታሰረ ለጥፋቱ ተመጣጣኝ የሆነ ቅጣት አግኝቷል፣ ታርሟል፣ ተስተካክሏል ተብሎ ይገመታል።በመሆኑም በተመሳሳይ ሁኔታ ከ20 ዓመት በላይ ታስሮ ምህረት ሳያገኝ በእስር ላይ የሚገኝ ሰው ካለ ተፈጻሚ መሆን ይኖርበታል። ነገር ግን የፍርድ ምርመራቸውን ያልጨረሱ ሰዎች ይኖራሉ። ምክንያቱም አንዳንዶቹ መጀመሪያ የታሰሩ ሰዎች ሁሉ ሲታሰሩ አንድ ላይ የታሰሩ ሳይሆን በኋላ እየዘገዩ የታሰሩ ሰዎች አሉ። ከውጭ ሀገርም ታስረው የመጡ ሰዎች አሉ። ስለዚህ  እነሱ ቅርብ ጊዜ ስለነበረ የታሰሩት፤ ይሄ 20 ዓመት የሚለው ጊዜ ወይም የተፈረደባቸው የእስር ዘመን ገና አልሞላ ይሆናል። ስለዚህ ያ አንድ ሰው የተፈረደበትን የእስር ዘመን መጠበቁ የግድ ይላል።እጅግ የተከበሩ የዓለም ሎሬት ዶክተር ጥበበ የማነብርሀን የኢትዮጵያ እርቀ ሠላም ኮሚሽን አባል ኮሚሽነር በበኩላቸው እንደሚሉት፤ የጊዜያዊ ወታደራዊ መንግስት ከፍተኛ ባለ ሥልጣናት የነበሩት ኮሎኔል ብርሃኑ ባዬ (በወቅቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የነበሩ) እና ሌፍተናንተ ጄኔራል አዲስ ተድላ (በወቅቱ ኤታማዦር ሹም የነበሩ) በጣሊያን ኤምባሲ የነበራቸው ከ29 ዓመታት በላይ ቆይታ በእስር ቤት ካለው ሁኔታ የማይተናነስ በመሆኑና መብታቸው ተገድቦ በመቆየቱ በአሁኑ ጊዜ ያለው የጤንነታቸው ሁኔታ እንዲሁም የዕድሜያቸው መግፋት ካሳለፉት የማህበረሰብ የመገለል ጊዜ አንፃር ጋር ተዳምሮ ከፍተኛ የሆነ የአካልና የስነ ልቦና ጫና አሳድሮባቸው ነበር።ስለሆነም ከሰብዓዊ ርህራሔ መብት አንፃር እና ያሉበትን ሁኔታ ከግምት ውስጥ በማስገባት በአመክሮ ምህረት ተደርጎላቸው ከቤተሰቦቻቸው ጋር እንዲገናኙ መንግስትን እንድንጠይቅላቸው በተደጋጋሚ በቤተሰቦቻቸው በኩል ጥያቄ ቀርቦ ነበር። መንግስትም ጉዳዩን በሕግ አግባብ ለመፍታት የቀረበውን ጥያቄ ለማስተናገድ የሔደበትን ርቀት የሚደነቅ ነው። በተለይም ለክብርት ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ለፍትህ አካሉና ለጠቅላይ አቃቢ ሕግ ከፍ ያለ ምስጋና ይገባቸዋል።መሰል ተግባራት ለሀገራችን ቀጣይ ጉዞ የሚኖራቸው አንድምታ ከፍተኛ እንደሚሆን በማመን፤ ለዚህ ሂደት መሳካት በተለየ አግባብ ለኮሚሽናችን ድጋፍ ላደረጉ አካላት ሁሉ ከፍ ያለ ምስጋና ለማቅረብ እንወዳለን ያሉት የዓለም ሎሬት ዶክተር ጥበበ፤ በሀገራችን ኢትዮጵያ እርቀ ሰላም ለማስፈን ለምናደርገው ጉዞ አንድ እርምጃ ከፋች እንደሚሆን እናምናለን ብለዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 16/2013
https://www.press.et/Ama/?p=38059
651
0ሀገር አቀፍ ዜና
የቀድሞ መንግሥት ባለሥልጣናት በአመክሮ ተለቀቁ
ሀገር አቀፍ ዜና
December 25, 2020
8
ዳግማዊት ግርማ አዲስ አበባ፡- የቀድሞ መንግሥት ባለስልጣናት ሌፍተናንት ጄኔራል አዲስ ተድላ እና ኮሎኔል ብርሃኑ ባየህ በአመክሮ መለቀቃቸውን የኢፌዴሪ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ገለጸ። በኢፌዴሪ ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ የሙስናና የተደራጁ ወንጀል ጉዳዮች ዘርፍ ምክትል ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ አቶ ፍቃዱ ፀጋ ትናንት በሰጡት መግለጫ እንዳስታወቁት፤ የቀድሞ መንግሥት ባለሥልጣናት የፍርድ ሂደታቸው በሌሉበት የታየ እና የጥፋተኝነት ውሳኔ ተላልፎባቸው የሞት ቅጣት ተጥሎባቸው ነበር። የጣልያን ኤምባሲ የቀድሞው ደርግ ባለስልጣናት የነበሩት ሰዎች በተመለከተ በሰጠው ኦፊሴላዊ ገለጻ ግለሰቦቹ ለረጅም ዘመናት ነፃነታቸው ተገድቦ የቆዩ ከመሆናቸው በተጨማሪ ከኤምባሲው ምንም አይነት ድጋፍ አይደረግላቸውም ነበር።በመሆኑም ከቤተሰቦቻቸው በሚላክላቸው ቀለብ በአንድ ቅጥር ግቢ በተወሰነ ስፍራ ብቻ ተወስነው ከእድሜ መግፋት እና ከተፈጥሮ ህመም ጋር በተገናኘም ተገቢውን ህክምና ለማግኘት በማይችሉበት ሁኔታ ውስጥ ሆነው መቆየታቸውን ኤምባሲው ማረጋገጡን ምክትል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕጉ ገልፀዋል።የእርቀ ሰላም ኮሚሽንም ግለሰቦቹ በሕግ አግባብ ተለቀው ቤተሰቦቻቸውን እንዲቀላቀሉ ለመንግስት ምክረ ሃሳብ ማቅረቡን ያስታወሱት ምክትል ጠቅላይ አቃቤ ሕጉ፤ በተመሳሳይ የወንጀል ድርጊት ክስ ተመስርቶባቸው በእስር ላይ ቆይተው የነበሩ የቀድሞው ደርግ አመራሮችም ከ10 ዓመታት በፊት ከእስር ወጥተው ከማህበረሰቡ ጋር እንዲኖሩ መደረጉን ገልጸዋል።በተቃራኒው በጣሊያን ኤምባሲ ውስጥ ተወስነው ለ30 ዓመታት የቆዩት እነኚህ ሰዎች ከመደበኛው የእርምት ስፍራ ባልተናነሰ በተወሰነ አነስተኛ ቅጥር ግቢ ውስጥ ወደ ህክምና ተቋማት እንኳን መውጣት በማይችሉበት ሁኔታ ውስጥ ከመንግስትም ሆነ ከቆዩበት የኤምባሲ ቅጥር ግቢ አስተዳዳሪ ምንም አይነት እንክብካቤ እና ድጋፍ ሳያገኙ መቆየታቸው በእስር ቢቆዩ ኖሮ ከሚፈጠርባቸው የመብት ገደብ አንጻር ቢበዛ እንጂ የሚያንስ እንዳልሆነ ግንዛቤ መወሰዱን አመልክተዋል።በመሆኑም መንግስት ከዚህም በላይ እነኚህን ሰዎች ከዚህ በኋላ ነጻነታቸውን ገድቦ ማቆየት የፍትህ አላማን ከማሳካትም አንጻር የሚጨምረው ውጤት የማይኖር በመሆኑ፣ ከፍርደኞቹ እድሜ እና የጤና ሁኔታ አንጻር የሰብዓዊነት እይታን ከግምት በማስገባት በግለሰቦቹ ላይ ተወስኖ የነበረውን የሞት ፍርድ ወደ እድሜ ልክ ጽኑ እስራት እንዲቀየር ለኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ሃሳብ ማቅረቡን ጠቁመዋል። በዚሁ ሃሳብ መሰረት ፕሬዚዳንቷ ቅጣቱ ወደ እድሜ ልክ ጽኑ እስራት ሕገ-መንግስቱ በሚፈቅደው መሰረት እንዲለወጥ መወሰናቸውን በመግለጽ፤ በዚህም መሰረት መንግስት ግለሰቦቹ ካሉበት ስፍራ መውጣት ስለሚችሉበት ሁኔታ ከሕግ ማዕቀፍ እይታ አንጻር አስፈላጊውን ጥናት አድርጎ ግለሰቦቹ እስካሁን በኤምባሲው ቅጥር ግቢ ውስጥ ነጻነታቸው ተገድቦ መቆየቱ አስተማሪነት ያለው መሆኑ ከግምት ገብቶ በአመክሮ እንዲለቀቁ አቤቱታ ለፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የቀረበ ሲሆን ፍርድ ቤቱም የቀረበውን አቤቱታ ተቀብሎ ግለሰቦቹ በአመክሮ እንዲለቀቁ መወሰኑን አስረድተዋል።የመንግስት ስርዓት ለውጡን ተከትሎ በጊዜያዊ ወታደራዊ አስተዳደር ደርግ መንግስት በኃላፊነት ላይ የነበሩ እና በወቅቱ ተፈጽሞ በነበረ ወንጀል ተጠርጥረው እና ክስ ተመስርቶባቸው ከነበሩት አመራሮች እና የደርግ አባላት የተወሰኑት ተጠርጣሪዎች ቀደም ብለው በአዲስ አበባ ከተማ ወደሚገኘው የጣሊያን ኤምባሲ ገብተው በዚያው ለ30 ዓመታት መቆየታቸው ይታወሳል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 16/2013
https://www.press.et/Ama/?p=38061
361
0ሀገር አቀፍ ዜና
የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር አዲስ የካቢኔ አባላትን ይፋ አደረገ
ሀገር አቀፍ ዜና
December 25, 2020
10
በጋዜጣው ሪፖርተር አዲስ አበባ፡- በትግራይ ክልል አዲስ የካቢኔ አባላት ተሹመው ወደ ስራ መግባታቸውን የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር አስታወቀ። እንደ ኢዜአ ዘገባ፣ የአስተዳደሩ የጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ገብረመስቀል ካሣ በክልሉ ከሚያስፈልጉ 16 የካቢኔ አባላት መካከል 11 ተሿሚዎች በይፋ ስራ መጀመራቸውን ገልጸዋል።በዚሁ መሠረት፡- ዶክተር ካህሣይ ብርሃኑ …… የክልሉ ፋይናንስ ቢሮ ኃላፊኢንጂነር አሉላ ሃብተአብ …… የኮንስትራክሽን፣ መንገድና ትራንስፖርት ቢሮ ኃላፊዶክተር ፋሲካ አምደ ስላሴ …… የጤና ቢሮ ኃላፊአቶ አበራ ንጉሴ ………. የፍትህ ቢሮ ኃላፊወይዘሮ እቴነሽ ንጉሴ ……… የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊአቶ ዮሴፍ ተስፋይ ………. የንግድ፣ ኢንዱስትሪና ከተማ ልማት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ተስፋይ ሰለሞን …….. የትምህርት ቢሮ ኃላፊዶክተር ገብረህይወት ለገሠ ……. የውሃ ጥናትና ዲዛይን ቢሮ ኃላፊአቶ ሰለሞን አበራ …….. የውሃ ሃብት ቢሮ ኃላፊአቶ አብርሃ ደስታ ……. የማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ እና አቶ ገብረመስቀል ካሣ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የጽህፈት ቤት ኃላፊ ሆነው መሾማቸው ተገልጿል።ሌሎች ያልተሟሉ የካቢኔ አባላት በቀጣዮቹ ሳምንታት ተሟልተው ወደ ስራ ይገባሉአዲስ ዘመን ታህሳስ 16/2013
https://www.press.et/Ama/?p=38069
141
0ሀገር አቀፍ ዜና
በመተከል እየተፈጸመ ያለው ግድያ በክልሉ የሰብዓዊ መብት ጥበቃ እጅጉን መዳከሙን እንደሚያሳይ ኢሰመኮ ተናገረ
ሀገር አቀፍ ዜና
December 25, 2020
18
 በጋዜጣው ሪፖርተር አዲስ አበባ፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን እየተበራከተ የመጣው እና ከሰሞኑ ሌሊት ላይ የታጠቁ ኃይሎች በእንቅልፍ ላይ በነበሩ ነዋሪዎች ላይ በለኮሱት እሳት እና በተኩስ ከ100 በላይ ሰዎች መገደላቸው በክልሉ ያለው የሰብአዊ መብቶች ጥበቃ በከፍተኛ ሁኔታ እየተዳከመ መሄዱን የሚያሳይ መሆኑን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ገለጸ። ኮሚሽኑ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ የሰዎች ደኅንነት ማረጋገጥ ቀዳሚው የመንግሥት ግዴታ መሆኑንም ተናግሯል።ኮሚሽኑ ታኅሣሥ 14 ቀን 2013 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ እንዳመለከተው፤ ታኅሣሥ 13 ቀን 2013 ዓ.ም. በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል፣ መተከል ዞን፣ ቡለን ወረዳ፣ በኩጂ ቀበሌ ከሌሊቱ 10፡00 ሰዓት ላይ የታጠቁ ኃይሎች በእንቅልፍ ላይ በነበሩ ነዋሪዎች ላይ በለኮሱት እሳት እና በተኩስ ከ100 በላይ ሰዎች መገደላቸው በክልሉ ያለው የሰብአዊ መብቶች ጥበቃ በከፍተኛ ሁኔታ እየተዳከመ መሄዱን ነው። በመሆኑም በቤኒሻንጉል ጉሙዝ የሰዎች ደኅንነት ማረጋገጥ ቀዳሚው የመንግሥት ግዴታ ነው።በመግለጫው እንደተመላከተው፤ ኢሰመኮ የጥቃቱን ሂደት በተመለከተ ታኅሣሥ 14 ቀን 2013 ዓ.ም ከሚመለከታቸው አካላት እና ከተጎጂዎች ጋር በመነጋገር ሲከታተልና ሲያጣራ ቆይቷል። በኩጂ ቀበሌ ከወረዳው መቀመጫ ከሆነችው ቡለን ከተማ 90 ኪ.ሜ. ርቃ የምትገኝ ሲሆን የሺናሻ፣ የኦሮሞና የአማራ ተወላጆች ይኖሩባታል። ለቀበሌው የተመደበ የፖሊስ ወይም የፀጥታ ኃይል አለመኖሩን ኮሚሽኑ በክትትሉ መሰረት ተረድቷል። ኮሚሽኑ ሁኔታውን እስካጣራበት ጊዜ ድረስ በቡለን ሆስፒታል 36 ተጎጂዎች እርዳታ እየተደረገላቸው ሲሆን አብዛኞዎቹ በጥይት ሌሎቹ በቀስት የቆሰሉ መሆናቸውን ኢሰመኮ በምልከታ አረጋግጧል። በተጨማሪም ሰዎች ጥቃት የደረሰባቸውን ሁኔታ የሚያሳዩና የሚረብሹ የፎቶግራፍ ማስረጃዎች ለኮሚሽኑ ደርሰውታል። በሰው ሕይወት እና በአካል ላይ ከደረሰው ጉዳት በተጨማሪ የደረሱ ሰብሎችና የተሰበሰቡ ማሳዎች በእሳት ጋይተዋል። ቢያንስ 18 ያክል ነዶዎች ሲቃጠሉ ማየታቸውን አንድ ተጎጂ አስረድተዋል። በጨላንቆ እና ዶሼ ቀበሌዎች ቤቶች እየተቃጠሉ እንደሆነ ከአካባቢው ለኮሚሽኑ የተላኩ መረጃዎች ያመለክታሉ። በድባጤ ወረዳ ዶንበን ቀበሌ ስጋት የገባቸው ነዋሪዎች ከታኅሣሥ 14 ቀን 2013 ዓ.ም. ጀምሮ ቀዬአቸውን ጥለው እየተሰደዱ እንደሆነም ኮሚሽኑ ረድቷል። አካባቢውን በቅርበት እንዲጠብቅ የተመደበው ብሔራዊ የመከላከያ ሠራዊት ታኅሣሥ 13 ቀን 2013 ዓ.ም. ለማረጋጋት ተግባር ወደቦታው ተልከው የነበሩ አንድ የፌዴራል እና ሁለት የክልሉ አመራሮችን ለማጀብ በሚል አካባቢውን ለቅቆ መሄዱ ታውቋል።ጥቃቱ የጀመረው ይህንኑ ተከትሎ እንደሆነና ሌሊቱን የጀመረው ጥቃት እስከ ቀኑ አጋማሽ ድረስ መዝለቁንም ለማወቅ ተችሏል። ኮሚሽኑ ያነጋገራቸው ተጎጂዎች እንደሚሉት በጥቃቱ ከሞቱ ሰዎች መካከል አብዛኛው የሺናሻ ተወላጆች ናቸው። ከዚህ ቀደም በነበሩ ጥቃቶች ፈጻሚዎቹ ከ”ጫካ” የሚመጡ ሰዎች የነበሩ ቢሆንም፣ በዚህኛው ጥቃት “በስምና በመልክ የሚያውቋቸው”የበኩጂ ቀበሌ ነዋሪዎች ጭምር መሳተፋቸውን ከጥቃቱ የተረፉ ተጎጂዎች ገልጸዋል። ኢሰመኮ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ የሚከሰቱ ጥቃቶችን ተደጋጋሚነትና የክልሉን ሰብዓዊ መብቶች ጥበቃ ሁኔታ አስመልክቶ፣ የፌዴራሉንና የክልሉን መንግሥታት የተጠናከረ ትብብርና ከፍተኛ ትኩረት እንደሚሻ ሲያሳስብ መቆየቱ ይታወሳል። ይሁንና ጥቃቶቹ በመልክ እና በስፋት እየተባባሱ መጥተዋል። ስለሆነም፣ በጥቃቱ ጉዳት ለደረሰባቸው እና ለተፈናቀሉ ሰዎች የህክምና እና ሰብዓዊ እርዳታ እንዲቀርብ፣ እንዲሁም ተገቢው ማጣራትና ጥቃቱን ባለመከላከልም ሆነ በሌላ መልኩ ጥቃቱን የፈጸሙና ያባባሱ ሰዎችን ሕግ ፊት የማቅረቡ ሂደት ከወዲሁ እንዲጀመር ኮሚሽኑ ያሳስባል። በአካባቢው የሚገኘውን የፀጥታ ኃይልና መዋቅር የሰዎችን ደኅንነት ሙሉ በሙሉ ለማረጋገጥ በሚያስችል መልኩ በከፍተኛ ደረጃ በአፋጣኝ እንዲጠናከር ኢሰመኮ ጥሪ አቅርቧል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 16/2013
https://www.press.et/Ama/?p=38060
414
0ሀገር አቀፍ ዜና
የቦስተን ማራቶን አሸናፊዎች ከዓለም ቻምፒዮኖች ጋር ይፋለማሉ
ስፖርት
February 1, 2020
14
ከዓለም ምርጥ የማራቶን ውድድሮች መካከል አንዱ የሆነው የቦስተን ማራቶን ከዚህ ቀደም ማሸነፍ የቻሉና የዓለም ቻምፒዮን የሆኑ አትሌቶች ዘንድሮ የሚፋለሙበት በመሆኑ በጉጉት እየተጠበቀ ይገኛል። የዓለም አትሌቲክስ የፕላቲኒየም ደረጃ የሰጠው ይህ ውድድር በተለይ በሴቶች ምድብ ባለ ክብረወሰኗን ኢትዮጵያዊት አትሌት ወርቅነሽ ደገፋን ጨምሮ ከዓለም ዙሪያ የተሰባሰቡ አምስት ከ2 ሰዓት ከ20 ደቂቃ እንዲሁም አስራ ሁለት 2 ሰዓት ከ23 ደቂቃ በታች ማራቶንን ማጠናቀቅ የቻሉ አትሌቶች ተሳታፊ መሆናቸው ውድድሩን ተጠባቂ አድርጎታል። የአሸናፊነት ቅድመ ግምቱ ለቦታው ባለ ክብረወሰን ለሆነችው አትሌት ወርቅሽ የሚሰጥ ቢሆንም፤ ከባድ ፉክክር የሚገጥማት መሆኑ ውድድሩን ይበልጥ አጓጊ አድርጎታል። እአአ በ2018 የውድድሩ አሸናፊ የነበረችው አሜሪካዊቷ ዴስሬ ሊንደን፣ የሁለት ጊዜ በየዓለም ቻምፒዮናዋ ኬንያዊት ኤድና ኪፕላጋት፣ እአአ በ2015 የቦታው ባለ ድል ካሮላይን ሮቲች እንዲሁም እአአ በ2014 የቦታውን ክብረ ወሰን የሰበረችው ኢትዮጵያዊቷ ብዙነሽ ዳባ የቦስተን ከተማ በምታስተናግደው ታላቁ የጎዳና ላይ ሩጫዋ ድምቀት የሚሆኑና ከ2 ሰዓት ከ20 ደቂቃ በታች መሮጥ የቻሉ አትሌቶች መሆናቸውን አዘጋጆቹ አረጋግጠዋል። እአአ በ2015 የዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮና ነሃስ ሜዳሊያ ባለቤቷ ማሬ ዲባባ እንዲሁም በዚያው ቻምፒዮና የ10 ሺ ሜትር የብር ሜዳሊያ ያገኘችው ገለቴ ቡርቃ፣ መስከረም አሰፋ፣ የብርጓል መለሰ፣ በሱ ሳዶ እንዲሁም ሃፍታምነሽ ተስፋይ ደግሞ ሌላኛዎቹ በውድድሩ ጠንካራ ተፎካካሪ እንደሚሆኑ የሚጠበቁ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ናቸው። የ2017ቱ የዓለም ቻምፒዮን ባህሬናዊቷ ሮዝ ቺሊሞ፤ ያለፈው ዓመት የቶሮንቶ ማራቶን አሸናፊዋ ማግዳላይኔ ማሳይ፣ በሮም ማራቶን የሶስት ጊዜ ባለድል ራህማ ቱሳ፣ በ2018 ቦስተን ማራቶንን በሶስተኝነት ያጠናቀቀችው ክሪስታ ዱቼኔ እንዲሁም የሁለት ጊዜ የዓለም ግማሽ ማራቶን ቻምፒዮናዋ ሜሪ ንጉጊም በዚህ ማራቶን ላይ ተሳታፊ የሚሆኑና ለአሸናፊነቱ ቀላል ግምት የማይሰጣቸው አትሌቶች ናቸው። በወንዶች በኩልም ብርቱ ፉክክር እንደሚኖር ማሳያ የሆኑ አትሌቶች እንደሚካፈሉ የታወቀ ሲሆን፤ ከእነዚህ መካከል አስር የሚሆኑት ማራቶንን 2 ሰዓት ከ07 እና ከዚያ በታች የሆነ ሰዓት ማጠናቀቅ የቻሉ አትሌቶች ናቸው። ያለፈው ዓመት የቦስተንና የቺካጎ ማራቶን አሸናፊው ኬንያዊ አትሌት ላውረንስ ቼሮኖ ክብሩን እንደያዘ ለመቆየት፤ ከዚህ ቀደም የነበሩ የቦስተን ማራቶን አሸናፊ አትሌቶችን መጋፈጥ የግድ ይለዋል። የሁለት ጊዜ የቦስተን ማራቶን አሸናፊውና የዶሃው የዓለም ቻምፒዮና ባለድሉ ሌሊሳ ዴሲሳ ዘንድሮም ሌላ ድል ለማስመዝገብ በቦስተን የሚገኝ መሆኑን አስታውቋል። እአአ የ2017 አሸናፊው ጃፓናዊ ዩኪ ካዋቺ እና የ2018ቱ የወርቅ ሜዳሊያ ባለቤቱ ጂኦፈሪ ኪሩይም በቦታው ድላቸውን ለመድገም ተዘጋጅተዋል። ኡጋንዳዊው የኦሊምፒክና የዓለም ቻምፒዮን ስቴፈን ኪፕሮቲች፣ አልበርት ኮሪር፣ ኤርትራዊው አብራር ኦስማን፣ ኢትዮጵያውያኑ ደጀኔ ደበላ፣ ፍቅሬ በቀለ፣ ጀማል ይመር እንዲሁም ከሌሎች አገራት የተውጣጡ በርካታ አትሌቶችም በአሜሪካው ግዙፍ የጎዳና ላይ ሩጫ ተሳታፊ መሆናቸውን አዘጋጆቹ አስታውቀዋል።አዲስ ዘመን ቅዳሜ ጥር 23/2012 ብርሃን ፈይሳ
https://www.press.et/Ama/?p=26509
349
2ስፖርት
የከዋክብቶች አርዓያው ኮከብ አሳዛኝ መጨረሻ
ስፖርት
February 2, 2020
67
ዓለማችን በታሪኳ ካየቻቸው የቅርጫት ኳስ ከዋክብቶች መካከል በግንባር ቀደምትነት ይጠቀሳል። ከስፖርቱ ዓለም ስኬቱ ባሻገር በተለያዩ ታላላቅ መድረኮች የሚያደርጋቸው አነቃቂ ንግግሮች ተወዳጅነትን ከማፍራት ባሻገር ለበርካታ የዓለማችን ወጣቶች አርዓያ መሆን ችሏል። ከቅርጫት ኳስ አፍቃሪዎች አልፎም ተፅዕኖው በሌሎች ስፖርተኞችና ከስፖርቱ ዓለም ውጪ ባሉ ወጣቶች ላይ ማረፍ ችሏል። ለዓለማችን በርካታ ከዋክብት ስፖርተኞች የአሸናፊነትና ጥሩ ምግባር አርዓያ የሆነው ኮከብ የቅርጫት ኳስ ተጫዋች ኮቤ ቢን ብርያንት ባለፈው ሳምንት በድንገተኛ የሄልኮፕተር መከስከስ አደጋ ሕይወቱ ማለፉ የስፖርት ቤተሰቡን ቢያስደነግጥም አመለ ሸጋው ኮከብ ወደ ፊትም ሲታወስ ይኖራል። ኮቢ ብራይንት እ.ኤ.አ በ1978 በፊላዴልፊያ የተወለደ ሲሆን ወላጅ አባቱ ጆኢ ብራይንት የቅርጫት ኳስ ተጫዋች ነበር። ኮቢ ማለት በጃፓን ተወዳጅ የስጋ ምግብ ነው። ይህም የቅርጫት ኳስ ፈርጥ ስሙን ከዚሁ አግኝቷል። 1 ሜትር ከ98 ሴንቲ ሜትር የሚረዝው ኮቢ ብራያንት 96 ኪሎ ግራም ይመዝናል። የ41 ዓመቱ ኮቢ አምስት ጊዜ የኤን ቢ ኤ ቻምፒዮን በመሆን በቅርጫት ኳስ ታሪክ ትልቅ ስምና ዝና ማትረፍ ችሏል። በ 20 ዓመት የቅርጫት ኳስ ፕሮፌሽናል ህይወቱ አያሌ ክብሮችን የጨበጠው ኮቢ ሁለት ጊዜ የኦሊምፒክ ቻምፒወን ሲሆን በ 2008 በመድረኩ ውዱ ተጫዋች መሆን ከመቻሉም በተጨማሪ 2006 ላይ ከቶሮንቶ ራፕቶርስ ጋር በገጠመበት ጨዋታ 81 ቅርጫቶችን በማስቆጠር 2ኛው የምንጊዜም ከፍተኛ ቅርጫት አስቆጣሪ ሆኖ በታሪክ ተመዝግቧል። የሀብት መጠኑ እስከ 650 ሚሊየን ዶላር የሚገመተው ኮቢ ብራያንት ለበርካታ ክዋክብት ስፖርተኞች እውነተኛ አርዓያ በመሆን መነሳሳትን የፈጠረ ታሪክ አኑሮ በካሊፎርንያ በደረሰው የሄሊኮፕተር መከስከስ አደጋ በ 41 ዓመቱ ህይወቱ አልፏል። ሁነቱን አስከፊ የሚያደርገው ደግሞ በአደጋው ወደፊት የአባቷን ሌጋሲ ለማስቀጠል ተስፋ የተጣለባት የ 13 ዓመቷ ጂያና ብራያንት ከአባቷ ጋር ህይወቷ ማለፉ ነው። ሌሎች ሰባት ሰዎችም በአደጋው ህይወታቸው አልፏል። የ 13 ዓመቷ ታዳጊ ጂያና ለመምባ ስፖርትስ አካዳሚ እየተጫወተች የምትገኝ ሲሆን በታሪካዊው የቅርጫት ኳስ ባለሟል በሆነው አባቷ እየሰለጠነች ጨዋታዋን ለማከናወን አገር አማን ብላ እየበረረች ባለበት ሰዓት ያልታሰበውና የሚሊዮኖችን ልብ የሰበረው የእርሷንና አባቷን ህይወት የቀጠፈው መሪር አደጋ ተከሰተ። ከ 4ቱ ልጆች 2ኛ የሆነችው ጂያና ፈጣን ፣ ቀልጣፋና ለቅርጫት ኳስ ጥልቅ ፍቅር የነበራት ሲሆን ከአባቷ የወረስችው እምቅ የክህሎት ሀብት ወደፊት የአባቷን ሌጋሲ ከማስቀጠልም ባለፈ ለቅርጫት ኳሱ አዲስ አብዮት እንደምታመጣ በርካቶች አመኔታ ጥለውባት ነበር። ለስፖርት የተጻፈን የፍቅር ደብዳቤ የሚተርክ 5 ደቂቃ የሚቆይ የአንሜሽን ፊልሙ በ 2018 ታላቁን የኦስካር ሽልማት አሸናፊ ያደረገው ኮቢ ብራያንት ከውድ ልጁ ጋር ወደ ማይመለስበት ዓለም ለመሄድ ተገዷል። የኮቢ ብራይንት ህልፈት የዘንድሮውን 62ኛውን የግራሚ ሽልማት ላይ የኀዘን ድባብ የፈጠረ ሲሆን የመድረኩ መሪ የሆነችው አሊሻ ኪስ መታሰቢያነቱ ‹‹ለእርሱ ይሁን›› ብላለች። ‹‹ከደቂቃዎች በፊት ሎስ አንጀለስ ፣ አሜሪካና መላው ዓለም ጀግናውን ተነጠቀ። ኮቢ ብራያንት የተለየና ለሚሊዮኖች መነሳሳትን የፈጠረ ዘመን ተሻጋሪ ነው። በሆነው ነገር ልባችን ክፉኛ ተሰብሯል›› ስትልም ታሪካዊውን የቅርጫት ኳስ ባለሟል አስባለች። በሎስ አንጀለስ ሌከርስ የክለብ ቆይታው 5 ጊዜ ቻምፒወን የሆነው ኮቢ ብራያንት ህልፈቱ ከተሰማ በኋላ በአሜሪካ የተሰናዱት ዝግጅቶች በታላቅ ክብር አስበውታል። የቅርጫት ኳስ ጨዋታዎች ሲከናወኑ አባታቸውን በማሰብ ለደቂቃ የቆየ የህሌና ጸሎት አድርገዋል። የእግር ኳሱ ዓለም ኮከቦችና ዝነኛ ክለቦች በኮቢ ብራያንት ህልፈት የተሰማቸውን ጥልቅ ኀዘን ከመግለፅ ወደ ኋላ አላሉም። ብራዚላዊው ኮከብ ኔይማር ጁኒየር ከሊል ጋር በተደረገው ጨዋታ 2 ጎሎችን ያስቆጠረ ሲሆን 2ኛውን ጎል መታሰቢያነቱ ለኮቢ ብራያንት አድርጓል። ቄንጠኛው ተጫዋች የእጆቹን ጣቶች ወደ ሰማይ ከፍ በማድረግም ኮቢ ብራያንትን በልዩነት አስቧል። ‹‹በመልካም ስነምግባር የታነጸው የአሸናፊነት መንፈስህ አሁን ላለሁበት ጥሩ ደረጃ መሰረት ሆኖኛል። አንተ ሁልጊዜም ለየት ያለ ማንነትን በመላበስ ነገን ለሚኖሩ ተምሳሌት ሆነሃል ፣ ጥለኸን በመሄድህ ልቤ በኀዘን ተሰብሯል፣ እጅግ በጣም እወድዳለሁ›› ሲል ቤልጄማዊው አጥቂ ሮሜሉ ሉካኩ የህይወት ምሳሌው ስለነበረው ኮቢ ብራያንት ህልፈት የተሰማውን ጥልቅ ኀዘን ገልጿል። በቅርጫት ኳስ ሜዳ ላይም ሆነ ከሜዳ ውጪ ለሁሉም ስፖርተኞች እውነተኛ ምሳሌ መሆኑን የጠቀሰው የባርሴሎና እግር ኳስ ክለብ ‹‹በሆነው ነገር አዝነናል ለቤተሰቦችህና በአጠቃላይ ለሚወዱህ መጽናናትን ከልብ እንመኛለን›› ሲልም ባርሰሎና እንደ ክለብ ተመኝቷል። ፖርቱጋላዊው ኮከብ ክርስቲያኖ ሮናልዶ በተፈጠረው ነገር መደናገጡን ገልጾ ‹‹ኮቢ ብራያንት ለበርካቶች አርዓያ የሆነ›› ሲልም አክሏል። ሮናልዶ ቀጥሎም ለቤተሰቦቹና በአደጋው ጉዳት ለደረሰባቸው ሁሉም ቤተሰቦች መጽናናትን ከልብ ተመኝቷል። ኤሲ ሚላን ‹‹ጨለማውን ክስተት ለመግለጽ ቃላቶች የሉንም ፣ በስፖርቱ ዘመን ተሻጋሪ ከሆኑ ጀግኖች ዋና ተዋናዩን አጥተናል። ስላበረከትከው እጹብ ድንቅ ነገር እና ስለደገፍከን ልባዊ ምስጋናችን በአለህበት ይድረስ፣ ስለ እውነት ሁላችንም ተደናግጠናል ሲል ደጋፊው ስለነበረው ኮቢ ኀዘኑን ገልጿል። ‹‹ለዚህ ትውልድ ትልቅ ተምሳሌት በመሆን ለበርካቶች በተስፋ ውስጥ መልካም ህይወት እንዳለ መምህር ሆነሃቸዋል። ለነብስህ ፍጹም ሰላምን ይስጣት›› አንድሪያ ፒርሎ የተመኘው ልባዊ የኀዘን ምኞት ነው።አዲስ ዘመን ጥር 24/2012 ቦጋለ አበበ
https://www.press.et/Ama/?p=26562
628
2ስፖርት
ኢትዮጵያ የፊፋን ጠቅላላ ጉባኤ ለማስተናገድ ዝግጅት ላይ ነች
ስፖርት
February 1, 2020
10
የዓለምን እግር ኳስ የሚመራውና 211 አባላት ያሉት ፊፋ ዓመታዊ ጠቅላላ ጉባኤውን ከአራት ወራት በኋላ ያደርጋል። ለአዘጋጅነቱ ደግሞ አፍሪካ የተመረጠች ሲሆን፤ የአህጉሪቱ መቀመጫ የሆነችው አዲስ አበባም ኃላፊነቱን ተረክባ ወደ ዝግጅቱ በመንደርደር ላይ ትገኛለች። ከሁለት ዓመታት በፊት የካፍን 60ኛ ዓመት ምስረታ ተከትሎ ጠቅላላ ጉባኤውን በስኬት ያጠናቀቀችው አዲስ አበባ ፤ 69ኛውን ጉባኤ ባሰናዳችውና ፕሬዚዳንት ጂያኒ ኢንፋንቲኖን ዳግም ለመሪነት በተመረጡበት የፓሪሱ ጉባኤ ላይ 70ኛውን መድረክ እንድታዘጋጅ መመረጧ ይታወቃል። ለዚህ የሚሆነውን ዝግጅት አስቀድማ የጀመረችው ኢትዮጵያ ለጉባኤው አስፈላጊ በሆኑ ጉዳዮች ላይ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን ከሰሞኑ ምክክር ያደረጉ መሆኑን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በድረ ገጹ አስነብቧል። ዝግጅቱን ለማድረግም ከስፖርት ኮሚሽን፣ እግር ኳስ ፌዴሬሽን፣ ፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን፣ የአዲስ አበባ ፖሊስ፣ የሴቶች ህጻናትና ወጣቶች ሚኒስትር፣ የባህልና ቱሪዝም ሚኒስትር፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር፣ የፕሬዚዳንት ጽህፈት ቤት፣ የኢሚግሬሽን ጉዳዮች፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጽህፈት ቤት፣ ኦሊምፒክ ኮሚቴ፣ አየር መንገድ፣ ገቢዎችና ጉምሩክ፣ የወጣቶች ስፖርት አካዳሚ፣ ጤና ጥበቃ ሚኒስትር፣ የብሮድካስት ባለስልጣን፣ ብሄራዊ መረጃ መረብ ደህንነት ኤጀንሲ የተውጣጡ አካላት ጥምረት ፈጥረዋል። ለጉባኤው ዝግጅት የሚያደርግ ብሄራዊ አብይ ኮሚቴም የተዋቀረ ሲሆን፤ የኮሚቴው የበላይ ጠባቂም የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ሳህለ ወርቅ ዘውዴ ናቸው። ሰብሳቢዎቹ ደግሞ ኮሚሽነሩ አቶ ኤሊያስ ሽኩርና የፌዴሬሽኑ ፕሬዚዳንት አቶ ኢሳያሥ ጂራ መሆናቸው ታውቋል። በመጠናቀቅ ላይ ባለው ሳምንትም ኮሚቴው በዕቅድ ዝግጅቱ ላይ ውይይት ያደረገ ሲሆን፤ የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር አቶ ዱቤ ጂሎ፣ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ኢሳያሥ ጂራ፣ የካፍ ተወካይ ወይዘሪት መስከረም ታደሰ እንዲሁም ሌሎች ተገኝተዋል። ጉባኤው ውጤታማ በሆነ መልኩ እንዲካሄድ የሚያስችል መነሻ ሰነድ ቀርቦም ምክክር ተደርጎበታል። በፊፋ ኮርፖሬት ኢቨንት ማናጀር ካትሪን አስተርበርገር በበኩላቸው ለጉባኤው ዝግጅት በቀዳሚነት መከናወን ያለባቸው ጉዳዮች ላይ ገለጻ አድርገዋል። ከተማዋ ትልልቅ ስብሰባዎችን ለማስተናገድ አዲስ ባትሆንም ወሳኝ የሚባሉ ጉዳዮች ላይ ግን በተለየ ቅድመ ዝግጅት ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን አሳስበዋል። የመጀመሪያውም ከፊፋ አባላት ባሻገር ቁጥራቸው በዛ የሚል ሌሎች አካላትም በጉባኤው ወቅት የሚገኙ መሆኑን ነው ማናጀሯ የጠቆሙት። 1 ሺ400 ከሚሆኑት የጉባኤው ተሳታፊዎች ባሻገር 600 ባለሙያዎች በኢትዮጵያ ወጣቶች ስፖርት አካዳሚና አፍሪካ ህብረት የሚሰሩ እንዲሁም ጉባኤውን ውጤታማ ለማድረግ የሚረዱ 300 ባለሙያዎች ከጉባኤው ሁለት ሳምንት አስቀድመው አዲስ አበባ የሚገኙ ይሆናል። በጉባኤው ተሳታፊ ለሚሆኑ አባል አገራት ተወካዮች ወደ ኢትዮጵያ ለመግባት የትኛውን የቪዛ ዓይነት መጠቀም እንደሚገባቸው መለየት እንዲሁም የህክምና አገልግሎት በምን መልክ ማግኘት አለባቸው በሚል ቅድመ ዝግጅት ማድረግም ሌላኛው ነው። ጉባኤው ሲካሄድ በመንገዶች የትራፊክ መጨናነቅ እናዳይፈጠር፣ የመጓጓዣ አማራጮች እንዲሁም መጓጓዣዎች የአቅጣጫ አመልካች መሳሪያ መግጠም እንደሚያስፈልግም ማናጀሯ አሳስበዋል። ለጉባኤው አስፈላጊ የሆኑ መሳሪያዎች ወደ አገሪቷ ሲገቡ በገቢዎችና ጉምሩክ እንዲሁም ሌሎች የሚመለከታቸው አካላት ትብብር እንዲያደርጉ፣ ጉባኤውን ለመዘገብ የሚገኙ የመገናኛ ብዙሃን የሚገቡበት ቪዛ ምን መሆን አለበትና የተሳታፊነት ማረጋገጫ ወረቀት በምን መልኩ ማግኘት አለባቸው በሚለው ጉዳይ ላይም ምላሽ መስጠት ይጠበቃል። ለቴሌኮም አገልግሎት የሚውሉ 400 ሲም ካርዶች፣ 4ጂ ኢንተርኔት እና የሬዲዮ መገናኛ ዘዴዎችን ማዘጋጀትም እንደሚያስፈልግና ለጉባኤው ተሳታፊዎች የደህንነት ዋስትና መስጠት እንደሚገባ ተጠቁሟል። አዲስ ዘመን ቅዳሜ ጥር 23/2012 ብርሃን ፈይሳ
https://www.press.et/Ama/?p=26501
414
2ስፖርት
እግር ኳስ የሞተበት ዕለት
ስፖርት
January 12, 2020
33
ባለፉት ሁለትና ሦስት ዓመታት በኢትዮጵያ እግር ኳስ ሜዳዎች ላይ ስርዓት አልበኝነት እየተንሰራፋ መምጣቱን ተከትሎ የ2012 ውድድር ዓመት ከጸጥታ ጋር በተያያዘ ትልቅ ስጋት አንዣቦበት እንደነበር ይታወሳል፡፡ እርግጥ ነው ባለፉት ዓመታት የታዩት የስቴድየም ሁከቶች አዝማሚያቸው አዲሱን የውድድር ዓመት ስጋት እንዲሰፍንበት ቢያደርግ አይገርምም፡፡ ይሁን እንጂ አስፈሪው ስጋት የበለጠ ጥፋት ሳያስከትል አልፎ አዲሱም የውድድር ዓመት በመልካም መንገድ ላይ ጉዞውን ቀጥሎ ፕሪሚየር ሊጉ ስምንተኛ ሳምንቱ ላይ ይገኛል፡፡ የስፖርታዊ ጨዋነት ጉዳይ ግን አልፏል ብለን የምንተወው ወይም ስጋት ሲፈጥርብን ብቻ የምናነሳው ጉዳይ አይደለም፡፡ ይልቁንም ካለፈው የምንማርበት ዘወትር የሌሎችን ተሞክሮና ታሪኮች አንስተን ነገን የተሻለ ለማድረግ የምንታትርበት መሆን ይገባዋል፡፡ በዛሬው የስፖርት ማህደር አምዳችንም አንድ ሰው ለኩሶት የብዙዎችን ሕይወት የቀጠፈ ዓለማችን የማይረሳ የስቴድየም ግጭት መለስ ብለን በማስታወስ ከታሪኩ የምንማርበት እንዲሆን ወደድን፡፡ የዚህ ዘግናኝ የስቴድየም ግጭት ታሪክ ከዚህ ይጀምራል፡፡እኤአ ሰኔ 29 ቀን 1985፣ በሄይሰል ስታዲየም፣ ቤልጅየም የአውሮፓ የክለቦች ውድድር ፍፃሜ ነበር። የሊቨርፑልና ጁቬንቱስ ጨዋታ ሊጀመር ደቂቃዎች ቀርተዋል። በ1920ዎቹ በተገነባው ያረጀ ስታዲየም 58ሺህ ተመልካች ተጠቅጥቋል። የጁቬንቱስ ደጋፊዎች ከስታዲየሙ ‹‹Z›› ክፍል የላይኞቹ ደረጃዎች ወደ ታችኞቹ፣ አንዳቸው ሌላቸው ላይ ተነባብረው እየተገፋፉ ጎረፉ። የብረት ዘንግ የያዙ የሊቨርፑል ደጋፊዎች ያባርሯቸዋል። ተቀጣጣይ ነገሮች ይወረወሩባቸዋል። ሁከት ነገሠ። የራስን ነፍስ ለማዳን ሲባል በሌሎች ላይ መረማመድ ግድ ሆነ። መራወጡ፣ መደራረቡ፣ መተፋፈጉ ቀጠለ። ማዕበሉ ሄዶ፣ ሄዶ በስታዲየሙ ግድግዳዎች ተገደበ። የሰው ልጅ በማይቆጣጠረው ኃይል ተገፍቶ ከሸክላና ጡብ ከተሰራ አጥር ጋር ተጣበቀ። ግድግዳዎቹም ግፊቱን መቋቋም አቅቷቸው ፈረሱ። የስፖርት ቤተሰቡ ከአርማታ ስብርባሪ ጋር ተደባልቆ ተጨፈላለቀ። የ20 ዓመቱ ሲሞኔ ስተርን ወደ ጨዋታው የመጣው በአባቱ ጉትጎታ ነበር። የገዛው ቲኬት ጣዕረ ሞት በተንሰፈሰፈበት የስታዲየሙ ደቡባዊ ክፍል ‹‹Z›› ያስገባል። አንድ መግቢያ ብቻ ስለነበር በራፉ ላይ ትርምስ ተፈጥሯል። በቅጡ አልተፈተሸም፣ ደጋፊዎች ያለቲኬት በሩን ሲያልፉ፣ የቢራ ጠርሙስ የያዙም ሲገቡ ማየቱን ያስታውሳል። ወንበር የሌላቸው ደረጃዎች መቀመጫ ከሆኑበት ከዚህ የስታዲየሙ ክፍል የሊቨርፑል ደጋፊዎች ከተሰጣቸው ሌላው ክፍል ጋር ይጎራበታል። የሚለያቸው በኋላ የተደረመሰው የሽቦ አጥር ብቻ ነው። የመጀመሪያው ቁስ በአንድ ደጋፊ ገና እንደተወረወረ አባቱ ‹‹ከስታዲየም እንውጣ›› ብለው ሲሞኔን አጣደፉት። ጨዋታውን ሳይመለከት መውጣትን ባለመፈለጉ አባቱን ለመከተል አመነታ። በመዘግየታቸው ሁለቱም በሺዎች ተገፍተው ከግድግዳ ጋር ተጣበቁ። ነፍስ ግቢ፣ ነፍስ ውጪ ሆነባቸው። ሲሞኔ የሞት ሞቱን ግድግዳ ቧጦ፣ ሽቦ ተንጠላጥሎ በስታዲየሙ መፀዳጃ ቤት ጣሪያ ላይ ወጣ። ከዚያም አባቱን ከመታፈግና መረጋገጥ ለማዳን ከላይ ሆኖ ወደ ታች እጃቸውን ይዞ መጎተቱን ቀጠለ።‹‹አብሮን እንደነበረ የማናውቀው አንዳች ጉልበት በዚያች ሰዓት መጣልን። አባቴን ጎትቼ ወደ ጣሪያው አወጣሁት›› ይላል ሲሞኔ። ከመታፈጉ ሲወጡ ግን አባት እጃቸው ይደማ ነበር። የሞት ሞታቸውን ራሳቸውን አድነው በስታዲየሙ አጠገብ ወዳለ የቀይ መስቀል እርዳታ ማዕከል ሲሄዱ ተረጋግጠውና ተጨፈላልቀው የሞቱ ደጋፊዎችን አስከሬን መሃል ራሳቸውን አገኙ፡፡ ስርዓት አልበኝነት ባስከተለው ጣጣ 32 ጣልያናዊያን፣ አራት ቤልጅየማዊያን፣ ሁለት ፈረንሳዊያን እና አንድ ብሪታኒያዊ ህይታቸውን አጡ። የልጅ ልጆች ያሏቸው ኦቴሎ ሎረንቲን የ‹‹Z›› ታዳሚ ነበሩ። ከልጃቸው ሮቤርቶ እና ከሁለት የልጅ ልጆቻቸው አንድሪያ እና ግራኒ ጋር በዚሁ ቦታ የፍፃሜውን ጨዋታ ለመመልከት ወደ ሄይሰል መጥተዋል። ከእነርሱ ጋር የህክምና ባለሙያው ሮቤርቶ ሎረንቲን ነበር። በመገፋፋቱና በመረጋገጡ ሰዎች በመጎዳታቸው ሮቤርቶ የሙያውን ለማበርከት ጉዳተኞችን ሊታደግ ወደኋላ ቀረ ። ‹‹እንግሊዛዊያኑ የማይወረውሩብን ነገር የለም። ሮቤርቶ!… ሮቤርቶ!… ና ውጣ!… እንሂድ! ብዬ ተጣራሁ። ብረት፣ የአርማታ ፍንካችና ድንጋይ ወደኛ ይዘንባል። ህፃናትና ሴቶች አብረውን አሉ። እየተገፋን፣ እየተገፋን ከግድግዳው ጥግ ደረስን። ከዚያ ራሴን በቅፅበት በመጫወቻ ሜዳው ላይ አገኘሁት›› በማለት ኦቴሎ ክፉውን ቀን ያስታውሳሉ።‹‹ወደ ደረጃዎቹ እያየሁ ሮቤርቶን መጣራቴን ቀጠልኩ። በፍለጋዬ መሃል የእህቴ ልጅ አንድሪያ ጭንቅላቱን በሁለት እጁ ይዞ ከድንጋጤ ጋር ቆሞ አየሁት። የጠራሁት ሮቤርቶ በስታዲየሙ መቀመጫ ደረጃ ላይ ተንጋሏል። ጆሮዬን ከደረቱ ላይ አጣብቄ አዳመጥኩ። የሚሰማኝ የራሴው የልብ ትርታ ብቻ ነበር። ህይወቱ አልፏል። ይህን ሳደርግ የቴሌቪዥን ካሜራ ባለሙያ ይቀርፀኛል። በኋላም የሞተውን ልጄን ስፈልግ የሚያሳየውን ፊልም በቴሌቪዥን አየሁት።›› ይላሉ፡፡ሮቤርቶ ሌሎችን ለመርዳት ሲል ህይወቱን አጥቷል። የደጋፊዎች አስከሬን ተሰብስቦ በጊዜያዊ ማዕከል ተከማቸ። አባት ኦቴሎ ሌሊቱን የልጃቸውን አስከሬን ለመረከብ ወደ ሆስፒታል ሄዱ። ‹‹በሆስፒታል ከሶስት ሰዓታት በላይ አስጠበቁን። ሌሊት 9:00 ሰዓት ላይ የልጄን አስከሬን አየሁት። የአንገቱ ሃብልና የጋብቻው ቀለበት ተወስደዋል። ‹ማንነቱን ለመለየት ብለን ነው ያወለቅናቸው› የሚል ምክንያት ሰጡኝ። ነገር ግን በልጄ ጌጣጌጥ ላይ ስሙ አልተፃፈባቸውም ነበር። ሰርቀዋቸው ነው›› ይላሉ።የሞት ትራፊዎቹ ደጋፊዎች ስለሄይሰል ማውራት አይፈልጉም። ለብዙ ጁቬዎች የሄይሰል ስም ነውር ነው። ከአደጋው በኋላ አንድ ደጋፊ የመናገር አቅም አጥቶ ደንዝዞ ቃል ለመተንፈስ ወራት አስፈልገውታል። ሌላው ደጋፊ ደግሞ ከጓደኛው ጋር ወደ ስታዲየሙ መጥቶ በአደጋው ያጣውን ባልንጀራውን አስከሬን ከሙታኑ መሐል አገኘው። በሃዘን ወደ መኪናው ቢመለስም የመኪናው ቁልፍ እርሱ ዘንድ እንዳልሆነ አስታወሰ። በአስከሬኑ ኪስ ውስጥ ነበር። በወቅቱ የ14 ዓመት ታዳጊ የነበረ ደጋፊ የአባቱን መሞት ሳያውቅ በሰዎች ላይ በእግሩ ተረማምዶ ራሱን ማዳኑን ዛሬ በፀፀት ያስታውሳል። “ቢሆንም በባዶ እግሬ ነበርኩ። ጫማዬ በግርግሩ ከእግሬ ላይ ወልቆ ጠፍቶብኝ ነበር” እያለ ያዝናል። ከዚህ ሁሉ ትራጀዲ በኋላ ጨዋታው እንዲደረግ መወሰኑ አወዛጋቢ ነበር። በዚያ ርጉም ቀን ጨዋታው ቢቀጥልም ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ የሊቨርፑሉ ማርክ ላውረንሰን የትከሻ ውልቃት ጉዳት ደርሶበት ተቀይሮ ወጣ። ጉዳቱ ከበድ ያለ ስለሆነ በአምቡላንስ ወደ ሆስፒታል ተወሰደ።“አምቡላንስ ውስጥ ተኝተህ ተጓዝ ተባልኩ። እኔ የፈለግኩት ደግሞ ተቀምጬ መሄድ ነበር። በድጋሚ እንድተኛ ታዘዝኩ። አሻፈረኝ አልኩኝ። እንደገና ኮስተር ባለ ትዕዛዝ እንድተኛ ተነገረኝ” ይላል። ትዕዛዙ የጠነከረበት፣ አንድ የሊቨርፑል ተጫዋች በአምቡላንስ ውስጥ መኖሩ እንዳይታወቅ ተብሎ ነበር። የመጣው ከእነ ማሊያው ነው። በላዩ ላይ የደረበበት የቱታ ጃኬትም ቀይ ነው። ማሊያውም ስለሚታይ ማንነቱን ለመለየት ቀላል ነበር። ሆስፒታል ሲደርስ በጓሮ በር አስገቡት። በሆስፒታሉ የሞቱትና ክፉኛ የቆሰሉት ደጋፊዎች ወገኖች ይገኛሉ። ሁሉም በሊቨርፑል ላይ አምርሯልና ላውረንሰን ተደብቆ መግባቱ ተገቢ ነበር። የወለቀ ትከሻውን በቦታው የመለሰው ቀዶ ጥገና ከተጠናቀቀ በኋላ ተጨዋቹን እዚያው አልጋ ላይ ተውት። አቅሉን መልሶ አግኝቶ ቀና ቢል አውቶማቲክ ጠብመንጃ የታጠቀ ወታደር በግርጌው ተቀምጦ አየ። ወታደሩም እጁን ዘርግቶ ፈጥኖ እንዲተኛ ምልክት ሰጠው። ላውረንሰንም ፈጥኖ ወደ አልጋው ተመለሰ።በነጋታው ጠዋት በባለቤቱና ከረዳት አሰልጣኞች በአንዱ ታጅቦ በድብቅ ከሆስፒታሉ ወጣ። የቤልጅየም ባለስልጣናትም አፋጥነው የሊቨርፑልን ተጨዋቾች ወደ ኤርፖርት ወስደዋቸው ወደ ሃገራቸው በረሩ። በወቅቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ማርጋሪት ታቸር ግፊት የእንግሊዝ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ክለቦቹ ከአውሮፓ ውድድሮች እንዲገለሉ አደረገ። የአውሮፓ እግር ኳስ ማህበር ደግሞ የሊቨርፑል ደጋፊዎችን ጥፋት ተመልክቶ የእንግሊዝን ክለቦች ለአምስት ዓመት ከማንኛውም ውድድር አገደ። ቅጣቱ ሄይሰል የተወውን የህሊና ጠባሳ ሊሽረው አልቻለም። በአንድ ደጋፊ የተጫረ ረብሻ ለብዙ ቤተሰቦች ጥልቅ ሐዘን ምክንያት ሆነ። ‹‹አዎን›› ይላል የወቅቱ የሊቨርፑል አምበል ፊል ኒል። ‹‹አዎን! በዚያ ቀን ምክንያት ከህይወት አስፈሪ ቅዠት ጋር ተጋፈጥኩ። ከጉዳቱ ለማገገምም ዘመናት አስፈለጉኝ።››አዲስ ዘመን ጥር 3/2012 ቦጋለ አበበ
https://www.press.et/Ama/?p=25533
896
2ስፖርት
አትሌቶች የፖለቲካ መልዕክት እንዳያስተላለፉ የተሰጠው አወዛጋቢ ማሳሰቢያ
ስፖርት
January 11, 2020
20
በቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ አትሌቶች የትኛውንም ዓይነት የፖለቲካ፣ የሃይማኖት፣ የዘርና መሰል ተቃውሞና መልዕክት እንዳያስተላልፉ የዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ፕሬዚዳንት ቶማስ ባኽ አሳሰቡ። ፕሬዚዳንቱ የ2020 የፈረንጆች አዲስ ዓመትን በተመለከተ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት ባስተላለፉበት ወቅት ‹‹የኦሊምፒክ መድረክ በፍፁም የፖለቲካ ተቃውሞ፣የሃይማኖትና የዘረኝነት መልዕክት የሚተላለፍባቸው መሆን የለበትም›› ብለዋል። በኦሊምፒኩ ወቅት በየትኛውም ስፍራ አትሌቶች ለተፎካካሪዎቻቸው ክብር ማሳየት እንዳለባቸውም ፕሬዚዳንቱ ተናግረዋል። ቶማስ ባኽ ስፖርትን የፖለቲካ መጠቀሚያ የማድረግ አዝማሚያ እየሰፋ በመጣበት በዚህ ወቅት በኦሊምፒክ መድረክ አላስፈላጊ መልዕክቶችን ማስተላለፍ ምንም ጥቅም እንደሌለውና የዓለምን ሕዝቦች ከመነጣጠል የዘለለ ፋይዳ እንደማይኖረው አብራርተዋል። ‹‹የኦሊምፒክ መድረክ ዓለም አቀፋዊ ይዘት ያለው አትሌቶች ስፖርታዊ ብቃታቸውን የሚያሳዩበት እንጂ የፖለቲካ ወይም ሌላ ፕሮፓጋንዳ የሚያስተላልፉበት አይደለም›› ያሉት ቶማስ ባኽ ስፖርትን የፖለቲካ መጠቀሚያ ለማድረግ የሚደረገውን ጥረት ለመታገል በመድረኩ እንደዚህ ዓይነት ማሳሰቢያዎችን ቀድሞ ማሳወቅ እንደሚገባ ተናግረዋል። አትሌቶችም ከፖለቲካ ነፃ ሆነው ለንፁህ ስፖርት ያላቸውን ወገንተኝነት ማሳየት እንደሚጠበቅባቸው ጠቁመዋል። በኦሊምፒክ መድረክ መሰል ተቃውሞና መልዕክት ማስተላለፍ እንደማይቻል የዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ባለፈው ወር ሉዛን ላይ በነበረው ስብሰባም ሃሳብ መነሳቱ ይታወሳል። ይሁን እንጂ በተለያዩ ዓለም አቀፍ የስፖርት መድረኮች የፖለቲካ ተቃውሞ፣ የሃይማኖትና የዘረኝነት መልዕክቶች በአትሌቶች በኩል ሲተላለፉ ማየት እየተለመደ መጥቷል። በተሸኘው 2019 የፈረንጆች ዓመት እንኳን በሃያ አራት ሰዓት ልዩነት ውስጥ አሜሪካውያን አትሌቶች በፓን አሜሪካን ጨዋታዎች የፖለቲካ ተቃውሞ በስፖርት መድረክ ሲያደርጉ በዓለም የውሃ ዋና ቻምፒዮና ወቅት አውስትራሊያዊው አትሌት ማክ ሆርተንና እንግሊዛዊው ዱንካን ስኮት ቻይናዊው ሰን የንግ አበረታች መድኃኒት ተጠቃሚነት ጋር ተያይዞ ስሙ የሚነሳ በመሆኑ በአንድ ላይ ቆመው ሽልማት አንቀበልም ማለታቸው መነጋገሪያ ሆኖ ቆይቷል። የዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ የአትሌቶች ኮሚሽን ሊቀመንበር ኪርስቴይ ኮቬንትሪ ባለፈው ጥቅምት ወር በርካታ አትሌቶች ኦሊምፒክ መድረክ ላይ የፖለቲካ ተቃውሞ ለማድረግ ተገቢው ቦታ መሆኑን እንደሚያምኑ በመናገር የአትሌቶቹን ሃሳብ መደገፋቸው በዓለም አቀፉ ኮሚቴ ውስጥ የተከፋፈለ ሃሳብ እንዳለ አሳይተዋል። ይህንንም ተከትሎ አትሌቶች በኦሊምፒክ መድረክ የፖለቲካ ተቃውሞ ማድረግ፣የሃይማኖትና የዘረኝነት መልዕክ ማስተላለፍ አለባቸው የለባቸውም የሚለው ሃሳብ አከራካሪ ሆኖ ቆይቷል። በታሪክ አጋጣሚ ግን አትሌቶች በተለያዩ ዓለም አቀፍ የስፖርት መድረኮች የፖለቲካም ይሁን ሌሎች መልዕክቶች ማስተላለፍ የተለመደና አሁንም ድረስ ያለ ተግባር ነው። ከቅርብ ጊዜ ክስተቶች ስንነሳ የኦሊምፒክ የነሐስ ሜዳሊያ ባለቤቱ አሜሪካዊ አትሌት ፌንሰር ኢምቦደን በሽልማት ላይ እያለ የአሜሪካን ብሔራዊ መዝሙር ሲዘመር በአንድ እግሩ ተንበርክኮ በአሜሪካን ስደተኞች ላይ የሚፈጸም እንግልት፣ ዘረኝነትና የጦር መሣሪያ ዝውውርን በተመለከተ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ያላቸውን አቋም ተቃውሟል። የመዶሻ ወርዋሪዋ ዌን ቤሪም በተመሳሳይ የስፖርት መድረክ የሜዳሊያ ሽልማት ሥነሥርዓት ወቅት የቀኝ እጇን ከፍ አድርጋ የአሜሪካን መንግሥት ላይ ተቃውሞ አሳይታለች። በዚህም የአሜሪካ ኦሊምፒክና ፓራሊምፒክ ኮሚቴ ሁለቱን አትሌቶች ለጥያቄ ያቀረባቸው ሲሆን ሌሎች አትሌቶችም የቶኪዮ ኦሊምፒክን ጨምሮ በሌሎች ውድድሮች ከተመሳሳይ ድርጊት እንዲቆጠቡና ድርጊቱን ፈፅመው ከተገኙ ከባድ ቅጣት እንደሚጠብቃቸው አሳስቧል። ወደ አገራችን አትሌቶች ስንመጣ በሪዮ 2016 ኦሊምፒክ የተፈጠረውን አጋጣሚ የስፖርት ቤተሰቡ አሁንም ድረስ ያስታውሰዋል። አትሌት ፈይሳ የኦሊምፒኩ የመዝጊያ ውድድር በነበረው የወንዶች ማራቶን ላይ በመሳተፍ የብር ሜዳልያ ለመጎናፀፍ ሲበቃ ርቀቱን በ2፡09፡54 ሰዓት በማጠናቀቅ ነበር። በዕለቱ አርባ ሁለት ኪሎ ሜትሩን ከኬንያዊው ኢሉድ ኪፕቾጌ ቀጥሎ ሁለተኛ ሆኖ ማጠናቀቁን ሲያረጋግጥ መላው ዓለም ባልጠበቀው ሁኔታ፤በወቅቱ በአገራችን የነበረውን የፖለቲካ ሥርዓት በመቃወም እጆቹን አጣምሮ ተቃውሞውን በመግለጽ የዓለምአቀፍ መገናኛ ብዙኃን ትልቅ የመነጋገሪያ ርዕስ መሆን ችሏል። ከዚያም በኋላ በሰጣቸው መግለጫዎች ይህን አቋሙን ደጋግሞ አንፀባርቋል። እጆቹን አጣምሮ ከፍ በማድረግ የተቃውሞውን ምልክት ካሳየ በኋላ ወደ አገር ቤት ሳይመለስም ቀርቷል።በወቅቱ የነበሩ የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት ፈይሳ ወደ ሀገር ቤት ቢመለስ ምንም ዓይነት ችግር እንደማይገጥመው ቢገልፁም እርሱ ግን ለመመለስ አልፈቀደም ነበር። ሌታስ ራን በተባለው ታዋቂ የአትሌቲከስ ድረገፅ የቀረበ አንድ አስተያየት ፈይሳ ሌሊሳ በአሜሪካ ተወዳጅነት እያገኘ መምጣቱን ጠቅሶ ያነሳው አጀንዳ ነበር። ፈይሳ አሜሪካ ከገባ በኋላ የተለያዩ መግለጫዎችን ለአሜሪካ እና ለሌሎች ዓለም አቀፍ ሚዲያዎች ሰጥቷል። በእነዚህ መግለጫዎች የተቃውሞ ምልክቱን በተደጋጋሚ ከማሳየቱም በላይ የዓለም ግዙፍና ተጽዕኖ ፈጣሪ መገናኛ ብዙኃን ትኩረትን ማግኘት ችሏል። የዋሽንግተን ፖስት የአፍሪካ ቢሮ ኃላፊ ‹‹የ2016 ሪዮ ኦሊምፒክ ብልህ ተግባር›› ብሎ አደነቀው። ከዚያም በኋላ የቢቢሲ ጋዜጠኛ የኦሊምፒኩ እጅግ አስደናቂ ክስተት ብሎ አስተያየት ሰጠበት። አልጄዚራና ሌሎችም ታላላቅ መገናኛ ብዙኃን «ብልሁና ጀግናው ኦሊምፒያን» በማለት አሞካሽተውታል። በአሜሪካዋ የሲያትል ከተማ የሚንቀሳቀሰው የአፍሪካ አትሌቶች ማህበር በየዓመቱ የሚያካሂደውን የ5ኪሜ የጎዳና ላይ ሩጫውን በፈይሳ ሌሊሳ ጀግንነት ሰይሞታል።በ1968 እአአ ላይ በሜክሲኮ ኦሊምፒክ ላይ ሁለት ጥቁር አሜሪካውያን አትሌቶች ቶሚ ስሚዝ እና ጆን ካርሎስ ካሳዩት የተቃውሞ አቋም ጋር እሱም ባለታሪክ ሆኖ እየተጠቀሰ ቆይቷል። ሁለቱ ጥቁር አሜሪካዊ አትሌቶች በ200 ሜትር እንደቅደም ተከተላቸው የወርቅ እና የነሐስ ሜዳልያ ከተሸለሙ በኋላ በሜዳልያ ሽልማት ሥነሥርዓት ላይ የአሜሪካ መዝሙር ሲዘመር የብላክ ፓወርን የሚያንፀባርቅ ክንዳቸውን አሳይተው ነበር። በዚህ ተቃውሟቸው ሁለቱም ሜዳልያቸውን ተነጥቀዋል። ሁለቱ ኦሊምፒያኖች በወቅቱ በሽልማት ሥነሥርዓቱ ላይ ተቃውሟቸውን ክንዳቸውን በማንሳት ሲገልፁ አንድ አንድ እጃቸው ላይ ጥቁር ጓንት አድርገው፤ ጥቁር ካልሲዎች ያለጫማ አድርገው የነበረ ሲሆን በጊዜው ተንሰራፍቶ የነበረውን ዘረኝነት በመቃወም ያደረጉት ነው። ዓለም አቀፉ የኦሊምፒክ ኮሚቴ በዘረኝነት ላይ የተቃውሞ ተግባር ማሳየታቸውን አውግዞ ቅጣት አስተላልፎባቸዋል። ሁለቱ ጥቁር አሜሪካዊ ኦሊምፒያኖች ሜዳልያዎቻቸውን ቢነጠቁም በትውልዳቸው ጀግኖች ነበሩ። በሳንሆዜ ሐውልት የቆመላቸው ሲሆን ዘጋቢ ፊልሞችም ተሰርቶላቸዋል። የኦሊምፒክ ቻርተር አንቀፅ 50 መሠረት በኦሊምፒክ መድረክ ማናቸውንም ዓይነት የፖለቲካ አጀንዳ፤ ተቃውሞ ወይንም ተግባር የማይፈቀድ እና የሚያስቀጣ መሆኑን ይደነግጋል። አዲስ ዘመን ጥር 2/2012 ዓ.ም ቦጋለ አበበ
https://www.press.et/Ama/?p=25498
718
2ስፖርት
በክልሉ ያለውን ሰፊ የቱሪዝም ሀብት አልምቶ ጥቅም ላይ ማዋል ላይ ክፍተቶች መኖራቸው ተነገረ
ሀገር አቀፍ ዜና
December 23, 2020
22
 ሃይማኖት ከበደ አዲስ አበባ፡- በኦሮሚያ ክልል ሰፊ የቱሪዝም ሀብት ቢኖርም ሃብቱን አልምቶ በጥቅም ላይ በማዋል ረገድ ክፍተቶች እንዳለበት የክልሉ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ገለጸ። የቢሮው ምክትል ኃላፊ አቶ ሁንዴ ከበደ በተለይ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለፁት፤ በክልሉ በርካታ የቱሪስት መስህቦች ቢኖሩም ያለውን ሀብት በሚፈለገው ልክ አልምቶ ለቱሪስቶች ምቹ ሆኖ እንዲጎበኝና ጥቅም ላይ እንዲውል አልተደረገም። ለዘርፉ ትኩረት ሰጥቶ ያለመሰራቱም በክልሉ ያለውን የቱሪስት ፍሰት አነስተኛ አድርጎታል። እንደ አቶ ሁንዴ ገለጻ፤ ለዘርፉ ከተሰጠው አናሳ ትኩረት ባለፈ ለክልሉ የቱሪስት ፍሰት አነስተኛ መሆን ምክንያት የሆኑት ነገሮች መካከል የሰላምና የፀጥታ ጉዳይ፣ በየደረጃው ያላው ግንዛቤ አናሳ መሆን፣ በዘርፉ ዕውቀትና ክህሎት ያለው የሰው ሀይል እጥረት፣ የመሰረተ ልማት ችግሮችና ሌሎችም ተጠቃሽ ናቸው። በክልሉ በአመት ውስጥ በሚከበሩበት በሃይማኖታዊ ክብረ በዓላት፣ለኢሬቻ፣ ለድሬ ሼክ ሁሴንና የመሳሰሉት በዓላት ምክንያት የሀገር ውስጥ ቱሪስት ፍሰቱ ከፍተኛ ቢሆንም የውጪ ሀገር ቱሪስት ግን ዝቅተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል ብለዋል ምክትል ቢሮ ኃላፊው። ቱሪዝም በዓለም አቀፍ ደረጃ በፍጥነት እያደገ ያለ ዘርፍ ነው ያሉት ምክትል ቢሮ ኃላፊው፤ የቱሪዝም ስራ ብዙ ወጪ የሚጠይቅ ስራ በመሆኑና ለበርካታ ዜጎች የስራ ዕድል የሚፈጥር ዘርፍ ስለሆነ መንግስትም ከዚህ በበለጠ ትኩረት ሰጥቶ ሊሰራበት እንደሚገባ ገልጸዋል። አሁን ላይ በክልሉ የቱሪዝም ሀብቶችን በመለየት የቱሪዝም ፍኖተካርታ ተዘጋጅቶ በመሰራት ላይ መሆኑን በመጠቆምም፤ ያለው የቱሪዝም ሀብት ለምቶና ተዋውቆ ጎብኚን እንዲስብ የተለያዩ የማስተዋወቂያ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑንም ተናግረዋል። እንደ አቶ ሁንዴ ማብራሪያ፤ ኢትዮጵያ ውስጥ ቱሪስት እንዲመጣ የሚያደርጉት በአብዛኛው አስጎብኚ ድርጅቶች ናቸው፤ በሀገሪቱም በርካታ የአስጎብኚ ድርጅቶች ቢኖሩም የክልሉን ሀብት ፓኬጅ ውስጥ አስገብቶ መስራት ላይ ክፍተት አለ። ከቱሪስት ፍሰቱ ጋር ተያይዞ በክልሉ ትልቅ ችግር የሚነሳው ከልማት ጋር ተያይዞ ያለው ነገር ሲሆን፤ ቱሪስቶች ወደ ክልሉ ሲመጡ በቂ የሆነ የሚያድሩበትና የሚመገቡበት ስፍራ አለመኖሩ አንዱ ችግር ነው። ለአብነትም፣ በባሌ አካባቢ የተለያዩ ለዩኔስኮ የታጩ ቦታዎች ቢኖሩም፤ ወደ እዛ ሲኬድ የቱሪስት አገልግሎት ሰጪ ተቋማት የሉም። ስለዚህ ቱሪስት ቢሄድም የሚያድርበት የሚዝናናበት ቦታ ስለሌለ ይሄ ነገር እንደ ስጋት ይታያል። ከዚህ አንፃር በክልሉ በቀጣይ አስር ዓመታት ወደ 25 የሚሆኑ የቱሪስት መዳረሻ ቦታዎች እንዲለሙ በዕቅድ ተይዞ እየተሰራ እንደሚገኝ ምክትል ቢሮ ኃላፊው ጠቁመዋል። በተለይ የመሰረተ ልማት ስራዎች ቅድሚያ ተሠጥቷቸው እንዲሰሩ ቢሮ ትኩት አድርጎ እየሰራ መሆኑን እና ከመንግስትና ከግል ባለሀብቱ ጋር በጋራ በመሆን ቱሪስቶች ሊጠቀሙባቸው ነገሮችን ለማሟላት እየተሰራ ነው ብለዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 14/2013
https://www.press.et/Ama/?p=37934
325
0ሀገር አቀፍ ዜና
ሰባት ከፍተኛ የጦር መኮንኖች ፍርድ ቤት ቀረቡ
ሀገር አቀፍ ዜና
December 23, 2020
17
በጋዜጣው ሪፖርተርአዲስ አበባ፡- እነ ሜጀር ጀነራል ገብረመድህን ፍቃዴን ጨምሮ 7 ከፍተኛ የጦር መኮንኖች በዛሬው ዕለት ፍርድ ቤት ቀርበው ጉዳያቸው ታይቷል። ኢቢሲ እንደዘገበው፤ በሀገር ክህደት ወንጀል የተጠረጠሩት የመከላከያ የመገናኛ ሬዲዮ መምሪያ ኃላፊ የነበሩት እነ ሜጀር ጀነራል ገብረመድህን ፍቃዴን ጨምሮ 7 ከፍተኛ የጦር መኮንኖች ትናንት ፍርድ ቤት ቀርበው ጉዳያቸው ታይቷል። የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ወንጀል ምርመራ ቢሮ የምርመራ ቡድን ተጠርጣሪዎች ላይ ከዚህ ቀደም ሲያቀርብ ከነበረው የወንጀል ተግባራት ባሻገር “በርካታ የመገናኛ ሬዲዮ ይወገድ በሚል ምክንያት ከማዕከል አጓጉዘው ለትግራይ ልዩ ኃይል ስለማስረከባቸው ያገኘሁት ማስረጃ ያመላክታል” ብሏል። የምርመራ ቡድኑ ተጠርጣሪዎች የሰሜን ዕዝ መገናኛ ሬዲዮ እንዲቋረጥ ትዕዛዝ ሰጥተዋልም ብሏል፤ ሌሎችንም በመጥቀስ ለተጨማሪ ምርመራ 14 ቀን ጠይቋል። የተጠርጣሪ ጠበቆች የደንበኞች የወንጀል ተሳትፎ ተለይቶ አልቀረበም፣ ተጨማሪ ጊዜ ለምርመራ ቡድኑ መፈቀድ የለበትም ብሏል። ችሎቱ ትዕዛዝ ለመስጠት ለታኅሣሥ 15 ቀን 2013 ቀጥሯል።በተያያዘ ዜና፣ ከመከላከያ ሰራዊት በጡረታ የተገለሉ አባላትን በማሰባሰብና በመመልመል የትግራይ ልዩ ሃይልን እንዲቀላቀሉ ሲያደርጉ ነበር የተባሉ ተጠርጣሪዎች ፍርድ ቤት መቅረባቸውን ፋና ብሮድካስት ኮርፖሬት ዘግቧል። በዘገባው እንደተመላከተው፤ ከአራቱ መካከል ከኮሎኔል ገብረመድህን ገብረመስቀል በስተቀር ቀሪዎቹ ከሰባት አመት በፊት በጡረታ የተገለሉ ሲሆኑ፤ ተጠርጣሪዎቹ ህገ መንግስቱን እና ህገ መንግስታዊ ስርአቱን በሃይል በመናድ ወንጀል ተጠርጥረው ምርመራ እየተከናወነባቸው ይገኛል። እነዚህም 1ኛ ኮሎኔል ምሩፅ በርሄ፣ 2ኛ ኮሎኔል ገብረመድህን ገብረመስቀል፣ 3ኛ ኮሎኔል ተስፋዬ ሃጎስ እና 4ኛ ኮሎኔል መብራቱ ተድላ ናቸው። መርማሪ ፖሊስ ከዚህ በፊት በተሰጠው 12 ቀናት ውስጥ የሰራቸውን በርካታ የምርመራ ስራዎች ለችሎቱ አብራርቷል። ፖሊስ ተጠርጣሪዎቹ ከሜጄር ጄኔራል ገብረመድህን ፍቃዴ (ወዲ ነጮ) ጋር በመሆን በሰሜን ዕዝ የመከላከያ ኔትወርክ ግንኙነትን በማቋረጥ ተሳትፎ እንዳላቸው በሰው ምስክርና በቴክኒክ ምርመራ በማስረጃ አረጋግጫለሁ ብሏል። የስምንት ሰዎችን የምስክርነት ቃል መቀበሉን የገለጸው መርማሪ ፖሊስ፤ በትግራይ ክልል የፌደራል ፖሊስ አባላትና ተቋማት ላይ የደረሰውን የጉዳት መጠን ለይቶ በማስረጃ በማረጋገጥ ከመዝገቡ ጋር ማያያዙንም ጠቅሷል። ተጠርጣሪዎቹ በበኩላቸው ከወንጀሉ ጋር ግንኙነት እንደሌላቸው በመጥቀስ የወንጀል ተሳትፏቸው ተለይቶ አለመቅረቡን በማንሳት በነጻ አልያም በዋስ እንዲወጡ ጠይቀዋል። መርማሪ ፖሊስም የእያንዳንዳቸውን ተሳትፎ ያብራራ ሲሆን በዚህም 1ኛ ተጠርጣሪ በሚሰሩበት የጥበቃ ስራ ላይ የራሳቸውን አባላት መልምለው በፌደራል ተቋማት ላይ ጥቃት ሊፈጽሙ እንደነበር በሰበሰብኩት ማስረጃ አረጋግጫለሁ ነው ያለው። እንዲሁም 2ኛ ተጠርጣሪ ሁለት ጊዜ በተሰማሩበት የሰላም ማስከበር ተልዕኮ ላይ አባላትን አደራጅተው የትግራይ ልዩ ሃይልንእንዲቀላቀሉ ማድረጋቸውን ማስረጃ መሰብሰቡን ጠቅሶ፤ 3ኛ ተጠርጣሪም ወንጀሉ ሲፈጸም ህክምና ላይ ነበሩ ተብሎ በጠበቃቸው ለተነሳው መቃወሚያ መርማሪ ፖሊስ ወንጀሉ ሲፈጸም ብቻ ሳይሆን ለወንጀሉ መፈጸም ከሁለት አመት በፊት ጀምሮ ለፀረ ሰላም ቡድኖች መረጃ ሲያቀብሉ እንደነበርም ማስረጃ መሰብሰቡን አስረድቷል። 4ኛ ተጠርጣሪም ቢሆኑ ከሜጀር ጀኔራል ገብረመድህን ጋር በመገናኘት ከመከላከያ በጡረታ የወጡ ሰዎችን በመሰብሰብ ለትግራይ ልዩ ሃይል አባላትን ሲመለምሉ እንደነበር ማስረጃ መሰብሰቡንም ነው ያስረዳው። ከዚህ ባለፈም በአዲስ አበባ ከተማ እያንዳንዳቸው ያደርጉት የነበረውን እንቅስቃሴ ማጣራቱንም ጠቅሷል። የሁለቱን ክርክር ያዳመጠው ችሎቱ ተጠርጣሪዎቹ የተፋጠነ ፍትህ የማግኘት መብት እንዳላቸው ጠቅሶ መርማሪ ፖሊስ ምርመራውን በፍጥነት እንዲያከናውን ትዕዛዝ ሰጥቷል። ለተጨማሪ ምርመራም ለፖሊስ 10 ቀናትን ፈቅዷል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 14/2013
https://www.press.et/Ama/?p=37931
412
0ሀገር አቀፍ ዜና
ኢትዮጵያ ከጎረቤት ሀገራት ጋር ግጭት ውስጥ እንድትገባ ወጥኖ የሚሰራ ኃይል መኖሩን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ
ሀገር አቀፍ ዜና
December 23, 2020
15
 በጋዜጣው ሪፖርተርአዲስ አበባ፡- የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከቅርብ አመታት ወዲህ የህዳሴው ግድብ መገንባትን ተከትሎ ኢትዮጵያ ከጎረቤት ሀገራት ጋር ግጭት ውስጥ እንድትገባ ወጥኖ የሚሰራ ኃይል መኖሩን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገልጿል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ዛሬ ለጋዜጠኞች ሳምንታዊ መግለጫ ሰጥተዋል።አምባሳደር ዲና እንደገለጹት፤ የምስራቅ አፍሪካን ሰላም የማይሹ ኃይሎች ሱዳን እና ኢትዮጵያ መሃል ክፍተት መፍጠር እንደ ትልቅ ሎተሪ እየተመለከቱት በመሆኑ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጉዳዩን በትኩረት እየተከታተለው ይገኛል፡፡ ኢትዮጵያ እና ሱዳን በሚጋሯቸው ድንበሮች ሰሞኑን እየተሰሙ ላሉ ግጭቶች አንዱ የዚህ ኃይል በጉዳዩ አጀንዳውን ለማስረፅ የሚሞክር እንደሆነ የጠቆሙት አምባሳደር ዲና፤ የድንበር ማካለሉ ስራ በትእግስት የሚሰራ ስለመሆኑም አንስተዋል።ባለፈው ሳምንት የተከናወኑ አበይት ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ጉዳዮችን በተመለከተ መግለጫ የሰጠው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፤ ፕሬዚዳንት ሣህለወርቅ ዘውዴ የሰባት ሀገሮች ዲፕሎማቶችን የሹመት ደብዳቤ የተቀበሉ እንደሆነ ተገልጿል። አምስት የኤዥያ ሀገራት እና ሁለት የአፍሪካ ሀገራት በኢትዮጵያ የተካሄደው የህግ ማስከበር ዘመቻ በተሳካ መልኩ በመጠናቀቁ የእንኳን ደስ አላችሁ መልእክት ማስተላለፋቸውም ነው የተገለፀው። የሰባት ሀገራት ዲፕሎማቶችን ሹመት ማስተናገድ ከህግ ማስከበር ጎን ለጎን ኢትዮጵያ በትክክለኛ የዲፕሎማሲ ጎዳና ላይ መሆኗን እና ከዓለም አቀፉ የዲፕሎማሲ ስርአት ጋር በመናበብ እየተንቀሳቀሰች መሆኗን ያጎላ ነው ብለዋል የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ። ከኢጋድ 38ኛው አስቸኳይ የመሪዎች ጉባኤ ጋር በተያያዘ አባል ሀገራቱ ችግሮቻቸውን ካለማንም ጣልቃ ገብነት በውይይት የመፍታት ባህል የማዳበር አቅጣጫ ተቀምጦ በስኬት መጠናቀቁንም አስረድተዋል። አምባሳደር ዲና ሙፍቲ በመግለጫቸው፤ በተለያዩ ሀገራት መሪዎችና ተቋማት በተለይም በህግ ማስከበር ዙሪያ በመንግስት ግንዛቤ በሚገባ ያስጨበጡ ስራዎች እንደተሰሩ የተገለፀ ሲሆን፤ እንደ ፊንላንድ ያሉ ሀገራት በህግ ማስከበር ጉዳይ ከመግባባት ባለፈ በቀጣይ ለሚሰሩ ስራዎች የገንዘብ ድጋፍ ለማድረግ ፈቃደኝነታቸውን አሳይተዋል።ከዚህ ባለፈም በዚህ ሳምንት ብቻ 327 ኢትዮጵያውያን ከሳውዲ አረቢያ እንዲመለሱ የማድረግ ስራ መሰራቱንም አምባሳደሩ ጠቁመዋል። በኢኮኖሚ ዲፕሎማሲ ረገድም ከተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት ጋር ስራዎች የተሰሩበት ሳምንት መሆኑን የገለፁት አምባሳደር ዲና ፤የኢትዮጵያ እና ግብፅን የንግድ ግንኙነት የተሻለ ለማድረግም የኢትዮ-ግብፅ የንግድ ስምምነቶችን የተሻለ ለማድረግም ጥረቶች ተደርገዋል ብለዋል። የአውሮፓ ህብረት ለኢትዮጵያ ይሰጥ የነበረውን ዘጠና ሚሊየን ዶላር ተሰረዘ ተብሎ የተወራው ሀሰት ስለመሆኑም የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ማስታወቁን የዘገበው ኢቢሲ ነው፡፡አዲስ ዘመን ታህሳስ 14/2013
https://www.press.et/Ama/?p=37932
299
0ሀገር አቀፍ ዜና
በኦሮሚያ ክልል ባለፉት አምስት ወራት 83 ቢሊየን ብር ካፒታል ያስመዘገቡ ፕሮጀክቶች ወደ ስራ መግባታቸው ተነገረ
ሀገር አቀፍ ዜና
December 23, 2020
13
በጋዜጣው ሪፖርተርአዲስ አበባ፡- በኦሮሚያ ክልል ባለፉት አምስት ወራት 83 ቢሊየን ብር ካፒታል ያስመዘገቡ 4 ሺህ 359 የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች ወደ ስራ መግባታቸውን በኦሮሚያ ክልል በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ዘርፍ አስተባባሪ አቶ አዲሱ አረጋ አስታወቁ።በኦሮሚያ ክልል ባለፉት አምስት ወራት 83 ቢሊየን ብር ካፒታል ያስመዘገቡ ፕሮጀክቶች ወደ ስራ የገቡ ሲሆን፤ ከእነዚህ ውስጥ 3 ሺህ 519 ወደ ባለሀብትነት የተሸጋገሩ አርሶ አደሮች ሲሆኑ 316ቱ ወጣቶች መሆናቸው ተገልጿል። 450ዎቹ ሀገር በቀል ባለሀብቶች እና የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት እና 74 የማስፋፊያ ጥያቄ ያቀረቡ መሆናቸውንም የተጠቆመ ሲሆን፤ ለእነዚህ አልሚዎች 35 ሺህ 920 ሄክታር መሬት ተላልፏል ያሉት አቶ አዲሱ፤ ፕሮጀክቶቹ በሙሉ አቅም ወደ ስራ ሲገቡ ለ313 ሺህ 566 ወጣቶች የስራ ዕድል ይፈጥራሉ ሲሉ አቶ አዲሱ መናገራቸውን የዘገበው ፋና ብሮድካስት ኮርፖሬት ነው፡፡አዲስ ዘመን ታህሳስ 14/2013
https://www.press.et/Ama/?p=37944
115
0ሀገር አቀፍ ዜና
አገርን ከብተና ያዳነው ርምጃና ቀሪ የቤት ስራዎች
ሀገር አቀፍ ዜና
December 24, 2020
14
ጽጌረዳ ጫንያለው በሀገራችን ከለውጡ ወዲህ ከ113 በላይ ግጭቶች መከሰታቸውን የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ መጥቀሳቸው ይታወሳል። የነዚህ ግጭቶች ዋነኛ ዓላማ ደግሞ አገርን መበተንና የማያባራ የእርስ በርስ ግጭት መፍጠር እንደነበር ይገለጻል። ሆኖም የብልጽግና ፓርቲ ሰሞኑን ባካሄደው ስብሰባ እንደገለፀው፤ መንግስት በወሰዳቸው ጠንካራ እርምጃዎች ሃገርን ከብተና ማዳን ተችሏል። የፖለቲካ ሳይንስ ምሁራንም ይህ እሳቤ ትክክል መሆኑን በመጥቀስ፤ በቀጣይ በርካታ የቤት ስራዎች እንዳሉ ይጠቁማሉ።በደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካል ሳይንስና አለማቀፍ ግንኙነት መምህር ረዳት ፕሮፌሰር ዳምጠው ተሰማ እንደሚናገሩት፤ አገር በብዙ መንገዶች ልትበተን እንደደረሰች የሚያሳዩ ምልክቶች ነበሩ። ከእነዚህ መካከልም እያንዳንዱ ክልል ከማዕከላዊ መንግስት ጋር ያለው ግንኙነት የተራራቀ መሆኑ አንዱ ነው። ህወሓት ወታደራዊ፣ የፋይናንስ ዘርፍና የፖለቲካ ግንኙነቱን ከፌደራሉ መንግስት በወጣ መልኩ ሲያከናውን ታይቷል። ስልጣንና ኃላፊነቱ የፌደራል መንግስት ሆኖ ሳለም በራሱ በአደባባይ የክልል መከላከያ ማቋቋሙን ሲናገር ነበር። ምርጫ ማካሄዱ፤ ከኢትዮጵያውያን ይልቅ የሌሎች አገራት ዜጎች ይሻሉኛል ማለት መጀመሩም ሌላው በመርህ ብቻ ሳይሆን በተግባርም አገር የማፍረስ ዘመቻ መኖሩን አመላካች ነበር። እንደ ረዳት ፕሮፌሰር ዳምጠው ገለጻ፤ የህወሓት ጁንታ 27 ዓመት ሙሉ ከትጥቅ እስከ ሀሳብ ማስታጠቅ ድረስ ሰርቷል። በክልሎች ሰላምና መረጋጋት እንዳይኖርም አድርጓል። ከኢትዮጵያ ክልልነት ውጪ አገር እንመሰርታለን ብለው የሚነሱ አካላትን ስፖንሰር ሲያደርግም ቆይቷል። ይህ ደግሞ አገር የማፍረስ እንቅስቃሴ እንደሆነ የሚያነሱት ረዳት ፕሮፌሰሩ፤ የቡድኑን የሥነልቡና፤ ቁሳዊና የፋይናንስ አቅሙን ማዳከም መቻሉ ጥሩ ጅማሮና አገርን ከትልቅ አፍራሽ ሀይል መታደግ ነው። ሆኖም ጅማሬ እንጂ ፍጻሜ አይደለም። ምክንያቱም የጽንፈኛው ቡድን ተላላኪዎች፣ በስልጣን የቆዘሙ ሀይላት በተለያዩ ክልሎች ይገኛሉ። ነገ ችግርም የሚሆኑበት አጋጣሚ አለ። የፌደራል መንግስት አሁን እየሰራ ያለው ስራ እንዳለ ሆኖ በዚህ ሂደት የሚረሱ ይኖሩና በማን ይነካኛል ስሜት የህወሓትን ጁንታን ሊያዩ ስለሚችሉ፣ የዚያን ጊዜ ደግሞ ይህንን ያህል ዋጋ አገር እንድትከፍል ትሆናለች የሚሉት ረዳት ፕሮፌሰሩ፤ የህወሓት ጁንታ መንግስትን ልፍስፍስ አድርጎ መሳሉና በይፋም ከሌሎች አገራት ጦር መሳሪያ መግዛትና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ማድረጉ መታየቱን ገልጸዋል። ዛሬም ይህ አስተሳሰብ ካልተገራ የአገር መበተን እርሾ ሆኖ እንዲቀጥል ያደርጋል ይላሉ። በደብረብርሀን ዩኒቨርሲቲ የስነዜጋና ስነምግባር መምህርና የፖለቲካ ሳይንስ ምሁሩ አቶ ሀሳቡ ተስፋ በበኩላቸው፤ ከ1983 በኋላ ያለው የፌደራል መንግስት አደረጃጀት ብሔር ተኮር መሆኑ በራሱ አገር ለማፍረስ መሰረት እንደነበር ያነሳሉ። የጋራ ማንነቶችና ታሪኮች ኮስሰው ልዩነቶች እንዲጎለብቱ አድርጓል። የአንድነት ቀን ሳይሆን የልዩነት ቀኖች እንዲከበሩም እድል ሰጥቷል። አካባቢያዊ ማንነቶች ጎልብተው የአንተ አይደለም አስተሳሰቦችም ቦታ አግኝተዋል። በዚህም አገር ለመበተን ደርሳ እንደነበር ይናገራሉ። ኢትዮጵያ የምትባለው አገር ብትኖርም ኢትዮጵያዊነት ሳይሆን አካባቢያዊነት የተለየ ትኩረት እንደተሰጠው የሚናገሩት መምህር ሀሳቡ፤ ህዝቦችም ሆነ መንግስት አገር ላይ ሳይሆን አካባቢ ላይ የሚደርስ አደጋን እየለየ እሳት እንዲያጠፋም አስገድዶታል። ስለሆነም አሁን የተጀመረው ሥራ አገርን ከመበተን ታድጓል ይላሉ። ነገር ግን ብሔርን መሰረት ያደረገ የፌደራል ሥርዓት በህግ ጭምር መፍትሄ ካላገኘ መልሶ አገር የመበተኑ እንቅስቃሴ የሚያገረሽ እንደሚሆን ይገልጻሉ። አንድን አካል በማስወገድ ብቻ አገር ማዳን አይመጣም። አብዲ ኢሌ በሱማሌ ክልል ሲያደርስ በነበረው የጥፋትና የመከፋፈል ሥራ ወቅት የተወሰደው እርምጃ የዚህ ማሳያ ነው። ከዚህ ያልተማረው የህወሓት ጁንታም ብቻዬን አገር ካልመራሁ ብሎ ለማፍረስ ሲጣጣር ሴራው መምከን ችሏል። ይሁን እንጂ ከህወሓት ጁንታ በኋላም ሌላ ላለመምጣቱ ማረጋገጫ የለም። እናም አሁን የተደረገው አገርን ከመበተን የማዳን ጅማሮ እንጂ ፍጻሜ አይደለም። ምክንያቱም አገር መመስረት ህገ መንግስታዊ መብት ነው። በመሆኑም ሥራው በህገ መንግስት ምላሽ ካላገኘ አገር እንደማይድን ይናገራሉ።መፍትሔው ጅምሩን እያደነቁ የወደፊት የአገራዊ አንድነት እየሸረሸሩ የሚሄዱ ጉዳዮችን ከመሰረቱ እያደረቁና እየፈቱ መሄድ እንደሆነ የሚገልጹት ረዳት ፕሮፌሰር ዳምጠው፤ ፖለቲካዊ፣ ህገመንግስታዊና ማህበራዊ ጉዳዮች ላይ ማለትም ማህበረሰቡን በትምህርት በስነልቦና መስራት ይገባል። የፖለቲካና የስነልቦና ትርክቶች አንድነትን ለማምጣት በሚያስችሉ ሁኔታዎችን መቅረጽ ያስፈልጋል። የህወሓት ጁንታ ኢትዮጵያዊነትን በሚያቀነቅን ህዝብ የተጠላ በመሆኑ ህዝብ እንቢ ብሎት ለመንግስት እድል እንዲሰጠው ሁሉ በህዝብ መወደድ ላይም መስራት ይገባል ይላሉ። እንደ ረዳት ፕሮፌሰሩ ገለጻ፤ የለውጡ መንግስት በድርድር ቢሆን ኖሮ ከህወሓት ጋር አንድም ጥይት አይታኮስም። ነገር ግን ህወሓት የግራ ዘመሙ ጉዳይ የተጠናወተው በመሆኑ በዚህ መሸነፍ አልቻለም። ስለሆነም በቀጣይም አፈንጋጩንና ኢትዮጵያን የሚጠላውን በሚገባው ቋንቋ ማናገርና አገርን ማዳን መሰረታዊ ጉዳይ መሆን አለበት። ለስርዓቱም ሆነ ለህዝብ አደጋ የሆነ አካልን መቅኔውን መስበር ከተቻለ አገር አዳንን ሊያስብል ይችላል። አገርን ከማዳን አንጻር የተጀመረው ነገር ህዝብ ከአመጽ አይነኬ የሚባለውን ሁሉ እንደሚያሳፍር የታየበት ነው። ስለዚህም ይህንን ማስቀጠልና ትርክትንማስተካከል፣ የጋራ ራዕይን በትምህርት መገንባት፣ የፖለቲካ ትርክቶችን ገዳይ አስገዳይ ፣ በዳይ አስበዳይ ከሚለው ማውጣት፤ የጋራ የሚያደርጉትን ማጉላትና ልዩነቶችን መቀነስ እንዲሁም የነበረ ማውደምን ሳይሆን ጥሩውን መምረጥንም መማርና በተግባር ማሳየት ላይ መስራት እንደሚገባም ያስረዳሉ። አቶ ሀሳቡ እንደሚሉት ደግሞ፣ ህወሓትን ማጥፋት አገርን በዘላቂነት ከብተና የሚያድን ተደርጎ መወሰድ የለበትም። መፍትሄው ተመሳሳይ ሀሳብ ያላቸውን አካላት አሁን በተጀመረ መልኩ መግታት ነው። የአገረ መንግስት ግንባታውንም እንደ ብልጽግና ውህድ ፓርቲ መስርቶ ሁሉም ዜጋ ለአገር ያገባኛል እንዲል ማስቻል ይገባል። እናም ይህ ተግባር በቋሚነት ውጤት በሚያመጣ መልኩ መቀጠል ይኖርበታል። ከ27 ዓመት በላይ በስነልቦና የተለያየ ህዝብ ወደ ጋራ ታሪኩ መመለስ ላይ መስራትም ይገባል። በችግር ውስጥ ተሆኖ የመጣውን ለውጥ ፍርደ ገምድል ሳንሆን መደገፍና አንድነት ላይ መስራት ከሁሉም እንደሚጠበቅ አስረድተዋል። በተለይ ግን ለሁሉም መፍትሄ የሚሆነው ህገመንግስቱን በታኝ ሳይሆን ከብሔር አስተሳሰብ ወጥቶ በአንድነት ውስጥ ልዩነትን መጥኖ እያስተናገደ ማሻሻል ሲቻል እንደሆነ ይገልጻሉ። ቀደም ሲል በደርግ ሥርዓት አገር ለማፍረስ የተሞከሩ ተግባራት ታይተዋል። ከእነዚህ ውስጥም አገር ሊያፈርስ የሚችሉ ውሳኔዎች መኖራቸው የመጀመሪያው ነው። በፍርድ ቤት እንዲገደሉ ያልተወሰነባቸውን 12 ጀነራሎችን ጸረ አብዮት በማለት መረሸናቸው ለአገር መከታ የሚሆኑትን ከማሳጣቱም በላይ አገርን ለብተና የዳረገ ነበር። አገር መፍረስም መዳንም የሚችለው በእሳቤና በህግ ወይም በሀሳብ ፍሰት መሆኑ ይታወቃል። ስለዚህም በቀጣይ ሊመጡ የሚችሉ ብዙ ቂም ያረገዙ ነገሮች ይኖራሉና እነርሱን መመለስ በሚያስችል መልኩ መሆን እንዳለበት ምሁራኑ ይናገራሉ።አዲስ ዘመን ታህሳስ 15/2013
https://www.press.et/Ama/?p=37980
773
0ሀገር አቀፍ ዜና
ባለፉት 5 ወራት ከወጪ ንግድ 1 ነጥብ 33 ቢሊየን ዶላር ተገኝቷል ተባለ
ሀገር አቀፍ ዜና
December 23, 2020
18
መላኩ ኤሮሴአዲስ አበባ፡- ባለፉት 5 ወራት ከወጪ ንግድ 1 ነጥብ 44 ቢሊየን ዶላር ለማግኘት ታቅዶ 1 ነጥብ 33 ቢሊየን ዶላር መገኘቱን የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ ገለጹ። የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስትር አቶ መላኩ አለበል ትናንት ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ እንደተናገሩት፤ ባለፉት አምስት ወራት ከወጪ ንግድ 1 ነጥብ 44 ቢሊየን ዶላር ለማግኘት ታቅዶ 1 ነጥብ 33 ቢሊየን ዶላር ተገኝቷል። በዚህም ለማሳካት ከታቀደው 94ነጥብ3 በመቶ ማሳካት ተችሏል። የአምስት ወር አፈጻጸም ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ224 ሚሊየን ብር ወይም የ20 በመቶ ብልጫ እንዳለው ያብራሩት ሚኒስትሩ፤ የህዳር ወር ብቻ ከታየም የ23 በመቶ ብልጫ የተመዘገበበት መሆኑን ገልጸዋል። የኮቪድ ወረርሽኝ በአለም ላይ ከፍተኛ ጫና ባሳደረበት እና እንደ ሃገርም ሰፊ የህግ ማስከበር ስራ እየተሰራ ባለበት ወቅት ይህ አፈፃፀም ከፍተኛ መሆኑንም ነው ሚኒስትሩ የተናገሩት። እንደ አቶ መላኩ ማብራሪያ፤ ባለፈው ዓመት ህዳር ወር ከወጪ ንግድ 191 ሚሊየን ዶላር የተገኘ ሲሆን በዚህኛው ዓመት በህዳር ወር ብቻ 232 ሚሊየን ዶላር ተገኝቷል። ይህም ከአምናው 43 ሚሊየን ዶላር ብልጫ አለው። ይህ ውጤት እንዲገኝ በማድረግ ረገድም የግብርናው ዘርፍ አጠቃላይ የወጪ ንግድ ወደ 62 በመቶ ሲሸፍን፤ ኢንዱስትሪ 12 በመቶ እንዲሁም ማዕድን ወደ 23 በመቶ እንደሚሸፍን ተናግረዋል። ባለፉት አምስት ወራት የግብርና የወጪ ንግድ ከእቅዱ 76 በመቶ ማሳካቱን ያብራሩት አቶ መላኩ፤የኢንዱስትሪ ውጤቶች ከእቅዱ 93 በመቶ እንዲሁም ማዕድን ከመቶ ፐርሰንት በላይ ማሳካት እንደተቻለ ተናግረዋል። እንደ ሚኒስትሩ ማብራሪያ፤ በፖሊሲ ደረጃ የተሰሩ ስራዎች እና እስከ ታች ድረስ ተቀናጅቶ መሰራቱ በወጪ ንግድ ዘርፍ ለተመዘገበው መልካም አፈጻጸም ከፍተኛ አስተዋጽኦ ነበረው። አሁን የተጀመረው ሰላም የማስከበር ሁኔታ፣ የንግድና ኢንዱስትሪ ማሻሻያ ስራዎች ሙሉ በሙሉ ወደ ተግባር ሲገቡ ደግሞ የወጪ ንግድ ስራዎች ከዚህ የተሻለ ውጤት ሊያስመዘግቡ ይችላሉ። ሚኒስትሩ በመግለጫቸው፣ አነስተኛና መካከ ለኛ ኢንዱስትሪዎች አስፈላጊነት፣ በሀገራችን ኢንዱስትሪዎቹን እያጋጠሙ ያሉ ችግሮች፣ ችግሮቹን ለመፍታት እየተሰሩ ያሉ ስራዎች እንዲሁም መሰረታዊ ምርቶች አቅርቦትን ለማሻሻል የተሰሩ ስራዎች ዙሪያ ማብራሪያ ሰጥተዋል። በዚህም የሀገሪቱ አነስተኛና መካከለኛ ኢንዱስትሪዎች የተቀናጀ ድጋፍ አላገኙም፤ መሬት የኤሌክትሪክና ሌሎች መሠረተ ልማቶች፣ የፋይናንስ አቅርቦት፣ የውጭ ምንዛሪ፣ የሰለጠነ የሰው ሃይል፣ የገበያ ችግር ኢንዱስትሪዎችን እየተፈታተናቸው መሆኑን ተናግረዋል። እነዚህን ችግሮች ለመቅረፍ እየተሰራ መሆኑን ያብራሩት ሚኒስትሩ፤ የፋይናንስ አቅርቦት ችግሩን ከመፍታት አንጻር ለሊዝ ፋይናንስ 2ነጥብ2 ቢሊየን ብር፣ ለስራ ማስኬጃ 3ነጥብ2 ቢሊየን ብር፣ እንዲሁም ለፕሮጀክት ፋይናንስ 3ነጥብ2 ቢሊየን ብር በድምሩ 8ነጥብ6 ቢሊየን ብር መቅረቡን አስረድተዋል። በዚህም 1ሺ990 ኢንዱስትሪዎች ተጠቃሚ መሆናቸውን ጠቁመዋል። የኢንዱስትሪዎቹን የቅንጅት ችግሮችን ለመፍታትና በቂ ድጋፍ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ ነው ያሉት ሚኒስትሩ፤ ከክልል ርዕሰ መስተዳድሮች ጋር ውይይት መደረጉን እና ከትናንት ጀምሮ እስከ ታህሳስ 20 ድረስ ከሁሉም ክልል የካቢኔ አባላት ጋር ቀደም ሲል በነበረው አፈፃፀምና ቀጣይ በሚኖረው ላይ ውይይት እንደሚደረግ አብራርተዋል። ለኢንዱስትሪዎቹ ቋሚ ድጋፍ የሚደረግበት የጋራ አሰራር መቀየሱን እና የግንዛቤ ፈጠራ ስራም በትኩረት እንደሚሰራ ተናግረዋል። እንደ አቶ መላኩ ማብራሪያ፤ ተበዳሪዎች በበቂ ዕውቀት ስራቸውን እንዲሰሩ ከኢንስቲትዩቶች ጋር የተቀናጀ ስልጠና በመስጠት ሙያቸውን እያሻሻሉ እንዲሄዱ ይደረጋል። የአቅርቦት ችግርን መፍታት ሌላኛው ትኩረት የሚሰጠው ጉዳይ በመሆኑም፤ የመሳሪያና የግብዓት አቅርቦት ችግሮችን ለመፍታት ኢግልድና ኢትዮ-ኢንጂነሪንግ በአዲስ መልክ ወደ ስራ እንዲገቡ ተደርጓል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 14/2013
https://www.press.et/Ama/?p=37943
428
0ሀገር አቀፍ ዜና
በሱዳን ካርቱም ሲካሄድ የቆየው ሁለተኛው የኢትዮጵያ-ሱዳን የድንበር ጉዳዮች ከፍተኛ ደረጃ የፖለቲካ ውይይት ተጠናቀቀ
ሀገር አቀፍ ዜና
December 24, 2020
8
በጋዜጣው ሪፖርተርአዲስ አበባ፡- ታህሳስ 13 እና 14 ቀን 2013 ዓ.ም በሱዳን-ካርቱም ለሁለት ቀናት ሲካሄድ የቆየው ሁለተኛው የኢትዮጵያ-ሱዳን የድንበር ጉዳዮች የከፍተኛ ደረጃ የፖለቲካ ውይይት ትናንት ተጠናቀቀ፡፡በውይይቱ፣ ሁለቱ ወገኖች በጋራ የድንበር አካባቢ ወቅታዊ ጉዳዮችን በተመለከተ ሃሳቦችን የተለዋወጡ ሲሆን፤ ከጥቅምት ወር መጨረሻ ጀምሮ በጋራ ድንበር አካባቢ በሱዳን በኩል የተደረጉ አዳዲስ ለውጦችና እንቅስቃሴዎች የቀደሙ ስምምነቶችን የሚጥሱ እና መሬት ላይ ያለውን እውነታ የሚለውጡ በመሆናቸው በአስቸኳይ እንዲቆሙና ወደ ቀደመ ቦታቸው እንዲመለሱ ኢትዮጵያ አሳስባለች።ከዚሁ ጋር ተያይዞ በገበሬዎች እና ባለሃብቶች ንብረት ላይ የደረሰ ከፍተኛ ጉዳት እና የዜጎች መፈናቀል ትኩረት እንደሚያሻው እና በአስቸኳይ መታረም ያለበት መሆኑን ኢትዮጵያ አሳስባለች።በተጨማሪም የሁለቱ አገሮች የጋራ ድንበር በተመለከተ ያሉ ማናቸውንም ዓይነት ልዩነቶች ሁሉንም በሚያስማማ መንገድ በውይይት ስለመፍታት እና የወደፊት አቅጣጫ ምን ይሁን በሚለው ዙሪያ መክረዋል።በኢትዮጵያ በኩል የድንበሩን ጉዳይ ሰላማዊ በሆነ መልኩ ከቀደሙ ስምምነቶች ጋር በተጣጣመ መንገድ ከድንበሩ ጋር በተያያዘ የተቋቋሙና ስራቸውን ያላጠናቀቁ ልዩ ልዩ ኮሚቴዎችን ስራቸውን እንደገና እንዲጀምሩ በማድረግ መፈታት እንዳለበት ተገልጿል። ይህም የሁለቱን አገራት ስትራቴጂካዊ እና ወንድማማቻዊ ግንኙነት እና የሁለቱን ሕዝቦች ዘላቂ ፍላጎትና ጥቅም የሚያስጠብቅ እንደሚሆን ተገልጿል።ሁለቱ ወገኖች በቀጣይ ምክክራቸውን ለሁለቱ ወገኖች በሚመች ጊዜ በአዲስ አበባ ላይ ለማካሄድና ለመሪዎቻቸው የዚህኛውን ስብሰባ ሂደትና ውጤት ሪፖርት በማቅረብ በሚሰጣቸው አቅጣጫ መሰረት ምክክራቸውን ለመቀጠል በመስማማት ስብሰባውን አጠናቅቀዋል። በቀጣይ ስብሰባ በአካባቢው ያሉ ለውጦችን በመገምገም የድንበር ኮሚቴዎች ስራቸውን የሚቀጥሉበት ሁኔታ ላይ እንደሚመክሩ ይጠበቃል።የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን በክቡር የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን የተመራ ሲሆን፤ ከሱዳን ጠቅላይ ሚኒስትር አብደላ ሐምዶክ እና የሉዓላዊ ምክር ቤት ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዚዳንት ጄኔራል ሞሐመድ ሐምዳን ዳጋሎ ጋር ተገናኝተው ውይይት አድርገዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 15/2013
https://www.press.et/Ama/?p=37982
233
0ሀገር አቀፍ ዜና
ሚሊዮን ወልዴ ወደ አትሌቲክስ አሰልጣኝነት ገብቷል
ስፖርት
January 15, 2020
42
ኢትዮጵያ ከፍተኛ ውጤት ባስመዘገበችበት የሲድኒ ኦሊምፒክ 5ሺ ሜትር ካሸነፈ በኋላ ደስታውን የገለፀበት የተለየ መንገድ በብዙዎች ዘንድ እስካሁንም እንዲታወስ ያደርገዋል፡፡ በወቅቱ ወጣት አትሌት የወርቅ ሜዳሊያ ማስመዝገቡ ከፍተኛ ደስታ የፈጠረ ቢሆንም በአትሌቲክስ ቤተሰቡ ዘንድ ተተኪ አትሌት መታየቱ ግን የተለየ ስሜት ያስገኘ ነበር፡፡ ነገር ግን ድንገት የታየው ተስፋ በቀጣይነቱ ሊገፋ አልቻለም፡፡ የያኔው ወጣት አትሌት ሚሊዮን ወልዴ ከሲድኒ ኦሊምፒክ ጣፋጭ ድሉ በኋላ በሌሎች ታላላቅ ውድድሮች ተጨማሪ ስኬት ያስመዘግባል ተብሎ እምነት ቢጣልበትም በውድድሮች ሳይታይ ቀርቷል፡፡ ውድድሩን እንዳጠናቀቀ ድሉን ያከበረበት መንገድ ከአብዛኛው ህዝብ የትዝታ ማህደር የማይደበዝዘውና እስካሁንም ለዓመታት መጥፋቱ የስፖርቱ ቤተሰብ ጥያቄ የሆነው የቀድሞው አትሌት ሚሊዮን ወልዴ ከጥቂት ዓመታት በፊት ለትምህርት ወደ አሜሪካን አገር እንደተጓዘ ይታወቃል፡፡ ኢትዮጵያ በጀግኖች አትሌቶቿ አራት የወርቅ፣ አንድ የብርና ሶስት የነሃስ በጥቅሉ በስምንት ሜዳሊያዎች ከምንጊዜውም የተሻለ ውጤት ባስመዘገበችበት የሲድኒ ኦሊምፒክ አንድ የወርቅ ሜዳሊያ እንዲመዘገብ ምክንያት የሆነው ሚሊዮን ለረጅም ጊዜ በትራክ እንዲሁም በተለያዩ ውድድሮች ባይታይም አሁን በባህር ማዶ ታዳጊዎችን በማሰልጠን ላይ ይገኛል፡፡ አትሌቱ በተለይ የታወቀው በሲድኒው ኦሊምፒክ ይሁን እንጂ በዓለም አቀፍ ውድድር ለመጀመሪያ ጊዜ የታየው እአአ በ1998 ሲሆን፤ በተሳተፈበት ርቀት የዓለም ወጣቶች ቻምፒዮን ነበር፡፡ በቀጣዩ ዓመት ደግሞ በቤት ውስጥ ቻምፒዮና ሃገሩን በመወከል ከታላቁ አትሌት ኃይሌ ገብረስላሴ ጋር ተሳትፎ በ3ሺ ሜትር የነሃስ ተሸላሚ ሆኗል:: ራን ብሎግ ራን የተሰኘው ድረገጽ ከአትሌቱ ጋር በነበረው ቃለምልልስ አንጋፋው አትሌት በአሜሪካ በሚገኝ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ውስጥ የሃገር አቋራጭ አትሌት ተማሪዎችን እያሰለጠነ እንደሚገኝ ተናግሯል፡፡ ወደ አትሌቲክስ ስፖርት እንዴት እንደገባ የተጠየቀው ሚሊዮን ‹‹ልጅ እያለሁ ኳስ ነበር የምጫወተው፤ ለሌሎች ስፖርቶችም ፍላጎት ነበረኝ፡፡ እኔ ከጓደኞቼ ጋር ኳስ በምጫወትበት ሜዳ ላይም በርካታ አትሌቶች በየቀኑ ልምምድ ሲሰሩ እመለከት ነበር፤ ይህም ፍላጎት አሳድሮብኝ ወደ ስፖርቱ ልገባ ቻልኩ›› ሲል መነሻውን አስታውሷል፡፡ ፈጣን ሯጭነቱ ወደ አትሌትነት ለመሸጋገሩ ምክንያት ሲሆን፤ ወደ ክለብ ለመቀላቀልም የወሰደበት ጊዜ አጭር ነበር፡፡ የገባበት ክለብ በሃገሪቷ የተሻለ ከሚባሉት መካከል በመሆኑም በውድድር ተሳታፊ ለመሆን ረጅም ጊዜ አልወሰደበትም፡፡ አሁን እያሰለጠነ በሚገኘው የሃገር አቋራጭ ውድድር ተሳታፊ የሆነው እአአ በ1996 የደቡብ አፍሪካዋ ኬፕ ታውን አስተናጋጅ የነበረችበት ውድድር ነው፡፡ በወቅቱ አሸናፊ በመሆኑ ከሃገሪቷ መሪ ኔልሰን ማንዴላ እጅ ሜዳሊያ የተበረከተለትን አጋጣሚም የማይዘነጋው ነው:: ሌላኛው የማይዘነጋና አስደሳቹ አጋጣሚ የኦሊምፒክ ወርቅ ሜዳሊያን ማጥለቅ ነው፡፡ ‹‹በህይወቴ ትልቅ ስፍራ ያለውም ነው፤ መንግስትን ጨምሮ ከበርካታ አካላትም ሽልማቶችን አግኝተናል›› በማለትም ሚሊዮን ያለፈውን ስኬት ያስታውሳል፡፡ በአሜሪካውያንና ኢትዮጵያውያን አትሌቶች መካከል ያሉትን ልዩነቶች እንዲጠቅስ የተጠየቀው ሚሊዮን የጎላ ልዩነት አለመኖሩን አንስቷል፡፡ ነገር ግን አሜሪካ በተሟላ የስልጠና ቁሳቁስና በሳይንሳዊ ስልጠና አትሌቶችን ስትደግፍ በኢትዮጵያ ያለው ሁኔታ በተወሰነ መልኩ ለስልጠና አስፈላጊ የሆኑ ቁሳቁስን ብቻ ማግኘት የሚቻልበት ሁኔታ ላይ ልዩነት እንዳለ ያብራራል፡፡ ለወጣት አትሌቶች ስኬታማነት ልምዱን ያካፈለው አሰልጣኝ ሚሊዮን ወጣት አትሌቶች ለራሳቸው ግብ በማስቀመጥ ጠንክረው መስራትና ጥረት ማድረግ እንዳለባቸው ያስቀምጣል:: ይህንን የሚያደርጉ ከሆነም በብቃታቸው ውጤታማ መሆን እንደሚችሉ ያለውን እምነት ገልጿል፡፡ አዲስ ዘመን ጥር 6/2012 ብርሃን ፈይሳ
https://www.press.et/Ama/?p=25653
402
2ስፖርት
የሕግ የበላይነት ባለመከበሩ፣ እንደ አገር ከተመዘገቡት ድሎች ያመለጡት ዕድሎች በእጅጉ የበዙ መሆናቸው ተገለፀ
ሀገር አቀፍ ዜና
December 24, 2020
35
ዋቅሹም ፍቃዱአዲስ አበባ፡- ኢትዮጵያ በተፈጥሮ ሀብት የበለጸገች፣ ህዝቦቿም በአንድም በሌላ በደም የተሳሰሩ ቢሆንም ሁሉንም በእኩል የሚዳኝ፣ የአገር ልማትና ፍትሐዊ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጥ ህግ ተግባራዊ ባለመደረጉ ምክንያት ባለፉት ዓመታት እንደ አገር ከተመዘገቡ ውጤቶች፣ ያመለጡ በረከቶች በእጅጉ እንደሚያመዝኑ የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር አበረ አዳሙ ገለጹ፡፡ኮሚሽነሩ፣ በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ በሰጡት አስተያየት፤ አገራችን በተፈጥሮ ሀብት የበለጸገች በመሆኗ በቀላሉ ሰርተው የሚለወጡባት፣ አየሯ ተስማሚና ለኑሮ የምትመች ናት፡፡ ይሁን እንጂ በከፋፋይ አስተሳሰብ የተቃኘና ከአገር ይልቅ የቡድኖች ህግ ለዘመናት ገዝፎ በመቆየቱ ለሌላ መትረፍ የምትችል አገር በምግብ እንኳ ራሷን መቻል አቅቷት ለውጭ እርዳታ እጇን ስትዘረጋ ቆይታለች፡፡ ዛሬም ከውጭ እርዳታ ባለመላቀቋ እና የዚህ ምክንያቱም ተፈጥሯዊ ሳይሆን ሰው ሰራሽ እንደመሆኑ ሁሉም ዜጋ በቀጣይ በኢትዮጵያ እድል ላይ አስቦና ትኩረት ሰጥቶ ሊሰራ ይገባል።እንደ ኮሚሽነር አበረ ገለጻ፤ ህግና ልማት የማይነጣጠሉ የአንድ ሳንቲም ሁለት ገጽታዎች ናቸው። ያለፉት ታሪኮች አገርና ህዝብ ባልተስተካከለ ሚዛን የሚመራ ህግ ተግባራዊ ባለመደረጉ ምክንያት ኢትዮጵያ አስከፊ ብጥብጥና ውድመት ለማስተናድ ተገዳለች። ይህ ደግሞ አገሪቱን አቅም አሳጥቶ፣ አመት ሙሉ ምርት ማምረት የሚያስችሉ ወንዞችና ለም አፈር እያላት የስንዴ ለማኝ ሆናለች።ወደ ዘመነ መሳፍንትና ከዚያ በፊት ያሉ ዘመናት በታሪክ ሲቃኙ የኢትዮጵያ ህዝቦች ከዳር ወደ መሀል አገር እንዲሁም ከመሀሉ ወደ ዳር በተደረገው እንቅስቃሴ በጋብቻ ያልተሳሰረና ያልተዋለደ እንደሌለ የሚናገሩት ኮሚሽነሩ፤ ከተወሰኑ ዓመታት ወዲህ ግን ጎጠኝነት በመንሰራፋቱ ምክንያት በደም መተሳሰራችን ተረስቶ፣ የህግ የበላይነትም ጠፍቶ፣ ይልቁንስ ህግ በአገር እይታ ሳይሆን በቡድን እይታ የሚተረጎምበትና የሚተገበርበት ዘመናት እንደ ነበሩ ያስረዳሉ።በቡድን የሚቃኝና የሚዳኝ ህግ ለአገር ዕድገት ትልቅ ማነቆ ስለሆነ፣ ለአገር እድገት ከታሰበ ህግ ለሁሉም ክፍት መሆን እንደሚያስፈልግ የጠቆሙት ኮሚሽነሩ፤ ህግ ከአገርና ከህዝብ ፍላጎት አንጻር እየተሻሻለ የሚሄድ እንጂ ከቡድን ፍላጎት አኳያ የሚሻሻል ወይም የሚተው አለመሆኑን ገልጸዋል። የቡድን ህግ ደግሞ በባህሪው ቡድኑን የሚጠቅምና የሌላውን የሚጎዳ በመሆኑ አገራችንን ምን ያህል ዋጋ እንዳስከፈላት ባለፉት 27 ዓመታትን ማየት ብቻ በቂ እንደሆነ ኮሚሽነሩ ገልጸዋል።እንደ ኮሚሽነሩ ገለጻ፤ ህግና ህገ መንግስታዊ ስርዓት ተግባራዊ እንዲሆን እንዲሁም የህግ የበላይነት እንዲረጋገጥ፣ በመጀመሪያ ደረጃ ሰው ህግን እንደ ቡድን ወይም እንደ ብሔር ሳይሆን እንደሰው በሳይንሳዊ ዘዴ ማሰብ አለበት። ካልሆነ የአገር ህልውናና የህዝቦች አብረው የመኖር ዋስትና አደጋ ላይ ይወድቃል። ሲቀጥል፣ የፍትህ ተቋማት በሙያዊ ስነ ምግባርን በተላበሰ መልኩ ያለምንም አድሎ ህዝብና አገር በቅንነትና በፍጹም ቁርጠኝነት ማገልገል ይጠበቅባቸዋል። ህዝብም እንደ ህዝብ ህግን አውቆ ለመብቱ ዘብ የመቆም፣ ግዴታውን በአግባቡ የሚወጣ መሆን አለበት። ከሁሉም በላይ ደግሞ መንግስት ለህግ የበላይነት እንዲረጋገጥ ግንባር ቀደም ሚና መጫወት ይጠበቅበታል።ለላቀ የአገር ልማት እና አንድነት ያገኘነው መልካም ውጤቶች በአግባቡ ለመያዝ እንዲሁም ያመለጡን ዕድሎች እጃችን ለማስገባት የህግ የበላይነት መከበር ቁልፍ ጉዳይ መሆኑን የገለጹት ኮሚሽነር አበረ፤ ሳይንሳዊ የህግ ምክሮችና የልማት ጉዳዮችን አስመልክተው በመጽሐፉ ያሰፈሩት ሀሳቦች በተቻለ መጠን በተለያዩ ቋንቋዎች ተተርጉሞ ህዝቡ ጋር እንዲደርስ ጥረት በማድረግ፣ አገራችን የጀመረችውን የብልጽግና ጉዞ እውን ለማድረግ እንደሚሰሩ አሳውቀዋል።ኮሚሽነሩ፣ ጊዜያዊ ችግሮች ላይ ከመጠመድ ይልቅ ዘላቂ መፍትሔ ላይ በማተኮር ያደጉ አገሮች የተከተሉት የህግ ሳይንስ በአገራችን ነባራዊ ሁኔታ ጋር በማስተሳሰር “የህግ የበላይነት ለሀገራዊ ልማት” በሚል ርዕስ የጻፉት መጽሐፍ ለአንባቢያን እንደበቃም ተናግረዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 15/2013
https://www.press.et/Ama/?p=37981
427
0ሀገር አቀፍ ዜና
ከጭጋጉ ማግስት ነዋሪዎቹን የተቀበለው ገደብ ወረዳ
ሀገር አቀፍ ዜና
December 24, 2020
13
ክፍለዮሐንስ አንበርብርወይዘሮ ሽታዬ ወትዬ፣ ጌዴኦ ዞን ገደብ ወረዳ ጎቲቲ ቀበሌ ነዋሪ ናቸው። ምንም እንኳን በአሁኑ ወቅት በመንግስት እና ዓለም አቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያውያን መብት በተሰኘው ግብረሰናይ ድርጅት ድጋፍና አያሌ ጥረት የሠላም አየር መተንፈስ ቢችሉም፤ በ2010 ዓ.ም የጉጂ ኦሮሞዎች እና ጌድኦዎች መካከል በተፈጠረው ግጭት በሕይወታቸው የማይረሳ ክፉ ጠባሳ ጥሎባቸው ያለፈ ወቅት መሆኑን ያስታውሳሉ።ወይዘሮ ሽታዬ፣ ‹‹በወቅቱ መንታ ወልጄ ነበር። ምንጩ ምንድነው የሚለውን እስከዛሬ በቅጡ በማናውቀው ግጭት አካባቢው የጦር አውድማ ሆነ። ግራ እና ቀኝ እሳት ነው፤ የማያቋርጥ ጥይት ሩምታ ነበር። አዝመራው ወደመ፣ እንስሳት ተዘረፉ። የተገኘውን ቤት ንብረት ማውደምና ማቃጠል ሆነ። ነገሩ የውጭ ወራሪ ጠላት የመጣ እንጂ ወንድማማች በሆኑ ሕዝቦች መካከል የተከሰተ ጊዜያዊ ግጭት አይመስልም ነበር። ከሰፈር ውስጥ ወንድና ሴቱ ሁሉ እግሬ አውጪኝ ብሎ ወደ ጫካ ተሰደደ። እኔም ሁለት ልጆቼን ታቅፌ በእግሩ ድክ ድክ የሚለውን ሌላኛውን ልጄን አስከትዬ ነብሴን ለማትረፍ ወደ ጫካ ብን ብዬ ሄድኩ። መሳሪያ በየአቅጣጫው ያለማቋረጥ ይተኮስ ነበር። በዚህ ጊዜ በእግሩ ይራመድ የነበረው ሕፃን ልጄ ወደየትኛው ሥፍራ እንደተሰወረ ማወቅ አልቻልኩም፤›› ይላሉ በወቅቱ ያሳለፉትን ከባድ ፈተና ሲያስታውሱ።በ2010 ዓ.ም በተፈጠረው ግጭት የመከራው ሰለባ ከሆኑት መካከል በአሁኑ ወቅት የ12ተኛ ክፍል ተማሪ የሆነው አቡሽ በቀለ ሌላኛው ባለታሪክ ነው። በወቅቱ የተከሰተው ችግር ሲያስታውስ እንባውን መቆጣጠር አልተቻለውም። “እንኳንስ ሰው ሣር ምድሩ ተጨንቆ ነበር። የዓለም ገበያን ትኩረት ይስብ የነበረው የቡና ምድር፤ የደም ምድር ሆኖ ዓለም አቀፍ ሚዲያዎች መሳለቂያ መሆናችን ያሳዝናል። ያኔ! አካባቢው ተወረረ። ቤት፣ ሳር ቅጠሉ ነደደ። የተገኘውን ሁሉ መግደልና መዝረፍ ሆነ። አቅመ ዳካማ ሴቶችና አባቶች ሳይቀሩ ፍዳቸውን አዩ። ሮጦ ማምለጥ ያልቻለ ሰው የጥይት ራት ሆነ። ይህ የሆነው ደግሞ በደስታም በመከራም ተለያይቶ በማያውቅ የአንድ አካባቢ ማህበረሰብ ሲሆን፤ የሆነው ሁኔታ ግን ያሳዝናል፤” ሲል በትካዜ የሆነውን ይናገራል።‹‹ግጭቱ ቢያልፍም የዘመናት ህልማችንን ይዞት ሄዷል። ከ30 ዓመት በፊት አባታችን የሰራው ቤትና በቤቱ ውስጥ የነበረው ንብረት በሙሉ ወድሟል። ያፈራው ጥሪት ወደ ዶጋ አመድ ተቀይሯል። ለነገ ብለን ያሰብነው ለዛሬውም ትውልድ ሳይሆን መጥፎ ታሪክ ልናወራ ተገደናል። አሁን ያለነው በፈጠሪ መልካም ምህረትና ግብረ ሰናይ ድርጅት እገዛ ነው›› የሚለው ተማሪ አቡሽ፤ በአሁኑ ወቅት ግን ትምህርቱን ቢቀጥልም አንድ ዓመት በችግሩ ምክንያት በሠላምና ስንቅ እጦት ትምህርት ማቋረጡን ተናግሯል።የገደብ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሲሣይ ታደሰ በበኩላቸው እንደሚሉት፤ ወቅቱን ለማስታወስና የሆነውን ለመናገር “የጨከነ ልብ” ያስፈልጋል። ያ ችግር እንዳይፈጠር ግን ቀደም ብሎ አልፎ አልፎ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለማቃለል ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ውይይቶች ሲደረጉ ነበር። በአካባቢ ችግሮች ቢኖሩ እንኳን በአባገዳዎችና የሃይማኖት አባቶች ተግሳፅ አፈንግጦ ለንብረት ውድመትና ለሕይወት መጥፋት የሚዳርግ ክስተት አልነበረም። በ2010 ዓ.ም የተፈጠረው ግን በአካባቢ ነዋሪዎች ዘንድ በእጅጉ የከፋ ጠባሳ ጥሎ ያለፈ ነበር።ሆኖም ችግሩ ከተከሰተ ጀምሮ አጎራባች ወረዳዎች፣ የደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል መንግስት፣ ኦሮሚያ ክልል መንግስት፣ የፌደራል መንግስትና የሚመለከታቸው አካላት ርብርብ በማድረግ ነገሮች ወደ መደበኛ ሁኔታዎች እንዲመለሱ ጥረት ተደርጓል። በአሁኑ ወቅትም ነዋሪው በመንግስትና ግብረ ሰናይ ድርጅቶች ትብብር ወደ ቀድሞ ቀያቸው ተመልሰው ኑሯቸውን በተለመደው ሁኔታ እያስኬዱ ለዘላቂ ሠላም ውይይት እየተደረገ ነው። በወረዳው 45ሺ ተፈናቃዮች እና በ13 ቀበሌዎች የሚገኙ 4ሺ200 ቤቶች ተቃጥለው እንደነበር ያስታወሱት አቶ ሲሳይ፤ በተደረገው ድጋፍ የወረዳው ነዋሪዎች ወደ ሰላማዊ መንገድ ከመመለሳቸውም በተጨማሪ፣ በአደጋው 855 ቤቶችና ቤተ እምነቶች በዓለም አቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያውያን መብት ግብረ ሰናይ ደርጅት ድጋፍ ተመልሶ መገንባታቸውን ተናግረዋል። በችግሩ ለተጎዱ ቤተሰቦችም የምግብና አልባሳት ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ፣ ዶሮዎችና በጎች መሰጠታቸውንም ገልጸዋል። ዓለም አቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያውያን መብት በአርቲስትና አክቲቪስት ታማኝ በየነ አስተባባሪነት በፈረንጆቹ አቆጣጠር በ2013 ሳዑዲ አረቢያ 163ሺ ኢትዮጵያውያንን አገሬ ለቃችሁ ውጡልኝ ብላ ከፍተኛ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ስታደርስና ኢትዮጵያውያን ሲንገላቱ የተመለከቱ ኢትዮጵያውያን ተቆርቋሪነት የተመሰረተ የበጎ አድራጎት ደርጅት ሲሆን፤ በኢትዮጵያ አራቱም አቅጣጫዎች ችግሮች ሲከሰቱ በርካታ እገዛዎችን ሲያደርግ መቆየቱን የሚናገሩት ደግሞ ዓለም አቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያውያን መብት የቦርድ አባል ፕሮፌሰር አቻለምየለህ ደበላ ናቸው።ፕሮፌሰር አቻምየለህ እንደሚሉት፤ ዓለም አቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያውያን መብት ከምስረታው ጀምሮ በውጭ እና በአገር ውስጥ ያሉ ኢትዮጰያውያን እክል በገጠማቸው ጊዜ ከአጠገባቸው አልተለየም። ለአብነትም ከቡራዩ፣ ሻሸመኔ፣ ወልቃይትና ጉራፈርዳ በግጭት ሳቢያ ለተፈናቀሉ ዜጎች በሚሊዮኖች የሚቆጠር ድጋፍ አድርጓል። የኮረና ቫይረስ ስርጭትን ለመግታት ብሎም ከዓመታት በፊት የቆሼ የቆሻሻ ክምር ተንዶ በዜጎች ላይ ላደረሰው ጉዳትም ድጋፍ አድርጓል።በጌዴኦ በተፈጠረው ግጭት ለተፈናቀሉ ዜጎች በወርልድ ቪዥን አማካኝነት የምግብና የአልባሳት ቁሳቁስ ሲያደርግ ቆይቷል። ከዚህ በተጨማሪም 37 ሚሊዮን 700ሺ ብር በማውጣት በእሳት የወደሙ ቤቶችንን የመገንባትና ነዋሪዎችን ወደቀያቸው የመመለስ ሥራ ማከናወኑንና በቀጣይም ለኢትዮጵያውያን ክብርና ሥም የሚመጥን በጎ ተግባር እንደሚያከናውን እና በመላው ዓለም ድጋፍ የማሰባሰብና አገር የመታደግ ሥራውን እንደሚያጠናክሩ ፕሮፌሰር አቻምየለህ አረጋግጠዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 15/2013
https://www.press.et/Ama/?p=37992
626
0ሀገር አቀፍ ዜና
“የህወሓት መኖር ለትግራይ ህዝብ ኪሳራ እንጂ ጥቅም አላስገኘለትም” ሲሉ የትግራይ ተወላጅ ዳያስፖራ አባላት ገለጹ
ሀገር አቀፍ ዜና
December 24, 2020
9
በጋዜጣው ሪፖርተርአዲስ አበባ፡- የህወሓት መኖር ለትግራይ ህዝብ ኪሳራ እንጂ ጥቅም አላስገኘለትም ሲሉ በአሜሪካ፤ በካናዳና በአውሮጳ የምንኖር ዳያስፖራ የትግራይ ተወላጆች ገለጹ፡፡ የፌዴራል መንግስት በክልሉ የወሰደውን የሕግ ማስከበር እርምጃ የሚደግፉ መሆኑንም በውጭ አገር የሚኖሩ (ዳያስፖራ) የትግራይ ተወላጆች የፌደራል መንግስት የጀመረውን ሕግን የማስከበር እርምጃን አስመልክቶ ባወጡት የጋራ የአቋም መግለጫ ገልጸዋል፡፡በመግለጫውም፣ እኛ በአሜሪካ፤ በከናዳና በአውሮጳ የምንኖር ዳያስፖራ የትግራይ ተወላጆች በሀገራችን በተለይም የህወሓት ጁንታ በለኮሰው እሳት ሳቢያ መንግስት እየወሰደ ያለው እልህ አስጨራሽ ሕግንና ስርዓትን የማስከበር እርምጃን አስመልክቶ ማሕበራዊ ሚዲያን በመጠቀም ተሰባስበን በመወያየት በተስማማንባቸው ሃሳቦች መሰረት የለውጡን አጋርነታችንን እንገልጻለን፤” ብለዋል። በመግለጫው አያይዘው እንዳመለከቱትም፤ “የህወሓት መኖር ለትግራይ ሕዝብ ኪሳራ እንጂ ጥቅም አላስገኘለትም። ህወሓት የትግራይ ሕዝብን ደም፤ ጉልበትና ሃብት ለሶስት ቡድናዊ አላማዎች ተጠቅሞበታል። በዚህም አንደኛ፤ የትግራይ ለጋ ወጣቶችን ከደደቢት እስከ አዲስ አበባ ቤተ መንግስት በትረ ስልጣን ለመጨበጥ እንደመረማመጃ አድርጎ ከተጠቀመባቸው በኋላ እንደ ሳልቫጅ ዕቃ ሜዳ ላይ እንዲወድቁ አድርጓል።ሁለተኛም፣ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ የትግራይ ለጋ ወጣቶች በሁለት ወንድማማች ሕዝቦች መካከል ደም ለማቃባት ሲባል በኤርትራ በሳሕል በረሃዎች የአሞራ ሲሳይ እንዲሆኑ አድርጓል። ሶስተኛ፣ በትግራይ ሕዝብ ስም የሀገራችን አንጡራ ሀብት በጠራራ ፀሐይ ለመዝረፍ ተጠቅመውበታል። ነገር ግን ከግማሽ በላይ የትግራይ ሕዝብ እስካሁን ድረስ ከውጭ የስንዴ እርዳታ ልመና አልወጣም። ወጣቱ ከዓረብ ሀገር ስደትና ውርደት አልዳነም። የሚበላው ይቅርና ሁሉም የትግራይ ከተሞች የሚጠጣ ንፁህ ውሃ እንኳን ማግኘት አልቻለም፤” በማለት አስረድተዋል።በዚህ መግለጫቸው እንዳስታወቁት፤ የትግራይ ሕዝብ የሚበላና የሚጠጣ ብቻ አይደለም ያጣው ሰላምም ጭምር የጠማው ሕዝብ ነው። ህወሓት ከተፈጠረ ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ በትግራይ ምድር ከሰባት ጊዜ በላይ ደማዊ ጦርነት ተደርጓል። አብዛኞቹ የጦርነቱ መንስኤ ደግሞ በማሌሊታዊና አብዮታዊ ዴሞክራሲ የደረቀ የህወሓት ጭንቅላት ያመጣው ጣጣ ነው። ከዚህ ሁሉ የተዛባና ጦረኛ ባህሪው የተነሳ የሚፈጠሩ ግጭቶች በአፈሙዝ ካልሆነ በስተቀር በዴሞክራሲ አግባብ በውይይት ለመፍታት ተፈጥሮው አይፈቅድለትም። ህወሓት ከፌዴራል መንግስት ጋር የነበረው ግጭትም በተመሳሳይ ትዕቢት፤ ንቀት፤ ድንቁርናና ጦረኛ አመለካከት የወለደው መሆኑንም ነው የገለጹት።አዲስ ዘመን ታህሳስ 15/2013
https://www.press.et/Ama/?p=37983
270
0ሀገር አቀፍ ዜና
ወደ ዳካር የሚያቀኑት ቦክሰኞች ተለይተዋል
ስፖርት
January 19, 2020
24
ለቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ ዝጅግት በቦክስ ስፖርት ኢትዮጵያን የሚወክሉ የቡጢ ተወዳዳሪዎችን ለመምረጥ ከወዲሁ ዝግጅት ተጀምሯል፡፡ ከትናንት በስቲያ በአዲስ አበባ ስታዲየም የዚሁ ዝግጅት አካል የሆነ ውድድርም ተካሂዷል፡፡ ከዚህ ውድድር የሚመረጡ ስፖርተኞችም ከየካቲት 9 እስከ 23 ቀን 2012 ዓ.ም ድረስ በሴኔጋል ዋና ከተማ ዳካር በሚካሄደው የአፍሪካ ቦክስ ቻምፒዮና ላይ በመሳተፍ ወደ ቶኪዮ ኦሊምፒክ የሚወስዳቸውን ውጤት ለማስመዝገብ የሚፋለሙ ይሆናል፡፡ የኢትዮጵያ ቦክስ ፌዴሬሽን ያዘጋጀው ይህ የብሔራዊ ቡድን ምርጫ የቦክስ ውድድር በአዲስአበባ ስታዲየም በደማቅ ሁኔታ ሲካሄድ በውድድሩ የአዲስ አበባ ፖሊስ የቦክስ ተወዳዳሪዎች በሁሉም ኪሎ ካታጎሪ የተዘጋጁትን ውድድሮች ማሸነፍ ችለዋል።በውድድሩ ከ52 እስከ 75 ኪሎ ግራም ስድስት ጨዋታዎች የተደረጉ ሲሆን፣ በ52 ኪሎ ግራም የአዲስ አበባ ፖሊሱ ዳዊት በቀለ ከፌዴራል ማረሚያ ቤቶች ቦክሰኛው ያዕቆብ በለጠ ጋር ተገናኝተው ዳዊት ማሸነፍ ችሏል፡፡ በ57 ኪሎ ግራም የድሬዳዋ ብቸኛ ተወካይ የሆነው አብዱልሰላም አቡበከር ከአዲስአበባ ፖሊሱ ፍቅረሰላም ያደሳ ጋር ተገናኝተው ብርቱ ፋክክር ቢያደርጉም ፍቅረሰላም ያደሳ አሸናፊ መሆን ችሏል።በ63 ኪሎ ግራም የአዲስ አበባ ፖሊስ ተወዳዳሪ አብርሃም ዓለም የፌዴራል ፖሊሱን ተጋጣሚ ሲያሸንፍ ፤ በተመሳሳይ በ69 ኪሎ ግራም የአዲስ አበባ ፖሊሱ መስፍን ብሩ የፌዴራል ፖሊሱን ቢኒያም ተስፋዬን አሸንፏል። በመጨረሻ በተካሄደው 75 ኪሎ ግራም ውድድር የአዲስ አበባ ፖሊሱ ተመስገን ምትኩ የፌዴራል ማረሚያ ቤቶች ተጫዋች ከሆነውን ባምላኩ ደጉ ጋ ተጋጥሞ በዳኛ ውሳኔ ማሸነፍ ችሏል።በሌላ በኩል በኢትዮጵያ እና ኤርትራ መካከል በተካሄደው የ63 ኪሎ ግራም የወዳጅነት ውድድር ኢትዮጵያዊው ካሳሁን ሀይሉ እና ቢኒያም ተስፋጋብር ተገናኝተው ካሳሁን ሀይሉ በጠባብ ውጤት አሸንፏል።በውድድሩ በርካታ የቦክስ አፍቃሪያን ተገኝተው የተከታተሉት ሲሆን የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሸን ኮሚሽነር ኤሊያስ ሽኩር ፣ የኢትዮጵያ ቦክስ ፌዴሬሽን አመራሮችና ሌሎች እንግዶች በውድድሩ ቦታ በመገኘት ጨዋታዎችን ተከታትለዋል፡፡ ለአሸናፊዎችም ኮሚሽነር ኤሊያስ ሽኩር እና ሌሎች እንግዶች የሜዳልያ ሽልማት አበርክተዋል።የውድድሩ ዋና ዓላማ በሴኔጋል ዋና ከተማ ዳካር ከየካቲት 9/2012 ዓ.ም ጀምሮ የ2020 ቶኪዮ ኦሊምፒክ ጨዋታ ለሚካሄደው የአፍሪካ ማጣሪያ ውድድር ኢትዮጵያን የሚወክሉ ስፖርተኞችን ለመምረጥ ነው። በዚህም መሠረት በውድድሩ አሸናፊ የሚሆኑ ቦክሰኞች በቀጥታ ወደ ዳካር እንደሚያቀኑ ይጠበቃል፡፡አዲስ ዘመን  ጥር 10/2012ቦጋለ አበበ
https://www.press.et/Ama/?p=25862
280
2ስፖርት
የለንደን ማራቶንን የተቀላቀሉ ኮከብ ኢትዮጵያውያን
ስፖርት
January 16, 2020
16
አትሌት ሞስነት ገረመውና ሙሌ ዋስይሁን በመጪው ሚያዝያ በሚካሄደው የለንደን ማራቶን ከዓለም ክብረወሰን ባለቤቱ አትሌት ኢሉድ ኪፕቾጌ ጋር ከሚፎካከሩ አትሌቶች መካከል እንደሚካተቱ አረጋግጠዋል። ሁለቱ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ባለፈው ዓመት የለንደን ማራቶን ውድድሩን አራት ጊዜ በተከታታይ ካሸነፈውና የቦታውን ክብረወሰን ከጨበጠው ኬንያዊ አትሌት ኪፕቾጌ ተከትለው በመግባት ሁለተኛና ሦስተኛ ሆነው ማጠናቀቃቸው ይታወሳል። ይህም ባለፈው ዓመት ከአንድ እስከ ሦስት በውድድሩ ማጠናቀቅ የቻሉ አትሌቶች ዘንድሮም የሚፎካከሩበት ዕድል እንዲፈጠር አድርጓል። አምና በውድድሩ አራተኛ፣ ካቻምና ደግሞ ሦስተኛ ሆኖ ማጠናቀቅ የቻለው ኢትዮጵያዊ አትሌት ሹራ ቂጣታ ቀደም ብሎ በዘንድሮው የለንደን ማራቶን እንደሚወዳደር ያረጋገጠ አትሌት ነው። ሞስነት ገረመው ባለፈው የለንደን ማራቶን ሁለተኛ ሆኖ ሲያጠናቅቅ 2፡02፡55 የሆነውን የዓለም አምስተኛ ፈጣን ሰዓት ማስመዝገብ የቻለ ሲሆን ክረምት ላይ ተካሂዶ በነበረው የዶሃው የዓለም ቻምፒዮና የብር ሜዳሊያ ማጥለቅ ችሏል። በተመሳሳይ ባለፈው ለንደን ማራቶን ሦስተኛ ሆኖ ሲያጠናቅቅ 2፡03፡16 ሰዓት ያስመዘገበው ሙሌ ዋስይሁን የዓለማችን አስራ አንደኛው ፈጣን ሰዓት ባለቤት ነው። እነዚህን ኮከብ አትሌቶች ጨምሮ ሌሎች በርካታ የርቀቱ ጠንካራ አትሌቶች በዘንድሮው ለንደን ማራቶን ተሳታፊ መሆናቸውን ተከትሎ ውድድሩ ከወዲሁ በጉጉት እየተጠበቀ ነው። ‹‹ያለፈው ዓመት ውድድር በተለይም በወንዶች የምንጊዜውም ምርጡ ነበር›› ያለው የኢሊት አትሌቶች ኃላፊ ስፔንሰር ባርደን የዘንድሮው የተሻለ እንደሚሆን ያለውን እምነት ገልጿል። በአምናው ውድድር ሞስነትና ሙሌ ኬንያዊውን ድንቅ አትሌት እስከ አርባ ኪሎ ሜትር ድረስ የፈተኑበት መንገድ ከዚህ ቀደም እንዳልገጠመው የተናገረው ባርደን ዘንድሮ እነዚህ አትሌቶች በተሻለ የራስ መተማመን ሊያሸንፉ የሚችሉበት ዕድል እንዳለ አብራርቷል። ከሦስት ወራት በፊት በቬና ማራቶን አርባ ሁለት ኪሎ ሜትርን ከ2፡00 ሰዓት በታች በማጠናቀቅ የመጀመሪያው የዓለማችን አትሌት የሆነው ኪፕቾጌ ዘንድሮ በለንደን ማራቶን ማሸነፍ ከቻለ አምስት ጊዜ ያሸነፈ ብቸኛው አትሌት በመሆን ተጨማሪ ታሪክ ያኖራል። በዘንድሮው ውድድር የ2017 የዓለም ቻምፒዮና የብር ሜዳሊያ አሸናፊው ታምራት ቶላን ጨምሮ ኬንያዊው ማሪየስ ኪፕሴሬምና ኖርዌያዊው ሶንድሬ ኖርድስታድ ተፎካካሪ መሆናቸው እንደተረጋገጠ አትሌቲክስ ዊክሊ አስነብቧል። በሴቶች መካከል በሚካሄደው ፉክክርም የዓለም ክብረወሰን ባለቤቷና ያለፈው ዓመት የለንደን ማራቶን አሸናፊዋ ኬንያዊት ብሪጊድ ኮስጌ ከትናንት በስቲያ ተሳታፊ መሆኗን ያረጋገጠች ሲሆን በቀጣይ ጊዜዎች ሌሎቹ ተሳታፊዎች ይፋ እንደሚደረጉ ይጠበቃል። አዲስ ዘመን ጥር 7/2012 ቦጋለ አበበ
https://www.press.et/Ama/?p=25696
290
2ስፖርት
የሠራተኞች የበጋ ወራት ውድድር እሁድ ይጀመራል
ስፖርት
December 26, 2019
19
 ህብረተሰቡ በሚኖርበት፣ በሚሰራበትና በሚማርበት አካባቢ ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎችን በማዘውተር ጤናማ እንዲሆን የስፖርት ፖሊሲው ይደነግጋል። ሰራተኛው ማህበረሰብ በብዙ ተቋማት በሚሰራበት አካባቢ ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች ላይ በስፋት ሲሳተፍ ባይስተዋልም ዓመታዊ የሰራተኞች ስፖርት ውድድሮች ላይ ሲሳተፍ ይታያል። ይህም የኢትዮጵያ ሰራተኛ ማህበራት ኮንፌዴሬሽን(ኢሠማኮ)በዓመት የተለያዩ መርሃ ግብሮች የሚያከናውናቸው የስፖርት መድረኮች ናቸው። ከነዚህ የኢሠማኮ የስፖርት መድረኮች ትልቅ ትኩረት የሚሰጠውም ዓመታዊው የሰራተኞች የበጋ ወራት የስፖርት ውድድር በጉልህ ተጠቃሽ ሲሆን ከታኅሣሥ ወር አንስቶ እስከ ግንቦት መጨረሻ የሚዘልቅ ነው፡፡ የሰራተኞች የበጋ ወራት የስፖርት ውድድር በአገራችን ስፖርት ታሪክ መካሄድ ከጀመረ ረጅም ዓመታትን ያስቆጠረና አንጋፋ ከመሆኑ ባሻገር አገርን ወክለው የመካከለኛና ምስራቅ አፍሪካ(ሴካፋ) ዋንጫን ጨምሮ በሌሎች ዓለም አቀፍ መድረኮች መሳተፍ የቻሉ ስፖርተኞችን ያፈራ ስለመሆኑ ይነገራል።ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በስፋት የተለያዩ ማህበራትን እያሳተፈ የሚገኘው ይህ ውድድር የመገናኛ ብዙሃን ትኩረትን ከመሳብ ባሻገር በአገራችን ከሚከናወኑ ታላላቅ የስፖርት መድረኮች አንዱ እየሆነ ይገኛል፡፡ በዚህም አዳዲስ ተሳታፊ ማህበራትን ወደ ውድድር ከመሳብ በዘለለ ቀድሞ ዝነኛ ተፎካካሪ የነበሩና ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ከውድድሩ የራቁ ማህበራትን ወደ ውድድር እየመለሰ ይገኛል።የፊታችን እሁድ በአዲስ አበባ ስቴድየም በሚጀመረው የበጋ ወራት ውድድርም አርባ አዳዲስና ነባር የሰራተኛ የስፖርት ማህበራት ተሳታፊ ለመሆን ዝግጅታቸውን እንደጨረሱ የኢሠማኮ የስፖርት ክፍል ኃላፊ አቶ ዮሴፍ ካሳ ለዝግጅት ክፍላችን ተናግረዋል፡፡ በሁለት ዲቪዚዮን ተከፍሎ በሚካሄደው የእግር ኳስ ውድድር ከሰላሳ ማህበራት የተውጣጡ 750 ተወዳዳሪዎች የሚሳተፉ ይሆናል፡፡ በሴቶች ቮሊቦል ውድድር ከአስራ አምስት ማህበራት 253 ተወዳዳሪዎች ሲሳተፉ በወንዶች ከአስር ማህበራት 150 ተወዳዳሪዎች ተሳታፊ ይሆናሉ፡፡ በሴቶች ቼስ ውድድር ከአምስት ማህበራት 25፣ በወንዶች ከአስር ማህበራት 50 ተወዳዳሪዎች ይሳተፋሉ፡፡ በጠረጴዛ ቴኒስ ወንዶች ከአስር ማህበራት 50 ተሳታፊዎች፣ በሴቶች ደግሞ ከዘጠኝ ማህበራት 45 ተሳታፊዎች ይወዳደራሉ፡፡ በወንዶች ዳርት ውድድር ከአስራ ሁለት ማህበራት 60 ተሳታፊዎች፣ በሴቶች ከስምንት ማህበራት 40 ተሳታፊዎች ይፎካከራሉ፡፡ በከረንቦላ ውድድር ከአስራ ሁለት ማህበራት የተውጣጡ 60 ተወዳዳሪዎች፣ በገበጣ ውድድር ከአስር ማህበራት 50 ተወዳዳሪዎች ተሳታፊ ይሆናሉ፡፡ በአትሌቲክስ ወንዶች ከስምንት ማህበራት 144 ተወዳዳሪዎች፣ በሴቶች ከሰባት ማህበራት 126 ተወዳዳሪዎች ተፎካካሪ ይሆናሉ፡፡ አዝናኝ በሆነው የገመድ ጉተታ ውድድር በወንዶች ከአምስት ማህበራት 75 ተፎካካሪዎችና በሴቶች ከሦስት ማህበራት 45 ተወዳዳሪዎች ተካፋይ ይሆናሉ፡፡ በአጠቃላይ በውድድሩ 1945 የሰራተኛ ስፖርት ማህበራት ተወዳዳሪዎች ተካፋይ ሲሆኑ 605 ያህሉ ሴቶች መሆናቸውን አቶ ዮሴፍ ገልፀዋል፡፡ ውድድሩ እሁድ ሲጀመርም ጠንካራ ፉክክር በሚደረግበት እግር ኳስ የኢትዮጵያ መድን ድርጅት ከኢስት አፍሪካን ቦትሊንግ ሼር ካምፓኒ(ኮካ ኮላ) ጋር የመክፈቻ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡ የሴቶች አራት መቶ ሜትርና የወንዶች አንድ ሺ አምስት መቶ ሜትር የአትሌቲክ ውድድሮችም በውድድሩ መክፈቻ እለት ይከናወናሉ።የገመድ ጉተታና እን ቁላል በማንኪያ ይዞ የመሮጥ አዝናኝ ውድድሮችም በመክፈቻ መርሃ ግብሩ ተካተዋል፡፡  አዲስ ዘመን ታኀሣሥ 16 / 2012   ቦጋለ አበበ
https://www.press.et/Ama/?p=24726
362
2ስፖርት
ከአገሩ በላይ ጃፓን ያከበረችው ኢትዮጵያዊ ጀግና
ስፖርት
December 29, 2019
97
1928 ፋሺስት ጣሊያን በአምባገነኑ ቤኒቶ ሞሶሎኒ እየተመራ ኢትዮጵያን ወረረ። ምስጋና ለማይዘነጉት ጀግኖቹ አርበኞቻችን ይግባና ሞሶሎኒና ግብረአበሮቹ ብዙም ሳይደላደሉ ከአገር ቤት በቅሌት ተባረሩ። ከሃያ አራት ዓመታት በኋላ ታላቁ አበበ ቢቂላ የወራሪዎቹን መዲና ሮምን በባዶ እግሩ ወሮ ዓለምን ጉድ አሰኘ፤ የምን ጊዜም የማራቶን ንጉሱ የአፍሪካውያን ኩራትና የነፃነት ተምሳሌት እንዲሁም፤ የመጀመሪያው ጥቁር የማራቶን ኦሎምፒክ የወርቅ ሜዳሊያ አሸናፊ በጥቁሮቹ በጀግኖቹ መታሰቢያ ወር የካቲት የጥቁር ህዝቦች ኩራት ሆኖ ከሃምሳ አምስት ዓመት በፊት በኢትዮጵያውያን አዲስ ዓመት ዋዜማ በሮም ኦሎምፒክ የፈፀመው ታሪካዊ ጀብድ በመላው ዓለም ያሉ ጥቁር አትሌቶችን በእጅጉ ያኮራና ያነሳሳ ነበር። ጷግሜ 5 ቀን 1952 አስራ ሰባተኛው የሮም ኦሎምፒያድ በታላቋ ሮም ጎዳናዎች አንድ ተዓምር ታየ፤ በርካቶች አይናቸውን ለማመን ተቸገሩ፤ በአንባገነኑ ሞሶሎኒ አገር በበርካታ ነጮች መሃል አንድ ጥቁር በባዶ እግሩ ታየ። የጥቁር ህዝቦች ተዓምርን ለመቀበል የሚተናነቃቸው ዘረኝነትን በደማቸው ያሰረፁ ነጮች እንዴት ይህ ሊሆን እንደቻለ ግራ ተጋቡ። አፍሪካውያንን ያኮራ ኢትዮጵያውያንን ከልብ ያስፈነጠዘ ታሪካዊ ድል። የአራት ዓመት ታዳጊ ሆኖ እናት አገሩ ኢትዮጵያ በጣሊያን ፋሺስት ስትወረር መጥፎውን ጊዜ ገና ባልጎለበተ የህፃን አዕምሮው የሚያስታውሰው አበበ ቢቂላ ሃያ ስድስት ዓመታት ጠብቆ ታላቁን የሮም ጎዳና በባዶ እግሩ ወሮ የማይደገመውን ታሪክ ሰራ። ከአራት ዓመት በኋላም 1956 በድጋሜ ጫማ አጥልቆ በቶኪዮ ኦሎምፒክ ክብረወሰን በማሻሻል ጭምር አሸንፎ ጥቁሮች በማይደፈረው ርቀት አሁን ላይ ቁንጮ እንዲሆኑ መሰረቱን አኖረ። እሱ በከፈተው በርም ቁጥር ስፍር የሌላቸው የማራቶን አትሌቶች ለዘመናት ርቀቱን የግላቸው አድርገው አሁን ድረስ ዘልቀዋል። የሻምበል አበበ ቢቂላ የህይወት ጉዞን የተመለከተ «ቤር ፉት ረነር» የተሰኘ መጽሐፍ ለንባብ ያበቁት እንግሊዛዊው ፓል ራምባኒ«ድንቅ ድል ነበር። በጥቁር አፍሪካዊ የተገኘ የመጀመሪያው የወርቅ ድል! በእርግጥ በዚያን ወቅት ሌሎች ጥቁር አፍሪካውያን ሯጮችም ነበሩ። ግን የሚሮጡት ቅኝ ለገዟቸው የአውሮፓ ሀገራት ነበር። የአበበ ድል ታላቅ የሆነው ለዚያም ጭምር ነው። አዎን! አበበ ለዓለም አዲስ ነገር አሳየ። የአፍሪካ ህዝብ በእኩል መወዳደርና ማሸነፍ እንደሚችል አረጋገጠ›› ሲሉ የአበበ ድል ከስፖርትም የተሻገረ መሆኑን መስክረዋል። በታሪክ ላይ ሌላ የታሪክ ካባ ጥቅምት 11 ቀን 1957 ዓ.ም. ነበር። በጃፓን ዋና ከተማ በተሰናዳው ቶኪዮ ኦሎምፒክ ሮም ላይ በባዶ እግሩ በመሮጥ የወርቅ ሜዳሊያ ያጠለቀው አበበ ተገኝቷል። አበበ ከአራት ዓመት በፊት የአሸናፊነት ግምት ሳይሰጠው ባለድል ቢሆንም፤ በቶኪዮ ዳግም ታሪክ ስለመስራቱ ብዙዎች ጥርጣሬ አድሮባቸዋል።«ማሸነፍ ቀርቶ ውድድሩን መጨረሱ ትንግርት ነው»ሲሉ መላምት የሰጡም አልታጡም። የሮሙ ጀግና አበበ የትርፍ አንጀት ቀዶ ሕክምና ማድረጉና ሳያገግምም ከውድድር ሥፍራ መድረሱ ነበር ለዚህ ድምዳሜ እንዲበቁ ያደረጋቸው። በውድድሩ ተሳታፊ የሆኑት 15 አትሌቶች የኦሎምፒኩን የወርቅ ሜዳሊያ ለማግኘት እንዲቋምጡ አድርጓቸዋል። የሮሙን የባዶ እግር ታሪክ ቀይሮ ካልሲ አጥልቆ፣ ጫማውን ተጫምቶ በመጣው አበበ ፊት ላይ የሚነበብ የነበረው ገጽታ አስገራሚ ነበር። ከኦሎምፒኩ መዳረሻ 6 ሳምንታት ሲቀሩት የቀዶ ህክምና ማድረጉን ረስቶ ለሌላ ድል ራሱን ሲያሰናዳ ነበር የሚታየው። በዚህ መልኩ ውድድሩ የጀመረው አበበ እስከ መጀመሪያዎቹ 10 ኪሎ ሜትር የአውስትራሊያው ሮን ክለርክ ቢፎካከረውም ጥሎት በመሔድ ያለአንዳች ተቀናቃኝ በ2 ሰዓት 12 ደቂቃ 11.2 ሰኮንድ በድል አድራጊነት ፈጸመ። ከእርሱ በፊት ማንም ያልፈጸመውን፣ ከርሱም በኋላ ማንም ያላደረገውን የኦሎምፒክ ማራቶን ሁለት ጊዜ አከታትሎ የመውሰድ ታሪክ ሰራ። በጃፓናውያን ልብ ያበበው አበበበቶኪዮ ኦሎምፒክ የሜዳሊያ ሽልማት ሥነ ሥርዓት ላይ አንድ ትልቅ ክስተት ተፈጠረ። ክስተቱ ለኢትዮጵያውያን የሚያስቆጭ ቢመስልም ፤ በጃፓናዊያን ልብ ውስጥ አበበ ቢቂላ እድሜ ልክ እንዲታተም ያደረገ ነበር። የኢትዮጵያ ሕዝብ መዝሙር የጃፓን ባለሥልጣኖችም ሆኑ የሙዚቃ ባንዱ አያውቁትም ነበር። የመድረኩ አዘጋጆች ጃፓናውያን አንድ ነገር ዘየዱ። የማርሽ ባንዱ አጋጣሚውን ተጠቀመ። የጃፓንን ሕዝብ መዝሙር ለኢትዮጵያ ድል ማብሰሪያ አደረገው። ሕዝቡም ፈነደቀ። 17 ቁጥር መለያን ያጠለቀው አበበም በጃፓን ሕዝብ ልቦና ውስጥ ታተመ። ጃፓናውያን ለአበበ ክብር በቀዬያቸው ሐውልት አቁመውለታል። ጃፓናውያን ለአበበ ቢቂላ ያላቸው ጥልቅ ከበሬታን በ2006 ዓ.ም ኢትዮጵያ የመጡት የጃፓኑ ጠቅላይ ሚኒስትር ሺንዞ አቤ በ1957 ዓ.ም. በተካሄደው የቶኪዮ ኦሎምፒክ በማራቶን ድል ያደረገውን አበበ ቢቂላ ለማክበር ከልጁ ከየትናየት አበበ ቢቂላ ጋር በሸራተን በመገኘት ይሄንኑ ነበር ያረጋገጡት። ጠቅላይ ሚኒስትር አቤ የቶኪዮውን ሩጫ በልጅነታቸው እንደተመለከቱትና የአበበ ቢቂላ ተወዳዳሪዎቹን በርቀት ጥሎ ማሸነፉ ትንግርት መሆኑንም መስክረዋል።በኢትዮጵያ ስፖርት ትልቅ ስፍራ ያላቸው ክቡር አቶ ይድነቃቸው ተሰማ በአንድ ወቅት በጃፓናውያን ዘንድ ትልቅ ቦታ ስላለው አበበ ቢቂላ የተናገሩትን እንጥቀስ። ‹‹…አበበ በድጋሚ በማሸነፉ በጃፓን ሕዝብ ለዘለዓለም የማይረሳ ትዝታ ትቷል። ዛሬም በጃፓን እንደጣዖት ይመለከቱታል። ማራቶን በጃፓን ውስጥ እንዲህ ተወዳጅ ሊሆን የቻለው ከአበበ ቢቂላ ድል በኋላ ነው። አሁንም ይኸው መንፈስ ቀጥሏል።››ብለው ነበር። በቶኪዮ ኦሎምፒክ በአጋጣሚ የተፈጠረችውን ታሪካዊ ክስተትን ዛሬ ያልረሱት ጃፓናውያን ከሁለት ሳምንት በፊት ጀግናውን ዘክረውታል። ጃፓናውያን የፍቅራቸው ገጸበረከት ሳይቀንስ ለሻምበል አበበ ቢቂላ መታሰቢያ ውድድር በጃፓን ካሳባ አድርገውለታል። በዚህ ውድድር ላይ በሁለቱም ፆታ ሃገራችንን የወከሉት አብዮት አብነትና እታለማሁ ስንታየሁ ሲያሸንፉ ውድድሩን የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ኮሎኔል ደራርቱ ቱሉ እና የፌዴሬሽኑ የጽፈት ቤት ኃላፊ አቶ ቢልልኝ መቆያ እንዲሁም የሻምበል አበበ ቢቂላ ልጅ የትናየት አበበ ከስፍራው ተገኝተው ታድመዋል። በመድረኩ እንደተገለጸውም አበበ ቢቂላን የመዘከር ተግባሩ ከትውልድ የሚሻገር መሆኑን ጃፓናውያኑ አረጋግጠዋል።ነብይ በሀገሩ ይከበርበኢትዮጵያውያን ዘንድ አንዲት የምትታወቅ አባባል አለች «ነብይ በሀገሩ አይከበርም»።ሀገራችን በተለያዩ ጊዜያት የተፈጠሩና በተሰማሩበት መስክ ሀገራቸውን ለዓለም ያስተዋወቁ ዓለም አቀፍ ጀግኖች ባለቤት መሆኗ እሙን ነው። ለአብነት ከሚጠቀሱት መካከል ደግሞ አበበ ቢቂላ ቀዳሚ ነው። ጀግናው አበበ ቢቂላ በተለይ ከሮም እስከ ቶኪዮ በሰራቸው አንፀባራቂ ታሪኮች ኢትዮጵያን በዓለም ህዝብ ዘንድ አስተዋውቋል። አበበ እስከ ህልፈት ህይወቱ ድረስ ሀገሩን ሲያገለግል የኖረ የትውልድ አርዓያ የሆነ ጀግና ነው። የአበበ የታሪክ ተወዳሽነት በኢትዮጵያም ብቻ ሳይሆን በዓለም ሀገራት ሳይቀር ክብርና አድናቆት የተቸረው መሆኑ ክብሩን የበለጠ ያጎላዋል። የአበበ ቢቂላን ጀግንነት በማድነቅና በማክበርም በተለየ መልኩ ጃፓናውያን ይዘክሩታል። እንደ ጃፓናውያኑ ሁሉ ጣሊያንም ለአበበ ክብሩን አልነፈገችም። የሮም ኦሎምፒክ 50ኛ ዓመትን ስትዘክር አንድ ድልድይ በስሙ ሰይማለች። ሰሜን አፍሪካዊቷ አገር ሞሮኮም በስሙ ስቴድየም አኑራለታለች። በአሜሪካን አገር በየዓመቱ የሚካሄድ ዓለም አቀፍ ሽልማትም አበበን ለማስታወስ በስሙ ተሰይሞ ይገኛል።‹‹የአፍሪካ ማራቶን አባት›› ተብሎም በዶክመንተሪው ፊልም ላይ ታሪኩ ሰፍሯል። ታላቁን ሽልማትም ልጁ የትናየት አበበ ቢቂላ ተረክቧል። በኢትዮጵያ አበበ ቢቂላን በቋሚነት የሚዘክሩ አዲስ አበባና አዳማ ከተማ የሚገኙ ስታዲየሞች በስሙ ይጠራሉ። በቅርቡ በተመረቀው አንድነት ፓርክ ውስጥ ከቆመው መታሰቢያ በቀር ለአበበ በእናት ሀገሩ የቆመለት ታሪኩን የሚመጥን መታሰቢያ ሃውልት አይገኝም። ዓለም በተለይም ጃፓናውያን ያከበሩትን ያህል ግን ኢትዮጵያ አበበን አላከበረችውም። ወይም ስሙንና ታሪኩን የሚመጥን በብዛትም በጥራትም መታሰቢያ አላበጀችለትም። አዲስ ዘመን ታኅሣሥ 19/2012 ዳንኤል ዘነበ
https://www.press.et/Ama/?p=24870
865
2ስፖርት
ለብሄራዊ ስታዲየም የሁለተኛ ዙር ግንባታ ዝግጅት እየተደረገ ነው
ስፖርት
January 1, 2020
23
በአደይ አበባ ቅርፅ እየተገነባ የሚገኘው ዘመናዊው ብሄራዊ ስታዲየም ሁለተኛ ዙር ግንባታ በቅርቡ የሚጀመር መሆኑን የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን አስታወቀ።መንግስት ለግንባታው ከፍተኛ ትኩረት የሰጠ በመሆኑ ግንባታው በተያዘለት ጊዜ እንዲጠናቀቅ ጥረት እንደሚደረግም ተገልጿል። በታህሳስ ወር 2008 ዓ.ም የተጀመረው የብሄራዊ ስታዲየም ግንባታ ወደ ሁለተኛው ምዕራፍ ለመሸጋገር በዝግጅት ላይ ይገኛል።በአዲስ አበባ ከተማ በሁለት ዙር የሚገነባው ስታዲየሙ የመጀመሪያ ዙር ግንባታ 99 በመቶ መድረሱን ኮሚሽኑ ትናንት ለመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች ባዘጋጀው የጉብኝት መርሃ ግብር ወቅት አስታውቋል።ቀሪው አንድ መቶኛ የሜዳ ግንባታና የመም ማንጠፍ ስራዎች፤ በመጀመሪያው ውል በስታዲየሙ ግንባታ ማጠቃለያ ላይ የሚገነቡ ይሆናል።የሁለተኛው ምዕራፍ ስራ የጨረታ ሂደት የተጠናቀቀ ሲሆን፤ ቴክኒካዊ ጉዳዮች በአማካሪው ድርጅት በመገምገም ላይ ይገኛል።በመሆኑም በቅርቡ ተጠናቆ የስምምነት ፊርማ ስነ ስርዓት ሲካሄድ የተቋራጩ ማንነት እንዲሁም የገንዘብ መጠን ለህዝብ ይፋ ይሆናል። ከፍተኛ ወጪ በሚጠይቀው በዚህ ፕሮጀክት መንግስት ከፍተኛ ትኩረት የሰጠ ሲሆን፤ አስፈላጊውን ሁሉ በማሟላት በተቀመጠው ጊዜ እንዲጠናቀቅ ጥረት እያደረገ መሆኑም ተገልጿል።የመጀመሪያው ምዕራፍ ግንባታ የተቀመጠለት የጊዜ ገደብ 900 ቀናት ቢሆንም ከውጪ በሚገቡ ቁሳቁስ ምክንያት ጥቂት መዘግየት አጋጥሟል።ይህ ግንባታም ከሁለት ዓመት ተኩል እስከ ሶስት ዓመት የሚፈጅ ሲሆን፤ በምንዛሬ ችግር በተለያዩ ክልሎች እንደሚስተዋለው መዘግየት እንዳያጋጥም መንግስት ከፍተኛ ትኩረት የሰጠ መሆኑን የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽነር ኤሊያስ ሽኩር ገልጸዋል። በጉብኝቱ ተገኝተው መግለጫ የሰጡት ኮሚሽነሩ፤ በመንግስት በኩል ፕሮጀክቱ ተጀምሮ እስኪያልቅ ድረስ ልዩ ትኩረት መስጠቱን አረጋግጠዋል።የመጀመሪያው ዙር ግንባታ በአጠቃላይ 2 ነጥብ 47 ቢሊየን ብር ወጪ ተደርጓል።ለሁለተኛው ዙር ግንባታ ከዚህ በላይ የሚያስፈልግ ሲሆን፤ መንግስት ለዚህ ዓመት ብቻ 2 ነጥብ 4 ቢሊየን ብር መድቧል። ሁለተኛው ዙር ግንባታ በስታዲየሙ፤ የዙሪያ ጣራ ማልበስ፣ የደህንነትና የድምጽ ሲስተሞችን መዘርጋት፣ የወንበርና ስክሪኖች ገጠማ እንዲሁም የተለያዩ ክፍሎች፣ ቢሮዎችና የመገናኛ ብዙሃን መገልገያ ክፍሎች ስራን ያጠቃልላል። ከስታዲየሙ ውጪም፤ ቢሮዎች፣ የዕቃ ማከማቻ ክፍሎች፣ የመኪና ማቆሚያና ሄሊኮፕተር ማረፊያ ስፍራዎች፣ ቲያትር ቤት፣ የባድሜንተን እና ሶስት በአንድ መጫወቻ ሜዳዎች፣ ሁለት የመለማመጃ ሜዳዎችን እንዲሁም በስታዲየሙ አጠገብ የሚያልፈውን ወንዝ አልምቶ ለመዝናኛ ማዋልን የያዘ ሰፊ ስራ ነው። አዲስ ዘመን ታኅሣሥ 22/2012 ብርሃን ፈይሳ
https://www.press.et/Ama/?p=25006
278
2ስፖርት
“የጉዳዮችመዘግየትና ተደጋጋሚ ቀጠሮዎች የፍትህ ተቋማቱ ያልተሻገሯቸው ችግሮች ናቸው”አቶ ፉአድ ኪያር የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት
ሀገር አቀፍ ዜና
December 22, 2020
8
እፀገነት አክሊሉአዲስ አበባ፦ የጉዳዮች መዘግየትና ተደጋጋሚ ቀጠሮ የፍትህ ተቋማት ያልተሻገሩትና እስከ አሁንም ድረስ አብሯቸው የቀጠለ ችግር መሆኑን የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ተናገሩ፡፡ፕሬዚዳንቱ አቶ ፉአድ ኪያር ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ እንደገለጹት፤ ቀልጣፋ የፍትህ አሰጣጥ፣ የጊዜ ቀጠሮ ማሳጠርና ሌሎች የፍትህ ሂደቶች ከለውጡ በፊትም ሆነ በኋላ የፍትህ ተቋማት በፍትህ ስርዓቱ ላይ መሻገር ካልቻሏቸው ነገሮች መካከል ይጠቀሳሉ።ለዚህ ችግር መሰረታዊ መፍትሔ ማምጣትና መሻገር የሚቻለው ደግሞ፣ አንድ ጉዳይ መቼ ተጀምሮ በምን ያህል ጊዜ ማጣራትና ክርክር ከተደረገበት በኋላ መጠናቀቅ አለበት በሚለው ላይ ቀመር አውጥቶ ከዳኞች በመግባባት ምክንያታዊ ጊዜ ሰጥቶ እንዲያልቁ ማድረግ ሲቻል ነው፡፡እንደ አቶ ፉአድ ገለጻ፤ የወንጀል ጉዳዮች ፍርድ ቤት ላይ ተጀምረው እዛው የሚያልቁ አይደሉም።ይልቁንም የሌሎች የወንጀል ፍትህ አስተዳደር አካላትን ቅንጅታዊ አሰራር ስለሚፈልጉ ናቸው።አንድ የወንጀል ተጠርጣሪ በቁጥጥር ስር ሲውልም ከፖሊስ ጀምሮ አቃቤ ህግ፣ ፍርድ ቤት በመጨረሻም ማረሚያ ቤት በሂደቱ ላይ የነቃ ተሳትፎ የሚያደርጉበት ነው።ለምሳሌ፣ ተከሳሹን በማቅረብ ጥራቱን የጠበቀ ምርመራ በመስራት ክሱን ጥርት አድርጎ በማቅረብና በፍርድ አሰጣጥ በኩል ከፍተኛ የሆነ የቅንጅት ስራ ያስፈልጋል፡፡ይሁን እንጂ በወንጀል የተጠረጠሩ ሰዎች ላይ የሚሰጠው የጊዜ ቀጠሮ መራዘም በፍርድ ቤት የስራመጓተት ብቻ ሳይሆን ፖሊስ በቶሎ ምርመራውን ያለመጨረስ߹ አቃቤ ህግ ጉዳዩን በቶሎ ወደፍርድ ቤት ያለማምጣት߹ ፍርድ ቤት ከመጣ በኋላ ደግሞ ጉዳዮች በቶሎ እልባት የሚያገኙበት የተቀመጠ የጊዜ ገደብ አለመኖር߹ መዝገብ ምስክር ማስረጃና ሌሎች ነገሮችም አልቀረቡም በማለት በተደጋጋሚ በሚሰጥ ቀጠሮ ምክንያት መዘግየቶችና ተደጋጋሚ ቀጠሮዎች እንደሚያጋጥሙ ነው አቶ ፉአድ የገለጹት፡፡በዚህ ረገድ የፍርድ ቤትን ድርሻ ወስደን የዘገዩ መዝገቦች ቅድሚያ አግኝተው እንዲሰሩ አልተመረመረም የሚባል መዝገብ እንዳይኖር ለማድረግ አብዛኞቹ ዳኞች ረዳቶች እንዲኖሯቸው ተደርጓል ያሉት አቶ ፉአድ፤በዚህም ለውጦች እየመጡ በመሆኑ ይህ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አስረድተዋል፡፡በሌላ በኩል ደግሞ የባለጉዳይ መስተንግዶ በሁሉም የህብረተሰብ ክፍል ዘንድ እንደ ችግር የሚነሳ መሆኑን የጠቆሙት አቶ ፉአድ፤ እንዴት ነው ባለጉዳይ የምናስተናግደው? የሚለው ከሰራተኛው ጀምሮ እስከ ዳኛ ድረስ የሚሄድና መስተካከል ያለበት እንደሆነም ገልጸዋል።በዚህ በኩል ያሉ ችግሮችንም ለይቶ በጥራት በቅልጥፍናና በውጤታማነት ለመስራት የተለያዩ ሙከራዎች መኖራቸውን አብራርተዋል፡፡እንደ አቶ ፉአድ ገለጻ፤ እንደመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የመዝገቦች መዘግየትን ለማጥፋት እድሜያቸው አንድ ዓመትና ከዛ በላይ ያስቆጠሩ መዝገቦች ላይ ልክ እንደ መኪና ታርጋ “የዘገየ” የሚል በመለጠፍ ዳኞች ከምንም ጉዳይ በፊት ቅድሚያ ሰጥተው እንዲያዩና እልባት እንዲሰጡ በማድረግ ባለፈው ዓመት ብቻ ከ 6ሺ 800 በላይ የሚሆኑ የተከማቹ መዝገቦችን እልባት መስጠት ተችሏል። በዚህም አንድ አመትና ከዛ በላይ የቆዩ መዝገቦች ተቃለዋል።ይህም ሆኖ ግን በየቀኑ የሚከፈቱ መዝገቦች ስላሉ ችግሩ ይቃለል እንጂ የመዝገቦቹ ብዛት እንዳለ ነው፡፡በመሆኑም ፍርድ ቤቱ ያሉበትን ችግሮች ለመቅረፍ “የኬዝ ፍሎው ማኔጅመንት” አሰራርን ለመከተል ያቀደ መሆኑን በመጥቀስ፤ ለምሳሌ፣ አንድ በስርቆት ወንጀል የተጠረጠረን ግለሰብ ክስ ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምሮ በአራት ወር ውስጥ ጉዳዩ እልባት እንዲያገኝ ለማድረግ እና ከዚህ ጊዜ በላይ የሚጠይቁ ወንጀሎችን ደግሞ ታሳቢ በማድረግ ስራዎች እንደሚሰሩም ፕሬዚዳንቱ ጠቁመዋል፡፡አዲስ ዘመን ታህሳስ 13/2013
https://www.press.et/Ama/?p=37863
394
0ሀገር አቀፍ ዜና
ሁለተኛው የካፕ ኦፍ ኤክሰለንሲ የምርጥ ቡና ቅምሻ ውድድር ይፋ ሆነ
ሀገር አቀፍ ዜና
December 22, 2020
10
ሰላማዊት ውቤአዲስ አበባ፡- ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ ቡና ላኪዎችን ብቻ ሳይሆን አምራቾችን በስፋት ለማሳተፍ ያለመው ሁለተኛው የካፕ ኦፍ ኤክሰለንሲ የምርጥ ቡና ቅምሻ ውድድር ይፋ ሆነ።ይሄን አስመልክቶም የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አዱኛ ደበሌ፣ የኢትዮጵያ ቡና ላኪዎች ማህበር የሥራ አመራር ቦርድ ፕሬዚዳንት አቶ ደሳለኝ ጀና እና የውድድሩ አስተባባሪ ወይዘሪት ቅድስት ሙሉጌታ ትናንት በሄልተን ሆቴል በጋራ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡ኃላፊዎቹ በሰጡት የጋራ መግለጫ እንዳስታወቁት፤ ከፍተኛ ጥንቃቄ የተሞላበት ዓመታዊው ሁለተኛው የካፕ ኦፍ ኤክሰለንሲ የምርጥ ቡና ቅምሻ ውድድር ከትናንት ጀምሮ ይፋ ሆኗል። በውድድሩ ናሙና ከአንድ የቡና ማሳ ይቀርባል። ከአንድ የቡና ማሳ በላይ በስሙ የተመዘገበ ማሳ ያለው አርሶ አደር ቢበዛ ሁለት ዓይነት ናሙና ማቅረብ ይችላል።ቡና ላኪዎችም የቡና ባለቤት አርሶ አደሮችን በመወከል ከአንድ በላይ ናሙና ማቅረብ የሚችሉ ሲሆን፤ ነገር ግን የቡናውን ባለቤት አርሶ አደር ዝርዝር አድራሻ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል። የቡና ማህበራት የቡና ማጠቢያ ጣቢያዎች ከአንድ በላይ ናሙና ማቅረብ ይችላሉ። የመጀመሪያው የኢትዮጵያ ቡና ቅምሻ ውድድር በ2012 ዓ.ም የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣንና በአሜሪካ ተራድኦ ድርጅት በሚደገፈው “ፊውቸር ኢትዮጵያ ቫልዩ ቻይን አክቲቪቲ” ጋር በመተባበር መካሄዱን ያስታወሱት የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አዱኛ ደበሌ፤ ለውድድር የሚቀርበው የናሙና ቡና መጠን ሦስት ኪሎ ግራም እንደሆነም ተናግረዋል።የኢትዮጵያ ቡና ላኪዎች ማህበር የሥራ አመራር ቦርድ ፕሬዚዳንት አቶ ደሳለኝ ጀና በበኩላቸው እንደገለፁት፤የውድድሩ ሂደት ከፍተኛ ጥንቃቄ በተሞላበት ሁኔታ በሦስት ደረጃዎች የሚያልፍ ሲሆን፤ በብሄራዊ ባለሙያ ዳኞች፣ በዓለም አቀፍ የታወቁ የቡና ላቦራቶሪዎች ተገምግሞ ማለፍ የሚጠበቅበት መሆኑን አብራርተዋል።የዚህ ውድድር ያለፈው ዓመት የኢትዮጵያ አሸናፊ እ.ኤ.አ ጁላይ 24 ቀን 2020 በተካሄደ ጨረታ አንድ ኪሎ ግራም ቡና በ407 የአሜሪካ ዶላር መሸጡን የተናገሩት የውድድሩ አስተባባሪ ወይዘሪት ቅድስት ሙሉጌታ፤ ሂደቱ ይፋ የሆነበት መድረክ የጅማሮ ብስራት መሆኑንና በቀጣይ በተለያየ ጊዜ የሚደረጉ የተለያዩ እንቅስቃሴዎች መኖራቸውን ገልፀዋል። የኢትዮጵያ ቡና ላኪዎች ማህበር ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ግዛት ወርቁ በበኩላቸው፤ ውድድሩ እ.ኤ.አ በ1999 ብራዚል የተጀመረ መሆኑን እና ውድድሩ ለዓለም ገበያ የሚፈለገው ምርጥ ቡና ተወዳድሮ የሚወጣበት ዘዴ እንደሆነ ተናግረዋል። ዘዴው በተሻለ ዋጋ እንዲሸጥ ምቹ ሁኔታ ስለሚፈጥር የተሻለ ቡና እንዲመረት የሚያበረታታ የማስታወቂያ ዘዴ ስለመሆኑም ጠቁመዋል፡፡ ባለፈው ዓመት ውድድር 1ነጥብ 3 ሚሊዮን ዶላር ማስገኘቱንና በዘንድሮው ዓመትም ከዚህ የበለጠ ይገኝበታል ተብሎ መታሰቡን ተናግረዋል።በመግለጫው ላይ የተገኙት የቡና ላኪዎች ማህበር የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ጌታቸው አድማሱ በበኩላቸው እንደገለጹት፤ ለሁለተኛ ጊዜ የሚዘጋጀው የቡና ቅምሻ ውድድር ኢትዮጵያ በዓለም ቡና ገበያ ተገቢውን ዋጋ እንድታገኝ አመቺ ሁኔታዎችን ይፈጥራል። ውድድሩ ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ ቡና ላኪዎችን ብቻ ሳይሆን አምራቾችን በስፋት የሚያሳትፍና የሀገሪቱን የውጪ ምንዛሪ የሚያሳድግ ነው። በቡና የውጪ ንግድ ከተሰማሩት ከ90 በመቶ በላይ የሚሆኑት በማህበሩ የታቀፉ ሲሆን፤ በማህበሩ ከተመዘገቡ 270 አባላት 245ቱ በዓለም ቡና ገበያ በከፍተኛ ደረጃ እንቅስቃሴ ላይ መሆናቸውን ተናግረዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 13/2013
https://www.press.et/Ama/?p=37864
382
0ሀገር አቀፍ ዜና
የትግራይ ብልጽግና ፓርቲ እና የጊዜያዊ አስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች በአዲግራት ከተማ የደረሰውን ጉዳት ጎበኙ
ሀገር አቀፍ ዜና
December 22, 2020
13
በጋዜጣው ሪፖርተርአዲስ አበባ፡- የትግራይ ብልጽግና ፓርቲ እና የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮች በአዲግራት ከተማ የህወሓት ጁንታ ያደረሰውን ጉዳት ጎብኝተዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት የአዲግራት ከተማ ሰላም እየተመለሰ እንደሆነም ተነግሯል፡፡ኢዜአ እንደዘገበው፤ በትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ዋና ስራ አስፈጻሚ ዶክተር ሙሉ ነጋ እና በትግራይ ብልጽግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራር ዶክተር አብርሃም በላይ የተመራ ልዑክ በአዲግራት ዩኒቨርሲቲና በአዲስ መድሃኒት ፋብሪካ ላይ የደረሰውን ውድመት ተዘዋውረው ተመልክተዋል፡፡በጉብኝቱም የህወሓት ጁንታ ለህዝብ የማያስብ እና ከህዝብ አብራክ የወጣ የማይመስል የጥፋት ቡድን መሆኑን በመሰረተ ልማቶች ላይ ባደረሰው ጥፋት ማሳየቱ በግልጽ እንደታየ የተገለጸ ሲሆን፤ የህወሓት ጁንታ በአዲግራት ዩኒቨርሲቲ ዝርፊያ ከመፈጸም አልፎ የቀረው ንብረት ለመጪው ትውልድ እንዳያገለግል ሰባብሮ እና ከጥቅም ውጪ አድርጎ መፈርጠጡም ተነግሯል።በአዲግራት ከተማ በሚገኘው አዲስ መድሃኒት ፋብሪካም ተመሳሳይ ድርጊት የፈጸመ ሲሆን፤ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ዶክተር ሙሉ ነጋ ቡድኑ በህዝብና በመንግስት ንብረት ላይ የከፋ ጉዳት ማድረሱን ጠቁመዋል፡፡ የቡድኑ የህገወጥ ድርጊት ሰለባ የነበረችው የአዲግራት ከተማ ሰላም በአሁኑ ወቅት እየተመለሰ እንደሆነም ተናግረዋል።በቀጣይ በትግራይ ክልል አጠቃላይ በህወሓት ጁንታ የደረሱ ጉዳቶች ተጠንተው ለፌዴራል መንግስት ቀርበው መፍትሄ እንዲያገኙ የሚደረግ ስለመሆኑ የተጠቆመ ሲሆን፤ የጉብኝት ልዑኩ የአካባቢውን ሰላም ለመጠበቅና የፈረሰውን የመንግስት መዋቅር መልሶ ለማቋቋም ከአዲግራት ከተማ ወጣቶች ጋር ምክክር አድርገዋል፡፡ በምክክር መድረኩ በጋራ ለመስራት የሚያስችል መግባባት ላይ ተደርሷል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 13/2013
https://www.press.et/Ama/?p=37855
182
0ሀገር አቀፍ ዜና
ሙስናን በዘላቂነት ለመከላከል ህዝቡን ባሳተፈ መልኩ መስራት እንደሚገባ ተገለጸ
ሀገር አቀፍ ዜና
December 22, 2020
11
 በጋዜጣው ሪፖርተርአዲስ አበባ፡- በሀገሪቱ የሚስተዋለውን ሙስናን በዘላቂነት ለመከላከል ህዝቡን በአግባቡ በማሳተፍ መስራት እንደሚገባ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ- ጉባኤ አቶ ታገሠ ጫፎ ገለጹ።ሀገር አቀፍ የፀረ- ሙስና መድረክ ትናንት በጎንደር ከተማ ተጀምሯል።እንደ ኢዜአ ዘገባ፤ አፈጉባኤው ሙስናን መታገል በዋናነት ከራስ እንደሚጀመር አመልክተው፤ የሀገሪቱን እድገት የሚፈታተን በመሆኑ ጊዜ ሳይሰጠው ህዝቡን በአግባቡ ማሳተፍ፣ በተደራጀ አግባብ መከላከልና ማስቆም እንደሚገባ አሳስበዋል። በሀገሪቱ ሙስናን ለመታገል የሚደረገውን ጥረት በመደገፍ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አስፈላጊውን እገዛ ያደርጋል ያሉት አፈ ጉባኤው፤ ሙስና በሀገሪቱ የተጀመረውን የብልፅግና ጉዞ እንዳያስተጓጉል በፅናት መታገል እንደሚገባም ነው ያስገነዘቡት።በመድረኩ የፌዴራል የሥነ- ምግባርና የፀረ ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ፀጋ አራጌና የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አገኘው ተሻገርን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ አመራሮችና ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ነው።ለሁለት ቀናት በሚካሄደው በዚህ መድረክ በፀረ ሙስና ዙሪያ ጥናታዊ ጽሁፎች እንደሚቀርቡና ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች እንደሚቀመጡ ታውቋል፡፡አዲስ ዘመን ታህሳስ 13/2013
https://www.press.et/Ama/?p=37865
125
0ሀገር አቀፍ ዜና
በኢትዮጵያና ሱዳን ድንበር ላይ የተከሰተው ችግር የሀገራቱን ወዳጅነትና ትስስር እንደማያሻክረው ተገለፀ
ሀገር አቀፍ ዜና
December 23, 2020
6
በጋዜጣው ሪፖርተርአዲስ አበባ፡- ረጅም ዘመናትን ያስቆጠረው የኢትዮጵያ እና የሱዳን ግንኙነት እርስ በርሱ የተጋመደ በአብሮነትና በወንድማማችነት መሰረት ላይ የተገነባ በመሆኑ ከሰሞኑ በሁለቱ ሀገራት ድንበር ላይ የተከሰተው ችግር የሀገራቱን ወዳጅነትና ትስስር እንደማያሻክረው ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ገለጹ። አቶ ደመቀ መኮንን ሁለተኛው የኢትዮ-ሱዳን የድንበር ጉዳዮች የከፍተኛ ደረጃ የፖለቲካ ውይይት ጉባኤ ላይ ተገኝተው ባደረጉት የመክፈቻ ንግግራቸው እንደገለጹት፤ የኢትዮ ሱዳን የሁለትዮሽ ግንኙነት በአብሮነትና በወንድማማችነት መሰረት ላይ ለረጅም አመታት የተገነባ በመሆኑ ከሰሞኑ በድንበር ላይ የተፈጠረው ክስተት ከሁለቱ ህዝቦች ፍላጎት በተቃራኒው የሆነ ተግባር ነው። የሱዳን ወታደሮች በአካባቢው ላይ በወሰዱት እርምጃ የአርሶ አደሮች ምርት በእሳት ቃጠሎ ደርሶበታል፣ ከመኖሪያ ቦታቸውም ተፈናቅለዋል፤ ንጹሐን ዜጎች ሕይወታቸው አልፏል። በአዲስ አበባ በተደረገው ስብሰባ ላይ ውጤታማ ውይይቶች ተደርገው ከስምምነት መደረሱን ያስታወሱት አቶ ደመቀ፤ በድንበር አካባቢ ያለው የጸጥታና የሰላም ጉዳዮችን በጋራ ለመፍታትና የአካባቢውን ማህበረሰብ ተጠቃሚ ለማድረግ መልካም ስራዎች መሰራታቸውን ተናግረዋል። በቅርቡ በሁለቱ ሀገራት ድንበር ላይ የተከሰተው ችግርም የሁለቱን ሀገራት ህዝቦች የሁለትዮሽ ግንኙነት እንደማያሻክረው ነው የገለጹት። እንደ አቶ ደመቀ ገለጻ፤ ሱዳን ከዓለም አሸባሪነት መዝገብ ዝርዝር ውስጥ በአሜሪካ መንግስት በመሰረዟ ሱዳን ከአጋር ድርጅቶች ጋር በጋራ መስራት የሚያስችላት ሲሆን፤ ይሄም የህዝቦቿን ልማት እና ዕድገት እውን ለማድረግ እገዛው የጎላ ይሆናል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 14/2013
https://www.press.et/Ama/?p=37922
179
0ሀገር አቀፍ ዜና
‹‹የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪን ለማሻሻል የዘርፉን ቴክኖሎጂ ወደአገሪቱ ነባራዊ ሁኔታ ለውጦ መጠቀሙ ፋይዳው የላቀ ነው››ዶክተር አስረግደው ካሳ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በቀድሞው አጠራሩ የህንጻ ኮሌጅ ረዳት ፕሮፌሰር
ሀገር አቀፍ ዜና
December 22, 2020
9
አስቴር ኤልያስ አዲስ አበባ፡- የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪን ይበልጥ ለማሻሻልና ለማስፋፋት የዘርፉን ቴክኖሎጂ ከአገራችን ነባራዊ ሁኔታ ጋር አጣጥሞ መጠቀሙ ፋይዳው የላቀ ነው ሲሉ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በቀድሞው አጠራሩ ህንጻ ኮሌጅ ረዳት ፕሮፌሰር ዶክተር አስረግደው ካሳ ገለጹ፡፡ዶክተር አስረግደው ካሳ የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ ቴክኖሎጂን በተመለከተ ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ እንዳስታወቁት፤ በአሁኑ ወቅት በዘርፉ እየወጡ የሚገኙ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎች የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪን እያሻሻሉ ሲሆን፤ የሚወጡትን ቴክኖሎጂዎች ደግሞ ከኢትዮጵያ ነባራዊ ሁኔታ ጋር አጣጥሞ መጠቀሙ ጠቀሜታው ጉልህ ነው። ቴክኖሎጂን መጠቀም ያለምንም ጥያቄ ፋይዳው ከፍ ያለ ስለመሆኑ አያጠራጥርም ያሉት ዶክተር አስረግደው፣ በአሁኑ ወቅት ያሉትም ቴክኖሎጂዎች ቢሆኑ የትየለሌ ስለመሆናቸው ተናግረዋል።በተለይም ከምርታማነት፣ ከደህንነት፣ ከጥራት፣ ከጊዜ፣ ከዋጋ፣ የግንባታን ሂደት ቀድሞ ከማየት አንጻር እንዲሁም ከሌሎች በርካታ ሁኔታዎች አኳያ ቴክኖሎጂ ወሳኝ ስለመሆኑ የሚያጠያይቅ ጉዳይ አይደለም ብለዋል።እንደ ዶክተር አስረግደው ገለጻ፤ የቴክኖሎጂው ጠቀሜታ በስራ ላይ ስህተቶች እንዳይከሰቱ ከማድረጉም በተጨማሪ ድግግሞሾች እንዳይኖርም ጭምር የሚያደርግ ነው።ቴክኖሎጂን መጠቀም መቻል የተዋጣለት ዲዛይንም እንዲኖር በማድረጉ በኩል ከፍ ያለ ሚና ይጫወታል።የስራውን ሂደት የተሳለጠ በማድረጉም በኩል ድርሻው ጉልህ ነው።ስለዚህ የተሻለ ውጤትን ለማግኘት እና የተሻለ አሰራርን ለመቀየር የሚያስችል ነው፡፡እንዲህ ሲባል ግን ትልቁ እና ማስተዋልን የሚጠይቀው ነገር ቴክኖሎጂውን ወደራሳችን ነባራዊ ሁኔታ ማምጣቱ ላይ ነው ያሉት ዶክተር አስረግደው፤ ቴክኖሎጂውን ወደአገራችን በምናመጣት ጊዜም ጥንቃቄ ማድረጉ መልካም ነው ሲሉ አስረድተዋል።ተማሪውም፣ ድርጅቶችም ሆኑ የተለያዩ ተቋማት የሰለጠነው ዓለም የሚጠቀምበትን ቴክኖሎጂ ወደራሱ በማምጣት አሰራሩን ሊያበለጽጉለት እንዲችሉ ሲያደርግ የአገሪቱን ተጨባጭ ሁኔታ ያገናዘበ መሆን ይኖርበታልም ብለዋል።እርሳቸው እንዳሉት፤ ቴክኖሎጂን አምጥቶ መጠቀሙ መልካም ነገር ነው፤ ነገር ግን የምናመጣውን ቴክኖሎጂ መልሰን ከአገሪቱ ተጨባጭ ሁኔታ ጋር ምርምር በማድረግ እና በጥናት በማስደገፍ ማላመድ ተገቢነት ያለው አካሄድ ነው።የሚመጣው ቴክኖሎጂ ከጊዜው ጋር የሚሄድ መሆኑን ማረጋገጥ የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪውን ውጤታማ የሚያደርግ ነው።ቴክኖሎጂን የማላመዱ ሂደት ከትምህርት ቤት መጀመሩ ደግሞ የፈጠራ ክህሎታቸውን ስለሚጨምር ተማሪዎችን የመፍትሄ ሰዎች ያደርጋቸዋል፡፡ተማሪዎች ገና ከመጀመሪያው ቴክኖሎጂ ላይ ትኩረት እንዲያደርጉ ማመቻቸቱ ሁሌም የሌሎች አገሮችን ቴክኖሎጂ አምጥተን ከማላመድ ሊያላቅቀን በመቻሉ ነው ሲሉም አክለዋል።የሌሎች አገሮችን ቴክኖሎጂ ለማላመድ በሚደረገው ጥረት መሰላቸትን ሊያመጣ ስለሚችል ከዚህ አይነት መሰላቸት ለመላቀቅ በራስ ወደተፈጠሩ መሄድን ከወዲሁ መጀመሩ ተገቢነት አለው ብለዋል፡፡አዲስ ዘመን ታህሳስ 13/2013
https://www.press.et/Ama/?p=37854
295
0ሀገር አቀፍ ዜና
በየዕለቱ ከ300 በላይ የኮቪድ ታማሚዎች ወደ ጽኑ ህክምና እንደሚገቡ የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ
ሀገር አቀፍ ዜና
December 23, 2020
12
 ፋንታነሽ ክንዴአዲስ አበባ፡- በየቀኑ ኮቪድ-19 ከሚገኝባቸው ሰዎች ውስጥ ከ300 በላይ የሚሆኑት ጽኑ ህክምና የሚያስፈልጋቸው መሆናቸውን እና ከእነዚህ ውስጥ እስከ 50 የሚደርሱት የመተንፈሻ አካልን የሚረዳ ማሽን የሚያስፈልጋቸው መሆኑን የጤና ሚኒስቴር ገለጸ፡፡ ይህን ተከትሎም ለስድስት ወራት የሚቆይ ኮቪድ 19ን የመከላከል ንቅናቄ ሊያካሂድ መሆኑን አስታውቋል፡፡ የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጀ ዱጉማ በተለይ ለአዲስ ዘመን እንደገለጹት፤ በአሁኑ ወቅት በኮቪድ የሚሞቱና ጽኑ ህክምና የሚያስፈልጋቸው ሰዎች ቁጥር እየጨመረ ነው፡፡ በየቀኑ ቫይረሱ ከሚገኝባቸው ሰዎች ውስጥ ከ300 በላይ የሚሆኑት ጽኑ ህክምና የሚያስፈልጋቸው ሲሆኑ፤ ከዚህ ውስጥ ከ40 እስከ 50 የሚሆኑት ደግሞ የመተንፈሻ አካልን የሚረዳ ማሽን ያስፈልጋቸዋል፡፡ በየቀኑ የሚገለጸው ቁጥር ምርመራ ከተደረገላቸው ውስጥ ብቻ ስለሆነ ትክክለኛውን ቁጥር አያሳይም ያሉት ዶክተር ደረጀ፤ አሁን እየተመረመረ ያለው በቀን ከ4ሺ እስከ 5ሺ ሰው በመሆኑ አሁን ከሚመረመረው በሶስትና አራት እጥፍ ከፍ ቢደረግ ውጤቱም በተመሳሳይ ከፍ ማለቱ እንደማይቀር ተናግረዋል። ከዚህ በፊት በሽታው የሚገኘው በአዲስ አበባና በክልል ከተሞች እንደነበረና አሁን ላይ ግን ከ900 በላይ በሚሆኑ ወረዳዎች ላይ ቫይረሱ ያለባቸው ሰዎች እንደተገኙም ገልጸዋል። ከዚህ በፊት ከተመረመረው ከሶስት እስከ አራት በመቶ ብቻ ቫይረሱ የሚገኝባቸው እንደነበርና አሁን ግን ከ10 እስከ 15 በመቶ በአንዳንድ ቦታዎች ላይም ከ30 እስከ 40 በመቶ ቫይረሱ እየተገኘ መሆኑንም ተናግረዋል። እንደ ዶክተር ደረጀ ገለጻ፤ ቀደም ሲል አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ታውጆ ትልቅ ስራ ባይሰራ ኖሮ አሁን ላይ የሚኖረው ከዚህ የከፋ ይሆን ነበር። የአዋጁን መነሳት ተከትሎ ምክር ቤቱ መመሪያዎች እንዲወጡ በመፍቀዱ መመሪያዎች እንዲዘጋጁ ተደርጓል። በመመሪያው ላይ ለህብረተሰቡና ለሚመለከታቸው አካላት ግንዛቤ መፈጠሩንም ተናግረዋል። የጤና ሚኒስቴር ያወጣውን መመሪያ ተመስርተውም በትራንስፖርት፣ በትምህርትና ቱሪዝም ዘርፎችም የየራሳቸውን መመሪያ እንዲያዘጋጁ የተደረገ ቢሆንም፤ በሚፈለገው ደረጃ ተግባራዊ አልተደረገም። በመመሪያው ላይ የህግ ክፍተት ባይኖርም፤ መተግበር ላይ ግን ክፍተቶች ተስተውለዋል። በህብረተሰቡ ዘንድ ህግን ተቀብሎ ተግባራዊ ለማድረግ ተነሳሽነት እየታየ አለመሆኑን የጠቀሱት ሚኒስትር ዴኤታው፤ ከታች እስከ ላይ ያለው የመንግስት አመራርም መመመሪያውን እያንዳንዱ ቦታ ላይ እንዲተገበር በማድረግ በኩል ቸልተኝነትና የቁርጠኝነት ማነስ እንደሚስተዋልበት አስረድተዋል። የሃይማኖት ተቋማትና ስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች ላይ በወጣው መመሪያ መሰረት ምን እየተሰራ እንደሆነ መከታተል ላይ ክፍተት መኖሩንም ገልጸዋል። ጸጥታ አካላትም መመሪያውን መሰረት አድርገው ህጉ ተፈጻሚ እንዲሆን በማድረግ በኩል ብዙ እንዳልሰሩበት አስረድተዋል። እንደ ዶክተር ደረጀ ገለጻ፤ የሚስተዋለውን ችግር ለመቅረፍ የስድስት ወራት ኮቪድን የመከላከል እቅድ አዘጋጅው ወደ ስራ ሊገቡ ተዘጋጅተዋል። በተለይ ማንም ሰው ማስክ ካላደረገ መንግስታዊና መንግስታዊ ባልሆኑ ተቋማት አገልግሎት እንደማያገኝ አውቆ እንዲስተካል፤ የህግ አካላትም በዚህ ላይ እንዲሰሩና የራሳቸውን ሀላፊነት እንዲወጡ፤ የሚዲያና ኮሚዩኒኬሽን ስራዎችን ማጠናከርና ህብረተሰቡን ለማስተማርና ለማንቃት ስለተወነ በቅርቡ ወደ እንቅስቃሴ እንደሚገባ ጠቁመዋል። ሚዲያዎች ከዚህ በፊትም በራሳቸው ተነሳሽነት ሲንቀሳቀሱ እንደነበር የጠቆሙት ሚኒስትር ዴኤታው፤ አሁንም የሚችሉትን እንዲያደርጉና መንግስትም የሚችለውን ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅበት በመጠቆም፤ ወቅታዊ ነገር እንዳለ ሆኖ ኮቪድ ደግሞ ሌሎችንም ነገሮች ሊያበላሽ ስለሚችል ትኩረት ሰጥቶ መስራት የሚያስፈልግ በመሆኑ በየደረጃው ካሉ የመንግስት የኮሚዩኒኬሽን ባለሙያዎች ጋር የተጠናከረ ስራ ለመስራት በእቅዳቸው ላይ ማስቀመጣቸውን ተናግረዋል። የሰዎች የመመርመር ፍላጎት መቀነስ፣ በመመርመሪያ ኪቶች ውድነትና በላብራቶሪ ስራ ላይ በሚሰሩ ባለሙያዎች በተወሰነ መልኩ እየታየ ባለው መሰላቸት ምክንያት በየዕለቱ የሚመረመሩ ሰዎች ቁጥር መቀነሱን የገለጹት ሚኒስትር ዴኤታው፤ ትልልቅ አቅም ያላቸው ብዙዎቹ ከዚህ በፊት የተገዙና በእጃችን ላይ ያሉ የአሜሪካ ማሽኖች ከዛው ከካምፓኒው የሚመጣ ‹‹ቴስት ኪት›› የሚጠቀሙ በመሆናቸው ምርመራውን ለማሳደግ እንቅፋት ሆኗል ብለዋል። ከዛ ውጪ በአብዛኛው ጥቅም ላይ የሚውሉት አገር ውስጥ የሚመረተው ‹‹ቴስት ኪት›› መሆኑን እና ያሉ ችግሮችን በመፍታት በቀጣይ እስከ 10ሺ የሚደርስ ዕለታዊ ምርመራ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል። እንደ ዶክተር ደረጀ ገለጻ፤ የጤና ባለሙያዎቻችን ምንም የተለየ ክፍያ ሳይከፈላቸው ለረጅም ጊዜ በርካታ ስራዎችን ሰርተዋል። በፌዴራል ደረጃ ቀጥታ በኮቪድ ላይ ለሚሰሩ ባለሙያዎች የተወሰኑ ድጋፎችን ለማድረግ ተሞክሯል። በክልል ደረጃ ግን ብዙ ገንዘብም ስለሚጠይቅ በሙላት አልተደረገም። ባለሙያዎች ስራ ላይ ሲያድሩ ግን አበል ይከፈላል። እናም አቅም በፈቀደ እሱን አሻሽሎ በመክፈል ለመደገፍ እና በዚህ ላይም ከክልሎች ጋር እየተወያዩ ይገኛል። በዚህ መልኩ መቀጠል ከባድ ስለሚሆንም ብዙ የሚሰሩ ሰዎችን በማሰልጠን በፈረቃ እንዲሰሩና ባለሙያውም ሳይደክመው የተወሰነ ሰዓት እንዲሰራ ለማድረግ በሁሉም ሆስፒታሎችና ቦታ ላይ ኮቪድን አቀናጅተው እንዲሰሩ የሚደረግም ይሆናል። ከዚህ ባለፈ አዲስ አበባ ላይ የተጀመረውን ከኮቪድ ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ላላቸው ባለሙያዎች ከሚከፈላቸው ክፍያ ላይ ግብር እንዲቀር የማድረግ እርምጃ ወጥ የሆነ አሰራር እንዲኖር የሚያስችል መመሪያ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት አቅርበው ውሳኔ እየጠበቁ መሆኑን በመጠቆም፤ የመድህን ኢንሹራንስ ለሁሉም የሚሰራ መሆኑንና አንድ ሰው በኮቪድ ህይወቱ ካለፈ ለቤተሰብ ካሳ እንደሚከፈል እና ከዚህ በፊት በኮቪድ ምክንያት ህይወታቸው ላለፉ ባለሙያዎችና የአስተዳደር ሰራተኞች ክፍያ እንዲያገኙ እየተደረገ መሆኑንም አብራርተዋል። በአጭር ጊዜ ውስጥ በአለም ላይ ተስፋ ሰጪ የሆኑ ክትባቶች እየተገኙ መሆኑን የጠቆሙት ዶክተር ደረጀ፤ ለአዳጊ አገራት ከአለም ጤና ድርጅት ጋር በመሆን ሌሎች ያደጉ አገሮችም እየደገፉ ክትባቱን እንዲያገኙ ስለተወሰነ ኢትዮጵያም የሚገባትን ድርሻ እንደምታገኝ ገልጸዋል። ሆኖም ክትባቱ ለሁሉም ህዝብ የሚደርስ ስላልሆነ ለጤና ባለሙያዎች፣ በበሽታው ሊጎዱ የሚችሉ የተለያዩ በሽታዎች ላሉባቸው፣ በእድሜ ለገፉና ተጋላጭ ለሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች ቅድሚያ እንደሚሰጥ አስረድተዋል። ሆኖም ክትባቱ ለመከላከል የሚደረገውን ጥረት የሚተካ ስለማይሆን ክትባት መጣ ስለተባለ ለመከላከል የሚደረገው ጥንቃቄ ላይ ቸልተኝነት ማሳየት አገርን ዋጋ ሊያስከፍል ስለሚችል መጠንቀቅ እንደሚገባ አሳስበዋል። ይህ መረጃ እስከተጠናቀረበት ጊዜ ድረስ በኢትዮጵያ ለ1ነጥብ 7 ሚሊዮን ሰዎች ምርመራ የተደረገ ሲሆን፤ ከ120ሺህ በላይ ሰዎች በበሽታው ሲያዙ፤ 1ሺህ 860 በላይ ሰዎች ደግሞ ህይወታቸው ማለፉን መረጃዎች ያሳያሉ።አዲስ ዘመን ታህሳስ 14/2013
https://www.press.et/Ama/?p=37921
727
0ሀገር አቀፍ ዜና
ኢትዮጵያ ሁለተኛዋን ሳተላይት አመጠቀች
ሀገር አቀፍ ዜና
December 23, 2020
25
በጋዜጣው ሪፖርተርአዲስ አበባ፡- ኢትዮጵያ ሁለተኛዋን ሳተላይት ማምጠቋን የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት አስታወቀ። ትናንት የመጠቀችው የኢትዮጵያ ሁለተኛዋ ሳተላይት በሰላም መምጠቋን ገልጿል፡፡ኢንስቲትዩቱ እንዳመለከተው ኢትዮጵያ አሁን ያመጠቀቻት ሳተላይት ET-Smart-RSS የምትባል ሲሆን፤ ኢትዮጵያ ባለፈው ዓመት ETRSS-1 የተባለች የመጀመሪያዋን የመሬት ምልከታ ሳተላይት ታኅሣሥ ወር 2012 ዓ.ም ማምጠቋ ይታወሳል።አምና የመጠቀችው ይህች ሳተላይትም መረጃ መላክ የጀመረች ሲሆን፤ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቆጣጠር፣ ከግብርና ጋር የተያያዙ ጥናት እና ምርምሮችን ለመሥራት እና ሌሎች ዘርፈ ብዙ የመሠረተ ልማት ተግባራትን በማከናወን ላይ እንደምትገኝም ነው መረጃዎች የሚያሳዩት፡፡አዲስ ዘመን ታህሳስ 14/2013
https://www.press.et/Ama/?p=37920
79
0ሀገር አቀፍ ዜና
ብልህ ከታናሹ ይማራል
ስፖርት
January 2, 2020
22
 የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ለአዲስ አበባ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በእድሜም፣ በስምም፣ በተቋም ግዝፈትም ታላቅ ስለመሆኑ የሚጠራጠር አይኖርም።እነዚህ ታላቅና ታናሽ ተቋማት አሁን ያሉበት ቁመናና ተግባር ከእግር ኳሱ ጥቅም አኳያ እንደሚለያይ ብዙ ማሳያዎችን ማስቀመጥ ይቻላል።በተለይም እግር ኳሱን በዘመናዊ መንገድ ከመምራት አንፃር ታናሹ የተሻለ ስኬት እስመዘገበ በጥሩ ጎዳና ሲጓዝ ታላቁ ወደ ኋላ እየቀረ መምጣቱን በማስረጃዎች መከራከር የሚቻልበት ደረጃ ላይ ተደርሷል።ብልህ ከታናሹ ይማራልና የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የአዲስ አበባ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በዘንድሮው የከተማዋ ዋንጫ ካሳካቸው ቁም ነገሮች ጥቂቶቹን እንኳን መማር ከቻለ ብዙ ነገር መለወጥ እንደሚችል ይታመናል። በእነ ኢንጂነር ሃይለእየሱስ ፍስሃ የሚመራው የአዲስ አበባ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አዲስ ባይሆንም ከጊዜ ወደ ጊዜ ለእግር ኳሱ የሚበጁና መደረግ ያለባቸውን ተግባራት በመፈፀም ላይ ይገኛል። ከጥቅምት 20 እስከ ህዳር 14/2012 ዓ.ም ድረስ በአዲስ አበባ ስታድየም ሲካሄድ የነበረውን የአዲስ አበባ ዋንጫ ውድድርን መነሻ በማድረግ፤ በውድድሩ ተሳታፊ ለነበሩት ብቻ ሳይሆን በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ለስፖርቱ እድገት አስተዋፅኦ አላቸው ላሏቸው ግለሰቦችና ተቋማት ምስጋናና እውቅና ሰጥቷል። በዚህም መሰረት ለክለቦች ከ150,000 ብር እስከ 752,000 ብር ድረስ እንደየደረጃቸው ሸልሟል።ለግለሰቦች ደግሞ ከ10,000 ብር እስከ 75,000 ብር ወጪ በማድረግ በድምሩ 2 ሚሊዮን ብር አካባቢ አበርክቷል። የአዲስ አበባ እግር ኳስ ፌዴሬሽንና የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን እንኳን ዓመቱን ሙሉ በሚያከናውናቸው ውድድሮች በታሪክ አሳክቶት የማያውቀውን የሽልማት መጠን በማሳካት ክለቦች የሚመጥናቸውን ክብር በመስጠቱ አለማድነቅ አይቻልም።በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የሚሳተፉ ክለቦች ለተጫዋቾች ዝውውር ፣ ደሞዝ፣ ትራንስፖርትና ሌሎች ወጪዎች በዓመት በአማካይ ከ10 ሚሊዮን ብር በላይ ያወጣሉ። በፕሪሚየር ሊጉ ሚሊዮኖችን ወጪ አድርገው ተሳትፈው የሚያገኙት አንዳች ነገር አለመኖሩ ግን አስገራሚ ነው።ዓመቱን ሙሉ ውድድር አድርጎ የፕሪሚየር ሊጉ ቻምፒዮን የሚሆን ክለብ 150 ሺህ ብር ይበረከትለታል። ይህ ደግሞ በአስር ቀን ውድድር ብቻ ከ750 ሺ ብር በላይ ሽልማት ከሚያስገኘው የአዲስ አበባ ዋንጫ አንፃር ምንም ነው። ቅዱስ ጊዮርጊስ ዘንድሮ የአዲስ አበባ ዋንጫን በማንሳቱ ይህን ሽልማት ወስዷል።በፕሪሚየር ሊጉ ይህን ያህል የገንዘብ ሽልማት ለማግኘት ግን በተከታታይ አምስት ዓመታት ቻምፒዮን መሆን ይጠበቅበታል።ፕሪሚየር ሊጉን የሚያሸንፍ ክለብ 150 ሺህ ብር የሚሸለም ሲሆን፤ የአዲስ አበባ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ለአዲስ አበባ ዋንጫ ለተሳትፎ ብቻ 150 ሺህ ብር የመጨረሻው ሽልማቱ ነው። ከዚህ በመነሳት ብሄራዊ ፌዴሬሽኑም ሆነ አዲሱ ሊጉን የሚመራው ዓብይ ኮሚቴ ከአዲስ አበባ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የሽልማት አሰጣጥ አንድ ነገር መማር እንዳለበት ብዙዎች ይስማማሉ። የአዲስ አበባ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ታህሳስ 14 ቀን 2012 ዓ.ም በኢንተርኮንቴኔንታል ሆቴል ባዘጋጀው መድረክ እውቅና ከሰጣቸው ተቋማት አንዱ ዳሸን ባንክ ነበር። ባንኩ በአሞሌ አማካኝነት ተመልካቾች ሳይጉላሉ በየቤታቸው ሆነው ትኬት ቆርጠው ስቴድየም እንዲገቡ በማድረግ ላበረከተው አስተዋጽኦ ሽልማቱ ሊበረከትለት ችሏል። ከዚህ ሁነት በመነሳት ብሄራዊ ፌዴሬሽኑ ልምድ ሊወስድ የሚገባው የትኬት አሻሻጥ ሥርዓት እንዳለ መረዳት ይቻላል።የተመልካቾች ስታዲየም መግቢያ ቲኬት ሲሸጥ የነበረው በዳሸን አሞሌ አማካይነት የኦን ላይን የአሠራር ሥርዓት በመዘርጋት ነበር። በአዲስ አበባ ስታዲየም የሚስተዋሉ ረዣዥም ሠልፎችን ያስቀረ ከመሆኑ ባሻገር፣ የተጭበረበሩ (ፎርጅድ) ትኬቶች ሥራ ላይ እንዳይውሉ ያስቻለ ቴክኖሎጂ ነው። ብሄራዊ ፌዴሬሽኑ ለ22 ዓመታት ከተጓዘበት መንገድ ለመውጣት የሚያስችል ቴክኖሎጂን ተግባራዊ ለማድረግ በተደጋጋሚ ሲገልጽ ቆይቶ ወደ ተግባር ሳይለውጥ መቆየቱን በማስታወስ፤ ከመዲናዋ እግር ኳስ መማር እንደሚገባውም የስፖርት ቤተሰቡ ያምናል። መስከረም 25 ቀን 2010 ዓ.ም ብሄራዊ ፌዴሬሽኑ በአዲስ አበባ ስታዲየም የመግቢያ ትኬት ለመቁረጥ የሚፈጠረውን ረጅም ሰልፍ የሚያስቀር ቴክኖሎጂ ስራ ላይ ሊያውል እንደሆነ መግለጫ ሰጥቶ ነበር። የፌዴሬሽኑ የማርኬቲንግ ዳይሬክተር አቶ ኢሳያስ ታፈሰ በጊዜው ቴክኖሎጂው ለዚሁ ስራ በሚከፈቱ ጣቢያዎች፣ በሞባይልና በኢንተርኔት አማካኝነት ጥቅም ላይ እንደሚውል ነበር የተናገሩት። የኢ-ቲኬት ሽያጭ አሰራሩን ተግባራዊ ለማድረግ ክፍያ ፋይናንሺያል ቴክኖሎጂ ከተሰኘ ተቋም ጋር ስምምነት መፈረሙ ይታወሳል። የኢ-ትኬት አገልግሎት ሽያጭ ከሚያዚያ 25 ቀን 2010 ዓ .ም ጀምሮ አገልግሎቱ በይፋ እንደሚጀመር ተነግሮ የነበረ ቢሆንም፤ የተባለው መሬት ላይ ወርዶ አልታየም። የአዲስ አበባ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ለመገናኛ ብዙሃንና ለስፖርት ጋዜጠኞች እውቅናና ሽልማት ማበርከቱ ሌላ የሚያስመሰግነው ተግባር ነው።ይህ ተግባር በተለይ ብሄራዊ ፌዴሬሽኑ ዝቅ ብሎ ሊቀስመው የሚገባ መልካም ተግባር እንደሆነ በብዙዎች ተነግሯል። ብሄራዊ ፌዴሬሽኑ ለመገናኛ ብዙሃን በሩን ክፍት አድርጎ መረጃን እንደማይሰጥ በተደጋጋሚ ቅሬታ የሚሰማበት መሆኑና ፤ ጋዜጠኞችን በሚሰሩት ሥራ በማበረታታት በአብሮነት ከመስራት ይልቅ በሩን ዝግ አድርጎ የሚሰራ መሆኑ ዘወትር ሲያስወቅሰው ይሰማል። የአዲስ አበባ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ውድድሩን በቀጥታ የቴሌቪዥን ስርጭት ሲያስተላልፍ የነበረውን የአዲስ ሚዲያ ኔትወርክን ልዩ ተሸላሚ ያደረገ ሲሆን ፤ ብሔራዊ ፌዴሬሽኑ ውድድሮችን በቀጥታ በማስተላለፍ ለህዝብ ተደራሽ ወደ ማድረግ አሰራር መግባት እንደሚገባው ልምድን መቅሰም እንዳለበት ያሳየ አጋጣሚ ነው።ብሄራዊ ፌዴሬሽኑ ከሶስትና አራት ዓመት በፊት በፕሪሚየር ሊጉ የተመረጡ ጨዋታዎችን በቴሌቭዥን የቀጥታ ስርጭት ለማስተላለፍ ስምምነት ላይ ደርሶ ነበር። በፕሪሚየር ሊጉ የሚደረጉ ጨዋታዎች የቀጥታ ስርጭት ሽፋን ማግኘት ተከትሎ ለፌዴሬሽኑም ሆነ ለክለቦች ከስፖንሰር ሺፕ ከፍተኛ የሆነ ገቢ ማግኘት የሚቻልበት አጋጣሚ ግን እስካሁን ተግባራዊ አልሆነም። አዲስ ዘመን ታኅሣሥ 23/2012 ዳንኤል ዘነበ
https://www.press.et/Ama/?p=25048
658
2ስፖርት
“ጠላቶች ኢትዮጵያን በብሔርና በሃይማኖት ለመከፋፈል ያላቸው ፍላጎት ዛሬም አልጠፋም’’ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ
ሀገር አቀፍ ዜና
December 23, 2020
16
በጋዜጣው ሪፖርተርአዲስ አበባ፡- ጠላቶች ኢትዮጵያን በብሔርና በሃይማኖት ለመከፋፈል ያላቸው ፍላጎት ዛሬም አልጠፋም ሲሉ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ተናገሩ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ትናንት በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ከመተከል ዞን ነዋሪዎች ጋር ተወያይተዋል፡፡ጠቅላይ ሚኒስትሩ በውይይቱ ወቅት፤ ጠላቶች ኢትዮጵያን በብሔርና በሃይማኖት ለመከፋፈል ያላቸው ፍላጎት ዛሬም አለመጥፋቱን የገለጹ ሲሆን፤ ምንም እንኳን ጠላቶች በዚህ መልኩ ቢሰሩም አስተዋይ ሕዝብ ይዘን ችግሮች እንዳይደገሙ አድርገን እንፈታዋለን ሲሉ ተናግረዋል፡፡“ከመተከል ነዋሪዎች ጋር ባደረግኩት ውይይት ሕዝባችን ለአንድነት፣ ለሰላም፣ ለልማት እና ለብልጽግና ያለው ፍላጎት የትኛውንም የመከፋፈል አጀንዳ እንደሚያከሽፍ ተመልክቻለሁ” ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ይህ በመሆኑ ምክንያትም ጠላቶቻችን ኢትዮጵያን በጎሳ እና በሃይማኖት የመከፋፈል ፍላጎታቸው አሁንም ድረስ ቢኖርም ይህ ፍላጎታቸው እንዳልተሳካላቸው ገልጸዋል። ይሄንን ጽኑና አስተዋይ ሕዝብ ይዞ ደግሞ ችግሮችን እንዳይደገሙ አድርጎ መፍታት እንደሚቻልም ተናግረዋል። በውይይት መድረኩ ላይ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰን፣ የሰላም ሚኒስትር ሙፈሪያት ካሚል፣ የኢፌዴሪ መከላከያ ሰራዊት ጠቅላይ ኤታማጆር ሹም ጄኔራል ብርሃኑ ጁላ እና ሌሎች የስራ ኃላፊዎች የተገኙ ሲሆን፤ በመድረኩ ላይ በአካባቢው የተከሰተውን የፀጥታ ችግር መፍታት በሚቻልበት አግባብ ላይ ውይይት የተካሄደበት መሆኑንም ነው ኢዜአ የዘገበው። በተያያዘ፣ ፋና ብሮድካስት ኮርፖሬት እንደዘገበው፤ ውይይቱ መድረኩ በመተከል ዞን በተደጋጋሚ የሚከሰቱ የፀጥታ ችግሮችን ለማስቆም ዘለቄታዊ የመፍትሔ አቅጣጫ ለማስቀመጥ ያለመ ሲሆን፤ በወቅቱም ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ለሀገሪቱ አንድነትና ሠላም ብቸኛው አማራጭ ኢትዮጵያውያን ከጥላቻ፣ ከስሜት እና ከመገፋፋት ወጥተው አንድነታቸውን እና አብሮነትን ማጠናከር ነው ብለዋል። በቀጣናው የተፈጠረውን የፀጥታ ችግር በዘላቂነት ለማስቆም ጥረት የተደረገ ቢሆንም በርካታ ተዋናዮች በመኖራቸው ችግሩን በአፋጣኝ እንዳይቆም አድርጎት መቆየቱንም ገልጸዋል። በመሆኑም አካባቢውን ወደ ሠላም የመመለሱ ሥራ በትኩረት እንደሚሠራ የጠቆሙት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ከዚህ ባለፈ ግን በዞኑ እየተካሄደ ያለው የህግ ማስከበር ተግባር ገለልተኛ እና ከአድሏዊነት በፀዳ መልኩ እንዲተገበር አሳስበዋል። በስሜት እና በብሶት የጁንታውን የጥፋት ተልዕኮ ተቀብሎ ወደ ጫካ የሸሸው ኃይል በሠላማዊ መንገድ እንዲመለሱ ለማድረግ አመራሩና በየደረጃው ያሉ ባለድርሻ አካላት ኃላፊነታቸውን እንዲወጡም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጥሪ አቅርበዋል።ከዚህ ባለፈ የክልሉን የተፈጥሮ ፀጋ በመጠቀምሥራ አጥ ወጣቶችን በማደራጀት የክልሉ መንግሥት ተጠቃሚ ለማድረግ በትኩረት እንዲሰራም መልዕክት አስተላልፈዋል። መንግሥት እየወሰደው ካለው እርምጃ ባሻገር በቀጣናው ዘላቂ ሠላም እንዲሰፍን የሀገር ሽማግሌዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ የወጣቶችና የሴቶች አደረጃጀቶች ጋር በዞኑ የተፈጠረውን የሠላም እጦት ለመፍታት ያላሰለሰ ጥረት እንዲያደርጉም ነው ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጥሪ ያቀረቡት።የውይይቱ ተሳታፊዎች በበኩላቸው፤ ኃላፊነት የጎደለው የማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀም እና ባለፋት 27 አመታት የህወሓት ጁንታ የፈፀመው የፖለቲካ አሻጥር በቀጣናው ዘላቂ ሠላም እንዳይረጋገጥ አድርጎ መቆየቱን ተናግረዋል። በመተከል ዞን በተደጋጋሚ የሚፈጠረውን የጸጥታ ችግር ለማስቆም ጥረት ቢደረግም፤ አባባሽምክንያቶችን ለይቶ መፍትሄ መስጠት ባለመቻሉ የፀጥታ ችግሩ እስካሁን መቀጠሉን አንስተዋል።ዞኑ የተለያዩ ብሔር፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ለዘመናት በአብሮነት የሚኖሩበት አካባቢ እንደመሆኑ መጠን፤ የህዝቦችን አንድነትና አብሮነትን ለማጠናከር መንግሥት በትኩረት ሊሠራ ይገባልም ሲሉ ነው ተሳታፊዎቹ ያስገነዘቡት።አዲስ ዘመን ታህሳስ 14/2013
https://www.press.et/Ama/?p=37919
378
0ሀገር አቀፍ ዜና
የፀረ ኤች.አይ.ቪ ኤድስ መድኃኒት ከቅዱሳን መጻህፍት አስተምህሮ አኳያ
ሀገር አቀፍ ዜና
December 23, 2020
8
አስመረት ብስራትበሃይማኖት አባቶች ፀሎት የተከፈተው ጉባኤ እጅግ መከባበር የሞላበት ነበር። በፀረ ኤች አይቪ መድሀኒት ላይ አተኩሮ የኤች፣አይ.ቪ ታካሚዎች ህክምናቸውን በመውሰድ እንዳያቋርጡ ለማድረግ የተከናወነው የቅስቀሳ መድረክ የተለያዩ ታላላቅ መንፈሳዊ አባቶች፤ የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ፤ የሰራተኛና የማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ዶክተር ኤርጎጌ ተስፋዬ፤ ቫይረሱ በደማቸው ውስጥ የሚገኝባቸው ሰዎችና ሌሎች ተሳታፊዎች ተገኝተውበት ነበር።የጉባኤውን መጀመር በእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር የጀመሩት የኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጠቅላይ ፀሀፊ ቀሲስ ታጋይ ታደለ፤ በሀገራችን የቫይረሱን ስርጭት ለመግታት የሚቻለው ቫይረሱ በደማቸው ውስጥ የሚገኝ ሰዎች የህክምና ክትትላቸውን በአግባቡ ማከናወን እንዲችሉ ሲደረግ ብቻ መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አዲስ እያንሰራራ ያለው የኤች.አይ.ቪ ቫይረስ ስርጭትን ለማቆም በሃይማኖት ሰበብ መድሀኒታቸውን የሚያቋርጡ ህሙማን ከዚህ ተግባር መቆጠብ እንደሚኖርባቸው አስረድተዋል።ኤች.አይ.ቪ ቫይረስ በደማቸው ውስጥ ከሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች የተወከሉት አቶ መኮንን አለሙ በበኩላቸው፤ ከፀበል፣ ከዱአና ከፀሎት ጎን ለጎን መድሀኒቱን መውሰድ ያለምክንያት የሚጠፋውን የቫይረሱ ተጠቂዎችን ህይወት ሊታደግ እንደሚችል አስረድተዋል። ከሃይማኖት አባቶች ጋር የሚደረግ ግንኙነት የመንፈስ ጥንካሬን እንደሚያጎናፅፍ በመጥቀስም፤ መንፈሳዊውንም ሆነ ዘመናዊውን ህክምና ጎን ለጎን ማስኬድ አዲስ ከቫይረሱ ጋር የሚወለዱ ልጆች እንዳይኖሩ ማድረግ እንደሚያስችል ገልፀዋል። ቀደም ሲል የበሽታውን ስርጭት ለመቆጣጠር የሃይማኖት አባቶች አስተዋፅኦ የላቀ መሆኑን ያስታወሱት የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ በበኩላቸው፤ አሁንም ቢሆን በመቀዛቀዝ ላይ ያለው ኤች.አይ.ቪ ቫይረስን የተመለከተ ንቅናቄ አሁንም በሃይማኖት አባቶች አስተምሮት ሊደገፍ እንደሚገባ አሳስበዋል። በሀገራችን ከ667ሺ በላይ ሰዎች በደማቸው ውስጥ ቫይረሱ መኖሩን በመጠቆም፤ በሁሉም ህብረተሰብ የጋራ ርብርብ መጥቶ የነበረው የአመለካከት ለውጥ ወደኋላ እንዳይመለስ የሃይማኖት አባቶች አስተምሮአቸውን አጠናክረው መቀጠል የሚገባቸው መሆኑን ጠቁመዋል።ብፁእ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትሪያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት እንዳሉት ደግሞ፤ ለመድሀኒት ሰሪዎች ጥበብን የሰጠው ፈጣሪ በመሆኑ መድሀኒትን መውሰድ ሃይማኖታዊ አስተምህሮ አይከለክልም። የሰው ልጅም በምድር ኖሮ ለማለፍ እስከተፈጠረ ድረስ በህይወቱ መቀለድ የለበትም። በመሆኑም ፀበሉንም እምነቱንም ፀሎቱንም ሳያቆሙ መድሀኒት በመውሰድ እራሳቸውን ከከፋ ህመም መጠበቅ የሚገባቸው መሆኑን ያሳሰቡት ብፁዕ አቡነ ማትያስ፤ በእምነት እያሳበቡ መድሀኒት ማቆም ራስን ከመግደል የማይተናነስ መሆኑን አስረድተዋል። ፈጣሪ ከፈጠራቸው ተክሎች የተፈጠሩ መድሀኒቶችን አልውጥም ማለትም በፍፁም ከመንፈሳዊ አስተምህሮት ውጪ ነው ብለዋል።የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሀጂ ኡመር እንድሪስ በበኩላቸው፤ የሰው ልጅ በቅድሚያ በበሽታ እንዳይጠቃ መጠንቀቅ እንዳለበት በመግለጽ፤ በበሽታ ከተያዘ በኋላ መድሀኒት አልወስድም ማለት ግን የእስልምና ሃይማኖት አስተምህሮ የማይደግፈው ተግባር መሆኑን አስረድተዋል። ህመም የመጣው ከፈጣሪ ማርከሻ መድሀኒቱም የሚገኘው በፈጣሪ ፍቃድ በመሆኑ የሃይማኖታዊ ስርአቶችን ከማከናወን ጎን ለጎን መድሀኒቶቻቸውን በአግባቡ መውሰድ የሚገባቸው መሆኑን አሳስበዋል።̋ካለ እርጅና ሞት በስተቀር፤ አላህ መድሀኒት የሌለው በሽታ አልፈጠረም፤” ያሉት ሀጂ ኡመር፤ ጥበቡን ሰጥቷቸው በቅንነት ሊረዱን የመጡ የህክምና ባለሙያዎችን ትዕዛዝ አለመተግበር ተገቢ አለመሆኑን ተናግረዋል። ብፁእ ካርዲናል ብርሀነ ኢየሱስ ሱራፌል ሊቀጳጳስ ዘካቶሊካውያን የካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን የጳጳሳት ጉባኤ ፕሬዚዳንት በበኩላቸው፤ በተወካያቸው በኩል ባስተላለፉት መልእክት፤ የሳይንስ ግኝት የፈጣሪ ፀጋ በመሆኑ መድሀኒቶች በምንም ሁኔታ ከሃይማኖታዊ ስርአት ጋር የማይጋጭ መሆኑን ተናግረዋል። በተለያዩ የመጽሀፍ ቅዱስ ክፍሎች የተለያዩ መድሀኒቶችን መጠቀም መፈቀዱን አስታውሰው፤ ከሃይማኖት አባቶች ጋር የሚከናወኑ መንፈሳዊ ተግባራት ለስነልቦና እጅግ በጣም ጠቃሚ በመሆኑ ከመድሀኒቱ ጎን ለጎን እምነታዊ ተግባራትን መፈፀም ተገቢ መሆኑን አስረድተዋል።በጉባኤው ላይ መልእክታቸውን ያስተላለፉ ሰባት የተለያዩ ሃይማኖቶች አባቶችም፤ መድሀኒት ማቋረጥ ሃይማኖታዊ አስተምህሮ አለመሆኑን አሳስበዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 14/2013
https://www.press.et/Ama/?p=37933
442
0ሀገር አቀፍ ዜና
አልጄሪያና የ2020 የአፍሪካ አትሌቲክስ ቻምፒዮና ዝግጅት
ስፖርት
January 1, 2020
14
 በቀጣዩ ሰኔ ወር የአፍሪካ ምርጥ አትሌቶች በሰሜን አፍሪካዊቷ አገር አልጄሪያ ለመፋለም ቀጠሮ ይዘዋል።መዲናዋ አልጄርስም በሃያ ሁለተኛው የአፍሪካ አትሌቲክስ ቻምፒዮና የአህጉሪቱ ኮከብ አትሌቶችን ለመቀበል ከወዲሁ ዝግጅቷን እያገባደደች እንደምትገኝ አሳውቃለች።የአፍሪካውያን አትሌቶች ከቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ አስቀድሞ በቻምፒዮናው ለኦሊምፒክ የሚያበቃቸውን ሰዓት ለማሟላት ብርቱ ፉክክር የሚያደርጉበት ትልቅ አጋጣሚ እንደሚሆን ይጠበቃል። የአፍሪካ አትሌቲክስ ኮንፌዴሬሽንም ይህ ቻምፒዮና የተሳካ እንዲሆን ከአልጄሪያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ጋር እየሰራ እንደሚገኝ አሳውቋል፡፡‹‹ ለቻምፒዮናው በሚደረገው ዝግጅት ረክተናል፣ ነገር ግን ይህ ለኛ አዲስ አይደለም›› በማለት ሰሞኑን ለመገናኛ ብዙሃን የተናገሩት የአፍሪካ አትሌቲክስ ኮንፌዴሬሽን ዳይሬክተር ላሚን ፋቲ የአልጄሪያን ዝግጅት ለመገምገም ወደ ስፍራው ያቀናው ቡድን ነገሮች በጥሩ መልኩ እየሄዱ እንደሚገኙ ማረጋገጡን አስረድተዋል።ለዚህም አልጄሪያ የሰውሃብትና አስፈላጊው ቁሳቁስ በበቂ ሁኔታ ያላት አገር መሆኗ ዝግጅቱን ቀላል እንዳደረገው ተናግረዋል። እ.ኤ.አ ከሰኔ 24 እስከ 28 በሚካሄደው ቻምፒዮና ውድድሮችን የሚያስተናግደው ‹ጁላይ 5› ስቴድየም እድሳትና አዳዲስ ቴክኖሎጂዎች እንዲካተቱበት ተደርጎ ሰማንያ ሺ ተመልካች እንዲይዝ የተለያዩ ስራዎች እየተከናወኑ ነው።እኤአ በ1972 በቀድሞው የአልጄሪያ ፕሬዚዳንት ሁአሪ ቡሜዴን ተመርቆ ስራ የጀመረው ስቴድየም በርካታ ታላቅ ውድድሮችን የማስተናገድ ልምድ አለው።እኤአ በ1975 በሜድትራኒያን ጨዋታዎች ይህ ስቴድየም የአትሌቲክስ ውድድሮችን በዋናነት ማስተናገድ ችሏል።እኤአ 1978ና 2007 የመላ አፍሪካ ጨዋታዎችን ከማስተናገዱ በተጨማሪ 2000 ላይ የአፍሪካ አትሌቲክስ ቻፒዮናን ማስተናገድ እንደቻለ ይታወሳል። የኮንፌዴሬሽኑ ዳይሬክተር ፋቲ ባለፈው ወር ለአልጄሪያ መገናኛ ብዙሃን ‹‹የስቴድየሙ እድሳት ገና ሳይጠናቀቅ ገምጋሚ ቡድኑ እየተከናወኑ በሚገኙ ስራዎች ረክቷል፣ በቀጣይ በሚከናወኑ ስራዎች ደግሞ የተሻለ ነገር እንደምናይ ተስፋ አለን›› ማለታቸው ይታወቃል።የአልጅሪያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ከአፍሪካ አትሌቲክስ ኮንፌዴሬሽን ጋር በጋራ በመሆን አትሌቶች፣ ጋዜጠኞችና ሌሎችም በቻምፒዮናው ለመታደም ወደ ስፍራው ለሚያቀኑ አካላት የቪዛና የትራንስፖርት አገልግሎቶችን ለማቀላጠፍ በርካታ ስራዎችን ከወዲሁ እያከናወኑ እንደሚገኙ አሳውቀዋል።ውድድሩ በበርካታ የአፍሪካ አገራት የቀጥታ የቴሌዥን ስርጭት ሽፋን እንዲያገኝም የተለያዩ ስራዎች ተሰርተዋል። በቻምፒዮናው የአትሌቶች አበረታች ንጥረ ነገሮች ተጠቃሚነት ላይ ጥብቅ ቁጥጥር እንዲኖር ከወዲሁ ዝግጅት መደረጉም ታውቋል።አልጄሪያ ይህን ቻምፒዮና ስታስተናግድ የዘንድሮው ሦስተኛዋ ይሆናል።ከዚህ ቀደም እኤአ በ1988 በአናባ ከተማ ቻምፒናውን ያስተናገደች ሲሆን ከሃያ ዓመት በፊት 2000 ላይ በአልጄርስ ቻምፒዮናውን ማስተናገድ ችላለች። በ1988 ቻምፒዮና አልጄሪያ በአስራ አንድ የወርቅ ሜዳሊያ ቀዳሚ ሆና ካጠናቀቀችው ናይጄሪያ በአንድ የወርቅ ሜዳሊያ ዝቅ ብላ በሁለተኛነት ማጠናቀቋ ይታወቃል።ከአስራ ሁለት ዓመታት በኋላ 2000 ላይ ባስተናገደችው ቻምፒዮና ግን አስራ ሁለት የወርቅ ሜዳሊያዎች በመሰብሰብ ቀዳሚ ሆና አጠናቃለች።አዲስ ዘመን ታኅሣሥ 22/2012 ቦጋለ አበበ
https://www.press.et/Ama/?p=25009
317
2ስፖርት
የቶኪዮ ኦሊምፒክ የጎዳና ላይ ውድድሮች ስፍራ ተቀየረ
ስፖርት
December 6, 2019
26
በ2020 ቶኪዮ ኦሊምፒክ የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድሮች የሚካሄድባቸው ስፍራዎች መቀየር ላይ ሲነሳ የቆየው አወዛጋቢ ሃሳብ መቋጫ አግኝቷል፡፡ የኳታር ዓለም ቻምፒዮና የማራቶን ውድድር ላይ የታየውን ክስተት ተከትሎ ዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ከዓለም አትሌቲክስ ጋር በመሆን ውድድሩ የሚካሄድበት ስፍራ እንዲቀየር ጥያቄ ማንሳታቸው የሚታወስ ነው፡፡ የቶኪዮ ኦሊምፒክ አዘጋጅ ኮሚቴው በበኩሉ የውድድር ስፍራውን ከቶኪዮ ወደ ሌላ ስፍራ የማዘዋወር ዓላማ እንደሌለውና በሃሳቡም እንደማይስማማ ማሳወቁ ይታወሳል፡፡ ትናንት በወጣው ዜና መሰረትም በውድድሮቹ ላይ የመርሃ ግብር ቅየራ መደረጉ ታውቋል፡፡ በዚህም መሰረት የማራቶን እና የእርምጃ ውድድሮቹ ከቶኪዮ በ800ኪሎ ሜትር ርቀት በሆካኢዶ ተራራማ አካባቢዎች በሚገኘውና ነፋሻማ የአየር ሁኔታ ባለው ሳፖሮ የተባለ ከተማ የሚካሄዱ ይሆናል፡፡ የውድድር ስፍራውን መቀየር ተከትሎ መርሃ ግብሮቹም ላይ ለውጥ የተደረገ ሲሆን፤ የሴቶች ማራቶን እና በሁለቱም ጾታ የእርምጃ ውድድሮች ለሶስት ተከታታይ ቀናት ይካሄዳሉ፤ የወንዶች ማራቶን ደግሞ እንደተለመደው የኦሊምፒኩ የመዝጊያ ውድድር ይሆናል፡፡ ሁለቱ ዓለም አቀፍ ተቋማት አትሌቶችን ከጉዳት ለመጠበቅ ሃሳቡን በቅድሚያ ያነሱት ሲሆን የውድድሩ አዘጋጆች ተቃውሟቸውን ሽረው ይሁንታቸውን ለመስጠት ምክንያት የሆነው የጃፓን ኦሊምፒክ ኮሚቴ እንዲሁም የአትሌቶች ማህበር መሆኑን ስካይ ስፖርት አስነብቧል፡፡ ከውሳኔው ጋር በተያያዘ አስተያየታቸውን የሰጡት በዓለም ዓቀፉ የኦሊምፒክ ኮሚቴ የአትሌቶች ኮሚሽነር ክርስቲ ኮቬንተሪ፤ የአትሌቶች ጤና ከሁሉ አስቀድሞ ትኩረት የሚሰጠው መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ አያይዘውም ‹‹የማራቶን እና እርምጃ ውድድሮችን ከቶኪዮ ወደ ሳፖሮ መውሰዳችንም በአትሌቶች ጉዳይ ምን ዓይነት አቋም እንዳለን የሚያሳይ ነው›› ብለዋል፡፡ ወራት ብቻ የቀሩት ኦሊምፒኩ በሚካሄድበት ወቅት በጃፓኖች ዘንድ በጋ ነው፤ በጊዜው የቶኪዮ የሙቀት መጠን ደግሞ እስከ 30ዲግሪ ሴሊሽየስ በማሻቀብ ከፍተኛ ወበቅ የሚያስከትል ይሆናል፡፡ ይህ ደግሞ ረጃጅም ርቀት ለሚሸፍኑት የውድድር ዓይነቶች የማይስማማ በመሆኑ በኳታር ያጋጠመው እንዳይደገም ያሰጋል፡፡ የውድድሩ አዘጋጆችም ሙቀቱን ለመቋቋም፤ መጠለያዎችን በማበራከት፤ የውሃ ማቀዝቀዣና ከፍተኛ የውሃ አቅርቦት እንዲኖር በማድረግ እንዲሁም አትሌቶች ዝግጅት በሚያደርጉበት ወቅት ሙያዊ እገዛ ለማድረግ ማሰባቸውን ነበር ያሳወቁት፡፡ሆኖም በዓለም አቀፎቹ ተቋማት በተደረገው ግፊት የውድድር ስፍራው እንዲለወጥ ተደርጓል፡፡ የቶኪዮ ኦሊምፒክ ስራ አስኪያጅ ቶሺሮ ሙቶ ‹‹በሳፖሮ የሚገኘው የኦዶሪ ፓርክ ለእነዚህ ውድድሮች የተመቸ ስፍራ ነው፡፡ በመሆኑም ውሳኔውን ተከትለን በፍጥነት ቦታውን በማዘጋጀት ላይ እንገኛለን፡፡ ኦሊምፒኩ ስምንት ወራት ብቻ ቢቀሩትም በትብብር ዝግጁ የምናደርገው ይሆናል›› ሲሉም ማረጋገጫ ሰጥተዋል፡፡አዲስ ዘመን አርብ ህዳር 26/2012 ብርሃን ፈይሳ
https://www.press.et/Ama/?p=23653
301
2ስፖርት
አፍሪካን ያገለለው የዓለም አትሌቲክስ ሌጋሲ
ስፖርት
December 2, 2019
28
 የኦሊምፒክ የ1500 ሜትር ቻምፒዮኑ እንግሊዛዊ አትሌት ሴባስቲያን ሎርድ ኮ የዓለም አቀፉን አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር በፕሬዚዳንትነት ለመምራት ከአራት ዓመት በፊት የተመረጡት አዲስ አበባ ላይ በተካሄደው የማህበሩ ጉባዔ ላይ ነበር። ኮ ከአራት ዓመት በኋላም ባለፈው መስከረም በዶሃ የዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮና ዋዜማ ላይ ማህበሩን ለቀጣይ አራት ዓመታት ለመምራት ይሁንታ አግኝተዋል። ዓለም አቀፍ ማህበሩ ስሙን ‹‹የዓለም አትሌቲክስ›› በሚል በቅርቡ ከመቀየሩ አስቀድሞ በቀድሞው የመካከለኛ ርቀት ኮከብ አትሌት ኮ ቆራጥ አመራር ሰጪነት በርካታ ነገሮችን እንደቀየረ ይታመናል። በተለይም የቀድሞ የማህበሩ ፕሬዚዳንት ሴኔጋላዊው ላሚን ዲያክ የአስራ አንድ ዓመት የስልጣን ዘመን በአትሌቲክሱ ዓለም የተበላሹ የአመራር ክፍተቶችን በመድፈን ረገድ ኮ የተሳካላቸው መሆኑን ብዙዎች ይመሰክሩላቸዋል። እኤአ ከ1999 እስከ 2015 ማህበሩን የመሩት ዲያክ መንበረ ስልጣናቸውን ባስረከቡ ማግስት በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው ዛሬ ላይ በሰማንያ ስድስት ዓመታቸው ፓሪስ ውስጥ በቁም እስር ላይ ይገኛሉ። የሃምሳ አራት ዓመቱ ልጃቸው ፓፓ ማሳታም ዓለም አቀፍ ማህበሩን ተገን አድርጎ ህገ ወጥ ገንዘብ ህጋዊ በማድረግና ስልጣናቸውን አላግባብ በመጠቀም አብረው ወህኒ ወርደዋል። የክስ ሂደታቸውም በፈረንጆቹ አዲስ ዓመት ማግስት መታየት ይጀምራል። በብዙ ዝቅጠት ውስጥ የነበረውን ማህበር ለመረከብ ኮ ከምርጫ ቅስቀሳቸው ወቅት አንስተው ያልገቡት ቃል የለም። አራት የወርቅ ሜዳሊያዎችን በታላቁ የኦሊምፒክ መድረክ ማሸነፍ የቻሉት ኮ በአመራር ዘመናቸው ትኩረታቸውን በአትሌቶች፣ በውድድሮች፣ በልማት፣ ግልፅነትና ተጠያቂነት ባለበት የአመራር ጉዳዮች ላይ ማድረጋቸው የብዙዎችን ድምፅ እንዲገዙ አስችሏቸዋል። ባለፉት አራት ዓመታትም የዓለምን አትሌቲክስ ቀዳዳዎች እየፈለጉ በመድፈንና በስፖርቱ ስር ነቀል ለውጦችን በመተግበር ተመስግነዋል። የዓለም የዓመቱ ምርጥ አትሌቶች ሽልማት ባለፈው ሳምንት በሞናኮ ሲካሄድም የዓለም አትሌቲክስ የፅህፈት ቤት ሃላፊውና የኮ ቀኝ እጅ የሆኑት ብሪቶን ጆን ሪድገን ለመገናኛ ብዙሃን‹‹ ቀጣዩ ስራችን እድገት ነው›› ሲሉ ተደምጠዋል። ሪድገን በንግግራቸው ጥራት ያላቸው ውድድሮችን በየትኛውም ደረጃ መፍጠር ዋና አጀንዳቸው መሆኑንም አብራርተዋል። ለተመልካቾች፣ ለስፖንሰሮችና ለንግድ አጋሮች ከዓለም ቻምፒዮና ባሻገር በሌሎች ውድድሮች ምቾትን መፍጠርም የዓለም አትሌቲክስ በቀጣይ ሙሉ አቅሙን ተጠቅሞ የሚሰራበት ጉዳይ መሆኑን ተናግረዋል። ኮ እንዲሁም ካቢኔያቸው የዓለምን አትሌቲክስ በገቢ ከማሳደግና የውድድር ጥራትን ከመፍጠር አኳያ የጀመሩት መንገድ የሚጠላ ባይሆንም አካሄዱ ላይ ጥያቄ ያላቸው ወገኖች አልጠፉም። በተለይም አፍሪካውያን። ከ2020 ጀምሮ በዳይመንድ ሊግ ውድድሮች ላይ የተደረገው ለውጥ የጥያቄው መሰረት ሲሆን ኢትዮጵያውያንና ኬንያውያን ከዚህ ለውጥ በተቃራኒ የቆሙ የአትሌቲክስ አገራት ናቸው። አምስትና ሦስት ሺ ሜትር መሰናክል ከዳይመንድ ሊጉ መቀነሳቸውን ተከትሎ የርቀቱ ፈርጥ የሆኑት ሁለቱ ጎረቤታሞች ቀደም ሲልም ቅሬታቸውን ሲያቀርቡ ቆይተዋል። ሪድገን ለምስራቅ አፍሪካውያኑ ጥያቄ ምላሽ ሲሰጡ ግን የተቀነሱት ርቀቶች ጥናት ተደርጎባቸው ከቴሌቪዥን ስርጭት ጋር እንዲስማሙና ለዓለም አትሌቲክስ የገቢ ምንጭ እንዲሆኑ ታስቦበት ውሳኔ ላይ እንደተደረሰ አብራርተዋል። ‹‹ዳይመንድ ሊግ ስፖንሰር የለውም፣ ውድድሩን የሚመለከቱ የስፖርቱ አፍቃሪዎች ቁጥርም እያሽቆለቆለ ነው፣ ዳይመንድ ሊግ ጥሩ ውድድር ነው፣ ስፖንሰሮችና የቴሌቪዥን ጣቢያዎች የተሻለ እንዲሆን ይሻሉ›› በማለት ሪድገን ቃል በቃል ተናግረዋል። እንደ ሪድገን ገለፃ የዳይመንድ ሊግ ውድድሮች ይበልጥ ሳቢና ለቴሌቪዥን ስርጭት አመቺ እንዲሆኑ ቀደም ሲል በቀጥታ የቴሌቪዥን ስርጭት 120 ደቂቃዎች ያስፈልጉት ነበር። አሁን ግን በዘጠና ደቂቃዎች ውስጥ በሚተላለፍ ቀጥታ የቴሌቪዥን ስርጭት እንዲከናወኑ ለማድረግ ነው በተለያዩ አምስት አገራት ጥናት ተደርጎ ረጅም ርቀቶችን መቀነስ ያስፈለገው። በዚህ ጥናት ውስጥ ግን የዳይመንድ ሊጉ ድምቀቶች፣ የአትሌቲክሱ ዓለም ውበት የሆኑት ምስራቅ አፍሪካውያን አልተካተቱም። በውሳኔው ላይም ድምፃቸው አልተሰማም። ሪድገን ለዚህ ምላሽ ሲሰጡ‹‹ በቀጣዩ ዓመት ሙሉ መልሶ ምልከታ እናደርጋለን›› ከማለት ውጭ የተነፈሱት ነገር የለም። የዓለም አትሌቲክስ በዳይመንድ ሊግ ላይ ሃያ አምስት በመቶ ድርሻ አለው። በቅርቡም ከቻይና ግዙፍ የቴሌቪዥን ጣቢያ ጋር የዳይመንድ ሊግ ውድድሮችን በቀጥታ የቴሌቪዥን ስርጭት ለማስተላለፍ ለአስር ዓመት የሚዘልቅ ስምምነት ማድረጉ ይታወቃል። ስለዚህ የዓለም አትሌቲክስ ዳይመንድ ሊጉ ላይ ለውጥ ለማድረግ በቻይና ተፅዕኖ ውስጥ ወድቋል ብለው የሚያምኑ የስፖርት ቤተሰቦች ጥቂት አይደሉም። ለዚህ ሌላ ማሳያው በዳይመንድ ሊጉ ለውጥ ለማድረግ ጥናት ሲካሄድ በአትሌቲክሱ ዓለም ትልቅ ድርሻ ያላቸው ምስራቅ አፍሪካውያን አገራት እያሉ ቻይና ተመራጭ መሆኗ ነው። ለዚህ ውሳኔ ይረዳቸው ዘንድ ኮ የዓለም አትሌቲክስ ትልቅ የስራ ሃላፊነቶች በራሳቸው አገር እንግሊዝ ዜጎች ቀደም ብለው እንዲያዙ ማድረጋቸው ማሳያ ተደርጎ ይቀርባል። ከኮ በተጨማሪ የዓለም አትሌቲክስ የፅሕፈት ቤት ሃላፊው እንዲሁም የኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ዋናው ሰው ጃኪ ብሮክ ዶይል እንግሊዛዊ መሆናቸውን እዚህ ላይ ልብ ይለዋል። በእርግጥ በዓለም አትሌቲክስ ውስጥ ይህ ነገር ብርቅ አይደለም። ከዚህ ቀደም ማህበሩን በፕሬዚዳንትነት ሲመሩት የነበሩት ላሚን ዲያክ ከልጃቸው ጀምሮ ሌጋሲያቸውን የሚያስቀጥሉላቸው እንደ ፕሪሞ ኔቢሎ አይነት ጣልያናውያንን በማህበሩ ቁልፍ ቦታዎች አስቀምጠው ነበር። የዓለም አትሌቲክስ በቅርቡ ይፋ ያደረገው ‹‹ኮንቲኔንታል ቱር›› የተባለው ሁለተኛ ትልቅ ውድድር በተለያዩ አስር የዓለማችን ከተሞች እንዲካሄድ ውሳኔ ላይ ሲደረስ አብዛኞቹ የውድድሩ መዳረሻ ከተሞች በአውሮፓ የሚገኙ መሆናቸው ሌላ ጥያቄ የሚጭር ጉዳይ ነው። ከነዚህ ውድድሮች መካከል ዘጠኙ በየትኛው ከተማ እንደሚካሄዱ ተወስኗል። ቶኪዮ፣ ናንጂንግ፣ ኦስትራቫ፣ ሄንግሎ፣ ቱርኩ፣ ኪንግስተን፣ ዤክስፈርቫር፣ ሲሌሲያና ዛግሬብ ውድድሩ የሚካሄድባቸው ከተሞች ናቸው። የኬንያ የስፖርት ካቢኔ ፀሐፊ አሚና ሞሐመድ እንዲሁም የኬንያ አትሌቲክስ ዋና ፀሐፊው ኪሪሚ ካቤሪያ ይህ ውሳኔ በሞናኮ ሲተላለፍ ናይሮቢ አስረኛው ውድድር እንዲሰጣት ጥያቄ ለማቅረብ በስፍራው ነበሩ። ጥያቄያቸው ግን አዎንታዊ ምላሽ እንደማያገኝ የዓለም አትሌቲክስ ተንታኞች ከወዲሁ ግምታቸውን እያስቀመጡ ነው። ምክኒያታቸውም ዓለም አቀፍ ማህበሩ ኢንቨስት የማድረግ ፍላጎት ያለው ዝግጁ በሆነ መሰረተ ልማት ላይ እንጂ እንደ አዲስ በሚገነባ ላይ እንዳልሆነ ነው። አስረኛው ውድድር ምናልባትም ለአፍሪካ መሰጠት ካለበት የደቡብ አፍሪካዋ ፕሪቶሪያ ከተማ ከናይሮቢ በበለጠ ተመራጭ ልትሆን ትችላለች።የዓለም አትሌቲክስ ግን ከሁለቱም የአፍሪካ ከተሞች በተሻለ በአሜሪካዋ ዩጂን ከተማ መዋዕለ ንዋዩን የማፍሰስ ፍላጎት እንዳለው መረጃዎች ያሳያሉ። ምክኒያቱም ዩጂን የ2021 የዓለም ቻምፒዮናን ለማስተናገድ በኦሪገን ግዛት በሐይዋርድ ፊልድ ዩኒቨርሺሲቲ አዲስ ስቴዲየም እያስገነባች ትገኛለች። የዓለም አትሌቲክስ በዓለም ዙሪያ የልማት ስራዎችን ለማከናወን መቶ ሚሊየን ዶላር እየመደበ ይንቀሳቀሳል። አሜሪካ ከዚህ ገንዘብ እስካሁን ተቋዳሽ እንዳልሆነች የሚናገሩ ወገኖች አሁን ላይ ተራው የዩጂን እንደሚሆን ጠንካራ እምነት አላቸው። ሪድገን ‹‹አሜሪካውያን አትሌቶች ከአሜሪካ ጎዳናዎች በተሻለ በአውሮፓ ጎዳናዎች ይታወቃሉ፣ ይህ ሆን ተብሎ የተፈጠረ ባይሆንም አሁን መቀየር አለበት›› ማለታቸው አስረኛው ውድድር ለዩጂን ስለመሰጠቱ ፍንጭ ይሆናል።አዲስ ዘመን ኅዳር 22/2012 ቦጋለ አበበ
https://www.press.et/Ama/?p=23446
807
2ስፖርት
ኢትዮጵያውያን በድልና በክብረወሰን የደመቁበት የቫሌንሲያ ማራቶን
ስፖርት
December 3, 2019
20
‹‹ስፖርታዊ ጨዋነት ለሰላማዊ ውድድር›› በሚል መሪ ቃል ክልላዊ የውይይት መድረክ በሀዋሳ ተካሄደ፡፡ በውይይቱ የደቡብ ክልል መስተዳድር ፕሬዚዳንት አቶ ርዕስቱ ይርዳው፣ የኢፌዴሪ ባህል ፣ ቱረዝምና ስፖርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴታ አቶ ሀብታሙ ሲሳይ፣ የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ኤልያስ ሽኩር፣ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት አቶ ኢሳያስ ጅራ፣ የክልሉ ስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ የሺዋስ ዓለሙና ሌሎች ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ሃላፊዎች መገኘታቸውን የክልሉ ፕሬዚዳንት ጽሕፈት ቤት መረጃ አመልክቷል፡፡ በውይይቱ ከፕሪሚየር ሊግ፣ ከብሔራዊ ሊግና ከፍተኛ ሊግ የመጡ አሰልጣኞች፣ ሥራ አስኪያጆች፣ ቡድን መሪዎች፣ ቴክኒካል ዳይሬክተሮችና የክልሉ ዞኖች ስፖርት ዘርፍ ሃላፊዎች፣ የፀጥታ ዘርፍ ሃላፊዎችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል። በ2012 ዓ.ም በክልሉም ሆነ በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚካሄዱ ስፖርታዊ ውድድሮች የፍቅር፣ የአንድነት፣ የሰላምና የመቻቻል እንዲሆኑ ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ አቶ ርዕስቱ ይርዳው ተናግረዋል። ስፖርታዊ ውድድሮችን የሁከትና የብጥብጥ ማዕከል ለማድረግ የሚፈልጉ አካላትን መታገልና መስመር ማስያዝ ጊዜ የሚሰጥ ጉዳይ አለመሆኑን የተናገሩት አቶ ርዕስቱ ችግር በሚፈጥሩት አካላት ላይ ህጋዊ እርምጃ እንደሚወሰድም አብራርተዋል፡፡ የአካል ጉዳተኛ ስፖርት ባለሙያዎች ስልጠና ለአካል ጉዳተኛ ስፖርት ባለሙያዎች የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና በአዳማ እየተሰጠ ነው። አካል ጉዳተኞች በስፖርታዊ እንቅስቃሴ ተሳታፊና እኩል ተጠቃሚ እንዲሆኑ ምቹ ሁኔታ ሊፈጠርላቸው እንደሚገባ በስፖርት ፖሊሲው የትኩረት አቅጣጫ ላይ በግልፅ ሰፍሯል። ይህን ተግባራዊ ለማድረግ በተለይም የአካል ጉዳተኛ የህብረተሰብ ክፍሎችን በስፖርት ተሳታፊና ተጠቃሚ ለማድረግ በተለያየ ጊዜ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኮች፣ ስልጠናዎች እንዲሁም የውድድር መድረኮች ሲፈጠሩ ቆይተዋል። ትናንት የተጀመረው ስልጠናም በፌዴራል ስፖርት ኮሚሽን የሴቶች ህፃናትና ወጣቶች ዳይሬክቶሬት ከኢትዮጵያ መስማት የተሳናቸው ፌዴሬሽንና ከኢትዮጵያ ፓራሊምፒክ ኮሚቴ ጋር በመተባበር ለፖራሊምፒክና መስማት ለተሳናቸው ስፖርት ባለሙያዎች በስርዓተ ፆታና በአመራርነት ዙሪያ የተዘጋጀ የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና መሆኑን የስፖርት ኮሚሽን መረጃ ያመለክታል፡፡ ስልጠናው ለተከታታይ 3 ቀናት የሚሰጥ ሲሆን ከሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች የተውጣጡ ከ60 በላይ ሙያተኞች ተሳትፈዋል። ስልጠናውን ከሲቪል ሰርቪስ ዩንቨርሲቲ በመጡ ባለሙያዎችና ከኢትዮጵያ መስማት የተሳናቸው ፌዴሬሽን ባለሙያዎች አማካኝነት እየተሰጠም ይገኛል። በሳምንቱ መጨረሻ በተካሄዱ የጎዳና ላይ ውድድሮች ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ድል ቀንቷቸዋል። የዓለም አትሌቲክስ የወርቅ ደረጃ በሰጠውና በስፔኗ ቫሌንሲያ በተካሄደው ውድድር ላይ በሁለቱም ጾታ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ቀዳሚውን ደረጃ በመያዝ አጠናቀዋል። በተለይ በሴቶች ምድብ በተካሄደው ውድድር በጎረቤት አገር ኬንያ አትሌቶች ጋር እስከ 10ኛው ኪሎ ሜትር ድረስ የአንገት ለአንገት ትንቅነቅ በተካሄደበት ውድድር ኢትዮጵውያን ባልሸነፍ ባይነት እስከ መጨረሻ ታግለው ድሉን የግላቸው ማድረግ ችለዋል። በውድድሩ እስከ 15 ኪሎ ሜትር ድረስ ሁለት አትሌቶች ወደ ፊት መውጣት ቢችሉም በማሬ ዲባባና ቪቪያች ቼሮይት መካከል የነበረው አስገራሚ ፉክክር ሩጫውን ከመነሻውም አጓጊ አድርጎታል። ከዚያ በኋላ ባሉት ኪሎ ሜትሮችም ኢትዮጵያ ውያኑ ሮዛ ደረጀ ፣ አዝመራ አብረሃና ብርሃኔ ዲባባ እየተፈራረቁ በመምራት ለኬንያውያኑ ፈታኝ መሆን ችለዋል። በነበረው ጠንካራ ፉክክር አትሌቶቹ የርቀቱን ግማሽ የሸፈኑበት ሰዓትም ፈጣን እንደነበር ለመታዘብ ተችሏል።፡ ከ40ኛው ኪሎ ሜትር በኋላ ሮዛ ደረጃ የበላይነቱን ብትይዝም በኬንያዊቷ አትሌት ብርቱ ፉክክር ገጥሟት ነበር። ሆኖም አዝመራ አብረሃ ተጭና በመሮጧ ምክንያት ሮዛ ወደ ፊት ለመውጣት ስታደርግ የነበረውን ጥረት እንዲሳካ አድርጋለች። በቅርቡ በተካሄደው የለንደን ማራቶን ሦስተኛ ደረጃን ይዛ ያጠናቀቀችው ሮዛም ባገኘችው ዕድል በመጠቀም ርቀቱን በቀዳሚነትና የቦታውን ክብረ ወሰን በማስመዝገብ ጭምር ለማጠናቀቅ ችላለች። የገባችበት ሰዓትም 2:18:30 ሆኖ ሲመዘገብ ቀድሞ ከነበራት ፈጣን ሰዓት በ47 ሰከንዶች የፈጠነ ሆኗል። ሮዛ ያስመዘገበችው ሰዓት በርቀቱ ቀዳሚ ከሆኑ አስር ባለ ፈጣን ሰዓት አትሌቶች መካከል እንድትካተት አስችሏታል። በርቀቱ ለድሉ መገኘት ከፍተኛ አስተዋጽኦ የነበራት የ21 ዓመቷ ወጣት አትሌት አዝመራ አብረሃ ደግሞ ጠባብ በሆነ ልዩነት 2:18:33 የሆነ ሰዓት በማስመዝብ ሁለተኛ በመሆን ውድድሩን ፈጽማለች። የድሉ ባለቤት የሆነችው ሮዛ በስፔን አገር ላይ ሮጣ ስታሸንፍ ይህ የመጀመሪያዋ አይደለም። በዚሁ ዓመት ከወራት በፊት አትሌቷ በባርሴሎና በተካሄደ ግማሽ ማራቶን 1:06:01 የሆነ ሰዓት በማስመዝገብ ቀዳሚ ሆና ማጠናቀቋ ይታወሳል። ሁለተኛ ድሏን ከትናንት በስቲያ ካስመዘገበች በኋላም ‹‹ቫሌንሲያ ከተማውንና ውድድሩን በጣም እወዳቸዋለሁ። ሁለተኛ ድሌን በስፔን በማስመዝገቤ እንዲሁም ሰዓቴን በማሻሻሌ እጅግ ደስተኛ ነኝ›› በማለት አስተያየቷን ሰጥታለች። ውድድሩን ሦስተኛ ሆና የፈፀመችው የ2015 የዓለም ቻምፒዮኗ ብርሃኔ ዲባባ ስትሆን የግል ሰዓቷን ያሻሻለችበትን 2:18:46 አስመዝግባለች። በውድድሩ ጫና ለመፍጠር የሞከረችው ኬንያዊት ቪቪያን ቼሩይት ደግሞ ከብርሃኔ በስድስት ሰከንዶች ዘግይታ አራተኛ ሆና ውድድሩን ፈፅማለች። ሌላኛዎቹ ኢትዮጵያዊያን ዘይነባ ይመር፣ ወርቅነሽ እዴሳ፣ አበባ ገብረመስቀልና ታደለች በቀለ ደግሞ አንዲት ኬንያዊትን ብቻ በጣልቃ ገብታባቸው ከአምስት እስከ ዘጠኝ ያለውን ደረጃ በመያዝ አጠናቀዋል። በወንዶች በኩልም ተካፋይ ከነበሩት አትሌቶች መካከል አራት የሚሆኑት ከዚህ ቀደም በማራቶን ከ2 ሰዓት ከ05 በታች መሮጥ የቻሉ መሆናቸው ከውድድሩ ቀደም ብሎ ከፍተኛ ፉክክር እንደሚካሄድበት ሲጠበቅ ነበር። ንፋሳማ በነበረው የአየር ሁኔታ አትሌቶቹ ከመነሻውም ተበታትነው ይሩጡ እንጂ ኢትዮጵያውያኑና ኬንያውያኑ አራት አትሌቶች ርዕስ በርዕስ ተከታጥለው ጠንካራ ፉክክር ሲያደርጉ ታይተዋል። የውድድሩን ግማሽ ወይም ሃያ አንድ ኪሎ ሜትሩን ለማገባደድ የፈጀባቸው ጊዜ 1:01:58 በመሆኑም የቦታው አዲስ ክብረወሰን እንደሚሰበር ፍንጭ የሰጠ ነበር። በመጨረሻም ክንዴ አጥናው መሪነቱን በማጠናከር አሸናፊ ሊሆን ችሏል። ርቀቱን በቀዳሚነት አጠናቆ ክሩን ለመበጠስ የፈጀበትም 2:03:51 የሆነ ሰዓት ነው። ከሩጫው በኋላም ‹‹አሁን ማራቶንን የማሸነፍ ጊዜው የእኔ መሆኑን አውቅ ነበር። በዝግጅት ወቅት አሸናፊ ለመሆን እሰራ ነበር፤ ይህም እውን ሆኗል›› ሲል ክንዴ አስተያየቱን ሰጥቷል። ቱርካዊው ካን ኪግን በ2:04:16 ሁለተኛ ሆኖ ሲገባ፤ ጉዬ አዶላና አበበ ደገፋ ደግሞ በሰከንዶች ልዩነት ሦስተኛና አራተኛ በመሆን ውድድሩን ፈጽመዋል። አሸናፊ ሞገስ፣ ፀጋዬ ጌታቸውና ልዑል ገብረሥላሴም እስከ አስር ባለው ደረጃ ተከታትለው መግብት የቻሉ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ናቸው። ከማራቶን ውድድሩ ቀደም ብሎ እዚያው ቫሌንሲያ በተካሄደው የአስር ኪሎ ሜትር ውድድር ዩጋዳዊው አትሌት ጆሹአ ቺፕቴጌ የዓለም ክብረወሰን በማሻሻል ማሸነፉ ያልተጠበቀ ነበር። ከሁለት ወራት በፊት በዶሃ የዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮና በአስር ሺ ሜትር ፉክክር ሳይጠበቅ ኢትዮጵያዊው ዮሚፍ ቀጄልቻን አስከትሎ በመግባት ማሸነፍ የቻለው ቺፕቴጊ 26፡38 በሆነ ሰዓት የክብረወሰን ባለቤት ሆኗል። ይህ አትሌት በውድድር ዓመቱ በዓለም አገር አቋራጭ ቻምፒዮና ላይ አሸናፊ እንደነበር ይታወሳል። ከሳምንት በፊት የዓመቱ የዓለም ምርጥ አትሌቶች ሽልማት በሞናኮ ሲካሄድ ቺፕቴጌ ከመጨረሻዎቹ አምስት እጩዎች መካከል አንዱ እንደነበር የሚታወስ ሲሆን አሁን ያሻሻለው ክብረወሰን ምናልባትም ከሳምንት በፊት ቢሆን የዓመቱ ምርጥ አትሌት ሽልማትን የማሸነፍ ከፍተኛ ዕድል ይኖረው ነበር። ቺፕቴጌ ያሻሻለው የዓለም የጎዳና ላይ አስር ኪሎ ሜትር ክብረወሰን እ.ኤ.አ 2010 ላይ በኬንያዊው ሊዮናርድ ፓትሪክ ኮመን የተያዘ ሲሆን ሰዓቱም 26፡44 ነበር። ሮዛ ደረጄ በቫሌንሲያ ማራቶን የቦታውን ክብረወሰን በማሻሻል አሸናፊ ሆናለች፣ አዲስ ዘመን ኅዳር 23/2012 ብርሃን ፈይሳ
https://www.press.et/Ama/?p=23492
856
2ስፖርት
የኢቨስትመንት ህጉ መሻሻል ለቴክኖሎጂ ሽግግርና የሥራ እድል ፈጠራ እንደሚያግዝ ተገለጸ
ሀገር አቀፍ ዜና
December 21, 2020
7
በኃይሉ አበራአዲስ አበባ:- የኢንቨስትመንት ህጉ መሻሻል የቴክኖሎጂ ሽግግሩን በማረጋገጥ፣ የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንትን በማሻሻል፣ የውጭ ምንዛሪ በማስገኘት እና ለበርካታ ዜጎች የሥራ እድል በመፍጠር በኩል ጠቀሜታው የጎላ መሆኑ ተገለጸ። የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ከሰሞኑ ከእስራኤል፣ ከእንግሊዝ እና ከአውስትራሊያ ከመጡ ባለሀብቶች ጋር በተሻሻለው የኢንቨስትመንት ህግና ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ በአዲስ አበባ የግንዛቤ ማስጨበጫ ውይይት አካሂዷል።በኢትዮጵያ የኢንቨስትመንት ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ መኮንን ኃይሉ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደገለጹት፤ መንግሥት የኢንቨስትመንት ህጉን በማሻሻል፣ የግሉን ዘርፍ ሚና በማጎልበት እንዲሁም ኢትዮጵያ ከመቼውም በላይ ለቢዝነስ የተሻለችና ምቹ እንድትሆን ከማድረግ አንጻር በትኩረት እየተሰራ ነው። ይህም የውጭ ባለሀብቶችን ተሳትፎ በማሳደግ ኢንቨስትመንቱን እያሳደገው ይገኛል።በሀገራችን በተካሄደው የፖለቲካ ሪፎርም በሌላኛው ጎኑ የኢኮኖሚ መሻሻሎች ማምጣቱን የገለጹት አቶ መኮንን፤ ኢትዮጵያ ያሻሻለችው የኢንቨስትመንት ሕግ በምስራቅ አፍሪካ ብቻ ሳይሆን በአፍሪካ ደረጃ በኢትዮጵያ ያለው መደላደል ምቹ መሆኑን ግንዛቤ መወሰዱን ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ ለኢንቨስትመንት ምቹ እንድትሆን ከማድረግ አንጻር ባለፉት ዓመታት በጠቅላይ ሚኒስትር ቢሮ አስተባባሪነት እና በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ቢሮ ተሳትፎ ተቋማቶችን ባካተተ መልኩ የንግድና ኢንዱስትሪ፣ የኤሌክትሪክ አገልግሎት፣ የባንክና ሌሎች መሰል ነገሮች ጋር በተያያዘ ኢንቨስትመንቱን የማቅለል ስራዎች እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። አቶ መኮንንን እንደሚሉት፤ አንክታድ በሚባል ዓለም አቀፍ ሪፖርት በቅርቡ ባወጣው መረጃ ኢትዮጵያ የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንትን በመሳብ ከምስራቅ አፍሪካ ግንባር ቀደም ላይ ትገኛለች፤ በአፍሪካ ደረጃ ደግሞ ከግብጽ፣ ከደቡብ አፍሪካ፣ ኮንጎና ሞሮኮ በመቀጠል በአምስተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች። በመሆኑም በሀገራችን የውጭ እና የሀገር ውስጥ ተሳትፎ የሚያሳድግ እና የግል ዘርፉን ሰፋ ባለ መልኩ ኢንቨስት እንዲያደርጉ የሚያስችል የኢንቨስትመንት ሕግ ተሻሽሎ መቅረቡ ሀገራችን የበለጠ የወጭ ባለሀብቶች ትኩረት እንዲኖራት ያስችላታል። ይህ ደግሞ ለዜጎቻችን ሰፊ የሥራ እድል ከመፍጠር አንጻር የጎላ እና የላቀ ሚና ይኖረዋል። እንዲሁም የውጭ ምንዛሪ ግኝት እና የቴክኖሎጂ ሽግግሩንም የተሻለ ያደርገዋል፤ ነው ያሉት።የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች በበዙ ቁጥር ኅብ ረተሰቡ በሚያገኘው አቅርቦት ከትምህርት ቤት፣ ከሆስፒታሎችና መሰል የመሠረተ ልማት እና የማህበራዊ ተቋማት አገልግሎት እያደጉ የሚመጡ በመሆኑ ለዜጎች የሥራ እድል ፈጠራ ባሻገር የማህበራዊ ተቋማት አገልግሎትን በማሳደግም በቀጥታ ማህበረሰቡን ተጠቃሚ እንደሚያደርጉም ነው አቶ መኮንን የገለጹት።በግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኩ ተሳታፊ የነበሩት አቶ አሰፋ፣ መንገሻ በኢትዮጵያ ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ በፀሐይ ኃይል ውሃ የሚያሞቁ መሳሪያዎችን የሚያመርት ፋብሪካ በሰንዳፋ የኢንዱስትሪ ዞን ውስጥ ያቋቋሙ ባለሃብት ናቸው። በእስራኤል ሀገር ከ30 ዓመት በላይ መኖራቸውን የገለጹት አቶ አሰፋ እንደሚሉት፤ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሸን ኢንቨስትመንት ከማሻሻል አንጻር ጥሩ እንቅስቃሴ ላይ መሆኑን ነገር ግን ከዋና ኮሚሽኑ ከወጣ በኋላ ያለው የቢሮክራሲ ሁኔታ በጣም መሻሻል ይኖርበታል።አሁን ያለው የኢንቨስትመንት ህግ መሻሻልን ተከትሎ የኢንቨስትመንት የአቀባበል ሁኔታውን ማፋጠን ከተቻለ፣ እስራኤል አነስተኛ አገር ብትሆንም የቴክኖሎጂ ባህር እንደመሆኗ በእርሻ፣ በሶላር እና ሌሎችም በርካታ ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎች ከእስራኤል ወደ ኢትዮጵያ ሊመጡ እንደሚችሉ ነው አቶ አሰፋ የተናገሩት። በፀሀይ ኃይል ውሃ የሚያሞቁ መሳሪያ ማምረቻው ወደ ሀገራችን ቢገባ ያለውን ጠቀሜታና አዋጭነት በማሰብ እና የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ለማበርከት በሚል ቴክኖሎጂውን ማቋቋማቸውን የገለጹት አቶ አሰፋ፤ ፋብሪካውን ካቋቋሙ ስድስት ዓመት እንደሆነውና ምርት ማምረት ከጀመረ አራት ዓመት እንደሆነው ተናግረዋል። ከብዙ ድካምና ውጣውረድ በኋላም በግል መኖሪያ ቤቶች በፔንሲዮኖች፣ በአፓርትመንቶች፣ በሆቴሎች እና ጤናጣቢያ ላይ ሁሉ መግጠም መጀመራቸውን ገልጸዋል። አቶ አሰፋ፣ በእስራኤል ሀገር ሲኖሩ በነበረበት ቅቡጽ በሚባል ኩሚዩናል በሚኖርበት አካባቢ የእርሻ ሂደቱን ታዝበዋል። በሦስት ወር እና በአራት ወር ውስጥ የተለያየየምርት አይነት ይመረትበታል ብለዋል። በሦስት ወር እና በአራት ወር ውስጥ መሬቱ በተለያየ የምርት አይነት ይሸፈናል። ብዙ ሄክታር መሬት በበቆሎ ተሸፍኖ ይታያል፤ ከተወሰነ ጊዜ በኋላ ደግሞ ያንን የዚያ ምርት ተሰብስቦ መሬቱን አለስልሰው በዚያ በቆላ መሬት ላይ የተንጣለለ የስንዴ ማሳ በአጭር ጊዜ ውስጥ ሲያሰሩ ይታያል፤ ከትንሽ ቆይታ በኋላ ደግሞ አትክልቶች ሲሰራበት መመልከታቸውን ገልጸዋል። ይሄንን ቴክኖሎጂ በሀገራችን ተግባራዊ በማድረግ ኢትዮጵያን በይበልጥ የአፍሪካ የዳቦ ቅርጫት ማድረግ ይቻላል፤ የስንዴ ቋት መሆን እንችላለን። ቴክኖሎጂውን ደግሞ ለመቀበል እና ወደ ፊት ለማራመድ በሀገራችን በእርሻ ኢንጂነሪንግ የተማሩ ሰዎች በኩል ቴክኖሎጂውን በማስፋፋት ለሀገራችን ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታውን በማገናዘብ ከራሳችን አልፈን ለሌላው ሀገር ማቅረብ የሚቻልበትን ሰፊ እድል አለ ብለዋል። በሀገራችን ባሌና አርሲ የስንዴ ሜዳ መሆናቸው እንደሚታወቀው ሁሉ በወሎ እና አፋር ድንበር ላይ ከፍተኛ የስንዴ ምርት ማምረት ይቻላል። በሱማሌ ክልል ገናሌና ሸበሌ ወንዞች አሉ ሜዳው የሰጠ ነው ሰላም እና ደህንነት እስካለ ድረስ ከራሳችን አልፈን ምርቱን ሽጠን ለሌላም ሀገር መቀለብ የሚያስችል አቅም አለ። ኢትዮጵያ ለኢንቨስትመንት ምቹ አይደለችም የሚለውን የውጪ ኢንቨስተሮች እይታ ለመቀየር ኢትዮጵያውያን የሀገራችንን ጥቅም በሚጠብቅ ሁኔታ ከኢንቨስትመንት ኮሚሽን ጋር በግልጽ በመወያየት እና ግብረመልስ መስጠት ተገቢ መሆኑን ጠቁመዋል። የምርት አይነት ይመረትበታል ብለዋል። በሦስት ወር እና በአራት ወር ውስጥ መሬቱ በተለያየ የምርት አይነት ይሸፈናል። ብዙ ሄክታር መሬት በበቆሎ ተሸፍኖ ይታያል፤ ከተወሰነ ጊዜ በኋላ ደግሞ ያንን የዚያ ምርት ተሰብስቦ መሬቱን አለስልሰው በዚያ በቆላ መሬት ላይ የተንጣለለ የስንዴ ማሳ በአጭር ጊዜ ውስጥ ሲያሰሩ ይታያል፤ ከትንሽ ቆይታ በኋላ ደግሞ አትክልቶች ሲሰራበት መመልከታቸውን ገልጸዋል። ይሄንን ቴክኖሎጂ በሀገራችን ተግባራዊ በማድረግ ኢትዮጵያን በይበልጥ የአፍሪካ የዳቦ ቅርጫት ማድረግ ይቻላል፤ የስንዴ ቋት መሆን እንችላለን። ቴክኖሎጂውን ደግሞ ለመቀበል እና ወደ ፊት ለማራመድ በሀገራችን በእርሻ ኢንጂነሪንግ የተማሩ ሰዎች በኩል ቴክኖሎጂውን በማስፋፋት ለሀገራችን ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታውን በማገናዘብ ከራሳችን አልፈን ለሌላው ሀገር ማቅረብ የሚቻልበትን ሰፊ እድል አለ ብለዋል። በሀገራችን ባሌና አርሲ የስንዴ ሜዳ መሆናቸው እንደሚታወቀው ሁሉ በወሎ እና አፋር ድንበር ላይ ከፍተኛ የስንዴ ምርት ማምረት ይቻላል። በሱማሌ ክልል ገናሌና ሸበሌ ወንዞች አሉ ሜዳው የሰጠ ነው ሰላም እና ደህንነት እስካለ ድረስ ከራሳችን አልፈን ምርቱን ሽጠን ለሌላም ሀገር መቀለብ የሚያስችል አቅም አለ። ኢትዮጵያ ለኢንቨስትመንት ምቹ አይደለችም የሚለውን የውጪ ኢንቨስተሮች እይታ ለመቀየር ኢትዮጵያውያን የሀገራችንን ጥቅም በሚጠብቅ ሁኔታ ከኢንቨስትመንት ኮሚሽን ጋር በግልጽ በመወያየት እና ግብረመልስ መስጠት ተገቢ መሆኑን ጠቁመዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 12/2013
https://www.press.et/Ama/?p=37781
771
0ሀገር አቀፍ ዜና
ጁንታው ለዘረፋ ያሰማራቸውን ወንጀለኞች በቁጥጥር ስር የማዋል ተግባር ተጠናክሮ መቀጠሉ ተገለጸ
ሀገር አቀፍ ዜና
December 21, 2020
14
በጋዜጣው ሪፖርተርአዲስ አበባ፡- የህወሓት ጁንታ ከማረሚያ ቤት በመልቀቅ ለዘረፋ ያሰማራቸውን ወንጀለኞች በቁጥጥር ስር የማዋሉ ተግባር ተጠናክሮ መቀጠሉን የፌዴራል ፖሊስ አስታወቀ። በፌዴራል ፖሊስ የወንጀል መከላከል ዘርፍ ኃላፊ ምክትል ኮሚሽነር መላኩ ፋንታ ዛሬ በመቀሌ ከተማ ለመገናኛ ብዙኃን መግለጫ ሰጥተዋል።ኢዜአ እንደዘገበው፤ ምክትል ኮሚሽነር መካሉ እንደገለጹት፤ ጁንታው ከተሞችን ለቆ ከመሸሹ በፊት በማረሚያ ቤት የነበሩ ወንጀለኞችን መሳሪያ አስታጥቆ በመልቀቅ በከተሞች አካባቢ ዝርፊያ እንዲፈጽሙ አድርጓል። እነዚህ ወንጀሎችም የመንግሥት ተቋማትን ንብረት ጭምር ዘርፈዋል። የፌዴራል ፖሊስ ከኅብረተሰቡ ጋር በመቀናጀት ወንጀለኞቹን በቁጥጥር ስር የማዋሉን ሥራ አጠናክሮ መቀጠሉንም የገለጹት ምክትል ኮሚሽነሩ፤ ወንጀለኞቹ የታጠቁትን የጦር መሳሪያዎች የማስፈታቱ ተግባር እየተከናወነ መሆኑንም ተናግረዋል። በተጨማሪም ህገ-ወጡ የህወሓት ጁንታ በመንግሥት ተቋማት ያሉ ሰነዶችንና ሰነድ የያዙ ኮምፒውተሮችን አቃጥሎ መሸሸኑም ገልጸዋል።ይህም ቡድኑ ከራሱ ስልጣን ውጭ ለህዝብ ምንም አይነት ደንታ የሌለው መሆኑን የሚያሳይ እንደሆነ በመጠቆምም፤ የአካባቢው ማኅበረሰብ የፌዴራል ፖሊስ እያከናወነ ያለውን ተግባር በመደገፍ ረገድ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑንም ምክትል ኮሚሽነሩ ተናግረዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 12/2013
https://www.press.et/Ama/?p=37783
136
0ሀገር አቀፍ ዜና
ኦነግ ሸኔን በመደምሰሱ ሂደት የህዝቡ ድጋፍ ትልቅ ድርሻ እንደነበረው ተገለጸ
ሀገር አቀፍ ዜና
December 21, 2020
25
ዋቅሹም ፍቃዱ አዲስ አበባ፡- በሰላም ለመታገል ወደ አገር ውስጥ ከገባ በኋላ ወደ ትጥቅ ትግል የተመለሰው ኦነግ ሸኔን በመደምሰስ ሂደት ህዝቡ ከጸጥታ አካሉ ጎን ሆኖ በአሰሳ እያገዘ፤ በሰላማዊ ሰልፍም ቡድኑን እያወገዘ መሆኑ ተገለጸ።ከመስከረም 2013 ዓ.ም ጀምሮ እስካሁን በተወሰደው እርምጃ 846 የኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች ሲደመሰሱ፤ ከ3ሺህ 700 በላይ ተጠርጣሪዎች በህግ ቁጥጥር ስር ሆነው ጉዳያቸው እየተጣራ መሆኑንም የኦሮሚያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጄኔራል አራርሳ መርዳሳ ተናግረዋል። ኮሚሽነር ጄኔራል አራርሳ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደተናገሩት፤ የኦነግ ሸኔ ቡድን ኃይሉን ለማጠናከር በክልሉ ጠረፋማ አካባቢዎች ተደብቆ የጥፋት ኃይሎችን በመመልመል ሲያሰለጥን፤ እንዲሁም በህወሓት ጁንታ ኃይል የሎጀስቲክ ድጋፍ ተደርጎላቸው በትግራይ ክልል ጭምር በመሄድ ስልጠና ሲወስድ ነበር። አሁን ላይ ግን ጁንታው በመደምሰሱ የቡድኑ ኃይል እየተዳከመ ከመሆኑ በተጨማሪ፤ ባለፉት ሦስት ወራት የክልሉ መንግሥት ህዝቡን በጎኑ በማሰለፍ በወሰደው እርምጃ 413 የኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች እጅ ባለመስጠታቸው ሲገደሉ፤ እጅ የሰጡና የተያዙ ደግሞ 433 ናቸው። በዚህም በጥቅሉ 846 የኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች ተደምስሰዋል።የኦነግ ሸኔ ቡድን እጅግ ጨካኝ ከመሆኑ የተነሳ ስልቱን በመቀያየር አንዳንድ አካባቢዎች እንደ ሆሮ ጉዱሩ ወለጋ በብሔር ላይ ያነጣጠሩ ጥቃት ይፈጽማል፤ በምስራቅ ኦሮሚያ አንዳንድ አካባቢዎች ደግሞ ሀይማኖታዊ መልክ ያለው ጥቃት በመፈጸም አገርን ለማተራመስ ይጥራል። በዚህ መልኩ እስካሁን መንግሥት ሹመኞችና በንጹኃን ዜጎች ላይ በወሰዳቸው እርምጃዎችም ከ500 በላይ ንጹኃን ህይወታቸውን አጥተዋል።አሁን ግን አንዳንድ እንደ ቄለም ወለጋ ያሉ አካባቢዎች ህዝቡ ወጥቶ አሰሳ እያደረገ፣ በሠላማዊ ሰልፍም እያወገዘ በመሆኑ እንደ ከዚህ በፊቱ ጉልበቱን አጠናክሮ የጥፋት ስራውን መፈጸም አይችልም። እንደከዚህ በፊቱም መንገድ ዝጉ እንዲ አድርጉ የሚሉ ትዕዛዞችን ህዝቡ እየተቀበለ አይደለም። የክልሉ ጸጥታ አካላትም ቡድኑ የሚንቀሳቀስበት አካባቢን ተቆጣጥረው እንዳሉ፤ እና ህዝቡም የጀመረውን ድጋፍ አጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባው ነው ኮሚሽነር ጄኔራል አራርሳ የተናገሩት።እንደ ኦነግ ሸኔ ቀጥታ ጠመንጃ አንግበው ህዝቡን የሚጨርሱና ተኩሰው ባይገሉም ኦነግ ሸኔን በቁሳቁስ፣ በገንዘብና በሞራል የሚደግፉ እንዲሁም ኦነግ ሸኔ የሚፈጽመውን ጥቃትና ጥፋት ወደ መንግሥት በማዞር በተሳሳተ መረጃ ህዝቡን የሚያደናግሩና መንግሥትን በተለይ የጸጥታ ኃይሉን ለማጠልሸት በኦነግ ሸኔ የተደራጁ በርካታ የሶሻል ሚዲያ ሠራዊት ጭምር መኖራቸውን የጠቆሙት ኮሚሽነር ጄኔራል አራርሳ፤ በዚህ መሰል ጥፋት የተሰለፉ ከ3ሺህ 700 በላይ ተጠርጣሪዎች በህግ ቁጥጥር ስር ሆነው ጉዳያቸው እየተጣራ መሆኑን ተናግረዋል። በቀጣይም ከመንግሥት መስሪያ ቤት ሳይቀር ሰፊ የማጥራት ስራ ለመስራት በቅርቡ እንደሚጀመር ተናግረዋል። ከአርቲስት ሃጫሉ ሁንዴሳ ግድያ ጋር ተያይዘው አገሪቱን የብጥብጥ ቀጠና ለማድረግ ሲንቀሳቀሱ የነበሩት 1ሺህ 700 በላይ በተለያዩ የስልጣን እርከን ላይ በነበሩት አመራሮች ላይ የተወሰደው እርምጃ አሁን በኦነግ ሸኔ ላይ እየተወሰደ ላለው እርምጃ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን የገለጹት ኮሚሽነር አራርሳ፤ በወቅቱ የተተኩ አዳዲስ አመራሮች በቁርጠኝነት የሰሩት ሥራ ኦነግ ሸኔን ለማድከም ትልቅ አስተዋፅዖ እንደነበረው ገልጸዋል። ህዝቡም ቡድኑን አሳልፎ በመስጠትና ለጸጥታ አካላት መረጃ በማቀበል ጉልህ ሚና መጫወቱንም አብራርተዋል።እንደ ኮሚሽነር ጄኔራል አራርሳ ገለጻ፤ በዓለም ተሞክሮ ሽምቅ ተዋጊ ኃይል በአንድ ቦታ ሆኖ በግንባር የሚዋጋ ኃይል ባለመሆኑ በአንድ ጀምበር ማጥፋት ሊያዳግት ይችላል። ሆኖም ሁለት መሠረታዊ ስልቶችን በመጠቀም በድኑን ከነ ዓላማው መቅበር ይቻላል። አንደኛው፣ በህዝቡ ላይ በመስራት የጥፋት ቡድኑን ብቻውን በማስቀረት ተስፋ ቆርጦ እንዲጠፋ ማድረግ ወሳኝ ስልትና ትልቁ የመንግሥት የቤት ስራ ሲሆን፤ ሁለተኛው ደግሞ ሁሉንም የድጋፍ በሮችን በመዝጋት የሎጅስቲክ ረሃብተኛ፣ ከዓለም የተነጠለ፣ ከህዝብ የተገለለ በማድረግ ይህን የሽምቅ ተዋጊ ቡድንን ከስራ ውጭ ማድረግ ይቻላል። በዚህ መልኩም እየተሰራ ነው።አዲስ ዘመን ታህሳስ 12 ቀን 2013  ዓ.ም
https://www.press.et/Ama/?p=37765
457
0ሀገር አቀፍ ዜና
ባንኩ እአአ 2020 መጨረሻ ከግብር በፊት ከግማሽ ቢሊዮን ብር በላይ ማትረፉን ገለጸ
ሀገር አቀፍ ዜና
December 21, 2020
84
ሞገስ ጸጋዬአዲስ አበባ፡- እየተጠናቀቀ ባለው የፈረንጆች ዓመት መጨረሻ ከግብር በፊት ከግማሽ ቢሊዮን ብር በላይ ማትረፉን፤ ይሄም ከባለፈው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር በበጀት ዓመቱ የትርፍ መጠኑ የ6ነጥብ9 በመቶ ቅናሽ ማሳየቱን ቡና ኢንተርናሽናል ባንክ አስታወቀ። ባንኩ ለተለያዩ ሀገራዊ ልማቶች 19 ሚሊየን ብር ድጋፍ ያደረገ ማድረጉንም ተገልጿል።የባንኩ የዳይሬክተሮች ቦርድ ሊቀመንበር ዶክተር ሰውአለ አባተ፣ ትናንት በአዲስ አበባ ባካሄደው የባንኩ ባለአክሲዮኖች 11ኛ መደበኛ እና 4ኛ ድንገተኛ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ የበጀት ዓመቱን ሪፖርት ለባለ አክሲዮኖች አቅርበዋል። በወቅቱም እንደተናገሩት፤ የበጀት ዓመቱ ለባንኩ ዘርፍ በርካታ እንቅፋቶች የነበሩበት ቢሆንም፤ እነዚህን ችግሮች በመቋቋም እአአ በ2020 ከታክስ በፊት የ582 ነጥብ 04 ሚሊዮን ብር ትርፍ ማግኘት ተችሏል።እንደ ዶክተር ሰውአለ ገለጻ፤ ባንኩ የውጭ ንግዱ 111 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ያስገኘ ሲሆን፤ ከውጭ ሀገር በሀዋላ እና በስዊፍት የተላከ ደግሞ የ28ነጥብ4 ሚሊዮን ዶላር አስገኝቷል። የባንኩ ሀብትም በበጀት ዓመቱ የ4ነጥብ37 ቢሊዮን ብር እድገት በማሳየት ጠቅላላ ሃብቱን ወደ 18ነጥብ87 ቢሊዮን ብር አሳድጓል።ዶክተር ሰውአለ እንደሚሉት፤ በተጠቀሰው በጀት ዓመት የተቀማጭ ገንዘብ መጠኑን በ3ነጥብ29 ቢሊዮን ብር በማሳደግ የባንኩን አጠቃላይ የተቀማጭ ገንዘብ መጠን 13ነጥብ88 ቢሊዮን ደርሷል። ከአጠቃላይ የባንኩ ተቀማጭ ገንዘብ ውስጥ የተንቀሳቃሽ ሂሳብ የ19 በመቶ ድርሻን ሲይዝ፤ በአንፃሩ የጊዜ ገደብ ተቀማጭ ደግሞ የ5 በመቶ ድርሻ ነበረው። ይህም የባንኩን አብዛኛው ተቀማጭ አስተማማኝ እንዲሆን አድርጎታል። ባንኩ በዓመቱ ውስጥ ለተለያዩ ኢኮኖሚያዊ ዘርፎች 3ነጥብ29 ቢሊዮን ብር ብድር የሠጠ ሲሆን፤ ይህም ባንኩ አጠቃላይ የሰጠውን ብድር በ40 በመቶ አሳድጎታል።ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር ባንኩ ትርፍ የብር 42ነጥብ99 ሚሊዮን ወይንም የ6ነጥብ9 በመቶ ቅናሽ ማሳየቱን የገለጹት ሊቀመንበሩ፤ ለዚህ ደግሞ የኮቪድ 19 ወረርሽኝ ዓለም አቀፍ የንግድ እንቅስቃሴውን ማቀዛቀዙ ግንባር ቀደምትነት ሚና እንዳለው ገልጸዋል። በአገሪቱ በአንዳንድ ክልሎች ተከስቶ የነበረው ማህበራዊና ፖለቲካዊ አለመረጋጋት ኢኮኖሚውን በጤናማ መንገድ እንዳይጓዝ በማድረግ በወጭና በገቢ ንግዱ ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ ማሳደሩ ባንኩ በበጀት ዓመቱ ለማሳካት ያሰበውን የትርፍ መጠን ባሰበው ልክ እንዳይሆን ማድረጉንም ጠቁመዋል።ባንኩ በ2030 በሀገራችን ሦስት ግንባር ቀደምና ተመራጭ ባንኮች መካከል አንዱ መሆንን አላማ አድርጎ ተነስቷል ያሉት ሊቀመንበሩ፤ የቡና ባንክ ማህበራዊ ኃላፊነቱን በመወጣት እንደ ‹‹ገበታ ለሀገር›› የመሳሰሉ ሀገራዊ የልማት እና ኮቪድ 19 ወረርሽኝ መከላከል የሚሆን ድጋፍ በማድረግ በድምሩ 19 ሚሊዮን ብር ድጋፍ ማድረጉን ተናግረዋል። ይህ ማህበራዊ ኃላፊነትን መወጣት ቀጣይነት እንደሚኖረው በመጥቀስም፤ 37 አዲስ ቅርንጫፎችን በመክፈት ቁጥሩን ወደ 242 አሳድጎ በመስራት በበጀት ዓመቱ ብቻ የተቀማጭ ሂሳብ የደንበኞችን ቁጥር በ268 ሺህ70 በማሳደግ የደንበኞችን ቁጥር 809 ሺህ 493 ማድረስ መቻሉ ዓመልክተዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 12/2013
https://www.press.et/Ama/?p=37782
343
0ሀገር አቀፍ ዜና
በመቀሌ ለነዋሪዎች ሰብዓዊ ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ገለጸ
ሀገር አቀፍ ዜና
December 21, 2020
13
በጋዜጣው ሪፖርተርአዲስ አበባ፡- መቀሌ ከተማ የደረሰው የእለት ደራሽ የምግብና የቁሳቁስ ድጋፍ ለዜጎች በመድረስ ላይ መሆኑን የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ገለጸ። እንደ ኢዚአ ዘገባ፣ በመቀሌ ከተማ ለ80 ሺህ ዜጎች ሰብዓዊ ድጋፍ ለማድረስ እየተሠራ መሆኑን የጊዜያዊ አስተዳደሩ የሰብዓዊ ድጋፍ አስተባባሪ ወይዘሮ ሳባ ገብረማርያም ገልጸዋል። የፌዴራል መንግሥት በክልሉ የምግብ፣ መድኃኒትና ሌሎች ቁሳቁሶችን በማቅረብ ላይ መሆኑን እና ጊዜያዊ አስተዳደሩም ለህዝቡ ተደራሽ እያደረገ እንደሚገኝም ነው ያስረዱት።እንደ ወይዘሮ ሳባ ገለጻ፤ አሁን ላይ ከ100 ሺህ ኩንታል በላይ እህል በመጋዘን ይገኛል። ይሄም እርዳታና ድጋፍ ለሚሹ ዜጎች በመከፋፈል ላይ ነው። በዚህም በመቀሌ ከተማ ብቻ ለ80 ሺህ ዜጎች ድጋፉን ተደራሽ ለማድረግ እየተሠራ ነው። ሰብዓዊ ድጋፉ በመቀሌ ብቻ ሳይሆን በክልሉ የተለያዩ ከተሞችና ወረዳዎች በመዳረስ ላይም ይገኛል።በርካታ የመቀሌ ከተማ ነዋሪዎችም በችግር ላይ ያሉ ወገኖችን በመደገፍ ላሳዩት ተነሳሽነት ምስጋና ያቀረቡት ወይዘሮ ሳባ፤ ከፌዴራሉ መንግሥት የተላከውን ከ16 ሚሊዮን ብር በላይ ወጭ የተደረገበት መድሃኒትም ማሰራጨት መቻሉን ገልጸዋል። ከፌዴራል መንግሥቱ በተጨማሪ ዓለም አቀፍ እና አገር በቀል የበጎ አድራጎት ድርጅቶችም ሰብዓዊ ድጋፍ እያደረጉ መሆኑን ተናግ ረዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 12/2013
https://www.press.et/Ama/?p=37784
152
0ሀገር አቀፍ ዜና
የአንበጣ መንጋ ወደ ሰብል አብቃይ አካባቢዎች እንዳይዛመት እየተሠራ መሆኑን ተነገረ
ሀገር አቀፍ ዜና
December 21, 2020
14
ወርቅነሽ ደምሰውአዲስ አበባ፡- እንደ አገር በስፋት ተከስቶ የነበረውና አሁን ላይ በሱማሌ ክልል ብቻ ቀርቶ የነበረ የአንበጣ መንጋ ወደ ኦሮሚያና ደቡብ ክልል ሰብል አብቃይ አካባቢዎች እንዳይዛመት የመከላከል ስራው ተጠናክሮ መቀጠሉን የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ። በግብርና ሚኒስቴር የእጽዋት ጥበቃ ዳይሬክተር አቶ በላይነህ ንጉሴ በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደተናገሩት፤ በሱማሌ ክልል ላይ ብቻ ተወስኖ የነበረው የአንበጣ መንጋ አሁን ላይ ወደ ኦሮሚያና ደቡብ ክልሎች በመስፋት ላይ ሲሆን፤ መንጋው ወደነዚሁ አካባቢዎች ሄዶ በደረሱ ሰብሎች ጉዳት እንዳያስከትል የኬሚካል ርጭት ተጠናክሮ እየተካሄደ ነው።እስካሁን በሱማሌ ክልል የነበረው የአንበጣ መንጋ በኩኩባነት ደረጃ ያለው ቢሆንም አሁን ላይ አድማሱን እያሰፋ በመብረር ላይ ስለሆነ በቀላሉ መዛመት የሚችል መሆኑን የጠቆሙት ዳይሬክተሩ፤ ከታህሳስ ወር ጀምሮ በከፍተኛ ደረጃ ከሱማሊያ አካባቢ ያደገው የአንበጣ መንጋ በስፋት ወደ ሀገራችን እየገባ በመሆኑ፤ የመከላከል ሥራም በተጠናከረ ሁኔታ እየተሰራ መሆኑን አመላክተዋል። በሱማሌ ክልል የመከላከል ሥራ እየተሰራ ቢሆንም በመኪና ሆነ በሰው ኃይል በመግባት አንበጣውን መከላከል በማይቻልባቸው አካባቢዎች መንጋው በቀላሉ የመራባት ዕድል በማግኘቱ እና በሱማሌ ላንድና በፑትላንድ የሚደረገው የመከላከል ስራም እምብዛም በመሆኑ በቀጣይ በቂ መከላከል ካልተደረገ ሰብል አብቃይ ወደ ሆኑ አካባቢዎች በቀላሉ የመዛመት ዕድሉ አለ። እስካሁን 13 አውሮፕላኖች በመጠቀም የአሰሳ፣ የኬሚካል ርጭት ስራዎች እንዲሰሩ የተደረገ መሆኑን የሚናገሩት ዳይሬክተሩ፤ ባለፈው ከተከሰተው የአንበጣ መንጋ ዝግጅት አንጻር የአሁን ዝግጅት በኬሚካል አቅርቦትም ሆነ በርጭት ረገድ በቂ ዝግጅት መደረጉን ገልጸዋል። የዓለም ምግብ ድርጅት(ፋኦ) ኬሚካልንና አውሮፕላኖችን በማቅረብ ከፍተኛ እገዛ በማድረጉ ርጭቱ በሰፊው እየተካሄደ መሆኑን ገልጸዋል።አሁን ላይ በሱማሌ ክልል አምስት ዞኖች ላይ በጀረር፣ በዶሎ ፣ በሸበሌ፣ በቆራሄ ና በአፍዴር ያደገው አንበጣ በብዛት ጎልቶ የሚታይባቸው ቦታዎች በመሆናቸው ከፍተኛ ሁኔታ ርጭት እየተካሄደ ነው ያሉት ዳይሬክተሩ፤ በተመሳሳይ በኦሮሚያ ክልል ከባሌ ሮቤ ላይ ተነስቶ ግኒርና ራይቱን ወደመሰሉ ቦታዎች፤ እንዲሁም በደቡብ በኦሮሚያና በሐመር አካባቢ ከአርባ ምንጭ በመነሳት ርጭት እየተካሄደ ይገኛል። አሁን ባለው ሁኔታ ቁጥጥሩ በተጠናከረ ሁኔታ እየተካሄደ ስለሆነ እስካሁን ከአቅም በላይ የሆነ የአንበጣ መንጋ የለም ብለዋል ።ከፌዴራል ጀምሮ ከክልሎች አርሶ አደሮችና አርብቶ አደሮች ጋር የተዘረጋው ቅንጅታዊ አሰራር ውጤት እያመጣ ነው ያሉት ዳይሬክተሩ፤ በተለይ አርሶ አደሩ አንበጣ ያለበትን መረጃዎች በመስጠትና በህብረት በመስራት የሚያደርገው ጥረት መንጋውንለመከላከል እንዳስቻለ አመልክተዋል።እንደ ዳይሬክተሩ ገለጻ፤ በሱማሌ ላንድ ላይ የአንበጣ መንጋን ለመከላከል እየተደረገ ያለው ጥረት አመርቂ ባለመሆኑ መንጋው በከፍተኛ ደረጃ ወደ ኢትዮጵያ ይገባል የሚል ስጋት ያለ ሲሆን፤ በዚህ በኩል የሚገባ ከሆነ ደግሞ ከዚህ በተሻለ ተጠናክሮ ካልተሰራ የንፋሱን አቅጣጫ ተከትሎ ወደ ደቡብ ሄዶ የመስፋፋት ሁኔታ ይኖራል። ምንም እንኳን ከሱማሌ ላንድ በኩል የሚመጣው የመንጋ መጠን ከፍተኛ እንደሚሆን ቢገመትም ኢትዮጵያ የመከላከል አቅሟን በማሳደጓና በቂ ቅድመ ዘግጅት በማድረጓ መንጋው ወደ ሀገር ውስጥ ቢገባም ከቁጥጥር ውጪ ይሆናል የሚል ግምት እንዳሌለ ያብራራሉ።የአንበጣ መንጋው ርጭቱ እየተካሄደ ያለው በቆላማ በሱማሌ ክልል አካባቢ ሲሆን፤ በሳር ላይና በግጦሽ ላይ ጉዳት እያደረሰ ቢሆንም እስካሁን ባለው ሁኔታ አካባቢ ላይ ሰብል ባለመኖሩ ጉዳትአልደረስም ያሉት ዳይሬክተሩ፤ ወደፊት የመስኖ ሰብሎች እየተመረቱ ያሉ ሲሆን፤ በተለይ ወደ ጎዴና ኦሮሚያ ውስጥ ራይቱ አካባቢ አሁን ላይ ሰብሎች በመዝራታቸው በተለይ ከቆላ ስንዴ ጋር ተያይዞ እየለሙ ያለበት ሁኔታ በመኖሩ በተቻለ አቅም ትኩረት በማድረግ እዚያ አካባቢ ሊያርፍ የሚችለውን የአንበጣ መንጋን ለመከላከል ጥረት እየተደረገ እንደሚገኝ አቶ በላይነህ ጠቁመዋል።በቀጣይም በፌዴራል፣ በክልሎችና መንግሥታዊ ባልሆኑ ድርጅቶች በኩል የተቀናጀ አሠራር በመዘርጋት መንጋው ጉዳት እንዳያስከትል የተናበበ ሥራ እንደሚሰራ የጠቆሙት ዳይሬክተሩ፤ መንጋው በመስኖ የሚለሙ ቦታዎች ላይ ጉዳት እንዳያደርስ በትኩረት እንደሚሰራ ጠቁመዋል። በድንበር በኩል ገብቶ የከፋ ጉዳት እንዳያስከትልም ከሶማሊያና ከኬኒያ መንግሥታት ጋር የተናበበ ሥራ እየተሰራ መሆኑን ዳይሬክተሩ አስረድተዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 12/2013
https://www.press.et/Ama/?p=37794
487
0ሀገር አቀፍ ዜና
በህግ ማስከበር ዘመቻው ግዳጃቸውን በጀግንነት ለፈጸሙ የሰራዊቱ አባላት እውቅና እንደሚሰጥ ተገለጸ
ሀገር አቀፍ ዜና
December 22, 2020
38
– የክልሎች አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑ ተገልጿል ሃይማኖት ከበደአዲስ አበባ:- በትግራይ ክልል በተደረገው የህግ ማስከበር ዘመቻ ግዳጃቸውን በጀግንነት ለፈጸሙ የሰራዊቱ አባላት በየደረጃው እውቅና እንደሚሰጥ የጦር ሃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹሙ ጄኔራል ብርሃኑ ጁላ ገለጹ። የክልል ልዩ ሃይሎች በየቦታው የነበራቸው አስተዋጽ ከፍተኛ መሆኑንም አስታውቀዋል። ጠቅላይ ኤታማዦር ሹሙ ጄኔራል ብርሃኑ ጁላ ትናንት ከኦቢኤን ጋር በነበራቸው ቆይታ ላይ እንዳስታወቁት፤ በዚህ የህግ ማስከበር ላይ የተሳተፉ የሰራዊቱ አባላት እንደየደረጃቸው የተለያዩ ሽልማቶችን የሚሸለሙ ይሆናል። ሜዳሊያ እና ማዕረግ የሚሸለሙ እንዲሁም ሌሎች የዕውቅና አሰጣጥ ሥነ ስርአቶችም የሚሰጡ ይሆናል።“ጀግኖች ይሸለማሉ ታሪካቸውም ተፅፎ ለትውልድ ይቀመጣል” ያሉት ጠቅላይ ኤታማዦር ሹሙ፤ እነዚህ ጀግኖች የሀገር ቅርስ ስለሆኑ እነሱን ማስተዋወቅ፣ መጠበቅና ማበረታታት ተገቢ ነው ሲሉም አስታውቀዋል።እንደ ጠቅላይ ኤታማዦር ሹሙ ማብራሪያ፤ በዚህ የህግ ማስከበር ስራ ላይ የህዝቡ ተሳትፎ ከፍተኛ የነበረ ሲሆን፤ የአማራ ክልል፣ የኦሮሚያ ክልል፣ የአፋር፣ የሶማሌ እና ሌሎችም ክልሎች በተለያዩ መንገዶች ያደረጉት አስተዋጽኦ ከፍተኛ እንደነበር አብራርተዋል።የቆሰሉ የሰራዊቱ አባላት በአብዛኛው በአማራ ክልል ሆስፒታሎች ሲታከሙ መቆየታቸውን የገለጹት ጄኔራል ብርሃኑ፤ በክልሉ ያሉ ሆስፒታሎችና የህክምና መስጫ ተቋማት ለሰራዊቱ ክፍት እንዲሆኑ በማድረግ አምቡላንስና የህክምና ባለሙያ መድበው ቁስለኞችን በሰፊው ማከማቸውንና ሪፈር የተባሉት ብቻ ወደማዕከል መምጣታቸውን አስታውቀዋል። “ጁንታው በውጊያ ሲወጠር ባዶ እጃቸውን አግኝቷቸው ሳይማርክ ማርኬያለሁ ብሎ የፎከረባቸውና የታገቱ አባሎቻችንን ጥሏቸው ሲጠፋ ወደአማራ ክልል ነው የመጡት፤ አማራ ክልል ከድንበሩ ጀምሮ እስከመጨረሻው የመሰባሰቢያ ወረዳ ድረስ አጓጉዞ፣ አብልቶ፣ ሞራል ሰጥቶ ወገናዊነቱን አሳይቶ ነው የሸኛቸው፤ ይህ በጣም ከባድ ስራ ነው” ሲሉም ነው የክልሉ ህዝብን አስተዋጽኦ የገለጹት።“እኛ ያደረግነው እነሱ ያሰባሰቡትን፣ ያደራጁትንና በዩኒቨርሲቲ ያቆዩትንና የመገቡትን ተቀብለን ኦረንቴሽን ሰጥተን ነው ወደክፍላቸው የመለስናቸው” ያሉት ጄኔራል ብርሃኑ፤ “እኛ የጁንታውን ዋና ሃይል እየመታን ስንሄድ በእያንዳንዱ ውጊያ የአማራ ክልል ልዩ ሃይል ብዙ ቀዳዳ ሸፍኗል፤ ውጊያ ያለበት እየተዋጋ ውጊያ የሌለበት ደግሞ ቀጣናውን በመሸፈን ሰራዊቱ ቀጣና እሸፍናለሁ ብሎ ሃይል እየቀነሰ እንዳይሄድ አድርጓል፤” ሲሉም ነው የተናገሩት።እንደ ጄኔራል ብርሃኑ ገለጻ፤ በኦሮሚያም በኩል የነበረው አስተዋጽኦ ከፍተኛ ነው። ከክልሉ ፕሬዚዳንት እና ከተወሰኑ አመራሮች በስተቀር ሁሉም አመራር ወደወረዳ አስገብቶ ልዩ ሃይሉን አስገብቶ በሸኔ በኩል ታቅዶ የነበረው እድል እንዳያገኝ የማድረግ ስራ ተሰርቷል። ሶማሌ ክልልም ራሱን ችሎ ጸጥታውን በመቆጣጠር ምንም ኮሽታ ሳይሰማ የህግ ማስከበር ዘመቻው መጠናቀቁን የገለጹት ጄነራል ብርሃኑ፤ በክልሉ በምስራቅ ዕዝ የሚጠበቁ ብዙ ተቋማት እንደነበሩና አልሸባብም በዚያ አካባቢ የሚንቀሳቀስ ቢሆንም ሁሉንም ስራ የክልሉ መንግስት ልዩ ሃይል በራሱ እንዳከናወነ አብራርተዋል። በተመሳሳይም የአፋር ክልል ልዩ ሃይል ያደረገው አስተዋጽኦ ላቅ ያለ መሆኑን የገለጹት ጄኔራል ብርሃኑ፤ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደርና ህዝብም በአጭር ጊዜ ከፍተኛ ገንዘብ አዋጥቶ ለሰራዊቱ ማበርከቱን በመጥቀስ መላው የአገሪቷ ህዝብ በተለያየ አስተዋጽኦ የተሳተፈበት ዘመቻ በድል መቋጨቱን አብራርተዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 13/2013
https://www.press.et/Ama/?p=37843
366
0ሀገር አቀፍ ዜና
“መገንባት የምንፈልገው ዴሞክራሲ ጥቂቶች ብቻ የሚጫወቱበት ሜዳ ሳይሆን ብዙሃንን የሚያሳትፍ ሜዳ እንዲሆን ይፈለጋል”ወይዘሮ ሙፈሪያት ካሚል የሰላም ሚኒስቴር
ሀገር አቀፍ ዜና
December 22, 2020
16
በጋዜጣው ሪፖርተርአዲስ አበባ፡- መገንባት የምንፈልገው ዴሞክራሲ ጥቂቶች ብቻ የሚጫወቱበት ሜዳ ሳይሆን ብዙሃንን የሚያሳትፍ ሜዳ እንዲሆን ስለሚፈለግ ለሁሉም የሆነች አገርን በመገንባት ሂደት ላይ ሁሉንም ለማሳተፍ የሚያስችሉ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን የሰላም ሚኒስትሯ ወይዘሮ ሙፈሪያት ካሚል ተናገሩ፡፡ትናንት በይፋ የተጀመረውን የብሔራዊ የማህረበሰብ ተኮር የምክክር መድረክን አስመልክቶ በሰጡት መግለጫ እንደተናገሩት፤ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የተሰጠውን መሰረታዊ ተልዕኮ ለመወጣት ከባለድርሻዎች ጋር በትኩረት እየሰራ ይገኛል።እንደ አገር መገንባት የምንፈልገው ዴሞክራሲ ጥቂቶች ብቻ የሚጫወቱበት ሜዳ ሳይሆን ብዙሃንን የሚያሳትፍ ሜዳ እንዲሆን ስለሚፈለግም፤ ብዝሃነት ባለበት አገር ሁሉም ድምጾች እንዲደመጡ እድል መስጠት የሚያስችል ስራዎችን አቅዶ እየሰራ ይገኛል፡፡የሰላም ሚኒስቴር ከተሰጡት መሰረታዊ ተልዕኮዎች መካከል አንዱ በአገሪቱ ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን፣ የህግ የበላይነት እና የዳበረ ዴሞክራሲ እንዲገነባ፣ እናም ብሔራዊ መግባባት እንዲፈጠር ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር መስራት መሆኑን የጠቆሙት ሚኒስትሯ፤ ይሄን መሰረት በማድረግም በሁለት እርከን የተከፈለ ብሔራዊ የምክክር መድረክ ለማዘጋጀት ባለፈው አንድ ዓመት ተኩል ጊዜ ሰፋፊ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ሲያከናውን መቆየቱን ተናግረዋል፡፡ይሄም የመጀመሪያው መድረክ ሕብረተሰብ ተኮር የሆነ በየእርከኑ በተለይም ህብረተሰቡ የሚገኝበትን የመጨረሻውን እርከን ቀበሌን ማዕከል ያደረገ ምክክር የሚካሄድበት መርሃ ግብር ሲሆን፤ ሁለተኛው በተለያየ ደረጃ የሚገኙ ልሂቃን የሚሳተፉበት የምክክር መድረክ ነው።በዚህም ከትግራይ ክልል በስተቀር በሁሉም ክልሎች ህብረተሰብ ተኮር ብሄራዊ የምክክር መድረኩ በይፋ የተጀመረ ሲሆን፤ ለቀጣይ ሶስት ተከታታይ ወራት ያህል በቋሚነት የሚቀጥል ይሆናል፡፡ምክክር ልብ ለልብ መገናኘትን፣ መደማመጥን፣ መቻቻልን፣ እውን ለማድረግ፤ ችግሮችና አለመግባባቶች እንኳን ቢኖሩ ስልጡን በሆነ መንገድ በውይይት የመፍታት ባህልን የሚያለማምድ፤ ደረጃ በደረጃም ይሄንን መፍጠር የሚያስችል ልምምድ ነው።በኢትዮጵያ ላለፉት በርካታ ምዕተ ዓመታት ጥሩ ጥሩ እሴቶች ያሉንን ያህል ችግሮቻችንን በሰለጠነ መንገድ ተቀራርቦ ከመፍታት አኳያ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተዳከመ የመጣ፤ በወጉም በተስተካከለ መሰረት ላይ ያልተገነባ እሴትና ባህል እንደመሆኑ መጠን፤ ችግርን በሃይማነ ጉልበት መፍታት አማራጭ ተደርጎ ሲወሰድ ቆይቷል።ይሄ ደግሞ የዴሞክራሲ ስርዓትን ለመገንባት ለሚተጋ አገር እጅግ አዳጋች የሆነ ጉዳይ ነው፡፡በመሆኑም በእነዚህ የውይይትና የምክክር መድረኮች ከአካባቢ ጉዳዮች ጀምሮ እስከ ብሔራዊናአገራዊ የሆኑ የጋራ የሆኑ ሀሳቦችና ጉዳዮችን የሚመለከት ስለሆነ የምክክር ሂደቱ መጨረሻ ላይ የሚያግባቡ አገራዊ ጉዳዮች ላይም የጋራ ድምዳሜ ይደረስበታል ተብሎ ይታመናል።ስለሆነም ትልቅ ዴሞክራሲን ለመገንባት ለምናደርገው ጥረት፤ ዘላቂ ሰላም ለመገንባት ለምናደርገው ጥረት መሰረታዊ የሆነ የእሳቤና የባህሪ ለውጥ ለማምጣት ያግዛል ተብሎ የተቀረጸ መርሃ ግብር ነው፡፡በዘሌ መንገድ ደግሞ ልሂቃን የሚያደርጉት ውይይት ተመሳሳይ ዓላማ ያለው ነው።ምክንያቱም ልሂቃን ሀሳብ የሚቀርጹ ናቸው።እናም የልሂቃን ሀሳብ በተስተካከለ መሰረት ላይ ማረፍ ከቻለ ለአገር ግንባታ ሂደት ትልቅ አበርክቶ ይኖረዋል።ስለዚህ ልሂቃንም በየፈርጃቸው አገራዊ በሆኑ ጉዳዮች ላይ የሚያደርጓቸው ውይይቶች እና የሚደርሱባቸው መግባባቶች ተመልሶ በህብረተሰብ ደረጃ ለሚካሄደው ውይይት፤ በህብረተሰብ ደረጃ የሚካሄደው ውይይትም የሚያወጣቸው ሀሳቦችና የጋራ የሆኑ ጉዳዮች መልሶ የልሂቃኑን ሀሳብ መልክና ቅርጽ ለማስያዝ የራሱ አበርክቶ ይኖረዋል፡፡ይሄ የሁለቱ ምግግቦሽ በአንድ በኩል ከላይ ወደታች ህብረተሰቡ ላይ አጀንዳ የሚጫንበት ሳይሆን በራሱ ይመለከተኛል፣ ያሳስበኛል፣ የሚለውን ጉዳይ አንጥሮ የሚያወጣበት ይሆናል።በዚህም መንግስት ከእነዚህ መድረኮች የሚገኙ ግብዓቶችን ወስዶ ህብረተሰቡን ለማድመጥና ተግባራዊ ምላሽ ለመስጠት ትልቅ አስተዋጽኦ ይኖረዋል።መጨረሻ ላይም የሁለቱ መድረከች በጋራ መጥተው ብሔራዊ የሆነ ምክክር፤ ስልጡን የሆነ ውይይት የሚደረግበት፤ የጋራ አቋም የሚወሰድበት ምዕራፍ ይኖረዋል፡፡እነዚህ ሁሉ ሂደቶች ለአገር ግንባታ ትልቅ አስተዋጽኦ ይኖራቸዋል፤ ብሔራዊ መግባባት መፍጠር ደግሞ ለአገር ግንባታ ትልቅ አስተዋፅኦ አለው ያሉት ሚኒስትሯ፤ መድረኩ የልሂቃን ብቻ እንዲሆን ያልፈለግነውና መሰረተ ሰፊ እንዲሆን የፈለግነው መገንባት የምንፈልገው ዴሞክራሲ ጥቂቶች ብቻ የሚጫወቱበት ሜዳ ሳይሆን ብዙሃንን የሚያሳትፍ ሜዳ እንዲሆን ስለሚፈለግ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ከዚህ አኳያ መሰረተ ሰፊ የሆነ ህብረተሰብ ተኮር ምክክር የፖለቲካ ፓርቲዎችን ጨምሮ ሌሎች ልሂቃን የሚሳተፉባቸው የምክክር መድረኮች ሲኖሩ፤ በጤናማ እና መሰረተ ሰፊ በሆነ ይዞታ ላይ የሚያርፍና የሚገነባ እንደሚሆን ተናግረዋል።ይህ ዘላቂ ለሆነ ሰላም ግንባታ የሚሆን የአገር ግንባታ ትልቅ አስተዋፅኦ እንዳለውም አስረድተዋል።የአገራት ልምድ የሚያሳየውም አገራት የአገር ግንባታ ሂደቶቻቸውን በየራሳቸው ነባራዊ ተጨባጭ ሁኔታ እንደየአመቺነቱ አስኪደውታል፤ በእኛ ተጨባጭ ሁኔታም ብዝሃነት ባለበት አገር ሁሉም ድምጾች እንዲደመጡ እድል መስጠት፤ ከዚህ ተነስቶም ለሁሉም የሚሆን አገር መስራት እጅግ አስፈላጊ መሆኑን አብራርተዋል፡፡መድረኩም ይሄን ታሳቢ ያደረገ ሲሆን፤ በቀጣይ ወራትም ተጠናክሮ የሚቀጥልና በቋሚነት የሚሰራ መሆኑን፤ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱም ሁሉንም ባለድርሻ ለማሳተፍ የሚያስችል ስራ ማከናወኑን በመግለጽ፤ በቀጣይ ጥቂት ቀናት ከሚካሄዱ መድረኮች የሚገኝ ልምድም በዘላቂነት ለሚካሄደው መድረክ ተቀምሮ የሚሰራበት እንደሆነም አስረድተዋል፡፡አዲስ ዘመን ታህሳስ 13/2013
https://www.press.et/Ama/?p=37844
568
0ሀገር አቀፍ ዜና
“በኃይል ወንበር እይዛለሁ ብሎ የሚመጣ ይጎዳል እንጂ አይጠቀምም ” ብርጋዴር ጄኔራል አዳምነህ መንግስቴ
ሀገር አቀፍ ዜና
December 22, 2020
72
በጋዜጣው ሪፖርተርአዲስ አበባ፡- ጥሩ አላማ እና ህዝብ ይጠቅማል የሚል ሃሳብ ይዞ ከመቅረብ ያለፈ በሃይል ወንበር እይዛለሁ ብሎ የሚመጣ ማንኛውም ኃይል ከመጎዳት ያለፈ ምንም እንደማይጠቀም የህወሓት ጁንታ አፍኗቸው ከነበሩት መካከል አንዱ የሆኑት የሰሜን ዕዝ ምክትል ኦፕሬሽን አዛዥ ብርጋዴር ጄኔራል አዳምነህ መንግስቴ ተናገሩ።መከላከያ ሰራዊቱም በሰላማዊ መንገድና በዴሞክራሲያዊ አካሄድ የሚመጣውን ብቻ ተቀብሎ ለመሄድ የሚሰራ እንደሆነም አስገንዝበዋል።ብርጋዴር ጄኔራል አዳምነህ እንደተናገሩት፤ የህወሓት ጁንታ ቡድን ለዓመታት የሀሰት ፕሮፖጋንዳ ላይ ተጠምዶ ከማሳለፉ ባሻገር በሃይል ወንበር ለመያዝ እንዲያመቸው በመከላከያ ሰራዊቱ አባላት ላይ የፈጸመው ጥቃት ውድቀቱን አፋጥኖለታል።መከላከያ ሰራዊቱም ለዚህ የሚመች ሃይል አለመሆኑን አሳይቷል።በመሆኑም የተሻለ ዓላማ ለህዝብ በሚጠቅም ሃሳብ ይዞ ከመስራት ባለፈ በሃይል ወንበር ለመያዝ የሚደረግ ሙከራ የማይጠቅም፤ ይልቁኑም ያንን ኃይል የሚጎዳ መሆኑን መገንዘብ ይገባል፡፡እንደ ብርጋዴር ጄኔራል አዳምነህ ገለጻ፤ የጁንታው ቡድን በህዝቡ ውስጥ ብቻ ሳይሆን መከላከያ ሰራዊትን የማጠልሸት እና የመከፋፈል ስራዎች ቀድሞ ሲያከናውን ነበር። ሰራዊቱ በአንድ መምሪያ እና ተቋም ስር ሆኖ ሳለ የሰሜን እዝ መጥፎ ነው ምዕራብ አሊያም ምስራቅ ዕዝ ጥሩ ነው የሚል መከፋፈል ሲታይ ቆይቷል። በማህበራዊ ድረገጾች እና በአካል ጭምር ሰራዊቱን የማጠልሸት ስራዎችን አከናውነዋል፤ በቻሉት መጠን የሰራዊቱን የውስጥ አንድነት ያናጋል ብለው የሚያስቡትን ለማድረግ ያልወረወሩት ጠጠር የለም። ሆኖም ችግሮቹ ከዛሬ ዛሬ ይስተካከላሉ በሚል ሀገር ተመልሳ ወደጦርነት እንዳትገባ ነበር ሰራዊቱ ነገሮችን በትዕግስት ለማለፍ የመረጠው። በዚህ መሃል ግን ሰራዊቱ ህይወቱን ብቻ ሳይሆን ከኪሱ አዋጥቶ ለህዝብ እያገዘ ባለበት ሥፍራ የጁንታው ቡድን የአፈና ተግባር የማፍያ ቡድንነቱን ያሳየበት ስራ ነው። ይሄን ተከትሎም በመንግስት በኩል የተሰጠው አቅጣጫ እና በመከላከያ ሰራዊቱ የተወሰደው የማጥቃት እርምጃ ደግሞ አገርን ከጥፋት የታደገ፤ በሃይል ስልጣንና ወንበር ለመያዝ ማሰብ ትርፉ ለራስ መጥፋት ምክንያት መሆኑን በተግባር ያረጋገጠ ክስተት ሆኖም አልፏል፡፡በዚህ ረገድ ህግን በማስከበር እርምጃው በመንግስትም ሆነ በመከላከያ ሰራዊቱ በጥበብና ጥንቃቄ በተመላበት መልኩ የተወሰደው ለመንግስትምለሰራዊቱም አድናቆትና ምስጋና የሚያስቸረው ነው።በቀጣይም የጁንታው አመራር አባላት ከያሉበት ተይዘው ለፍርድ እንዲቀርቡ ያደረግ ሲሆን፤ እኛም የጁንታው ቀሪ ቡድን ተይዞ ለህግ እንዲቀርብ የሚደረገው ጥረት ላይ ለመሳተፍ ዝግጁ ነን፣ ሲሉ ብርጋዴር ጄኔራል አዳምነህ ተናግረዋል።መከላከያ ሰራዊት ከፖለቲካ ነጻ ሆኖ እንዲሰራ የተጀመረው ስራ እንዲጠናከር እንሰራለን ያሉት ብርጋዴር ጄኔራል አዳምነህ፤ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይም በምርጫ ከተሸነፉ ስልጣን ለመልቀቅ ፍቃደኛ መሆናቸውን በተደጋጋሚ ከማሳወቃቸው ጋር ተያይዞም መከላከያ ሰራዊቱ በሰላማዊ መንገድና በዴሞክራሲያዊ አካሄድ የሚመጣውን ተቀብሎ ለመሄድ እየሰራ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡በመሆኑም ጥሩ አላማ እና ህዝብ ይጠቅማል የሚል ሃሳብ ይዞ ከመቅረብ ያለፈ፣ በጉልበትና በሃይል ወንበር እይዛለሁ ብሎ የሚመጣ ኃይል ቢኖር የሚጎዳ እንጂ የሚጠቀም አለመሆኑን መገንዘብ እንዳለበት አሳስበዋል።ችግር ቢኖር እንኳን በሃይል ሳይሆን በቀጣይ ችግሮችን አርሞ እና አሻሽሎ መምጣት አስፈላጊ መሆኑን በመጠቆምም፤ ለተወሰነ የስልጣን ፈላጊ ቡድን ሲባል ብሔር ብሔረሰቦች በማንነታቸው፣ ባህላቸውና በወጋቸው ላይ ድርድር ስለማይኖር ሁሉም አካል ህዝብን መሰረት አድርጎ መስራት እንደሚገባው ተናግረዋል፡፡እንደ ብርጋዴር ጄኔራል አዳምነህ ገለጻ፤ የአንዱ መብት መከበር የሌላኛው መከበር፣ የአንዱ መብትና ጥቅም አለመከበርም የሌላኛው አለመከበር መሆኑን መገንዘብ ያስፈልጋል።ከዚህ ባለፈ ደግሞ የጋራ እሴቶች ላይ መሰራት ይኖርበታል። ጁንታው ግን በጋራ አንድነት ላይ የማዳከም እና ሁሉ ነገር ላይ መሰማት አለብኝ ሲል እና ሌሎች የተናገሩት ውሸት እኔ የተናገርኩት ግን እውነት ነው ብሎ ሲያምታታ የኖረ እንደመሆኑ በፍላጎቱ ተመርቶ ሞቱን አፋጥኗል።በመሆኑም ከዚህ ትምህርት ወስዶ ሁሉም አካል የጋራ ተጠቃሚነት የሚያበለጽጉ አካሄዶችን በማዳበር ድህነትን ለማስወገድ መስራት፤ ወንበርም ከጦርነት ይልቅ በዴሞክራሲያዊ መንገድ የመያዝ ልምድን ማዳበር ይኖርባቸዋል፡፡አዲስ ዘመን ታህሳስ 13/2013
https://www.press.et/Ama/?p=37845
458
0ሀገር አቀፍ ዜና
ማራቶንን በተፈጥሯዊ መንገድ ከ2 ሰዓት በታች የመሮጥ ውጥንነው፡፡
ስፖርት
November 25, 2019
15
ነገር ግን የድል ዜናው ቦታውን ቀይሮ በተገናኙባቸው ውድድሮች ኬንያዊው አትሌት የርቀቱ ፈጣን ተሰኘ፡፡ በጉዳት ምክንያት ከውድድር ርቆ የቆየው የሃገር አቋራጭ ንጉሱ ቀነኒሳም በርቀቱ ያለውን ተስፋ ከማሳየት በቀር ለሁለት ዓመታት ውጤት አላስመዘገበም ነበር፡፡ እአአ 2016 ግን የፓሪስ ማራቶንን በማሸነፍ በጠባብ የደቂቃዎች ልዩነት ሁለተኛው የርቀቱ ፈጣን አትሌት ለመሆን ችሏል፡፡ በቀጣዩ ዓመት በለንደን ማራቶን ያስመዘገበው ሰዓት ከፈጣኑ የዘገየ መሆኑ በርቀቱ ያለውን ተስፋ አጠራጣሪ አድርጎት ነበር፡፡ ምክንያቱ ደግሞ በ5 እና 10ሺ ሜትር የሶስት ጊዜ የኦሊምፒክ ቻምፒዮኑ ቀነኒሳ የባት ፣ የቁርጭምጭሚት፣ ተረከዝ፣ ሽንጥ እና ቋንጃ ጉዳቶች ጋር ትግል ሲያደርግ በመቆየቱ ነው፡፡ የአትሌቱ የረጅም ጊዜ ማኔጀር ጆስ ሄርሜንስም ስለ ቀነኒሳ ከሰሞኑ በዓለም አትሌቲክስ ድረ ገጽ አጠቃላይ መረጃ ሰጥቷል፡፡ አሰልጣኙ አትሌቱ የነበረበትን ሁኔታ ሲገልጽም ‹‹በአዲስ አበባ ያለው ህይወቱ ውጥረት የበዛበት በመሆኑ ለልምምድ እንዲሁም ለማገገም የተመቸ ጊዜ የለውም፡፡ ከሩጫው ባሻገር በቢዝነስ ስራዎችም ላይ ተሳታፊ እና የልጆች አባት እንደመሆኑም አብዛኛውን ጊዜውን በዚህ ያሳልፋል፡፡ በዚህ ሂደትም ጊዜውን ያለእረፍት እያሳለፈ ነበር›› ሲልም ይገልጻል፡፡ ‹‹የማራቶን ሁለተኛውን ሰዓት ካስመዘገበበት የበርሊን ማራቶን ሁለት ወራት አስቀድሞም ለጥቂት ጊዜ ከውጥረት መላቀቅ እንዳለበትና ጥሩ የማገገሚያ ጊዜ እንደሚኖረው አስረዳነው›› ይላል ማኔጀሩ፡፡ ይህን ማሳመን ቀላል ባይሆንም በመጨረሻ ግን ከቤተሰቦቹ ተለይቶ ለሁለት ወራት በሆላንድ በምትገኝ አንዲት ከተማ ለማሳለፍ የግድ ሆነ፡፡ አትሌቱም የሩጫ ህይወቱን ከማቋረጡ አስቀድሞ በማራቶን አንድ ታሪክ ማስመዝገብ የሚፈልግ በመሆኑ ከጉዳቱ በቶሎ አገግሞ ወደ ልምምድ እንዲገባ የቻሉትን ሁሉ ማድረጋቸውን ማኔጀሩ ያስታውሳል፡፡ ክብደቱ በመጨመሩም በሆላንዳዊው የስነ ምግብ ፕሮፌሰር አርማንድ ቤቶንቬል እገዛ የአመጋገብ ሁኔታውን ማስተካከል ተችሏል፡፡ በአዲስ አበባ ቆይታው የአመጋገብ ሁኔታው የተጠና አልነበረም፤ አብዛኛውን ጊዜ የሆቴል ምግብ የሚያዘወትር ከመሆኑ ጋር በተያያዘ እንደ አትሌት በሚጠበቅበት ሁኔታ ላይ አልነበረም፡፡ በባለሙያዎቹ አማካኝነትም ፕሮቲን፣ ሩዝ እና ድንች በተሻለ ሁኔታ እንዲያገኝ ተደርጓል፡፡ ስልጠናውንም በአግባቡ ነበር የሚከታተለው፡፡ ወደ ዋናው ስልጠና ከገባም በኃላ በሳምንት እስከ 50 ኪሎ ሜትር በመሸፈን ጥሩ የሚባል ጊዜ አሳልፏል፡፡ የመልካም አስተሳሰብ ባለቤት በመሆኑም ከታሰበው በተሻለ ፍጥነት መሻሻል ሊያሳይ ችሏል፡፡ ወደ አዲስ አበባ ከተመለሰ በኃላም በአሰልጣኝ ሃጂ አዲሎ ስር በመሆን ስልጠናውን ሳያዘባ ሲሰራ ስለ ነበር በጥቂት ጊዜ ወደ ቀደመ አቋሙ ሊመለስ ችሏል፡፡ ዝግጅቱ በርቀቱ ከፈጣኖች ተርታ ከሚሰለፈውና ከዓለም ቻምፒዮኑ አትሌት ሌሊሳ ዴሲሳ ጋር መሆኑም የተሻለ ነገር አስገኝቶለታል የሚል እምነት እንዳላቸው ኸርሜንስ ይናገራሉ፡፡ በእርግጥ ስልጠናውን በሚያደርግበት ወቅት አዲስ አበባ ዝናባማ የአየር ሁኔታ ነበራት፤ ይህም አስቸጋሪ ስለነበር ስልጠናውን በበፊቱ ልክ ማከናወን አንዳልተቻለም አልዘነጉም፡፡ ‹‹ውድድሩ ሲቃረብም በአትሌቱ ብቃት ሁላችንም ከመተማመን ላይ ደርሰን ነበር፡፡ እኛ በስልጠናው ወቅት ሲያሳይ በቆየው ብቃት ከፍተኛ ተስፋ ስንሰንቅ እርሱ ደግሞ በጥሩ ውጤት ማጠናቀቅን አላማው አድጎ ነበር፡፡ ከሚታመነው በላይ ጠንካራ አትሌት ነው፤ በውድድሩ ላይ ኬንያዊው አትሌት ከያዘው ክብረወሰን በሁለት ሰከንዶች ብቻ ዘግይቶ ገብቷል›› በማት አ ድ ና ቆ ታ ቸ ው ን ይገልፃሉ፡፡ እውቅና ያልተሰጠውና ሰው ሰራሽ በሆነ መንገድ ቢሆንም የሰው ልጁ 42ኪሎ ሜትሮችን ከ2ሰዓት በታች መግባት ይችላል የሚለው ሙከራ በኬንያዊው ኪፕቾጌ እውን ከተደረገ በኃላም የስፖርት ቤተሰቡ ጥያቄ ተመሳሳይ ሆኗል፡፡ ‹‹ቀጣዩ ምንድነው?›› የሚለው ፤ ምላሹም ቀነኒሳን ከማየት የተሻለ አለመኖሩን የሚያሳይ ነው፡፡ ቀነኒሳ ማራቶንን በተለመደው መንገድ ሮጦ በቴክኖሎጂ ሳይታገዝ ከ2፡00 በታች መሮጥ እንደሚችል በቅርቡ አብሮ እየሰራ የሚገኘው አሰልጣኙ ሃጂ አዲሎም በቅዳሜው እለት እትማችን ባደረጉት ቃለ ምልልስ መግለፃቸው ይታወቃል፡፡ አሰልጣኙ ሃጂም ‹‹ ቀነኒሳ ሩጫ ከማቆሙ አስቀድሞ ማራቶንን ከ2፡00 በታች ይሮጣል፣ በየትኛው ውድድር እንደሚሆን ግን መናገር አይቻልም›› ይላሉ፡፡ ቀነኒሳ ምናልባትም ይህን ለማሳካት የቀጣዩን ዓመት የበርሊን ማራቶን መታገስ ላይጠበቅበት ይችላል፡፡ በቀጣዩ ሚያዝያ በለንደን ማራቶን ለመሳተፍ በሆላንድ አገር የሚያደርገው ዝግጅት በታሰበው ልክ ከሄደ ህልሙን በቅርቡ እውን ሊያደርግ እንደሚችል ይጠበቃል፡፡አዲስ ዘመን ኅዳር 15/2012 ብርሃን ፈይሳ
https://www.press.et/Ama/?p=23109
504
2ስፖርት
ሉሲዎቹ ወደ አፍሪካ ዋንጫ የመመለስ ሰፊ እድል አላቸው
ስፖርት
December 6, 2019
25
 የ2020 የሴቶች አፍሪካ ዋንጫ ቅድመ ማጣሪያና ማጣሪያ ጨዋታዎች ድልድል ይፋ ተደርጓል። በዚህም መሰረት የኢትዮጵያ ሴት ብሔራዊ ቡድን (ሉሲዎቹ) በቅድመ ማጣሪያና ማጣሪያ ጨዋታዎች የሚገጥሙትን ቡድን አውቀዋል። ሉሲዎቹ የቅድመ ማጣሪያ ጨዋታቸውን ከጅቡቲ ብሔራዊ ቡድን ጋር የፊታችን ሚያዚያ አራት ቀን የሚያደርጉ ሲሆን ጅቡቲን በደርሶ መልስ ጨዋታ ድምር ውጤት የሚያሸንፉ ከሆነ በመጨረሻው የማጣሪያ ጨዋታ ከሞሮኮ ብሔራዊ ቡድን ጋር የሚጫወቱ ይሆናል። በአሰልጣኝ ብርሃኑ ግዛው የሚመራው የኢትዮጵያ ሴት ብሔራዊ ቡድን ለ2020 የሴቶች የአፍሪካ ዋንጫ ለማለፍ ከወዲሁ ለውድድሩ ትኩረት በመስጠት ከፍተኛ ስራዎችን እየሰራ የሚገኝ ሲሆን አሰልጣኙ ቡድኑን ለአፍሪካ ዋንጫ ማሳለፍ ካልቻሉ ራሳቸውን ከአሰልጣኝነት ስራ እንደሚያገሉ መግለፃቸው ይታወሳል። ለመጀመሪያ ጊዜ ሰላሳ ሁለት አገራትን የሚያሳትፈው የ2020 የሴቶች የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ 2018 ተካሂዶ ከነበረው ውድድር አስራ ሁለት አገራትን ጨምሮ ሲካሄድ ዘንድሮ የመጀመሪያው ይሆናል። ይሁን እንጂ ይህን ውድድር የሚያዘጋጀው አገር እስካሁን አልታወቀም።ካፍ የ2020 የሴቶችን የአፍሪካ ዋንጫ ሞሮኮ እንድታዘጋጅ ፍላጎት እንዳለው የተለያየ መረጃ እየወጣ ይገኛል።ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ከበጀት እጥረት ጋር ተያይዞ የ2020 የሴቶች አፍሪካ ዋንጫን እንደማታዘጋጅ ከተገለጸ ወዲህ የአፍሪካ እግር ኳስን በበላይነት የሚመራው ካፍ ደቡብ አፍሪካ ውድድሩን እንድታዘጋጅ ጥሪ ቢያቀርብላትም ለ2023 የሴቶች ዓለም ዋንጫን ለማዘጋጀት ፉክክር ውስጥ በመግባቷና የዓለም ዋንጫውን ለማዘጋጀት ከፍተኛ ስራ ውስጥ በመገኘቷ ጥያቄውን ውድቅ ማድረጓ ይታወቃል። ካፍ የ2020 የሴቶች አፍሪካ ዋንጫን አዘጋጅነት ጥያቄ በቅርቡ የመላው የአፍሪካ ጨዋታዎችን በድምቀት ወደ አዘጋጀችው ሞሮኮ ፊቱን በማዞር ጥያቄ ሊያቀርብ እንደተዘጋጀ ታውቋል። ሞሮኮ የ2020 የሴቶች አፍሪካ ዋንጫን የምታዘጋጅ ከሆነ ሉሲዎቹ ከጅቡቲ አቻቸው ጋር በሚያደርጉት ጨዋታ የአፍሪካ ዋንጫ ትኬታቸውን በቀላሉ የሚቆርጡበት እድል ሰፊ ይሆናል። የጅቡቲ ብሔራዊ ቡድን ከአራት ሳምንት በፊት ተካሂዶ በነበረው የመካከለኛና ምስራቅ አፍሪካ(ሴካፋ) ዋንጫ ላይ ከዩጋንዳ፣ኬንያና ኢትዮጵያ ጋር ተደልድሎ በኬንያ 13ለ0፣ በዩጋንዳ 12ለ0 እንዲሁም በኢትዮጵያ 8 ለ 0 ተሸንፎ በውድድሩ በአጠቃላይ ሰላሳ አንድ ግቦች በማስተናገድ አንድም ግብ ሳያስቆጥር መቅረቱ ይታወሳል። ይህም ሉሲዎቹ በቅድመ ማጣሪያው ጨዋታ በቀላሉ አሸንፈው ወደ ቀጣዩ ማጣሪያ እንደሚያልፉ ከፍተኛ ግምት እንዲሰጣቸው አድርጓል። እኤአ 1991 ላይ በተጀመረው የአፍሪካ ሴቶች ዋንጫ ላይ ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ 2002 ተሳታፊ መሆን ብትችልም በውድድሩ ከምድብ ጨዋታዎች ማለፍ እንዳልቻለች ይታወሳል። 2004 ላይ ዳግም ተሳታፊ በመሆን አራተኛ ደረጃን ይዛ ያጠናቀቀችበት ውጤት በታሪክ ትልቁ ሲሆን ለመጨረሻ ጊዜ በመድረኩ የተሳተፈችው 2012 ላይ ነው። ዘንድሮ ግን ከስምንት ዓመታት በኋላ ወደ መድረኩ የመመለስ ትልቅ ተስፋ ሰንቃለች።አዲስ ዘመን አርብ ህዳር 26/2012 ቦጋለ አበበ
https://www.press.et/Ama/?p=23656
330
2ስፖርት
ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ ወጣት ሴት ተማሪዎችን ከስኬታማ ሴቶች ጋር በማጣመር የድጋፍና የምክር አገልግሎት ማስጀመር ውጤታማ ሴቶችን ለማፍራት እንደሚያግዝ ተገለጸ
ሀገር አቀፍ ዜና
December 22, 2020
12
ሞገስ ተስፋአዲስ አበባ፡- የመሰናዶ ትምህርታቸውን አጠናቀው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ ወጣት ሴት ተማሪዎች በስራ አለምና በህይወት ተሞክሮ ስኬታማ ከሆኑ ሴቶች ጋር በማጣመር የድጋፍና የምክር አገልግሎት እንዲያገኙ ማድረግ፣ ወጣት ሴት ተማሪዎችን ውጤታማ እንደሚያደርጋቸው የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ፕሬዚዳንት ሳህለ ወርቅ ዘውዴ አስታወቁ፡፡የሴቶች ህፃናትና ወጣቶች ሚኒስቴር ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ ሴት ተማሪዎች ውጤታማ ሆነው እንዲወጡ ከስኬታማ ሴቶች ጋር የምክክርና ድጋፍ የማስጀመሪያ መርሃ ግብር አካሂዷል፡፡በመርሃ ግብሩ ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ እንደተናገሩት፤ 12ኛ ክፍልን በጥሩ ሁኔታ አጠናቀው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ ሴቶችን የደጋፊና መካሪ አገልግሎት እንዲያገኙ በህይወታቸው ስኬታማ ሴቶች ጋር ጥምረት እንዲፈጠር መደረጉ መንግስት ሴቶችን ወደ አመራር ለማምጣት ለሚያደርገው ጥረት አጋዥ ነው፡፡ በፖለቲካው፣ በኢኮኖሚውና በማህበራዊው ዘርፍ ስኬታማ የሆኑ ሴቶች፣ ለወጣት ሴት ተማሪዎች የድጋፍና የምክር አገልግሎት እንዲሰጡ ማድረግ ትልቅ ስኬት ነው፡፡ እንደ ፕሬዚዳንቷ ገለፃ፤ ወጣት ሴት ተማሪዎች የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ሲቀላቀሉ የሚሄዱት አዲስ አካባቢና አዲስ ሁኔታ ውስጥ እንደመሆኑ ብዙ ውጣውረዶች ይገጥሟቸዋል፡፡ በዚህ ወቅት የሚደግፋቸውና የሚመክራቸው መኖሩ በራስ የመተማመን አቅማቸውን አሳድገው አንገታቸውን ቀና ሊያደርግ፤ የአስተሳሰብ አድማሳቸውን በማስፋት የሚጎሏቸው ነገር ላይ በመምከር የበለጠ ሊያዘጋጇቸው የሚችል ነው፡፡ የደጋፊና መካሪ ስራ ደግሞ በቃላት ብቻ ሊገለፅ የማይችል ጥቅም ስላለው ለተማሪዎች በትምህርታቸው ላይም ሆነ ትምህርታቸውን አጠናቀው ወደስራ ዓለም ለመቀላቀል በሚዘጋጁበት ጊዜም ትልቅ አቅም ይፈጥርላቸዋል፡፡ በተለይም እንደተምሳሌት የሚያዩአቸው ሴቶች መኖራቸው ወደፊትም ለሚኖራቸው ራዕይ አርቀው እንዲያስቡ ያግዛቸዋል፡፡ ምክንያቱም የወጣት ሴት ተማሪዎች የደጋፊና የመካሪ መርሃ ግብር መጀመሩ በተለይም የወደፊት ራዕያቸውን በመመልከት በሚገጥማቸው ፈተና ሳይደናገጡ አላማቸውን ለማሳካት ትልቅ ፋይዳ አለው፡፡ከዚህ በፊት ያለፍንበት ሁኔታ እንድንፎካከር እንጂ እንድንደጋገፍ የሚረዳ አልነበረም ያሉት ፕሬዚዳንቷ፤ በዚህ ሁኔታ ውስጥ ምንም አይነት ችግር ሳይበግራቸው ለስኬት የበቁ ሴቶችን አብነት በመውሰድ ወጣት ሴት ተማሪዎች ከፍተኛ ውጤት በማስመዝገብ ለትልቅ ኃላፊነት ራሳቸውን ሊያዘጋጁ እንደሚገባም አሳስበዋል፡፡ በዚህ ረገድ የደጋፊና የመካሪ አገልግሎት መርሃ ግብር መጀመሩ መልካም እድል መሆኑን በመጥቀስ፤ አንድ ስኬታማ ሴት የደገፈቻትና ያማከረቻት ተማሪ ለኃላፊነት በቅታ ማየቷ የራሷ ስኬት አድርጋ ልትቆጥረው እንደሚገባ፤ ይህ ሲሆን የምክርና ድጋፍ አገልግሎት መስጠት በሁለቱም ወገን ጥቅም ከፍተኛ እርካታ እንዳለው ተናግረዋል፡፡አገልግሎቱ ከ45 ዩኒቨርሲቲዎች የተውጣጡ 50 ለሚሆኑ ተማሪዎች ሲሆን፤ ከአንድ ወር በኋላ ከአንድ ሺ 500 በላይ የሁለተኛና ከዚያ በላይ ያሉ ተማሪዎች የምክርና ድጋፍ አገልግሎት እንደሚጀምር ተነግሯል፡፡አዲስ ዘመን ታህሳስ 13/2013
https://www.press.et/Ama/?p=37853
311
0ሀገር አቀፍ ዜና
ዋልያዎቹ በሴካፋ ዋንጫ ከዩጋንዳ ጋር ተደልድለዋል
ስፖርት
November 27, 2019
18
የ2019 የመካከለኛውና ምስራቅ አፍሪካ ዋንጫ(ሴካፋ) በዩጋንዳ አዘጋጅነት ከህዳር 27 እስከ ታህሳስ 9 ይካሄዳል፡፡ ውድድሩ በሦስት ምድብ ተከፍሎ የሚካሄድ ሲሆን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ዋልያዎቹ በምድብ አንድ ከኤርትራ ብሔራዊ ቡድን ጋር ተደልድለዋል፡፡ በዚሁ ምድብ አዘጋጇ ዩጋንዳና ቡሩንዲም ተደልድለዋል፡፡ በምድብ ሁለት በተጋባዥነት የምትሳተፈው ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ከሱዳን፣ ደቡብ ሱዳንና ሶማሊያ ጋር የተደለደለች ሲሆን በመጨረሻው ምድብ ኬንያ፣ ታንዛኒያ፣ ጅቡቲና ዛንዚባር መደልደላቸው ታውቋል፡፡ ርዋንዳ በዚህ ውድድር ጠንካራ ተፎካካሪ ትሆናለች ተብሎ ቢጠበቅም በበጀት እጥረት እንደማትካፈል ተረጋግጧል፡፡ ርዋንዳ በዚሁ የውድድር ዓመት በዩጋንዳ አዘጋጅነት ተካሂዶ በነበረው ከአስራ ሰባት ዓመት በታች የሴካፋ ዋንጫ ላይ በተመሳሳይ ምክኒያት ካለመሳተፏ ባሻገር ከቀናት በፊት በታንዛኒያ አዘጋጅነት ተካሂዶ በተጠናቀቀው የሴቶች ሴካፋ ዋንጫ ላይ በተመሳሳይ ምክኒያት መሳተፍ አለመቻሏ ይታወሳል ዋልያዎቹ ከሳምንት በፊት ለ2021 የካሜሩን አፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ የምድባቸውን ሁለተኛ ጨዋታ ባህርዳር ላይ በማድረግ ትልቅ የእግር ኳስ ደረጃ ያላትን ኮትዲቯርን ሁለት ለአንድ በሆነ ውጤት ማሸነፋቸው ይታወሳል፡፡ ይህም በቡድኑ ላይ ትልቅ መነቃቃት የፈጠረ ቢሆንም ቀጣዩን የማጣሪያ ጨዋታ ከበርካታ ወራት በኋላ ለሚያደርጉት ዋልያዎቹ ስጋት እንዳለው ሲነገር ቆይቷል፡፡ ዋልያዎቹ የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያውን ነሐሴ ወር ላይ ማካሄዳቸው አሁን የተፈጠረውን መነቃቃት እንዳያደበዝዘው እንደ ሴካፋ አይነት ውድድሮች አስተዋፅኦ ይኖራቸዋል ተብሎ ይታመናል፡፡ ዋልያዎቹ ከዚህ ቀደም በተደጋጋሚ የወዳጅነት ጨዋታዎችን በብዛት ማድረግ አለመቻላቸው ካተቀረፈ፣ የቡድኑ ስብስብም ለረጅም ጊዜ ተለያይቶ ሲገናኝ አሁን ያለው የአሸናፊነት መንፈስና መነቃቃት በነበረበት ላይገኝ ይችላል የሚሉ ስጋቶች አሉ፡፡ ዋልያዎቹ ቀጣዩን የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታ እስኪያደርጉ ቻንን በመሳሰሉ ዋንጫዎች አለመሳተፋቸው ተጨማሪ ጉዳት ቢሆንም እንደ ሴካፋ አይነት ውድድሮች ላይ መሳተፍ መቻላቸው አሰልጣኝ አብረሃም መብራቱ ቡድኑን ለመገንባት በሚያደርጉት ሂደት ትልቅ ፋይዳ እንደሚኖረው ይጠበቃል፡፡አዲስ ዘመን ኅዳር 17/2012 ቦጋለ አበበ
https://www.press.et/Ama/?p=23237
233
2ስፖርት
ኢትዮጵያውያን የደመቁባቸው ዓለም አቀፍ ክብሮች
ስፖርት
November 26, 2019
19
 የዓመቱ የምርጥ አትሌቶች ሽልማት እጩዎች ከሦስት ሳምንት በፊት ይፋ ሲደረግ አንድም ኢትዮጵያዊ አትሌት ከምርጥ አስር እጩዎች ውስጥ መካተት አልቻለም ነበር። ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ይህን ክብር ደጋግመው ማግኘት ቢችሉም ባለፉት ሁለት ዓመታት በሁለቱም ፆታ ከእጩዎቹ መካከል እንኳን ሳይካተቱ መቅረታቸው አስገራሚ ነበር። ያም ሆኖ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በዋናው ሽልማት በእጩነት ያልተካተቱበት አጋጣሚ በወጣቶች ወይም ከሃያ ዓመት በታች በእድሜ ክልል ውስጥ የሚገኙ አትሌቶች በሚሳተፉበት ሽልማት ሁለት ወንዶችና አንድ ሴት አትሌት መካተት ችላለች። ከእጩነት ባሻገርም ወጣቱ አትሌት ሰለሞን ባረጋ ሽልማቱን ማሸነፍ ችሏል። ባለፈው ቅዳሜ በሞናኮ በተካሄደው የሽልማት ስነስርዓት ላይ ኢትዮጵያውያን በኮማንደር ደራርቱ ቱሉ አማካኝነት ተጨማሪ ዓለም አቀፍ ሽልማት ማግኘት ችለዋል። እኤአ 1992ና 2000 ላይ በተካሄዱት የባርሴሎናና የሲድኒ ኦሊምፒኮች በአስር ሺ ሜትር የወርቅ ሜዳሊያዎችን ያጠለቀችው ጀግናዋ አትሌት ደራርቱ ቱሉ በዓለም አትሌቲክስ ‹‹ዘንድ የዓመቱ ምርጥ ሴት›› በሚል ሽልማት አግኝታለች። ደራርቱ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽንን በተቀዳሚ ምክትል ፕሬዘዳንትነት እየመራች ላሳየችው የላቀ አስተዋፅኦ ይህ እውቅና ተችሯታል። ደራርቱ በአፍሪካ አትሌቲክስ ኮንፌዴሬሽን የምክር ቤት አባል ስትሆን የምስራቅ አፍሪካ አትሌቲክስ ምክትል ፕሬዚዳንት በመሆንም እያገለገለች መገኘቷ ለሽልማቱ አብቅቷታል። የአስራ ዘጠኝ ዓመቱ ኢትዮጵያዊ አትሌት ሰለሞን ባረጋ የዘንድሮውን ዓመት የወጣትና ተስፈኛ አትሌቶች ሽልማት ለመጀመሪያ ጊዜ ማሸነፍ ችሏል። ሰለሞን በዶሃ በተካሄደው የዓለም ቻምፒዮና በአምስት ሺ ሜትር የብር ሜዳሊያ ከማጥለቁ በተጨማሪ በዓለም አገር አቋራጭ ቻምፒዮና አምስተኛ ደረጃን ይዞ አጠናቋል። በውድድር ዓመቱ የዓለም ከሃያ ዓመት በታች የአምስትና አስር ሺ ሜትር ርቀቶችን 12፡53፡04ና 26፡49፡46 በሆነ ጊዜ መሪ ሰዓቶች ማስመዝገቡ ለሽልማቱ አብቅቶታል። ባለፉት ሁለት ዓመታት በመካከለኛና ረጅም ርቀቶች ድንቅ ብቃት እያሳየ የሚገኘው አትሌት ሰለሞን ባረጋ ባለፈው ዓመትም ከመጨረሻዎቹ አምስት እጩዎች ስም ዝርዝር ውስጥ መካተቱ ይታወሳል።የደቡብ ፖሊሱ ክለብ አትሌት የሆነው ሰለሞን ባረጋ ከእድሜው ከፍ ብሎ ከታላላቆቹ ጋር በመወዳደር እያስመዘገበ ላለው ስኬት ባለፈው ዓመት ክለቡ የኢንስፔክተርነት ማዕረግ የሰጠው ሲሆን ባለፉት ሦስት ዓመታት እያሳየ ያለው አስደናቂ ብቃት ወደ ፊት ተስፋ እንዲጣልበት አድርጓል። ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ወደ ታላላቅ የውድድር መድረኮች መጥቶ በአጭር ጊዜ ውስጥ የስፖርት ቤተሰቡ አይን ማረፊያ የሆነው ወጣት አትሌት ሰለሞን ባረጋ ውጤቱና አስደናቂ ብቃቱ ኢትዮጵያ በቅርቡ በታላላቅ መድረኮች አረንጓዴውን ጎርፍ ዳግም የማየት ብሩህ ተስፋ እንዳላት ማሳያ መሆኑን በርካቶች ይመሰክሩለታል። ድንቅ የሩጫ ተሰጥኦው በመካከለኛና ረጅም ርቀቶች በቅርብ ጊዜ ውስጥ ዙፋን ላይ እንደሚወጣ የስፖርቱ ባለሙያዎች በተደጋጋሚ መስክረውለታል። በ2018 የውድድር ዓመት የአምስት ሺ ሜትር አጠቃላይ የዳይመንድ ሊግ አሸናፊ መሆን የቻለው ሰለሞን ባረጋ በርቀቱ ከሃያ ዓመት በታች የዓለም ክብረወሰንን 12፡ 43፡02 በሆነ ሰዓት ከመጨበጡ ባሻገር እኤአ 2005 ላይ ቀነኒሳ በቀለ በርቀቱ ካስመዘገበው ሰዓት ወዲህ ፈጣን ሰዓት ሆኖ መመዝገቡ ይታወሳል። በዶሃው የዓለም ቻምፒዮና ኢትዮጵያ በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ በሦስት ሺ ሜትር መሰናክል የብር ሜዳሊያ እንድታገኝ ያስቻለው አትሌት ለሜቻ ግርማ ከአምስቱ ተስፈኛ እጩዎች መካከል አንዱ በመሆን ከሰለሞን ጋር ሽልማቱን ለማሸነፍ ተፎካክሯል። ለሜቻ በውድድር ዓመቱ በርቀቱ ከሃያ ዓመት በታች መሪ የሆነውን ሰዓት በ8፡01፡36 ያስመዘገበ ሲሆን የኢትዮጵያን ክብረወሰንም የግሉ ማድረግ ችሏል። በዓለም ቻምፒዮናውም የወርቅ ሜዳሊያ ያመለጠው በ0ነጥብ01 ማይክሮ ሰከንድ ተቀድሞ እንደነበረ አይዘነጋም። ከሁለቱ ኢትዮጵያን እጩዎች ጎን ለጎን ብራዚላዊው የአራት መቶ ሜትር መሰናክል ተወዳዳሪ አሊሰን ዶስ ሳንቶስ፣ ኖርዌያዊው አትሌት ጃኮብ ኢንግብሪትሰን፣ ዩክሬናዊው መዶሻ ወርዋሪ ማይክሃይሎ ኮክሃን በሽልማቱ ተፎካካሪ ነበሩ። በወጣት ሴቶች ዘርፍ ከሰለሞን ባረጋ ጋር ተመሳሳይ ሽልማት ማሸነፍ የቻለችው ዩክሬናዊታ ያሮስላቫ ማሁቺክ ናት። ይህች አትሌት በከፍታ ዝላይ የተሻለ አቅም ያላት አትሌት ስትሆን 2 ሜትር ከ04 ሳንቲ ሜትር በመዝለል የክብረ ወሰን ባለቤት ናት። በዶሃው የዓለም ቻምፒዮናም የብር ሜዳሊያ አግኝታለች። ከዚህም ባሻገር አውሮፓ ቻምፒን መሆን የቻለች ጠንካራ አትሌትም ናት። ይህን ሽልማት ለማሸነፍ ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ለምለም ኃይሉ ከመጨረሻዎቹ አምስት እጩዎች ውስጥ ተካታ ተፎካካሪ መሆን ችላለች። ጃማይካዊቷ ብሪታኒ አንደርሰን፣ የኢኳዶሯ እርምጃ ተወዳዳሪ ግሌንዳ ሞርጆን፣ አሜሪካዊቷ 100 ሜትር የወጣቶች ባለክብረወሰን ሻካሪ ሪቻርድሰን የመጨረሻዎቹ ተፎካካሪዎች ነበሩ። ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ከእጩዎች መካከል ያልተካተቱበት የዓመቱ የምርጥ አትሌቶች ሽልማት በወንዶች ዘርፍ ኬንያዊው ኢሉድ ኪፕቾጌ ለሁለተኛ ተከታታይ ጊዜ ማሸነፍ ችሏል። የማራቶን ፈርጡ ኢሉድ ኪፕቾጌ በውድድር ዓመቱ ሁለት ፉክክሮች ላይ ብቻ ቢታይም ያስመዘገበው ታሪክ ሽልማቱን ለማሸነፍ አብቅቶታል። ኪፕቾጌ በውድድር ዓመቱ የለንደን ማራቶንን ክብረወሰን በማሻሻል በ2፡02፡37 ሰዓት ማሸነፉ ይታወሳል። ከዚህ በላይ ግን ከወር በፊት በቬና ማራቶን የሰው ልጅ የብቃት ጥግ ወሰን እንደሌለው ያሳየበት ውድድር አይዘነጋም። ኪፕቾጌ ከትጥቅ አምራች ኩባንያው ናይኪ ጋር በመሆን በተለያዩ ቴክኖሎጂዎች ታግዞም ቢሆን ማራቶንን ከሁለት ሰዓት በታች ማጠናቀቅ እንደሚቻል አስመስክሯል። 1፡59፡40 በሆነ ሰዓት ማራቶንን በማጠናቀቅ በታሪክ የመጀመሪያው አትሌት ለመሆን ቢበቃም የተመዘገበው ሰዓት በዓለም ክብረወሰንነት እንዳልተያዘ ይታወሳል።ያም ሆኖ ዓለም ዓቀፍ ሽልማቱን ከማሸነፍ አላገደውም። ባለፈው የዶሃ የዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮና የአስር ሺ ሜትር ቻምፒዮን የሆነው ዩጋንዳዊው ጆሹአ ቺፕቴጌ የመጨረሻዎቹን አምስት እጩዎች መቀላቀል የቻለ ሲሆን፣ አሜሪካዊው ምርኩዝ ዘላይ ሳም ኬንድሪክስ በውድድር ዓመቱ ካደረጋቸው አስራ ሰባት ከቤት ውጪ ውድድሮች አስራ ሁለቱን በድል በማጠናቀቅ የሽልማቱ ተፎካካሪ ነበር።አሜሪካዊው የአጭር ርቀት አትሌት ኖህ ላይልስና ኖርዌያዊው የአጭር ርቀት ኮከብ አትሌት ካርልስተን ዋርሆልም የሽልማቱ ተፎካካሪ ነበሩ። በሴቶች መካከል የተደረገውን ሽልማት አሜሪካዊቷ ደሊላ ሙሃመድ አሸንፋዋለች። በዓመቱ በ400 ሜትር ያሳየችው አቋም ለሽልማቱ ያበቃት ሲሆን አትሌቷ በሃገር አቀፍ ቻምፒዮና 52ሰከንድ ከ20ማይክሮ ሰከንድ መበመግባት ቀዳሚ ናት። በ400 ሜትር መሰናክል በራሷ የተያዘውን ክብረወሰን 52ሰከንድ ከ16ማይክሮ ሰከንድ በማሻሻል ብቃቷን አስመስክራለች። በ4በ 400 ሜትርም በተመሳሳይ የዓለም ቻምፒዮን ናት። በርዝመት ዝላይ ቬንዙዌላዊቷ ዩሊማር ሮጃስ ለመጨረሻው ዙር በመድረስ የተፎካከረች ሲሆን የአጭር ርቀት ተወዳዳሪዋ ጃማይካዊት አትሌት ሼሊ- አን ፍራዘር-ፕረይሲ፣የማራቶን ክብረወሰንን ሰበረችው ኬንያዊት አትሌት ብርጊድ ኮስጊ፣በዶሃው የዓለም ቻምፒዮና በ1ሺ500 እና10ሺ ሜትር አሸናፊ የሆነችው ትውልደ ኢትዮጵያዊቷ የኔዘርላንድስ አትልት ሲፋን ሃሰን ለመጨረሻ እጩነት ቀርበው ተፎካካሪ ሆነዋል።አዲስ ዘመን  ህዳር 16 ቀን 2012 ዓ.ምቦጋለ አበበ
https://www.press.et/Ama/?p=23174
776
2ስፖርት
”በኢትዮጵያና ሱዳን ድንበር አካባቢ የተፈጠረው የጸጥታ ችግር ከተሳሳተ ግምት የመነጨ ነው” – አምባሳደር ዲና ሙፍቲ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ
ሀገር አቀፍ ዜና
December 20, 2020
43
ዋቅሹም ፍቃዱአዲስ አበባ፡- በኢትዮጵያና ሱዳን ድንበር አካባቢ የተስተዋለው የፀጥታ ችግር በተወሰኑ የሱዳን ሚሊሻዎች እና ጥቂት ወታደሮች የተሳሳተ ግምት በመነጨ በድንበር አካባቢ ተኩስ በመክፈታቸው ምክንያት የተፈጠረ እንደነበር የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ገለጹ። አምባሳደር ዲና በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደተናገሩት፤ የህወሓት ጁንታ በመከላከያ ሠራዊት ላይ የፈጸመውን ጥቃት ተከትሎ መንግሥት በሰሜኑ የአገራችን ክፍል ህግ የማስከበር ሥራ ላይ ባለበት በአሁኑ ወቅት የኢትዮጰያ በድንበር አካባቢ ትኩረት አይሰጥም በሚል የተሳሳተ ግምት የተወሰኑ የሱዳን ሚሊሻዎች እና ጥቂት ወታደሮች የተሳሳተ ግምት በመነጨ በድንበር አካባቢ ተኩስ ከፍተዋል። ይሁን እንጂ መንግሥት ሙሉ ትኩረቱን በሰሜን የህግ ማስከበር ላይ ቢያደርግም በድንበር አካባቢም የጸጥታ ችግር እንዳይከሰት በትኩረት እየሠራ መሆኑን የገለጹት አምባሳደር ዲና፤ በድንበር አካባቢ ያሉ የሱዳን ሀይሎች ግን “የኢትዮጵያ መንግሥት በድንበር አካባቢ ትኩረት አይስጥም” በማለት በተሳሳተ ግምት የድንበር አካባቢ ህዝባችን ለማጥቃት ተኩስ የከፈቱ ቢሆንም በመከላከያ ሠራዊትና በአካባቢው ሚሊሻ እንደ ተመከቱ ተናግረዋል። የደረሰ ጉዳት ካለም የጉዳቱ መጠን ለወደፊት ተጣርቶ የሚገለጽ ይሆናል ብለዋል። እንደ አምባሳደር ዲና ገለጻ፤ ግጭቱ የሁለቱም አገራትም መሪዎችም ፍላጎት አይደለም። የኢትዮጵያ መንግሥትም ጉዳዩን አስመልክቶ ከሱዳን ጋር ተነጋግሯል። በቀጣይም በአካባቢው አልፎ አልፎ ለሚከሰተው ችግር መንግሥት ትኩረት ሰጥቶ በአጭር ጊዜ ውስጥ ዘላቂ እልባት እንዲያገኝ ይሰራል። የተጀመረው የህግ ማስከበር ስራም በአጭር ጊዜ ውስጥ ስለተጠናቀቀ ወንጀለኞችንም አድኖ ለመያዝ ከሱዳን መንግሥት ጋር በቅርበት እየሰራ ይገኛል። በአካባቢው ሰላምና መረጋጋት እንዳይኖርና አርሶ አደሩ ምርቱን በአግባቡ እንዳይሰበስብ ፍላጎታቸውን በትርምስ ለማሳካት የሚንቀሳቀሱ ሀይሎች በርካታ መሆናቸውን የገለጹት አምባሳደር ዲና፤ ኢትዮጵያ ግን የሁለቱም አገራት ዘላቂ ጥቅሞች በሚያስከብር መልኩ ከሰዳን ጋር እንደምትሰራ፣ እየሰራችም እንደ ሆነ ተናግረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ፣ ሰሞኑን ጉዳዩን አስመልክቶ በሰጡት አስተያየት “የተፈጠረውን ችግር ለማባባስ የሚጥሩ ኃይሎች፣ የኢትዮጵያና የሱዳን ታሪካዊ ትስስር ካለማወቅና ችግሮቻቸውን በድርድር ሲፈቱ መቆየታቸው ካለመገንዘባቸው የተነሳ ነው” ማለታቸው አይዘነጋም።አዲስ ዘመን ታህሳስ 11/2013
https://www.press.et/Ama/?p=37691
258
0ሀገር አቀፍ ዜና
ቢሮው 73 ከመቶ ያህል ሰብል መሰብሰቡን አስታወቀ
ሀገር አቀፍ ዜና
December 20, 2020
11
-127 ሚሊዮን ኩንታል ሰብል ለመሰብሰብ እቅድ ተይዟል አስናቀ ፀጋዬአዲስ አበባ፡- በዘንድሮው የመኸር እርሻ ከ73 ከመቶ በላይ የሚሆን ሰብል መሰብሰቡን የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ አስታወቀ። 127 ሚሊየን ኩንታል ምርት ለመሰብሰብም መታቀዱ ተገልጿል። የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ተስፋሁን መንግስቴ ለአዲስ ዘመን እንደገለፁት፤ የዘንድሮው የግብርና ምርት አሰባሰብ በጎርፍና መሬት መንሸራተት፣ አምበጣ፣ ኮቪድና ጦርነት የተፈተነ ቢሆንም 73 ከመቶ በላይ የሚሆነውን ምርት መሰብሰብ ተችሏል። እንደ ምክትል ቢሮ ኃላፊው ገለፃ፤ በክልሉ የተከሰተው የአምበጣ መንጋ 900 ሄክታር የሚጠጋ መሬት ላይ የነበረ ሰብል ቢያወድምም፤ አምበጣው የተከሰተበት አካባቢ እምብዛም ምርታማ ባለመሆኑ ተፅእኖው ያን ያህል የከፋ አልሆነም። በክልሉ ባጠቃላይ 4 ሚሊዮን 282 ሺ 517 ሄክታር መሬት በሰብል መሸፈኑን የተናገሩት ምክትል ቢሮው ኃላፊው፤ እስካሁን ድረስ 3 ሚሊዮን 112 ሺ 165 ሄክታር ሰብል መሰብሰቡን አስታውቀዋል። በዚህም ከ73 ከመቶ በላይ ሰብል መሰብሰብ መቻሉን ጠቁመዋል። በዚሁ የሰብል አሰባሰብ ወቅት 115 የሚሆኑ ኮምባይነሮችን በመጠቀም 847 ሺ 515 ኩንታል ስንዴ ለመውቃት መቻሉንም ገልፀዋል። ይህም 23 ሺ 30 ሄክታር የሚጠጋ መሬት እንደሆነና ከባለፈው ዓመት ጋር ሲወዳደር የተሻለ አፈፃፀም እንደሆነም ምክትል ቢሮ ኃላፊው ጠቁመዋል። በግዳጅ ላይ ያሉ የአማራ ክልል ሚሊሻ አባላትን በማሳተፍ ሰብል እንዲሰበሰብ መደረጉንም ያነሱት ምክትል ቢሮ ኃላፊው፤ ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ ሊመጣ ስለሚችል በከፍተኛ ርብርብ ሰብል የማሰባሰብ ተግባሩ እየተከናወነ እንደሚገኝም አመልክተዋል። በዚህ ዓመት ባጠቃላይ ወደ 127 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ለመሰብሰብ እንደታቀደና በዓመቱ የታየው መልካም የዝናብ መጠንና ስርጭት የዘንድሮውን የምርት አሰባሰብ የተሻለ እንደሚያደርገውም ጠቅሰዋል። ያጋጠሙ ችግሮች እንዳሉ ሆነው የሰብል አሰባሰቡ አምና ከነበረው ጋር ሲነፃፀር መልካም የሚባል መሆኑንም ምክትል ቢሮ ኃላፊው ጠቁመዋል። የሰብል አሰባሰብ አጠቃላይ አፈፃፀም የምርት ግምገማ ከተካሄደ በኋላ የሚታወቅ መሆኑንም ምክትል ቢሮ ኃላፊው ጠቁመው፤ ቀሪ 27 ከመቶ የሚሆነውና በደጋማው የክልሉ ክፍሎች የሚገኘው ያልተሰበሰበ ሰብል እንደደረሰ በቀጣይ እንደሚሰበሰብም ጠቅሰዋል። በምርት አሰባሰብ ወቅት ብክነት እንዳያጋጥም እንደተለመደው ኮምባይነሮችንና ሌሎችንም የግብርና ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም ምርት እየተሰበሰበ መሆኑንም ምክትል ቢሮ ኃላፊው አያይዘው ገልፀዋል። በጥቅሉ የክልሉ የዘንድሮው የሰብል አሰባሰብ ያለበት ደረጃ መልካም የሚባል መሆኑንም አስታውቀዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 11/2013
https://www.press.et/Ama/?p=37698
288
0ሀገር አቀፍ ዜና
ሆፕ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ በአምስት የትምህርት መስኮች ያሠለጠናቸውን 424 ተማሪዎች አስመረቀ
ሀገር አቀፍ ዜና
December 20, 2020
10
ዳንኤል ዘነበ አዲስ አበባ ፦ሆፕ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ በአምስት የትምህርት መስኮች በመጀመሪያ ዲግሪና እና በድህረ ምረቃ መርሐ ግብር ያስለጠናቸውን 424 ተማሪዎችን ትናንት አስመረቀ። በዕለቱ የተመረቁት ተማሪዎች በ2012 ዓ.ም መመረቅ የነበረባቸው እና በኮቪድ 19 ወረርሽኝ ምክንያት ትምህርት በመቋረጡ ምክንያት የተላለፈ መሆኑም ታውቋል፡፡የዩኒቨርሲቲ ኮሌጁ ፕሬዚዳንት ዶክተር ተረፈ ፈየራ በምረቃው ሥነ ሥርዓት ላይ እንደተናገሩት፤ የመማር ማስተማር ሂደቱ በኮቪድ -19 ወረርሽኝ ምክንያት ቢቋረጥም፤ ተማሪዎቹ የማካካሻ ትምህርት ወስደው ለምርቃት በቅተዋል። በዚህም ዩኒቨርሲቲ ኮሌጁ በአምስት የትምህርት መስኮች በመጀመሪያ ዲግሪ እና በድህረ ምረቃ መርሐ ግብር ሲያስተምራቸው የነበሩ 424 ተማሪዎችን አስመርቋል ብለዋል።ዩኒቨርሲቲ ኮሌጁ ካስመረቃቸው አጠቃላይ ተማሪዎቹ 368 በመጀመሪያ ዲግሪ፤ 44ቱ ደግሞ በድህረ ምረቃ መርሐ ግብር በቀንና በማታው የትምህርት መርሐ ግብር ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የነበሩ መሆናቸውን ገልፀዋል። በመጀመሪያ ዲግሪ ለሰባት ተከታታይ ጊዜያት በሁለተኛ ዲግሪ ደግሞ ለመጀመሪያ ጊዜ ማስመረቁን ተናግረዋል።«ዩኒቨርሲቲ ኮሌጁ የትምህርት ፍላጎትና አቅም እያላቸው ከፍለው መማር የማይችሉ ችግረኛ ወጣቶችንም የከፍተኛ ትምህርት ዕድል ይሰጣል» የሚሉት ፕሬዚዳንቱ፤ ወጣቶቹ ራሳቸውንና ቤተሰቦቻቸውን መርዳት እንዲችሉ ብሎም በሀገር ግንባታ ላይ አዎንታዊ ሚና እንዲኖራቸው የራሱን ድርሻ በማበርከት ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል።ተቋሙ በየዓመቱ ከ200 ተማሪዎች በላይ የነፃ የትምህርት እድል ተጠቃሚ እያደረገ መሆኑን በመጠቆምም፤ በዚሁ መሰረት በዲግሪ መርሐ ግብር ተመራቂ ከሆኑት 368 ተማሪዎች 58 በነፃ እድል ተጠቃሚ የነበሩ መሆኑን አብራርተዋል። ሆፕ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጁ ባለፉት ሰባት ዓመታት በመጀመሪያ ዲግሪ 1ሺህ488 ተማሪዎች፣ ለመጀመሪያ ጊዜ ደግሞ 44 ተማሪዎችን በድህረ ምረቃ፤ በአጠቃላይ 1ሺህ532 ተማሪዎችን ያስመረቀ መሆኑ ታውቋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 11/2013
https://www.press.et/Ama/?p=37703
205
0ሀገር አቀፍ ዜና
ተመራቂዎች ቴክኖሎጂን በማህበረሰቡ ውስጥ ለማስረጽ መስራት እንዳለባቸው ተገለጸ
ሀገር አቀፍ ዜና
December 20, 2020
7
ፋንታነሽ ክንዴአዲስ አበባ፡- የከፍተኛ ትምህርት ተቋም የሚወጡ ተመራቂዎች ሳይንስ በማህበረሰቡ ውስጥ ባህል ሆኖ እንዲሰርጽ መስራት እንዳለባቸው የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ፕሮፌሰር አፈወርቅ ካሱ ገለፁ፡፡ የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ትናንት ተማሪዎችን አስመርቋል፡፡በምርቃት ስነ-ስርዓቱ ላይ የተገኙት ፕሮፌሰር አፈወርቅ፣ ለተመራቂ ተማሪዎችና ለወላጆቻቸው እንኳን ደስ ያላችሁ መልዕክት ካስተላለፉ በኋላ፤ “ተመራቂዎች በዩኒቨርሲቲ ቆይታቸው ያካበቱትን እውቀትና ክህሎት ከፍ ላለ ውጤት ለማዋል መዘጋጀት ይጠበቅባቸዋል” ሲሉ አሳስበዋል፡፡ እንደ ፕሮፌሰር አፈወርቅ ገለጻ፤ ሳንይንስና ቴክኖሎጂ የአንድ አገር ሁለንተናዊ እድገት መሰረት ነው፡፡ ሳይንስ የኅብረተሰባችንን ሁለንተናዊ እድገት እንዲደግፍና የዕለት ከዕለት ህይወታቸው አካልና ባህል እንዲሆን ያስፈልጋል፡፡ የሳይንስ ባህል ግንባታ ላይ ትኩረት ሰጥቶ መስራት ያስፈልጋል፡፡ ተመራቂዎችም ሳይንስ ባህል ሆኖ ወደ ማህበረሰባችን በመስራት እንዲሰርጽ ሊደግፉንና ኃላፊነታቸውን ሊወጡ ይገባል፡፡በእውቀትና በክህሎት ያደገ ማህበረሰብ ቴክኖሎጂ የመፍጠርና የመጠቀም አቅሙ ያድጋል፤ ህግና ስርዓት የሚያከብርና የአካባቢውን ችግር የሚፈታ ሀሳብ ያመነጫል፤ ያሉት ፕሮፌሰር አፈወርቅ፤ ከዚህ አኳያ አገራችን አሁን ካለችበት ዘርፈ ብዙ ችግር እንድትወጣና ከፊት ለፊቷ ያሉትን በርካታ ተስፋዎች እንድትጠቀም ለማስቻል ተመራቂዎች መስራት እንዳለባቸውም አሳስበዋል፡፡የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶክተር ለሚ ጉታ በበኩላቸው እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ ከግብርና መር ወደ ኢንዱስትሪ መር ኢኮኖሚ እንድትሸጋገር በማድረግ ረገድ ዩኒቨርሲቲው የተሰጠውን ኃላፊነት እየተወጣ ሲሆን፤ ለዚህ የሚሆን በሳይንስና ቴክኖሎጂ የሰለጠነ አቅም ያለው የሰው ኃይል እያፈራ ይገኛል፡፡ በዩኒቨርሲቲው መምህራን የምርምር ሥራዎችም እያደጉ በመምጣታቸው በአገራዊ ፕሮጀክቶች ላይ በመሳተፍ ጭምር በኢንዱስትሪ-ዩኒቨርሲቲ ትስስሩ ትልቅ ሚና እየተወጣ ይገኛል፡፡በምርምርና ልህቀት ማዕከላቱ አማካኝነትም በህዋ ሳይንስ ላይ የበኩሉን ለመወጣት እየሰራ ሲሆን፤ ከዚህ በተጓዳኝ ለህብረተሰቡም ሙያዊ ድጋፍ እየሰጠ ይገኛል፡፡ በቀጣይም በርካታ ግዙፍ የምርምር ፕሮጀክቶችን እየሰራ ሲሆን፤ ኮሮናን በመዋጋት ጭምር ሲወጣ የነበረው ጠንካራ ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ነው ዶክተር ለሚ ያረጋገጡት፡፡ተመራቂ ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲው ቆይታቸው ላሳዩት መልካምና ዓርአያነት ላለው ስነምግባር በማመስገን ለተመራቂዎችና ለቤተሰቦቻቸው እንኳን ደስያላችሁ ያሉት ዶክተር ለሚ፤ ለተመራቂ ተማሪዎች “አገሪቱን ወደፊት የሚያራምዱ ተግባራትን ማከናወን እንዲሁም የህዝቡን ኑሮ የማሻሻልና ተገቢውን አገልግሎት መስጠት ከእናንተ ይጠበቃል እና የመማራችሁን ትርጉም በመገንዘብ ይሄንኑ በታላቅ ትጋትና ሥነምግባር እንድትፈጽሙ አደራ እላለሁ” ሲሉ አሳስበዋል፡፡ መጪው ዘመን በተሰማራችሁበት የስራ መስክ መልካም ውጤት የምታመጡበት እና ህዝባችሁን በቀናነት የምታገለግሉበት፣ አገራችሁንም ወደ ብልጽግና የምታሸጋግሩበት ዘመን ይሁንላችሁ፤ ሲሉም መልካም ምኞታቸውን ገልጸውላቸዋል፡፡ዩኒቨርሲቲው ትናትን 1ሺህ240 ከመጀመሪያ ዲግሪ እስከ ሦስተኛ ዲግሪ በተለያየ መርሐ ግብር ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች ያስመረቀ ሲሆን፤ ከተመራቂዎች ውስጥ 1ሺህ 228 በመጀመሪያ ዲግሪ፤ 2 ደግሞ በዶክትሬት ዲግሪ የተመረቁ ናቸው፡፡ በዕለቱ ከተመረቁት ውስጥም 274 ሴት ተመራቂዎች መሆናቸው ተገልጿል፡፡አዲስ ዘመን ታህሳስ 11/2013
https://www.press.et/Ama/?p=37704
336
0ሀገር አቀፍ ዜና
ተፎካካሪ ፓርቲዎች እና ህዝቡ መጪው ምርጫ በስኬት እንዲጠናቀቅ የበኩላቸውን እንዲወጡ ጥሪ ቀረበ
ሀገር አቀፍ ዜና
December 20, 2020
9
በጋዜጣው ሪፖርተርአዲስ አበባ፡- በህጋዊ መንገድ ተመዝግበው በመንቀሳቀስ ላይ የሚገኙ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች እና መላው የአገሪቱ ህዝብ ወደ እውነተኛ የዲሞክራሲ ስርዓት ለመሸጋገር የተወሰዱ የአገራዊ ለውጥ እርምጃዎችን እንደ መልካም አጋጣሚ በመጠቀም መጪው ምርጫ ሰላማዊ፣ ዲሞክራሲያዊ፣ ነጻና በሂደቱም ሆነ በውጤቱ በህዝቡ ዘንድ ተቀባይነት ያለው ሆኖ እንዲጠናቀቅ የበኩላቸውን አስተዋጽዖ እንዲያደርጉ የብልጽግና ፓርቲ ጥሪ አቀረበ። የብልጽግና ፓርቲ ማዕከላዊ ኮሚቴ ከታህሳስ 8 ቀን 2013 ዓ.ም ጀምሮ ለሁለት ቀናት ሲያካሂድ የቆየውን መደበኛ ስብሰባ አጠናቅቋል። በጉባኤው ማጠናቀቂያ ባወጣው መግለጫ እንዳስታወቀው፤ ብልጽግና ፓርቲ =በመጪው ምርጫ ጠንካራ ተወዳዳሪ ሆኖ በውጤታማነት እንዲያጠናቅቅ በሚያስችሉት ጉዳዮች ላይ መክሮ አቅጣጫ አስቀምጧል። በአገሪቱ በህጋዊ መንገድ ተመዝግበው የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎችም ለምርጫው ውጤታማነት እና በህዝብ ዘንድ ተአማኒነት ኖሮት እንዲጠናቀቅ በማድረግ በኩል የሚጠበቅባቸውን ሁሉ ማበርከት ይኖርባቸዋል። ፓርቲው ባወጣው መግለጫ እንዳመለከተው፤ የፓርቲው ማዕከላዊ በሰላም፣ በልማት፣ በዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታና መጪውን አገራዊ ምርጫ በተመለከቱ አጀንዳዎች ላይ በጥልቀት ተወያይቶ አቅጣጫዎችን አስቀምጧል። በዋናነት ባለፉት ሁለት ዓመታት ተኩል በኢትዮጵያ የታየው ለውጥ በርካታ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ፈተናዎችን ተጋፍጦ የኢትዮጵያን ብልጽግና እውን ለማድረግ ሰፊ እድል የፈጠረና አገራችንን ከብተና አደጋ ያዳነ መሆኑ በውይይቱ ከስምምነት ተደርሷል። በተለይም ብልጽግና ውሁድ ህብረ ብሄራዊ አገራዊ ፓርቲ ሆኖ መደራጀቱ አንድ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ማህበረሰብ ለመገንባት ከፍተኛ እድል ከመፍጠሩም በላይ ከአገሪቱ ፖለቲካዊ ተሳትፎ ተገለው የዳር ተመልካች የነበሩ በርካታ የኅብረተሰብ ክፍሎችን ለማቀፍና ለማሳተፍ የቻለ የመጪው ትውልድ ፓርቲ መሆኑ ተረጋግጧል። በአገራዊ ለውጡ የተገኙ ድሎችን ጠብቆ በማስቀጠል ወደ ሁለንተናዊ ብልጽግና ማሳደግ እንደሚያስፈልግ የተገለጸ ሲሆን ለዚህም የፓርቲውን መርሆዎች፣ እሴቶችና አሰራሮችን በጥብቅ ዲሲፕሊን ተግባራዊ ማድረግና ጠንካራ ተቋማዊ ባህል መገንባት አስፈላጊ መሆኑ ከስምምነት ተደርሷል። ከዚህ በተጓዳኝ፣ ኮሚቴው በሁለቱ ቀናት መደበኛ ስብሰባው በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ በጥልቀት ከተወያየ በኋላ የሚከተሉትን አቅጣጫዎች አስቀምጧል። ከእነዚህ መካከል አንዱ የቀጣዩን ምርጫ የሚመለከት ሲሆን፤ ብልጽግና ፓርቲ በመጪዉ ምርጫ ጠንካራ ተወዳዳሪ ሆኖ በውጤታማነት እንዲያጠናቅቅ በፓርቲው ማኒፌስቶ ላይ በጥልቀት ተወያይቶ አጽድቆታል። መላው የፓርቲው አመራሮችና አባላት የጸደቀውን ማኒፌስቶ መሰረት በማድረግ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት እንዲያደርጉ አቅጣጫ ተቀምጧል። በህጋዊ መንገድ ተመዝግበው በመንቀሳቀስ ላይ የሚገኙ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ወደ እውነተኛ የዲሞክራሲ ስርዓት ለመሸጋገር የተወሰዱ የአገራዊ ለውጥ እርምጃዎችን እንደ መልካም አጋጣሚ በመጠቀም መጪው ምርጫ ሰላማዊ፣ ዲሞክራሲያዊ፣ ነጻና በሂደቱም ሆነ በውጤቱ በህዝቡ ዘንድ ተቀባይነት ያለው ሆኖ እንዲጠናቀቅ የበኩላቸውን አስተዋጽዖ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርቧል። መላው የአገሪቱ ህዝቦች ባለፉት ሁለት ተኩል ዓመታት በኢትዮጵያ የታዩ ለውጦችና የተገኙ ድሎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ፣ መጪው አገራዊ ምርጫ ሰላማዊ፣ ዲሞክራሲያዊ፣ ነጻና ተቀባይነት ያለው ሆኖ እንዲጠናቀቅና የዜጎች ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ብልጽግና የተረጋገጠባት ጠንካራ አገር ለመገንባት በሚደረገው ርብርብ ውስጥ የሚጠበቅባቸውን አስተዋጽዖ ሁሉ እንዲያደርጉም ነው ፓርቲው ጥሪውን ያስተላለፈው።
https://www.press.et/Ama/?p=37697
361
0ሀገር አቀፍ ዜና
«በአገራችን ሰፊውን ህዝብ በአግባቡ ሊያንቀሳቅሱ የሚችሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች አልተፈጠሩም»ዶክተር ዲማ ነገዎ የፖለቲካ ምሁር
ሀገር አቀፍ ዜና
December 21, 2020
10
አስቴር ኤልያስ አዲስ አበባ፡- በኢትዮጵያ ሰፊውን ህዝብ በአግባቡ ሊያንቀሳቅሱ እና ሊያነሳሱ የሚችሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች ገና አልተፈጠሩም ሲሉ የፖለቲካ ምሁሩ ዶክተር ዲማ ነገዎ ተናገሩ። ዶክተር ዲማ፣ በወቅታዊ አገራዊ ጉዳዮች ላይ ከአዲስ ዘመን ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ እንደተናገሩት፤ በአገሪቱ አንዱ እና ትልቁ ችግር የፖለቲካ አደረጃጀት ጉዳይ ነው። በዚህም እስካሁን ሰፊውን ህዝብ ሊያንቀሳቅሱ የሚችሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች መፈጠር አልቻሉም።“በአገራችን እስካሁን ድረስ የፖለቲካ ቡድኖች እንጂ የፖለቲካ ፓርቲዎች የሉም” የሚሉት ዶክተር ዲማ፤ ከዚህም የተነሳ “ሰፊውን ህዝብ በአግባቡ ሊያንቀሳቅሱ እና ሊያነሳሱ የሚችሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች ገና አልተፈጠሩም” ብለዋል።በቀጣይ በአገራችን የተሻለ ዴሞክራሲያዊ ስርዓት እንዲፈጠር የፖለቲካ ፓርቲዎች መፈጠር መቻል አለባቸው የሚል እምነት አለኝ ያሉት የፖለቲካ ምሁሩ ዶክተር ዲማ፤ ለዚህ ምክንያታቸው ደግሞ በአገሪቱ ያሉት የፖለቲካ ፓርቲዎች በትክክል የህዝብን ፍላጎት ያገናዘበ እንቅስቃሴ ሲያድርጉ ባለመታየታቸው የፖለቲካ ፓርቲዎች ናቸውለማለት የማያስችል በመሆኑ እንደሆነ አመልክተዋል።እንደ ዶክተር ዲማ ገለጻ፤ አንድ የፖለቲካ ፓርቲ መሆን የሚጠበቅበት የሕዝቡን ልዩ ልዩ ጥቅም የሚያንጸባርቅ እንጂ የተወሰነውን ቡድን ስሜት ብቻ የሚከተል መሆን የለበትም። ስለዚህ ሰፋ ያለውን የህዝቡን ፍላጎት የሚያንጸባርቁ የፖለቲካ ድርጅቶች መፈጠር አለባቸው። እስካሁን ያሉት በቡድን ደረጃ ነው። ስለሆነም ትልቁ የሚቀረው ነገር ቢኖር በትክክል የተዋቀሩና ህዝብን መሰረት ያደረጉ የፖለቲካ ፓርቲዎች መፈጠር እንደሚኖርባቸው ማወቅ ነው። ለተቋማት መገንባት ደግሞ ሰፋ ያለ ፍላጎት ላይ የተመሠረቱ የፖለቲካ ፓርቲዎች ያስፈልጋሉ።በኢትዮጵያ ውስጥ የተረጋጋ እና ዴሞክራሲያዊ የፖለቲካ ስርዓት ለመገንባት ቢያንስ ገለልተኛ የሆነ የአገሪቱን እና ህዝቡን የሚያገለግል የመንግሥት ስርዓት መኖር አለበት የሚለውም ጉዳይ ሊተኮርበት እንደሚገባ የሚናገሩት ዶክተር ዲማ፤ የፖለቲካ ፓርቲዎችም በስርዓት መገንባት እና መደራጀት እንዳለባቸው ገለጸዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 12/2013
https://www.press.et/Ama/?p=37768
218
0ሀገር አቀፍ ዜና
ጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አህመድ ከምሥራቅ አፍሪካ ሀገራት መሪዎች ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አደረጉ
ሀገር አቀፍ ዜና
December 21, 2020
8
በጋዜጣው ሪፖርተር አዲስ አበባ፡- የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ከምስራቅ አፍሪካ ሀገራት መሪዎች ጋር የሁለትዮሽ ውይይት ማድረጋቸውን በትዊተር ገጻቸው ገልጸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በ38ኛው አስቸኳይ የኢጋድ የመሪዎች ጉባዔ ላይ ለመሳተፍ ጅቡቲ ይገኛሉ። ጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ በትዊተር ገጻቸው እንዳሰፈሩት፤ በ38ኛው አስቸኳይ የኢጋድ የመሪዎች ጉባዔ ላይ ለመሳተፍ ጅቡቲ መግባታቸውን ተከትሎ፤ ከሱዳኑ ጠቅላይ ሚኒስትር አብደላ ሓምዶክ፣ ከሶማሊያው ፕሬዚዳንት መሀመድ ፋርማጆ፣ ከኬንያው ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ እና ከደቡብ ሱዳን ምክትል ፕሬዚዳንት ሬቤካ ንያዴግ ዲ ማቢዮር ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አድርገዋል። መሪዎቹ ጁቡቲ እየተካሄደ በሚገኘው 38ኛው አስቸኳይ የኢጋድ የመሪዎች ጉባዔ ላይ የተሳተፉ ሲሆን፤ ጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አህመድም ከመሪዎቹ ጋር የተናጠል ውይይት አካሂደዋል። በዚህም የኬንያው ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ እና ከሶማሊያው ፕሬዚዳንት  መሀመድ ፋርማጆ በተናጥል ካነጋገሯቸው በኋላ፤ ሁለቱን መሪዎች በአንድ ላይ በማምጣት አነጋግረዋል። ይሄንንም ‘’ከመሪዎቹ ጋር በአካባቢያችን አንገብጋቢ በሆኑ ጉዳዮች ላይ በጠረጴዛ ዙሪያ በመወያየታችን ደስ ብሎኛል’’ ሲሉ ነው ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ የገለጹት። በጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አህመድ የሚመራው የጉባዔው ተሳታፊ ልዑክ የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር እና ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎችን ያካተተ ሲሆን፤ ጉባዔውም በአፍሪካ ቀንድ የሰላም እና ፀጥታ ጉዳይ እንዲሁም በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ዙሪያ የሚመክር ይሆናል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 12 ቀን 2013  ዓ.ም
https://www.press.et/Ama/?p=37764
176
0ሀገር አቀፍ ዜና
አድሏዊ የመገናኛ ብዙኃን ዘገባ የህዝብን ጥላቻን በማባባስ የአገር አደጋ እየሆነ መምጣቱ ተገለጸ
ሀገር አቀፍ ዜና
December 21, 2020
20
ጽጌረዳ ጫንያለው አዲስ አበባ፡- የመገናኛ ብዙኃን ዘገባዎች በከፍተኛ ሁኔታ አድሏዊነት እየታየባቸው በመምጣታቸው ጥላቻን በማባባስ የአገር አደጋ እየሆነ መምጣቱን አስተያየታቸውን ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ የሰጡ የዘርፉ ምሑራን ተናገሩ። በውጪ ሚዲያዎች የሚታየው የአድሎ ዘገባ ምንጩ ችግሩን ከምንጩ አለመረዳት እና ችግሩ ያደረሰውን እንጂ ያመጣውን ማየት አለመፈለጋቸው መሆኑንም ገልጸዋል።በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጋዜጠኝነት መምህር ዶክተር ሙላቱ አለማየሁ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደተናገሩት፤ መገናኛ ብዙኃን የህዝብ ልሳን በመሆናቸው የሁሉንም ሀሳብ በእኩል ደረጃ ማስተናገድ ቢኖርባቸውም ይሄን እያደረጉት እንዳልሆነ በተለያየ መንገድ ይታያል። በዚህም ግለሰቦችን ለማጉላት ሲሞክሩ፤ የአንድ ወገን ሀሳብ ብቻ ሲያስተናግዱ፤ ከጋዜጠኛው ጀርባ ያሉ አካላት ፍላጎትን ሲያሳኩም ይስተዋላል። ይህ ደግሞ በህዝብ መካከል ጥላቻን በማባባስ አገርን አደጋ ውስጥ እንድትገባ እያደረጋት ይገኛል። በመገናኛ ብዙኃኑ ዘገባዎች የጋዜጠኛው ፍላጎት፣ የአገራት ፍላጎት፣ የፖለቲካና የሚፈለገው የርዕዮተዓለም ፍላጎት እንዲሁም የብሔር ፍላጎት ሰፊውን ድርሻ ወስዶ በመዘገቡ የህዝብን ሀሳብ እየታፈነ እንደሆነ ይታያል የሚሉት ዶክተር ሙላቱ፤ መገናኛ ብዙኃኑ የህዝብ አገልጋይነታቸውን መልቀቃቸውን እና ሀሳቦች እንዳይንሸራሸሩም ወገንተኝነታቸው መብዛቱን ይገልጻሉ። በተለይም የክልል ሚዲያዎች በዚህ ዙሪያ ከፍተኛውን ድርሻ እየወሰዱ መሆኑን፤ ይህ ደግሞ በህዝብ መካከል ጥላቻና ቂም እንዲፈጠር እድል መስጠቱን፤ ሂደቱም አማራጭ የመፍትሄ ሀሳቦች እንዳይኖሩም እያደረገ መሆኑን አስረድተዋል። የዜጎች ድምጽ መታፈንን ከሚያመላክቱ መንገዶች አንዱ አድሏዊ ዘገባ እንደሆነ የሚጠቁሙት ዶክተር ሙላቱ፤ ሀሳብ ሳይወጣ ሲቀር ፍርሀትና ስጋት ይፈጥራል። ይህ ደግሞ ቂም አርግዞ ለቀጣይ ጊዜ ከፍተኛ ችግር በህዝቦች መካከል እንዲከሰት ያደርጋል። የተረጋጋ ህይወት ለመኖርም አያስችልም። ሁለቱ ወገኖች ያላቸውን ልዩነት በትክክል እንዳያዩ ያደርጋቸዋል። ስለዚህም አሁን በጥናት ባይረጋገጥም አገሪቱ ላይ እየሆነ ያለው ይሄው መሆኑን ተናግረዋል። ወቅቱ ብዙ ችግሮችን አርግዞ የቆየበት በመሆኑ የአገር ውስጥ ሚዲያዎች በተለይም የክልል መገናኛ ብዙኃን ትልቅ ጥንቃቄ ማድረግ እንዳለባቸው የሚናገሩት ዶክተር ሙላቱ፤ ተጎጂውም ሆነ ጎጂው የአንድ አገር ዜጋ በመሆኑ መገናኛ ብዙኃን ሁለቱንም ማዕከል ያደረገና ግራ ቀኙን ያየ ዘገባ ማዘጋጀት እንዳለባቸው አስረድተዋል። የሰላም ግንባታ ላይ መስራት ሚዲያው ለቆመለት አላማ ከመታመንም በላይ ህዝብንና አገርን ከችግር መታደግ ነው። ስለሆነም መገናኛ ብዙኃኑ ዘገባቸውን እንደ መከላከያ ለህዝብና ለሰላም ወገንተኝነትን መሰረት ያደረገ መሆን ይኖርበታል። ለዚህ ደግሞ አድሏዊነትን ትተው ሚዛናዊነትን ማስቀደም እንደሚገባቸውም ገልጸዋል። እንደ ዶክተር ሙላቱ ገላጻ፤ በውጪ ሚዲያዎች የሚታየው የአድሎ ዘገባ ምንጩ የተለያየ ሲሆን፤ የመጀመሪያው ችግሩን ከምንጩ አለመረዳት ነው። ሌላው ችግሩ ያደረሰውን እንጂ ያመጣውን ማየት አለመፈለጋቸው ነው። ነገሮችን ተከታትሎ አለመዘገብ፣ የራሳቸውን ፍላጎት ማስቀደምም፣ ሌላው የአድሎአዊነት መሰረታቸው ነው። ስለሆነም በአገር ውስጥም ሆነ በውጪ የሚገኙ አድሎአዊ ዘገባዎችን ለማስቀረት ከራስ የጀመረ ሥራ ያስፈልጋል። እንደ ሚዲያ ያለውን ህግ መሰረት አድርጎ ግራ ቀኝ አይቶ መዘገብ ደግሞ የመጀመሪያ መፍትሄ ነው። መረጃ የሚሰጡ አካላት ትክክለኛውን መረጃ ወቅቱን በጠበቀ መልኩ ሊሰጡ እንደሚገባ የጠቆሙት ዶክተር ሙላቱ፤ በተለይም ለውጪ ሚዲያዎች በየቀኑ መግለጫ መስጠትና እውነታውን ማሳየት እንደሚገባ አስረድተዋል። በተመሳሳይ በኢንባሲዎች አካባቢ ሥራዎች መሰራት ያስፈልጋል። እንደመንግሥት ጋዜጠኞችን ወቅታዊ ጉዳይ ባለበት ስፍራ ይዞ በመጓዝም እውነታውን ማሳየት ተቀዳሚ ተግባር መሆን አለበት ብለዋል። በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የጋዜጠኝነትና ኮሚኒኬሽን መምህር እና በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የዶክትሬት ዲግሪ ተማሪው መምህር ፍሬዘር እጅጉ በበኩላቸው እንደሚናገሩት፤ ከለውጡ በኋላ በተሰጠው የሚዲያ ነጻነት ጥናት ተደርጎ እንደተገኘው በአገሪቱ ያሉ የሚዲያ ተቋማት ዘገባ ከፍተኛ አድሏዊነት የሚታይበት ነው። የአንድ ወገንን ሥራ የሚያጎላም ነው። ይህ ደግሞ ቀጣይነት ያለው ችግር እንደሚፈጥር የታየበት ሲሆን፤ አሁን የተፈጠረውም ከዚሁ ግምት ጋር ይያያዛል።ከውጪ ሚዲያ አንጻር ሲታይ ደግሞ አፍሪካ በዓለም መገናኛ ብዙኃን የምትወከለው የጦርነት ምድርና የችግር ምሳሌ በመሆን ስለሆነ በፊት ገጻቸው ከዚህ የተለየ ማስፈርን እንዳይችሉ አድርጓቸዋል። ምክንያቱም የውጪ ሚዲያዎች በአፍሪካ ያለውን ሰላም፣ ስኬትና ልማት የሚያዩበት መነጽር የተሳሳተ ስለሚሆን ለተነባቢነታቸው ስለሚጨነቁ መዘገብ አይፈልጉም።እንደነዚህ አይነት ችግሮችን ለመፍታት ሁለት መንገዶችን መጠቀም እንደሚበጅ የሚናገሩት መምህር ፍሬዘር፤ በውጪዎች እይታ የሚደማ ነገር ካለና መጥፎ ዜና ከሆነ ጥሩ ዜና ተብሎ ፊት ገጽ እንዲሆን ይፈቀዳልና ይህንን ባህሪያቸውን አቅርቦ በጥሩ መቀየር እንደሚገባ ይገልጻሉ። ለዚህ ደግሞ አሁን በወቅታዊ ጉዳዮች እንደተቋቋመው የመረጃ ፍሰት ማዕከል አቋቁሞ ከፍተኛ የህዝብ ግንኙነት ስትራቴጂን መፍጠር ትልቅ ውጤት እንደሚያስገኝ ተናግረዋል። የአገር ውስጥ ሚዲያው መፍትሄ ደግሞ፣ ህዝብን ለውዥንብርና ብዥታ የሚዳርጉ ሚዲያዎችን ብሮድካስት እርምጃ እየወሰደ ማስተካከል እንደሚገባ በመጠቆም፤ ሚዲያው በራሱ የተለያየ ሀሳብ ያላቸውን ሰዎች በመጋበዝ ሚዲያው የሀሳብ ማንሸራሸሪያ መድረክ እንዲሆን መስራት ይኖርባቸዋልም ብለዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 12/2013
https://www.press.et/Ama/?p=37769
571
0ሀገር አቀፍ ዜና
በአማራ ክልል በ1 ነጥብ 8 ቢሊየን ብር 14 የንፁህ መጠጥ ውኃ ፕሮጀክቶች ሊገነቡ ነው
ሀገር አቀፍ ዜና
December 21, 2020
17
 በጋዜጣው ሪፖርተርአዲስ አበባ፡- በመጭዎቹ ሦስት ዓመታት በአማራ ክልል ዝናብ አጠር እና ደረቃማ አካባቢዎች በ1 ነጥብ 8 ቢሊየን ብር 14 የንፁህ መጠጥ ውኃ ፕሮጀክቶች እንደሚገነቡ ተገለጸ። ፕሮጀክቶቹ፣ በአማራ ክልል መካከለኛ ከተሞች እና የገጠር ቀበሌዎች ያለውን የንፁህ መጠጥ ውኃ አቅርቦት ለማሳደግ ያስችላል የተባለለት ይህ ፕሮጀክት በዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር፣ በኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር፣ በሰሜን ወሎ፣ ማዕከላዊ ጎንደር፣ ደቡብ ወሎ እና ሰሜን ሸዋ ዞኖች እንደሚገነባም ነው የአማራ ብዙኃን መገናኛ ድርጅት የዘገበው። በዘገባው እንደተመላከተው፤ የፕሮጀክቱ አካል የሆኑት በዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ከተማ እና በሰሜን ወሎ ዞን ሰኞ ገበያ የሚገነቡት የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች ግንባታ የፊርማ ሥነ ሥርዓት የተከናወነ ሲሆን፤ የግንባታ ውሉ የፊርማ ሥነ ሥርዓትም በፕሮጀክቱ አስፈፃሚ የአማራ ክልል ውኃ፣ መስኖና ኢነርጂ ቢሮ እና በሚገነባው የጢስ እሳት ኮንስትራክሽን ድርጅት መካከል ተካሂዷል። በወቅቱም፣ የአማራ ክልል ውኃ፣ መስኖና ኢነርጂ ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ማማሩ አያሌው እንደገለጹት፤ 14ቱ የመጠጥ ውኃ ፕሮጀክቶች በአየር ንብረት አይበገሬነት የመጠጥ ውኃ አቅርቦት ፕሮግራም የሚከናወኑ ሲሆኑ፤ ግንባታቸው በመጨዎቹ ሦስት ዓመታት ይጠናቀቃል ብለዋል። የንፁህ መጠጥ ውኃ ፕሮጀክቶቹን ገንብቶ ለማጠናቀቅ 1 ነጥብ 8 ቢሊየን ብር ተመድቧል።በፕሮጀክቱ ግንባታ የፊርማ ሥነ ሥርዓት ላይ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተፈጥሮ ሃብት ውኃ መስኖና ኢነርጂ ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ክብርት ፈትያ የሱፍ፣ የውኃ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትር ዶክተር ኢንጂነር ስለሽ በቀለ እና የአማራ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ፋንታ ማንደፍሮ የተገኙ ሲሆን፤ ለፕሮጀክቶቹ ተፈፃሚነት የውኃ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር፣ የውኃ ልማት ኮሚሽን እና የአማራ ክልል ውኃ መስኖና ኢነርጂ ቢሮ በጋራ እንደሚሰሩም ዶክተር ኢንጂነር ስለሽ በቀለ መናገራቸውን ነው አብመድ የዘገበው። አዲስ ዘመን ታህሳስ 12/2013
https://www.press.et/Ama/?p=37772
227
0ሀገር አቀፍ ዜና
ኢትዮጵያዊቷ አትሌት እገዳ ተጣለባት
ስፖርት
November 28, 2019
57
ኢትዮጵያዊቷ የማራቶን ሯጭ እታፈራሁ ተመስገን አበረታች መድሃኒት ተጠቅማ በመገኘቷ ጊዜያዊ እገዳ ተጣለባት። አትሌት እታፈራሁ በዓለም አትሌቲክስ ገለልተኛ ሆኖ በተቋቋመው የአበረታች ንጥረ ነገሮች ምርመራ ቡድን በተደረገላት ምርመራ ብቃቷን ከፍ የሚያደርግ መድሃኒት ተጠቅማ በመገኘቷ እገዳው እንደተጣለባት ኢንሳይድ ዘጌምስ ዘግቧል። የሰላሳ ዓመቷ አትሌት እታፈራሁ ባለፈው ሰኔ በኦታዋ ማራቶን ተሳትፋ 2፡28፡44 በሆነ ሰዓት ሦስተኛ ደረጃን ይዛ ማጠናቀቋ የሚታወስ ሲሆን ከወር በፊት በቶሮንቶ ማራቶን 2፡27፡ 21 በሆነ ሰዓት ስምንተኛ ደረጃን ይዛ ማጠናቀቋ ይታወቃል። እ ኤ አ በ2018 በሜክሲኮ ማራቶን አትሌቷ 2፡40፡10 በሆነ ሰዓት ማሸነፍ ችላለች። አትሌት እታፈራሁ የተደረገላትን ምርመራ ማለፍ ባለመቻሏ በየትኛውም ስፖርት ላልተወሰነ ጊዜ ተሳታፊ እንዳትሆን ጊዜያዊ እገዳ የተጣለባት ሲሆን የዓለም አትሌቲክስና ገለልተኛው የምርመራ ቡድን ከአበረታች መድሃኒት ተጠቃሚነት ጋር የተያያዙ ዓለም አቀፍ ህግጋቶችን መሰረት አድርገው ወደ ፊት በቋሚነት ቅጣት እንደሚያስተላልፉ ዘገባው አመልክቷል። ከወር በፊት በመላ አፍሪካ ጨዋታዎች የአስር ሺ ሜትር አሸናፊ የሆነው ኢትዮጵያዊው አትሌት ብርሃኑ ፀጉ የተደረገለትን የአበረታች መድሃኒት ምርመራ ማለፍ ባለመቻሉ ተመሳሳይ እገዳ እንደተጣለበት ይታወሳል። ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በአትሌቲክሱ አበረታች መድሃኒት ወይም ንጥረ ነገሮች ተጠቃሚነት ጋር በተያያዘ ሩሲያን የመሳሰሉ ታላላቅ አገራት ከታላላቅ ውድድሮች እስከመ ታገድ ደርሰዋል። እነዚህ አገራት አትሌ ቶቻቸው በብዛት አበረታች መድሃኒት ተጠቃሚ ሆነው ከመገኘታቸው ጋር ተያይዞ በመንግሥት ጭምር ይደገፋሉ በሚል ከውድድሮች መታገ ዳቸው ይታወቃል። የዓለም አቀፉ ፀረ አበረታች መድሃኒቶች ኤጀንሲ እነ ሩሲያን በቀጣበት ወቅት ኢትዮጵያና ኬንያ አደጋው በከፍተኛ ሁኔታ እንደሚያሰጋቸው በማሳወቅ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ምክረ ሃሳብ ሰጥቷቸው ነበር። ሁለቱ አገራት በተለይም ኢትዮጵያ ለጉ ዳዩ ትኩረት ሰጥታ በመስራት አበረታች ውጤት ማስመዝገቧም በኤጀንሲው ጭምር ተመስክሮላታል። ያም ሆኖ ስጋቱ ሙሉ ለሙሉ ተቀርፏል ለማለት አይቻልም። ባለፈው ዓመት የዓለም አትሌቲክስ ኢትዮጵያና ኬንያን በአበረታች መድሃኒት (ዶፒንግ) ምክንያት ስጋት ካለባቸው አገራት ቀዳሚውን ደረጃ እንደሚይዙ ማሳወቁ ይታወሳል። ዘንድሮም ሁለቱ አገራት በአበረታች መድሃኒት ስጋት ቁንጮውን ደረጃ መያዛቸው እንደማይቀር እየወጡ ያሉ መረጃዎች ጠቋሚ ናቸው። ለዚህም ባለፉት ጥቂት ወራት ብቻ አምስት የአፍሪካ አገራት አትሌቶች አበረታች መድሃኒት ተጠቃሚ ሆነው መገኘታቸው ማሳያ ተደርጓል። ቤላሩስና ዩክሬን ሁለቱን የአፍሪካ አገራት ተከትሎ ስማቸው ከቁንጮዎቹ ተርታ ተፅፏል። ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በተለይም በግል ውድድሮች ብቻ የሚታወቁት አልፎ አልፎ በአበረታች መድሃኒት ሲቀጡ ይታያል። ይሁን እንጂ አገርን ወክለው በሚወዳደሩ አትሌቶች ይህ ቅሌት አይታይም ማለት ይቻላል። ባለፈው ክረምት በሞሮኮ ራባት በተካሄደው የመላ አፍሪካ ጨዋታዎች ኢትዮጵያን ወክሎ በአስር ሺ ሜትር ወርቅ ማጥለቅ የቻለው ብርሃኑ ፀጉ ኢፒኦ የተባለ ንጥረ ነገር ተገኝቶበት ላልተወሰነ ጊዜ ከስፖርቱ ታግዷል። ይህ የሃያ ዓመት አትሌት ባለፈው ወር በኮፐንሃገን ግማሽ ማራቶን ላይ ሁለተኛ ሆኖ ማጠናቀቁ ይታወሳል። ብርሃኑ ሔንግሎ በተካሄደው የዓለም ቻምፒዮና የኢትዮጵያውያን ማጣሪያ ውድድር ላይ 10ሺ ሜትሩን 27፡00፡73 በሆነ ሰዓት ማጠናቀቅ ችሏል። ብርሃኑ በመላ አፍሪካ ጨዋታዎች ሲያሸንፍ ኤርትራዊው አሮን ክፍሌና ሌላኛው ኢትዮጵያዊ ጀማል ይመር ተከትለውት መግባታቸው ይታወሳል። ብርሃኑ የወርቅ ሜዳሊያውን ተነጥቆ ለኤርትራዊው አትሌት፣ የብር ሜዳሊያው ደግሞ ለጀማል ይመር የሚሰጥ ሲሆን አራተኛ ሆኖ ያጠናቀቀው ኬንያዊው ኤድዊን ሦይ የነሐስ ሜዳሊያ ሊያገኝ እንደሚችል መረጃዎች እየወጡ ነው። በአዲስ አበባ አበረታች መድሃኒቶች በስታድየም አካባቢ ካለ ሐኪም ማዘዣ ጭምር እንደሚሸጡ የእንግሊዝ ሚዲያዎች መዘገባቸውን ተከትሎ የዓለም አትሌቲክስ ኢትዮጵያን ማስጠንቀቁ ይታወሳል። ይህንንም ተከትሎ የኢትዮጵያ ፀረ አበረታች መድሃኒቶች ፅሕፈት ቤትና የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ለአትሌቶች የተለያዩ ትምህርቶችን እየሰጡ ይገኛሉ።አዲስ ዘመን ኅዳር 18/2012 ቦጋለ አበበ
https://www.press.et/Ama/?p=23270
451
2ስፖርት
”ለመከላከያ ምንም ድጋፍ ቢደረግ ለሀገርና ለህዝብ የዋለውን ውለታ መመለስ አይቻልም” – አቶ የሺዋስ አሰፋ የኢዜማ ሊቀመንበር
ሀገር አቀፍ ዜና
December 20, 2020
42
ሶሎሞን በየነአዲስ አበባ:- ለአገር መከላከያ ሠራዊቱ የሚደረገው ማንኛውም ድጋፍ ሞራል ለመስጠትና አጋርነትን ለማሳየት ያህል ካልሆነ በስተቀር ሠራዊቱ አጥንቱን ከስክሶ አገር እንዳዳነው፣ ደሙን አፍሶ የኢትዮጵያን ሃጢያት እንዳጠበው እንደማይሆን የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ ፓርቲ (ኢዜማ) ሊቀመንበር አቶ የሺዋስ አሰፋ ገለጹ።አቶ የሺዋስ ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቃለመጠይቅ እንደገለጹት፤ የህወሓት ጁንታ ቡድን ጥቅምት 24 ቀን 2013 ዓ.ም በሰሜን ዕዝ ላይ የፈጸመውን ጥቃት ተከትሎ የአገር መከላከያ ሠራዊት ህግን ለማስከበርና የአገርን ህልውና ለማዳን መስዋዕትነት ከፍሏል፤ እየከፈለም ይገኛል። ይሄን ተከትሎም ኅብረተሰቡ ለመከላከያ ሠራዊቱ ሰፊ ድጋፍ እያደረገ ይገኛል። ሆኖም በዚህ መልኩ የሚደረገው ማንኛውም ድጋፍ ለሠራዊቱ ሞራል ለመስጠትና አጋርነትን ለማሳየት ያህል ካልሆነ በስተቀር ማንም ምንም አይነት ድጋፍ ቢያደርግ መከላከያ ሠራዊቱ አጥንቱን ከስክሶ አገር እንዳዳነው፣ ደሙን አፍሶ የኢትዮጵያን ሃጢያት እንዳጠበው አይሆንም።በአገር መከላከያ ላይ የተፈጸመው ክህደት እኛ ካልመራን አገር ትጠፋለች ከሚል አስተሳሰብ የመነጨ እንደሆነ የጠቆሙት አቶ የሺዋስ፤ ይህ አጥፊ ቡድን እራሱ የቆሰቆሰውን የኤርትራ ጦርነት ምክንያት አድርጎ የአገሪቱ ትልቁ የነዳጅ ማጠራቀሚያ ዲፖ፣ ብረት ለበስ ወታደራዊ ኃይል፣ የአገሪቷ መካናይዝድ ጦር፣ ስምንት ትልልቅ ክፍለጦር ያሁሉ የጦር መሳሪያ በአንድ ቦታ በማከማቸት የየራሱን ጉልበት ሲያጠናክር መቆይቱን ተናግረዋል። የጁንታው ቡድን በህዝብ ቁጣ አንድ ቀን ስልጣኔን አጣለሁ ብሎ ስለሚሰጋ ሰልጣን ከያዘ ጊዜ ጀምሮ ለጦርነት ሲዘጋጅ እንደቆየና ጉድጓድ ሲቆፍር፣ ነዳጅና የጦር መሳሪያ ሲያከማች ጊዜውን እንዳጠፋ በመግለጽም፤ ከዚህ ባሻገር በአገሪቱ የመጣውን ለውጥ ተከትሎ ከለውጥ መንግሥቱ ጋር ተባብሮ ከመስራት ይልቅ በሰበብ አስባቡ ጠብ እየፈለገ ሁከት ለመፍጠር ሲሞክር መቆየቱን አብራርተዋል። በመጨረሻም ቡድኑ ለ21 ዓመታት ያህል ድንበር ሲጠብቅ የቆየውን ሠራዊት ከትግራይ አይወጣም በማለት በሠራዊቱና በመንግሥት ላይ ጫና ለማሳረፍ ከመሞከሩም ባሻገር፤ ለትግራይ ህዝብ አለኝታና መከታ በነበረው ሠራዊት ላይ ጥቃት በመፈጸም ጁንታው ወራዳነቱን አሳይቷል። ይህ ድርጊቱም የትግራይን ህዝብ ባህልና ማንነት የማይገለጽና በታሪክ ታይቶ የማይታወቅ አውሬያዊ ስብስብ ባህሪ ነው ያሉት አቶ የሺዋስ፤ ድርጊቱ በክርስትናም ሆነ በእስልምናም ነውርና የተወገዘ መሆኑንም አስረድተዋል። ከህዝብ ጋር ሆኖ አንበጣ ሲከላከል፣ የህዳሴ ግድብን ሲጠብቅ፤ ሰብል ሲሰበስብ፤ ከሌለው ላይ አዋጥቶ ትምህርት ቤት ሲያሰራ በነበረን የህዝብ ሠራዊት ከኋላው መውጋት ከከሃዲነትም በላይ መሆኑን ገልጸዋል። ቡድኑ የፈጸመው አስጸያፊ ድርጊት ኢትዮጵያንም ሆነ ፖለቲካውን ከአለማወቅ፣ ሃሳባቸውም ያረጀና ያፈጀ መሆኑን ካለመገንዘብ ነው ያሉት አቶ የሺዋስ፤ በመከላከያ ላይ የተሰራው ግፍ ሁሉም ኅብረተሰብ ከራስ ጸጉሩ እስከ እግር ጥፍሩ ስሜቱ ዘልቆ የተሰማው መሆኑንም ገልጸዋል። በዚህም በኮቪድ እና ህዳሴ ግድቡ ወቅት ካሳየው የአንድነት ስሜት በላቀ መልኩ የህወሓት ጁንታ ቡድን ህግ መጣሱን ተከትሎ መከላከያ በወሰደው ህግን የማስከበር እርምጃ እንደአንድ ሰው ስሜቱ መተሳሰሩን ተናግረዋል። የህብረተሰቡ አንድነት ደግሞ ለኢትዮጵያ ትልቅ ተስፋ እንደመሆኑ በዚህ ረገድ ፓርቲዎችን፣ ሽማግሌዎችን፣ የኃይማኖት አባቶችን በአጠቃላይ የኢትዮጵያን ህዝብ ሊመሰገን ይገባዋል፤ ብለዋል። እንደ አቶ የሺዋስ ገለጻ፤ ህግን ለማስከበርና ሀገርን ለማዳን መከላከያ የወሰደው እርምጃ ሌላም ተመሳሳይ ዕኩይ ባህሪ ላላቸው አካላት አስተማሪ ነው። ሀገር ከማዳኑም ባሻገር ኢትዮጵያ የምትኮራበት ተቋም መገንባት መቻሉንም ያመላከተ ነው። መከላከያ ሠራዊቱ በአጠቃላይ መከላከያ ተቋሙ ምን ያክል ጠንካራ እንደሆነ ያስገነዘበ፤ ከአየር ኃይሉ እስከ እግረኛው ድረስ ከአገር ውስጥ ላለው ቦርቧሪ ከውጭ ለሚያስበውም ወራሪ በጣም ጥሩ ትምህርት የሰጠ እና ጀግኖችን ያፈራ ሂደትም ሆኗል። አምባገነን ሁል ጊዜ ጠብ የሚጭረው ከወጣቱ ባሻገር እናቶችን፣ አረጋዊያንና በሽተኞችን ጭምር ለማስፈጀት ነው ያሉት አቶ የሺዋስ፤ እንደፓርቲ ደም በመለገስ ገንዘብ በመስጠት በምንችለው ሁሉ ከመከላከያ ጎን ቁመናል። ኅብረተሰቡም የሚችለውን ሁሉ ለመከላከያ ድጋፍ እያደረገ ነው። ይህ ድጋፍ እስከመጨረሻ ድረስ እንዲዘልቅ በማድረግ ሁሉም አጋርነቱን ሊያሳይ ይገባል ሲሉ አመልክተዋል። ‹‹ከመከላከያ ጎን ቆማችኋል ተብለው በገመድ ታንቀው የተገደሉ የትግራይ ልጆች አሉ። ይህ ሲታሰብ ያለአግባብ የተከፈለው መስዋትነት በጣም ብዙና ያሚያም ነው” ያሉት አቶ የሺዋስ፤ ፖለቲካ ማወቅ ዓለማወቅ፣ ህዝብ ይቅርታ መቀበል አለመቀበል ሌላ ነገር ሆኖ በተለይ በሰሜን ዕዝ ላይ የፈጸሙት አረመኔያዊ ተግባር ፈጽሞ ከሰውነት የወጡ ከትግራይ ህዝብ ጋር የማይተዋወቁ ከሌላ ዓለም የመጡ ፍጡራን ናቸው እንድንል አድርጎናል ሲሉም ተናግረዋል። ይህ እኩይ ቡድን ለፍርድ እስኪቀርብ ድረስም ሁሉም ኢትጵያ ህዝብ ከመከላከያና ከጸጥታ አካላት ጎን እንዲቆምም ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 11/2013
https://www.press.et/Ama/?p=37692
548
0ሀገር አቀፍ ዜና
የቮሊ ቦል ፕሪሚየር ሊግ ከ2ሳምንት በኋላ ይጀመራል
ስፖርት
November 27, 2019
25
 የሀበሻ ሲሚንቶ የቮሊቦል ፕሪሚየር ሊግ የውድድር ዓመቱን ከሁለት ሳምንት በኋላ የሚጀምር ይሆናል፡፡ በ2011 ዓ.ም የሊጉ አፈጻጸምም ግምገማ መሰረትም የተሻለ የውድድር ዓመት እንደነበረም ተመልክቷል፡፡ በዘጠኝ ክለቦች መካከል የሚካሄደው የ2012 ዓ.ም የሀበሻ ሲሚንቶ የፕሪሚየር ሊግ ውድድር መርሃ ግብሩን በሁለት ሳምንታት ውስጥ የሚጀምር መሆኑን የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን በድረ-ገጹ አስነብቧል፡፡ ፌዴሬሽኑ የዕጣ ማውጣት ስነ ስርዓት ያከናወነ ሲሆን፤ ያለፈውን የፕሪሚየር ሊግ ውድድር ደረጃ መነሻ በማድረግም የመጀመሪያ ዙር የውድድር መርሀ ግብር ድልድል ይፋ ሆኗል፡፡ በዚህም መሰረት ወላይታ ድቻ ከውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን፣ መደወላባ ዩኒቨርስቲ ከፌደራል ማረሚያ ቤት፣ ሙገር ሲሚንቶ ከጣና ባህርዳር እንዲሁም አዲስ አበባ ፖሊስ ከመከላከያ እንደሚገናኙ ታውቋል ፡፡ ፌዴሬሽኑ የ2011 ዓ.ም የሀበሻ ሲሚንቶ የወንዶች የፕሪሚየር ሊግ ውድድር ላይ ግምገማ ያካሄደ ሲሆን፤ በግምገማውም የክለብ አመራሮች፣ የዳኞች ኮሚቴ፣ የቴክኒክ ኮሚቴ እና የውድድርና ስነ ስርዓት ኮሚቴዎች ተሳትፈዋል፡፡ ፌዴሬሽኑ በ 2 ዙር በአራት ከተሞች ባካሄዳቸው ውድድሮች ላይ የነበሩ ጠንካራ አፈጻጸሞችንና ክፍተቶችን በመለየት የመከረ ሲሆን፤ የፕሪሚየር ሊጉ ውድድር ወቅቱን ጠብቆ መጠናቀቅ፣ ጠንካራ የፕሪሚየር ሊግ ፉክክር መታየት፣ የኮኮቦች ምርጫ ያለምንም ቅሬታ መካሄድ እና አንፃራዊ የስፖርታዊ ጨዋነት መስፈን በጥንካሬ ከተነሱ ነጥቦች መካከል ተጠቃሾቹ ናቸው ፡፡ ካለፉት ዓመታት ጋር ሲነጻጸር የ2011 የሀበሻ ሲሚንቶ ፕሪሚየር ሊግ የተሻለ ውድድር የተካሄደበትም ነው፡፡ ነገር ግን በዳኞች የሚታዩ የዳኝነት ክፍተቶች፣ ከሜዳ ውጪ የሚታዩ የስፖርታዊ ጨዋነት ጉድለቶች፣ አሰልጣኞች በውድድር ሜዳ የሚያሳዩት ያልተገባ ስነ-ምግባር፣ የውድድር ኮሚሽነሮች የተሟላ ሪፖርት ያለ ማቅረብ፣ በአንዳንድ ተጨዋቾች የሚታዩ የስነ-ምግባር ጉድለቶች፣ ውጤትን በፀጋ ያለመቀበል እና ክለቦች ለውድድር ቅድመ ዝግጅት ባለማድረግ ችግሮች እንደነበሩበት በተሳታፊዎች ተነስቷል፡፡ በአዲሱ የፕሪሚየር ሊግ ዓመት እንዳይደገሙም የመፍተሄ አቅጣጫ ተቀምጧል ፡፡ ፌዴሬሽኑ ከግምገማ እና እጣ ማውጣት ስነ- ስርዓት በኋላ በውድድሩ ለሚሳተፉ ክለቦች የቁሳቁስ ድጋፍ ማበርከቱንም በዘገባው ተጠቁሟል፡፡አዲስ ዘመን ኅዳር 17/2012 ብርሃን ፈይሳ
https://www.press.et/Ama/?p=23241
247
2ስፖርት
ከሽንፈት ማግስት የሚደረጉት ወሳኝ የብሔራዊ ቡድን ፍልሚያዎች
ስፖርት
November 19, 2019
27
ባለፈው ቅዳሜና ዕሁድ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድኖች በሁለቱም ፆታ ያደረጓቸውን ጨዋታዎች በሽንፈት ማጠናቀቃቸው ይታወሳል። የወንዶች ብሔራዊ ቡድን ዋልያዎቹ ቅዳሜ ዕለት ለ2021 የካሜሩን አፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ የምድባቸውን የመጀመሪያ ጨዋታ ከሜዳቸው ውጪ አድርገው በማዳጋስካር አንድ ለምንም መሸነፋቸው ይታወሳል። የሴቶች ብሔራዊ ቡድን ሉሲዎቹ ደግሞ በመካከለኛውና ምሥራቅ አፍሪካ(ሴካፋ) ዋንጫ ዕሁድ ዕለት የምድባቸውን የመጀመሪያ ጨዋታ አድርገው በኬንያ ሁለት ለዜሮ ተረተዋል። ሁለቱም ብሔራዊ ቡድኖች ዛሬ ከሽንፈታቸው ማግስት ወሳኝ ፍልሚያ የሚጠብቃቸው ይሆናል። በኬኒያ አቻቸው በሁለት ደቂቃ ውስጥ ሁለት ግብ አስተናግደው የተሸነፉት ሉሲዎቹ ከምድባቸው ለማለፍ ዛሬ ከዩጋንዳ ጋር የሚያደርጉት ወሳኝ ጨዋታ ይጠብቃቸዋል። አሰልጣኝ ብርሃኑ ግዛው በዛሬው ጨዋታ መጠነኛ የተጫዋች ለውጥ እንደሚኖር ጠቅሰው፤ የሚችሉትን ሁሉ ሜዳላይ ለማድረግ ተጫዋቾቹ ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል። ‹‹ተጫዋቾቹ ምንም የሚፈረድባቸው ነገር የለም፣ በርካታ ወራት አርፈው ነው የመጡት፣ ክለቦቻችን ዕረፍት ላይ ስለነበሩ የዝግጅት ጊዜ አልነበራቸውም፣ የኔ እና የተጫዋቾቼ ህልማችን በ2020 ብሔራዊ ቡድኑን ወደ አፍሪካ ዋንጫ ማሳለፍ ነው፣ ይህ ውድድር ደግሞ እንደ ዝግጅት ይጠቅመናል፣ ብናሸንፍም ጮቤ አንረግጥም ምክንያቱም አልሠራንም፣ ነገር ግን ያለንን ጊዜ በመጠቀም ህልማችንን እናሳካለን፣ ይህን ማድረግ ካልቻልን መጠየቅ ያለብኝ እኔ እንጂ ተጫዋቾቼ አይደሉም፣ ዝግጅት ሳይሠሩ ውጤት መጠበቅ እንጀራ ሳያዘጋጁ ወጥ አቅርቦ ምሳ እንብላ እንደማለት ነው፣ ስለዚህ ከዚህ ውድድር ብዙ እንማራለን ለአፍሪካ ዋንጫው ሠርተን ለማለፍ እንጥራለን›› በማለት ለሽንፈቱ ኃላፊነቱን እንደወሰዱ በስፍራው ለሚገኙ መገናኛ ብዙሃን ተናግረዋል። በታንዛኒያ አዘጋጅነት የሚካሄደው የሴቶች ሴካፋ ዋንጫ ኢትዮጵያ ከኬንያ፣ ዩጋንዳና ጅቡቲ ጋር መደልደሏ ይታወቃል። ሉሲዎቹ የመጀመሪያውን ጨዋታ መሸነፋቸውን ተከትሎ ወደ ቀጣዩ ዙር ለማለፍ ያላቸውን ተስፋ የሚያለመልሙት ዛሬ ከዩጋንዳ ጋር በሚኖራቸው ወሳኝ ፍልሚያ ይሆናል። ይህን ጨዋታ በሽንፈት ደምድመው በመጨረሻው የምድብ ጨዋታ ጅቡቲን ቢያሸንፉ እንኳን ወደ ቀጣዩ ዙር የማለፍ ተስፋ አይኖራቸውም። የዛሬውን ጨዋታ ማሸነፍ የግድ ቢሆንም በአቻ ውጤት መለያየት ከቻሉ የሌሎቹን ውጤት ጠብቀው ወደ ቀጣይ ዙር የማለፍ ተስፋቸውን ሊያለመልሙ ይገደዳሉ። ይህ በእንዲህ እንዳለ በ2021 በካሜሩን አስተናጋጅነት ለሚካሄደው የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የምድቡን የመጀመሪያ ጨዋታ ከማዳጋስካር ጋር ከሜዳው ውጪ አድርጎ በ 1 ለ 0 ውጤት መሸነፉ ይታወቃል።ዋልያዎቹ በጨዋታው የታዩባቸውን በተለይም ኳስን ከመረብ የሚያገናኝ ጨራሽ አጥቂ ክፍተቶች ለመሸፈን አልጣኝ አብርሃም መብራቱ በውጭ ያሉ ተውልደ ኢትዮጵያውያን ተጫዋቾችን በቀጣይ ጨዋታዎች ለማካተት እንዳሰቡ ለመገናኛ ብዙሃን ተናግረዋል። አሰልጣኙ ‹‹በዛሬው ጨዋታ ቡድናችን ከሜዳ ውጪ ከዕረፍት በፊት በመከላከል ላይ ያተኮረ እንቅስቃሴ አድርጓል፣ ኳስን በመቆጣጠር ከዕረፍት መልስ በማጥቃት ላይ ያተኮረ እንቅስቃሴም አድርጓል›› ብለዋል።የማዳጋስካር ቡድን ከወራት በፊት በአፍሪካ ዋንጫ እነ ናይጄራያንና ኮንጎን አሸንፎ ግማሽ ፍፃሜ የደረሰ መሆኑን ያስታወሱት አሰልጣኙ ቡድናቸው 1ለ0 መሸነፉ መጥፎ የሚባል ውጤት እንዳልሆነ አብራርተዋል። በዋልያዎቹ ስብስብ አብዛኞቹ ተጫዋቾች አዲስ መሆናቸውን የጠቆሙት አሰልጣኝ አብረሃም በቀጣዩ ጨዋታ ክፍተቶችን እንደሚያርሙ ተናግረዋል። ‹‹የቡድኑን የአጥቂ ችግር ለመቅረፍ ከአገር ውስጥም ወይም ከውጭ ያሉትን በቀጣይ ጨዋታ እናካትታለን›› ሲሉም አስተያየታቸውን ሰጥተዋል። ዋልያዎቹ ከማዳጋስካሩ ጨዋታ ሽንፈት በኋላ ጊዜ ሳያጠፉ ወደ ባህርዳር ያቀኑ ሲሆን ዛሬ ጠንካራዋን ኮትዲቯር የሚገጥሙ ይሆናል። ዋልያዎቹ በአፍሪካ ዋንጫው ማጣሪያ ከኮትዲቯር፣ማዳጋስካርና ኒጀር ጋር መደልደሏ ይታወቃል። ኮትዲቯር ቅዳሜ ዕለት ከሜዳዋ ውጪ ኒጀርን ገጥማ አንድ ለዜሮ በሆነ ውጤት ማሸነፏ ይታወሳል። አዲስ ዘመን ህዳር 9 ቀን 2012 ዓ.ምቦጋለ አበበ
https://www.press.et/Ama/?p=22770
430
2ስፖርት
ለተሰንበት ግደይ የዓለም ክብረወሰን አሻሻለች
ስፖርት
November 19, 2019
35
ኢትዮጵያዊቷ ወጣት አትሌት ለተሰንበት ግደይ የዓለም አስራ አምስት ኪሎ ሜትር ክብረወሰንን መጨበጥ ችላለች፡፡ ለተሰንበት ከትናንት በስቲያ በኔዘርላንድስ ‹ሰቨን ሂልስ ረን› በተባለ የጎዳና ላይ ውድድር ክብረወሰኑን ያሻሻለች ሲሆን ውድድሩን ያጠናቀቀችበት ሰዓት 44፡20 ሆኖ ተመዝግቧል፡፡ ከወር በፊት በዶሃው የዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮና በአስር ሺ ሜትር አስደናቂ ብቃት በማሳየት የብር ሜዳሊያ ማሸነፍ የቻለችው ለተሰንበት በዓለም አገር አቋራጭ ቻምፒዮና በወጣቶች ምድብ ለሁለት ተከታታይ ዓመታት ቻምፒዮን እንደነበረች ይታወሳል፡፡ ለተሰንበት የዓለም የአስራ አምስት ኪሎ ሜትር ክብረወሰንን ከአንድ ደቂቃ በላይ ያሻሻለች ሲሆን ይህ ክብረወሰን ከሁለት ዓመት በፊት በኬንያዊቷ ጆይስሊን ጂፕኮስጌ 45፡37 በሆነ ሰዓት በፓራጓይ ግማሽ ማራቶን ውድድር ላይ የተመዘገበ መሆኑን የዓለም አትሌቲክስ ድረ ገፅ ዘገባ አመልክቷል፡፡ የሃያ አንድ ዓመቷ አትሌት ለተሰንበት ከውድድሩ በኋላ ‹‹ገና ለውድድሩ ዝግጅት ሳደርግ በጥሩ አቋም ላይ እንዳለሁ አውቅ ነበር፣ በውድድሩም ላይ ምቾት ተሰምቶኛል፣ እውነቱን ለመናገር የቀድሞውን ክብረወሰን በምን ያህል ሰዓት እንዳሻሻልኩኝ ለማየት ጓጉቼ ነበር›› በማለት የዓለም ክብረወሰን ስለመጨበጧ እርግጠኛ እንደነበረች ተናግራለች፡፡ ለተሰንበት ውድድሩን ከማሸነፏና የዓለም ክብረወሰን ከማሻሻሏ ባሻገር የመጨረሻዎቹን አስር ኪሎ ሜትሮች የሮጠችበት ፍጥነት የአትሌቲክሱን ቤተሰብ ያስደነቀና ወደ ፊት ትልቅ ተስፋ እንዲጣልባት ያደረገ ነበር፡፡ ለተሰንበት የመጨረሻዎቹን አስር ኪሎ ሜትሮች 29፡12 በሆነ ሰዓት ያገባደደች ሲሆን ይህም አልማዝ አያና በ2016 ሪዮ ኦሊምፒክ የአስር ሺ ሜርት የዓለም ክብረወሰንን ስታሻሽል ካስመዘገበችው 29፡17፡45 ሰዓት የፈጠነ ነው፡፡ የአስራ አምስት ኪሎ ሜትር የዓለም ክብረወሰን ከዚህ ቀደም እ.ኤ.አ 2009 ላይ በተመሳሳይ ውድድር በጥሩነሽ ዲባባ ተሻሽሎ እንደነበር ይታወሳል፡፡ ጥሩነሽ በወቅቱ የርቀቱን ክብረወሰን 46፡28 በሆነ ሰዓት ስታሻሽል ከእሷ በፊት ክብረወሰኑ 46፡55 በሆነ ሰዓት በጃፓናዊቷ ካዮኮ ፉኩሺ የተያዘ ነበር፡፡ ጥሩነሽ ይህን ክብረወሰን ባስመዘገበችበት ውድድር በወንዶች ባለቤቷ አትሌት ስለሺ ስህን ከዩጋንዳዊው ኒኮላስ ኪፕሮኖ ጋር እስከ መጨረሻ አንገት ለአንገት ተናንቆ በተመሳሳይ ሰዓት በመግባት አሸናፊ እንደነበር አይዘነጋም፡፡ ለተሰንበት በነገሠችበት የዘንድሮው ዓመት ውድድር በስቶች ኬንያዊቷ ኢቫሊን ቺርቺር 46፡32 በሆነ ሰዓት ሁለተኛ ሆና ስታጠናቅቅ ሌላኛዋ ኬንያዊት ኢቫ ቺሮኖ 48፡14 በሆነ ሰዓት ሦስተኛ ደረጃን ይዛ ፈፅማለች፡፡ በወንዶች መካከል የተካሄደውን ውድድር የሃያ ሦስት ዓመቱ ዩጋንዳዊ ስቲፈን ኪሳ 41፡49 በሆነ ሰዓት ማሸነፍ ችሏል፡፡ እሱን ተከትለው ኬንያውያኑ ኤድዊን ኪፕቶ በሁለት ሰከንድ ዘግይቶ ሁለተኛ፣ ሞሰስ ኮይች በ42፡05 ሰዓት ሦስተኛ ደረጃን ይዘው አጠናቀዋል፡፡አትሌት ለተሰንበት ግደይ ክብረወሰን ከማሻሻል ባለፈ ያሳየችው አስደናቂ አቋም ተስፋ እንዲጣልባት አድርጓል፣አዲስ ዘመን ህዳር 9 ቀን 2012 ዓ.ምቦጋለ አበበ
https://www.press.et/Ama/?p=22774
325
2ስፖርት
ዋልያዎች ከዝሆኖች ገዝፈው የታዩበት ምሽት
ስፖርት
November 20, 2019
25
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን(ዋልያዎቹ) ከኮትዲቯር ብሔራዊ ቡድን(ዝሆኖቹ) ጋር ለ2021 የካሜሩን አፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ የምድባቸውን ሁለተኛ ጨዋታ ትናንት 10 ሰዓት ላይ ከማድረጋቸው በፊት እንደ ቅፅል ስማቸው ፍፁም የተለያየ የእግር ኳስ አቅምና ደረጃ እንዳላቸው የዓለም ሕዝብ ያውቃል፡፡ ዋልያዎቹ በዓለም ካላቸው የእግር ኳስ ደረጃና ዝና አኳያ ዝሆኖቹ እንደ ስማቸው የገዘፈ ታሪክ ይዘው በዋልያዎቹ መንደር ሲከትሙ ጨዋታውን በቀላሉ እንደሚያሸንፉ እርግጠኞች ነበሩ:: ለዚህም ዝሆኖቹ ዋልያዎቹን ባህርዳር ላይ ለመግጠም በቀጥታ ከአገራቸው እንደመጡ ምንም አይነት ልምምድ ሳይሠሩ ወደ ሜዳ በመግባት ያሳዩት ንቀት ማሳያ ነበር፡፡ እርግጥ ነው ዋልያዎቹ የዓለም ዋንጫና የቻን ማጣሪያ ጨዋታዎች ላይ ከዝሆኖቹ ያነሱ ቡድኖችን እንኳን ማሸነፍ እየተሳናቸው ተደጋጋሚ ሽንፈት እያስተናገዱ መምጣታቸው እንዲናቁ አድርጓቸዋል፡ ፡ ባለፈው ቅዳሜም በዚሁ የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ የምድቡን የመጀመሪያ ጨዋታ ከሜዳቸው ውጪ አድርገው በማዳጋስካር 1ለ0 በመሸነፋቸው ደጋፊያቸው ሳይቀር ከዝሆኖቹ ጋር በሚያደርጉት ጨዋታ ተስፋ ሊጥልባቸው አይችልም፡፡ እግር ኳስ ግን እንዲህ አይደለም:: ያልተጠበቀ ውጤት ማስተናገድ፣ ያሰቡት ቀርቶ ያላሰቡት ነገር መከሰት እግር ኳስን በዓለም ሕዝብ ዘንድ ተወዳጅ ካደረጉት ምክኒያቶች ዋነኛው ነው፡፡ በትናንቱ የዋልያዎቹና የዝሆኖቹ ጨዋታም የታየው ነገር ተቃራኒ ነው፡፡ እንደ ስማቸው ግዙፍ የእግር ኳስ ታሪክ ተሸክመው ወደ ሜዳ የገቡት ዝሆኖቹ በሜዳ ላይ እንቅስቃሴም ይሁን በውጤት ረገድ ከዋልያዎቹ አንስው ተገኝተዋል፡፡ በታላላቅ የአውሮፓ ሊጎች ተፅዕኖ ፈጣሪ የሆኑ በርካታ ከዋክብት ተጫዋቾችን ይዘው የመጡት ዝሆኖቹ ገና በሦስተኛው ደቂቃ ከቆመ ኳስ ግብ አስቆጥረው መምራት ሲጀምሩ በሙሉው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ዋልያዎቹ በምን ያህል የግብ ልዩነት እንደሚሸነፉ ያሰሉ ብዙዎች ናቸው፡፡ ይሁን እንጂ ከ2007 ዓ.ም ጀምሮ በተለያዩ ደረጃዎች የሚገኙ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድኖችም ሆኑ ክለቦች ሽንፈት አስተናግደው የማያውቁበት ገዳሙ የባህርዳር ስቴድየም ትናንትም ዋልያዎቹን አላሳፈራቸውም፡፡ ሱራፌል ዳኛቸው 15ኛው ደቂቃ ላይ በዝሆኖቹ የግብ ክልል አካባቢ ያገኛት ቅጣት ምት ተጨርፋ ከመረቡ ጋር በመዋሃድ ዋልያዎቹን አቻ አድርጋለች፡፡ አሰልጣኝ አብረሃም መብራቱ ዋልያዎቹን መምራት ከጀመሩበት ጊዜ አንስቶ የተሻለ የቡድን እንቅስቃሴና ውህደት ማሳየት የቻሉት ዋልያዎቹ ዝሆኖቹን ለማንበርከክ መጠበቅ የነበረባቸው እስከ 24ኛው ደቂቃ ድረስ ብቻ ነበር፡፡ ጨዋታ አቀጣጣዩ ሽመልስ በቀለ በግሩም እንቅስቃሴ ኳስና መረብን አገናኝቶ ዋልያዎቹ ገና የጨዋታው አንድ አራተኛ ክፍለ ጊዜ ሳይጋመስ ከመመራት ወደ መሪነት አሸጋግሯቸዋል፡፡ በሁለተኛው የጨዋታ ክፍለ ጊዜም ዋልያዎቹ ዝሆኖቹን ቁልቁል እየተመለከቱ በድንቅ እንቅስቃሴና መስዋዕትነት ውጤቱን አስጠብቀው መውጣት ችለዋል፡፡ አሰልጣኝ አብርሃም መብራቱ በዋሊያዎቹ አስራ ስምንት ወራት የኃላፊነት ቆይታቸው አስራ አራት ጨዋታዎችን አድርገዋል፡፡ እንደትናንቱ አይነት ጣፋጭ ድል አጣጥመው ግን አያውቁም፡፡ አሰልጣኙ ከእነዚህ አስራ አራት ጨዋታዎች መካከል የትናንቱን ጨምሮ አራቱን በአሸናፊነት ሲወጡ፣ አምስቱን በአቻ ውጤት ደምድመዋል፡፡ ቀሪዎቹን አምስት ጨዋታዎች ደግሞ ሽንፈት አስተናግደውባቸዋል፡፡ ከዚህም በላይ ዋልያዎቹ ዝሆኖቹን ማንበርከካቸው እየተዳፈነ በመጣው የኢትዮጵያ እግር ኳስ ላይ አዲስ ተስፋን የሚያጭር ክስተት ሆኗል፡፡ ምክኒያቱም ያንበረከኩት ኮትዲቯርን ነው፡፡ የዚህ ድል ትጉሙ ከኳስም በላይ የሚሻገር ስለመሆኑ መዘርዘር አያስፈልግም፡፡ ዋልያዎቹ ያስመዘገቡትን ያልተጠበቀ ድል ተከትሎ ወደ 2021 የካሜሩን አፍሪካ ዋንጫ የማለፍ ተስፋቸው በእጅጉ ለምልሟል፡፡ ዝሆኖቹ ባለፈው ቅዳሜ በመጀመሪያው የምድብ ጨዋታ ኒጄርን በሜዳዋ አንድ ለምንም ማሸነፋቸውን ተከትሎ በሦስት ነጥብ እየመሩ ነበር፡፡ ዋልያዎቹም በምድቡ ተፎካካሪ የሚያደርጋቸውን ሦስት ነጥብ በእጃቸው አስገብተዋል:: በዚህ ምድብ የሚገኙት ማዳካስካርና ኒጄር ትናንት ምሽት ሁለተኛ ጨዋታቸውን አድርገዋል፡፡ ውጤታቸው ማተሚያ ቤት እስከገባንበት ሰዓት ድረስ አልደረሰንም:: ይሁን እንጂ ማዳጋስካር በቅዳሜው ጨዋታ በሜዳዋ ከዋልያዎቹ ያገኘችው ሦስት ነጥብ በምሽቱ ጨዋታ ሽንፈት ቢገጥማት እንኳን በምድቡ እኩል ተፎካካሪ የመሆን እድል እንዳላት ግልፅ ነው፡፡ አዲስ ዘመን ኅዳር 10/2012 ቦጋለ አበበ
https://www.press.et/Ama/?p=22835
463
2ስፖርት
‹‹ ወንጀል ፈጽመው ወደጎረቤት ሀገራት የሸሹ የጁንታው አባላት የሰላም ጠንቅ እንዳይሆኑ ከፍተኛ ሥራ መሠራት አለበት››-ወይዘሮ ያየሽ ተስፋሁነኝ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ብቸኛ የትግራይ ክልል ተወካይ
ሀገር አቀፍ ዜና
December 19, 2020
29
ማህሌት አብዱል አዲስ አበባ፡- በግጭቱ ወቅት ወንጀል የፈፀሙና ሸሽተው ወደጎረቤት ሃገራት የሄዱ ወንጀለኞችና የጁንታው አባላት ተጠናክረው በመምጣት የአገር ሰላም ጠንቅ እንዳይሆኑ ከወዲሁ መሥራት እንደሚያስፈልግ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ብቸኛ የትግራይ ክልል ተወካይ ወይዘሮ ያየሽ ተስፋሁነኝ አስታወቁ። ወይዘሮ ያየሽ ተስፋሁነኝ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንዳስታወቁት፤ በማይካድራም ሆነ በሌሎች አካባቢዎች ላይ በንፁሐን ላይ ጭፍጨፋ ፈፅመው ያመለጡ አንዳንድ የሳምሪ ቡድኖችም ሆኑ ሌሎች የጁንታው አባላት ተጠናክረው ተጨማሪ የሰላም ጠንቅ ከመሆናቸው በፊት መንግሥትና ህዝቡ በመተባበር የጥፋት ኃይሉን በማደን ሊይዙና በህግ ተጠያቂ ሊያደርጉ ይገባል። ‹‹እነዚህ ወንጀለኞች ሸሽተው ሄደው ተጠናክረው በመመለስ የሰላም ጠንቅ እንዳይሆኑ ከጎረቤት አገራት ጋር ባለን ጥሩ ዲፕሎማሲ ግንኙነት በመፍጠር በትብብር መሥራትና ጉዳዩንም መልክ ማስያዝ ይገባል›› ያሉት ወይዘሮ ያየሽ፤ በተለይም የአገሪቱን ሰላም ከማይሹ የውጭ ኃይሎችጋር ተቀናጅተው ችግር ከማስከተላቸው በፊት በከፍተኛ ጥንቃቄ መሠራት እንደሚገባ አሳስበዋል። በሌላም በኩል ጦርነቱን ሸሽተው የተሰደዱ ንፁሐንን ለይቶ ወደ ቀያቸው እንዲመለሱ የማድረጉ ሥራ ተጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባዉ የተናገሩት ወይዘሮ ያየሽሽ ‹‹በዚህ ጉዳይ ላይ ትልቅ ስጋት ነው ያለኝ። መደበላለቅ የለበትም፤ የእውነት ንፁሐን የሆኑትን መለየትና ወደ አገራቸው እንዲገቡ ማድረግ ያስፈልጋል›› ብለዋል። ‹‹ጦርነት ሁልጊዜም ቢሆን አስፈሪ በመሆኑ ጦርነትን ሸሽተው የሄዱ ዜጎቻችንን በተቻለ መጠን አሳምነን መመለስ አለብን›› ያሉት ወይዘሮ ያየሽ፤ ይህም ጠላት ያልሆነውን ወደ ጠላትንት እንዳይቀር የሚያግዝ መሆኑን አስረድተዋል። የጁንታው አመራሮች ህዝቡን “እከሌ መጣብህ፣ ተከበብክ” እያሉ ሲያሳምኑት እንደኖሩት ሁሉ በተሰደዱበት አገርም ተመሳሳይ ሊሠሩ ስለሚችሉ ይህ መልሶ የአገር ሰላም ጠንቅ እንዳይሆን ለይቶ ግንዛቤ መስጠትና መመለስ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 10/2013
https://www.press.et/Ama/?p=37619
211
0ሀገር አቀፍ ዜና
“አሁን ያለችው ትግራይ 95 በመቶ ህግና ሥርዓት የተተገበረባት ናት ” -አቶ ሊላይ ኃይለማርያም፣ የትግራይ ጊዜያዊ መንግሥት ከፍተኛ አስተዳደር
ሀገር አቀፍ ዜና
December 19, 2020
65
አዲሱ ገረመው አዲስ አበባ፡- አሁን ላይ ያለችው ትግራይ የአምባገነኑ ጁንታ እንቅስቃሴ እምብዛም የማይታይበት 95 በመቶ ህግና ሥርዓት የተተገበረባት መሆኗን የትግራይ ጊዜያዊ መንግሥት ከፍተኛ አመራር የሆኑት አቶ ሊላይ ኃይለማርያም ተናገሩ። የህወሓት ጁንታ ከአሁን በኋላ እንደማይመለስና ለመጨረሻ ጊዜ ወደ ገሀነም መውረዱን በመገንዘብም ደጋፊዎችና አባሎቻቸው ወደ ህዝባቸው ተመልሰው ሰላማዊ ኑሯቸውን እንዲመሰርቱና በጋራ አገር ግንባታ ውስጥ እንዲሳተፉም ጥሪ አቅርበዋል። አቶ ሊላይ በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደተናገሩት፤ አሁን ትግራይ በአጠቃላይ 95 በመቶ ህግና ሥርዓት የተተገበረባት ሆናለች። የአምባገነኑ ጁንታ እንቅስቃሴ የሚታይበት ሁኔታ ብዙም የለም። አውሮፕላንን ጨምሮ ትራንስፖርት ከጫፍ እስከ ጫፍ ይንቀሳቀሳል። መብራት እስከ አዲግራት እየሠራ ሲሆን፤ በዚህ ሳምንት ዓደዋና አክሱም ይገባል። አብዛኛው ከተሞችም መብራት ያገኛሉ። የውሃና የኔትዎርክ አገልግሎትም እየተዳረሱ ነው። በሚቀጥለው ሳምንትም የባንክ አገልግሎት በሰፊው ይጀመራል። መቀሌም በጥሩ እንቅስቃሴ ውስጥ ነው ያለችው። ወደ ቀደመ መልኳ ተቀይራለች።የመንግሥት ተቋማት አገልግሎት እንዲሰጡ ከማድረግ አንጻር መቶ በመቶ እንዲከፈቱ ተደርገዋል። በሰለማዊ መንገድ የሚንቀሳቀሰው ሁሉም ሰው ወደ ሥራ ገበታው ገብቷል። ጥሪውን ተቀብለው ወደ ሥራ ያልገቡ ሠራተኞች ላይ በአገሪቷ ህግ መሠረት ዕርምጃ ይወሰዳል። ይሄ ደግሞ የተሾሙት ካቢኔዎች ኃላፊነት ነው። ትጥቅን የማስፈታት እንቅስቃሴውም በጥሩ ሁኔታ እየተካሄደ ይገኛል። ታጥቆ የነበረው ትጥቅ በየቦታው እየተፈታ ነው።ትጥቅን በማስፈታት ረገድ “ከሞላ ጎደል ህዝቡ ሳንጠይቀው ነው እየመጣ ትጥቅ እያስረከበ ያለው” ያሉት አቶ ሊላይ፤ የህወሓት ጁንታ ከጩቤ ጀምሮ እስከ ከባድ ብረቶች ከ200 ሺ በላይ ትጥቅ ያስታጠቀ ቢሆንም እነዚህ እየተመለሱ መሆኑን አስረድተዋል። አንድ ነጥብ ሁለት ሚሊየን ታጣቂ ያለበት ክልል እንደመሆኑ ትጥቅ የማስፈታት ሂደቱ ቀላል እንቅስቃሴ እንዳልሆነና በአንድ ቀን የሚመለስ ሳይሆን ጊዜ የሚጠይቅ መሆኑን በመጠቆምም፤ ህዝቡ ግን በፈቃደኝነት እየመለሰ መሆኑንም ተናግረዋል። ይህ ተግባር ቀጣይነት ያለው መሆኑን እና በዚህ ረገድ መከላከያው እየረዳን ስለሆነ መከላከያ ባለበት ቦታ እየሄዱ ቀበሌ በተመሠረተበት በየወረዳው፣ በየዞኑ በየከተማው አጥጋቢ በሆነ መልኩ እየመለሱ መሆኑንም አብራርተዋል። እንደ አቶ ሊላይ ማብራሪያ፤ ከሰብዓዊ ድጋፍና የመድኃኒት አቅርቦት ጋር ተያይዞ በተለይ በጤና አገልግሎት ባለው ሂደት የፌዴራል መንግሥት በአቅሙ እየረዳ ነው። በቀጣይም ብዙ የሚፈለግ ነገር አለ። ምክንያቱም ሆስፒታሎችና ጤና ጣቢያዎች በጁንታው ተዘርፈዋል። ጁንታው ሲሸሽ ዘርፎ ነው የሄደው። በዚህ ረገድ ብዙ መሥራት ያለብን ነገሮች አሉ። ከዚህ ባለፈ ግን የሰብዓዊ ድጋፉም እየተከፋፈለ ሲሆን፤ በቀጣይ ትምህርት ቤቶችን ለመክፈት በተቀላጠፈና በተጠና መንገድ እየተሠራ ነው። ይሄን ተግባር እንዲፈጽም ኃላፊነት የተሰጠው ጊዜያዊ አስተዳደርም ከተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎችና ዘመናዊ አመለካከት ባላቸው ሰዎች ጋር በመሆን የተዋቀረ ሲሆን፤ የአረና፣ የትዴፓና የብልጽግና ፓርቲዎች በዚህ ውስጥ ከተካተቱት መካከል ናቸው። የፓርቲ አባል ያልሆኑ ግለሰቦችም አሉ። የጊዜያዊ አስተዳደሩ ዕድሜም ስድስት ወር እንደመሆኑ፤ በዚህ ስድስት ወር ጊዜ ውስጥ ህግና ስርዓትን በማስከበር ትግራይን ማረጋጋት ዋና ተግባሩ ይሆናል። ስድስት ወሩ ካለቀ በኋላ ምርጫ ማካሄድ እና የፖለቲካ ፓርቲዎች ተወዳድረው ምርጫ እንዲያደርጉም ይደረጋል። በዚህም ከቀበሌና ወረዳ ጀምሮ ባለው ሂደት ነፃ ምርጫ ይደረጋል። ሰው የፈለገውን እንዲመርጥ ይደረጋል። እንደ ከዚህ ቀደም በካድሬ የሚመራ ሳይሆን በአገር ሽማግሌ እንዲመራ ነው የሚፈለገው። ነፃ በሆነ መንገድ ሰው በወንዙ ልጅ ይመረጣል፤ ይዳኛልም። የጊዜያዊ አስተዳደሩም አቋም ይሄው ነው። ማንም የፖለቲካ ፓርቲ የፈለገውን አመለካከት ይዞ በነፃ በትግራይ በሠላማዊ መንገድ መንቀሳቀስ ይችላል። ህልማችን ክልሉ የዴሞክራሲ ምልክት የሠላም ምልክት የልማት ምልክት እንዲሆን ስለምንፈልግ ምርጫው ፍጹም ሠላማዊ፣ ህዝባዊና ዴሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ ይካሄዳል፤ በማለት አቶ ሊላይ ገልጸዋል።በመጨረሻም “የኢትዮጵያ ህዝብ ለትግራይ ህዝብ የሚያደርገውን ትብብር ማጠናከር አለበት። በዚህም አጋጣሚ የህወሓት ጁንታ ከአሁን በኋላ እንደማይመለስና ፍጹም ለመጨረሻ ጊዜ ወደ ገሀነም እሳት መውረዱን ለደጋፊዎችና ለአባሎቻቸው እየገለጽኩኝ፤ ወደ ህዝባቸው ተመልሰውና ተቀላቅለው ሰላማዊ ኑሯቸውን እንዲመሠርቱ እና እነርሱ ላለፉት 46 ዓመታት ያወደሙትን አገር እንደገና በጋራ እንድንገነባ ጥሪ አቀርባለሁ” በማለት አቶ ሊላይ መልዕክት አስተላልፈዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 10/2013
https://www.press.et/Ama/?p=37618
500
0ሀገር አቀፍ ዜና
በሦስት አገራት 800 ሺ ሕፃናትን ተጠቃሚ የሚያደርግ የትምህርት ፕሮጀክት ሊተገበር ነው
ሀገር አቀፍ ዜና
December 19, 2020
9
አስመረት ብስራት አዲስ አበባ፡- በሦስት የምሥራቅ አፍሪካ ሀገራት ተግባራዊ የሚደረግ ከሦሰት እስከ አስራ ሁለት ዓመት ዕድሜ ክልል ውስጥ የሚገኙ 800 ሺህ ሕፃናትን በጨወታ መልክ ለማስተማር የሚያስችል ለአምስት ዓመታተ ተፈፃሚ የሚሆን ፕሮጀከት ስምምነት ተፈረመ።የፕሮጀክቱ መክፈቻ የፊርማ ስነ ስርዓት ትናንት በኢንተር ኮንቲኔንታል ሆቴል በተከናወነበት ወቅት የፕሮጀክቱ ዳይሬክተር ማረቲን ኦምኩባ እንዳስታወቁት፤ ፕለይ ማተር በሚል ስያሜ በኢትዮጵያ፥ በታንዛኒያና በዩጋንዳ የሚገኙ በስደተኛ ካምፖች ውስጥ የሚኖሩ ሕፃናት ፤ ብሎም በስደተኛ ካምፖች አካባቢ የሚኖሩ የማህበረሰብ ክፍሎች ልጆችን ያጠቃለለ እየተጫወቱ የሚማሩበት ዓይነት የትምህርት ስርዓት ለማዳረስ የሚያስችል ፕሮጀክት ነው።ይህ ፕሮጀክት ከሊጎ ፋውንዴሽን በተገኘ መቶ ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር ተፈፃሚ የሚደረግ መሆኑን የተናገሩት ዳይሬክተሩ፤ በሀገራችን በአፋር፣ በቤኒሻንጉል ጉምዝ፣ በጋምቤላ በሶማሌና በትግራይ ክልሎች ተፈፃሚ እንደሚሆንም ተናገረዋል።ሕፃናት በባህሪያቸው ከቦታ ቦታ በሚንቀሳቀሱበት ጊዜ፤ የተለያዩ የጦረነትና በችግር ሁኔታ ውስጥ ሲቆዩ የተለያዩ የስነልቦና ጫናዎች ሊገጥሟቸው እንደሚችሉ የተናገሩ ሲሆን፤ በቅድመ መደበኛና በመደበኛ ደረጃ የሚገኙ ሕፃናት በስነልቦና፤ በጠቅላላ እውቀት በአዕምሯዊና በአካላዊ ዕድገት ሊደግፋቸው የሚችል የትምህረት ስርዓት መሆኑ ተጠቁማል።እንደ ዳይሬክተር ማረቲን ገለፃ፤ ሕፃናትን በተለያዩ የጨዋታ መልኮች በማስተማር አወንታዊ ተፅእኖዎቹ በጣም ከፍተኛ መሆኑን አስረድተው፤ በመማር ማስተማር ስርዓቱ ውስጥ ቤተሰቦቻቸው፤ የተለያዩ በቅርበት የሚገኙ አካላትና በስደተኛ ካምፑ ውስጥ የሚኖሩ የተለያዩ አገልገሎት ሰጪዎች ተሰታፊ የሚሆኑበት ነው።የፕሮጀክቱ መጨረሻ ላይ እንደ ግብ የተቀመጠው በመማር ማስተማሩ ልጆቹ የተሻለ የትምህርት አቅም መገንባታቸው ታይቶ እንደየአካባቢው ነባራዊ ሁኔታ በመቀያየር ውጤት ላይ መድረስ መሆኑን ጠቁመዋል። በፕሮጀክቱ መክፈቻ እና የፊርማ ሥነስርዓት ላይ የስደተኛ ጉዳዮች ተወካይ፣ ከትምህርት ሚኒስቴር የተወከሉ ግለሰብና፣ በፕሮጀክቱ ላይ ተሳታፊ የሚሆኑ ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 10/2013
https://www.press.et/Ama/?p=37629
218
0ሀገር አቀፍ ዜና
በዘንድሮ የመስኖ ልማት ከቆላማ አካባቢዎች በተጨማሪ በሌሎች ክልሎች ለማስፋት መታቀዱ ተገለጸ
ሀገር አቀፍ ዜና
December 19, 2020
9
እፀገነት አክሊሉ ባለፉት ሁለት ዓመታት በቆላማ አካባቢዎች ላይ ስንዴን በመስኖ በማልማት የተገኘውን ውጤት በመቀመር ዘንድሮ ደግሞ ወደሌሎች ክልሎች በማስፋት ውጤታማ ሥራዎችን ለመሥራት መታቀዱን የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ። በግብርና ሚኒስቴር የአነስተኛ መስኖ ልማት ማስፋፊያ ዳይሬክተር አቶ ኤልያስ አወል በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደተናገሩት ባለፉት ዓመታት በተለይም በቆላማ አካባቢዎች ላይ ስንዴን በመስኖ ለማልማት የተጀመረው ሥራ እንደ ጠቅላላ መልካምና ጥሩ ውጤት የታየበት ነበር፤ በዚህም በአፋርና በሶማሌ ክልሎች ላይ የተሠሩት ሥራዎች ብዙ ጥረት የጠየቁ ቢሆንም በውጤት ደረጃ ግን ሲመዘኑ አበረታች ናቸው።እንደ አቶ ኤልያስ ገለጻ ዘንድሮ ደግሞ ያለፉትን ጊዜያት ተሞክሮ በመቀመርና ከቆላማ አካባቢዎች በተጨማሪ በአማራ። ኦሮሚያና ደቡብ ላይ መስኖን በመጠቀም የተለያዩ ሰብሎችን ለማምረት ታቅዷል። በዚህም መሰረት ክልሎች የየራሳቸውን እቅድ ይዘው እየተንቀሳቀሱ እንደሚገኙ አብራርትዋል። በየዓመቱ የመኸሩ የግብርና ሥራ እንደተጠናቀቀ የሚገባው ወደመስኖ ሥራ ነው ያሉት አቶ ኤልያስ ፤ በያዝነው ዓመትም ይህንኑ አቅጣጫ በመከተል ለአመራሩ የግንዛቤ ማስፋት እስከ ወረዳ ድረስ ላሉ ባለሙያዎች ደግሞ ስልጠናዎችን በመስጠት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል። አምና የመስኖ ሥራውን ለማስፋፋት በአብዛኞቹ ክልሎች ላይ ከከርሰ ምድር ውሃን ለመሳብ የሚያገለግሉ የውሃ መሳቢያዎች (ፓምፖች) በየክልሎቹ የማከፋፈል ሥራ ተከናውኗል ያሉት አቶ ኤልያስ፤ አሁን ላይ በብልሽት የቆሙም ካሉ ተጠግነው ሙሉ በሙሉ ወደሥራ እንዲገቡና የግብርና ሥራውን እንዲያቀላጥፉ ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ መሆኑንም ጠቁመዋል። በሌላ በኩልም በግብርና ሚኒስቴር የሚተዳደሩ የመስኖ አውታሮች በተለያዩ ፕሮጀክቶችና በመንግሥት በጀት የሚሠሩ እንዳሉ የገለጹት አቶ ኤልያስ እነዚህም አምና የተጀመሩ በመሆኑ አሁን በተጠናከረ መልኩ ተጠናቀው ወደ ሥራ መግባት ስላለባቸው ከፍተኛ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራ መሆኑንም አብራርተዋል። በተመሳሳይም አርሶ አደሩ በራሱና በቤተሰቦቹ ጉልበት እንዲሁም በአቅራቢያው የሚገኙ ቁሳቁሶችን ተጠቅሞ ከከርሰ ምድር ውሃ እያወጣ እንዲሁም በጓሮው የውሃ ማቆር ሥራን እያከናወነ የልማት ሥራውን እንዲያከናውን ሰፋፊ ሥራዎች እየተሠሩ መሆኑንም ተናግረዋል። በተለይም በቤተሰብ ደረጃ የተዘጋጁትን ከጥር ወር ጀምሮ ወደሥራ ለማስገባትና ውጤታማ ሥራን ለማከናወን እንደ ግብርና ሚኒስቴር ዝግጅቱ መጠናቀቁንም አብራርተዋል።የዘንድሮው የመስኖ ሥራ ከወትሮው በተለየ መልክ አምበጣም ኮሮና ቫይረስም በምርት ላይ ያሳደሩትን መጠነኛ ተጽዕኖ ለማለፍ በሚያስችል መልኩ ለመሥራትና ውጤታማ ለመሆን የሚያስችል ዝግጅት ስለመኖሩም ጠቁመዋል። በዚህ መሰረት በዘንድሮው የመስኖ ልማት ሥራ በሽፋንም በአጠቃላይ በምርትም በኩል ጥሩና አበረታች ለውጦች ይገኛሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ አቶ ኤልያስ ተናግረዋል። በተለይም በስምጥ ሸለቆ አካባቢ ባሉ ቦታዎች ላይ እንደ ሽንኩርት߹ ቲማቲምና ቃሪያ የመሳሰሉ አትክልቶችን በማምረትና ወደገበያ በማምጣት ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግ በርካታ የመስኖ ውሃ መሳቢያ ማሽኖች (ፓምፖች) መሰራጨታቸውንና ይህ ሥራ ደግሞ በግለሰብ ደረጃም እንዲሁም የአካባቢው አርሶ አደሮች ተደራጅተው የሚሠሩት መሆኑን ከግብርና ሚኒስቴር የተገኘ መረጃ ያመለክታል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 10/2013
https://www.press.et/Ama/?p=37620
349
0ሀገር አቀፍ ዜና
የጋራ ሀብት ለጋራ ጥቅም
ሀገር አቀፍ ዜና
December 19, 2020
15
ጽጌረዳ ጫንያለው የህወሓት ጁንታ የአገሪቱን የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ በጥቂት ተቋማቱ አማካኝነት የግሉ አድርጎት ቆይቷል። ነገር ግን ሲጠቀምበት የቆየው የአገር ሀብት በመሆኑ እነዚህ የታገዱ ተቋማት በመንግሥት ተወርሰው አገርን ተጠቃሚ በሚያደርጉበት መልኩ ሊሠራባቸው እንደሚገባ የምጣኔ ሀብት ባለሙያዎች ይናገራሉ። በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የኢኮኖሚ መምህር ዶክተር አሰፋ አድማሴ እንደተናገሩት፤ ነፃ ገበያ ማለት ዋና መርሁ ሁሉም በእኩል ደረጃ መገበያየት የሚለውን ይይዛል። የማወዳደሪያ ሜዳውም እኩል የሆነ ነው። ነገር ግን የህወሓት ጁንታ የሃገሪቱን ሀብት በመዝረፍ በቁጥጥሩ ስር አድርጎ በመቆየቱ፤ ገበያውን እኩል መቀላቀል አይፈቀድም ነበር። በዚህም ያለፉት በርካታ ዓመታት እንደ አገር የነበረው ኢኮኖሚ በጥቂቶች የተያዘና ጥቂቶች የሚዘውሩት ነበር። በተለይም ከመንግሥት ጋር የተጣበቁ ኩባንያዎች፣ ድርጅቶችና ግለሰቦች የበላይነትን ያገኙበት ነበር። የመወዳደሪያ መንገዱንም ለሥርዓቱና ለራሱ ተከታዮች ብቻ በማድረግ ሜዳውን አጥብቦት ቆይቷል። ይህ ደግሞ ሀቀኛ የነበሩ ግለሰቦች፣ ድርጅቶችና ኩባንያዎችን ከጨዋታ ውጪ አድርጓቸዋል። እንደ ዶክተር አሰፋ ማብራሪያ፤ አሁን ታገዱ የተባሉት የጁንታው ኩባንያዎች በተለይ የአገሪቱን ማክሮ ኢኮኖሚ ሲዘውሩት ነበር። በነፃ ገበያ ስም ከሥርዓቱ ጋር እጅና ጓንት የነበሩ የተጠቀሙበት ነው። በዚህም ህግ የሚያስፈጽሙ ህጋዊ ተቋማት ሳይቀሩ የዚህ ድርጊት ተሳታፊ ነበሩ። ስርዓቱን ለማስፈጽም የተለያዩ ቢሮክራሲ ተጠቅመው የአገር ሀብትን እንዲበዘበዝ አድርገዋል። ህጋዊ የሆኑ ኩባንያዎች፣ ድርጅቶችና ግለሰቦችም ከጨዋታ ውጪ እንዲሆኑ በማድረግ የአገር ሀብት ወደ አንድ ቋት እንዲገባም ሲሠሩ ነበር። የኢኮኖሚ ጉዳይ የህወሓት ጁንታ መወገድ ጉዳይ ብቻ እንዳልሆነ የሚያነሱት ዶክተር አሰፋ፤ ስርዓቱ ሙሉ ለሙሉ ካልተወገደና አሠራሩ በሚባለው የኢኮኖሚ ህግ መመራት ካልቻለ አሁንም ቢሆን ችግሩ አይቀሬ ነው፤ የህወሓት ጁንታ የፈጠረው አስተሳሰብ አሁንም በኢኮኖሚው ሴክተር ላይ ይታያል ብለዋል። እነዚህ የጁንታው የንግድ ተቋማትም አሁን መታገዳቸው እንዳለ ሆኖ ወደ ተግባር ሲገቡም ጥንቃቄ እንደሚያስፈልጋቸው ጠቁመዋል። የኢኮኖሚና ፖለቲካ ምሁሩ አቶ ሸዋፈራሁ ሽታሁን በበኩላቸው እንደሚናገሩት፤ እንዲህ ዓይነት ችግሮች የሚፈጠሩት የአገሪቱ ልሂቃን የአገሪቱን አንጡራ ሀብት ለታችኛው የህብረተሰብ ክፍል የሚደርስበትን ሁኔታ የሚወስኑበት ተቋማዊ አሠራር ሲጠቀሙ ነው። ይህም ፖለቲካዊ ኢኮኖሚ ይባላል። ስለሆነም የህወሓት ጁንታም የተጠቀመው ይህንን አሠራር ነው። በዚህም እርሱ ለፈቀዳቸውና አጋሬ ናቸው ለሚላቸው ገበያውን አመቻችቷል። ተጠቃሚም አድርጎበታል። ይህ ደግሞ ጥቂቶች በአገሪቱ ሀብት እንዲያዙ ዕድል ሰጥቷቸዋል። የፖለቲካ ስልጣን የያዘ አካል ሀብቱን የመያዝ ዕድሉ የተመቻቸ በመሆኑ ኢኮኖሚውን መዘወሩ እንደማይቀር የሚገልጹት አቶ ሸዋፈራሁ፤ የህወሓት አብዮታዊ ዴሞክራሲ ስርዓትን ተከታይ እንደመሆኑ ይህ አስተሳሰብ ጠላትና ወዳጅን የመያዝን መርህ የተከተለ እንደሆነ አስረድተዋል። በመሆኑም ልማታዊ ባለሀብት፣ አርሶአደር፣ ወዘተ፣ እያለ ከእርሱ ወገን ያሰለፈውን ሲጠቅም የቀድሞ ናፋቂ ያላቸውን ደግሞ ሲጎዳና ከውድድር ውጪ ሲያደርግ መቆየቱን ተልጸዋል። በዚህ አስተሳሰቡም የአገሪቱን ሀብት የጥቂቶች መፈንጫ ማድረጉን እና ዛሬ ታገዱ የተባሉት ተቋማትም የተፈጠሩት በዚህ አማካኝነት እንደሆነ ይናገራሉ። የህወሓት ጁንታ ደግሞ ለሞራልም ለህግም የማይገዛ በመሆኑ ነው የአገሪቱን ሀብት በጥቂቶች እጅ እንዲገባ ያደረገው የሚሉት የምጣኔ ሀብት ባለሙያው፤ በራሱ ብቻ የሚንቀሳቀስ ባለመሆኑ በአጋሮቹ አማካኝነት ጭምር ተቋማትን መስርቶ ታክስ የማይከፍሉ፣ ብድር ወስደው የማይመልሱ አድርጓል። ከዚያም አልፎ የአገሪቱ ሀብት ወደ አገር እንዳይመለስ እንዲባክንና ወደውጪ እንዲወጣ በታትኖታል። ሀገሪቷንም እዳ አሸክሟታል። ከዚያ ያለፈውን ደግሞ በብሔር እየከፋፈለም ሀብቱ በታገዱት ተቋማት አማካኝነት እንዲቀመጥ እንዳደረገም ይገልጻሉ። መፍትሔው የህወሓትን ጁንታ ሲደግፉና በሞኖፖል የአገሪቱን ገበያ ሲይዙ የነበሩ ተቋማት መታገዳቸው አንዱ መሆኑን የሚጠቁሙት ዶክተር አሰፋ፤ የተቋማቱ መታገድ የገበያ ተወዳዳሪነታቸውን ያሳልጣል፤ የእውነተኛ ተቋማትን ተወዳዳሪነትን አብዝቶ ነጋዴውም ሆነ ሸማቹ በእኩል ደረጃ እንዲጠቀም ያስችላል። አገር ላይ እየታየ ያለው የዋጋ ግሽበት ተጽዕኖም ይቀንሳል። ዋጋ የሚተመነው ሜዳ ላይ በሚደረገው ፉክክርና ባለው አገልግሎት ልክ ይሆናል። በተለይ እስከአሁን ቅሬታ የነበረው የመወዳደርና ገበያውን የመቀላቀል ጉዳይን መፍትሔ ይሰጣል፤ ሲሉ አብራርተዋል። እነዚህ ተቋማት በመታገዳቸው ጊዜያዊ የሆኑ ችግሮች ሊፈጠሩ እንደሚችሉ የሚያነሱት ዶክተር አሰፋ፤ እስከአሁን በነበረው ሥርዓት ገበያውን ጠቅልለው የያዙት ጥቂቶች በመሆናቸው ሌሎች ተወዳዳሪ ግለሰብና ድርጅቶች እንዳይኖሩ ሆናል። ስለዚህም የተወዳዳሪ ድርጅቶች እጥረት ያጋጥማል። ነገር ግን ፍላጎትን በማስፋትና ውድድሮችን ክፍት በማድረግ በአሠራር ይህንን መመለስ እንደሚቻል አስረድተዋል። አቶ ሸዋፈራሁ በበኩላቸው፤ መፍትሔ ነው የሚሉትን ያነሳሉ። የመጀመሪያው የታገዱ ተቋማት በመንግሥት መወረስ አለባቸው። ወደ ግል ተዛውረው ቁጥጥሩ በመንግሥት ሆኖ አገራዊ ዓላማን አንግበው አገልግሎት መስጠት ይኖርባቸዋልም ባይ ናቸው። ምክንያታቸውም ተቋማቱ ከአመሰራረታቸው ጀምሮ የአገር ሀብት የፈሰሰባቸው ናቸው። የባለቤትነት ጉዳይም ሌላው ችግር ይሆናል። ተቋማቱ የተቋቋሙት በኢትዮጵያ ሀብት በመሆኑ የኢትዮጵያውያን እንጂ የአንድ ብሔር አይደሉም። ስለሆነም የባለቤትነት ጥያቄን እንዳያስነሱ ተደርጎ ሊሠራባቸው ይገባል። እነዚህ ተቋማት በኢኮኖሚው ህግ መሪ ሴክተር ሞዴል ሊሆኑም የሚችሉ ናቸውና አጠቃላይ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴውን እንዲመሩና ተጠቃሚነቱ የአገር እንዲሆን ማድረግ ከተቻለ እስከ ዛሬ የነበሩትን ስህተቶች በማረም ጭምር ዕድል እየሰጡ ያስጉዙናል ይላሉ። በተደረጉ አንዳንድ ውሳኔዎች ብቻ ለውጡ ከመጣ በኋላ ከፋይናንስ ተቋማት ውስጥ በዋናነት የሚጠቀሱት ባንኮችና ኢንሹራንሶች ከፍተኛ ለውጥ አምጥተዋል። ለአብነት አሥራ ስድስቱ የግል ባንኮች ያስመዘገቡት ትርፍ ከአሥር ቢሊዮን ብር በላይ ደርሷል። ከ120 ሚሊዮን ብር ጀምሮ እስከ 2 ነጥብ 9 ቢሊዮን ብር አትርፈዋል። የባንኮቹ ተቀማጭ ገንዘብም ቢሆን እንዲሁ ከ720 ቢሊዮን ብር በላይ ሆኗል። አጠቃላይ ሀብታቸውም ከአንድ ትሪሊዮን ብር በላይ እንደደረሰ የ2010 ሪፖርት ያስረዳል። የኢንሹራንስ ኩባንያዎችም እንዲሁ ከ1 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በላይ ያተረፉበትና በጠቅላላው የኢንሹራንስ ኩባንያዎች ከ8 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ የሰበሰቡበት ዓመት እንደነበር የኢንዱስትሪው ዓመታዊ የሒሳብ ሪፖርት ያመለክታል። በቀጣይ ሁለቱም ባለሙያዎች እነዚህ ተግባራት ቢፈጸሙ የሃገር ሀብት የግለሰቦች መጠቀሚያ አይሆንም ይላሉ። የመጀመሪያው የዴሞክራሲ ስርዓቱን በይበልጥ በህብረተሰቡ ውስጥ ማስረጽ፤ ያለፈው ስርዓት ብዙ ያስተማረው ነገር አለና ያንን ላለመድገም መሞከር፤ ሁሉም የኢኮኖሚ አጋር በእኩል ዓይን እንዲታይ ማድረግ፤ የገበያ ሁኔታን ክፍት ማድረግ ናቸው። አንዱ ተሸናፊ ሌላው አሸናፊ የሚለውን አስተሳሰብም ማስወገድ፤ አሸናፊ ሆኜ እወጣለሁ የሚለውን አስተሳሰብ መስበር፤ ፍትሐዊ የሆነ የምርት ስርዓት፣ የሀብት አጠቃቀምና የኢኮኖሚ ፖሊሲ ማውጣትና ተግባራዊ ማድረግ ሌላው አማራጭ ነው።አዲስ ዘመን ታህሳስ 10/2013
https://www.press.et/Ama/?p=37634
760
0ሀገር አቀፍ ዜና
ምክር ቤቱ ለሀገራዊ የኢኮኖሚ ማሻሻያና የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጣና ስኬታማነት የበኩሉን ድጋፍ እንደሚያደርግ ገለጸ
ሀገር አቀፍ ዜና
December 19, 2020
9
በጋዜጣው ሪፖርተር አዳማ፡- በሀገሪቱ እየተካሄደ ያለው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያና የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጣና ስምምነት ውጤታማ እንዲሆን ድጋፍ እንደሚደረግ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ ታገሰ ጫፎ አስታወቁ። በንግድ ስርዓት ማሻሻያ፣ በአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጣና ስምምነት አተገባበርና ኢትዮጵያን የዓለም ንግድ ድርጅት አባል ለማድረግ እየተከናወኑ ባሉ ሥራዎች ዙሪያ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት የተዘጋጀ የግንዛቤ መፍጠሪያ መድረክ ትላንት በአዳማ ከተማ ተጀምሯል።የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ ታገሰ ጫፎ በወቅቱ እንደገለጹት ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያና የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጣና ስምምነት ውጤታማ እንዲሆን በትብብር መሥራት ይገባል። ምክር ቤቱ ነፃ የንግድ ቀጣና ስምምነት ማፅደቁን የገለጹት አፈ ጉባኤው ለስምምነቱ ውጤታማነት ምክር ቤቱ ተገቢውን ድጋፍ እንደሚያደርግ አስታውቀዋል። በንግድ ዘርፉም ሆነ አጠቃላይ የኢኮኖሚ ማሻሻያው የታሰበለትን ውጤት እንዲያመጣ ምክር ቤቱ የህግ ማዕቀፎችን ከማሻሻል ጀምሮ ተገቢውን ድጋፍና ክትትል እንደሚያደርግ አመላክተዋል። “በአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጣና ውስጥ ከጎረቤት ሀገራት ጋር የሚያስተሳስር መሰረተ ልማት ቁልፍ ሚና አለው” ያሉት አፈ ጉባዔው ከኬንያ፣ ደቡብ ሱዳን፣ ጅቡቲና ሌሎች ሀገራት ጋር እየተከናወነ ያለው የመሰረተ ልማት ትስስር ለዚህ አንዱ ማሳያ መሆኑን ጠቅሰዋል። በቀጣይም ህጎችና አሠራሮችን በመፈተሽ ማሻሻያ የማድረግ ሥራው ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አፈጉባኤው ጠቁመዋል። በሀገሪቱ ለተጀመረው የንግድ ዘርፍ ስር ነቀል ለውጥ ከህግ አውጪው ጀምሮ ሁሉም በቅንጅት መሥራት እንዳለበት አስገንዝበዋል። በመድረኩ የተሳተፉ የምክር ቤቱ አባላት በጉዳዩ ዙሪያ በቂ ግንዛቤ እንዲይዙ በማድረግ በቀጣይ ለሚሠሩ ሥራዎች ውጤታማነት ተገቢው ድጋፍና ክትትል እንደሚደረግ አፈ ጉባኤው አስታውቀዋል። የሀገሪቱን የንግድ ስርዓት ለማዘመን እየተሠራ መሆኑን የገለጹት ደግሞ የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ተወካይ አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ ናቸው።የውጪ ንግድን ማሳደግ፣ የገበያ መዳረሻዎችን ማስፋት፣ ምርትና ምርታማነትን መጨመር፣ የቴክኖሎጂ ሽግግር ማሳደግና ማስፋፋት ላይ በትኩረት እየተሠራ መሆኑንም አምባሳደር ምስጋኑ ጠቅሰዋል። የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ማሻሻያ እንዲሳካ፣ ከመጪው ጥር ወር ጀምሮ ተግባራዊ ከሚሆነው የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጣና ተጠቃሚ እንድትሆንና የዓለም የንግድ ድርጅት አባል የማድረግ ሥራ ተጠናክሮ መቀጠሉን አመልክተዋል። “ውህደቱ በሚፈጥረው ምቹ ሁኔታ ሀገሪቱ የተሻለ አገልግሎት እንድታገኝና ተወዳዳሪ እንድትሆን ጭምር እየሠሩ መሆናቸውንም አምባሳደር ምስጋኑ ተናግረዋል ሲል የዘገበው ኢዜአ ነው።አዲስ ዘመን ታህሳስ 10/2013
https://www.press.et/Ama/?p=37635
288
0ሀገር አቀፍ ዜና
ዩኒቨርሲቲዎቹ በ2013 ሰላማዊ የመማር ማስተማር እንዲኖር እየሠሩ መሆኑን ገለጹ
ሀገር አቀፍ ዜና
December 19, 2020
12
 • የኮቪድ-19 መከላከልን ታሳቢ አድርገው ተመራቂ ተማሪዎችን መቀበላቸውንም ጠቁመዋል ፋንታነሽ ክንዴ አዲስ አበባ፡- ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ በተደጋጋሚ የሚከሰትን የፀጥታ ችግር ከግንዛቤ በማስገባት በ2013 የትምህርት ዘመን ሰላማዊ የመማር ማስተማር እንዲኖር የሚያስችሉ ሥራዎችን እየሠሩ መሆኑን የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ እና ወልዲያ ዩኒቨርሲቲዎች ገለጹ። ዩኒቨርሲቲዎቹ በሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ኮቪድ 19ን ለመከላከል የተቀመጡ ቅድመ ዝግጅቶችን በማጠናቀቅ ተመራቂ ተማሪዎችን መቀበላቸውንም አስታውቀዋል።የየዩኒቨርሲቲዎቹ አመራሮች ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደገለጹት፤ ባለፉት ዓመታት በዩኒቨርሲቲዎች የሚስተዋል የፀጥታ ችግር በመማር ማስተማር ሂደቱ ላይ እክል ሲፈጥር ቆይቷል። በዚህ ዓመት ግን ያን ዓይነት ችግር እንዳያጋጥምና ሰላማዊ የመማር ማስተማር ሂደት እንዲፈጠር እየሠሩ ይገኛል። የወቅቱ ስጋት የሆነው የኮቪድ-19 ወረርሺኝን ለመከላከልም እየሠሩ ሲሆን፤ ተመራቂ ተማሪዎችን የተቀበሉትም በሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር የተቀመጠውን መስፈርት በማሟላት ነው።የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ዓለም አቀፍ ግንኙነትና ኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ዶክተር ካሣዬ ጉተማ በተለይ ለአዲስ ዘመን እንደገለጹት፤ ቀደም ሲል በተማሪዎች ምክንያት በዩኒቨርሲቲው የሚታዩ የፀጥታ ችግሮች የነበሩ ቢሆንም፤ በ2013 ዓ.ም ያን ዓይነት የፀጥታ ችግር እንዳያጋጥም እና ሰላማዊ የመማር ማስተማር ሂደት እንዲፈጠር ለማድረግ ሥራዎችን ሲሠሩ ቆይተዋል። በዩኒቨርሲቲው ከሚሠሩ ሥራዎች በተጓዳኝም በግቢው ውስጥ የፌዴራል ፖሊስ ጥበቃ እያደረገ ይገኛል።እንደ ዶክተር ካሣዬ ገለጻ፤ በዩኒቨርሲቲው ውስጥ የፀጥታ ችግር እንዳያጋጥም ከከተማ አስተዳደሩ ጋር በመሆን የዩኒቨርሲቲውን ጥበቃ እና የፌዴራል ፖሊስን በማቀናጀት ለተማሪዎች የግንዛቤ መፍጠር ሥራ ተሠርቷል። ተማሪዎች በሚንቀሳቀሱባቸው ቦታዎች የሚገጥማቸው ትንኮሳ ካለ ለሚመለከታቸው የፀጥታ አካላት ሪፖርት ማድረግ እንዳለባቸው ተነግሯቸዋል። ቀጣይ ሌሎች ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲው በሚመጡበት ወቅትም በየባቻቸው የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራ ይሠራል።ከፀጥታ ሥራው ባሻገር የኮቪድ-19 ወረርሺኝን መከላከል ላይ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራ መሆኑን የተናገሩት ዶክተር ካሣዬ፤ በዚህም በሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር እንዲሟሉ የተቀመጡ መመዘኛዎችን በማሟላትና ይሄንኑ በማስገምገም ተመራቂ ተማሪዎችን ተቀብለው ማስተማር እንደሚችሉ ማረጋገጫ ከተሰጣቸው በኋላ ተማሪዎችን መቀበላቸውን ተናግረዋል። እንደ ዶክተር ካሣዬ ማብራሪያ፤ ዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲው ሲገቡ የኮቪድ 19 ምር አድርገው እንዲገቡ፤ ኮቪድን ለመከላከል የሚያግዝ ሳኒታይዘር በዩኒቨርሲቲው ተመርቶ ለተማሪዎች እንዲቀርብ ተደርጓል። ከዚህም ባለፈ በኮቪድ ፕሮቶኮል መሰረት በዩኒቨርሲቲው ያሉ የተማሪዎች ማደሪያ፣ መታጠቢያና የመመገቢያ ቦታዎች ተጎብኝተው ብቁ መሆናቸው የተረጋገጠ ሲሆን፤ በተለይ ከተማሪዎች ማደሪያ ጋር በተያያዘ በአንድ ዶርም ውስጥ አንድ አንድ ተማሪ ብቻ እንዲመደብ ተደርጓል። በመማሪያ ክፍሎችም ከ20 ያልበለጡ ተማሪዎችንመራ ብቻ በመመደብ የተመራቂ ተማሪዎች የመማር ማስተማር ሥራውን ሲያከናውን የቆየና ተማሪዎቹም እንደሚመረቁ የጠቆሙት ዶክተር ካሳዬ፤ ቀሪ ተማሪዎችን ታህሳስ 15 ቀን 2013 ዓ.ም እንደሚቀበሉ አስታውቀዋል።የወልድያ ዩኒቨርሲቲ ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር አቶ ተፈራ አስናቀ በበኩላቸው፤ በዩኒቨርሲቲው የመማር ማስተማር ሥራው በፀጥታ ችግር እንዳይስተጓጎል በማሰብ በርካታ ሥራዎች ተሠርተዋል። የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴርም ይሄን ታሳቢ ያደረገ የትምህርትና ስልጠና አማካሪ ምክር ቤት ማቋቋሚያ መመሪያ የላከ ሲሆን፤ ይህን ተከትሎ 30 አባላት ያሉት አማካሪ ምክር ቤት ተቋቁሟል። አማካሪ ምክር ቤቱ የዞኑ አስተዳዳሪ የሚመሩትና የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ፀሐፊ የሆኑበት ሲሆን፤ ከከተማው የአገር ሽማግዎች፣ የሃይማኖት አባቶችና ወጣቶች የተካተቱበት ነው።እንደ አቶ ተፈራ ገለጻ፤ አማካሪ ምክር ቤቱ በየጊዜው እየተገናኘ በግቢው ውስጥ ለግጭት ምክንያት ሊሆኑ የሚችሉ ነገሮች መኖራቸውን እየገመገመ የመማር ማስተማር ሥራው በትክክል እንዲቀጥል የሚያደርግ ነው። ምክር ቤቱ በዩኒቨርሲቲው በመገኘት ዝግጅቱ ምን ይመስላል የሚለውን የገመገመ ሲሆን፤ ዩኒቨርሲቲውን ከሚጠብቁ ፌዴራል ፖሊሶችና የግቢው ጥበቃዎች ጋር በመሆን የተለያዩ ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛል።በአገልግሎት አሰጣጥ፣ በምግብ አቅርቦት፣ በቤተመጽሐፍ በተለይም ደግሞ ከመብራትና ውሃ አቅርቦት ጋር ተያይዞ የሚነሱ ችግሮች ሲኖሩ ያንን መነሻ አድርገው ለግጭትና ለሁከት የሚዳርግ ነገር ሲፈጠር እንደነበር ያስታወሱት አቶ ተፈራ፤ ይህንን ለመፍታት ዩኒቨርሲቲው የራሱ የሆነ የውሃ መስመር እንዲኖረው መደረጉን እና የመብራት መቆራረጥ በሚኖርበት ጊዜም ጀነሬተር ማዘጋጀቱን ተናግረዋል። ከዚህ ባሻገር በዩኒቨርሲተው ዙሪያ የንግድ ቤቶች መኖራቸውንና በእነዚህ ቤቶች ደግሞ መጠጥ እና ሌሎች አደንዛዥ እጾች ሽያጭ እየተበራከተ እንደመሆኑ፤ እንዲህ ዓይነት ግጭቶች እንዲባባሱ በማድረግ በመማር ማስተማር ሂደቱ ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ የሚያሳድሩ ችግር ለማስወገድም ጉዳዩ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን እየተሠራ መሆኑን ተናግረዋል።በጸጥታ ሥራው በተጓዳኝ የኮቪድ 19 መከላከል ሥራ ላይ ትኩረት አድርገው እየሠሩ መሆኑን የጠቆሙት አቶ ተፈራ፤ የመማር ማስተማር ሥራው ኮቪድ 19ኝን በመከላከል እንዲቀጥል በተሰጠው አቅጣጫ መሰረት ተመራቂ ተማሪዎችን ተቀብሎ እያስተማረ መሆኑን ተናግረዋል። ኮቪድን ለመከላከል በተዘጋጀው ፕሮቶኮል መሰረት የተለያዩ ዝግጅቶችን ሲያደርጉ መቆየታቸውን የገለጹት አቶ ተፈራ፤ ሳኒታይዘር በግቢው ውስጥ በማምረት ለተማሪዎችና ለዩኒቨርሲቲው ማሕበረሰብ እንዲቀርብ ተደርጓል። በዩኒቨርሲቲው ለተማሪዎች የተዘጋጀ ማስክም ተሰራጭቷል። ከእጅ ንክኪ ነፃ የሆነ የእጅ መታጠቢያ በየቦታው መቀመጡንም ተናግረዋል። እንደ አቶ ተፈራ ገለጻ፤ ከዚህ በፊት በአንድ ዶርም ውስጥ ስድስት ተማሪዎች ይመደቡ ነበር። በአሁኑ ወቅት ግን ሁለት ተማሪዎች ብቻ እንዲመደቡ ተደርጓል። በመማሪያ ክፍሎችም ሃያ አምስት እስከ ሠላሳ ተማሪዎች ብቻ እንዲማሩ በዩኒቨርሲቲው ሰኔት ተወስኗል። በቤተ መጽሐፍት እና በመመገቢያ አዳራሾችም አስፈላጊውን እርቀት ጠብቀው እንዲስተናገዱ ለማድረግ እየተሠራ ነው። ዩኒቨርሲቲው ለአካባቢው ማህበረሰብ የኮቪድ 19 ምርመራ አገልግሎት ሲሰጥ እንደነበር ጠቅሰው፤ በሂደት ችግር ቢፈጠር እንኳን በግቢው ውስጥ ምርመራ እንደሚካሄድ ገልጸዋል። ይህንን ታሳቢ በማድረግም የለይቶ ማቆያ ቦታዎች ተዘጋጅተዋል። በኮቪድ መከላከል ፕሮቶኮል ዙሪያ ከተማሪዎች ጋር ውይይት መደረጉን እና ከተማሪዎች ጋር ቅርብ ግንኙነት ላላቸው ሠራተኞች የግንዛቤ ፈጠራ ሥራ መሠራቱንም አስረድተዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 10/2013
https://www.press.et/Ama/?p=37627
677
0ሀገር አቀፍ ዜና
ከሀገራዊ የልማት እቅዱ ጎን ለጎን የዋጋ ግሽበትን በመቆጣጠር እውነተኛ ዕድገት ማምጣት እንደሚቻል ተጠቆመ
ሀገር አቀፍ ዜና
December 19, 2020
19
ፍሬህይወት አወቀ አዲስ አበባ፡- ከ10 ዓመቱ ሀገራዊ የልማት እቅድ ጎን ለጎን የዋጋ ግሽበትን በመቆጣጠር በሀገሪቱ ኢኮኖሚ ላይ እውነተኛ ዕድገት ማምጣት እንደሚቻል ተጠቆመ።በሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የኢኮኖሚክስ መምህር ዶክተር ሞላ ዓለማየሁ ለአዲስ ዘመን እንደተናገሩት፤ የዋጋ ግሽበትን በመቆጣጠር በአስር ዓመቱ አገራዊ ልማት እውነተኛ ዕድገት ማምጣት የሚቻል ሲሆን፤ የሀገሪቱን የ10 ዓመት የልማት እቅድ ማሳካት የሚቻለውም እቅዱን ለማሳካት ከሚሠሩ ሠራዎች ጎን ለጎን የዋጋ ግሽበቱን መቆጣጠር ከተቻለ ብቻ መሆኑን አመልክተዋል። እንደ ዶክትር ሞላ ገለጻ፤ የ10 ዓመት የልማት እቅዱ ታሳቢ ካደረጋቸው ጉዳዮች አንዱ የሀገሪቱን ዜጎች የነፍስ ወከፍ ገቢ ከፍ ማድረግ ላይ ነው። ነገር ግን ከነፍስ ወከፍ ገቢ ጎን ለጎን የዋጋ ግሽበቱን መቆጣጠር ካልተቻለና ግሽበቱ ከፍ ካለ የህብረተሰቡ የኑሮ ደረጃ እያሽቆለቆለ ይሄዳል እንጂ የታሰበው ዕድገት አይመጣም። ስለዚህ ከ10 ዓመት የልማት እቅዱ ጎን ለጎን የዋጋ ግሽበትን መቆጣጠር ተገቢ ነው። በዚህ ረገድ የ10 ዓመት መሪ እቅድ የሀገሪቱን አጠቃላይ የዕድገት አቅጣጫ የሚጠቁም በመሆኑ፤ ግሽበቱን መቆጣጠር ከተቻለ እውነተኛ የሆነ የሀገር ዕድገትን ማምጣት ይቻላል። ይህ ሲሆን ደግሞ አብዛኛውን የማህበረሰብ ክፍል ተደራሽ ማድረግ የሚችል በመሆኑ ፍትሐዊ የሆነ የሀብት ክፍፍል እንደሚኖርም ነው የገለጹት። ይህ የሀገሪቱን አጠቃላይ የዕድገት አቅጣጫ የሚጠቁም የ10 ዓመት ኢኮኖሚያዊ እቅድ የኦፕሬሽን ዕቅድ አለመሆኑን የጠቆሙት ዶክትር ሞላ እቅዱ ግን ለሀገሪቱ ኢኮኖሚያዊ ዕድገት እጅጉን ጠቃሚ መሆኑንም አስረድተዋል። ከዚህ በፊት የነበረውን ሁለተኛው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ መጠናቀቁን ተከትሎ ያንን ማስቀጠል የሚችል የ10 ዓመት የልማት ዕቅድ መዘጋጀቱም ተገቢነት ያለው ከመሆኑም በላይ ዕቅዱ ጠቋሚ ዕቅድ እንደመሆኑ የሀገሪቱን አጠቃላይ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ያሳያልም ብለዋል።ዕቅድ ሲታቀድ ያለፈውን መነሻ በማድረግ እንደሆነ የጠቆሙት ዶክትር ሞላ፤ ይህም ባለፈው ጊዜ የነበሩ ጠንካራና ደካማ ጎኖችን መለየት የሚያስችል እንደሆነ አስረድተዋል። በመሆኑም መንግሥት ካለፈው ስህተቱ በመማር በሀገሪቱ የ10 ዓመት የልማት ዕቅድ ላይ ባለሙያዎችን ተሳታፊ ማድረጉ የሚበረታታና መለመድ ያለበት ተግባር እንደሆነም ተናግረዋል።በሀገሪቱ አጠቃላይ ዕቅድ ላይ ቢቻል ማህበረሰቡን ማሳተፍ ተገቢ መሆኑን ያነሱት ዶክተር ሞላ፤ ከዚህ በፊት በነበረው አሠራር በጉዳዩ ላይ የሚመለከታቸው አካላት ተሳታፊ ሳይሆኑ የመንግሥት ፍላጎት ብቻ እጅግ በተጋነነ ሁኔታ ይስተናገድ እንደነበር አስታውሰዋል። በመሆኑም ይህ የመንግሥትን ፍላጎት ብቻ መሰረት ያደረገ እቅድ ህብረተሰቡን ያላማከለ በመሆኑ ክንውኑ ዜሮ እንደሚሆን ተናግረዋል። በዚህኛው እቅድ ላይም ከባለሙያዎች ባለፈ፣ ምቹ ሁኔታ ካለ በሀገሪቱ ዕቅድ ላይ ህብረተሰቡን ተሳታፊ በማድረግ የእኔ ብሎ እንዲረዳውና የበኩሉን እንዲወጣ ማስቻል፤ ህብረተሰቡን አሳታፊ በሚያደርግ መልኩ ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና ፖለቲካዊ እንቅስቃሴ ማድረግ እንደሚገባም ተናግረዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 10/2013
https://www.press.et/Ama/?p=37642
331
0ሀገር አቀፍ ዜና
የኢትዮጵያ የውጭ ግንኙነት ፖሊሲ ህዝብና አገርን ያማከለ ሳይሆን በፖለቲከኞች ፍላጎት ላይ የተንጠለጠለ እንደነበር ተገለጸ
ሀገር አቀፍ ዜና
December 19, 2020
35
ዋቅሹም ፍቃዱ አዲስ አበባ፡- ባለፉት ዓመታት የኢትዮጵያ የውጭ ግንኙነት ፖሊሲ ህዝብና አገርን ያማከለ ሳይሆን አገሪቱን ሲመሩ የቆዩት ግለሰቦችና በሚያራምዱት ፖለተካ ላይ ብቻ የተንጠለጠለ እንደነበር ዶክተር ዲማ ነገዎ ተናገሩ። ዶክተር ዲማ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ በሰጡት አስተያየት፤ ባለፉት ዓመታት የኢትዮጵያ የውጭ ግንኙነት ፖሊሲ የአገርና ህዝብን ፍላጎት ያማከለ ባለመሆኑ አገሪቱ በውጭ ግንኙነት ፖሊሲ ስኬታማ አልነበረችም። ምክንያቱም በጊዜዉ የነበሩት የኢትዮጵያ የውጭ ግንኙነት ፖሊሲ የአገርና ህዝብን ሳይሆን የገዥዉ ቡድን ጊዜያዊ የፖለቲካ ጥቅም ሲያስጠብቁ የነበሩ ከመሆናቸውም በላይ፤ ግለሰቦች ከስልጣን ሲወርዱ አብረዉ የሚጠፉ እንጂ አልፈዉ ህዝብና አገርን የሚጠቅሙ አልነበሩም። እንደ ዶክተር ዲማ ገለጻ፤ ኢትዮጵያ ቅኝ ያልተገዛችና የጥቁር ህዝቦች ተምሳሌት ብትሆንም፤ በተለያዩ ምክንያቶች ኢትዮጵያን ሊገፉ የሚፈልጉ እና ኩርፊያ ውስጥ ያሉ አንዳንድ አገሮችም አሉ። ከዚህ አንጻር ከቅርብም ከሩቅም በተለያዩ ምክንያቶች በብዙ ጠላቶች ከበባ ዉስጥ መሆኗን መረዳት ይቻላል። እነዚህ አገራት ደግሞ የፖለቲካ አኩራፊዎችን በማስታጠቅ ኢትዮጵያን ለማተራመስ ሲሠሩ ታይተዋል። ኢትዮጵያ ከድሮም ጀምራ ከፍተኛ የዉጭ ተጽዕኖ ሲደረግባት የነበረች መሆኗን የሚናገሩት ዶክተር ዲማ፤ በዚህ ረገድ በተለይ ከሱዳንና ግብፅ ጋር በጋራ ተጠቃሚነት፣ በዘላቂ ልማትና ሰላም ዙሪያ የተሠራዉ ሥራ ዝቅተኛ መሆኑን ያሚያሳዩ ክስተቶች መኖራቸውን ገልጸዋል። ለዚህ ጉልህ ማሳያ የሚሆነው ደግሞ የህዳሴው ግድብ መሆኑን በመጠቆምም፤ በዚህ ረገድ ግብፅ የዓባይ ጉዳይ በፊትአውራሪነት የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ሥራ እዉን እንዳይሆን ከአህጉር እስከ ዓለም አቀፍ መድረክ ያደረገችዉ ግፊት ቀላል እንዳልነበረ ይገልጻሉ። በሱዳን በኩልም ቢሆን የሚዋዠቅ አቋም እንደነበር እና ሀያላን አገራት ሳይቀር በግድቡ ዙሪያ የሚያሳዩት አቋም ለአንድ ወገን ያደላ መሆኑን የሚናገሩት ዶክተር ዲማ፤ በኢትዮጵያ በኩል ባለፉት ሁለት ዓመታት በዚህ በኩል የተሠራው ሥራ መልካም ቢሆንም አጥጋቢ እንዳልነበር ግን አልሸሸጉም። እንደ ዶክተር ዲማ አባባል፤ አሁን ላይ በትኩረት መሥራት ከተቻለ ኢትዮጵያ ጠንካራ የውጭ ግንኙነት ፖሊሲ ኖሯት ተጽዕኖ ፈጣሪ እንድትሆን የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች አሏት። ለዚህ ደግሞ ገለልተኛ ተቋማትን የመገንባት ሥራ ማጠናከር፤ እንዲሁም ነፃ እና ፍትሐዊ የምርጫ ስርዓት እንዲኖር መሠራት አለበት። የህዳሴ ግድቡ ሲጠናቀቅም ከኢኮኖሚ ፋይዳ ባሻገር በፖለቲካውም ሆነ በውጭ ግንኙነቱ ረገድ የሚያሳድረው አዎንታዊ ተጽዕኖ ከፍተኛ መሆኑን በመገንዘብ በትብብር ዳር ማድረስ ያስፈልጋል። በተመሳሳይ ኢትዮጵያ ያላትን መልካም ገጽታ በማጉላት የሚታወቀው የመከላከያ ኃይሉን ተጠቅሞም ኢትዮጵያን በየትኛዉም የዓለም ክፍል የፀጥታ ማስከበር ላይ ማሳተፍ የሚያስችላት የወታደራዊ አቅም ለማጎልበት በበለጠ መሥራት ያስፈልጋል። ምክንያቱም መከላከያ ሠራዊቱ በዚህ መልኩ ሲሠራ ከሰላም ማስከበሩ ጎን ለጎን ለአገሩ አምባሳደር ሆኖ ይሠራል። በዚህ መልኩ ኢትዮጵያን ከውጭ አገራት ጋር ያላትን ግንኙት ዘላቂ ጥቅሟን በሚያስከብር መልኩ ጠንካራ ሥራ መሠራት እንዳለበት የጠቆሙት ዶክተር ዲማ፤ ከዚህ ጎን ለጎን የዉጭ ግንኙነቱ በአመዛኙ በዉጭ ቋንቋ የሚከወን በመሆኑ ለዉጭ ቋንቋዎች ትኩረት በመስጠት የቋንቋ አቅሙ ከፍ ያለ የሰው ኃይል በብዛትና በጥራት ማፍራት ላይ በትጋት ሊሠራ እንደሚገባም ምክረ ሃሳብ ለግሰዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 10/2013
https://www.press.et/Ama/?p=37628
378
0ሀገር አቀፍ ዜና
ከትልቅ ድል የተገኘ ትልቅ ተስፋ
ስፖርት
November 21, 2019
19
 የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን (ዋልያዎቹ) በ2021 የካሜሩን አፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታ የምድባቸውን ሁለተኛ ፈተና እንደ ተራራ የገዘፈ የእግር ኳስ ስም ካላት ኮትዲቯር ጋር ባህርዳር ላይ ተፋልመው የሚፈልጉትን ውጤት አግኝተዋል። የተጋጣሚያቸው ክብደት ከተመዘገበው ድልና የጨዋታ የበላይነት አኳያ ዳግም የኢትዮጵያን የእግር ኳስ ትንሳዔ ከማነቃቃት ባለፈ በፖለቲካ ትኩሳት እየተሸረሸረ የመጣውን ብሔራዊ ስሜት የመጠገን ሃይል እንዳለው መታዘብ ይቻላል። ይህ ድል ኢትዮጵያ እንዳለፉት ዓመታት ወደ መሰረተችው የአፍሪካ ዋንጫ ለመመለስ ዳግም ሦስት አስርት ዓመታት እንደማትጠብቅ ጠቋሚም ነው። ያምሆኖ ይህ የተነቃቃ መንፈስ እንዳይከስም ሥጋት የለበትም ማለት አይደለም። የዋልያዎቹ አለቃ ኢንስትራክተር አብረሃም መብራቱ ‹‹ጨዋታውን እንደተመለከታችሁት በብዙ ብልጫ ኮትዲቯርን የበለጥነበትና በተሻለ የኳስ ቁጥጥር እንዲሁም የግብ ሙከራ ያሸነፍንበት ነው:: አምላክ ደግሞ ልፋታችንን ቆጥሮ ለድል አብቅቶናል:: ከሁሉም በላይ ቡድኑ ላይ እየታየ ያለው መሻሻል ጥሩ ነው:: በማሸነፍ ውስጥ የተፈጠሩትን ስህተቶችና የሚጎሉ ነገሮችን እያሟላን ጠንካራ ቡድን መገንባቱን እንቀጥላለን:: እግር ኳስ ሂደት ነው: ይሄን ጨዋታ ስላሸነፍን ሂደቱ አለቀ ማለት አይደለም:: ይሄ ድል ትልቅ የሞራል ስንቅ ይሆነናል›› በማለት ከጨዋታው በኋላ ለመገናኛ ብዙሃን አስተያየት ሰጥተዋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንን ጠንካራ ለማድረግ የውጭ ሀብት እንደሚያስፈልግ የጠቆሙት አሰልጣኙ ‹‹ውጭ ያሉ ተጨዋቾቻችን ሀብቶቻችን ናቸውና በነሱ አጠቃቀም ላይ ጠንካራ ሥራ መሥራት ይኖርብናል። ምክንያቱም እነሱ የሚያገኙት ስልጠና: የሚገኙትን ኢንተርናሽናል ተጽዕኖና ፕሮፌሽናሊዝም አስተሳሰብ ለብሔራዊ ቡድናችን ይጠቅመናል:: ከዚህም ሌላው አገርን ወደው ለመምጣት መፈለጋቸው የበለጠ ብሔራዊ ቡድኑን ይገነዘባዋል የሚል ጠንካራ አሳብ አለኝ›› ብለዋል። አሰልጣኙ እንደገለፁት በውጭ አገራት ሊጎች የሚጫወቱ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ተጫዋቾች ለቡድኑ ቀጣይ ጥንካሬ ጉልህ አስተዋጽኦ ማበርከቱ አይቀርም። ከዚያ ባሻገር ግን ይህን የተለኮሰ መነቃቃት እንዳይቀዘቅዝ በተለይም ፌዴሬሽኑ በርካታ ሥራዎች እንደሚጠብቁት እውን ነው። የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታዎች በተራራቀ ጊዜ መካሄዳቸው የተፈጠረውን መነቃቃት ሊያቀዘቅዙ ከሚችሉ ነጥቦች አንዱ ሊሆን እንደሚችል ይገመታል። ዋልያዎቹ ዝሆኖቹን ባሸነፉ ማግስት ሌሎች ጨዋታዎችን ቢያከናውኑ የተፈጠረው መነቃቃት ሳይቀዘቅዝ ሌላ ድል ለማስመዝገብ ላይቸገሩ ይችላሉ። ይሁን እንጂ ቀጣዩን የማጣሪያ ጨዋታ ከበርካታ ወራት በኋላ በዓመቱ መጨረሻና መጀመሪያ አካባቢ ማድረጋቸው አሁን የተፈጠረው መነቃቃት ላይ ውሃ ሊቸልስበት ይችላል። የቡድኑ ስብስብም ለረጅም ጊዜ ተለያይቶ ሲገናኝ አሁን ያለው የአሸናፊነት መንፈስና መነቃቃት በነበረበት ላይገኝ ይችላል። ይህን ሥጋት ግን ፌዴሬሽኑ ከወዲሁ ትኩረት ሰጥቶ ከተዘጋጀበት መቅረፍ እንደሚችል ይታመናል። በዋናነት ይህን ችግር ለመቅረፍ የወዳጅነት ጨዋታዎችን በፊፋና በካፍ መርሐ ግብር መሠረት ማከናወን ነው። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድኖች በየትኛውም ደረጃ የወዳጅነት ጨዋታዎች ማድረግ የዘወትር ችግራቸው መሆኑ ይታወቃል። ይህን ክፍተት ፌዴሬሽኑ እየደፈነ መሄድ ከቻለና ቡድኑ ተደጋጋሚ የአቋም መለኪያና የወዳጅነት ጨዋታ ማግኘት ከቻለ አሁን ያለውን መነቃቃት ማስቀጠል ብቻም ሳይሆን የቡድኑ ውህደት ላይ ትልቅ ለውጥ መፍጠር እንደሚቻል ይታመናል። በአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያው አሁን ላይ ማዳጋስካር በ2 ጨዋታ፣ በ6 ነጥብና በ5 ንፁ ግብ ዋልያዎቹ የሚገኙበትን ምድብ ትመራለች። ኢትዮጵያ በ2 ጨዋታ፣ በ3 ነጥብና በ0 ግብ ሁለተኛ ስትሆን ኮትዲቯር ከዋልያዎቹ ጋር በተመሳሳይ ነጥብና የግብ ልዩነት ትቀመጣለች። ኒጀር በ2 ጨዋታ በ0 ነጥብና በ5 የግብ ዕዳ መጨረሻ ላይ ትገኛለች። ይህ ዋልያዎቹን ከስምንት ዓመታት በኋላ በአፍሪካ ዋንጫ ለመመልከት በእጅ ያሚገኝ ትልቅ ዕድል ነው። የምድቡን ቀሪ ጨዋታዎችና ተጋጣሚዎች ከግምት በማስገባት ዋልያዎቹ አፍሪካ ዋንጫው ላይ ለመድረስ ያላቸውን ተስፋ ካሰላነው ወደ ተወዳጁ መድረክ ለመመለስ ከዚህ የተሻለ ዕድል እንደሌለ መገንዘብ ይቻላል። ቀጣይ የማጣሪያ ጨዋታዎች ከበርካታ ወራት በኋላ መካሄዳቸው አሁን የተፈጠረውን መነቃቃት እንዳያቀዘቅዙት ሥጋት እንደመፍጠሩ ሁሉ ዋልያዎቹ ያላቸው ቀሪ መርሐ ግብር ተስፋ የሚሰጥ ነው። ይህም በሜዳቸው የገነደሱት የምድቡ ሃያል ቡድን ኮትዲቯር ጋር የሚያደርጉት የመልስ ጨዋታ የማጣሪያው መጨረሻ መሆኑ ነው። ዋልያዎቹ ዝሆኖቹን ከመግጠማቸው አስቀድመው ከኒጄር ጋር የደርሶ መልስ ጨዋታ ያደርጋሉ። ከዚያም ማዳካስካርን በሜዳቸው ይገጥማሉ። በዚህ መርሐ ግብር መሰረት አሰልጣኝ አብረሃም ከጊዜ ወደ ጊዜ እየገነቡት የሚሄዱት ቡድን እንዳሁኑ አዳዲስ ለውጦችን መፍጠር ከቻለ በሜዳዋ ሁለት ሽንፈቶችን ከቀመሰችውና የምድቡ ደካማ ቡድን ከያዘችው ኒጄር ጋር በሚኖሩት የደርሶ መልስ ጨዋታዎች ቢያንስ አራት ነጥብ ማግኘት ከባድ አይሆንም። ዋልያዎቹ ኒጄርን በሜዳዋ ገጥመው አንድ ነጥብ ይዘው ከተመለሱ በሜዳቸው ሦስት ነጥብ መሰብሰብ ይሳናቸዋል ተብሎ አይጠበቅም። ቀጣይ ተጋጣሚ ማዳካስካር እንደመሆኗ ከዚህ ጨዋታም ቀላል ባይሆንም ሦስት ነጥብ መሰብሰብ የማይቻል ነገር አይደለም። ምክኒያቱም ማዳጋስካርን የሚገጥሙት እዚሁ በሜዳቸው ነው። ባለፈው ቅዳሜ ማዳጋስካር በሜዳዋ ዋልያዎቹን 1ለ0 ስታሸንፍ ያን ያህል ከባድ ቡድን እንዳልሆነች ታይቷል። ይህን ስሌት ዋልያዎቹ ማሳካት ከቻሉ የመጨረሻውን ማጣሪያ ከሜዳቸው ውጭ በኮትዲቯር ቢሸነፉ እንኳን ወደ ካሜሩን የሚወስዳቸውን ትኬት በቀላሉ ማግኘት ይችላሉ ማለት ነው። በዚህ ስሌት መሰረት ነገሮች ሊጓዙ የማይችሉበት አጋጣሚ እንዳለ ሁሉ እንዳለፈው ጨዋታ ያልተጠበቁ ድሎች ሊመዘገቡ እንደሚችሉም እውን ነው። ይህም ለዋልያዎቹ ቀጣይ የአፍሪካ ዋንጫ ጉዞ ትልቅ የሥነ ልቦና ስንቅ ሆኖ ያገለግላቸዋል። ይህን ተስፋ እንዳይከስም ግን የወዳጅነት ጨዋታዎችን ጉዳይ ከወዲሁ አጥብቆ መያዝ ለነገ የሚባል የቤት ሥራ አይሆንም። አዲስ ዘመን ኅዳር 11/2012 ቦጋለ አበበ
https://www.press.et/Ama/?p=22892
646
2ስፖርት
አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የእገዳ ውሳኔውን አነሳ
ስፖርት
November 20, 2019
14
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በአትሌቶች ተወካዩ ሚስተር ሁሴን_ማኪ ላይ አሳልፎት የነበረውን የእገዳ ውሳኔ አነሳ። በዶሃው የዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮና ላይ በማራቶን ውድድር ተሳትፈው የነበሩ አትሌቶች ከማገገሚያ ሦስት ወራት በፊት ውድድር እንዳያደርጉ ውሳኔ አሳልፎ የነበረ ቢሆንም በሚስተር ሁሴን ማኪ ወይንም ‹‹Elite Sport Management›› ስር ያሉ የተወሰኑ አትሌቶችን በኒውዮርክ ማራቶን ውድድር ላይ መሳተፋቸውን ተከትሎ ፌዴሬሽኑ ከተወካዩ ሁሴን ማኪ ጋር የነበረውን ውል እንዳቋረጠ ይታወቃል:: ፌዴሬሽኑ ከትናንት በስቲያ ከሰዓት በኋላ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ግን ይህን የውል ማቋረጥ እገዳ እንዳነሳ አሳውቋል፡፡ በመሆኑም ውሳኔውን የሰሙት ማናጀሩ የይቅርታ ደብዳቤያቸውን ለፌዴሬሽኑ ከማስገባታቸውም በተጨማሪ የጉዳዩን አሳሳቢነት ከግንዛቤ በማስገባታቸው ከሚኖሩበት አሜሪካ ተነስተው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ቢሮ ድረስ በአካል በመቅረብ ስህተታቸውን አምነው ይቅርታ እንዲደረግላቸው በመጠየቃቸው ፌዴሬሽኑ ጥያቄያቸውን በሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴው በኩል ከመረመረ በኋላ ይቅርታቸውን ተቀብሎ እርምጃው ለሌሎችም አስተማሪ ይሆን ዘንድ ወደ ገንዘብ ቀይሮላቸዋል። የፌዴሬሽኑ ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዚዳንት ኮማንደር አትሌት ደራርቱ ቱሉ በመግለጫው ወቅት ለጋዜጠኞች እንዳስረዱት ሚስተር ሁሴን ማኪ ከ120 በላይ ስመጥር አትሌቶችን ይዘው ለ13 ዓመታት ከፌዴሬሽኑ ጋር እየሠሩ ይገኛሉ፡፡ በአራቱም የአገሪቱ ዋና ዋና ቦታዎች የታዳጊዎች አትሌቲክስ ፕሮጀክት ከፍተው እየሠሩ ከመሆናቸው ባሻገር፣ በአዲስ አበባ ቢሮ ከፍተው እየሠሩ ይገኛሉ፡፡ በዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮናና በኦሊምፒክ በርካታ ውጤታማ አትሌቶችን ለአገራችን ማፍራታቸውን ከግምት በማስገባት የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴው ይቅርታቸውን ተቀብሎ ቅጣታቸውን ወደ ገንዘብ ሊቀይር ችሏል፡፡ እገዳው በሃያ አምስት ሺ የአሜሪካን ዶላር እንደተቀየረላቸው የተገለጸ ሲሆን ቅጣቱ በቂ ነው ባይባልም ሌሎች እንዲማሩበት ውሳኔው መተላለፉን ኮማንደር ደራርቱ አብራርታለች፡፡ አዲስ ዘመን ኅዳር10/2012 ቦጋለ አበበ
https://www.press.et/Ama/?p=22840
210
2ስፖርት
ኢትዮጵያ በቀጣዮቹ አሥር ዓመታት ሦስት ሳተላይቶችን ታመጥቃለች
ሀገር አቀፍ ዜና
December 20, 2020
41
ሞገስ ተስፋአዲስ አበባ፡- ኢትዮጵያ በቀጣዮቹ አሥር ዓመታት ለተለያየ አገልግሎቶች የሚውሉ ሦስት ሳተላይቶችን እንደምታመጥቅ የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት አስታወቀ። የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ አብዲሳ ይልማ እንደገለፁት፤ በቀጣዮቹ አሥር ዓመታት ውስጥ ለተለያዩ አግልግሎቶች የሚውሉ ሦስት ሳተላይቶችን ለማምጠቅ ታቅዷል። በአሥር ዓመቱ ከሚመጥቁት ሳተላይቶች ውስጥ አንደኛው የኮሚዩንኬሽን እና ብሮድካስት ሲሆን፤ የተቀሩት ሁለቱ የመሬት ምልከታ ሳተላይቶች ናቸው። እንደ ዋና ዳይሬክተሩ ገለፃ፤ የኮሚዩንኬሽን እና ብሮድካስት ሳተላይት የሚባለው በብሮድካስት ሚዲያዎች ለኢንተርኔት፣ ለስክልና ለኮሚዩንኬሽን አገልግሎት የሚውል ነው። በአሁኑ ሰዓት ሀገራችን እነዚህን አገልግሎቶች ከውጭ በመከራየት በሚሊዮን ዶላር የሚገመት ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ታወጣለች። ለአብነትም፣ ከብሮድካስቲንግ በዓመት እስከ አሥር ሚሊዮን ዶላር ወጪ ይደረጋል። ለቴሌ ኮሚዩንኬሽን ደግሞ በርካታ ሚሊዮን ዶላሮች ወጭ ይሆናሉ። ስለዚህ ሳተላይት የመገንባት እቅዱን በተግባር በማረጋገጥ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ወጪን መቀነስ ተገቢ ነው። ከኮሚዩንኬሽን እና ብሮድካስት ሳተላይት በተጓዳኝ ሁለት የመሬት ምልከታ ሳተላይቶች የሚገነቡ ሲሆን፤ በጥቅሉ በዚህ ዘርፍ የሚደረገው ልማት የህዝባችንን ኑሮ በማሻሻል ገቢውን ከማሳደግ አንጸር ከፍተኛ ሚና ይኖረዋል ሲሉ አቶ አብዲሳ ተናግረዋል። አቶ አብዲሳ እንደሚሉት፣ ቴክኖሎጂን ከማሳደግ ጎን ለጎን የሥራ እድል በመፍጠር ከፍተኛ የሆነ የውጭ ምንዛሬን ማስቀረት እና ዘርፉ የራሱ የገቢ ምንጭ ሆኖ የውጭ ምንዛሬ እንዲያስገኝ ለማድረግ ይሰራል። በዘርፉ የሚደረግ ልማት የህዝቡን ኑሮ ለማሻሻል የሥራ እድል ለመፍጠር እና በየዘርፉ የታዩ ችግሮችን በስፔስ ሳይንስ ስኬታማ ስራዎችን በመስራት ሀገርን በሁሉም ዘርፍ ለማሳደግ መስራት ነው። በተለይም ከፍተኛ የሆነ የውጭ ምንዛሬ በማስቀረት የስፔስ ሳይንስ ዘርፉ የውጪ ምንዛሬ የሚያገኝበትን መንገድ አላማ አድርጎ በትኩረት እየተሰራ ይገኛል። ዋና ዳይሬክተሩ እንደገለጹት፤ በ2011 ዓ.ም የወጣው ፖሊሲ በግልፅ እስንዳስቀመጠው ዘርፉ በራሱ ኢንዱስትሪ ሆኖ በመውጣት የሥራ እድል ለመፍጠርና በቀጣይ ተወዳዳሪነቱን ለማሳደግ ዛሬ ላይ የሚሰራው ስራ እና በስፔስ ሳይንስ ውስጥ የሚኖረው ተሳትፎ ወሳኝ ነው። የቴክኖሎጂ አቅምን ከመገንባት አንፃር የሚሰራው ስራም ጥቅም ላይ ሊውሉ የሚችሉ መተግበሪያዎችን ወደስራ በማስገባት የላቀ ውጤት ማስመዝገብ እንደሚቻል አቶ አብዲሳ ተናግረዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 11/2013
https://www.press.et/Ama/?p=37690
271
0ሀገር አቀፍ ዜና
‹‹ለአፍሪካ ዋንጫ ማለፍ ካልቻልን ራሴን አገላለሁ››
ስፖርት
November 13, 2019
22
የኢትዮጵያ ሴት ብሔራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ብርሃኑ ግዛውና የብሔራዊ ቡድኑ አምበል ብርቱካን ገብረክርስቶስ ከትናንት በስቲያ ከሰዓት በኋላ በኢትዮጵያ ሆቴል አጠቃላይ ስለ ብሔራዊ ቡድኑ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል። የሉሲዎቹ አዲስ አሰልጣኝ ብርሃኑ ‹‹እቅዴ ለ2020 የአፍሪካ ዋንጫ ማለፍ ነው፣ ይህን ማሳካት የማልችል ከሆነ በራሴ ፍቃድ ከኃላፊነት እራሴን አገላለሁ››በማለት በጋዜጣዊ መግለጫው ተናግሯል፡፡ አሰልጣኙ ቀደሞ የነበሩ አሰልጣኞች በቡድኑ የሰሩትን መልካም ስራ በማጠናከርና የጎደለው በመሙላት ስህተቱን አርሞ ለአፍሪካ ዋንጫ ማለፍ የሚችል ጠንካራ ብሔራዊ ቡድን የመገንባት ፍላጎት እንዳለው አብራርቷል፡፡ አሰልጣኝ ብርሃኑ ሉሲዎቹን ለመምራት ከፌዴሬሽኑ የተሰጠው የስራ ውል ለሦስት ወራት ብቻ የሚዘልቅ ቢሆንም ፌዴሬሽኑ በ2020 አፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታዎች፣ በምስራቅና መካከለኛው አፍሪካ(ሴካፋ) ውድድር በሚያስመዘግበው ውጤት መሰረት ውሉ የሚታደስ ይሆናል፡፡ ያም ሆኖ በአፍሪካ ዋንጫው ቡድኑን ማሳለፍ ካልቻለ ‹‹በእጄ ፈርሜ እንደገባሁ ፈርሜ ለመውጣት ዝግጁ ነኝ›› ብሏል። ከምስራቅና መካከለኛው የሴቶች የአፍሪካ ዋንጫ ጋር ተያይዞ አሰልጣኙ ቡድኑን ለማዘጋጀት ያለው ጊዜ አጭር መሆኑን በመግለፅ ተጫዋቾቹ ከእረፍት እንደመምጣታቸው ከፍተኛ የአካል ብቃት ችግር እንደተስተዋለባቸው ተናግሯል፡፡ በአሁን ወቅት አሰልጣኙና ረዳቶቹ መስራት የሚችሉት ነገር ተጫዋቾቹ በሜዳ ላይ የተሻለ ቅንጅት እንዲፈጥሩና ያላቸውን አቅም አውጥተው መጠቀም የሚችሉበትን ነገር መፍጠር መሆኑን አብራርቷል፡፡ ‹‹በሴካፋው ይህን ውጤት አመጣለሁ ብዬ መናገር የምንችልበት ነገር የለም፣ ውጤት ብናመጣም ባናመጣም ብዙም የሚያስከፋም የሚያስጨፍርም ነገር የለም፣ እኛ እቅዳችን የአፍሪካ ዋንጫ ለመሳተፍ ነው፣ የሴካፋን ውድድር የብሔራዊ ቡድናችንን እንቅስቃሴ የምናይበትና ችግራችንን እያረምን የምንሄድበት ነው›› ሲልም አክሏል፡፡ አሰልጣኝ ብርሃኑ ግዛው ከፌዴሬሽኑ የሚደረግለት ድጋፍ ጥሩ መሆኑን በመግለፅ ቡድኑ የጎደለበት ነገር እንደሌለና ይህም ከፍተኛ ለውጥ እንደሆነ ተናግሯል፡፡ በተለያዩ መገናኛ ብዙሃን አሰልጣኙ ከፌዴሬሽኑ ጋር እንደማይስማማ ሲነሳ ስለነበረው ሃሳብ አሰልጣኙ ምላሽ ሲሰጥ ‹‹ፌዴሬሽኑ የኔን ሃሳብ በበጎ እንጂ በመጥፎ አልተመለከተውም፣ ለ18 ዓመት በሴቶች እግር ኳስ በውድድር ውስጥ አሳልፌያለሁ ብዙ ውጣ ውረዶችን ፣ አስቸጋሪ ጊዚያቶችን አሳልፌያለሁ የሴቶች እግር ኳስ ለኔ ደሜ ነው ለፍቼበታለሁ የማነሳው ሃሳብ ለውጥ እንዲመጣ እንጂ ለመጥፎ አይደለም›› ሲል ገልጿል። የብሔራዊ ቡድኑ አምበል ብርቱካን ገብረክርስቶስ በበኩሏ ቡድኑ የአንድ ሳምንት ዝግጅት ማድረጉን ገልፃ፣ በሜዳ ላይም ከሜዳ ውጪም ትምህርት መውሰዳቸውን አብራርታለች፡፡ ‹‹ በአሰልጣኞቻችን ጥሩ ስልጠና እየተሰጠን ነው፣ ጥሩ መነሳሳት ላይ እንገኛለን፣ እኔ ከበርካታ አሰልጣኞች ጋር ጥሩም መጥፎም ጊዜ አሳልፌያለሁ፣ አሁን ካለፈው ተምረን በመከባበርና ድክመታችን ላይ በመስራት ተደጋግፈን ወደ አፍሪካ ዋንጫ ለመግባት ነው እቅዳችን›› ብላለች። ሉሲዎቹ ትናንት ጠዋት ከ15 ዓመት በታች ወንድ ቡድኖች ጋር የመጨረሻ የወዳጅነት ጨዋታውን ያደረጉ ሲሆን ዛሬ ወደ ታንዛኒያ ያቀናሉ። በታንዛኒያ አዘጋጅነት የሚካሄደው የሴቶች ሴካፋ ዋንጫ ሕዳር ስድስት የሚጀምር ሲሆን ኢትዮጵያ በውድድሩ ከኬኒያ፣ ዩጋንዳና ጅቡቲ ጋር መደልደሏ ይታወቃል፡፡ የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ በምድብ ‹‹ሀ›› ታንዛኒያ፣ ብሩንዲ፣ ዛንዚባርና ደቡብ ሱዳን ተደልድለዋል፡፡ በምድብ ‹‹ለ›› ኬንያ፣ ዩጋንዳ፣ ኢትዮጵያና ጅቡቲ ይገናኛሉ፡፡ በቻማዚ ስታዲየም በሚደረገው ውድድር ኢትዮጵያ የመጀመሪያውን ጨዋታ ከኬንያ ጋር ታደርጋለች፡፡ አዲስ ዘመን ጥቅም3/2012 ቦጋለ አበበ
https://www.press.et/Ama/?p=22445
387
2ስፖርት
”በወረቀት የሰው በደም የእኛ ናቸው»
ስፖርት
November 10, 2019
29
በረሃማነት በእጅጉ ከሰፈነባቸው የአረብ ሃገራት ነዳጅ እንጂ አትሌት ይፈልቃል ተብሎ አይጠበቅም፡፡ በሪዮ ኦሊምፒክ የታየው ግን ተቃራኒ ነበር፡፡ በአማዞን ጥላ ስር በተካሄደው የቁንጮ አትሌቶች ፍልሚያ ባህሬን የመጀመሪያውን ሜዳሊያ ስታስመዘግብ የተለየ ትኩረት የሰጣት አልነበረም፡፡ ሁለተኛውን ስትደግም ግን ዓለም አይኑን ሊጥልባት ተገደደ። ባህሬን ሰንደቅአላማዋን በዓለም ሕዝብ ፊት ከፍ አድርገው ያውለበለቡላት አትሌቶች የኋላ ታሪክ ሲጠናም አምጣ ወልዳ አየሯን ተንፍሰው ያደጉ ሳይሆኑ ከሚስኪኗ አህጉር አፍሪካ ማህፀን የወጡ ኬንያዊያን መሆናቸው ተገለጠ፡፡ ይህ አይነቱ አጋጣሚ ለባህሬን ብቻም ሳይሆን ለአሜሪካ እና ለቱርክ በጥቅሉ ከ30 በላይ የሚሆኑ ኬንያዊያን በወረቀት ላገኙት ዜግነት እንደሚሮጡ መታወቁ አነጋጋሪ ነበር፡፡ ይህ በአትሌቲክስ ብቻ ሲሆን በሌሎች የኦሊምፒክ ስፖርቶችም የደም ሳይሆን የወረቀት ዜግነት ላገኙባቸው በርካታ አገራት የተለያዩ አትሌቶች አንፀባርቀዋል፡፡ኑሮን ለማሸነፍ በየተኛውም ዘርፍ ጠንክሮ መሮጥ የግድ በሆነባት ዓለም በቀጥተኛው መንገድ መጓዝ አሊያም አቋራጮችን መጠቀም የግድ እየሆነ ይመስላል፡፡ ከእነዚህ አቋራጮች መካከል አንዱ ደግሞ የተሻለና ምቹ ሁኔታ ወዳላቸው ባለፀጋ ሃገራት መጠጋት ነው፡፡ ይህ ሁኔታ በዚህ ወቅት የተለመደ ሲሆን፤ በርካታ አትሌቶች በዚህ መልክ የፈለጉትን አሳክተዋል፡፡ በአትሌቲክስ የተሻለ ብቃት ያላቸው የምስራቅ አፍሪካ ሃገራት ደግሞ አትሌቶቻቸውን ለሌሎችም በማጋራት ቀዳሚዎቹ ናቸው ቢባል ማጋነን አይሆንም፡፡ የኬንያ፣ የናይጅሪያ፣ ሞሮኮ፣ የኢትዮጵያ አትሌቶችም ከትውልድ ሃገራቸው ቀጥሎ አሜሪካ፣ የአውሮፓ እና አረብ ሃገራት ዋነኛ መዳረሻቸው ነው፡፡ ሃገራቱም ያላቸውን የኢኮኖሚ ጡንቻ በመጠቀም አትሌቶችን ከማስኮብለል ወደኋላ አይሉም፡፡ ለአብነት ያህል በሪዮ ኦሊምፒክ ኳታር ካሰለፈቻቸው 39 አትሌቶቻ 23 የሚሆኑት ትውልዳቸዉ በሌሎች ሃገራት ነው፡፡ ሃገሪቷ እአአ በ2000 በአንድ ውድድር ላይ ለማሳተፍ ስምንት ቡልጋሪያዊያንን በአንድ ሚሊዮን ዶላር ማስማማቷን ፋይናንሻል ታይምስ ያስታውሳል፡፡ እንግሊዝም ብትሆን እአአ 2012 ባስተናገደችው ኦሊምፒክ ካሳተፈቻቸው 542 ስፖርተኞች መካከል 60 የሚሆኑት እትብታቸው በሃገሪቷ ያልተቀበረና በወረቀት ዜግነት ያገኙ ነበሩ፡፡ ዓለም አቀፉ የአትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበር እአአ ከ2000-2017 በየሃገራቱ ባደረገው ጥናት መሰረት የኀያሏ ሃገር አሜሪካ ፍላጎት በማሻቀቡ ቀዳሚውን ስፍራ ይይዛል፡፡ ባህሬን፣ ኳታር እና እንግሊዝ ደግሞ ተከታዮቹ ሃገራት ናቸው፡፡ በዶሃው ቻምፒዮና በ1500ና 10ሺ ሜትር በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ሁለት ወርቅ ያጠለቀችው የኑዘርላንድስ አትሌት ሲፈን ሃሰንን ጨምሮ የዓለም ቻምፒዮኗ አበባ አረጋዊ፣ ኤልቫን አቢይ ለገሰና ሌሎችም በርካታ ስመ ጥር አትሌቶች ‹‹በወረቀት የሰው በደም የዕኛው ናቸው››፡፡ ከሰላሳ በላይ የሚሆኑ አትሌቶቿም በወረቀት ላገኙት ዜግነት ከአገራቸው ወጥተው እየሮጡ ይገኛሉ፡፡ ባህሬን፣ ቱርክ፣ ኳታር፣ የተባበሩት አረብ ኤሜሬትስ፣ ሆላንድ፣ እንግሊዝ፣ ፖላንድ፣ ቤልጂየም፣ ስፔን፣ ስዊድን፣ ጀርመን እና አሜሪካ ደግሞ ዜግነት የሰጧቸው ሃገራት ናቸው። ጥናቶች እንደሚያሳዩት ከሆነም በዚህ ወቅት በመቶዎች የሚቆጠሩ አትሌቶች የተለያዩ ሃገራትን መለያ ለብሰው ይሮጣሉ፡፡ አንዳንዶች ለዚህ በምክንያትነት ድህነትንና በፌዴሬሽን በኩል ያለ ብልሹ አሰራርን ምክኒያት አድርገው ያነሳሉ፡፡ ቱርክን በተለያዩ ኦሊምፒኮች የወከለው ትውልደ ኬንያዊው አትሌት አክዳክ አሌክስ ኪፕኪሩይ፤ ‹‹ወላጆችን ጨምሮ የማስተዳድራቸው አራት እህት እና ወንድሞች ነበሩኝ፤ ኑሮን ለማሸነፍ ስሮጥም አንድ አሰልጣኝ ፈቃደኛ መሆኔን ጠየቀኝ›› ሲል ሁኔታውን ፌር ፕላኔት ለተባለ ድረ ገጽ አስታውሷል፡፡ አሁን ቤተሰቦቹ በሚፈልጉት ሁሉ እየረዳቸው ሲሆን፤ የታናናሾቹን የትምህርት ወጪም መሸፈን ችሏል፡፡ በርካቶች በእንዲህ አይነቱ ጉዳይ እንደይስማሙ ይታወቃል፤ ምክንያታቸው ደግሞ ገንዘብ ከሃገር አይበልጥም የሚል ነው፤ ኪፕኪሩይ ግን ከድህነት አላቆታልና በዚህ አይስማማም በድርጊቱም እንደምይጸጸት ነው የሚገልጸው፡፡ ኬንያ ሳለች ማሪያም ጅፕቶ ትባል የነበረችው ሌላኛዋ ባህሬን ዜጋዋ ያደረገቻት አትሌትም የኪፕኪሩይን አስተሳሰብ ትጋራለች፡፡ ስሟን አሊያ ባስማ በሚል የቀየረችው አትሌቷ ኬንያ ውስጥ በርካታ ወጣት አትሌቶች ቢኖሩም ለዓለም አቀፍ ውድድሮች የመታጨት እድላቸው አነስተኛ መሆኑን ትጠቁማለች፡፡ ለልሎች ሃገራች የመሮጥ እድል ቢመቻችላቸው ግን በኦሊምፒክ እና ዓለም ቻምፒዮናዎች ላይ ለመሳተፍ እንደማይቸገሩ ልምዷን ታካፍላለች፡፡ በርካታ አፍሪካዊያን አትሌቶች የመነሻ ምክንያት ኑሮን ማሸነፍ ይሁን እንጂ የተቀሩት ደግሞ በልጅነታቸው በማደጎ ወደ ሌላ ሃገራት በመሄድ እንዲሁም ከቤተሰቦቻቸው ጋር በመሰደድ ነው ሁለተኛ ሃገርን የሚወክሉት፡፡ በተለይ የሰሜን አፍሪካ ሃገራት ወደ አውሮፓ በሚያደርጉት ስደት ምክንያት እግር ኳስ እና አትሌቲክስን ጨምሮ በሌሎች ስፖርቶች ተሳታፊ የሆኑ አትሌቶች ከትውልድ ሃገራቸው ይልቅ ላደጉበት ሃገር ለመወዳደር ይገደዳሉ፡፡ የተቀሩት ደግሞ በሃገራቸው ምቹ ሁኔታ ባለማግኘትና በመገፋታቸው በቀላሉ ዜግነት ወደ ሚሰጧቸው ሃገራት ያማትራሉ። በስፖርት አመራሮችና አሰልጣኞች ያለው የቀናነት ጉድለት፣ ለብሄራዊ ቡድን በሚደረገው ምርጫ የሚቀመጠው የማያስማማ መስፈርት፣ ለስፖሩቱ እና ለአትሌቶቹ የሚሰጠው ትኩረት አነስተኛ መሆን፣ አትሌቶቹ የሚከፈላቸው ደመወዝ አነስተኛ መሆን፣ በልምምድ እና በማገገሚያ ወቅት በቂ ቁሳቁስ እንዳስፈላጊነቱ ባለማግኘት እና ሌሎች ምክንያቶችም አትሌቶች ከትውልድ ቀያቸው ይልቅ የሌሎች ሃገራትን ክብር እንዲገነቡ ሆነዋል፡፡ ወደ ባለጸጎቹ የመካከለኛው ምስራቅ አረብ ሃገራት መጓዝ ለአትሌቶቹ የተሻለ ነገር እንደሚያስገኝ ይታሰብ እንጂ፤ በተቃራኒው የስፖርት ባርነትን እንደሚያተርፍም ዘ ጋርዲያን የተሰኘው ድረገጽ በአንድ ዘገባው አስነብቧል፡፡ ኢትዮጵያዊቷ ሊሊ አብዱላይቫ ያሰቡት ካልተሳካላቸው አትሌቶች መካከል ትተቀሳለች። አትሌቷ ለቱርክ ለመሮጥ የተስማማችው በ300ዶላር ወርሃዊ ክፍያ እንዲሁም ስታሸንፍ ተጨማሪ 1ሺ ዶላር ሊከፈላት እንዲሁም ቤትና መኪና ሊሰጣት ነበር። ይሁን እንጂ ቃል የተገባላት አልተፈጸመላትም፣ የሽልማት ገንዘቧንም ማግኘት አልቻለችም፡፡ ሌላኛው ኬንያዊ ልዮናርድ ሙቹሩም የዚህ ታሪክ ገፈት ቀማሽ ነው፡፡ አትሌቱ ጉዳት ባጋጠመው ወቅትም የባህሬን አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ደመወዙን ሊሰጠው ፈቃደኛ እንዳልነበረም ገልጣል፡፡በርካቶች ጉዳዩን ከህገወጥ ሰዎች ዝውውር ለይተውም አያዩትም፤ ዓለም አቀፍ ውድድሮችንም አደጋ ላይ ይጥላል በሚል ይገልጹጻል፡፡ ዓለም አቀፉ የአትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማህበርም በተመሳሳይ በዚህ ጉዳይ አይስማማም፤ ማህበሩ ፕሬዚዳንት ሰባስቲያን ኮ በአትሌቲክስ እና እግር ኳስ ስፖርቶች ዜግነት እንዳይቀይሩ የሚከለክል ጠንካራ ህግ ባለመኖሩ ይህ ዓይነቱ ዝውውር እያደገ መምጣቱ አሳሳቢ መሆኑን በአንድ ወቅት ተናግረዋል፡፡ አብዛኛዎቹ አትሌቶችም ኦሊምፒክን መሰል ትልልቅ ውድድሮች ሲቃረቡ ወደ ዜግነት መለወጥ እንቅስቃሴ ይገባሉ፡፡ በመሆኑም በቅርቡ አዲስ ደንብ የሚወጣ መሆኑን ጠቁመው ነበር እስካሁን ምንም የተባለ ነገር ባይኖርም፡፡ በእርግጥ ከሁለት ወይም ከሦስት ዓመታት በፊት የወጣ አንድ ህግ አለ፡፡ ይህ ህግ አንድ አትሌት ዜግነቱን ቀይሮ ከመሮጡ በፊት ለትውልድ አገሩ ለሁለት ዓመታት መሮጥ እንዳለበት የሚደነግግ ነው፡፡ ይህ ግን አትሌቶችን ከስደት የሚታደግ አልሆነም፡፡ አዲስ ዘመን ጥቅም30/2012 ብርሃን ፈይሳ
https://www.press.et/Ama/?p=22258
767
2ስፖርት
የዓመቱ ምርጥ አትሌቶች ሽልማት የመጨረሻ እጩዎች
ስፖርት
November 12, 2019
24
የዓለም አትሌቲክስ በየዓመቱ የሚያዘጋጀው የዓመቱ ምርጥ አትሌቶች ሽልማት በሞናኮ ሊካሄድ ዛሬ አስራ አንድ ቀን ብቻ ይቀረዋል። ለሁለት ተከታታይ ዓመታት በሁለቱም ፆታ አንድም ኢትዮጵያዊ አትሌት ከመጀመሪያዎቹ አስር እጩዎች ውስጥ እንኳን መካተት እንዳልቻለ ይታወሳል። በተመሳሳይ ወጣትና ተስፈኛ የሆኑ ከሃያ ዓመት በታች ያሉ አትሌቶች በሚወዳደሩበት ሽልማት ዘርፍ ሁለት ወንዶችና አንድ ሴት ኢትዮጵያዊት አትሌት ከመጨረሻዎቹ አምስት እጩዎች ውስጥ መካተታቸው ይታወቃል። የዓለም አትሌቲክስ ትናንት ከሰዓት በኋላ በዘንድሮው ዓመት በወንዶች የመጨረሻዎቹን አምስት እጩዎች ዝርዝር ይፋ አድርጓል። የመጨረሻዎቹ ሴት እጩዎችም ዛሬ የሚለዩ ይሆናል። ጆሹአ ቺፕቴጌ ባለፈው የዶሃ የዓለም አትሌቲክስ ቻምፒዮና የአስር ሺ ሜትር ቻምፒዮን የሆነው ዩጋንዳዊው ጆሹአ ቺፕቴጌ የመጨረሻዎቹን አምስት እጩዎች መቀላቀል የቻለ ሲሆን አትሌቱ በ2019 የውድድር ዓመት ያሳየው አስደናቂ ብቃት ሽልማቱን የማሸነፍ እድል እንዳለውም አመላካች ነው። ጆሹአ አርሁስ በተካሄደው የዓለም አገር አቋራጭ ቻምፒዮና አሸናፊ መሆኑን ተከትሎ በውድድር ዓመቱ ትኩረት የተሰጠው አትሌት ሆኗል። ባልተጠበቀ መልኩም ጠንካራዎቹን ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በዳይመንድ ሊግ በማሸነፍ በአምስት ሺ ሜትር አጠቃላይ አሸናፊ ለመሆን በቅቷል። በዶሃው የዓለም ቻምፒዮናም 26፡48፡36 የሆነ መሪ ሰዓት አስመዝግቦ በውድድር ዓመቱ ለታላቅ ስኬት እጩ መሆን ችሏል። ሳም ኬንድሪክስ አሜሪካዊው ምርኩዝ ዘላይ ሳም ኬንድሪክስ በውድድር ዓመቱ ካደረጋቸው አስራ ሰባት ከቤት ውጪ ውድድሮች አስራ ሁለቱን በድል አጠናቋል። የውድድር ዓመቱ የዳይመንድ ሊግ አጠቃላይ አሸናፊ ከመሆኑ ባሻገር የዓለም ምርኩዝ ዝላይ ቻምፒዮን ነው። በአሜሪካ የምርኩዝ ዝላይ ቻምፒዮና 6 ነጥብ 06 ሜትር በመዝለል ያስመዘገበው ስኬት ለዓለም ምርጥ አትሌቶች ሽልማት የመጨረሻ እጩነት አብቅቶታል። ኢሉድ ኪፕቾጌ ያለፈው ዓመት የሽልማቱ አሸናፊ የሆነው ኬንያዊው የማራቶን ፈርጥ ኢሉድ ኪፕቾጌ በውድድር ዓመቱ ሁለት ፉክክሮች ላይ ብቻ ቢታይም ያስመዘገበው ታሪክ ለመጨረሻ እጩነት አብቅቶታል። ኪፕቾጌ በውድድር ዓመቱ የለንደን ማራቶንን ክብረወሰን በማሻሻል በ2፡02፡37 ሰዓት ማሸነፉ የሚታወስ ነው። ከዚህ በላይ ግን ከወር በፊት በቬና ማራቶን የሰው ልጅ የብቃት ጥግ ወሰን እንደሌለው ያሳየበት ውድድር አይዘነጋም። ኪፕቾጌ ከትጥቅ አምራች ኩባንያው ናይኪ ጋር በመሆን በተለያዩ ቴክኖሎጂዎች ታግዞም ቢሆን ማራቶንን ከሁለት ሰዓት በታች ማጠናቀቅ እንደሚቻል አስመስክሯል። 1፡59፡40 በሆነ ሰዓት ማራቶንን በማጠናቀቅ በታሪክ የመጀመሪያው አትሌት ለመሆን ቢበቃም የተመዘገበው ሰዓት በዓለም ክብረወሰንነት እንዳልተያዘ ይታወሳል። ኖህ ላይልስ አሜሪካዊው የአጭር ርቀት አትሌት ኖህ ላይልስ የሁለት መቶና አራት በአራት መቶ ሜትር ዱላ ቅብብል ቻምፒዮን ነው። በሉዛን ዳይመንድ ሊግ ሁለት መቶ ሜትርን 19፡50 በሆነ ሰከንድ በማጠናቀቅ በታሪክ አራተኛው ፈጣን ሰዓት ባለቤት መሆኑም አይዘነጋም። የዳይመንድ ሊግ የመቶና ሁለት መቶ ሜትር አጠቃላይ አሸናፊ መሆኑም በመጨረሻዎቹ እጩዎች ዝርዝር ውስጥ እንዲካተት አድርጎታል። ካርልስተን ዋርሆልም ኖርዌያዊው የአጭር ርቀት ኮከብ አትሌት ካርልስተን ዋርሆልም በአራት መቶ ሜትር መሰናክል የዓለም ቻምፒዮን ነው። ይህ አትሌት በውድድር ዓመቱ በተለያዩ ርቀቶች በቤት ውስጥም ሆነ ከቤት ውጪ ውድድሮች ሽንፈት አልገጠመውም። ዳይመንድ ሊግን ጨምሮ የአውሮፓ ቻምፒዮን ሲሆን ያስመዘገበው 46፡92 በታሪክ ሁለተኛው ፈጣን ሰዓት ሆኗል። ይህም ስኬቱ ምናልባትም ከዩጋንዳዊው አትሌት ጋር ሽልማቱን ለማሸነፍ ጠንካራ ተፎካካሪ ያደርገዋል ተብሎ ይጠበቃል። አዲስ ዘመን ኅዳር 2 /2012   ቦጋለ አበበ
https://www.press.et/Ama/?p=22339
405
2ስፖርት
“በትግራይ ተጨማሪ የጅምላ መቃብር መገኘቱ አይቀርም” ሲሉ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ አስታወቁ
ሀገር አቀፍ ዜና
December 17, 2020
61
በጋዜጣው ሪፖርተሮች አዲስ አበባ፡- ባለፉት አስርት ዓመታት የህወሓት ጁንታ የተለያ የፖለቲካ አመለካከትና አቋም ያላቸውን የትግራይ ተወላጆች በጭካኔ ሲገድል ከመቆየቱ ጋር በተያያዘ በክልሉ ተጨማሪ በርካታ የጅምላ መቃብሮች መገኘታቸው አይቀርም ሲሉ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ አቶ ነጋሲ በየነ ተናገሩ።የኢትዮ-አሜሪካ ሲቪክ ካውንስል እና የኢትዮጵያዊያን ሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች ባዘጋጁት የዌብናር ውይይት ላይ የተሳተፉት አቶ ነጋሲ በየነ እንደተናገሩት፤ ጁንታው ስርዓቱን ያዋቀረው ከአልባኒያ ኮሚኒዚም በመኮረጅ ወዳጅና ጠላት በሚል ሲሆን፤ ከእርሱ ውጪ ያለን አስተሳሰብና አቋም የሚያራምዱ ግለሰቦችንና ቡድኖችን ባለመቀበል ሲያስርና ሲገድል ኖሯል። በመሆኑም በትግራይ ክልል በቅርቡ ተጨማሪ የጅምላ መቃብር መገኘቱ አይቀርም። የህወሓት ጁንታ በ17 ዓመቱ የሽምቅ ውጊያ ወቅት በድርድር ሰበብ የጠራቸውን የትግራይ ነፃነት ግንባር (TLF) አመራሮችን ራት ጋብዞ ሌሊት በተኙበት እንደገደላቸው ያስታወሱት አቶ ነጋሲ፤ በተመሳሳይ አሁንም በመከላከያ ሠራዊት የሰሜን ዕዝ አባላት ላይ የፈጸማቸው ክህደትና ግፍ የቡድኑ ተፈጥሯዊ ባህሪ ስለሆነ ዓለም ሊረዳውና ሊያወግዘው ይገባል ነው ያሉት። በኢትዮጵያ ከተደረገው የፖለቲካ ለውጥ በኋላ ኩርፊያ ውስጥ የገባው ጁንታው ለልማትና ለመልካም አስተዳደር ዞር ብሎ አይቶት የማያውቀው የትግራይ ህዝብ ጉያ ውስጥ ገብቶ ተደብቆ ቆይቷል ያሉት የሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ፤ ለፖለቲካ ስልጣን ጥሙ ሲል የትግራይ ህዝብ በጠላቶች እንደተከበበ እንዲሰማው ለማድረግ ሲደክም ቆይቷል፤ በሰዎች መካከልም ፍርሐትን ለመጫን ሞክሯል፤ ራሱንም ብቸኛ የትግራይ ህዝብ ተከላካይ አድርጎ አሳይቷል ነው ያሉት። ከለውጡ በኋላም ወደ ትግራይ የተመለሰው የህወሓት ጁንታ ለትግራይ ወጣቶች ምንም ዓይነት የተሻለ የሥራ ዕድል አልፈጠረም፤ ይልቁንም ወጣቱን በልዩ ኃይል ስም እያሰባሰበ ሲያሰለጥን ምሽግ ሲያስገነባ መቆየቱን ነው ያብራሩት። በዚሁ ዌብናር ላይ የተሳተፉትና የውይይቱ አስተባባሪ አንድነት እምሩ እንደተናገሩት፤ ጁንታው ከውድቀት ለመዳን በተለያዩ ማህበራዊ ገጾች ላይ ከፍተኛ የሐሰተኛ መረጃዎችን በማሰራጨት ሕብረተሰቡን ለማወናበድና ኢትዮጵያን ለመበተን ከፍተኛ ጥረት ማድረጉን ማረጋገጥ እንደቻሉ አስረድተዋል፡፡ጁንታው በትግራይ ክልል በተለያዩ አካባቢዎች በሁሉም የሰሜን እዝ ላይ እና ሁሉም ወታደራዊ ካምፖች ላይ የተቀናጀ ጥቃት መፈጸሙን ያነሱት አቶ አንድነት፤ ጁንታው ጥቃቱን የፈጸመበትን እቅድ ባለማሳካቱ፤ ሐሰተኛና የፈጠራ መረጃዎች በመንዛት በሌላ የጥፋት መንገድ ተጠምዶ እንደነበር ማረጋገጥ እንደተቻለ ገልጸዋል፡፡ ይሁን እንጂ ይህ እቅዱም ከውድቀት ሊታደገው አልቻለም ሲሉ ነው ያስረዱት።ጁንታው በሕግ ማስከበሩ ሂደት በተወሰደበት ዕርምጃ ላይነሳ ተንኮታኩቷል፤ በመሆኑም እየሸሸ ሲሄድ በብዙ መቶዎች የሚቆጠሩ ንጹሐን ዜጎችን ሕይወት ከማጥፋቱም ባለፈ በሺዎች የሚቆጠሩትን ደግሞ ለማገት ሞክሮ በሁሉም ረገድ ለሽንፈት መዳረጉን አቶ አንድነት ለተሳታፊዎቹ አብራርተዋል። የአሜሪካ ሴኔት አባላት፣ የምክር ቤቱ የውጭ ግንኙነት ሠራተኞች፣ የአፍሪካ ፕሮግራም አስተባባሪዎች፣ የሃሳብ አመንጪዎች (ቲንክ ታንክ) እና ዓለም አቀፍ የመገናኛ ብዙሃን በተደረገው ገለጻ መሳተፋቸው ተገልጿል፡፡አዲስ ዘመን ታህሳስ 8 2013/ዓ.ም
https://www.press.et/Ama/?p=37523
342
0ሀገር አቀፍ ዜና
“የትግራይ ወጣት ራሱን ከነባራዊ ሁኔታ ጋር በማስማማት ወደ ኃላፊነት ሊመጣ፣ ሃገሩንና ህዝቡንም ሊያገለግል ይገባል” – አቶ ነብዩ ስሑልሚካኤል የትግራይ ብልጽግና ጽህፈት ቤት ኃላፊ
ሀገር አቀፍ ዜና
December 18, 2020
29
እፀገነት አክሊሉአዲስ አበባ፦ የትግራይ ወጣት የጁንታው ቡድን ማንንም የማይወክል መሆኑን በመረዳት ራሱን ከነባራዊ ሁኔታ ጋር በማስማማት ወደኃላፊነት በመምጣት ሃገሩንና ህዝቡን እንዲያገለግል የትግራይ ብልጽግና ፓርቲ ጥሪ አቀረበ። የጽህፈት ቤት ኃላፊው አቶ ነብዩ ስሑልሚካኤል ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንዳሉት፤ የህወሓት ጁንታ ቡድን ውድቀት የትግራይ ህዝብም ሆነ ወጣት ውድቀት ሳይሆን የራሱ የጁንታው ብቻ ነው። በመሆኑም ወጣቱ በተፈጠረው ነገር መቆዘም ሳይሆን በተፈጠረው ትልቅ ዕድል በመጠቀም ወደ ኃላፊነት መምጣት፣ አገሩንና ህዝቡንም ለማገልገል መዘጋጀት ይጠበቅበታል። እንደ አቶ ነብዩ ገለጻ፤ አንዳንድ ወጣቶች የህወሓት ጁንታ ቡድን ውድቀት እነርሱንም አብሮ የሚጥላቸው ስለሚመስላቸው በቁዘማ ውስጥ ገብተው ይታያሉ። ሊያውቁት የሚገባው እውነት ግን የህወሓት ጁንታ ከወጣቱ፣ ከህዝቡ፣ ከመንግሥትና ከተለያዩ አካላት ብዙ ምክርና ዕድል ተሰጥቶት አልጠቀምም ብሎ በራሱ እብደትና ቅሌት ለዚህ ማብቃቱ ሲሆን፤ የጁንታው ውድቀትም ከትግራይ ወጣቶችም ሆነ ከማንኛውም ትግራዋይ ጋር የማይገናኝ መሆኑ ነው። ይልቁንም የሆነ ቡድን በራሱ መንገድ ብቻ እያየ ሲሄድ የጠፋ አድርጎ መውሰዱ ይገባል። ለጁንታው ቡድን ምክርና ሃሳብ ካዋጡ አካላት አንዱ  የትግራይ ወጣት መሆኑን የገለጹት አቶ ነብዩ፤ “ምከረው ምከረው እምቢ ካለ መከራ ይምከረው” እንደሚባለው ሁሉ አሁን ላይ ጁንታው በራሱ መንገድ ተጉዞ የጠፋ እንደመሆኑ ወጣቱ ለዚህ ቡድን ምንም ማድረግ አይችልም። ስለዚህ ወጣቱ የጁንታው ቡድን ማንንም የማይወክል መሆኑን በመረዳት ራሱን ከነባራዊ ሁኔታ ጋር አስማምቶ መቀጠል እንደሚጠበቅበት ጠቁመዋል። በሌላ በኩልም ወጣቱ ለውጡ የራሱ እንደሆነ በመረዳት ይህንን ደማቅ ምዕራፍ እውን አድርጎ ለራሱም ተጠቃሚ የሚሆንበት፣ ከመቼውም ጊዜ በተሻለ ሁኔታ አገሩንም ህዝቡንም የሚያገለግልበትን ዕድል በአግባቡ ሊጠቀም፤ ከአንዳንድ አላስፈላጊ ቁዘማዎችና መፋዘዞችም ሊላቀቅ እንደሚገባው አቶ ነብዩ አሳስበዋል። የጁንታው መወገድ ለትግራይ ህዝብ የነፃነት ቀኑ ተብሎ ሊጠቀስ የሚገባው ነው ያሉት አቶ ነብዩ፤ የታገለላቸው የዴሞክራሲ፣ የልማት እና የእኩል ተጠቃሚነት ዓላማዎች ተሳክተው የሚያይበት ትልቅ ምዕራፍ መሆኑንም አብራርተዋል። በተለይም አዲሱ ትውልድ “እኛ ብቻ እናውቅልሃለን” ከሚለው አካል የተላቀቀበት እንደመሆኑ፤ አሁን ባገኘው ዕድል ተጠቅሞ የራሱን አስተዋጽዖ እንዲያበረክትና ወደ ኃላፊነት መጥቶ ህዝቡን እንዲያገለግል የሚያስችለው ጊዜ በመሆኑ አጋጣሚውን እንደ ወርቃማ ጊዜ ሊመለከተው እንደሚገባም መክረዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ9/2013 ዓ.ም
https://www.press.et/Ama/?p=37582
281
0ሀገር አቀፍ ዜና
ኮሚሽኑ በበጀት ዓመቱ አራት ቢሊዮን ዶላር ኢንቨስትመንት ለመሳብ አቅዶ እየሠራ መሆኑን ገለጸ
ሀገር አቀፍ ዜና
December 18, 2020
11
ሞገስ ጸጋዬአዲስ አበባ፡- በበጀት ዓመቱ አራት ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር ከኢንቨስተሮች ለመሳብ አቅዶ እየሠራ መሆኑን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን አስታወቀ። ኪሚሽኑ፣ ከአሜሪካና ከካናዳ ባለሀብቶች እንዲሁም ከሚሽነሪዎች ጋር በሃያት ሪጅንሲ ሆቴል ትናንት ተወያይቷል። ውይይቱ ላይ የኮሚሽኑ ምክትል ኮሚሽነር አቶ ዳንኤል ተሬሳ እንደገለጹት፤ በተያዘው በጀት ዓመት በርካታ ባለሀብቶችን በመሳብ ከአራት ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር እንዲለማ እየተሠራ ነው። እንደ አቶ ዳንኤል ገለጻ፤ የኢንቨስትመንት ህግ መሻሻሉ በኢኮኖሚው ላይ ብዙ ለውጦች እያመጣ ነው። በርካታ የአሜሪካና የካናዳ ባለሀበቶች በአዲስ መልክ በአዳዲስ ዘርፎች ላይ መዋዕለ ነዋያቸውን ለማፍሰስ ጥናት እያደረጉ ነው። ከዚህ በፊት በተለያዩ ዘርፎች ተሰማርተው ሲያለሙ የነበሩ ባለሀብቶችም ተጨማሪ ዘርፎች ላይ ለመሰማራት አማራጮችን እየተመለከቱ ነው። በተለይ በተሻሻለው የኢንቨስትመንት ህግ በርካታ ዘርፎቸን ለውጭ ባለሀብቶች ክፍት አድርጓል። ይህ ደግሞ ኢትዮጵያን በኢንቨስተሮች ተመራጭ ያደርጋታል። ዝግ የነበሩ የኢንቨርስትመንት ዘርፎችን ክፍት መደረጉ ለማልማት ፍላጎት እያላቸው ያልቻሉ ባለሀብቶችን ወደ ዘርፉ እንዲቀላቀሉ ያደርጋል ያሉት አቶ ዳንኤል፤ ፍላጎት ያላቸው የአሜሪካና የካናዳ ባለሀብቶች ለመሰማራት በዝግጅት ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል። የኢንቨስትመንት ህጉ መሻሻሉ በምሥራቅ አፍሪካ ያለንን የኢንቭስትመንት ተመራጭነት ለማስቀጠል ይጠቅማል ያሉት አቶ ዳንኤል፤ ምቹ ሁኔታዎችን በማሳወቅ ባለሀብቶች ወደ ሀገር ውስጥ ገብተው እንዲያለሙ እየሠራ መሆኑን ገልጸዋል።እንደ አቶ ዳንኤል ገለጻ፤ የኮቪድን ተጽዕኖ ከፍተኛ በመሆኑ መንግሥት ካምፓኒዎች እንዳይጎዱ በማለት የተለያዩ ድጎማዎችን ሲያደርግ ነበር። እንዲሁም ወደ ውጭ ሲልኩ ለነበሩ ድርጅቶች በሀገር ውስጥ እንዲሸጡና የገንዘብ ዕርዳታ እንዲያገኙ በማድግ ሊዘጉ የሚችሉ ድርጅቶች ሳይዘጉና ሠራተኞቻቸውን ሳይበትኑ መቆየት ችለዋል። በቀጣይም ከባለድርሻ አካላት ጋር በጋራ በመሥራት እቅዶችን ለማሳካትና አልሚዎችን በምቹ ሁኔታ እንዲሠሩ ለማድረግ በርካታ ቅድመ ሁኔታዎች እተሠሩ ነው። የበርዳን አማካሪ ድርጅት ማናጀር የሆኑት ትዕግስት ገረመው በበኩላቸው እንዳሉት፤ የተሻሻለው የኢንቨስትመንት ህግ ለባለሀብቶች ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል። ሆኖም በኢንቨስትሮች ላይ ሁሌም ይነሳ የነበረውን የግብር ችግር ለመፍታት ኮሚሽኑ ከሚመለከታቸው አከላት ጋር ቢሠራ በጣም ጥሩ ነው። እንዲሁም ከመሬት ይዞታና ከባንኮች ጋር መሠራት ቢቻል ኢትዮጵያን በቀላሉ ተመራጭ ማደረግ ይቻላል። አልሚዎች በምን ዘርፍ መሳተፍ እንዳለባቸው የሚያሳዩ ማስታወቂያዎች ቢኖሩ በርካታ ኢንቨስተሮችን መሳብ ይቻላል ያሉት ማናጀሯ፤ ከምንም በላይ ደግሞ አዳዲስ ዘርፎች ለውጭ ባለሀብቶች መፈቀዳቸው ጥሩና አበረታች ነው። ኢንቨስተሮች በመጡ ቁጥር ለሀገር ዕድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ስለሚኖራቸው መንግሥት ከአማካሪ ድርጅቶች ጋር በጋራ ሊሠራ ይገባል ብለዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 9/2013 ዓ.ም
https://www.press.et/Ama/?p=37590
308
0ሀገር አቀፍ ዜና
የአንጋፋው የኪነ ጥበብ ባለሙያ የአርቲስት ተስፋዬ ገሰሰ ስርዓተ ቀብር ተፈጸመ
ሀገር አቀፍ ዜና
December 18, 2020
7
በጋዜጣው ሪፖርተርአዲስ አበባ፡- ከትናንት በስቲያ ከዚህ ዓለም በሞት የተለየው አንጋፋው የኪነ ጥበብ ባለሙያ ተባባሪ ፕሮፌሰር አርቲስት ተስፋዬ ገሰሰ ቀብር ሥነስርዓት ዛሬ ተፈጽሟል።ተባባሪ ፕሮፌሰር ተስፋዬ ገሰሰ የህይወት ታሪክ እንደሚያስረዳው፤ በቀድሞው ሐረርጌ ክፍለ ሀገር ጎሮጉቱ በሚባል አካባቢ ከአባቱ ከአቶ ገሰሰ ቆለጭ እና ከእናቱ ወይዘሮ በለጥሻቸው ያየህይራድ መስከረም 17 ቀን 1929 ዓ.ም ነው የተወለደው። በስምንት ዓመት ዕድሜው በአዲስ አበባ ተፈሪ መኮንን ትምህርት ቤት የገባ ሲሆን፤ በትምህርት ቤቱ ስካውት ተሳትፎ ነበረው።በልጅነቱም ደራሲ ከበደ ሚካኤል በደረሱት “የትንቢት ቀጠሮ” ቴአትር ላይ የሚያለቅስ ሕፃን ልጅ ገጸ ባህሪይ ተላብሶ ተጫውቷል። በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር (በወቅቱ መጠሪያው የቀዳማዊ ኃይለስላሴ ቴአትር ቤት) ከመጽሐፍ ቅዱስ የኢዮብን ታሪክ በመውሰድ በተዘጋጀ ተውኔት በመሪ ተዋናይነት የተጫወተ ሲሆን፤ በተውኔቱ ዳይሬክተር ጋባዥነት ንጉሰ ነገስት ቀዳማዊ አፄ ኃይለስላሴ አርቲስት ተስፋዬ ሲተውን ተመልክተዋል። አርቲስቱ በመሪ ተዋናይነት የተጫወተበት ይህ ተውኔት ወደ ቴአትር ሙያ እንዲገባ በር የከፈተለት እንደሆነም ይነገራል።አርቲስት ተስፋዬ ገሰሰ በልጅ እንዳልካቸው መኮንን ወደ ፈረንሳይ ተልከው የሕግ ትምህርት ይማሩ ተብለው ከተመለመሉ ሰዎች እንዱ የነበረ ሲሆን የእሱም ፍላጎት የሕግ ትምህርት መማር ነበር። ይሁንና ቀዳማዊ አፄ ኃይለስላሴ ኢትዮጵያ በቴአትርና ስነ ጥበብ ብዙ ባለሙያዎች ስለሌሏት ውጭ አገር በዚሁ ዘርፍ ብትማር ይሻላል ብለው በወቅቱ ለአርቲስቱ ያቀረቡለትን ጥያቄ ተቀብሏል። በ1951 ዓ.ም በጄነራል ሂውማነቲስ የመጀመሪያ ዲግሪውን ያገኘ ሲሆን፤ በ1953 ዓ.ም በኖርዝዌስተርን ዩኒቨርሲቲ የቴአትር ትምህርት ቤትም ተመርቋል። አርቲስቱ በ1954 ዓ.ም ወደ አገሩ በመመለስ በቴአትር ሙያው መሥራቱን ቀጥሏል። ወደ አገሩ ከተመለሰ በኋላ በሙያው ቴአትር መሥራትና ማዘጋጀት የጀመረ ሲሆን፤ “የሺ፣ እቃው፣ ፀረ ኮሎኒያሊስት፣ ተሃድሶ፣ “Cherchez Les Femmes” እና “ፍርዱ ለእናንተ” የተሰኙ ቴአትሮችን አዘጋጅቷል። በተለይም በ1968 ዓ.ም የደርግ ስርዓትን በሚተቸው “እቃው” ቴአትር ምክንያት በዋና ዳይሬክተርነት ተሹሞ ይሠራበት ከነበረው የአገር ፍቅር ቴአትር ቤት ታግዶ ለእስር ተዳርጓል። በፀረ-ኮሎኒያሊስትና ተሃድሶ ቴአትሮቹ በፖለቲካ ጉዳይ ያነሳቸው ሃሳቦች አወዛጋቢ እንደነበሩም ይገለጻል። አርቲስቱ የብሔራዊ ቴአትር ቤት ዳይሬክተር ሆኖም አገልግሏል።አርቲስት ተስፋዬ ገሰሰ በ2010 ዓ.ም “የመጨረሽታ መጀመርታ” የተሰኘ ታሪክና ሕይወት ቀመስ ሽሙጥ ልቦለድ መጽሐፍ ለንባብ አብቅቷል። በዘመኑ የኡመር ካያምን ሩቢያቶች የግጥም መድበልን ጨምሮ በርካታ ድርሰቶች፣ ትርጉሞችና የተውኔት ጽሑፎችንም ለንባብ አብቅቷል። የቴአትር ምሁር፣ ተዋናይ፣ ደራሲ፣ መምህር፣ ተመራማሪና ተርጓሚ ተባባሪ ፕሮፌሰር ተስፋዬ ገሰሰ በሙያው ለኢትዮጵያ ዘመናዊ ቴአትር መሰረት የጣለና ባለሙያዎችንም ያፈራ እንደሆነ ይነገርለታል።አገር ወዳድ፣ ቅን፣ ታታሪና በሰዎች ስኬት የሚደሰት እንደሆነም የቅርብ ወዳጆቹና የሙያ አጋሮቹ ይመሰክራሉ። ተባባሪ ፕሮፌሰር አርቲስት ተስፋዬ ገሰሰ የሦስት ወንዶችና የሁለት ሴቶች ልጆች አባት የነበረ ሲሆን 10 የልጅ ልጆችንም አይቷል። የአርቲስቱ ስርዓተ ቀብር ዛሬ ወዳጅ ዘመዶቹ የሙያ አድናቂዎቹና የሥራ ባልደረቦቹ በተገኙበት በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ተፈጽሟል፤ ሲል የዘገበው ኢዜአ ነው።አዲስ ዘመን ታህሳስ 9/2013 ዓ.ም
https://www.press.et/Ama/?p=37592
366
0ሀገር አቀፍ ዜና
ተመራቂዎች የኢትዮጵያን ሰላምና ልማት በማረጋገጥ የህዝብ አገልጋይ መሆን እንዳለባቸው ተገለጸ
ሀገር አቀፍ ዜና
December 18, 2020
7
በጋዜጣው ሪፖርተርአዲስ አበባ፡- ተመራቂ ተማሪዎች የኢትዮጵያን ሰላምና ልማት በማረጋገጥ የህዝብ አገልጋይ መሆን እንደሚገባቸው የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር  ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዶክተር ሙሉ ነጋ ገለጹ። የመቐለ የኒቨርሲቲ ለ28ኛ ጊዜ ያሰለጠናቸውን ከ3 ሺህ በላይ ተማሪዎቹን ትናንት ማስመረቁን ኢዜአ ዘግቧል። በምርቃ መርሐ ግብሩ ላይ የተገኙት የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዶክተር ሙሉ ነጋ፤ በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ምክንያት ተቋርጦ የቆየውን ትምህርት ቀጥለውና የተለያዩ ችግሮችን አልፈው ለምረቃ በመብቃታችሁ ‘እንኳን ደስ ያላችሁ’ መልዕክት ለተመራቂዎች ያሲተላለፉ ሲሆን፤ ተመራቂዎች ለአገራቸው ሰላምና ልማት በመሥራት ህዝባቸውን ማገልገል እንዳለባቸውም አሳስበዋል። ተመራቂዎቹ በዩኒቨርሲቲ ቆይታቸው ያካበቱትን እውቀት ሕዝባቸውን ለማገልገል እንዲጠቀሙበት ያስገነዘቡት ዶክተር ሙሉ፤ በክልሉ በተካሄደው የሕግ ማስከበር ዘመቻ ወቅት የመቀሌ ከተማ ነዋሪዎች ተማሪዎች ጉዳት እንዳይደርስባቸው ላደረጉት አስተዋጽኦም ምስጋና አቅርበዋል። በቀጣይም የመቀሌ ከተማ ነዋሪዎች ከጊዜያዊ አስተዳደሩ ጎን በመሆን የከተማዋን ልማት እንዲያረጋግጡም ጠይቀዋል።ተመራቂ ተማሪዎች በበኩላቸው፤ በውጣ ውረዶች ውስጥ አልፈው ለዚህ በመብቃታቸው መደሰታቸውን የገለጹ ሲሆን፤ ከዚህ በኋላም ያገኙትን እውቀት ተጠቅመው በቅንነትና በተታሪነት አገራቸውን ለማገልገል መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል። በዕለቱ ከተመረቁ ተማሪዎች አንድ የሦስተኛ ዲግሪ ተመራቂ ሲሆን፤ የተቀሩት የመጀመሪያ ዲግሪ ተመራቂዎች ናቸው። ከተመራቂዎቹ መካከልም 38 በመቶዎቹ ሴቶች ናቸው። ዩኒቨርሲቲውም በሁሉም የትምህርት መርሐ ግብሮች ከ30 ሺህ በላይ ተማሪዎችን በማስተማር ላይ እንደሚገኝም ታውቋል።በምርቃ መርሓ ግብሩ ላይ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዶክተር ሙሉ ነጋን ጨምሮ የዩኒቨርሲቲው የቦርድ አባላት መታደማቸውን ነው ኢዜአ የዘገበው።አዲስ ዘመን ታህሳስ9/2013 ዓ.ም
https://www.press.et/Ama/?p=37587
197
0ሀገር አቀፍ ዜና
በትግራይ ከጁንታው ጋር ተሰልፎ የነበረው የኦነግ ሸኔ አባል
ሀገር አቀፍ ዜና
December 18, 2020
12
ኢያሱ መለሰፈይሳ ተካ ይባላል። የ22 ዓመት ወጣት ነው። ትውልድና ዕድገቱ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን ግንደ በረት ከተማ ነው። ትምህርቱን ከስምንተኛ ክፍል አቋርጦ ሀገራችንን ነፃ እናውጣ እያለ በሚሰብከው ታደሰ ጆንሴ በሚባል ሰው አማካኝነት ለኦነግ ሸኔ ሠራዊትነት ተመልምሎ ጊንጪ አካባቢ ጭልሞ በምትባል ቦታ ከጥር 2012 ዓ.ም ጀምሮ ከ26 ባልደረቦቹ ጋር ስልጠና እንደወሰደ ይናገራል። ከስልጠና በኋላም ሁሉም ወደ መጡበት አካባቢ እንዲመለሱና ስልክ ሲደወልላቸው የሚፈለጉበት ቦታ ድረስ እንዲመጡ ትዕዛዝ ተሰጣቸው። እንደተነገራቸውም፣ የሰሜን ዕዝ ሠራዊት ላይ ጥቃት ከመፈጸሙ አስቀድሞ ማንነቱን በማያውቀው ሰው አማካኝነት ስልክ ተደወለለት። በተባለው ቦታ ተሰባሰቡና ጉዟቸውን ወደ ትግራይ አደረጉ፤ በእግርም በተሽካርካሪም ከተጓዙ በኋላ ጨርጨር አካባቢ ከትግራይ ታጣቂዎች ጋር ተቀላቀሉ። ፈይሳ ተካ ስም ተቀየረለትና የትግል ስሙ ብሩክ ተካ ሆነ። ምግብና ትጥቅ ተሟላላቸው፤ በወር ከስድስት ሺህ እስከ ሰባት ሺህ ብር እንደሚከፈላቸውም ተነገሯቸው ስምሪት ተሰጠው፡፡ከጥቂት ቀናት በኋላ በሰሜን እዝ ሠራዊት ላይ ጥቃት እንዲፈጽሙ ትዕዛዝ ተሰጥቷቸው እንደነበርና እርሱ ግን አለመሳተፉን ነው ፈይሳ የሚናገረው። በአመራሮች በኩልም የትግሉ ዓላማ ሀገሪቱን ነፃ ለማውጣት እንደሆነ ይነግሯቸው እንደነበርም ይገልጻል። ቃል የተገባላቸውን የወር ደመወዝ ሲጠይቁ ግን መንግሥት የኢኮኖሚ ምንጮችን ስለዘጋብን መክፈል አንችልም የሚል መልስ እንደተሰጣቸው ፈይሳ ይናገራል። በዚህ መሃል መከላከያ ሠራዊት ህግን የማስከበር ዕርምጃ ሲጀምር ፈይሳ እጁን በሰላማዊ መንገድ ሰጥቷል። በማያውቀው ነገር በሰዎች ተታሎ በጥፋት ዓላማ ውስጥ  መሳተፉ እንደጸጸተው ነው ፈይሳ የሚናገረው። እንደ ፈይሳ ሁሉ፣ በርካታ የኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች ከጁንታው ጋር አብረው ተሠልፈው የነበረ ሲሆን፤ ብዙዎቹም እጃቸውን ለሀገር መከላከያ ሠራዊት እየሰጡ ይገኛሉ። ሌተናል ጄኔራል ባጫ ደበሌ፣ በሃገራቸው የቀረበላቸውን ጥሪ ተከትለው ወደሃር መከላከያ ሠራዊት ከተመለሱ በኋላ አካባቢውን ጎብኝተው በተመለሱ ማግስት በሰጡት መግለጫ፤ አንዳንድ የኦነግ ሸኔ አባላት ከህወሓት ጁንታ ቡድን ጋር መሰለፋቸውን መግለጻቸው የሚታወስ ነው።አዲስ ዘመን ታህሳስ9/2013 ዓ.ም
https://www.press.et/Ama/?p=37581
245
0ሀገር አቀፍ ዜና
የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ሙስናን ለመዋጋት እየሠራ መሆኑን አስታወቀ
ሀገር አቀፍ ዜና
December 18, 2020
5
ፋንታነሽ ክንዴአዲስ አበባ፡- ሙስናን ለመዋጋት በርካታ ተግባራትን እያከናወነ መሆኑን የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አስታወቀ። 17ኛውን ዓለም አቀፍ የፀረ-ሙስና ቀንንም ትናንት አክብሯል። የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት ምክትል ፕሬዚዳንት ወ/ሮ አሸነፈች አበበ በተለይ ለአዲስ ዘመን እንደገለጹት፤ ፍርድ ቤት ከፈጣሪ በታች ህግን ለማስከበር ትልቅ ስልጣን ያለው፤ ህገመንግሥቱን የማክበርና የማስከበር ኃላፊነት የተጣለበት አካል ነው። ሙስናን ለመዋጋትና ለመከላከል ጉልህ ሚና የሚጫወት እንደመሆኑም ሙስናን ለመዋጋት የሚያስችሉ በርካታ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል። እንደ ወ/ሮ አሸነፈች ገለጻ፤ ሌሎች ህግን እንዲያከብሩ ለማድረግ በመጀመሪያ በተቋሙ ውስጥ ያሉ ሠራተኞች ህግን እንዲያከብሩ ማድረግ ይጠበቃል። ዳኞች የሚሰጧቸው ትክክለኛ ውሳኔዎች ሌሎች ሙስናንና ህገወጥነትን እንዲከላከሉና ህግን እንዲያከብሩ ያግዛሉ። ሌሎች የተቋሙ ሠራተኞች የሚሰጡት የተቀላጠፈ አገልግሎትም ህገ ወጥነትን ለመከላከልና ሙስናን ለመዋጋት የማይተካ ሚና አለው። የዳኝነት አካሉ በሰው ሕይወት፣ ሀብትና ንብረት እንዲሁም ነፃነት ላይ ውሳኔ የሚሰጥና ትልቅ ኃላፊነት ያለበት አካል መሆኑን የጠቀሱት ወ/ሮ አሸነፈች፤ ሙስናን እና በአጠቃላይም ህገ ወጥነትን ከመከላከል አንጻር ትልቅ ኃላፊነት እንዳለበት ተናግረዋል። ይህንን ለማረጋገጥ ዳኞች ስነ-ምግባርን በጠበቀ መልኩ ለተገልጋዮች በእኩልነትና በገለልተኝነት አገልግሎት እንዲሰጡ ለማድረግ ተከታታይ ስልጠና ሲሰጥ መቆየቱን ገልጸዋል።የዳኞች መተዳደሪያ የስነ ምግባር ደንብ በመሻሻል ለመጽደቅ በሂደት ላይ መሆኑን ያስታወቁት ወ/ሮ አሸነፈች፤ የፌዴራል መጀመሪያ ፍ/ቤት የሥራ ክፍል ኃላፊዎችና የሠራተኞች የስነ-ምግባር መተዳደሪያ ደንብም መዘጋጀቱን ገልጸዋል። ከእነዚህ ተግባራት በተጓዳኝ የመንግሥት የሥራ ሰዓትን ካለማክበር አስከ ትልልቅ ጉቦ መቀበል ድረስ ችግር የተስተዋለባቸው ሠራተኞች ላይ ከሥራ እስከማሰናበት የሚደርስ ዕርምጃ እንዲወሰድባቸው መደረጉንም አብራርተዋል። እንደ ወ/ሮ አሸነፈች ማብራሪያ፤ ዕርምጃ ከተወሰደባቸው ባሻገር ከየምድብ ችሎቱ ሬጅስትራሮችና አስተባባሪዎች ጋር በመተባበር የስነ-ምግባር ችግር ያለባቸው 60 ሠራተኞች መለየታቸውንና ምን ዕርምጃ ይወሰድባቸው በሚለው ላይ በማኔጅመንት ደረጃ ውይይት እየተደረገበት ነው። የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት በዓለም ለ17ኛ ጊዜ በኢትዮጵያ ለ16ኛ ጊዜ የሚከበረውን የዓለም የፀረ-ሙስና ቀን ‹‹የትውልድ የሥነ-ምግባር ግንባታን በጠንካራ ዲሲፕሊን በመምራት ሌብነትና ብልሹ አሠራርን በመታገል የህዝብ አመኔታን ያተረፈ የዳኝነት ስርዓት እንገነባለን›› በሚል መሪ ቃል አክብሯል። በበዓሉ ላይ የመነሻ ጽሑፍ ቀርቦ ውይይት የተደረገበት ሲሆን፣ የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት የሥራ ክፍል ኃላፊዎችና የሠራተኞች የስነ-ምግባር መተዳደሪያ ደንብ መጽሐፍ ምርቃትም ተከናውኗል። አዲስ ዘመን ታህሳስ 9/2013 ዓ.ም
https://www.press.et/Ama/?p=37589
291
0ሀገር አቀፍ ዜና
በኮቪድ 19 ምክንያት በከፊል አቋርጦ የነበረው የህዝብ ቤተ መጽሐፍት ወደሥራ ሊመለስ መሆኑ ተገለጸ
ሀገር አቀፍ ዜና
December 18, 2020
9
ሞገስ ተስፋአዲስ አበባ፡- በኮቪድ-19 ምክንያት ለሥምንት ወራት አገልግሎቱን በከፊል አቋርጦ የነበረው የህዝብ ቤተ መፅሐፍት አገልግሎት ክፍት ሊደረግ መሆኑን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቤተ መዛግብትና ቤተ መፅሐፍት ኤጀንሲ አስታወቀ፡፡በኤጀንሲው የህዝብ ቤተ መፅሐፍት ዳይሬከተር አቶ ያሬድ ተፈራ እንደገለጹት፤ የህዝብ ቤተ መፅሐፍቱ ኮቪድ-19 በኢትዮጵያ ከተከሰተበት መጋቢት ወር ጀምሮ ለሥምንት ወራት በስፋት አገልግሎት መስጠት ሳይችል ቆይቷል፡፡ አሁን ላይ ግን የኮሮና ቫይረስን በመከላከል የህዝብ ቤተ መፅሐፍቱ አገልግሎት መስጠት የሚችልበት መመሪያ በመዘጋጀቱ አገልግሎቱ ክፍት ይደረጋል፡፡እንደ አቶ ያሬድ ገለጻ፤ የህዝብ ቤተ መፅሐፍቱ ከዚህ በፊት ተመራማሪዎችና ቤተ መዛግብትን ለመጠቀም ለሚመጡ ተገልጋዮች አገልግሎት ሲሰጥ የቆየ ቢሆንም ለብዙሃኑ ህዝብ ዝግ ሆኖ መቆየቱ ለተጠቃሚዎች ጫና ፈጥሮ ቆይቷል፡፡ ችግሩን ለመቅረፍ አሁን ላይ ከሕፃናት ውጪ ለሌሎች ተጠቃሚዎች ከፍት የሚሆንበት ሁኔታ እየተመቻቸ ሲሆን፤ መመሪያውም ተገልጋዮችም ሆኑ ሠራተኞች ከጤና ጥበቃ ሚኒስቴርና ከኢትዮጵያ ህብረተሰብ ሳይንስ ኢንስቲትዩት የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል የሚወጡ መመሪያዎችን በሚገባ ለመተግበር የሚያስችል ነው፡፡በኤጀንሲው የስልጠና እና የምርምር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ መኮነን ከፍያለው በበኩላቸው፤ የህዝብ ቤተ መፃሕፍቱ ለህዝብ ክፍት በሚሆንበት ወቅት መመሪያው በሚፈቅደው መሰረት በቤተ መፃሕፍቱ ውስጥ ያሉትን ወንበሮች በመቀነስ በአንድ ጠረንጴዛ ውስን ሰዎች እንዲገለገሉ የሚያስችል አሠራር ተዘርግቷል ብለዋል፡፡ በዚህም ከዚህ በፊት ከ1ሺ 200 በላይ ሰዎችን ያስተናግድ የነበረው ቤተ መፃሕፍት አሁን ላይ ኮሮናን ለመከላከል በሚያስችል መንገድ 326 ወንበሮች መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል፡፡ይህ የሆነውም የቤተ መፃሕፍቱ ወንበሮች ደንበኞች ከተገለገሉባቸው በኋል ከሦስት እስከ ሰባት ቀን ኳራንቲን በማድረግ አስፈላጊውን የኬሚካል ርጭት ተደርጎላቸው አገልግሎት ለመስጠት ታስቦ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡የብሔራዊ ቤተ መዛግብትና ቤተ መፃሕፍት ኤጀንሲ ከዚህ በፊት ከ2፡30 እስከ 9 ሰዓት ይሰጥ የነበረው አገልግሎት በአሁኑ ሰዓት የ24 ሰዓት አገልግሎት ለመስጠጠት ዝግጅቱን ማጠናቀቁም ተገልጿል፡፡አዲስ ዘመን ታህሳስ 9/2013 ዓ፣ም
https://www.press.et/Ama/?p=37597
231
0ሀገር አቀፍ ዜና
ቡሬ አግሮ ኢንዱስትሪ ፓርክ ተጨማሪ ባለሀብቶችን ለመቀበል ዝግጅቱን ማጠናቀቁ ተገለጸ
ሀገር አቀፍ ዜና
December 18, 2020
25
ዳግማዊት ግርማአዲስ አበባ፡- የቡሬ አግሮ ኢንዱስትሪ ፓርክ ተጨማሪ ባለሀብቶችን ለመቀበል ዝግጅቱን መጨረሱን የአማራ ክልል ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ የአዲስ አበባ ማስተባበርያ ፅህፈት ቤት አስታወቀ፡፡የማስተባበርያ ፅህፈት ቤቱ ኃላፊ አቶ ያየህ አዲስ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደተናገሩት፤ የቡሬ አግሮ ኢንዱስትሪ ፓርክ የነበሩበትን ችግሮች ቀርፎ ለባለሀብቱ ምቹ ሁኔታዎችን እየፈጠረ፤ በፓርኩ ኢንቨስት ለሚያደርጉ ባለሀብቶችም የተሻሉ ማበረታቻዎችን እያደረገ ይገኛል፡፡ለኢንዱስትሪ ፓርኩ የሚውሉ ግብአቶች በአካባቢው የሚገኙ መሆናቸው ለባለሀብቶች ትልቅ ዕድል መሆኑን የተናገሩት አቶ ያየህ፤ በስፍራው ያለው ሰላማዊ እንቅስቃሴም ለባለሀብቶች ምቹ እንቅስቃሴን የሚፈጥር መሆኑንም ተናግረዋል፡፡ኢንዱስትሪ ፓርኩ የመሰረተ – ልማት ችግር እንደነበረበት ያወሱት ኃላፊው፤ በአሁኑ ጊዜ ግን የአስፓልት መንገድ መሠራቱን፣ የመብራት አገልግሎት መኖሩን፣ ለሥራ የሚሆን መሬትም ተዘጋጅቶ ማለቁን እንዲሁም ለትምህርት ቤቶች እና ለሌሎች አገልግሎት የሚውሉ ስፍራዎች ተሠርተው መጠናቀቃቸውን ገልጸዋል፡፡ፓርኩ 600 ሄክታር ላይ ያረፈ ሲሆን፤ ከዚህም 200 ሄክታር ያህሉ መልማት መቻሉን፤ ከለማው መሬት ውስጥም 100 ሄክታሩ ለባለሀብት መሰጠቱን፤ እንዲሁም መሬት ከያዙት ባለሀብቶችም ሥራ የጀመሩ እንዳሉና በአግሮ ኢንዱስትሪ ስር የሚገኘው አንድ የዘይት ፋብሪካም በቅርቡ ሥራ እንደሚጀምር ነው አቶ ያየህ የገለጹት፡ የቡሬ አግሮ ኢንዱስትሪ ፓርክ የሚፈልጋቸው ባለሀብቶች በምግብና ምግብ ነክ ቁሳቁሶች ላይ መሥራት የሚፈልጉና ለሀገር ውስጥ እና ለውጭ ገበያ ማቅረብ የሚችሉ መሆኑን በመግለጽ፤ የክልሉ ኢንቨስትመንት ቢሮም የበለጠ ምቹ ሁኔታዎችን ለመፍጠር እየሠራ እንደሆነ እና በክልሉ ውስጥ የመሳተፍ ፍላጎት ያላቸው ባለሀብቶች ከወዲሁ ዝግጅት እዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል፡፡አግሮ ኢንዱስትሪዉ ከፍተኛ የሆነ የአግሮ ፕሮሰሲንግ ኢንዱስትሪ ማዕከል ለመሆን እንዲሁም በክልሉ የሚገኘውን የእርሻ ምርት ውጤት በተሻለ ጥራት እሴት ጨምሮ ለመላክ የሚያስችል ሲሆን፤ ኢንዱስትሪዉ ሙሉ ሥራውን ሲጀምር ከ10ሺህ በላይ ለሚሆኑ ሰዎች የሥራ ዕድል እንደሚፈጥርም አቶ ያየህ አዲስ ተናግረዋል፡፡አዲስ ዘመን ታህሳስ 9/2013 ዓ፣ም
https://www.press.et/Ama/?p=37598
230
0ሀገር አቀፍ ዜና
“ከጁንታው ጎን ተሰልፈው ሀገርን ለማተራመስ የሚሠሩ የውጭ ኃይሎችን በኢትዮጵያዊነት መንፈስ መታገል ይገባል” – ኦባንግ ሜቶ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች
ሀገር አቀፍ ዜና
December 18, 2020
533
 ጽጌረዳ ጫንያለውአዲስ አበባ፡- ከህወሓት ጁንታ ጎን ተሰልፈው ሀገርን ለማተራመስ የሚጥሩ የምዕራባውያን ጁንታዎችን ሴራ ለማጋለጥ በኢትዮጵያዊነት ስሜት በመቆም መታገል እንደሚገባ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ አቶ ኦባንግ ሜቶ ገለጹ። አቶ ኦባንግ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደተናገሩት፤ የእኔ ብሔር ብቻ ማለት ባለፉት 27 ዓመታት የወረስነውና ያሳደግነው አስተሳሰብ ነው። ይህ ደግሞ ለነጭ ጁንታዎች ተጠቃሚነት ሰፊ ዕድል የሰጠና ኢትዮጵያን የችግር ቋት ውስጥ የከተተ ነው። በመሆኑም ከብሔር አስተሳሰብ ወጥቶ በኢትዮጵያዊነት መንፈስ ቆሞ የነጭ ጁንታዎችን እጅ ማሳጠር ያስፈልጋል። በአሁኑ ወቅት አንዳንድ የውጭ ኃይሎች ከሚያስተላልፉት መልዕክት ጀምሮ ኢትዮጵያን ለማቆርቆዝ ያለመ ሥራ እየሠሩ ይገኛሉ ያሉት አቶ ኦባንግ፤ የነዚህን ኃይሎች ድርጊት ለማስቆም በቅንጅት መሥራት ካልተቻለ አደጋው የከፋ ይሆናል ብለዋል። የህወሓት ጁንታ በ27 ዓመታት የአገዛዝ ዘመኑ ከነጭ ጁንታዎች ጋር በመሆን አገሪቱን ለብዙ ችግር ዳርጓታል የሚሉት አቶ ኦባንግ፤ አሁንም ይህንን አሠራር ነጭ ጁንታዎች ይፈልጉታልና የተለያዩ ሪፖርቶችን ለህዝብ በማቅረብ ከህወሓት ጁንታ ጎን መሆናቸውን እያሳዩ መሁኑን ተናግረዋል። አቶ ኦባንግ እንደገለጹት፤ እነዚህ ነጭ ጁንታዎች በአገሪቱ የተፈጠረውን ግጭት መነሻ አድርገው የተሳሳተ ፕሮፓጋንዳ እየነዙ ይገኛሉ። በተለይም የሰብዓዊ መብት ተቆርቋሪ መስለው የሌለና የሀሰት መረጃ ከመስጠት አንጻር ከባድ ችግር እየፈጠሩ ነው። ነገር ግን የኢትዮጵያ ህዝብ እውነታውን ስለሚያውቀው ይህንኑ እውነታ ለዓለም ማህበረሰብ ማሳወቅ አለበት። ለዚህ ደግሞ በተናጠል ሳይሆን በአንድ ሃሳብ በአንድነት መቆም ይገባል። በኢትዮጵያ ያለው ጉዳይ የኢትዮጵያ እንጂ የነጭ ጁንታዎች ጉዳይ እንዳልሆነ ግልጽ ነው ያሉት አቶ ኦባንግ፤ እነዚህ ነጭ ጁንታዎች ግን እኛ እናውቅላችኋለን በሚል እየተንቀሳቀሱ ነው ብለዋል። እንደ አቶ ኦባንግ ገለጻ፤ አሁን አገር እያተራመሰ ያለው ጁንታ ቀደም ሲል ከእነዚህ ነጭ ጁንታዎች ጋር ወዳጅ ነበር። በዚህ የተነሳ ጁንታው ሀገር በሚመራበት ወቅት ይፈጽም የነበረውን አሰቃቂ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ለማሳየት አይፈልጉም። አሁን ግን የህግ ማስከበር ሥራ ሲሠራ ጩኸታቸው ሁሉ ሰብዓዊ መብት ሆኗል። አሁን አሁን ደግሞ የግጭቱ ፈጣሪ መንግሥት እንደሆነ ለማሳየት ይሞክራሉ። ‹‹የሰብዓዊ መብት ጉዳይ የመንግሥታት ድጋፍ ጉዳይ ሳይሆን ሰው የመሆን ጉዳይ ነው›› የሚሉት አቶ ኦባንግ፤ ነጭ ጁንታዎች ግን ይህንን ትተው 27 ዓመት ሙሉ የነበረውን አሰቃቂ ሰብዓዊ ጥሰት ሳያነሱ ዛሬ እየሆነ ያለውን ይኮንናሉ ብለዋል። ይሄን የሚሉ ኃይሎች ደግሞ ማመዛዘን እንኳን የተሳናቸው ለመሆናቸው ብዙ ምክንያት መጥቀስ ይቻላል የሚሉት አቶ ኦባንግ፤ የግጭቱ ጀማሪ የህወሓት ጁንታ ስለመሆኑ ጁንታው እራሱ ምስክርነቱን ሰጥቶ እያለ እነርሱ ግን መንግሥት ዋሽቷል ብለው ሲያቀነቅኑ መታየታቸውን ገልጸዋል። ከዚህ አንጻር የእነርሱ ድጋፍ ለጁንታው እንጂ ለሰብዓዊነት አለመሆኑን ነው አቶ ኦባንግ የገለጹት። እንደ አቶ ኦባንግ ገለጻ፤ የአውሮፓ ህብረት በተለያየ መንገድ ጫና እያሳረፈ እንደሆነ እሙን ነው። ስለሆነም ይህንን መመከት የሚቻለው ጉዳዩ የአገር መሆኑን አምኖ በተቀናጀ መልኩ የአመለካከት ለውጥ ማምጣት ላይ በመሥራት ነው። ለዚህ ደግሞ መንግሥትን ጨምሮ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች ጥልቅ ጥናት አድርገው ሁኔታውን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ማስረዳት አለባቸው። የማይወክለንንም ሃሳብ አይወክለንም ማለት ያስፈልጋል። የህወሓት ጁንታ ከሠራው ሥራ አንዱ የመደራጀትና ሃሳብን በነፃነት የመግለጽ መብት ተግባራዊ እንዳይሆን ማድረግ ነው ያሉት አቶ ኦባንግ፤ አሁን ግን ይህ ኃይል በመደምሰሱ ትክክለኛ ፍትህና የሰብዓዊ መብት መከበርን ማረጋገጥ ይገባናል ብለዋል። ለዚህ ደግሞ ሁሉም በሚያውቀው ቋንቋ እውነታውን ማስረዳትና የኢትዮጵያን ገጽታ መገንባት ላይ መረባረብ ከመቼውም ጊዜ ይልቅ ያስፈልጋል፤ የነጭ ጁንታዎችን የረዘመ እጅ መቁረጥም ይገባል ብለዋል። በቅርቡ ወደ አሜሪካ አቅንተው የአገሪቱን ነባራዊ ሁኔታ ሲያስረዱ እንደቆዩና አሁንም በዚህ ሥራ ላይ እንደሆኑ የሚያነሱት የሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ አቶ ኦባንግ፤ በተለያዩ የአሜሪካ ግዛቶች ከኮንግረንስ እስከ ቲንክ ታንክ ግሩፕ ድረስ ወርደው መሥራታቸውን ተናግረዋል። አሁንም ቢሆን ነጭ ጁንታዎች ጠንካራ የኢትዮጵያ መንግሥት እንዲኖር ስለማይፈልጉ እነርሱ እጃቸው እንዲያጥር በመሥራት ላይ እንደሚቀጥሉም ገልጸዋል። ሆኖም በግለሰቦች ደረጃ የሚደረገው እንቅስቃሴ በቂ ስላልሆነ ሁሉም በቻለው ሁሉ መሥራት እንዳለበት አስገንዝበዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 9/2013 ዓ፣ም
https://www.press.et/Ama/?p=37602
501
0ሀገር አቀፍ ዜና
የዳይመንድ ሊግ ለውጥ ተቃውሞ እያስተናገደ ነው
ስፖርት
November 14, 2019
6
የዓለም አትሌቲክስ በየጊዜው የሚያስተላልፋቸው አዳዲስ ውሳኔዎች የስፖርቱን ቤተሰብ በማስከፋት የቀጠለ ይመስላል።የዓለም አትሌቲክስ በራሱ በሚያጸድቃቸው ሃሳቦች በበርካቶች ዘንድ ተቃውሞም ይቀርብበታል፤ ይሁን እንጂ ተግባራዊ ከማድረግ ወደ ኋላ አላለም።ከእነዚህ መካከል አንዱ በዳይመንድ ሊግ ይካሄዱ የነበሩ ውድድሮች መቀነሳቸው ነው።ሃሳቡ በተነሳበት ወቅት ኢትዮጵያን ጨምሮ አፍሪካዊያን የስፖርት ማህበራት ተቃውሟቸውን ቢያሰሙም ተቀባይነት ሊያገኙ ሳይችሉ ወደ ውሳኔ ተቀይሯል።ከአዲሱ የፈረንጆች አመት ጀምሮም ከዳይመንድ ሊግ እንዲቀነሱ የተደረጉ ውድድሮችን ተከትሎ በርካቶች ተቃውሟቸውን በማሰማት ላይ ይገኛሉ።በተለይ የአሜሪካ አትሌቶች ለጥያቄ ያመቻቸው ዘንድ ማህበር በመመስረት ላይ የሚገኙ መሆኑን ሜይል ኦንላይን አስነብቧል።በርዝመት ዝላይ የኦሊምፒክ ቻምፒዮኑ ክርስቲያን ቴይለር በጉዳዩ ላይ አትሌቶች መታገል እንዳለባቸው በማህበራዊ ገጾች በመጠቀም አትሌቶችን እያነሳሳ ይገኛል።አትሌቱ በመግለጫው ላይ ስፖርቱን እያጠፉት መሆኑን የጠቀሰ ሲሆን፤ ለአትሌቶች መብት መታገል እንደሚገባም ገልጧል።ስፖርቱ እንዲያድግም መሰል ድርጊቶች መቆም እንዳለባቸውም ነው ያመላከተው። የውድድሩ አዘጋጆች ውድድሮቹ በቴሌቪዥን ሲተላለፉ ሳቢ እና ማራኪ እንዲሆኑ በማሰብ የቀነሷቸው የውድድር አይነቶች ላይ የዓለም አትሌቲክስ አሸማጋይ የሆነ ሃሳብ ከማንሳት ይልቅ ድጋፉን መስጠቱ ያበሳጫቸው አትሌቶችም ደብዳቤ ለዓለም አቀፉ የበላይ አካል ጽፈዋል።‹‹ውድድሩ በዓለም ህዝብ ዘንድ ሳቢ እንዲሆን ለውጦች መዳረጋቸውንና ማስፈለጋቸውን ብናምንም የዓለም አትሌቲክስ ግን አትሌቶችን ከግንዛቤ ያስገባ አይመስልም።በውሳኔው ላይ አትሌቶች አስተያየት እንዲሰጡ አለመደረጉም  ትክክል አይደለም›› ሲሉም አክለዋል።ማህበሩን በርካታ አትሌቶች እየተቀላቀሉት ሲሆን፤ ከእነዚህም መካከል እንግሊዛዊያኑ የዓለም ቻምፒዮን ዲያና አሸር ስሚዝ እንዲሁም የቀድሞው ርዝመት ዝላይ አትሌት ጆናተን ኤድዋርድስ ይጠቀሳሉ።አንጋፋው አትሌት የዓለም አትሌቲክስ በርካታ ስህተቶችን በመስራት ላይ እንደሚገኝም ጠቁመዋል።ሆኖም ስፖርቱን በበላይነት የሚመራው አካል አስካሁንም የሰጠው ምላሽ ወይም አስተያየት የለም።አዲስ ዘመን ጥቅም4/2012 ብርሃን ፈይሳ
https://www.press.et/Ama/?p=22483
211
2ስፖርት
የብሔራዊ ስፖርት ምክር ቤት ማቋቋሚያ ጉባኤ ተካሄደ
ስፖርት
November 15, 2019
34
 የብሔራዊ ስፖርት ምክር ቤትን በአዲስ መልክ ለማቋቋም የሚረዳ መስራች ጉባኤ ተካሄደ። ምክር ቤቱ በሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 446/2011 ድንጋጌ መሰረትም የሃገሪቷን ስፖርት በበላይነት የሚመራ ሲሆን፤ ከዚህ ቀደም ከነበረው በተሻለ አደረጃጀት ወደ ተግባር ለመግባት እንደሚያስችልም ተጠቁሟል። የኢትዮጵያን ስፖርት ለመምራት ለኢፌዴሪ ባህልና ቱሪዝም ሚኒስትር እንዲሁም ስፖርት ኮሚሽን ከተሰጠው ኃላፊነትና ተግባር ባሻገር በሚኒስትሮች ምክር ቤት የብሔራዊ ስፖርት ምክር ቤት በማቋቋም ስፖርቱ ስለሚዳብርበት፣ ስለሚስፋፋበትና ስለሚመራበት ሁኔታ የተደነገገ መሆኑ ታውቋል።የምክር ቤቱ ሰብሳቢ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ጉባኤውን በማስጀመር የስራ መመሪያ ሰጥተዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚሁ ወቅት እንዳሉት መንግስት የተጠበቀውን ያህል ባይሆንም ለዘርፉ ድጋፉን ሲያደርግ ቆይቷል፤ ለወደፊትም ይበልጥ ተጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል። ዘርፉ በተለያዩ ጫና ዝግመታዊ ለውጥ ውስጥ መግባቱን ተከትሎ ችግሮች ቢስተዋሉም በውስን ስፖርቶች ግን አሁንም ሃገርን በማስጠራት ላይ ይገኛል ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ የስፖርት ዘርፍን ተወዳዳሪነት ለማላቅ፣ የህዝብ ኃላፊነትን ለማጎልበት፣ ዘርፉ እውቀት ባላቸው እንዲመራ የማድረግና ሁሉም ነገር በተወዳዳሪነት፣ በግልጽነትና በተጠያቂነት እንዲሁም በውጤታማነት ብቻ መመራት እንደሚኖርበትም ጠቁመዋል። እንደ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገለፃ በስፖርቱ ዘርፍ ፋይዳቸው ሚዛን በሚደፋ ጉዳዮች ላይ በማተኮር በህጻናትና ታዳጊዎች በማተኮር ሃብትና ጉልበት በሚጠይቀው ሁሉ ዘርፉን ማዘመን የግድ ነው። ምክር ቤቱም ከዚህ አኳያ ኃላፊነቱን ለመወጣት ተጠናክሮ ወደ ተግባራዊነት ሊገባ ይገባል። የምክር ቤቱ ምክትል ሰብሳቢዋ የኢፌዴሪ ባህልና ቱሪዝም ሚኒስትር ዶክተር ሂሩት ካሳው በበኩላቸው እንደገለፁት ምክር ቤቱ ምስረታ ስፖርቱ ደረጃውን በጠበቀና ወቅቱ በሚጠይቀው መልኩ እንዲመራ ያደርጋል። መንግሥት እስከ ታችኛው አደረጃጀት በመውረድና ከዘርፉ ጋር ተቀራርቦ ለመስራት የሚያግዝ በመሆኑ በስፖርቱ የሚስተዋለውን ማነቆ ለመፍታት ያስችላል። ከዚህም ባለፈ ስፖርቱ ከእስካሁኑ በጠነከረ ሁኔታ እንዲጓዝ፣ አስተማማኝና ሰላማዊ ሆኖ እንዲካሄድ እንዲሁም ለኢኮኖሚው ጠንካራ መሰረት እንዲጥል የምክር ቤቱ መመስረት የሚረዳ መሆኑንም አብራርተዋል።ስፖርቱ በ1990 በተቀረጸው ፖሊሲ መሰረት ከመጓዝ ይልቅ በርካታ ስር ነቀል መፍትሄ የሚፈልጉ ችግሮች ያሉበት በመሆኑ እንዲሁም እንደሚጠበቀው በጥሩ ቁመና ላይ አለመገኘቱ አዲስ ፍኖተ ካርታ መቀረጹንም በማቋቋሚያ ጉባኤው ላይ ተገልጿል። በፍኖተ ካርታው ላይ እንደተገለጠው ከሆነም የስፖርት ፖሊሲው በአፈጻጸም በኩል ችግሮች እንዳሉበት ተጠቁሟል። ስፖርት አደረጃጀቱ ብቃትና ጠንካራ አለመሆን፣ የማህበረሰብ ስፖርት ተሳትፎ አናሳ መሆን፣ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች፣ ትጥቅና ቁሳቁስ እጥረት፣ የስፖርት ባለሙያዎች ልማት ጥራትና አቅርቦት ችግር፣ የላቁ ስፖርተኞች ልየታና ልማት ችግሮች፣ ከስፖርት ውድድሮች፣፣ ከትምህርትና ምርምር ጋር ተያይዞ የሚታይ ችግር እንዲሁም እስካሁን ያልተሰራበት የስፖርት ለማህበራዊ ልማትና ለሃገር ብልጽግና አለማዋል ዋናዋናዎቹ ችግሮች መሆናቸው በሰነዱ ላይ ተዘርዝሯል።በመፍትሄ ሃሳብ ደረጃም በስፖርት ፖሊሲው ላይ ክለሳ ማድረግ፣ የአደረጃጀት ማሻሻያ፣ ዓለም አቀፍ ህግጋትን ህዝብ ወደሚረዳው ቋንቋ በመተርጎም ተደራሽ ማድረግ፣ የገንዘብ አቅርቦትና የሃብት ክምችትን ማሳደግ፣ የላቁ ስፖርተኞች ልየታ ልማት፣ የሃገር ውስጥና ዓለም አቀፍ ውድድሮች ተሳታፊነትን ማሳደግ፣ ዘመናዊ የስፖርት ትምህርትና ስልጠና መስጠት እንዲሁም ስፖርትን ለማህበራዊ ልማትና ለሃገር ብልጽግና ለማዋል የሚያስችሉ ዘዴዎችን ተግባራዊ ማድረግ የሚሉት ተጠቅሰዋል። ከዚህ ጎን ለጎንም ብሔራዊ የስፖርት ሙዚየም መገንባት አስፈላጊ መሆኑም ተመልክቷል።የቀረበውን ፍኖተ ካርታ ተከትሎ በምክር በተሳታፊዎች ግብዓት የሚሆኑ ሃሳቦች ተሰንዝረዋል። በምክር ቤቱ ማቋቋሚያ የስፖርት ባለሙያዎችን ባካተተ መልኩ አለመሆኑ ቅሬታ የፈጠረ ሲሆን፤ የተጠሪና የፈጻሚ መስሪያ ቤቶች የሥራ ድርሻ ተለይቶ በፍኖተ ካርታው ላይ መቅረብ እንዳለበት ተጠቁሟል። ይህ ችግርም ከዓለምና ሃገር አቀፍ ስፖርት ማህበራቱ ጋር ለመስራት ችግር እንደሆነበት እና ለአሰራር ምቹ እንዲሆን ራሱን መቻል እንደሚገባ ተገልጿል። መንግሥት ለሌላው ዘርፍ የሚሰጠውን አይነት ትኩረት መስጠት እንደሚገባውና ስፖርቱ ራሱን እስኪችል ማገዝ እንደሚገባም በውይይቱ ተሳታፊዎች ተነስቷል። የባለሃብቶች ተሳትፎ አናሳ መሆንን ተከትሎ በዘርፉ ተሳታፊ እንዲሆኑ ማበረታቻ ቢደረግ፣ ለትልልቅ ስታዲየሞች መተዳደሪያ የሚሆን ደንብ አለመኖር፣ ስፖርታዊ ውድድሮች የችግር ምክንያት በመሆናቸው በፍኖተ ካርታው ላይ አቅጣጫ ሊቀመጥለት እንደሚገባም ተጠይቋል። በፖሊሲው ላይ የህዝባዊ አደረጃጀቱ በአማተሮች እንዲመራ የሚጠቁም ቢሆንም ለስፖርቱ ውጤታማነት አመራሩ ከፊል ፕሮፌሽናል መሆን እንደሚገባውም ተገልጿል። በአካል ጉዳተኞች ዙሪያም ፍኖተ ካርታው የተሻለ ትኩረት እንዲሰጥ፣ ስፖርተኞች ማበረታቻ አለመኖር ከብሄራዊ ቡድን እያራቃቸው በመሆኑ ቢታሰብበት፣ በየክልሉ ያሉ ስታዲየሞች ደረጃ ከመስፈርት በታች በመሆኑ ትኩረት ቢሰጠው እንዲሁም ስፖርቱን ከሰላምና ጠና መድረክነቱ ባለፈ በቱሪዝምና ገቢ ማግኛ መንገድ ማሳደግ ቢቻል የሚሉ ሃሳቦች ተንጸባርቀዋል። በመድረኩ ማጠቃለያ ላይም የተነሱ አስተያየቶችን በማካተት ሪፎርሙ እንደሚሻሻልም ተጠቁሟል።በማቋቋሚያ ጉባኤው ላይ የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን፣ የኢፌዴሪ ባህልና ቱሪዝም ሚኒስትር ዶክተር ሂሩት ካሳው፣ በሚኒስቴሩ የስፖርት ዘርፍ ዲኤታ አቶ ሃብታሙ ሲሳይ፣ የስፖርት ኮሚሽነሩ ኤልያስ ሽኩር፣ ምክትል ኮሚሽነሩ ጌታቸው ባልቻ፣ የክልልና ከተማ አስተዳደር ስፖርት ቢሮ ኃላፊዎች፣ የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ፣ ሃገር አቀፍ ስፖርት ማህበራት ፕሬዚዳንቶችና የጽህፈት ቤት ኃላፊዎች፣ ለስፖርቱ እድገት ጉልህ ሚና ያላቸው የክብር እንግዶችና ባለድርሻዎች ተገኝተዋል። አዲስ ዘመን ጥቅም5/2012 ብርሃን ፈይሳ
https://www.press.et/Ama/?p=22532
613
2ስፖርት